Tuesday, October 8, 2013

የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የግብረሰዶም አራማጆች “የመደራጀት መብታችን ይከበር” የሰጡት አስቂኝ ምላሽ

Oktober 7/2013

በቅርቡ አንድ የመዲናችን የግል ኮሌጅ በሥራ አመራር የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ሲያስመርቅ፤ ግብረ ሰዶማዊነት በአገራችን እያስከተለ ስላለው አደጋ የሚያስቃኝ በጥናት የተደገፈ ጽሑፍ ቀርቦ ነበር፡፡ ፅሁፍ አቅራቢው፤ የግብረሰዶም አራማጆች ለኢትዮጵያ መንግስት “የመደራጀት መብታችን ይከበር” በሚል ያቀረቡትን ጥያቄና የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር የሰጡት ምላሽ በሚል ያቀረቡት ቀልድ ለአንባቢያን የሚያስተላልፈው ቁም ነገር አያጣምና ልጥቀሰው። ጠ/ሚኒስትሩ የመብት ጠያቂዎቹን ተወካዮች አስጠርተው እንዲህ አሏቸው፡:

“እንድትደራጁ ከመፍቀዳችን በፊት ጥያቄያችሁ ከሕግ፣ ከሞራል፣ ከባህል፣ ከሥነ ምግባር…አንፃር ተቀባይነት ይኖረው አይኖረው እንደሆነ ማጣራት አለብን፡፡ ይሄን ለማጣራት ደግሞ የእናንተም ትብብር ያስፈልገናል፡፡ የመጀመርያው ተግባራችሁ የሚሆነው የድጋፍ መጠየቂያ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ነው፡፡ የሰልፉ መነሻ መሐል መርካቶ ይሆናል፡፡ ድምፃችሁን እያሰማችሁ፣ መፈክሮቻችሁን በጽሑፍ ይዛችሁ በመጀመሪያ የምታልፉት በራጉኤል ቤተክርስቲያን በኩል ይሆናል፡፡ በመቀጠል አንዋር መስጊድን ታቋርጣላችሁ፡፡ ከዚያ ወደ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ትዘልቃላችሁ፡፡ በአፍንጮ በር በኩል በ6 ኪሎ ዩኒቨርስቲና የሰማዕታት ሐውልትን ካለፋችሁ በኋላ፣ በ4 ኪሎ ዩኒቨርስቲ በኩል የነፃነት ሐውልትን አቋርጣችሁ፣ በሁለቱ ቤተመንግስቶች መሐል በመጓዝ መስቀል አደባባይ መድረስ ከቻላችሁ፣ የመደራጀት ጥያቄያችሁ ምላሽ ያገኝ ይሆናል”

Monday, October 7, 2013

ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ

Oktober 7/2013

ባለፈዉ ዐርብ መስከረም 25 ቀን 2006 ዓ.ም. የወያኔዉ ሎሌ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አዲስ አበባ ዉስጥ ለአገር ዉስጥና ለዉጭ አገር ጋዜጠኞች በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በየእሁዱ ለሚጠሩት ሰልፍ ጥበቃ ማድረግና በየእሁዱ ተመሳሳይ ጥያቄ ማድመጥ መንግስትን ከሚገባዉ በላይ ያሰለቸዉ ስለሆነ እነዚህ አንድ አይነት ጥያቄ ያነገቡ ሰልፎች የሚቀጥሉ ከሆነ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረግ ይከለከላል በማለት ጌቶቹና ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የመብትና የነጻነት ጥያቄ የሚያነሳ ማንንም ሰዉ ለማሰር፤ ለመደብደብና ለመግደል ያላቸዉን እቅድ በግልጽ ተናግሯል። የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ባቀረቡ ቁጥር መሪዎቻቸዉ የሚታሰሩባቸዉ፤ አባላቶቻቸዉ የሚደበደቡባቸዉና ቢሯቸዉ ተሰብሮ ንብረታቸዉ የሚዘረፍባቸዉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች አንድም ቀን ሰለቸን ሳይሉ ደብዳቢዉ፤ አሳሪዉና የተቃዋሚ ድርጅቶችን ቢሮ እየሰበረ ንብረታቸዉን የሚዘርፈዉ ወያኔ ሰላማዊ ሰልፍ “ሰለቸኝ” ማለቱ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረግ ምንም አይነት ትግል የሱን የስልጣን “ዘለአለማዊነት” የሚጻረር መስሎ ከታየዉ ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ የማይመለስ ፀረ ህዝብ ኃይል መሆኑን እንደገና አረጋግጧል።
 
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ቤት ውስጥ ሆነው ይጠይቁት የነበረውን ጥያቄ አሁን አደባባይ ወጥተዉ መጠየቅ መቻላቸዉ ዲሞክራሲያዊ ስኬት ነው ያለዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በሌላ በኩል ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ በችርቻሮ የሚሰጥ የወያኔ ችሮታ ይመስል ሰልፉ በየእሁዱ የሚቀጥል ከሆነ ሰልችቶናልና እንከለክላለን ማለቱ እንደ ግንቦት 7 እምነት ቀድሞዉንም ቢሆን ወያኔ ሰላማዊ ሠልፍ ማድረግ ይቻላል ብሎ ፈቃድ የሰጠዉ ለዲሞክራሲ ካለዉ እይታና እራሱ የጻፈዉን ህገ መንግስት ተከትሎ ሳይሆን እርዳታ ሰጪ ምዕራባዉያን አገሮችን ለማስደሰት ብቻ ነዉ።

አገር ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከቅርብ ግዜ ወዲህ የተቀናጀ ትግል ማድረግ በመጀመራቸዉ ክፉኛ የተደናገጠዉ ወያኔ “ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” አንደሚባለዉ እነዚህን ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ፤ እኩልነትና፤ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን የሚታገሉትን ፍጹም ህዝባዊና ፍጹም ሰላማዊ የሆኑ ድርጅቶች ለማጥፋት ሰበብ ሲፈልግ የተለመደዉን ግንቦት 7 የሚል ዘፈኑን መዝፈን ጀምሯል። የወያኔ አገዛዝ በአፉ አንደሚናገረዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስብና የሚጨነቅ ከሆነ ማድረግ ያለበት ከኢትዮጵያ ህዝብ ለሚቀርብለት ጥያቄ ተገቢዉን ምላሽ መስጠት ብቻ ነዉ። አለዚያ ህዝብ ጥያቄ ባነሳና ለመብቱና ለነጻነቱ በታገለ ቁጥር የሐይማኖት አክራሪዎች፤ የቀድሞ ስርዐት ናፋቂዎች ወይም የግንቦት ሰባት ተከታዮች ናችሁ እያለ ቢያቅራራ እንዲህ አይነቱ የተለመደ የአምባገነኖች ቀረርቱ ያ የማይቀረዉ ክፉ ቀን ሲመጣ ስንቅ እንደማይሆነዉና ከህዝባዊ ቁጣ እንደማያድነዉ ከወዲሁ ሊገነዘብ ይገባል። ደግሞም ግንቦት 7 አላማዉ፤ ለህዝብ ያለዉ ክብርና ለኢትዮጵያ አንድነት ያለዉ ቀናኢነትና የማያወላዉል አቋም በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ በአጭር ግዜ ዉስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አስገኝቶለታልና የወያኔን የዕለት በዕለት አስተዋዋቂነት በፍጹም አይሻም።

ግንቦት 7 አላማዉና ፍላጎቱ እንደ ስሙ ፍትህ፤ ነጻነትና ዲሞክራሲ ነዉና የህዝባዊ ትግላችን አላማ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን መደምሰስ ብቻ ሳይሆን አገራችን ዉስጥ የህግ የበላይነት ሰፍኖ ኢትዮጵያ ዛሬም ነገም ከሽብርተኝነት የነጻች አገር አንድትሆን ነዉና ወያኔ ያሰኘሰዉን ቢናገር ወይም እንዳሰኘዉ ቢፎክር ንቅናቄያችን ከዚህ ህዝባዊ አላማዉ ንቅንቅ እንደማይል ለወገንም ለጠላትም ማረጋገጥ ይፈልጋል። ግንቦት 7 የኢትዮጵያና የህዝቦቿ ዋነኛ ጠላት ወያኔ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ክንድ ያነጣጠረዉ በዚሁ በዋነኛዉ የህዝብና የአገር ጠላት ላይ ብቻ እንደሆነ ኢትዮጵያዉያንና ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምና ብልጽግና የሚመኙ ሁሉ እንዲገነዘቡለት ይፈልጋል።

ግንቦት 7 ህዝባዊ አላማ አንግቦ፤ ግብ አስቀምጦና ወዳስቀመጠዉ ህዝባዊ ግብ የሚያደርሰዉን የትግል ስልት በጥንቃቄ ነድፎ የሚንቀሳቀስ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ነዉ። ግንቦት 7 ወያኔና ዘረኛ ስርዐቱ ተደምስሰዉ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ሙሉ ፍላጎትና ፈቃድ ብቻ የምትመራ አገር የመሆኗ ሀቅ የማይቀርና ምንም አይነት ምድራዊ ኃይል ገድቦ ሊያቆመዉ የማይችል ህዝባዊ ማዕበል ነዉ ብሎ ያምናል። ግንቦት 7 በዚህ አጋጣሚ በየዋህነት ተሳስተዉና ግዜያዊ ጥቅም አታሏቸዉ ከሚንቋቸዉና እንደ ቤት ዉስጥ ዕቃ ከሚጠቀሙባቸዉ ዘረኞች ጋር እጅና ጓንት የሆኑ እንደ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አይነቶቹ የዋሆች የበደሉትን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀዉ ህዝባዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪ ያቀርብላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ግንቦት 7 ባለፉት ሁለት አመታት በተለይም ከወያኔዉ ቁንጮ ሞት በኋላ ከወያኔ ጋር ከፍተኛ ቅራኔ ዉስጥ የገባችሁ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችና በድርጅቶቹ ዉስጥ የምትገኙ የኢትዮጵያ ህዝብ ወገኖች ወያኔን ለማስወድ ከዛሬ የተሻለ ግዜ አይመጣምና ኑና በጋራ ጠላታችን ላይ እንዝመት የሚል ህዝባዊ ጥሪዉን ያስተላልፋል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

Sunday, October 6, 2013

ወያኔና ጽንፈኝነቱ ! ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔን መቃወም ብቻ ሳየሆን አለመደገፍ በራሱ ከተቃዋሚነት ጎራ ይፈርጃል ።

Okteber6/2013

ወያኔ ከጽንሰቱ ጀምሮ ፣ ውለደቱና እድግቱ የሆነው ጽንፈኝነትና ዘረኝነት ሆኖ ከሚታወቅበት ተነስተን ባሁኑ ወቅት አክራሪነትን ሲቃወም እና ሌሎችን ሲወነጅል መስማቱ <ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ> ያስብላል ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔን መቃወም ብቻ ሳየሆን አለመደገፍ በራሱ ከተቃዋሚነት ጎራ ይፈርጃል ።
ነጋዴው ለሃገሪቱ የሚያስመዘግበው የንግድ ዕድገትና ለዜጎች የሚከፍተው የስራ ዕድል እና ተያያዥ አስተዋጾኦች ባሻገር ወያኔን መደገፉን በተለያየ መልኩ ካላስመሰከረና በተጨማሪም ንግድ ቤቱ ግድግዳ ላይ የማቹን ጠ/ሚ ፎቶ በመስቀል የመለስ አምልኮ ተከታየነቱን ካላረጋገጠ ያገልግሎቱ ጠቀሜታ በ ዜሮ ተባዝቶ ከንግዱ አለም ጨዋታ ውጪ ይደረጋል።

ገበሬው ማዳበሪያ ለማግኘትና ዘርቶ ለማጨድ ወያነ ባዘጋጀለት መንገድ ብቻ መግዋዝ ይኖርበታል። ይህን ማድረግ ካልቻለ ግን ከፍተኛ ትጽእኖ የሚደርስበት ሲሆን ከዚያም አልፎ በቀጥታ የሚያረሰው መሬት ተነጠቆ ለልመና ለስደት ሊዳረግ ይችላል።

የሀይማኖት አባቶች የመለስን አምልኮ ካለስብኩ በተቃዋሚ ፓለቲከኞች ጎራ ይምድባሉ
የመንግስት ሰራተኛ ሆኖ ለመቀጠር ቢጫው የወያነ የአባልነት ካርድ ከትምረት ማሰረጃና ከስራ ልምድ በላይ ዋንኛ የቅጥር መስፈረት ነው ።

ተማሪውም ከከፍተኛ የት/ም ተቐማት ተመርቆ ለመውጣት (የትምር ጠራት ችግሩ እነዳለ ሆኖ) የወያኔ አባልነት ፎርም እንዲሞላ ይገደዳል።
ፍርድ ቤቶች በህግ የበላይንት ሳይሆን ለወያኔዎች በሚመች መልኩ በንጹሀን ዜጎች ላይ በግፍ ይፈርዳሉ።

ዜጎች መኖሪአቸው ተነጥቆ ለወያኔ አባላትና ለደጋፊዎቻቸው ተሰጥቶ ለጎዳና ህይወት ይዳረጋሉ ።

ሰላማዊ ታጋዮች ፣ጋዜጠኞች ግለሰቦች የሀይማኖት መሪዎች ለወያኔ ያልተመቸ ማንኛውም ዓየነት እንቅስቃስ የሚያደርግ አካል በአሸባሪነትና በአክራሪት ተፈርዶበት እስር ቤት ይወርወራሉ።

ወያኔ አገራችንን ከተቆጣጠረበት ጀምሮ እስካሁን ድርስ ስንፈኝነትንና እና አክራሪነትን በተቀነባበረ መልኩ ሬት ሬት እያለን ሲግተን የቆየና ዘረኝነትን በየቦታው ሲሰብክና ህዝቡን ሲያወክ የኖረና በተግባር ያሳየን መሰሪ ቡድን አሁን ደሞ ባዲስ መልኩ በቲዮሪ ላስተምራችሁ ብሎ የዩነቨረሲቲ ተማሪዎችን እያስገደደ ይገኛል። ይህ ባዲስ መልኩ የሚንቀሳቀሱበት አካሄድ ጤናማ ያልሆነና ሰራአቱ የህብረተሰቡን ያመለካከት አቅጣጫ በማስቀየር የፈለጉት ኢሰባዊ የሆነወን ያገዛዝ እድሜያቸውን ለማራዘም ያቀዱት ነገር እነዳለ ያሰታውቃል።
ወያኔን የሚያሰጋው እና እንዲህ እንቀልፍ የሚነሳው የወጣቱ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ እያደረገ ያለውን አምጽ እነድሆነ የታወቃል። ወጣቱ ትውልድ ዘመናዊ ባርነትን እሺ ብሎ የማይቀበል ተፈጥሮ ሰጠችውን ነጻነት በአምባገነኖች ሲነጠቅ ዝም የማይል በመሆኑ ለወያኔ አገዛዝ የማያመች ሆኖበታል ።
ሰሞኑን ሀገር ውስጥ እየታየ ያለው በተለይ ወያኔ በኢትዮጵያ ውስጥ ያጸደቀው የጸረሽብር ህግ ሳይገታው ህዝቡ ለነጻነቱ ለመታገል ዝምታን ሰብሮ አደባባይ በመውጣት ተቃውሞውን በገለጸበት እና ባሳየው ወኔና ቁጣ ወያኔን ማሸበሩ በወቅቱ ከድሬዎችና ፈደራል ፖሊስ ካደርጉት ህገወጥ እንቅስቃሴ ማረጋገጥ ይቻላል። ወያኔን እነቅለፍ መነሳት እና እነዲ ማሸበር ልኛ የነጻነት ቀናችን መቅረቡን ከበስበስ የቆየው ለወያኔ አገዛዝ ደግሞ መውደቂያው መቅረቡ የሚያሳይ ነው ።

Saturday, October 5, 2013

ወያኔ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ በማጓጓዝ ስራ መጠመዱ ተሰማ

Oktober 5/013
ከአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚወስዱ አዉራ መንገዶች ታንኮችን፤ መድፎችንና ሌሎችም ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በተሸከሙ ከባድ ወታደራዊ የጭነት ማመላለሻ ከሚዮኖች እየተጨናነቁ መሆኑን ኢሳት ቴሌቪዥንና ሬድዮ የአይን እማኞችን ጠቅሶ ዘገበ። ወያኔ ከኤርትራ ጋር ባለበት የድንበር አተካሮ ብዙም ዉጥረት በማይታይታይበት በአሁኑ ወቅት የጦር መሳሪያዎቹን በዚህ ደረጃ ለማንቀሳቀስ ለምን እንዳስፈለገ ብዙም የሚታወቅ ነገር ባይኖርም አንዳንዶች ወይኔ ሀይሉን ለማሳየት የሚያደርገዉ ከንቱ የእዩኝ እዩኝ ዘመቻ ነዉ ሲሉ ሌሎች ደግሞ በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢ ከቀን ወደ ቀን እያየለ የሚጣዉን የአማጽያን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ነዉ ይላሉ። ያም ሆነ ይህ ወታደራዊ እንቅስቃሴዉን አስመልክቶ ከአገዛዙ ባለስልጣናት የተሰጠ መግለጫ ካለመኖሩም በላይ ሦስተኛ አካላት ጉዳዩን ለማጣራት ከመንግስት ጋር ያደረጉት ግንኙነትም ፍሬ አልባ ሆኗል።
ሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ፤ ጎንደርና አፋር ዉስጥ የወያኔን ስርዐት በኃይል ለመናድ የሚንቀሳቀሱ አያሌ መሳሪያ ያነገቡ ድርጅቶች የሚገኙ ሲሆን እነዚህ ላለፉት ሃያ አመታት በተናጠል ወያኔን የተዋጉ ኃይሎች ከቅርብ ግዜ ወዲህ የጋራ ግንባር እየፈጠሩ መምጣታቸዉ ወያኔን እንዳሳሰበዉና ክፉኛ እንዳስደነገጠዉም ታዉቋል። እንደብዙ የፖለቲካ ተንታኞች ግምት ይህ ከሰሞኑ የታየዉ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴም የዚሁ ድንጋጤ ዉጤት ነዉ የሚሉ ብዙዎች ናቸዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በየክልሉ የነጻነት ኃይሎችን ለመቀላለቀል የሚደረገዉ እንቅስቃሴ እያደገ መምጣቱ ሌላዉ የወያኔ ስጋት ስለሆነ የሰሞኑ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረገዉ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከመሀል የአገሪቱ ክፍሎች ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎች የሚወስዱ መንገዶችንና ኬላዎችን ለመዝጋት ነዉ የሚሉም አልታጡም። በዚህ ተኬደ በዚያ የሰሞኑ የወያኔ ወታደራዊ ሩጫ አላማዉ ባዕዳንን ለመከላከል ሳይሆን ለአገር አንድነትና ለህዝብ መብትና ነጻነት የሚታገሉ ኃይሎችን ለማፈን ነዉ።

ግንቦት7 የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለወገኑ ነጻነት የሚቆምበትን መንገድ እያዘጋጀ መሀኑን ገለጸ

Oktober 5/2013

ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በወያኔ የዘረኝነት አለንጋ የሚለበለበዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እራሱንና ወገኑን ነጻ የሚያደርግበትን መንገድ መከላከያ ሰራዊቱ ዉስጥ እየቀየሰ መሆኑን የንቅናቄዉ ዋና ጸሀፉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ። ዋና ጸሀፊዉ ይህንን የተናገሩት ኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ዉስጥ የግንቦት ሰባት ኃይሎችን ለመርዳት በተደረገዉ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ባሰሙት ንግግር ነዉ። አቶ አንዳርጋቸው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቱን አስመለሰክተዉ ባደረጉት ንግግር እንደዚህ አይነቱ ወገናዊ ዝግጅት በአንድ በኩል በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል አባላት ዉስጥ ከፍተኛ መነቃቃት የሚፈጥር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ወራዊቱ የተጣለበት ህዝባዊ አደራ ምን ያክል ከፍተኛ መሆኑን የሚያስታውሰን ነው ብለዋል።
በቅርቡ ከኢትዮጵያ አየር ሀይል ከድተው ህዝባዊ ሰራዊቱን ስለተቀላቀሉት ጀግኖች ተጠይቀዉ በሰጡት መልስ የአየር ኃይል አባላቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዉ ንቅናቄያቸዉ በመከላከያ ሰራዊት፤ በደህንነት መስሪያ ቤትና በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ዉስጥ ወያኔ ሊደርስበት በማይችልበት መልኩ የግንኙነት መስመር እየዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።
ኖርዌይ ኦስሎ ዉስጥ የተካሄደዉን አይነት የግንቦት ሰባት ኃይሎች የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሌሎች አገሮችና ከተሞች ዉስጥ ለማድረግ እቅድ አላችሁ ወይ ተብለው የተጠየቁት አቶ አንዳርጋቸው፣ ህዝባዊ ሀይሉ ከተግባር ጋር በተዛመደ መልኩ የገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት መርሀ ግብሩን ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በህዝባዊ ሀይሉ ወይም በግለሰቦች ስም ምንም አይነት የገቢ መሰባሰቢያ ዝግጅት እንደማይደርግ ገልጸዋል። በሌላ ዜና ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላቸው ኖርዌ፤ ሲዉድንና በአካባቢዉ አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር እንደተወያዩ ለማወቅ ተችሏል። በዚህ ዉይይታቸዉ ወቅት አቶ አንዳርጋቸው የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይልን ዓላማዎች፤ ተልዕኮዎችና ራዕይ በማስተዋወቅ ህዝባዊ ሃይሉ ከምስረታው ጀምሮ አሁን ድረስ ያለበትን ደረጃ በምስልና በጽሁፍ በተደገፈ ገለጻ ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።
ከአቶ አንዳርጋቸው እስካሁን ድረስ የተካሄደዉ የህዝባዊ ኃይሉ ስልጠና የንቅናቁዉን የአመራር አካላት ያካተተ መሆኑን ጠቅሰዉ ወታደራዊ ስልጠናዉ የበታችና የበላይ የሚባል ልዩነት እንደሌለበት አስገንዝበዉ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል የተመሰረተዉ ቤተሰባቸውን፤ ስራቸውን፤ገንዘባቸውንና የተደላደለ ኑሯቸውን ትተው ከኢትዮጵያና ከመላው ዓለም በተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን እንደሆነ እንደሆነ ገልጸዋል። የግንቦት ሰባት ዓላማ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ማስፈን ብቻ ሳይሆን ባለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያውያን የተገፈፉትን ክብራቸውን ማስመለስ ጭምር መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው አስምረውበታል።

ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይቀጥል ይችላል አሉ

Saturday, 05 October 2013
f44997cb312b542bbd55c895274ee230_XLተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚያደርጓቸው የተቃውሞ ሰልፎች ተደጋጋሚና መንግስት አቋም የያዘባቸውን ጉዳዮች የሚያነሱ እንደሆኑ የጠቆሙት ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ፤ መንግስት ለእያንዳንዱ ሰልፍ ጥበቃ ማድረግ ስለማይችል ሰልፎቹ በተለመደው መልኩ ላይቀጥሉ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ትናንት በጽ/ቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች የራሳቸው የፓርቲዎቹ ሳይሆኑ የሌሎች ሃይሎች እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡
ፓርቲዎቹ ሰልፍ ማካሄድ ህገመንግስታዊ መብታቸው መሆኑን የጠቀሱት ጠ/ሚኒስትሩ፤ መንግስት በተደጋጋሚ ጥበቃ ሲያደርግ ቢቆይም፣ በሰልፎቹ የሚነሱት ጥያቄዎች ፋይዳ ቢስ ከመሆናቸውና ከፓርቲዎቹ ብዛት አንፃር መንግስት በቀጣይ ለሰልፎች ጥበቃ ለማድረግ የሚቸገርበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል አስረድተዋል፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ መንግስት በተደጋጋሚ ምላሽ የሰጠባቸውን ጥያቄዎች መላልሰው የሚያቀርቡት በመንግስት ላይ ጫና በመፍጠር አቋሙን ለማስቀየር በማሰብ ሊሆን ይችላል ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ ይሄ ግን በፍፁም የማይሳካ ሃሳብ ነው ብለዋል፡፡ “ግንቦት ሰባት” በቅርቡ መንግስትን ለመጣል ወታደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ በይፋ መግለፁን በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱም፣ የፓርቲው አመራሮችና ደጋፊዎች ተጨባጭ ያልሆነ ህልም ውስጥ ሆነው የተናገሩት ነገር እንደሆነና ከህልማቸው ሲነቁ እውነታውን እንደሚገነዘቡት ጠ/ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ መከፋፈልና የሃይል መጠባበቅ አለ የሚለውን መረጃ በተመለከተም “ይህ የአንዳንድ አፍራሽ ሃይሎች ከንቱ ምኞትና ተጨባጭ ያልሆነ አሉባልታ ነው” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡

Friday, October 4, 2013

ገዢው ፓርቲ በጠራቸው ስብሰባዎች ላይ ሁሉ ተቃውሞ ገጠመው

Oktober 4 / 2013

መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ባለፈው ሳምንት በመላ አገሪቱ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችን እየሰበሰበ በ2005 የስራ አፈጻጸምና የ2006 ዓም በጀት እቅድ ትግበራ ላይ ሲያወያይ ቢሰነበትም፣ ለኢሳት ሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በሁሉም ቦታዎች ላይ በተደረጉት ስብሰባዎች ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞታል።

በአዳማ የተካሄደውን ስብሰባና ተሰብሳቢዎች ያቀረቡዋቸውን ቅሬታዎች ኢሳት ቀደም ብሎ የዘገበ ሲሆን፣ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን በአርማጭሆ ወረዳ የነበረው ስብሰባም እንዲሁ በተመሳሳይ ተቃውሞ መጠናቀቁን በውይይቱ የተሳተፉ የመንግስት ሰራተኞች ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ በርካታ አጀንዳዎች የነበሩ ሲሆን፣ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ የተነሱት ጉዳዮች ተሰብሰባዊውን በከፍተኛ ሁኔታ አወዛግበዋል።

በ2006 ዓም የጸረ ሰላም ወይም የጥፋት ሀይሎችን ማምከን የሚል በእቅድ እንዲካተት በቀረበው አጀንዳ ላይ ጸረ ሰላም ማን ነው የሚለው ጥያቄ በተሰብሳቢው ተነስቶ የመድረኩ መሪዎች የተለያዩ መልሶችን ሰጥተዋል። የዞኑ የጸጥታ ጉዳዮች ሀላፊ የሆኑት አቶ ወርቁ ሀ/ማርያም ” ነሀሴ ወር ገደማ 30 የሚሆኑ ሰዎች በጎንደር ከተማ ህዝቡን ተነስ በማለት ሲቀሰቅሱ የነበሩ ሰዎች ጸረ ሰላም ሀይሎች ናቸው።” በማለት አንድነት ፓርቲ በጎንደር ያካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ በምሳሌነት አንስተዋል።

ሌላው የሲቪል ሰርቪስ ባለስልጣን የሆኑት አቶ ገዛሀን ተክሌ በበኩላቸው ” የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን ተሰጠ ብሎ መናገር ጸረ ሰላምነት ነው” ሲሉ አብረራርተዋል። ባለስልጣኑ አክለውም ህገመንግስቱን ለመጣስ የሚነሳ ሁሉ ጸረሰላም ተብሎ ይፈረጃል ብለዋል።

የጸጥታ ጉዳዮች ዘርፍ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ደግሞ ” ከመድረክ አፈንግጦ መውጣትና ሳያስፈቅዱ መናገር፣ ሳያስፈቅዱ ጽሁፍ መጻፍና ማሰራጨት፣ ሳያስፈቅዱ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ፣ በጥፋት መልእክተኝነት ያስፈርጃል ሲል ገልጸዋል።
አቶ ፈንታ የተባሉ ባለስልጣንም እንዲሁ ” የጎንደርን መሬት ኢህአዴግ አሳልፎ እየሰጠ ነው ” ብሎ መናገር ጸረ-ሰላም ተግባር ነው በማለት የራሳቸውን ትርጉም አቅርበዋል።

ስለ ጸረ ሰላም ሀይሎች፣ አክራሪነትና ሽብረተኝነት ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ትምህርት እንዲሰጠጥ በቀረበው ሀሳብ ላይ ደግሞ በስብሰባው የተሳተፉ ተቃውሞአቸውን ገልዋል። ተሳታፊዎቹ ከ15 ዓመት በታች ያሉ ህጻናትን ስለ ሽብረተኝነት፣ አክራሪነትና ጸረሰላም ሀይሎች ማስተማር በህጻናቱ ላይ የስነልቦና ጫና ይፈጥራል በማለት ተከራክረዋል።

ሌላው አወዛጋቢ የነበረው ነጥብ ” ኢህአዴግ የ2006 እቅድን ተቋሞችን በድርጅት አባላት በመሙላት እናሳካለን በማለት ያቀረበው ” ሲሆን፣ ተሰብሳቢዎቹ የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ሁሉ በድርጅት አባላት ከሞላችሁ የተቃዋሚ ድርጅት አባላትን ምን ልታደርጉዋቸው ነው?” በማለት ጥያቄ አንስተዋል።

ለሱዳን ተላልፎ የተሰጠውን መሬት በተመለከተ የአካባቢው ሰራተኞች የሁለቱን

Ethiopia: Anti-Terrorism Law Among Targets of Addis Ababa Protest

October 4, 2013   

PRESS RELEASE

A major street protest took place in Addis Ababa on 29 September in response to a call from Unity for Democracy and Justice, an opposition political party headed by the previous president, Dr. Negasso Gidada.

The demonstrators protested against the arbitrary detention of journalists, human rights activists and dissidents, which is made possible by the 2009 anti-terrorist law.

Independent estimates put the number of demonstrators at between 12,000 and 15,000 while government sources said they were a few hundred.

The urgent need to amend this repressive law was of one of the recommendations that Reporters Without Borders included in its submission on Ethiopia to the United Nations Human Rights Council for the 19th Universal Periodic Review session to be held between April and May next year.

“The anti-terrorism law is one of the most serious obstacles to the promotion and protection of freedom of information in Ethiopia,” Reporters Without Borders said. “Ever since its adoption, the government has used it as a legal tool to clamp down on dissidents and create a cloud of fear that limits the ambition and activity of the media.

“Without taking any position on the politics of the demonstrators, we urge the government to respond to the widespread demand by concerned citizens and activists for immediate and participatory reform of the anti-terrorism law. We also call on the government to respect the freedom of expression of all news and information providers, regardless of their political views.”
According to the organizers, the demonstration’s aim was not only to
condemn the law but also to demand the release of opposition members and journalists who have been jailed under it. They include activist Eskinder Nega, detained since 15 September 2011 for alleged “links with terrorist organizations and conspiracy to harm national security”.

Journalists Reyot Alemu, winner of the 2013 UNESCO/Guillermo Cano press freedom prize, and Woubeshet Taye, the deputy editor of the Amharic-language weekly Awramba Times, have been detained under this law since June 2011.

Reyot Alemu has been reportedly subjected to mistreatment including solitary confinement, minimal access to medical care and restricted visits from family and friends. They are serving jail terms of five and 14 years respectively, on charges of “conspiring with a terrorist organization and taking part in planning terror attacks”.

Two Swedish journalists working for the Kontinent news agency, reporter Martin Schibbye and photographer Johan Persson, were arrested on 1 July 2011 after illegally entering Ethiopia’s southeastern Ogaden region from Somalia with members of the separatist Ogaden National Liberation Front (ONLF) with the aim of investigating human rights violations in the region. Sentenced to 11 years in prison on a charge of “terrorist activities”, they were released after 450 days in detention thanks to pressure from the international community.

In an interview for Reporters Without Borders, Schibbye said: “The mere fact that these protests are taking place is a positive sign in Ethiopia. This shows the growing implication of the youth, namely through social networks, and their refusal to live in a society where journalists and dissidents can be jailed arbitrarily.”

Ethiopia is ranked 137th out of 179 countries in the 2013 Reporters Without Borders press freedom index.

ለሕዝባዊ ተቃውሞ የወያኔ ፈቃድ የማይጠየቅበት ቀን እንዲመጣ እንታገላለን!!!


         
መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም. አንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ከሌሎች በርካታ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር የጠራው ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ይህ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ከዝግጅቱ እስከ ፍፃሚው ብቻ ሳይሆን ከፍፃሚው በኋላም በድርጊቶች የታጀበ ነበር።


ወያኔ ለሰልፉ እውቅና ሰጥቶ እያለ “መቀስቀስ አይቻልም፤ ፓስተር መለጠፍ አይቻልም፤ በዚህ ማለፍ፣ በዚያ መዞር አይቻልም” እያለ የፓርቲው መሪዎችን፣ አባላትንና ደጋፊዎችን ሲያስር፣ ሲፈታ፣ ሲያዋክብ ሰንብቷል። ይህም ሆኖ ግን የፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎች ወከባውን ተቋቁመው ሰላማዊ ሰልፉን መጀመር ቻሉ።

ወያኔ ሰልፈኛው ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይደርስ የለመደውን ጉልበት ተጠቀመ። ከተለያዩ አቅጣጫዎች ይተሙ የነበሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች እንዳይገናኙ በፓሊሶች ታገቱ። ኢትዮጵያ ውስጥ አፈና የደረሰበት ደረጃ ጎልቶ ታየ። ሰልፈኛው ሊደርስ ያሰበው ቦታ – መስቀል አደባባይ – መድረስ ሳይችል ቀረ። የሰልፉ አስተባባሪዎች የነበሩበት ብዛቱ በመቶ ሺህ የተገመተ ስብስብ ሊደርስ በቻለበት ቦታ የመዝጊያ ሥነሥርዓት ፈጽሞ ተበተነ።

የወያኔ ጆሮ ጠቢዎች ከሰልፊ በፊት፣ በሰልፉ ጊዜ እና ከሰልፉ በኋላ ግንባር ቀደም የሰልፉ ተዋንያንን የማደን፣ የማዋከብ፣ የማሠር፣ የመደብደብ “ሥራ” በዝቶባቸው ሰንብቷል። ባሠሩና ባዋከቡ መጠን ግን የሕዝብ ምሬት እየበረታ መጥቷል።

ወያኔ ሰልፉን ለመቆጣጠር እጅግ ብዙ የሆነ የፓሊስ፣ የጦርና የሰላይ ሠራዊት ለማሠማራት ተገዷል። ይህ ራሱ አንድ ድል ነው።
ከዚህ ሰልፍ የተገኘው ጥቅም ግን ይህ ብቻ አይለም። ወያኔ በሕዝብ ልብ ውስጥ ዘራሁት ያለው ፍርሀት በኖ የሚጠፋ መሆኑ፤ እድል በተፈጠረ ጊዜ ሁሉ ወጣቶች በፈጠራ ሥራዎቻቸው ተመልካችን ማስደመም የሚችሉ መሆኑን፤ የተለያዩ ሀይማኖቶች ተከታዮችን ለማጋጨት ወያኔ የሸረበው ድር የተበጣጠሰበት መሆኑ ሰልፉ አሳይቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ በወታደር እና በሰላዮች ብርታት ላይ የቆመ ሥርዓት መሆኑን አሳይቷል። ወያኔ በጠመንጃና በስለላ ላይ ያለው ሞኖፓሊ ካልተሰበረ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችንም እሱ ከሚፈልጋቸው ክበብ እንዳይመጡ ማፈን የሚችል መሆኑ አሳይቷል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን የወያኔ ወታደራዊና የስለላ ሞኖፖሊ መስበር የሥራው አንድ አካል አድርጎ ይመለከታል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሕጋዊና ሰላማዊ መንገድ አምባገነኑን ወያኔ በመገዳደር ላይ ያሉትን ወገኖች ትግል ያደንቃል። እንዳንዳንዳችን የየበኩላችን ጥረት ካደረግን የኢትዮጵያን የመከራ ጊዜ በእጅጉ እንደምናሳጥር ያምናል።
ግንቦት 7 ሕዝብ ተቃውሞ ለማቅረብ የወያኔን ባለሥልጣኖች ፈቃድ መጠየቅ የሚያበቃበት ጊዜ እንዲመጣ ተግቶ ይሠራል። ለዚህ ዓላማም ተባብረን እንድንቆምም ጥሪ ያደርጋል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Ethiopia most restrictive Sub Saharan Country, Freedom House reports

October 4/2013
Introduction: 

Ethiopia is the second most populous country in Africa, but poor infrastructure and a government monopoly over the telecommunications sector have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs). Consequently, Ethiopia has one of the lowest rates of internet and mobile telephone penetration on the continent. Despite low access, the government maintains a strict system of controls and is the only country in Sub-Saharan Africa to implement nationwide internet filtering.
 
In 2011, in the wake of the Arab Spring protests in the Middle East and several online calls for similar demonstrations in Ethiopia,[1] the government reacted by strengthening internet censorship and carrying out a systematic crackdown on independent journalists, including at least one blogger.
 
Beginning in June 2011, over ten journalists were sentenced to long prison terms,[2] mostly on questionable charges of terrorism. Among them was the editor of an exiled online news website who was sentenced in abstentia to life imprisonment. A prominent dissident blogger based in Ethiopia was also arrested in September 2011 and sentenced to 18 years in prison in July 2012.[3] The latest crackdown is part of a broader trend of growing repression against independent media since the 2005 parliamentary elections, in which opposition parties mustered a relatively strong showing.[4]
Internet and mobile phone services were introduced in Ethiopia in 1997 and 1999, respectively.[5] In recent years, the government has attempted to increase access through the establishment of fiber-optic cables, satellite links, and mobile broadband services. It has refused to end exclusive control over the market by the state-owned Ethiopian Telecommunication Corporation (ETC). However, in December 2010 France Telecom took over management of ETC for a two-year period, renaming it Ethio Telecom in the process.[6] China has also emerged as a key investor and contractor in Ethiopia’s telecommunications sector.[7] Given allegations that the Chinese authorities have provided the Ethiopian government with technologies that can be used for political repression, such as surveillance cameras and satellite jamming equipment,[8] some observers fear that the Chinese may assist the authorities in developing more robust internet and mobile phone censorship and surveillance capacities in the coming years.
 
Obstacles to Access: 

Ethiopia’s telecommunications infrastructure is among the least developed in Africa and is almost entirely absent from rural areas, where about 85 percent of the population resides. In 2011, only 829,000 fixed telephone lines were in actual operation (a decrease from 908,000 lines in 2010[9]), serving a population of 83 million for a penetration rate of less than 1 percent, according to the International Telecommunication Union (ITU).[10] Similarly, as of the end of 2011, internet penetration stood at 1.1 percent, up from 0.75 percent in 2010.[11] Mobile phone penetration in 2011 was higher at roughly 17 percent with a little over 14 million subscriptions, up from an 8 percent penetration rate in 2010.[12] While all of the above reflect very slight improvements in access compared to 2010 (except for fixed-telephone lines), such penetration rates represent extremely limited access to ICTs by global comparison.
 
The combined cost of purchasing a computer, initiating an internet connection, and paying usage charges places internet access beyond the reach of most Ethiopians. A 2010 study by the ITU found that Ethiopia’s broadband internet connections were among the most expensive in the world when compared with monthly income, second only to the Central African Republic,[13] and merely 27,000 broadband subscriptions were recorded in 2011.[14] Prices are set by Ethio Telecom and kept artificially high. In April 2011, Ethio Telecom announced a new set of pricing packages,[15] reducing the subscription charge from US$80 to US$13 and the monthly fee from over US$200 per for unlimited usage to fees of between US$17 and US$41 for between 1 GB and 4 GB of use. By comparison, the annual gross national income (GNI) per capita at purchasing power parity was US$1,110 (or US$92.50 per month) in 2011.[16] Although the new tariffs have rendered the service slightly more affordable—though still relatively expensive—for individual users, cybercafe owners have complained that the lack of an unlimited usage option could hurt the financial viability of their business.[17] Furthermore, an adult literacy rate of 30 percent means that the majority of Ethiopians would be unable to take full advantage of online resources even if they had access to the technology.
 
[18]] Radio remains the principal mass medium through which most Ethiopians obtain information.
The majority of internet users rely on cybercafes to access the web, though connections there are often slow and unreliable. Internet access via mobile phones has grown over the past year,
 
particularly in semi-urban areas, but slow speeds are a constant problem. A 2010 study commissioned by Manchester University’s School of Education found that accessing an online email account and opening one message took six minutes in a typical Addis Ababa cybercafe with a broadband connection.[19] The number of cybercafes has grown in recent years and continues to expand in large cities, after a brief period in 2001–02 during which the government declared them illegal and forced some to shut down. Since July 2002, the Ethiopian Telecommunications Agency (ETA) has been authorized to issue licenses for new cybercafes.
 
The authorities have placed some restrictions on advanced internet applications. In particular, the use or provision of Voice over Internet Protocol (VoIP) services or internet-based fax services—including at cybercafes—is prohibited,[20] with potential punishments including fines and up to five years in prison.[21] The government instituted the ban on VoIP in 2002 after it gained popularity as a less expensive means of communicating and began to drain revenue from the traditional telephone business belonging to the state-owned Ethiopian Telecommunication Corporation (ETC), or Ethio Telecom.[22] Despite the restriction on paper, many cybercafes offer the service with few repercussions.
 
Social-networking sites such as Facebook, the video-sharing site YouTube, and the Twitter microblogging service are available, though very slow internet speeds make it impossible to access video content. International blog-hosting websites such as Blogger have been frequently blocked since the disputed parliamentary elections of 2005, during which the opposition used online communication to organize and disseminate information that was critical of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF).[23] In addition, for two years following the 2005 elections, the ETC blocked text-messaging via mobile phones after the ruling party accused the opposition of using the technology to organize antigovernment protests. Text-messaging services did not resume until September 2007.[24]
Around May 26, 2011, on the eve of a planned opposition demonstration inspired by anti-government protests in the Middle East and celebrations for the anniversary of the ruling party coming to power, the internet was cut off for at least half a day.[25] It remained unclear whether the cause of the shutdown was a deliberate government attempt to restrict communication at a sensitive time, a technical problem, or sabotage of a fiber-optic cable. Separately, when high-profile international events, such as a meeting of the African Union, have taken place in Addis Ababa and other major cities, the government has redirected much of the country’s bandwidth to the venues hosting visitors, leaving ordinary users with even slower connections than usual.
 
Ethiopia is connected to the international internet via satellite, a fiber-optic cable that passes through Sudan and connects to its international gateway, and another cable that connects through Djibouti to an international undersea cable.[26] In an effort to expand connectivity, the government has reportedly installed several thousand kilometers of fiber-optic cable throughout the country in recent years.[27] There are also plans in place to connect Ethiopia to a global undersea cable network through the East African Submarine Cable System (EASSy) project. The EASSy project itself was completed and launched in July 2010, but its effects on Ethiopia have yet to be seen.[28] The government has sought to increase access via satellite links for government offices and schools in rural areas. WoredaNet, for instance, connects over 500 woredas, or local districts, to regional and central government offices, providing services such as video conferencing and internet access. Similarly, SchoolNet connects over 500 high schools across the country to a gateway that provides video- and audio-streamed educational programming.[29] The impact of such projects has been limited, however, as internet speeds across these networks remain almost prohibitively slow and outages are common.
 
 

Thursday, October 3, 2013

በአንድነት እና በተደራጀ ሃይል ጠላትን ዳግም እንዳይነሳ አድርጓ መቅበር ይቻላል ::(ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)

Oktober 4/2013
ከገዛኸኝ አበበ

በአሁኑ ሰአት አገራችን ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደመትገኝ  በበዙዎች ዘንድ እየተነገረ ይገኛል:: በሀገሪቷ ውስጥ የሚኖሩ የሀገሪቷ  ዜጎች እንደ ዜጋ መብታቸው ሳይከበር  አገሪቱን እየመራው ነው በሚለው ሀይል ጨቋኝ አገዛዝ የተነሳ  መብታቸው  ታፍኖ እና ተረግጦ በተወለዱበት እና በተፈጠሩበት ሀገር በነፃነት መኖር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ እና ወያኔ ኢሕአዲግ በየባታው በየሰፈሩ በየመስሪያ ቤቱ አሉኝ የሚለውን የራሱን ካድሬዎችን በማሰልጠን እና በማሰማራት በህዝባችን ላይ አደገኛ የስለላ መረቡን በመዘርጋት ህዝባችንን በማሸበር እና በማወክ ላይ እንደሚገኝ ካለኝ መረጃ ለማወቅ ችያለው ::

ይህም ሊሆን የቻለበት ዋንኛው ምክንያት በሀገር ቤትም እና ከሀገር ውጪ ያሉት የመንግስት ተቀዋሚዎች እያሳዩት ያለው ወኔ እና ቆራጥነት የተሞላበት ትግል ለወያኔ ኢሕአዲግ አመራሮች የራስ ምታት ሳይሆን እንዳልቀረ ይገመታል::

በአሁኑ ሰአት በሀገር  ውስጥ የሚገኙት የተቀዋሚ ድርጅቷች እንደ ሰማያዊ ፓርቲ እና እንደ  እንድነት ፓርቲ ያሉ ሀገር በቀል ድርጅቷች ትግሉን በሙሉ ሀይል በመግፋት ላይ ሲሆኑ እነዚህ ድርጅቶች እያደረጉ ያለውን የሀገር ወኔ የተሞላበት ሰላማዊ ትግል ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ  ሊያበረታታው እና ሊደግፈው ከጓናቸውም ሊቆም ይገባል ባይ ነኝ :: እነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች የወያኔን መንግስት ምን ያህል እያሰደነበሩት እና እያስደነገጡት እንዳለ ወያኔ እያደረገ ካለው ነገር መረዳት እንችላለን::

እነዚህ የፖለቲካ  ድርጅቶቸ ባለፈው ሳምንታት አዘጋጅተውት በነበረው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሰልፉን ለማሰናከል  የወያኔ መንግስት ዘውትር እንደሚያደርገው ሁሉ አባሎችን ሲያስር ሲገርፍ እና ሲያሰቃይ እንደነበር በአደባባይ የታየ ሀቅ ነበር::ይህም ሀገርን በነጻነት እየመራው ነው ከሚል ከአንድ መንግስት የማይጠበቅ  እና እንዲሁም የወያኔ መንግስት ምን ያህል የዱርዬ እና የወሮበላ መንግስት መሆኑን ለሀገራችን እና ለአለም ህዝብ  በተግባር ያሳየበት ነበር :: የወያኔ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ህዝቡን ይሰር ይግረፍ ያሳቃይ እንጂ ነገሩ ግን ሌላ ነው :: አፈናው ወከባው እስራቶ እና ስቃዩ ያልበገረው ህዝብ ግን ለወያኔ ዛቻ እና አሰልቺ ፕሮፖጋንዳ የሚገዛ እና የሚንበረከክ አይመስልም:: በፓርቲዎቹ የጠነከረ እና የበሰለ አመራር እና በአባላቱ ወኔን የተሞላበት ተነሳሽነት የወያኔ መንግስት የተደናገጠ ይመስላል::

  ሰሞኑን ሀገር ቤት ከሚኖር አንድ በጣም ከምቀርበው እና የወያኔን ሚስጥር ያውቃል ከምለው ሰው ጋር ተገናኝቺ ነበር :: በአገር ቤት እየተደረገ ባለው ትግል የህዝቦች ልብ ምን ያክል እንደራቀው የተረዳው የወያኔ መንግስት በየቦታው የሚገኙትን ካድሬዎቹን በየስፍራው ሰብስቦ ውይይት ከካድሪዎቹ ጋር እንዳደረገ እና  በውይይቱም ወቅት አባላቶቹ የተፈለገውን ያክል እየተንቀሳቀሱ እንዳይደለ እና ምንም ነገር እየሰሩ እንዳልሆነ  ከዚህ በሆላ ግን በትጋት መስራት እንዳለባቸው ቁጣን የተሞላበት ትህዛዝ ለካድሬዎቹ እንዳስተላለፈ እና ለስለላ ካድሬዎችን በስፋት እንዳሰማራ እና ወያኔ ያሰለጠናቸው የወያኔ ካድሬዎች ከስለላው ጉን ለጉን  በየመስሪያ ቤቱ፣ በየዪንቨርስቲዎች ፣ በየኮሌጆች እና በእየትምህርት ቤቱች፣ በየቀበሌው እና በየሰፈሩ  ወያኔን የብርሃን መላአክ አስመስለው በህዝባችን ዘንድ ለመቅረብ በስፋት እየሰሩበት እንዳለ ለማወቅ ችያለው:: ወያኔ ይሳካልኛል ብሎ ይህን ያድርግ እንጂ ሀቁ ግን ሌላ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ወያኔ ማን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል:: የወያኔን ጭራቅነት እና አረመኔነተ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መንገረም አያስፈልግም:: ይህ ሕዝብ በሃያ ሁለት ዓመታት የወያኔ አገዛዝ ዘመን ውስጥ የመኖር ህልውናው ጥያቄ ውስጥ የወደቀበት ሁኔታ ውስጥ እየተገኛ ወያኔ ኢሕአዲግ በሕዝብ ዘንድ እራሱን የብርሃን መላአክት አስመስሎ ለማድረግ የሚያደርገው ሮጫ የሚያዋጣው አካሄድ አይመስለኝም ::

በሀገር ውስጥ እየተደረገ ያለው ተቃውሞ እና ትግል ብቻ አይደለም ለወያኔ መንግስት የራስ ምታት እየሆነበት ያለው በውጭ ሀገር የሚገኙትም የፖለቲካ ድርጅቶች እና ሀይሎችም በውጪ ሀገር የሚኖረውም የኢተዮጵያ ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በተለየ መንገድ በሀገራዊ ስሜት እየተሰባሰቡ፣ እየተደራጁ እና ሀይላቸውን እያጠናከሩ  የወያኔንን መንግስት አከርካሪውን ለመስበር በዝግጅት ላይ መሆናቸው እና ወያኔ የግሌ የእራሴ ናቸው ብሎ የሚመካባቸው ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ሳይቀሩ ይሄን ትግል በመቀላቀል የወገን አጋርነት እያሳዪ መሆናቸው እና በተለይም ሰሞኑን የግንቦት ሰባት ዋና ጸሀፊ አቶ እንዳርጋቸው ጽጌ ግንቦት ሰባት በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ መስመሩን እየዘረጋ እንደሆነ  መናገራቸው በወያኔ መንግስት ላይ የጭለማ ዘመን እየመጣ እንዳለ አመሳካሪ ሲሆን ወያኔን በሀይል ለመፋለም የተነሱት ድርጅቶች ደግሞ በርቷ የሚያሰኝ ታላቅ ስራ እየሰሩ እንዳለ እና በውጭ ሀገር የሚኖረው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊም በታላቅ ሀገራዊ ስሜት በማንኛውም መንገድ ከጓናቸው እንደሚገኝ እያስመሰከረ ይገኛል:: ለዚህም ምስክር የሚሆነው በ 28/9/2013 በኖርዌይ ኦስሎ የሚኖሩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያን ዜጎች  ወያኔን በሃይል ለመፋለም ቋርጧ የተነሳውን የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሀይልን ለመደገፍ በራሳቸው ተነሳሽነት ባዘጋጁት የገንዘብ ማሠባሠቢያ ፕሮግራም ላይ ምን ያክል ወያኔንን ለማዳከም ቆርጠው መነሳታቸውን እና ከሕዝባዊ ሀይል ጓን መሰለፋቸውን ያስመሰከሩበት እና በፕሮግራሙም ላይ ሕዝባዊ ሀይሉን ለማጠናከር ከፍተኛ ገንዘብ ከሕዝብ እንደተሰበሰበ እና በሁሉም በኩል የተሳካ ዝግጅት እንደነበር ለማየት ችለናል :: ፕሮግራሙን ለመታደም ከተለያዩ አውሮፓ ሀገሮች ሰዎች እንደተገኙ እና በነበረው ዝግጅት በጣም መደሰታቸውን ለማወቅ ችለናል ::

በተቃራኔው ወያኔ ያሰማራቸው የወያኔ ካድሬዎች ከመጀመሪያው አንስቶ ፕሮግራሞ እንዳይሳካ ከፍተኛ መሯሯጥ ሲያደርጉ እንደነበር እና ዝግጅቱ እንዲቋረጥ ክፉኛ እንደሮጡ ነገር ግን የገቢ ማሰባሰቢያውን ባዘጋጁት ኮሚቴዎች የበሰለለ አመራር ሳይሳካላቸው እንደቀረ እና በፕሮግራሙ መጨረሻ የፕሮግራሙን በጥሩ ሁኔታ መሳካት ሲያውቁ እርስ በእርስ መደባደባቸውን ከፕሮግሙ በኋላ በደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል ::

ከፕሮግራሙ መጠናቀቅ በኍላም ባሉት ቀናት ውስጥም የወያኔ መንግስት ክፉኛ እንደተደናገጠ የሚያሳዩ ነገሮች እየታየ ሲሆን በኦስሎ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ውስጥ የወያኔ ዲፕሎማት እና የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የዲፕሎማቲክ የሚስጥር ውይይት ያደረጉ ሲሆን የወያኔው እኝው የወያኔ ዲፕሎማት ኢሕአዲግን የብርሃን መላእክት አስመስሎ በማቅረብ በኖርዌይ የሚኖሩት ተቀዋሚ ኢትዮጵያኖች የተለያየ ቃላትን ሲከሱ እንደነበር ማወቅ ችለናል ::

የወያኔ መንግስት የግንቦት ሰባት አካሄድ ክፉኛ ያስደነገጠው ይመስላል በዚህም በተለያዩ አውሮፓ አገሮች በመዞር በግንቦት ሰባት ላይ ያለውን ፍርሃት የወለደውን ፕሮፖጋንዳውን ለመዝራት እየሞከረ ሲሆን ይህ አካሄዱ ደግሞ በየትኛውም አገራት ተቀባይነትን እያገኘ አይደለም:: በአሁኑ በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ እየጠነከረ ባለው ትግል በታላቅ ፍርሃት ውስጥ እና መደናገጥ ውስጥ የገባውን ይሄን ዘረኛ እና አረመኔ መንግስት ለአንዴና ለመጨረሻ ጌዜ ዳግም እንዳይነሳ ለመቅበር በሀገር ውስጥም በውጭም ያሉት  በተለያየ አቅጣጫ እየታገሉ ሀይሎች አንድነት ሀይል ነው እና በአንድነት እና በተደራጀ ሃይል መነሳት ይጠበቅባቸዋል ::

   አንድነት ሃይል ነው!!!

   ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!





የእስክንድር መልዕክት!

Oktober 03.2013 

የእስክንድር መልዕክት!


ትናንትና ሰብሰብ ብለን ወደ ቃሊቲ አምርተን ነበር፡፡ አንዱአለምንና ርዕዮትን መጠየቅ ባይፈቀድልንም እስክንድር መጠየቅ ችለናል፡፡ 

በእርግጥ እስክንድርን እንደ እስረኛ አይደለም የጠየቅነው፡፡ እስክንድር ምኑም እስረኛ አይመስልም፡፡ እርሱ ራሱ በእንግድነት የተቀበለን ነው የሚመስለው፡፡ እሱን ለመጠየቅ ሄደን ተጽናንተን የመጣነው እኛው ነን፡፡ ስለ አገራችን መጻኢ እድል፣ የትግሉ ምስቅልቅል፣ የህዝብ መከራ፣ የፖለቲካ ሀይሎች ድክመት …..ስለ በርካታ ነገሮች ስንማር ውለን ነው የተመለስነው፡፡
በስተመጨረሻ ስንሰነባበት ደግሞ የሚያወቁኝን ሁሉ ሰላም በሉልኝ ብሎናል፡፡ መቼም ፌስ ቡከኛ ሆኑ እስክንድርን የማያውቅ የለምና የእስክንድርን የከበረ ሰላምታ ተቀበሉት፡፡


ሌላም መልዕክት አስተላልፏል፡፡ ‹‹ፌስ ቡክ ላይ ያላችሁን እንቅስቃሴ ማጠናከር ይገባችኋል፡፡ ፌስ ቡክ እንዲሁ ማህበራዊ ድህረ ገጽ ሲባል ለለውጥ ምንም ፋይዳ የሌለው ሊመስል ይችላል፡፡ ሆኖም የአሁኑ ዘመን ትግል አንድ አጋር ሆኗልና በሚገባ ተጠቀሙበት፡፡›› የእስክንድር መልዕክት ነው፡፡


ግብጽን በምሳሌነት የሚያወሳው እስክንድር ‹‹የሙስሊም ወንድማማኞች ፌስ ቡክ መጠቀም ባይችልም ፌስ ቡከኞችን የግብጽ ወጣቶች ተጠቅሞ ሙባረክን አሸንፏል፡፡ ሙስሊም ወንድማማኞች ራሱ አምባገነን ለመሆን ሲቃጣውም ፌስ ቡክን ጠንቅቀው በሚያውቁት ግብጻዊያን ወጣቶች አይኑ እያየ በዚህ በተናቀው ድህረ ገጽ አውርደውታል፡፡›› ሲል የፌስ ቡክን ጠቀሜታ በአጽንኦት አስታውሶናል፡፡


የእስክንድርን ጥልቅ ትንተና መስማት የምትፈልጉ ሁሉ ወደ ቃሊቲ ጎራ ብትሉ ተጽናንታችሁ እና በርትታችሁ ትመለሳለችሁ፡፡ እናም እስክንድርን አግኙት፡፡ በተራችሁም መልዕክት አስተላልፉልን፡፡


በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን ትግል እንደግፋለን!

Oktober 3/2013

Ethiopian National Transitional Council
P.O.Box 9929
Alexandria, VA 22304
Tel: 1-571-335-4637
Tel: +44-7958-487-420
Email: contact@etntc.org
Website: http://www.etntc.org

በአሁኑ ሰአት ሀገር ውስጥ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ትግሉን በሙሉ ሀይል በመግፋት ላይ መሆናቸውን ሁላችንም
እይተከታተልን ነው። ወያኔ-ኢሃዴግም ያለ የሌለ ሀይሉን እየተጠቀመ ያቺ አይቀሬ የሆነቸውን ቀን ለማዘግየትና የስልጣን
እድሜውን ለማራዘም አፈናውን፤ ግድያውንና እስሩን በስፋት ተያይዞታል።

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ከሳምንት በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ያዘጋጀው የተቃውሞ ሰልፍ እንዲሰናከል አባላቶችን በማሰርና
በመደብደብ፤ መንገዶች በመዝጋትና ሰልፈኛውን በማዋከብ ሲያደርግ የነበረውን ድርጊት በተመሳሳይ በአንድነት ፓርቲና
በ33ቱ ፓርቲዎች ላይ ባሳለፍንው ሳምንት ዸግሞታል። ይህ ድርጊት በወያኔ የሚሽከረከረው የአምባገነኑ ስርአት በ99.6%
ሕዝብ መርጦኛል ያለውን አሰልቺ ፕሮፖጋንዳው የተጋለጠበት፤ መረጠኝ የሚለውንም ህዝብ ምን ያህል እንደሚፈራ
ያሳየበትና የወያኔ ስርአት ፍጹም የአፓርታይድ አገዛዝ መሆኑን ለኢትዮጵያኖችና ለአለም አቀፍ ህብረተሰቡ ግልድ ባለ መልኩ
ያስመሰከረበት ድርጊት ነው። በመነሻነት ድምጻችን ይሰማና የሰማያዊ ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲነቃቃና በድፍረት
ለመብቱ እንዲነሳ ያሳዩት ፈጣንና ቆራጥ አመራር በተከታታይ ለተደረጉ እንቅስቃሴዎች መሰረት በመሆናቸው ልናወድሳቸው
ይገባል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ለነዚህ ቆራጥ የፖለቲካ ድርጅቶች በተለይም ለሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ድርጅት
አመራርና አባላቶች፤ እንዲሁም በየእስር ቤት ተወርውረው ለሚጊኙት የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ደራሽ ጀግኖች የድርጅት
መሪዎችና ጋዜጠኞች፤ ያለንን ከፍተኛ አድናቆት ከመግለጽ ባሻገር፤ ይህንን ግፈኛ ስርአት በህዝባዊ አመጽ መታገልና ማስወገድ
የድርጅታችን መርህ ከመሆኑ አኳያ ሙሉ ድጋፋችንን የምንሰጥ መሆኑን እናረጋግጣለን። በአለም አቀፍ ህበረተሰቡ ዘንድ
የህሊና እስረኞች መሆናቸው የተረጋጋጠላቸውና የተለያየ ሽልማት በማግኘት ላይ ያሉትን ብርቅዬ ወገኖቻችንን አወድሳችኋል
በሚል ድንቁርናና እብሪት በተሞላበት ሁኔታ፤ በወያኔ ሳንባ የሚተነፍሱት አፈቀላጤ አቶ ሽመልስ ከማል የሰጡትን አይን
ያወጣ ማስፈራራት እናወግዛለን።

በተለያዩ አቅጣጫዎች እየታዩ ያሉ መነቃቃትና የነጻነት ትግሎች ወደ ህዝባዊ ማእበል ሲለወጡ የወያኔ/ ኢሕአድግ ስርአት
የማብረድም ሆነ የመጨፍለቅ አቅም እንደማይኖረው እራሱም ጠንቅቆ ያውቀዋል ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ከስርአቱ
ውድቀት በኋላ ስርአቱን የሚተካ ሃይል ቅድመ ዝግጅት፤ እቅድና ስምምነት ባልተደርገበት ሽግግር አሁን በግብጽ በሶርያና
በሌሎች የአለም ሀገራት የምናየው ችግር ውስጥ እንዳትገባ፤ አገርና ህዝቡ ለከፍተኛ አደጋና ቀውስ እንዳይጋለጥ፤ ድርጅታችን
ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ምስረታ ሂደት ላይ ጠንክሮ እየሰራ ይገኛል። ይህንን በተመለከተ ባለፈው ጁላይ ወር ላይ
ከተለያዩ ድርጅቶች፤ የሀይማኖት ተቋማት፤ ምሁራንና ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የምክክር ጉባኤ አካሂዶ የሽግግር
ሂደት ቅድመ ዝግጅት ሂደት እንዲጠናከር የሚያግዝ ኮሚቴ አቋቁሟል። ቀጣይ እንቅስቃሴዎችና እርምጃዎችን አስመልክቶ
ተከታታይ መግለጫዎች የምናወጣ መሆኑን እየገለጽን የጉዳዩ ባለቤት የሆነው ወገናችን አደጋውን በመገንዘብና ተሳትፎ
በማድረግ በጋራ በአገራችንን አስተማማኝ ለውጥ እንድናመጣ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የምናደርገው ዕንቅስቃሴ ህዝብን
መሰረት ያደረገ ሁሉን አቀፍ እንቅስቃሴ በመሆኑ ስርአቱን ስታገለግሉ የነበራችሁና የከዳችሁ ሽግግር ምክር ቤቱን በመቀላቀል
ታሪካችሁን እንድታድሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ለዘላቂና አስተማማኝ ለውጥ እንሳተፍ እንደራጅ!

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት አመራ

Wednesday, October 2, 2013

G7 is forming a network within the Defense Forces: Andargachew

October 2/ 2013

Andargachew Tsige, the Secretary General of the opposition Ginbot 7 Movement said that they are forming their own network within the Ethiopian Defense Forces. He said this after a successful fund raising event held in Norway over the weekend.

Andargachew said the fund raising, on the one hand, motivates the members of the Ginbot 7 Popular Forces and also reminds us that we have a huge public responsibility. He said the four defecting Air Force pilots that joined the Movement were in a good condition and his Movement has been instituting lines within the Army, the Air Force, and the Intelligence on a conduct that the securities cannot trace.

He also stressed that there should not be any fund raising event in the name of the Popular Force or individuals until the Force makes its own fund raising programs public in the future.

Similarly, Andargachew also gave a visual and textual explanation of the aims, missions and visions of the Popular Force up until its present condition to a crowed in Stockholm, Sweden.

During the event he said the Force was not hierarchical but horizontally structured where everyone was treated equally. It is also a Force founded by Ethiopians that hailed from all parts of the world  leaving their families, children and life aside, Andargachew added.

According to him, the aim of Ginbot 7 is not only establishing a democratic system but it is also returning the values that Ethiopians have been stripped of for the past 22 years

የአዜብ መስፍን የመያዝ እድል እየሰፋ ነዉ የሙስና ንሰሃ አባቷ እና ባልደረባዋ ተይዟል።

Oktober 2 / 2013
የአዜብ መስፍን የመያዝ እድል እየሰፋ መቷል። የሙስና ንሰሃ አባቷ እና ባልደረባዋ ተይዟል። በከፍተኛ ደረጃ በሙስና በመዘፈቅ ያለአከራይ ከባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ለቁጥር የማይገመት ሃብት አፍርተዋል የተባሉት ሃያሁለት አካባቢ የሚገኘው የኮሜት ሕንጻ ባለቤት አቶ ገብረስላሴ ሃይለማርያም (አለቃ ገብረስላሴ) በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተከትሎ በባለስልጣናት ዙሪያ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል። የካፒታል ሆቴል ባለቤት የሆነው ልጃቸውም እንዲሁ ሁኔታዎች እየተጣሩበት ሲሆን የአለቃ ገብረስላሴ የሙስና መዝገቦች ከገብረዋህድ ጋር የተቆራኙ እና ከዚህም ጋር በተያያዘ አዜብ መስፍንን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር ይውላሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሙስና ንሰሃ አባት የሚባሉት እና በአቋራጭ የከበሩት በማናለብኝ ጭነት እና በትዕቢት በመንግስት ባለስልጣናት የሚመኩት አለቃ ገብረስላሴ ባለፉት አራት ወራት ከተያዙት እና የአዜብ መስፍን የሙስና አጋሮች ከሚባሉት መላኩ ፋንታ፣ ገብረዋህድ ፣ወ/ጊ ፣ነጋ ገ/እግዜር ፣ስማቸው ከበደ፣ ከተማ ከበደ እና ሌሎች የሙስና ባላባቶች ጋር እንደተያዙ ወዲያውኑ የቃሊቲን ቂሊንጦ ጎራ ተቀላቅለዋል።

እስካሁን ድረስ በፍርድ ቤት የቀረበባቸው የክስ ዝርዝር ባይታወቅም በመጪው የጥቅምት 14 እና 18 2013 ክሱ የሚሰማ መሆኑ ታውቋል። ውስጥ አዋቂዎች እንደሚሉት አለቃ ገብረስላሴ ክስ ሳይመሰረትባቸው ቃሊቲ መውረዳቸው አጠያያቂ ነው ሲሉ ተደምጥጠዋል። ሆኖም እንደመርማሪዎቹ ምንጮች ከሆነ የተከሰሱት በገብረዋህድ መዝገብ ጋር በአንድነት እንደሆነ ታውቋል። ፋይሉ አካባቢ ያሉ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በተከለከለው ከፍራንኮ ቫሉታ በመጠቀም በህገወጥ መንገድ ሲሚንቶ አስገብተዋል የተለያዩ እቃዎችን ቀረጥ ሳይከፍሉ አስገብተዋል በጉቦ እና በህገወጥ ገንዘብ ዝውውር ወዘት የሙስና ተግባራት ከባለስልጣናት ጋር ተመሳጥረዋል በሚለው ፋይል የተካተቱ ሲሆን በዚህ ፋይል ደግሞ የአዜብ መስፍን የሙስና አጋሮች ገብረዋህድ እና ሚስቱ ሃይማኖት እንዲሁም የስዬ አብርሃ ወንድም ምህረተአብ ይገኙበታል::
 
 ምንሊክ ሳልሳዊ

አንድነት በመንግስት ዛቻ አንደናገጥም አለ

Oktober 2 / 2013

 አንድነት  ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በመሆን መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በቀበና አካባቢ በተወሰነው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በሽብርተኝነት ጥፋተኛ ተብለው የታሰሩ ሰዎችን ይፈቱ ማለቱ፣ እንዲሁም ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ያለን የሙስሊም ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱ መጠየቁና ባልተፈቀደ ቦታ ሰላማዊ ሰልፍ አድርጓል በሚለውን የመንግስት ምላሽ ማዘኑንና በመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስቴር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ዛቻ እንደማይደናገጥም አስታወቀ።


የፓርቲው ምክትል ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ጉዳዩን በማስመልከት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት በመንግስት በኩል ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ፈጣን ምላሽ በአቶ ሽመልስ ከማል በኩል መገለፁን ፓርቲው መገንዘቡን ከገለፁ በኋላ በሚኒስትር ዲኤታው በኩል የተገለፀው ነገር የመንግስት አቋም ስለመሆኑ ቢያጠራጥርም ምላሹ ግን የህግ ትርጓሜን በማዛባት የቀረበ ነው ብለዋል።

“አቶ ሽመልስ ከመዛት ግላዊ ባህሪያቸው ተነስተው “ሕግ የሚያመጣውን መዘዝ ለመቀበል ይዘጋጁ” ማለታቸው ሁላችንንም ያሳዘነ አገላለፅ ነው። እኛ ሕግ አስተማሪና ቀጪ መሆኑን እንጂ መዘዝ መሆኑን አናውቅም። ካጠፋን ልንማር እንችላለን መንግስትም ካጠፋ ከስህተቱ ሊማር ይገባል ብለን እናምናለን። ስለዚህ የህግ መዘዝ አለው ማለት ለእኛ ከዛቻ የተሻለ ትርጉም የለውም” ብለዋል። አቶ ሀብታሙ ጨምረው እንደገለፁት የሚኒስትር ዲኤታው ንግግር በፖለቲካ ይዘትም ሆነ ከህግ አንፃር መሰረት የሌለው ነገር ከመሆን በዘለለ ይሄንን ሀገር በተሻለ ብቃት የመምራት አቅም ማጣታቸውን ማሳያ ነው ብለዋል።

አቶ ሽመልስ ከማል ካነሱዋቸው ነጥቦች መካከል “ሰልፉ ባልተፈቀደ ቦታ ተካሂዷል” የሚለው ወቀሳ ነው ያሉት አቶ ሀብታሙ “በእርግጠኝነት የአዲስ አበባ አስተዳደር ለአንድነት ፓርቲ በፃፈው ደብዳቤ የሰላማዊ ሰልፉ መነሻ ከፓርቲው ጽ/ቤት ተነስቶ በቀበና አደባባይ አድርጎ፣ ወደ ጃንሜዳ አምርቶ፣ ሰልፉ እዛው ጃንሜዳ እንዲጠናቀቅ የሚል ነው። ይህ ውሳኔ የደረሰንም የእኛን ሰልፍ ለማደናቀፍ፣ ያቀረብናቸውን ዘጠኝ አማራጮችንም በመቀልበስ፣ ባልፈለግነውና ባልመረጥነው ቦታ እንዲፈፀም ነው የተደረገው። ይህ ነገር ከሞራልም ከህግም አንፃር ተቀባይነት ባይኖረውም ለህግ ተገዢ በመሆን ወደ መስቀል አደባባይ የምናደርገውን ጉዞ በፖሊስ በከፍተኛ ኃይል መጥቶ መንገድ በመዘጋቱ፤ ከፖሊስ ጋር ግብግብ መፍጠሩን በመተው ወደቀበና አደባባይ በመዞር ቀበና አደባባይ ላይ ሰልፉን ለማጠናቀቅ ተገደናል። ወደጃንሜዳ ያልሄድንበት ምክንያት ኢህአዴግ ህግ እንድንጥስ በር ሲከፍትልን ህግ ላለመጣስ ብለን ወደጃንሜዳ አልሄደንም። ጃንሜዳ ያልሄድነው ቦታው ከጦር ካምፕ በ20 ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ በመሆኑ የሀገሪቷ ህግ ደግሞ ማናቸውም ሰላማዊ ሰልፍም ሆነ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከጦር ካምፕ ካለበት ቢያንስ 500 ሜትር ርቆ መካሄድ አለበት ስለሚል ነው” ብለዋል። ይህም ባልተፈቀደ ቦታ ሰልፍ ማካሄድ ሳይሆን ለሀገሪቱ ህግ ያለንን ተገዢነት ያሳየንበት ስለሆነ ሁኔታው የእኛን ሕጋዊነት ያሳየ ሲሆን በአንፃሩ እነ አቶ ሽመልስ የሚመሩት መንግስት ሕገ-ወጥነት ማረጋገጫ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በሕግ አግባብ ሲታይ ሃያ ሜትር የጦር ካምፕ ስር ሄዶ መሰለፍ ነው ወይስ እንዲሰለፉ ፈቃድ የሰጠው አካል  የሚጠየቀው? ሲሉ ጥያቄውን በጥያቄ መልሰዋል።


























“ሌላው በነፃ ፍርድ ቤት አሸባሪ የተባሉትን ሰዎች እንደ ሰማዕት አስመስለው “መልዕክቶቻቸውን አንብበዋል” የሚለው የአቶ ሽመልስ ማስፈራሪያ ከሀገሪቱ ሕገ-መንግስት ጋር ይጋጫል የሚሉት አቶ ሀብታሙ የሀገሪቱ ሕገ-መንግስት በግልፅ እንዳስቀመጠው ማንኛውም የፍርድ ቤት ውሳኔ ከፍርድ ውሳኔ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ መቃወም ወንጀል ሳይሆን መብት ነው ብለዋል። እንኳንስ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ቀርቶ አንድ ግለሰብ ከፍርድ ውሳኔ በኋላ ውሳኔውን መቃወም መብት ሆኖ ሳለ አቶ ሽመልስ ግን ነፃ በሚሉት ፍርድ ቤት የተወሰነውን ውሳኔ ጥሳችኋል ማለታቸው ተገቢም ተቀባይነትም የለውም ብለዋል።

“አቶ ሽመልስ የሚመሩት ድርጅት በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ነፃ ናቸው ብሎ ያምናል። በአንፃሩ የእኛ ፓርቲ ደግሞ ነፃ ፍርድ ቤት የለም ብሎ ያምናል። በዚህ ረገድ የአቋም ልዩነት አለን። ነፃ ፍርድ ቤት የለም ብለን አቋም መያዝ የፖለቲካ መብታችን ነው። አቶ ሽመልስ ይሄ የፖለቲካ መብት መሆኑ ካልገባቸው በቀር ነፃ ፍርድ ቤት የለም ብለን ስናበቃ፤ ነፃ ያልሆነ ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ አንቀበልም ማለት በእኛ እምንት ተገቢ ነው። ህግ መጣስ የሚመጣው ያ ነፃ አይደለም ያልነው ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ በኃይል ለመቀበልስ ከሄድን ብቻ ነው። እኛ ግን ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሰላማዊ መንገድ ነው የተቃወምነው። ይሄ ደግሞ መብት ነው እንጂ ወንጀል አይደለም” ሲሉ አቶ ሀብታሙ መልሰዋል።

በተጨማሪ አቶ ሽመልስ “በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ሽብርተኝነት አበረታተዋል” ሲሉ ከሰውናል ያሉት አቶ ሀብታሙ በመጀመሪያ ደረጃ እኛ የታሰሩት ሰዎች ሽብርተኛ ናቸው ብለን አናምንም። አለማመን ደግሞ መብት ነው። ፍርድ ቤቱ የሰጠውንም ውሳኔ ተገቢ ነው ብለን አናምንም። እንደ ፓርቲም መቃወማችንን እንቀጥላለን። እነሱ ሽብርተኛ ያሉዋቸው ሰዎች ቀደም ሲል እስር ቤት ሆነው ኀሳባቸውን በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሔቶች ሲገልፁ ቆይተዋል። ነገር ግን ለኢህአዴግ ህመም የፈጠረበት በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ሲገለፅ ነው። ይሄ ደግሞ የሰልፉ ውጤት ኢህአዴግን ስላስከፋው እንጂ ህግ መጣስ አይደለም። በተጨማሪም አንድ ሰው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ኃይሉ ዜሮ በሆነበት ሁኔታ “አበረታታችኋል” ማለቱ ትርጉም የለውም። ስለዚህ ሽብርተኝነትን የምናበረታታበት ምንም ዕድል የለም ብለዋል።

የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን በተመለከተም በትክክልም በፍርድ ሂደት ላይ ያለ ጉዳይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሀብታሙ በፍርድ ሂደት ላይ ያለን ነገር መቃወም ተገቢ አይደለም ብለዋል።

“ነገርግን አቶ ሽመልስ የተረዱን አይመስለኝም” ያሉት አቶ ሀብታሙ እኛ እየተቃወምን ያልነው ፍ/ቤቱን ሳይሆን ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን “ጀሀዳዊ ሀረካት” የሚል ዘጋቢ ፊልም ሰርቶ ተጠርጣሪዎቹን “አሸባሪ” ብሎ ከፍርድ ቤቱ በፊት መወሰኑን ነው። ይሄንን ደግሞ በአደባባይ መቃወም አሸባሪን መደገፍ አይደለም። ፍርድ ቤቱ የሚወስነውን ከወሰነ በኋላ ደግሞ የምንይዘውን አቋም እንይዛለን። ነገር ግን አሁን ፍርድ ቤቱ “ተጠርጣሪ” እያላቸው ኢቲቪ ግን “አሸባሪ” ብሏቸዋል። እኛ ደግሞ “የለም እነዚህ ሰዎች ተጠርጣሪ እንጂ አሸባሪ አይደሉም” ብለን ተሟግተናል። የምንቃወም ይሄንኑ ነው በማለት አስረድተዋል።

“ሌላው በሽብርተኝነት የታሰሩ ይፈቱ ብላችኋል” የሚለው የአቶ ሽመልስ ከማል ክስ በተመለከተም ፍ/ቤት በነፃነት የመወሰን መብቱ ኢቲቪ ባስተላለፈው ፊልም ነፃነቱን በመጋፋቱ በተያዙት ሰዎች ላይ ነፃ ፍርድ ይሰጣል ብለን አናምንም። ስለዚህም ሰዎች በነፃ ይለቀቁ ብለን መጠየቃችንን የሕግ መዘዝ ያመጣል ማለት የመንግስት ስልጣናቸውን ከመመካት የሚመነጭ እንጂ የሕግ መሰረት የለውም ብለዋል። በአጠቃላይ የአቶ ሽመልስ ምላሽ በግብታዊነት ፓርቲው ላይ እርምጃ ለመውሰድና ሰላማዊ ትግሉን ለማዳፈን በመሆኑ መዘዙ የከፋ ነው ሲሉ በበኩላቸው መልሰዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እሁድ ዕለት ማምሻውን ለኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት በሰጡት ማብራሪ አንድነት ፓርቲ ባልተፈቀደለት ቦታ ሰልፍ ማካሄዱን እንዲሁም በሰልፉ ላይ በሽብርተኝነት ጥፋተኛ ተብለው የታሰሩ ሰዎችን በማወደስና እንዲፈቱ በመጠየቅ ሽብርተኝነት ማበረታታቱን በመግለፅ ህገ ወጥ ተግባር መፈፀማቸውንና ፓርቲውም ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ መጠየቃቸው አይዘነጋም።

Tuesday, October 1, 2013

የአንዱዓለም አራጌ መልክት ከቃሊቲ (በሰላማዊ ሰልፍ ላይ የተነበበ)

Oktober /1/ 2013

ከሁሉ አስቀድሜ በዚህ ታላቅ ህዝባዊ ሠላማዊ ሠልፍ ለተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼለእያንዳንዳችሁ በተናጠል ልባዊ የአክብሮትና የናፍቆት ሠላምታዬ በግፍ ከታሰርኩባት ጠባቧ ክፍል ይድረሳችሁ
Andualem Aragie (3)ኢትዮጵያውያን ለዘመናት እውን ያላደረግነውን የህዝባዊ ልዕልና ጥያቄና ሌሎች ከነፃነት እጦት ጋር የተቆራኙ በአገዛዙ የሚፈፀሙ አያሌ የአፈና ተግባሮችን ለመቃወም በተጠራው በዚህ ሠላማዊ ሠልፍ ላይ ከጎናችሁ መሠለፍ ባለመቻሌ ባዝንም፣ ከተሰለፋችሁላቸው ዓላማዎች አንዱ የእኔና የጓደኞቼን ከእስር መቀቀቅ የሚመለከትና የታሰርኩለትም ዓላማ አካል በመሆኑ በመንፈስ ከጎናችሁ እንዳለሁ አምናለሁ፡፡ በዚህም ታላቅ ደስታ ይሰማኛል፡፡

ኢትዮጵያ ህዝባዊ ልዕልና የሠፈነባት የነፃነትና የዴሞክራሲ ምድር ትሆን ዘንድ የቀደሙ ትውልዶች ከፍተኛ መሰዋእትነት ከፍለዋል፡፡ ሌላውን ትተን የዛሬ 4ዐ ዓመት የተደረገውን ትግል ብቻ መጥቀስ ጥሩ ማሳያ ይሆናል፡፡ የዛሬ 4ዐ ዓመት ‹‹ሕዝባዊ መንግሥት›› ለመመስረት በሚል በተደረገ ትግል ሊለካ የማይችል መስዋዕትነት ተከፍሏል፡፡ ነገር ግን ‹‹ከጎናቸው ተሰልፈን ታገልን የሚሉን ወገኖች ዛሬ የኢትዮጵያን ህዝብ እግረ ከወርች አስረው እየረገጡት ይገኛሉ፡፡

ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሉዓላዊ ሥልጣኑ ባለቤት መሆን አልቻለም፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ ሕዝብ ከገጠር እስከ ከተማ በካድሬዎች ፈርጣማ መዳፍ እየታሸ ነው፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ ከማደናገሪያ ስልትነት ባለፈ የህዝብ የመናገርና የመፃፍ መብት አልተከበረም፡፡ ዛሬም 4ዐ ዓመት በኋላ አገዛዙን የሚቃወሙ ዜጎች በበሬ ወለደ ክስ በግፍ ይታሰራሉ፡፡

እኔና ጓደኞቼ ለዚህ ማሳያዎች ነን፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው ሳይሆን አፈ-ሙዝ ያገነነው በምርጫ ተውኔት 99.6% የህዝብ ድምጽ በመዝረፍ ሀገራችንን በዓለም ፊት የሚያኮስስና የህዝቧን ክብር የሚያዋርድ ተግባር የሚፈፀምባት ሀገር ነች፡፡ ዛሬም ከ4ዐ ዓመት በኋላ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ በጥቂት የወቅቱ አምባገነኖች በገዛ ሀገሩ እስረኛ ሆኖ ይገኛል፡፡
ዛሬ እየተካሄደ ያለው ሠልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዘመናት እስራት ነፃ ለመውጣት የሚያደርገው አጠቃላይ ትግል አካል ነው፡፡ ኢትዮጰያውያን የየትኛውም ቋንቋ ተናጋሪዎች ብንሆን፣ የየትኛውም እምነት ተከታዮች ብንሆን፣ የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባሎች ብንሆን፣ በየትኛውም የፆታና የእድሜ ክልል ብንገኝ ሁላችን አንድ የሚያደርግ ሰብአዊ ልዕልናችን ተከብሮ በነፃነት የመኖር ተቀዳሚ አጀንዳ አለን፡፡

ነፃነት ማንም በችሮታ ወይንም በአዋጅ የሚያረጋግጥልን ሳይሆን በነፃነት ለነፃነት የተፈጠርን ሉዓላዊ ፍጡራን መሆናችንን ከልብ ስናምን የምንጎናፀፈው ፀጋ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ትልቁ የነፃነት ጠላት እራስን ዝቅ አድርጎ ከማየት የሚመጣ ፍርሃት ነው፡፡ ፍርሃትን ያላሸነፈ ሕዝብ በአዋጅ ነፃ ሊወጣ አይችልም፡፡ አዋጅ መች ቸገረንና? ፍርሃትን ያላሸነፈ ህዝብ የነፃነቱ ባለቤት ሊሆን አይችልም፡፡ ፍርሃትን ያላሸነፈ ህዝብ ለልጆቹ ነፃ ሀገር ሊያወርስ አይችልም፡፡ የፍርሃትንና የግለኝነት ወረርሽኝ ማስወገድ ፈጽሞ ጊዜ የሚሰጠው ተግባር አይደለም፡፡ ፍርሃትንና ለኔነትን ድልነስታችሁ ዛሬ ለነኀነት መሰለፍ በመቻላችሁ የተግሉን የመጀመሪያና ወሳኝ መዕራፍ ተሻግራችኋል፡፡

ፍርሃትን በማሸነፍ ለነፃነት መታገል ወሳኝ የመሆኑን ያህል፣ ከቀደሙ ስህተቶቻችን መማር፣ ትግሉን በተጠናና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ማካሄድም የዚያኑ ያህል አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡

እስከ አሁን በዝምታችን አምባገነኖች የልብ ልብ እንዲሰማቸው ብሎም አፍነው እንዲገዙን እድል ሰጥተናቸዋል፡፡ እስከ አሁን መብቶቻችንና ሰብአዊ ክብራችን በግደለሽነት እንዲረገጡ በመፍቀዳችን ኢትዮጵያና ሕዝቧ የጥቂት ገዢዎች አንጡራ ሀብት ሆናለች፡፡ እስከ አሁን በቁርጠኝነት ባለመታገላችን ዛሬም እንደ አዲስ ከአምባገነንነት ጋር ግብግብ መግጠም ግድ ሆኖብናል፡፡ የአፈናውን የክፋት ደረጃና የአገዛዙን አሙለጭላጭ የአፈና ስልቶች ግንዛቤ ውስጥ ያስገባና ዘመኑን የሚመጥን የፀና ሠላማዊ ትግል ማድረግ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ይጠበቃል፡፡

ሠላማዊ ትግል በአንድ ወይንም በሁለት ሠልፍ የሚቋጭ ሳይሆን አያሌ ስልቶችንና ሠፊና ቀጣይነት ያለውን እንቅስቃሴ የሚያካትት ነው፡፡ የፖለቲካ ባህላችንና አስተሳሰባችንን ከማዘመን ጀምሮ ገዢዎች ነፃነትን የማይፈሩበትን ስነ-ልቦና እንዲላበሱ ማድረግና ለበርካታ ዘመናት በጭቆና ደቅድቅ ጨለማ ውስጥ ያለችውን ሀገራችን የነፃነት ብርሃን ከደር እስከዳር የሚበራባት ሀገር እስክትሆን ድረስ መታገል ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ የላቀና የከበረ ምን ቁም ነገር ይኖራል?

ይህ ትውልድ ለማመን የሚከብዱ ታላላቅ ገድሎችን የሰሩ አባቶች ልጆች መሆናችንን ለአፍታ እንኳ መዘንጋት አይገባውም፡፡ በተግባርም የላቀ ገድል በመስራት ማንነቱን ሊያስመሰክር ይገባል፡፡ አባቶቻችን የሞቱላትንና የአጽማቸው ማረፊያ፣ እትብታችን የተቀበረባትንና የሁለንተናዊ ማንነታችን ማህደርና የልጆቻችን ተስፋና መኖሪያ የሆነችውን የምንወዳትን ሀገራችንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የሰፈነባት የማይደርቅ የህዝባዊ ሉዓላዊነት ምንጭ እስክናደርጋት ድረስ እጅ ለእጅ ተያይዘን ትግላችንን በጽናት መቀጠል የጠበቅብናል፡፡ የዓላማና የህሊና ንጽህናን ተላብሰን ለወንድማማችነት፣ ዴሞክራሲና ነፃነት በምናደርገው ሠላማዊ ትግል ፈጣሪም ከእኛ ጋር እንደሚሆን አምናለሁ፡፡

በመጨረሻም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በእስራኤል አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እየከፈልኩት ላለው ዋጋ እውቅና ሰጥተው ስለዘከሩኝ፣ የኢሳት ቴሌቭዥን ተመልካቶችና የዘ-ሀበሻ ድረ-ገጽ ታዳሚዎች ‹‹የዓመቱ ሰው›› ብለው በመምረጠ ላጎናፀፉኝ ትልቅ ክብር ከፍ ያለ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እንዲሁም ሰማያዊ ፓርቲ በግፍ የታሰርን ሰዎች እንድንፈታ በመጠየቁ አመሰግናለሁ፡፡ በአጠቃላይ በፀሎት ከማሰብ ጀምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ከጎኔ በመቆማችሁ የላቀ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡ ይህ የመከራ የሀሩር ወቅት አልፎ ብርሃን በሞላው የፀደይ ወቅት በነፃነት ለመኖር ትግላችንን ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ አጠናክረን ልነቀጥል ይገባልይገባናል፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ ህሊናዩን የሚያሳዝን አንዳችም ነገር ፈጽሜአለሁ ብዬ አላምንም! ፍፁም ሠላም ይሠማኛል፡፡ እኔን እዚህ ያቆመኝ የነፃነት ናፍቆት ነው፡፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!

አንዱዓለም አራጌ   (የህሊና እስረኛ)

ሰው ለሰው እና አስናቀ ትንቅንቅ ውስጥ ገቡ።አስናቀ በቁጥጥር ስር

Oktober 1/2013

የሰውለሰው የቴሌቪዥን ድራማ ተውኔት በመንግስት ሃይሎች ትእዛዝ መሰረት ትንቅንቅ ውስጥ መግባታቸውን እና መንግስት በአቶ አስናቀ ገጸባህርይ መላቅጡ እንደጠፋው እና ትክክለኛውን የመንግስትን ገጸባህርይ የሚተረጉም እንደ ሆነና መንግስትም ይህንን ባህርይው ለህዝብ ይፋ መገለጹ ስላለወደደው ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጦ ምርምር እንዲደረግበት አዞአል ።

እንደ መንግስት ሃይሎች ትእዛዝ መሰረት ከሆነ አስናቀ በቁጥጥር ስር ውሎ በፖሊስ ምርመራ እንዲደረግበት የታዘዘ ስለሆነ   ሌሎች ገጸባህርያቶች እንዲቀጥሉ ታዟል  የዚህም ድራማ ጊዜ አጭር እንዲሆነ ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፎአል ደራሲዎቹም የስድስት ወር ጊዜ ገደብ ጠይቀዋል  ።

ይህ ከሆነ የፊልሙ መቼቱም ሆነ ሴራው ምን እንደሆነ እና ትርጉም አልባ ሊሆን የሚችል እንደሆነ ለማወቅ እና ለመገንዘብ አያዳግትም ::ይህ በእንዲህ እንዳለ የሰው ለሰው ድራማ ከአረብ አገር ተከታታይ ድራማ ላይ የተቀዳ ነው በሚል ከፍተኛ ትችት እንደደረሰበት እና ፊልሙ የተቀዳበትን ዋነና የፊልም ስራ ምን እንደነበር በመግለጽ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃኖች የቀረበ ከመሆኑም በላይ አስደንጋጭ የሆነ የሰው ልጆችን የስራ ፈጠራ ስርቆት ነው በሚል ሲተች መቆየቱ ይታወሳል። አንዳንድ መረጃ መረቦች በሰው ለሰው ድራማ መቋረጥ አስመልክቶ ከጻፉት መካከል ተስፋዬ ገብረአብ እንዲህ ሲል አቅርቦታል ሙሉውን እናስነብባችኋለን


አበበ ባልቻ እንደ አዜብ መስፍን

 
 “ሰው ለሰው” የተባለው ተወዳጅ ተከታታይ ድራማ ይቋረጥ ዘንድ ታዞአል። የተሰጠው ምክንያት፣ የአበበ ባልቻ (አስናቀ) ገፀባህርይ ከህግ በላይ መሆኑ እየበረታ መሄዱ ነው ተብሎአል። አስናቀ (አበበ ባልቻ) ህወሃትን ወክሎ እስከተጫወተ ድረስ የግድ ከህግ በላይ ሆኖ መቀጠል አለበት። ስለዚህ የድራማው ደራስያን ምንም ስህተት አልሰሩም። ያለውን ተጨባጭ እውነታ ነው ያንፀባረቁት። ሕወሓት ራሱን ማየት ደብሮት ይሆን?
 
ደራስያኑ የታዘዙት አስናቀን በቁጥጥር ስር አውለው ድራማውን እንዲጨርሱት ነው። ይሄ ግን ሊሆን አይችልም። ከእውነታው ጋር ይቃረናል። ምናልባት አበበ ባልቻ (አስናቀ) አዜብ መስፍንን ብቻ ወክሎ እየተጫወተ ነው ከተባለ ግን ያስኬዳል። ሆኖም አበበ ባልቻ ድራማው ላይ በቁጥጥር ስር ከዋለ በገሃዱ አለም አዜብም መታሰር አለባት።

የድራማው ደራስያን ድራማውን ለመቋጨት የስድስት ወራት ጊዜ ጠይቀዋል። የሃይለማርያም መንግስት ምላሽ እየተጠበቀ ነው።   በሌላም በኩል የወያኔው ቀንደና መል እክተኛ እየተባለ የሚጠራው Fitsum Berhane ፍጹም ብርሃኔ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዲህ ሲል አስፍሯል
ፖሊስ ሰለሰው ድራማ ላይ "የኣስናቀ" ገፀ ባሀርይ በሕግ ቁጥጥር ስር ውሎ ድራማው እንዲጠናቀቅ ኣዘዘ፡፡
ፌዴራል ፖሊስ በኣስናቀ ገፀ ባህርይ በሸቀ መሰለኝ፡፡

ግንቦት7 በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ መስመሩን እየዘረጋ መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ

September 30 / 2013
መስከረም ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸው ይህንን የተናገሩት በኖርዌይ ከተካሄደው ደማቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሁዋላ ነው።
የግንቦት7 ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅቱ በአንድ በኩል በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል አባላት ላይ ከፍተኛ መነቃቃት የሚፈጥር በሌላ በኩል ደግሞ የተጣለብን ህዝባዊ አደራ ከፍተኛ መሆኑን የሚያስታውሰን ነው ብለዋል።
በቅርቡ ከኢትዮጵያ አየር ሀይል ከድተው የሄዱት ሰዎች በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኙ የገለጹት አቶ አንዳርጋቸው ፣ በመከላከያ ሰራዊት በእግረና፣ በአየር ሃይልና በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ሊደርሱበት በማይችሉበት መንገድ መስመር እየዘረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
በውጭ አገራት ተመሳሳይ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ለማድረግ እቅድ አላችሁ ወይ ተብለው የተጠየቁት አቶ አንዳርጋቸው፣ ህዝባዊ ሀይሉ ከተግባር ጋር በተዛመደ መልኩ የገቢ መሰባሰብ ዝግጅት መርሀ ግብሩን ይፋ እስከሚያደርግ ድረስ በህዝባዊ ሀይሉ ወይም በግለሰቦች ስም ምንም አይነት የገቢ መሰባሰቢያ ዝግጅት መደረግ እንደሌለበት ገልጸዋል
በሌላ ዜና ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላቸው በስቶክሆልም እና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር ውይይት አድርገዋል። አቶ አንዳርጋቸው የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይልን ዓላማዎች፡ተልዕኮዎች እና ራዕይ በማስተዋወቅ ህዝባዊ ሃይሉ ከምስረታ ጀምሮ አሁን ያለበትን ደረጃ በምስልና በጽሁፍ የተደገፈ ገለጻ ለተሰብሳቢው አቅርበዋል።
እሳቸው እና ሌሎች የአመራር አካላት እንዲሁም አባላት የተገኙበት የውትድርና ስልጠና አንዱ የበታች አንዱ የበላይ እንዳልሆነ በማስገንዘብ ይህ ህዝባዊ ሃይል ቤተሰባቸውን፡ስራቸውን፡ ገንዘባቸውን፡ እና የተደላደለ ኑሯቸውን በመተው ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን የተዋቀረ እንደሆነ ገልጸዋል።
የግንቦት ሰባት ዓላማ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ማስፈን ብቻ ሳይሆን ባለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያውያን የተገፈፉትን ክብራቸውን ማስመለስ ጭምር መሆኑን አቶ አንዳርጋቸው አስምረውበታል ሲል ቴዎድሮስ አረጋ ከስዊድን ዘግቧል።