Thursday, April 18, 2013

ከፈንጂ ማምከኛ ድርጅት በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ሀብት ተዘረፈ

ሚያዚያ ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በአፍሪካ ውስጥ ካሉ ሶስት የፈንጅ አምካኝ ድርጅቶች መካከል በአገልግሎት ዘመኑም ሆነ በተግባሩ በግንባር ቀደምነት ስሙ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ፈንጅ አምካኝ ድርጅት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ እንደፈርስ መደረጉን ተከትሎ፣ ከተለያዩ የውጭ አገራት በእርዳታ ከተሰጠው በመቶ... ሚሊዮኖች ከሚቆጠር ገንዘብ በተጨማሪ፣ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቹ በወታደራዊ መኮንኖች እንዲዘረፍ መደረጉን የውስጥ ምንጮች ገለጹ።

አብዛኞቹ የድርጅቱ ከባድ መኪናዎች እና ሌሎች ንብረቶች በወታደራዊ አዛዦች መወሰዳቸውን የገለጡት ምንጮች ጉዳዩ ያሳሳበው የጸረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቢጀምርም ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ምርመራውን አቋርጣል።

ከ100 እስከ 150 ሚሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ መዘረፉን የገለጡት ምንጮች፣ ከዝርፊያው ጋር እጃቸው አለበት የተባሉት መኮንኖች በዘረፉት ገንዘብ ከፍተኛ ህንጻዎችን እያስገነቡበት መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአንድ የመምሪያ ሀላፊነት ቦታ ላይ የነበሩ ሰው ድርጅቱ ከአውሮፓ እና ከአሜሪካ መንግስት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገለት በጥሩ ሁኔታ ሲሰራ ከቆየ በሁዋላ፣ በድንገት የተወሰኑ ወታደራዊ አዛዦች በድንገት ተመካክረውና በቂ ጥናት ሳይደረግበት ከ7 መቶ በላይ ሰራተኞችን በማባረር እንዲፈርስ አድርገውታል ብለዋል። ወታደራዊ አዛዦቹ የተወሰኑ ቁሳቁሶችን ለፌደራል ፖሊስ ያስረከቡ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ንብረት ያለጠያቂ በመከፋፈል መውሰዳቸውን እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።

ከ3 ወራት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው የነበሩት የድርጅቱ ሰራተኞች ሰሚ አጥተው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውንም እኝህ ባለስልጣን ገልጸዋል።

ድርጊቱ በህወሀት ታማኝ ጀኔራሎች መካከል የጥቅም አለመግባባት ፈጥሮ እንደነበርም ታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል ፍቼ ከተማ የነበረው ጽህፈት ቤት ፈርሶ በአሁኑ ጊዜ ሌላ ጽህፈት ቤት መቀሌ ውስጥ እንዲከፈት መደረጉንም እኝሁ ባለስልጣን ገልጸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

በኢትዮጵያ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚገኙ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ሙስና በአገሪቱ ውስጥ የሚታየውን የኑሮ ውድነት ከማባባስ በተጨማሪ በህብረተሰቡ ውስጥ ያለው የኑሮ ልዩነት እንዲሰፋ እያደረገው ነው።

ለገዢው ፓርቲ ቅርብ የሆኑ ሰዎች በአንድ ጀምበር ሚሊየነር የሚሆኑበት አሰራር በመጨረሻ አገሪቱን እንደሚጎዳ ብዙዎች አስተያየት ይሰጣሉ።

ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ የተባለው ተቋም ባለፉት ስምንት አመታት ከኢትዮጵያ ከ 180 ቢሊዮን ብር በላይ ተዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች መከማቸቱን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በሌላ በኩል ግን አገሪቱ ከቻይናና ከህንድ የተበደረችውን ገንዘብ ሳይጨምር 150 በሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ የውጭ እዳ አለባት።

ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች እና የመንግስት ባለስልጣናት በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች የሚገነቡዋቸውን አንዳንድ ህንጻዎች በፎቶ ግራፍ በማስደገፍ ማቅረባችን ይታወሳል።

ኢህአዴግ በ9ኛው ጉባኤ ሙስናን ለመዋጋት ቃል መግባቱ ይታወሳል።
See More

Wednesday, April 17, 2013

Behind the Ethnic Cleansing in Benishangul-Gumuz

by Fekade Shewakena

The despicable and barbaric action of targeting, evicting and deporting ethnic Amaharas from the Benishangul-GumuzThe despicable and barbaric action of targeting, evicting and deporting ethnic Amaharas. ethnic state in western Ethiopia is a horrific crime and a crime against humanity by any measure and the outrage of Ethiopians across the world is justified. The stories we hear from the victims themselves and the witnesses who saw it are heart wrenching. Thanks to social media and communication technology, we are hearing from the victims themselves and seeing some of their tragic pictures in real time irrespective of where we live. Thanks to the folks at ESAT TV and Radio for the relentless coverage. I have even heard many supporters of the Ethiopian regime, at least those who live outside of Ethiopia, condemn this barbarism. They should be applauded for that. What kind of sane person cannot be outraged when watching this replay of a Nazi pogrom that targets an ethnic group who were literally frog-marched and, in the words of the victims themselves, told to go to “their country” and “wherever their ancestors were born”? What do you feel when you are told this nonsense in your own country, the country your fathers and forefathers defended and died for? The victimized ethnic Amharas were beaten, violently dragged off their homes and forced to pay for the trucks that packed them inhumanely, transported them out of the Benishangul Gumuz state, and dump them at the edge of another ethnic homeland without anything to help them stay even for a day. The government has not even denied or confirmed reports that one truck loaded with more than sixty people had overturned at night and fifty nine deportees were killed. We heard that women were giving birth in the wilderness and children died of suffocation. What kind of decent human being would watch this unconscionable action of a government do this to its own people, particularly to the most vulnerable and not get outraged?

While we are at it, it is good to know that this is a part of Ethiopia where even Sudanese nationals related to tribes inside Ethiopia freely move in and out as they wish and depending on the season of their comfort. Note also that the Amharas are not a minority in this ethnic region. Based on the 2007 census, Amharas with 21.8% are the second largest ethnic group among six other ethnic groups inhabiting the area. The largest ethnic group, the Berta, is only slightly larger than the Amhara at 25.4%. Important to note is also that the Amhara are allowed only to elect officials to all levels of government but cannot be elected themselves – democracy Ethiopian style. And lo and behold, this is the area where we are building the huge Nile Dam that we are being asked to contribute money for and that Sudan and Egypt hate like the plague.

Only the Ethiopian government media thinks it is hiding this horrific story. Embassies of Ethiopia’s donor countries in Addis Ababa, who tirelessly tell us how they care for civilization and human rights, have also chosen to look the other way. This barbarism is theirs too as they are underwriting it in so many ways. That may partly explain their silence. The only silver lining I found in this whole sad story is that the local, indigenous tribes and ethnic groups have not joined the officials in this crime. Many, we even heard, were sympathetic to the victims. We all need to be proud of them. They have not lost their senses even as their chiefs lost theirs.

But here is the major point. Many Ethiopians seem to miss the root cause of this crime and get outraged at the chaffs. The root cause of this ethnic cleansing and the factor that created it is embedded in the vision set out for Ethiopia by its rulers, the TPLF/EPRDF, as soon as they took power. The officials of the Benishangul-Gumuz state and those in Guraferda, Bench Maji Zone, in the Southern Ethiopia Regional State, were executing a Grand Vision imbedded in the creation of the ethnic homeland – the Killil. That is why some officials seem to be surprised by our surprise and were giving incoherent responses to some media interviews. In a way, you can argue that the local officials who are doing this crime are also victims of the Grand Vision which they were told was a good official policy.

The Benishangul officials somehow failed to learn from their comrades in the Southern Regional State in Guraferda Bench Maji who as we speak are doing the same thing. Had they done it a few victims at a time, the outcry would have been easily muted. In the Guraferda case, they seem to get smarter after doing a massive eviction when they started out last year. Now they are doing it on “a smaller group of victims at a time” basis. They seem to have learnt that the larger their victims the louder the visibility and outrage. Other than that, the local officials are doing their job prescribed in the Grand Vision.

When Meles Zenawi said, “what is Axum to the Wolayita and the Castles of Gondar to the Oromo”, he may have spilled the beans quite early in his tenure, but he was not saying it out of ignorance or saying anything outside of what he believed. The suggestion was to create a psychology among people that anybody born outside of your ethnic homeland does not belong with you – that Ethiopia’s numerous ethnic groups are mechanically joined units that share very little among one another. The Grand Vision stipulates that the best way to divide and rule Ethiopia, and fight age-old and powerful Ethiopian nationalism that stood on their way, was to reduce it to divided units and inward-looking ethnic nationalism. Of course, this was not an innovation by Meles or TPLF. It was first invented by the Italians who twice invaded Ethiopia and, to their unforgettable surprise, found out that Ethiopian nationalism is more powerful to tear down, and that it is hard to divide Ethiopians along their ethnicity and conquer their country. A version of the current ethnic map is first made by Italian strategists and visionaries, if you can call them that.

Please don’t get me wrong. I am all for the rights of ethnic groups to promote their cultures, languages, etc., and believe that any attempt at democratizing Ethiopia should do its best to do away with ethnic inequality in the country. I also know it is a challenge for any government trying to address it. I have monkeyed with Marxism- Leninism when I was a collage kid. When I began to see and understanding my country fully, I found out that any solution for Ethiopia’s ills can only be based by studying and understanding Ethiopia and its complexities and devising indigenous solutions and not by importing European ideas. I believe we can find our own solutions.

Anybody who thinks that the motive behind the manufacturing of the “killil state” by the TPLF/EPRDF was to empower ethnic groups and help them promote their language, culture etc, and do away with ethnic inequality, was apparently taken for a ride or has not paid attention to the philosophy embedded in the formation of ethnic homelands – the killil. The fact is you don’t necessarily need the ethnic killil to make ethnic groups or so called “nations” and “nationalities” and “peoples” equal. In fact, for ethnic groups to be equal citizens in the country, you don’t necessarily have put them inside a geographic enclave. I am a student of geography. I can make you digital maps of ideal federal states that can be optimally used to help avoid inequality between ethnic groups, fight poverty, and strengthen the Ethiopian union, all at the same time, by crunching hundreds of variables on a computer. It is even possible to avoid the current ridiculous hierarchical classification of ethnic groups into “nations”, “nationalities” and “peoples” which inherently perpetuates inequality.

The current practice only exposes the regime that it does not have even a slight commitment to the rights of ethnic groups. I know many have come to this conclusion by looking at what the regime is doing to the Agnuak in Gambella. According to current practice in Ethiopia, you will lose your citizenship rights, if you are a citizen at all, as soon as you move from your designated ethnic homeland and move to another. Think about it. In the country where I currently live, the son of a Kenyan immigrant is the President of the country. When I think of it, it painfully reminds me of how far in the past my beautiful Ethiopia still lives in. My children and grand children can become presidents or senators in the country that gave me refuge. My relatives who live outside of their ethnic homeland in their own country are not allowed to run and hold even a “kebele” office. It is simply unconscionable that this is happening in the twenty first century. Has anybody wondered why individuals of mixed ethnicity, which probably number more than thirty million, are forced to choose between their father’s and mother’s ethnicity when they are issued ID cards? Isn’t this a crime against an entire people?

So please don’t tell me that the ethnic homeland states of Ethiopia are set up with the good intention of helping ethnic groups achieve equality. Ato Meles Zenawi and those who shared his Marxist- Leninist views very well know that there cannot be a sustainable oppression of one group of people by another without an economic basis. The only economic basis with which the ruling classes in Ethiopia in the past, be it Amahara or a multiethnic class, was able to oppress another group for a long period of time was because of unequal land ownership. But the dergue, Mengistu Hailemariam’s government, has done away with that seventeen years before the TPLF took over. The dergue also targeted Amharas and killed many. In the absence of an economic basis to point to as the basis of oppression, TPLF leaders have to manufacture some tool. The only tool they found in their tool box was linguistic differences and the hatred of the “other”. People were encouraged to hate one another and feel their differences with others more than what they share in common. That was why they dismissed Ethiopia’s long recorded history, the very thing that joins us in pride as Ethiopians as “Teret” (folk tale). I see many countries use even mythologies to help them promote their union. In Ethiopia we are asked to despise even the facts on our record.

It appears that this hate is bearing bigger fruits with time and that is exactly what we are seeing in Benishangul Gumuz and Guraferda now. What we are reaping is what has been sawn, and I am afraid this is not going to be the end of it and may not stop at the Amhara. We are hearing that some of the Benishangul deportees are now allowed to return. Most probably this is due to the need to mute the worldwide outcry and appease some donors but not out of the realization of the wrong they did. The damage is already done. I have no idea how this traumatized people would live a normal and secure life even if they are returned. Some who are very traumatized are even saying they will better die on a street anywhere than return back.

If Ato Meles Zenawi was alive today, I am sure he would pull all his word-craft to justify the crime in Benishangul-Gumuz. He already did justify the deportation from Guraferda in front of the “parliament” last year by saying that the Amhara “settlers” were destroying forests and doing unplanned use of land. He didn’t even care his justification run in violation of the constitution. You see, in civilized communities across the world, the constitution is meant to protect the people from government excesses and the power government holds over people. In Ethiopia it is only quoted when there is a need to protect the government from the people and often to intimidate and throw critics and opponents into the kaliti dungeon.

The whole idea and talk about oppression of nations and nationalities, as they call them, was propagated only to patronize the ethnic elites and facilitate their cooperation in the Bantustanization of Ethiopia and reduce the country to units manageable to rule. That was how you could manufacture surrogate ethnic parties. This was the reason the multiethnic Ethiopian People’s Democratic Movement (EPDM) was forced to become an ethnic Amhara party overnight, though it is obvious that none of it looks like a party created to help Amharas.

Folks, whether you like it or not, this is the vision that will definitely challenge Ethiopia’s survival as a nation in the future. And this is the vision that all of Ethiopia’s officialdom and party cadres are swearing to preserve. Be afraid not only for the Amhara, this poison embedded in the philosophy of our government’s ethnic policy can destroy Ethiopia if left unreformed. This fire will catch more forests. You ain’t seen nothin’ yet, as my American friends would say.

Yes, we are witnessing a painful tragedy in progress and I understand why many of you are crying. I myself did shade some tears when listening to the voices of the unfortunate. But don’t let your tears cloud you from seeing the real reason. There is a need for a huge change in Ethiopia.
Fekadeshewakena@yahoo.com

Tuesday, April 16, 2013

Ethiopian journalist Reeyot Alemu wins 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize

Imprisoned Ethiopian journalist Reeyot Alemu has won the 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize.

Reeyot Alemu, the 31 year-old young Ethiopian heroine of press freedom
Reeyot was recommended by an independent international jury of media professionals in recognition of her “exceptional courage, resistance and commitment to freedom of expression,” UNESCO said in a press release on Tuesday. The Jury took note of Reeyot Alemu’s contribution to numerous and independent publications. She wrote critically about political and social issues, focusing on the root causes of poverty, and gender equality. She worked for several independent media. In 2010 she founded her own publishing house and a monthly magazine called Change, both of which were subsequently closed. Alemu was arrested n June 2011, while working as a regular columnist for Feteh, a national weekly newspaper. She is currently serving a five year sentence in Kality prison.
The UNESCO Guillermo Cano World Press Freedom Prize was created in 1997 by UNESCO’s Executive Board. It is awarded annually during the celebration of World Press Freedom Day on 3 May, which will take place this year in Costa Rica.

ገዢው ፓርቲ ያልጠበቀውን የምር ጫ ውጤት አገኘ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ያለምንም ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ባደረገው ምርጫ ያልጠበቀውን ውጤት ማግኘቱን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ያሰባሰብናቸው መረጃዎች አመለከቱ።

ምንም እንኳ ኢህአዴግ ምርጫውን ከ99 እስከ 100 ፐርሰንት እንደሚያሸንፍ ቢጠበቅም ህዝቡ በምርጫ ካርዶች ላይ ያሰ...ፈረው መልእክት ግን ገዢው ፓርቲ ያልጠበቀውና ያለሰበው ነበር እንደ ታዛቢዎች አገላለጽ።

በአንዳንድ አካባቢዎች የቀበሌ እና የወረዳ ሹሞች የምርጫ ታዛቢዎች እና የድምጽ ቆጣሪዎች የተመለከቱዋቸውን ነገሮች በሚስጢር እንዲጠብቁ ሲያግባቡዋቸው መታየታቸውን ተዛቢዎች ገልጸዋል።

በሰሜን ወሎ ዞን ወልድያ ውስጥ በሚገኝ አንድ የምርጫ ጣቢያ ከገቡት የምርጫ ወረቀቶች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ባዶ ነጭ ወረቀት፣ ሌሎቹ ደግሞ ገዢው ፓርቲ ከስልጣን እንዲወርድ የሚጠይቁ ነበሩ። የሀይማኖት ነጻነታችን ይከበር፣ የታሰሩ መሪዎች ይፈቱ፣ የኑሮ ውድነቱ አስመርሮናል፣ ኢህአዴግ በቃህ ውረድ፣ ለውጥ እንፈልጋለን የሚሉት ጽሁፎች በዚህ የምርጫ ጣቢያ በብዛት ከተላለፉት መልእከቶች መካከል ይጠቀሳሉ እንደ አይን እማኞች አገላለጽ።

በሰሜን ሸዋ አጣየ ከተማ በሚገኝ አንድ ጣቢያ ደግሞ አብዛኛው ህዝብ ምንም ምልክት ሳያደርግ ነጭ ወረቀት ብቻ ማስገባቱን አንድ ታዛቢ ተናግረዋል::

በአዲስ አበባ አንድ የምርጫ ጣቢያ ደግሞ ጥቂት መራጮች ብቻ ድምጽ የሰጡ ሲሆን፣ ሌሎች መራጮች ገዢውን ፓርቲ የሚሰድቡ እና ለውጥን የሚጠይቁ መልእክቶችን ማስገባታቸውን በቦታው የነበረው ታዛቢ ገልጿል::

በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለከተማ ዋልያ ትምህርት ቤት ውስጥ በነበረው ምርጫ ደግሞ አስመራጮች ሰው በማጣታቸውን ቁርስ እንብላ በማለት የምርጫ ጣቢያውን ዘግተው መሄዳቸውን ተከትሎ፣ በግዳጅ ለመምረት እንዲወጡ የተገደዱት ሰዎች፣ ጣቢያው ተዘግቶ በማየታቸው ወደ የቤታቸው የተመለሱ ሲሆን፣ ጉዳዩን ሰምተው የመጡት የኢህአዴግ ካድሬዎች ከአስመራጮች ጋር አምባጋሮ ፈጥረው ነበር።

በአዋሳ ከተማ ደግሞ ምርጫው ከመካሄዱ ከአንድ ቀን በፊት የኢህአዴግ ካድሬዎች ቤት ለቤት እየዞሩ የምርጫ ካርድ ያካሂዱ ነበር። በጎንደር ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ እና አደባባይ ኢየሱስ ባሉ የምርጫ ጣቢያዎች እስከ ሐሙስ ሚያዚያ 3 ቀን 2005ዓ.ም. ድረስ የመራጮች ካርድ ሲሰጥ መዋሉን ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዛሬ ባወጣው ዘገባ አመልክቷል።

ምርጫ ቦርድ በመላው ሃገሪቱ በሚገኙ 954 ወረዳዎች ፣ በተዘጋጁ 44 ሺ 509 የምርጫ ጣቢያዎች ፥ 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን እጩዎችም ለውድድር ቀርበው 90 በመቶው ድምጹን መስጠቱን ገልጿል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና ህብረተሰቡ በምርጫው ያሳየው ተሳትፎ የጎላ እንደነበር ገልጸው ተሳትፎው ህዝቡ ስለምርጫና ስለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ያለው ግንዛቤ ከፍተኛ እንደሆነ ያሳየበት ነበር ብለዋል።

በአንዳንድ አካባቢዎች የወጡ የምርጫ ውጤቶች እንደሚያሳዩት ኢህአዴግ ከ99 እስከ 100 በመቶ አሸንፎአል። በዚህ ምርጫ ገዢው ፓርቲ በ2002 ዓም ይዞት የነበረውን የ99 ነጥብ ስድስት በመቶ ውጤት ረከርድ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ የተገኘውን ሪከርድ ሁሉ የሚያሻሽልና ለዘመናትም ሳይሰበር እንደሚቆይ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።



 



የእርዳታ ድርጅቶች በዝቅተኛው የኦሞ ሸለቆ የደረሰውን የህዝብ መፈናቀል ከቁም ነገር አለመቁጠራቸውን አንድ ድርጅት አስታወቀ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል ለኢሳት በላከው ዘገባ በኦሞ ሸለቆ ላይ የሚገነባው ግልገል ጊቤ 3 እና ለስኳር እርሻ በሚል የሚካሄደው የመሬት ወረራ በአካባቢው ህዝብ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ቢያስከትልም፣ መንግስትን በገንዘብ የሚደጉሙት ለጋሽ አገራት ለችግሩ ተገቢውን ትኩረት አልሰጡትም። በቦዲ. ክዌጎ እና ሙርሲ ህዝቦች ኩራዝ እየተባለ ለሚጠራው የስኳር ፕሮጀክት መሬቱ ይፈለጋል በሚል ከቦታቸው እንዲፈናቀሉ ተደርጓል። ነዋሪዎቹ አብዛኛውን ከብቶቻቸውን በመሸጥ የተወሰኑ ከብቶችን ብቻ እንዲይዙ መመሪያ የተላለፈላቸው መሆኑንም ድርጅቱ ገልጿል።

... ከዚሁ የስኳር ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ከ200 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ሊታረም በማይችል አደጋ ውስጥ መውደቃቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

አሜሪካ እና እንግሊዝ ለኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ እርዳታ የሚሰጡ አገሮች ቢሆኑም፣ በዚህ በኩል ምንም እርምጃ አለመውሰዳቸውን ድርጅቱ አመልክቷል።

የእርዳታ ድርጅቶች በዝቅተኛው የኦሞ ሸለቆ የደረሰውን የህዝብ መፈናቀል ከቁም ነገር አለመቁጠራቸውን አንድ ድርጅት አስታወቀ
ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል ለኢሳት በላከው ዘገባ በኦሞ ሸለቆ ላይ የሚገነባው ግልገል ጊቤ 3 እና ለስኳር እርሻ በሚል የሚካሄደው የመሬት ወረራ በአካባቢው ህዝብ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ቢያስከትልም፣ መንግስትን በገንዘብ የሚደጉሙት ለጋሽ አገራት ለችግሩ ተገቢውን ትኩረት አልሰጡትም። በቦዲ. ክዌጎ እና ሙርሲ ህዝቦች ኩራዝ እየተባለ ለሚጠራው የስኳር ፕሮጀክት መሬቱ ይፈለጋል በሚል ከቦታቸው እንዲፈናቀሉ ተደርጓል። ነዋሪዎቹ አብዛኛውን ከብቶቻቸውን በመሸጥ የተወሰኑ ከብቶችን ብቻ እንዲይዙ መመሪያ የተላለፈላቸው መሆኑንም ድርጅቱ ገልጿል።

ከዚሁ የስኳር ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ ከ200 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ሊታረም በማይችል አደጋ ውስጥ መውደቃቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

አሜሪካ እና እንግሊዝ ለኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ እርዳታ የሚሰጡ አገሮች ቢሆኑም፣ በዚህ በኩል ምንም እርምጃ አለመውሰዳቸውን ድርጅቱ አመልክቷል። 

Monday, April 15, 2013

Protesters disrupted Woyanne attempt to sell Nile bond in Houston – (video, photo)

Elias Kifle | April 15th, 2013
An attempt by Woyanne ambassador Girma Biru to sell Nile bond was disrupted by freedom-loving Ethiopians carrying and chanting slogans: Freedom! Stop Ethnic Cleansing! Stop Genocide!

Many of the protesters entered the meeting hall and shouted: ‘Freedom!’ ‘Freedom!’ – a slogan that sends shivers through Woyanne spine.

The Woyanne junta and its embassy in Washington DC are selling bonds in the United States in violation of the Securities and Exchange Commission’s (SEC) rules, according to a recent statement by the Ethiopian National Transitional Council (ENTC). The embassy is not licensed to sell stocks and bonds in the U.S.

See a photo and video of the Houston protest below


ኢህአዴግ ብቻውን የሮጠበት ምርጫ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንዳች አይፈይድም!!

ፍኖተ ነፃነት ሚያዝያ 6 ቀን 2005 ዓ.ም

ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርአት መገለጫ ቢሆንም ምርጫን ያካሄደ መንግስት ሁሉ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ገንብቷል ለማለት አያስችልም፡፡ በተለያዩ የአለም ክፍሎች የሚገኙ  አምባገነን   መንግስታት እንደሚያደርጉት ሁሉ ኢህአዴግም ስልጣን ከያዘበት ወቅት አንስቶ በህዝብ ይሁንታን ያላገኙ፣ በምርጫ ስም የተደረጉ ድራማዎችን አካሂዷል፤ እስከአሁን ግን ዴሞክራሲያዊ ስርአት አልገነባም፡፡

ለምርጫ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን ሳያሟሉና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እኩል የመወዳደሪያ ሜዳ ሳይሰጡ “ነፃ ምርጫ” አካሄድን የሚሉት የኢህአዴግ ባለስልጣናትና ተላላኪያቸው የሆነው ምርጫ አስፈፃሚው ምርጫ ቦርድ ቆም ብለው ሊያስቡት የሚገባው አንድ ቁም ነገር አለ እሱም የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫ ስም የበሚደረጉ ድራማዎች መሰላቸቱን ነው፡፡

ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንዲገነባና ኢትዮጵያውያን በነፃነት እንዲኖሩ እንደማይፈልግ ላለፉት 21 አመታት በተግባር አሳይቷል፡፡ ገዢው ፓርቲ በአምባገነናዊ እርምጃ ተፎካካሪዎቹን በማዳከም ብሎም በማጥፋት ጎልቶ ለመውጣት ችሏል፡፡
ለዚህ ያበቃው ዋንኛው ዘዴው የመንግስትነትና የፓርቲነትን ድንበር በማጥፋት ከህዝብ የሚሰበሰብን ግብርንና በብድር የሚገኘውን የመንግስት ሀብት ለፓርቲ ስራ ማዋሉ ነው፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን የሀገሪቱ ህግ ከሚፈቅደው ውጪ በህገወጥ መንገድ ግዙፍ የንግድ ተቋማትን በማቋቋም በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ማንቀሳቀሱ ነው፡፡

ኢህአዴግ የመንግስትን መዋቅር ተጠቅሞ በግዳጅ አባላትን ከመመልመል ባለፈ የምርጫ ወቅት ሲደርስ ይሄንኑ የመንግስት መዋቅር ተጠቅሞ ህገወጥ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡ ዛሬ በተጀመረውና በመጪው ሳምንትም በሚደረገው የአካባቢና የከተማ አስተዳደሮች ምርጫም ኢህአዴግ የተለመደውን ድራማ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

የአሁኑ ድርጊቱ አስገራሚ እንዲሆን ያደረገው የተለመደው ህገወጥ ድርጊቱን ብቻውን እየተወዳደረም መድገሙ ነው፡፡ ለጋዜጣችን የደረሱ መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ኢህአዴግ በአሁኑ ምርጫም ህገወጥና አሳፋሪ በሆነ መንገድ በመንግስት መዋቅሮች በተፃፈ ደብዳቤ ከባለሀብቶችና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በግዳጅ ገንዘብ ሰብስቧል፣ የምርጫ ቅስቀሳ በማይፈቀድባቸው ቦታዎች(በትምህርት ቤቶችና በእምነት ተቋማት) ቅስቀሳ አካሂዷል፣ የመንግስት ንብረት በሆኑ ተሸከርካሪዎችና ቁሳቁሶች ቅስቀሳ አድርጓል፣ የመራጮች ምዝገባ ከተጠናቀቀ በኋላ በካድሬዎች አማካኝነት የምርጫ ካርድ አድሏል፡፡

እነዚህ ህገ ወጥ ተግባራት መፈፀማቸው ምርጫውንም ህገወጥ እንደሚያደርገው ግልፅ ነው፡፡ አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከላይ የተዘረዘሩት ህገወጥ ድርጊቶች እንደሚፈፀሙ አስቀድመው በመረዳታቸውና ለውድድር የሚያመቹ ሁኔታዎች ባለመኖራቸው ዛሬ በተጀመረውና በመጪው ሳምንትም በሚደረገው የአካባቢና የከተማ አስተዳደር ምርጫ ራሳቸውን አግልለዋል፡፡

ፓርቲዎቹ ከምርጫ እንዲወጡ ያስገደዳቸው መሰረታዊ ምክኒያት ኢህአዴግም ሆነ ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ነፃ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ሜዳ አለማመቻቸታቸው ነው፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግም ሆነ ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ከጥፋት ጉዟቸው በመመለስና የተቃዋሚ ፓርቲዎች ያቀረቧቸውን ህጋዊ ጥያቄዎች በመመለስ ምርጫው እንዲደገም ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይሄን ሳያደርጉ ከመቀጠሉ ግን ለገዢው ፓርቲም ሆነ ለጀሌዎቹ መዘዙ ከፋ እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡

Abebe Gellaw: The journalist who silenced the tyrant

by Hilina Taye
There is no doubt that 2012 was one of the most memorable years in our history. We witnessed high dramas, anAbebe Gellaw Ethiopian Man of the Year. unforgettable protest, a tyrant’s global hide-and-seek game, the elite’s wailing and cries, a mass hysteria, a dictator’s funeral in par with North Korea, the coronation of a puppet…. All these happened from mid to the end of the year.
Thousands of listeners and viewers of the Ethiopian Satellite Television and Radio residing across the world have cast their votes for the honor, “Ethiopian Man of the Year in 2012,” to select the man that had a noticeable and significant impact in the year.

Over 20 prominent Ethiopians were nominated. Yenesew Genre, the man who self-immolated himself calling for freedom, artist and activist Tamagn Beyene, jailed journalists Eskinder Nega, Reeyot Alemu, and Wubishet Taye, Ethiopian Muslim movement leader Ustaz Abubaker Ahmed, Dr. Berhanu Nega, Andualem Arega, Prof. Mesfin Woldemariam, pop sensation Teddy Afro…and even the late tyrant Meles Zenawi.

When the results of the votes were revealed, one man stood out tall among the crowd. Forty-eight percent of the votes went to the man who generated the most significant buzz and impact in the year by writing the last chapter of Meles Zenwi’s fall and demise. Journalist and press freedom activist Abebe Gellaw was selected ESAT’s audience and viewers’ Ethiopian Man of the Year.

I find this a fitting tribute to a man who took a great risk at the G8 Food Security Symposium on May 18, 2012. When Meles Zenawi was in the middle of his insipid lecture in front of world leaders, distinguished scholars and corporate leaders, Abebe stood up and told Zenawi the bitter truth he tried to avoid in his 21-year long misrule. It was a shock therapy to the arrogant tyrant that shattered and broke the tyrant in front of world leaders.

At the G8 summit what broke Meles was not Abebe thunderous voice that shrank the tyrant, but the toxic truth he spoke loudly for the world to hear. Interrupting Zenawi in the middle of his lecture of lies, the powerful words that became the highlight of the “G8 food security” meeting carried the weightiest messages that overshadowed even the speeches of U.S. President Barack Obama and Secretary of State Hillary Clinton, who delivered the opening and closing speeches respectively.
“Meles Zenawi is a dictator! Meles Zenawi is dictator! Free Eskinder Nega and political prisoners! You are a dictator! Stop committing crimes against humanity! Don’t talk about food without freedom! We need freedom more than food! We need freedom! Freedom! Freedom! Freedom! Meles Zenawi is a dictator! Meles Zenawi is a dictator! Free Eskinder Nega and all political prisoners!” No one could stop the message.

These words will remain valid until Ethiopia is free from dictatorship, injustice, abuse of power and misrule. For me and millions of Ethiopians across the word, those words represented us at the highest level. They represent our aspirations, interests and dreams. They will be etched in our mind as long as we remain oppressed.

Journalist Abebe Gellaw deserves the honor. A true journalist is not always afraid to take risks for the sake of speaking out truth to power. The words that irreparable broke and silenced Meles Zenawi have uplifted us and injected inspiration in our struggle for freedom.
Award winning journalist Abebe Gellaw has already collected a few awards and recognition He was one the 2011 recipients of Human Rights Watch Hellman/Hammett press freedom award, he was named a Young Global Leader (YGL) by the World Economic Forum in 2010. Former John S. Knight Journalism Fellow at Stanford University and Yahoo International Fellow in 2009, journalist Abebe Gellaw has clearly and steadily demonstrated that commitment to make a difference will eventually pay off. But no honor is as good as those that are closer to home. That is why such an honor from ordinary men and women the most coveted.

I congratulate journalist Abebe Gellaw for being selected man of the people. As much as you lifted up our spirit, Ethiopians have unequivocally spoken that they do not forget their heroes and heroines that fight for freedom. This coveted honor is not just for you but for all those who take risks for the sake of freedom. Ethiopia and Ethiopians will never forget the history you have made.

Abebe will be remembered in history as the journalist who silenced and broke Meles Zenawi, who went to his grave humbled and humiliated. It is an ironic miracle that the man who silenced and broke a nation for 21 years was permanently silenced and broken in less than a minute. It is for this reason why Ethiopians have chosen the man responsible for such an audacious act at a meeting of the great powers.

Dictators and oppressors should take a serious note that the day of judgment is always around the corner. No amount of armory can protect tyrants from harsh judgments as this case attests. Encouraged by our Godsend victory, we should finish off the ruthless TPLF tyranny and oppression that has taken away our freedom and dignity.
Thank you, Abebe Gellaw! You spoke for me and millions of Ethiopians. You are a true voice for the voiceless!
We shall prevail! Freedom! Freedom! Freedom!

በብሄር ከፍፈሎ መግዛት የዛገ ፖሊሲ ነዉ! ግንቦት 7

Ginbot 7 weekly editorialበሀገራችን ኢትዮጵያ የዜጎች የመዘዋወር፣ ንብረትን የማፍራት፣ የመኖር፣ የመናገር፣ የመምረጥ እና የመመረጥ መብቶች የሚወሰነው በጥቂት የህወሃትና ጀሌ ባለስልጣኖች መልካም ፈቃድ እንጅ በመሰረታዊ የሰው ልጆች መብት ድንጋጌ አይደለም።

በሩዋንዳ የተፈጸመው የሰውልጅን ዘር የማጥፋት ድርጊት፣ በሀገራችንም ኢትዮጵያ በህወሃት ኢህአዴግ አማካኝነት እየታየ ነው። ዜጎች በማንነነታቸው ከየት አካባቢ/ ብሄር/ ዘር ማንዘር ነው የመጣኸው/ሽው? እዚህ ለመኖር፣ ለመስራት፣ ንብረት ለማፍራትና ለመሳሰሉት የመኖሪያ ፈቃድ አለህ/ሽ ወይ? በሚል ብሄርን ከፋፍሎ መለያ በመስጠት ተከባብሮ የኖረን ህዝብ በትውልድ ሀገሩ እርስ በርሱ ለማጋጨት እየተደረገ ያለው የዛገ የፖለቲካ ፖሊሲ የሀገራችንን ህልውና እየተፈታተነ ነው።

በብሔር ብሔረሰብ ክፍፍል ላይ የተመሰረተ ዘርን በማጥፋት ፖለቲካ የተጠመዱት ወያኔዎች፣ እንደ ሰደድ እሳት በአገራችን ዜጎች ላይ ያላቸውን ጥላቻ ከወዲያ ወዲህ እየሄዱ ያሳዩናል። በተለይም በአማራው የተጀመረው የበቀል ርምጃ ቀጥሎና ተባብሶ የጥፋት በትራቸው የገረፋቸው የኦጋዴን፤ የጋምቤላ፤ የደቡብ ክልል፤ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የዋልድባ አባቶች የቅርብ ግዜ በደሎች ሳይረሱ ከበደል ላይ በደል፣ ከጩኸት ላይ ጩኸት እየጨመረ በማን አለብኝነት የጀመረውን ዘርን የማጥፋት አባዜ ቀጥሎበታል።

የዜጎችን ሰዋዊ መብት ወያኔ በጠበንጃ ሃይል ጉልበት በመተማመን ንብረትን ቀምቶ፤ ነፍሰጡርንና አራስን አፈናቅሎ፣ ህጻናትን ሜዳ ላይ በትኖ ማባረር፣ የድብደባና የግድያ ወንጀሎች በአማራው ሕዝብ ላይ መፈጸሙ አዲስ ያልሆነና ከበፊቱም የነበረውን የወያኔን የከፋፍለህ ግዛ የዛገ ፖሊሲ ተግባራዊ እያደረጉት እንደሆነ ያሳየ ምልክት ነው። ይህ ዓይነቱ ዘግናኝ ወንጀል በተለያዩ ጊዜያትና አካባቢዎች በተለይም በኦጋዴን፣ በአኝዋክ፣ በኦሮሞ፣ በደቡብ፣ በአፋር፣ በሙርሲ እና በሌሎችም የማህበረሰባችን ክፍል ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ተፈጽሟል። አሁንም እየተፈጸመ ነው።

ህወሃት/ኢህአዴግ ይህንን የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚፈጽመበት ዋናው ምክንያት የአንድን ዘር የፓለቲካ፣ የኤኮኖሚና ወታደራዊ የበላይነቱን ለማስጠበቅ ስለሆነ፤ ለዚህ እኩይ ዓላማው መሳካት እንቅፋት ናቸው ብሎ በሚገምታቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ ወደፊትም ተመሳሳይ እርምጃ ከመፈጸም እንደማይቆጠብ እየነገረን ነው።
ይሁን እንጅ ወያኔና አበሮቹ ይህ ዘርን የማጥራት (Ethinc Cleansing) ወንጀል ሲፈጽሙ በየትኛውም ግዜና ዘመን ከተጠያቂነት ወይም በወንጀል ከመፈለግ እንደማይድኑ የተረዱ አልመሰለንም።

የወያኔን የዘር ማጥራት ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚቃወመዉ እና በተለይም አማራዉ ከትውልድ ቀዪው በግዳጅ ተባሮ ለጎዳና ተዳዳሪነት ሲዳረግ የተመለከተ የአካባቢዉ ነዋሪ ህዝብ በፍጹም ወያኔን ያልደገፈና ያልተባበረ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ማፈናቀሉን ተቃዉሞ ተፈናቃዮቹን እንባ እያፈሰሰ፣ ለስደት ጉዟቸው ይሆን ዘንድ ራሱ አማራው አርሶና ቆፍሮ እሸት ካፈራበት ማእድ ወይም የዛሬ የበይ ተመልካች ከሆነበት ማሳ ስንቅ እየቋጠረ ነበር የሸኛቸው።

ለብዙ አመታት አብረዉ ከመኖራቸዉ የተነሳ የአብሮ መኖር ኢትዮጵያዊነት መንፈስ የገነቡና በጋብቻና በማህበራዊ ኑሮ የተሳሰሩ ዜጎች በወያኔ ፖሊሲ ምክንያት ሳይፈልጉ ሲለያዩ ማየት ምን ያህል አሳዛኝ መሆንን የኢትዮጵያ ህዝብ ይረዳል።
በሌሎች አለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩበት የስደት ሀገር የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት በፍርድ ቤት እና በተለያዩ ሚዲያዎች የመኖር መብታቸው ይከበር ዘንድ ሲከራከሩ፤ እኒህ ምስኪን የሀገራችን ዜጎች ግን በትውልድ ሀገራቸው፣ መንደራቸው የመኖሪያ ፈቃድ ተነፍጓቸው፣ ይህንንም እንዳይጠይቁ ሆነው ይባረራሉ።

ታዲያ ይህንና ሌሎች በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደሎች በጋራ ሆነን ለመታገል እንዲሁም ለአለም ድምጻችን ለማሰማት ኢትዮጵያዉያን ለብዙ ግዜ በትላልቆቹ የአገራችን ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም መያዝ አቅቶን ብዙ ዘመን ቆይተናል:: አሁን ግን ሌላ ቢቀር ከምን ግዜም በተሻለ ሁኔታ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች በኢትዮጵያ አንድነትና በዚህ አንድነት ዉስጥ መመስረት ሳለለበት የዲሞክረሲ ስርአት የጋራ አመካከት መጥቷል።

ይህንን ኢትዮጵያዊ አንድነት የጋራ ትግልና የዜጎችን ሁለንተናዊ መብት የማስጠበቅ የነጻነት ትግልን ትብብር እውን እንዲሆን ባለፈው ግዜ በከማል ገልቹ የሚመራዉ የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር ከሁለት አመት በፊት የወሰደዉ የአቋም ለዉጥ እና በቅርቡ ደግሞ በኦነግ ታሪክ ዉስጥ ከፍተኛ ቦታ የነበራቸዉ ሰዎች የወሰዱት ተመሳሳይ አቋም የሚያሳየዉ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዉያን በብሄር ከፋፍለህ ቅጣዉ ፖሊሲ ከኢትዮጵያ መወገድ እንዳለበት እና በሁሉም ወገናችን የሚደርሰው በደል ሰቆቃና ስደት የሁሉም ፖለቲካ ድርጅቶች ጉዳይ መሆኑንና በጋራ ሆነን የዛገን የወያኔን የዘር ማጥራት ፖሊሲ የምናስቆበት፣ ለአንዴ ለመጨረሻ ግዜ ታግለን የምናስወግድበት ሰአት ላይ ነን።

በተጨማሪ ወያኔ አገራችንን በብሄር መነጽር ብቻ የሚመለከትበትን መንገድና የሚሸርበዉ ሴራ በብሄር የተደራጁ ድርጅቶችንም እያንገሸገሻቸዉ መምጣቱን፣ ወቅቱ የሚጠይቀውን ወያኔን የማስወገድ እና ኢትዮጵያን የማዳን የትግል ደወል ጥሪ ላይ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው።

ስለሆነም ግንቦት 7 ለፍትህ፣ ለዴሞክራሲና ነጻነት ንቅናቄ በህዝባችን እየደረሰ ያለውን መፈናቀልና እልቂት ለማስቆም የሚያደርገውን ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል። የዲሞክራሲ ሃይላት ድርጅቶችም ሆነ የሀገራችን ወጣቶች፤ የአማራውና የተቀረው ህዝባችን ጮኸትና ዋይታ በደልና ሰቆቃ በሁሉም የሀገራችን ህዝቦች እየደረሰ ያለ ጥቃት ነውና ለጥሪያቸው የማያዳግም መልስ ለመስጠት ትግሉን ትቀላቀሉ ዘንድ ጥሪያችን ነው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Sunday, April 14, 2013

“አማራንና አማርኛን ማጥፋት የህወሃት ፕሮግራም ነው”

evicted

አማርኛ ተናጋሪዎችን የማመናመን፣ የማደህየት፣ የማራቆትና ክልላቸውን እያሳነሱ የማጥፋት እቅድ በህወሃት መርሃግብር ውስጥ የተካተተ ዋና ተግባር እንደሆነ ተገለጸ። አማርኛ ቋንቋንም ማሽመድመድ የዚሁ እቅድ አካል መሆኑ ተዘግቧል።
 
አቶ ገ/መድህን አርአያ ከኢሳት ሬዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ በህወሃት ፕሮግራም ገጽ 18 አካባቢ “አማራ የትግራይና የኤርትራ ህዝብ ጠላት እንደሆነ ተመልክቷል” ብለዋል፡፡ አያይዘውም አማራ ማጥፋት የቅስቀሳው ዋና መሳሪያ ቢሆንም የትግራይ ህዝብ አልተቀበለም ብለዋል። ቅስቀሳውን አንቀበልም ያሉ “የትግራይ ሸዋ” ተብለው መገደላቸውን ይፋ አድርገዋል።
 
በተለይ የድርጊቱ ዋና አስተባባሪ በማለት የጠቀሷቸው አቶ መለስ ዜናዊ፣ አቶ ስብሃት፣ አቶ ስዩም መስፍን፣ አቶ አባይ ጸሐዬን የጠቀሱት አቶ ገ/መድህን፣ በ1972 በሰሜን ጎንደር የዘር ማጥፋት ወንጀል መፈጸሙን አጋልጠዋል። በወቅቱ የተካሄደው ጭፍጨፋ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደሆነም አመልክተዋል። “በሰላም እጃቸውን የሚሰጡ ወታደሮች እንኳ አማርኛ የሚናገሩ ከሆነ ይረሸኑ ነበር” ሲሉ እነ መለስ ያለቸውን በዘር ላይ የተመሰረተ ቆሻሻ አመለካከት አጋልጠዋል።
 
“ኢትዮጵያ የምትበተነው አማራ ሲጠፋ ነው” በሚለው የነመለስ ሃሳብ መተግበር የጀመረው ህወሃት አዲስ አበባ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑንን ያወሱት አቶ ገ/መድህን፣ ህወሃት ያሰማራቸው ከ350ሺህ በላይ ካድሬዎች ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ አማራዎች በተለያዩ ምክንያቶች እንዲጨፈጨፉ ማድረጋቸውን አመልክተዋል።
 
ብአዴንን “አማራን ለማጥፋት የተፈጠረ፣ ጸረ አማራ ድርጀት” ሲሉ የሰየሙት አቶ ገ/መድህን፣ አመራሮቹ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን በርግጠኛነት ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ የተወከለው “በባንዳ ልጆችና የኤርትራ ተወላጆች ነው” ሲሉም ህዝቡ አደጋ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱን “የባሻ ወልዱ ልጅ ነው” በማለት የትግራይ ህዝብ በባንዳ ኤርትራዊ ልጅ እንደሚመራ ያመለከቱት አቶ ገ/መድህን፤ ብርሀነ ገብረክርስቶስ፣ ቴድሮስ ሃጎስ፣ ቴድሮስ አድሃኖም፣ በማለት በመዘርዘር የባንዳ ልጆች መሆናቸውን ይፋ አድርገዋል።
 
“አማራው የሚኖርበትን መሬት በመውሰድ መሬቱን ያጠቡበታል፣ ከሌላው ክልል በማባረር የሚኖርበትን ክልል ያጠቡታል” ያሉት አቶ ገ/መድህን፣ ይህ የሚደረገው ከመጀመሪያው እንዲጠፋ የተወሰነበትን ህዝብ አጥብቦ በማፈን በችግር ለመግረፍና ለመቆጣጠር ተብሎ እንደሆነ ገልጸዋል።
 
ዘር የማጥራት የህወሃት የቀደመ ድርጅታዊ መዋቅር እንደሆነ በማመልከት መለስን የጠቀሱት አቶ ገ/መድህን፣ “አማራውን ዝም ካልነው አያስቀምጠንም” የሚለው የመለስ መፈክር አካል የሆነው የቤኒሻንጉል ክልል ርምጃ የህወሃት ቤት ስራ እንደሆነ አረጋግጠዋል። አማራውን ፋታ ማሳጣት፣ ማንገላታት፣ ስነልቦናውን መግፈፍ ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ የያዘው እቅድ ስለሆነ ወደፊትም እንደሚቀጥል አቶ ገ/መድህን ተናግረዋል።
 
“ሞት መፍራት አያስፈልግም። የተቀደሰ ሞት መሞት ክብር ነው” ሲሉ በቃለ ምልልሳቸው መጨረሻ የተናገሩት የቀድሞው የህወሃት የፋይናንስ ሃላፊ ህዝቡ ተባብሮ ህወሃትን ማስወገድ ካልቻለ ማፈናቀሉና መሰደዱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቀዋል።
 
 ጎልጉል ድረ ገጽ

እነ ማን ነበሩ? አሁንስ ማን ናቸው?

ገብረመድህን አርአያ
ፐርዝ፤ አውስትራሊያ

ይህ ጽሑፍ ትኩረት የሚሰጠው በትግል በረሃ በነበርንበት ወቅት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት.) በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖቶች ላይ ሲከተል የነበረውን አቋሙን
Gebremedhin Araya former TPLF
አቶ ገብረመድህን እርአያ
ተቀብሮ ከነበረበት ጉድጓድ አውጥቼ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እነማን ናቸው የሚለውን ታሪካቸውን እና የተፈጸመውን ጸረ-እምነት ግፍ በአጭሩ ለማሳወቅ ነው።

ህ.ወ.ሓ.ት. ገና ሲፈጠርና ተ.ሓ.ህ.ት. ተብሎ እንደተመሰረተ ሙልጭ ያለ ጸረ-ዲሞክራሲ ድርጅት ነው። በጸረ-ኢትዮጵያነትና በጸረ- ሕዝብነት የተሰማራ ቅጥረኛ ድርጅት መሆኑን ብዙ ጊዜ በጽሑፍና በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ለኢትዮጵያ ህዝብ ተናግሬአለሁ። የአሁኑ ጽሑፌ ህ.ወ.ሓ.ት. በሃይማኖት ላይ ሲከተለው የነበረውን ፖሊሲ ገና ከመጀመሪያ ትግሉ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ የነበረውን ጸረ- ሃይማኖት ተግባራቱን የኢትዮጵያ ሕዝብ በግልጽ አውቆታል እኔ ደግሞ የራሴን ልበል።

በ1969 መጀመሪያ ጀምሮ “ወይን” በሚለው የድርጅቱ ልሳን መጽሔት ላይ በተደጋጋሚ “የክርስትና ሃይማኖትና አማራው” በሚል ርእስ ተጽፎ የሚወጣው ጽሑፍ፣ “የክርስትና ሃይማኖት የአማራው ዋና መሳሪያና የግዛቱን ህልውና ማስጠበቂያ ነው፣ በመሆኑም የትግላችን ጠላት አማራውና መሳሪያው የተዋህዶ ክርስትና ስለሆኑ አብረው እንዲጠፉ ማድረግ አለብን” እያለ ያትት ነበር። ይህንን መጽሔት በሰፊው ለታጋዩና ለአባላቱ በማሰራጨት ሰፊ ቅስቀሳ አካሂዶበታል። በነሐሴ 1969 “ወይን” መጽሔት አማርኛ ቋንቋም አብሮ መጥፋት እንዳለበት ሃተታ ይዞ ወጥቷል።

“ወይን” የምትለውን መጽሔት የሚያዘጋጁት ከፍተኛ የአመራር አባላት በፕሮፓጋንዳ ቢሮ ሆነው ለዚሁ ተግባር የተዘጋጁ ጽሑፎችን በስፋት የሚያሰራጩት፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየና መለስ ዜናዊ ነበሩ። እነዚህ ሶስቱ የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር አባላት እብዶችና በጸረ- ሃይማኖት፣ ጸረ-አማራ ባህሪያቸውና አቋማቸው በሰላማዊው ህብረተሰብና ታግዩም ጭምር በግልጽ የሚታወቁ ናቸው።

የሕዝብ ግንኙነት ቢሮ የሚመራውም በነዚህ ሶስት እብድ አመራሮች ነበር። ከዚህ በመነሳት መስከረም 1970 በጸረ-ሃይማኖት፣ በተለይም በተዋህዶ ኦርቶዶክስ ላይ ቅስቀሳውን በስፋት ለማካሄድ በማሰብ፣ ሕዝብ ያሳምናሉ ተብለው የሚታመንባቸውን ታጋዮች መርጠው እገላ ወረዳ መሬቶ ተብላ በምትጠራ ቁሽት ውስጥ ተሰብስበው ቦታ ተዘጋጅቶ ከላይ በተጠቀሱት ሶስቱ አመራር ሴሚናር ተዘጋጀ። በሴሚናሩ ላይ የሚከተሉት ታጋዮች ተካፍለው ነበር፤

1. መርሳ ረዳ 9. ጉእሽ ጓእዳን
2. ሃለቃ ፀጋይ በርሄ 10. ቢተው በላይ
3. ቴዎድሮስ ሃጎስ 11. ሃድሽ ገዛኸኝ
4. አባይ ወልዱ 12. ሮማን ገ/ሥላሴ
5. ሃዳስ ዓለሙ 13. አፈራ ተክለሃይማኖት
6. ኃ/ሥላሴ ገ/ኪዳን 14. ወልደገብርኤል ሞደርን
7. ሃሪያ ሰባጋድስ 15. አዲስዓለም ባሌማ
8. ቅዱሳን ነጋ
ከላይ የተጠቀሱት ታጋዮች በተካሄደው ሴሚናር በጸረ-ክርስትና እና በጸረ-እስልምና አስተሳሰብ በሶስት ቀን ውስጥ ተጠምቀው ጨረሱ። እንደጨርሱም በሶስት ሪጅን ተመደቡ፤ አመዳደባቸውም፤ ሪጅን 1 መርሳ ረዳ፤ ሪጅን 2 ሃለቃ ጸጋይ በርሄ፤ ሪጅን 3 አዲስዓለም ባሌማ በሃላፊነት እንዲመሩት ተመረጡ። ቀሪዎቹም በእነዚህ የበላይ ተጠሪዎች ስር ተደለደሉ።
ሪጅን 1 ሪጅን 2 ሪጅን 3

መርሳ ረዳ ተጠሪ ጸጋይ በርሄ ተጠሪ አዲስዓለም ባሌማ ተጠሪ

1-ጉእሽ ጓእዳድ 1-ቅዱሳን ነጋ 1-ቴዎድሮስ ሃጎስ
2-አባይ ወልዱ 2-ሃዳስ ዓለሙ 2-ወ/ገብርኤል ሞደርን
3-ኃ/ሥላሴ ገ/ኪዳን 3-ቢተው በላይ 3-አፈራ ተ/ሃይማኖት
4-ሃርያ ሰባገድል 4-ሃድሽ ገዛኸኝ
5-ሮማን ገብረሥላሴ

በዚህ መልክ ተደራጅተው በየሪጅኑ ተሰማሩ። ድጋፍ ሰጪ የሕዝብ ግንኙነት ካድሬዎችም በየድርጅቱ በስፋት ተሰማሩ። እነዚህም በተጠናከረ ሃይል ጸረ-ክርስትና፣ ጸረ-አማራ፣ ጸረ-እስልምና ቅስቀሳቸውን ቀጠሉበት። በተዋህዶ ክርስትና ላይ ሙሉ ሃይላቸውን በመጠቀም በስፋት ጸረ-ክርስትና ቅስቀሳውን በተከታታይ እሁድና ሌሎች በዓላት እንዳይከበሩና የሥራ ቀን መሆናቸውን በማወጅ በህብረተሰቡ ላይ ካባድ ተጽእኖ አሳደሩበት። ቀሳውስትና ዲያቆናት በማንኛውም በዓላት ቤተ ክርስቲያን ከፍተው ሲቀድሱ ቢገኙ ከባድ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠነቀቁ። አልፎ አልፎ ተቃውሞ ይገጥማቸው ስለነበር በበላይ አመራሩ ለእነ ስብሃት ነጋ ምን እናድርግ እያሉ ሪፖርት ያቀርቡ ነበር። ከአመራሩ የተሰጠው ምላሽ፣ ማንም ያንገራገረ ቄስ፣ ባህታዊ፣ ዲያቆን ወይም ሌላ እዛው ባለበት በሕዝቡ ፊት ግደሉት የሚል መመሪያ ተሰጣቸው። በዚህ መሰረት አድዋ አውራጃ እንዳባጻህማ ወረዳ የሚገኘው እንዳሥላሴ ተብሎ የሚታወቀው ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን መሪ አባ ሃይለሥላሴ የሚባሉ ቄስ፣ “ሃይማኖታችንን አታርክሱት፣ የተቀደሰ ሃይማኖት ነው” ብለው ስላሉ በቦታው የነበረ ጸጋይ በርሄ የሚባል ታጋይ በያዘው አጭር ጓንዴ ተኩሶ ጭንቅላታቸው ላይ በመምታት በሕዝብ ፊት ገደላቸው። ቀሪው ምእመናን ተደናግጦና በርግጎ ተበታተነ። ሃለቃ ጸጋይ በርሄ በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረውን ንብረትና ሃብት ጠራርጎ ወሰደው። በተመሳሳይ፣ ዛና ወረዳ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን መሪ የነበሩት አባ ቄስ አርአያ ከአንድ የ90 ዓመት አዛውንት ባህታዊ ጋር ሆነው፣ “እባካችሁ ሃይማኖታችንን አታርክሱብን” በማለታቸው ከቢተው በላይ ጋር ተደራቢ ሆኖ የሄድው አርከበ እቁባይ ሁለቱን ንጹሃን ዜጎች በሕዝቡ ፊት ገደላቸው። በስብሃት ነጋ፤ አባይ ፀሃየና መለስ ዜናዊ የሚመራው ጸረ-ክርስትና ሃይማኖት ከላይ የተጠቀሱትን 15 ታጋዮች የተግባሩ ፋጻሚዎች በማድረግ በርካታ ቤተ ክርስቲያናትን አቃጥለዋል። ከአድዋ፣ አክሱምና ተምቤን አውራጃዎች ብዙ ቀሳውስትና ባህታውያን እንዲሁም ዲያቆናት ሌሊትና ቀን እየታፈኑ ተውስደው የውሃ ሽታ ሆነው ቀርተዋል።

የእስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ፤ እስልምና ተከታይ ኢትዮጵያውያን ጸሎት ለመድረግ በሚሰበሰቡበት ጊዜ እየጠበቁ ጸረ-እስልምና ሰበካዎችን ለማራመድ በየመንገዱ ቅዱሱን ነብዩ መሃመድን እና ቅዱስ ቁርአንን ማብጠልጠልና ማራከስ በጀመሩበት ወቅት፤ ከሪጅን 1-3 በሚገኘው የእስልምና ተከታይ ሰፊ ተቃውሞ ገጠማቸው። በተለይ በሪጅን 3 አፋሮች የእስልምና ተከታዮች ስለሆኑ ጸረ-ወያኔ ተቃውሞ በማሰማት ለእምነታችን እንሞታለን፤ እንዋደቃለን በማለት ከፍተኛ ተቃውሞ አሰሙ። በሪጅኑ የተመደቡትን የህ.ወ.ሓ.ት. አባላት ተከታትለው በማደን ገደሏቸው። ከተገደሉት መካከል፣ ትእግስት አሰፋ፣ የኋላሸት ገ/መድህን (አላሚን)፣ ፀሃየ አብርሃ ወዘተ ይገኙበታል። የዚህ አይነቱን ተመሳሳይ እጣ በታጋዮች ላይ በተደጋጋሚ አድርሰዋል። የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር ስለሁኔታው ሲጠየቅ እስከ አሁን ድረስ ድርጊቱን በመካድ በጦርነት ሞቱ እያለ ይዋሻል። በጦርነት ሳይሆን ነቢዩ መሃመድን በማንቋሸሻቸውና ቅዱስ ቁርአንን በማቃጠላቸው በአፋር ሕዝብ የተገደሉ ናቸው። ቀሪዎቹ ማለትም አዲስዓለም ባሌማ፣ ቴዎድሮስ ሃጎስና አፈራ ተክለሃይማኖት ጨለማን ተገን በማደግ ሸሽተው በዱር በገደል ሲያመልጡ ተሰባብረውና ገርጥተው ባንድ ወር ጊዜ አጋሜ አውራጃ ሶቦያ ደርሰው ሕይወታቸውን አዳኑ። በዚህ ምክንያት ህ.ወ.ሓ.ት. እስከ 1976 ድረስ አፋር ውስጥ መግባት ስለፈራ እንቅስቃሴውን አቆመ።

በዚህ ወቅት በርካታ ቅዱስ ቁርአን እና መጽሐፍ ቅዱስ በህ.ወ.ሓ.ት. የተዘረፈ ንብረት ማጠራቀሚያ ውስጥ ታጉረው ለእሳት ማቀጣጠያ ይደረጉ እንደነበር በርካታ በጊዜው የነበሩ ታጋዮች የሚናገሩት የነበረ ሃቅ ነው።
የእስልምና ታከታዩ ኢትዮጵያዊ በወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. የተጀመረውን ጸረ-እስልምና እንቅስቃሴ በሶስቱ ሪጅን የሚኖረው አማኝ ከፍተኛ ተቃውሞ በማስነሳት በአንድነት ቆመ። ወይ ወያኔ ይጨርሰን አለበለዚያ እኛ እንጨርሳችኋለን እንጂ በሃይማኖታችን አትገቡብንም በማለት የህ.ወ.ሓ.ትን አመራር ጉሮሮ ያዙት። የወያኔ አመራር በሁኔታው ተደናገጠ። በገጠርም ሆነ በከተማ የሚኖረው ሕዝብ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙት የአመራር አባላት የሆኑት ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊና አባይ ፀሃየ መሆናቸውን በማወቁ እነዚህ ግለሰቦች በፍርሃቻ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ አቆሙ፣ ከተንቀሳቀሱም በታጋይ እየታጀቡ ሆነ። በዚህ ጊዜ ወያኔ በኢ.ዲ.ዩና በኢ.ህ.አ.ፓ. የተወረረበት ወቅት ስለነበረ የአመራሩ የትግል ስሜት መሬት የወረደበት ጊዜ ነበር። ከዚህ በመነሳት ለጸረ-ሃይማኖት ተግባር ለተመደቡት ታጋዮች አስቸኳይ ትእዛዝ በማስተላለፍ ጸረ-እስልምና እንቀቃሴአቸውን እንዲያቆሙ፣ ጸረ-ክርስትና ሃይማኖት ሥራቸውን ግን እንዲቀጥሉበት ታዘዙ። ጸረ- ክርስትናው ቀጠለ። በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት የሚኖሩት የእስልምና ሃይማኖት እህቶቻን እና ወንድሞቻችን ከዛች ቀን ጀምሮ ለወያኔ መታዘዛቸውን አቆሙ። ክርስቲያኑ ወገን የህ.ወ.ሓ.ት. ንብረት አመላላሽ እየሆነ ሲያገለግል የእስልምና ተከታዮች ኢትዮጵያውያን ግን ሳይደፈሩ ተፈርተው ለዓመታት ቆዩ።

የካቲት 1971 የህ.ወ.ሓ.ት. 1ኛው ጉባኤ በተካሄደበት ጊዜ የተመረጠው አመራር ማለትም፤ የድርጅቱ ሊቀ መንበር ስብሃት ነጋ፣ የፕሮፓጋንዳው ሃላፊዎች መለስ ዜናዊን እና አባይ ፀሃየን መረጠ። እነዚህ ሶስቱ ጸረ-ሕዝብ አመራሮች ሃይላቸውን እና ጉልበታቸውን በማጠናከር ድርጅቱ ያወጣውን በርካታ አዳዲስ ፖሊሲ ግንባር ቀደም በማድረግ በሥራ ላይ ማዋል ጀመሩ። እነሱም፣ የተዋቅህዶ ክርስትና ሃይማኖት የአማራው መሳሪያና መገልገያ ስለሆነ፣ እግዚአብሄር የሚባል ነገርም ስለሌለ፣ ከአሁን ጀምረን ከነፃ መሬታችን ጠራርገን ማጥፋት አለብን። ለወደፊትም የሃገራችን የትግራይ መንግሥት ሲቋቋም ሕዝባችን ከማንኛውም አጉል እምነቶች ነፃ የሆነ ሃገር እንመሰርታለን በማለት የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር ወሰነ።
ከላይ የተጠቀሰው እንዳለ ሆኖ፣ በአዲስ ጉልበትና አዲስ ጸረ-ተዋህዶ ክርስትናን ማዳከሚያ ፖሊሲ ተጠናክሮ ወጣ። በተግባር ከተፈጸሙት መካከል፣

1. በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት የሚገኙት አብያተክርስትያናት ያላቸውን ሃብትና ንብረት በሙሉ ለህ.ወ.ሓ.ት. እንዲያስረክቡ ታዘዘ፣
2. ቄሶች ቆባቸውን እና ጥምጥማቸውን አውልቀው በመጣል የህ.ወ.ሓ.ት. “ወየንቲ” (ሚሊሻ ማለት ነው) እንዲሆኑ ተወሰነ፤ በተግባርም ታየ። ቄሶች የህ.ወ.ሓ.ት. ምንሽር፤ ጓንዴ፤ አልቤን እየተሸከሙ የህ.ወ.ሓ.ትን ነፃ መሬት ጠባቂ ሆኑ።
3. በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት የሚገኙ ዲያቆናት ትዳር የመሰረተ ትዳሩን አፍርሶ ከነሚስቱ ወደ ትግል ሜዳ እንዲቀላቀሉ፣ ትዳር የሌለው ደግሞ በቀጥታ ወደ ትግሉ እንዲገባ ተብሎ ተወሰነ። ብዙ ትዳር ፈርሶ በውዴታም በግዴታም የህ.ወ.ሓ.ት. ታጋይ ተደረጉ።
ወላጆች ጧሪ አልባ ሆነው ቀሩ። አብያተ ክርስቲያናት ካለ ቀዳሽና አገልጋይ ክፍት ሆነው ቀሩ። አብያተ ክርስቲያናት በዘራፊው የህ.ወ.ሓ.ት. ማፊያ ቡድን ተዘረፉ። በወያኔ አመራር የተዘረፈው ጥንታዊና ታሪካዊ መጽሐፍት፤ ውድና ብርቅ ጥንታዊ ታሪካዊ ንብርቶች ሲዘረፉ፣ በርካታ የግእዝ የብራና መጽሐፍትና ቅዱሳን መጽሀፍት ተቃጠሉ።

ይህንን ጸረ-ሃይማኖት ድርጊትና የማውደም ሥራ እንዲከናወን በተለያዩ ጊዜያት ትእዛዝና አመራር የሰጡት፤ ስብሃት ነጋ፣ መለስ ዜናዊና አባይ ፀሃየ ነበሩ። በተባባሪነት ተጨማሪ እርዳታ የሚያደርጉት ደግሞ፣ አርከበ እቁባይ፣ ኤርትራዊው ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ አውአሎም ወልዱ፣ ዘርአይ አስገዶም፤ ስየ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን ሳይጠቀሱ የማይታለፉ ናቸው። እነዚህ የአመራር አባላት የነመለስ፣ አባይና ስብሃት ታማኝና አገልጋይ አሽከሮች በመሆን ሕዝበ እስላሙን እና ክርስቲያኑን ሲያቃጥሉ የታዩ ናቸው። ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም በማቃጠል አውድመዋል፡

ይህ በዚህ አይነት እየቀጠለ ባለበት ጉዞ፣ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ በውድም በግድም የለቀቁ ቄሶችና ዲያቆናት የካድሬ ሴሚናር ለሳምንታት ለመስጠት የሚከተሉት “መሪሕ ባእታ” ካድሬዎች ተመረጡ፤

1. ሙሉጌታ ጫልቱ 6. ጎበዛይ ወ/አረጋይ
2. ዘርአይ አስገዶም 7. አባይ ወልዱ
3. መርሳ ረዳ 8. ቅዱሳን ነጋ
4. አክሊሉ ደንበአርቃይ 9. ግደይ በርሄ
5. ገብረኪዳን ደስታ 10. ቢተው በላይ

እነዚህ ካድሬዎች በሪጅን 1 እና 2 በመመደብ በተለያዩ ቦታዎች በመሰማራት ቀሳውስትና ዲያቆናትን ከ1973 መጀመሪያ አንስቶ ለስድስት ወራት በመዘዋወር የማርክሲስም ሌኒኒዝም ትምህርት በማስተማር በክለው ጸረ-ክርስትና ሃይማኖት አደረጓቸው። በሚመረቁበት ጊዜ በእነ ኢያሱ በርሄ የሚመራው የባህል ቡድን በበዓሉ ላይ በመገኘት ቀሳውስቱ እስክስታውን (ስእሲኢት) አወረዱት፣ አምላክን አወገዙት፣ “ክርስትና ሃይማኖት ከአማራው ጋር አብረው ይደመሰሳሉ” እያሉ በየስብሰባው መክፈቻ መፈክራቸው አደረጉት።

4. በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት የሚከተሉት በአዋጅ ታግደው ነበር። በሕዝብ ግንኙነት በኩል ተፈጻሚ እንዲሆኑም ትእዛዝ ተሰጥቶባቸው ነበር፣ እነሱም

4.1 በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት ሠርግ ታገደ
4.2 ተስካር (ተዝካር) እና የሞት ፍትሃት ታገደ
4.3 አዲስ ለሚወለዱ ሕፃናት ክርስትና እና ጥምቀት ታገደ
4.4 በየወሩ በመሰባሰብ ጸበል ፀዲቅ ማድረግ ታገደ
4.5 በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት በየትኛውም ቦታ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በየዓመቱ የሚያካሂዱት በዓላት ታገዱ።
ከላይ የተጠቀሱትን የህ.ወ.ሓ.ት ትእዛዝ የጣሰ እንደ ጸረ-ህ.ወ.ሓ.ት ተቆጥሮ ሃለዋ ወያነ 06 ገብቶ አስፈላጊው እርምጃ ይወሰድበታል። ሃብት ንበርቱ ለህ.ወ.ሓ.ት ገቢ ይደረጋል። የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ታጋዮችም ይህንን ተግባራዊ አደርገውታል።

 ስለሆነም ሕዝብ በሃሰት እየተከሰሰ ሃለዋ ወያነ በመግባት የስንቱ ሕይወት በከንቱ ጠፍቷል። ንብረታቸው ተወርሶ እናትና ልጆቿ ለክፉ መከራ ተጋልጠዋል። አብያተ ክርስቲያናት ገንዘባቸውና ሃብት ንብረታቸው ተዘርፏል። ይህ በ1969 የተጀመረው ድርጊት ህ.ወ.ሓ.ት እስከ መጨረሻው ቀጥሎበት ፖሊሲውን በተግባር አውሎታል።

ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ በ1969 መጀመሪያ ህ.ወ.ሓ.ት እንደ ግንባር ቀደም ፖሊሲው ያደረገው አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው የሚለውን ነበር። ለዚህ ዓለማ ብለው የህ.ወ.ሓ.ት አመራር በፕሮግራሙ (ሕገ ደንቡ) የተጻፈውን ቀዳሚውን ፖሊሲውን በአጭሩ እንመልከት፤

አማራው በትግራይ ሕዝብ ላይ የሚፈጽመውን ተጽእኖ በማጠናከር በትግራይ ሕዝብ ላይ በሚያካሂደው የኢኮኖሚ ብዝበዛ ሕዝባችንን ለድህነት፤ ለረሃብ፤ ለውርደትና መንከራተት ዳርጎታል።

ይህንን ግፍና በደል ጨቋኙ የአማራ ብሄር ሆን ብሎ ፈጽሞታል። በዚህም የተነሳ የትግራይ ሕዝብ በኑሮው እንዲጎሳቆል፤ ለሥራ አጥነት፤ ለሽርሙጥና፤ ለስደት፤ ለለማኝነትና መንከራተት ዳርጎታል። በተጨማሪም የትግራይን ሕዝብ ታሪኩን፣ ቋንቋውን እና ባህሉን እንዲጠፋ አድርጓል። የሶስት ሺህ ዓመታት ታሪካችንን ተነጥቀን የአማራው መመኪያና የግል ታሪኩ አድርጎታል። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ያላት ታሪክ ከንጉሥ ምኒልክ የሚጀምርና እንደሃገር የኖረችውም ከ100 ዓመት አይዘልም። ኢትዮጵያ እንደ ሃገር የተፈጠረችው በአማራው ተስፋፊነት የተነሳ ስለሆነ ከምኒልክ ንግሥና በኋላ ነው።

የአማራው ብሄር የትግራይን ሕዝብ ከአቅሙ በላይ ግብር እንዲከፍል በማድረግና በማስገደድና ጭቆናውን በማራዘም የትግራይን ሕዝብ ከሰብአዊ ፍጡር ውጭ አድርጎታል። የትግራይን ሕዝብ እንደ እንሰሳ በመቁጠር በሚደርስበት ጭካኔ የተሞላ አገዛዝ (ኢሰብአዊነት) ድህነት፣ ረሃብ፣ ውርደትና ስደት እንዲደርስበት አድርጓል። በተጨማሪም የትግራይ ሕዝብ ለረጅም ዘመን ሰብአዊና ፖለቲካዊ መብቱ ተንፍጎ ሲጠላና ሲናቅ እንዲሁም አድልዎ ሲፈጸምበት ቆይቷል። ይህንን በደል ጨቋኟ የአማራ ብሄር ሆን ብላ እንደመንግሥት መመሪያዋ አድርጋ ስትሠራበት ነበር። ከላይ በጥቂቱ የዘረዘርኩት በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም ግጽ 8-14፣ 15-16፤ 18 ላይ ተመልክቷል። በአጠቃላይ ፕሮግራሙ ከመነሻው እስከ መጨረሻው አማራን ይወነጅላል። አሁን ደግሞ ደርግ ቀጥሎበታልም ይላል። የትግራይን ሕዝብ ቂሙን እና ጥላቻውን እያለ ይገልጻል። ጨቋኟ አማራም ሕብረተሰባዊ እርፍትና ስላም አታገኝም ብሎ ይደመድማል። ገጽ 16 ላይ ይመልከቱ። ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚያውቀው በኢትዮጵያ ውስጥ የአማራ መንግሥት የሚባል የለም፣ አልነበረምም። ኢትዮጵያ ብዙ ነገሥታትን አፍርታለች። ነገሥታቱም የሚነግሡት በዘር ሃረጋቸው ነበር። ይህም የቤተ መንግሥቱን መቀመጫ በሃይል ሳይሆን በቅብብሎሽ የሚደረግ ነበር። የአክሱም ቤተ መንግሥት ወደ ላስታ ተዘዋወረ፣ ከዚያም ወደ ሸዋና ጎንደር ሲዘዋወር በነገሥታቱም በሕዝቡም ተቀባይነት እያገኘ ነበር። በመጨረሻም ወንበሩ ሸዋ፣ አዲስ አበባ ላይ ሆነ። አፄ ኃ/ሥላሴም በዚሁ በዳግማዊ ምኒልክ ቤተ መንግሥት ውስጥ ነገሡ። የአፄ ኃ/ሥላሴ መንግሥትም ከኦሮሞ፣ ከትግራይ፣ ከኤርትራ፣ ከአማራ፣ አፋር፣ ጉራጌ ወዘተ ኢትዮጵያውያንን ማእከል ያደረገ ከፍተኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ነበራቸው። ከሚኒስቴር ዲኤታ እስከ መምሪያ ሃላፊዎች ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያቀፈ መንግሥት ነበር።

እንዲያውም ቁልፍ የሆኑትን የሚንስቴር ቦታ ይዘው የነብሩት ትግሬዎች ነበሩ። በሥልጣን ክፍፍሉ አድልዎ አይታይም ነበር። በጤና እና በትምህርት ዋን ተጠቅሚ ትግራይ ነበረች። በዚህም አድልዎ አልታየም። አርመኔያዊ አገዛዝ፣ ኢሰብአዊነት (Dehumanisation) እያለ የህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም የሚለፍፈው እንደዚህ አይነት ተግባር በትግራይ አልታየም። እውነቱን እንነጋገር ከተባለ የአፄ ኃ/ሥላሴ መንግሥት ምርጥ ምርጡን ለትግራይ ይሰጥ የሚል ስርዓት ነበረው። የትግራይ ሕዝብም ንጉሠ ነገሥቱን ከልብ ይወዳል፤ ንጉሡም የትግራይን ሕዝብ ይወዱ ነበር። ደርግ አፄ ኃ/ሥላሴን እንደገደላቸው ባወቀ ጊዜ የትግራይ ሕዝብ ከትንሽ እስከ ትልቁ ደርግን ክፉኛ አውግዞት ነበር። የትግራይ ሕዝብ ከአፄ ኃ/ሥላሴ ሞት በኋላ በኑሮው የተጎሳቆለና ለችግር የተጋለጠ ሕዝብ ሆነ። በደርግ ስርዓትም ቢሆን የትግራይ ሕዝብ ለችግርም ሆነ ለረሃብ ብዙ የተጋለጠ አልነበረም። ደርግ የመሬት አዋጁን በትግራይ ውስጥ ተግባራዊ አላደረገውም። ምክንያቱም የእርሻ መሬቱ አነስተኛ በመሆኑ ነበር። ደርግ በሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ በትግራይ ሕዝብ ላይ የፈጸመው ወንጀል የለም። በኑሮም አልተጎሳቆለም። በቀይ ሽብርም ቢሆን የተጠቃው አማራው ነበር። የትግራይን ሕዝብ ያጠቃ፣ ለድህነት የዳረገ፣ ለስደት፣ ለሸርሙጥና እና ለመንከራተት ያበቃውና ችግርና መከራ ይዞለት የመጣው ህ.ወ.ሓ.ት. ብቻ ነው። የህ.ወ.ሓ.ትን ፕሮግርራምና አፈጻፀሙን ካየን፣ ተግባራዊንቱን ደግሞ እንመልከት።

ወደዚህ ከመግባታችን በፊት ግን መመልከት ያለብን ነጥብ አለ። የአፄ ኃ/ሥለሴ መንግሥት ሃገር አቀፍ የሆነ ስርዓት እንጂ በአማሮች ብቻ የሚመራ መንግሥት አልነበረም። አማራው እንደቀሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ የተለየ ጥቅም ተቀባይ አልነበረም። እውነታው ይህ ሆኖ እያለ ህ.ወ.ሓ.ት. ለምን አማራውን ብቻ በጨቋኝነት፣ በዝባዥነትና በጸረ-ሰውነት ፈረጀው? ህ.ወ.ሓ.ት. በ48 ገጾች ሆን ብሎ አማራውን ለማጥቃት ያሰናዳው ፕሮግራም ወንጀል ነው። ከትግሉ መነሻ ጀምሮ አማራን ለማጥፋት 48 ገጽ ፕሮግራም ያወጣው ህ.ወ.ሓ.ት. ነው። አሁንም በሥልጣን ላይ ሆኖ በአማራው ላይ የዘር ማጥፋት ድርጊት የሚፈጽመው ህ.ወ.ሓ.ት. ነው።

ፕሮግራሙን አርቅቀው እንዲተገበር ያደርጉት እነማን ናቸው? ዝርዝር ስማቸውን እንመልከት፤

1. አረጋዊ በርሄ 8. ተወልደ ወ/ማርያም
2. ስብሃት ነጋ 9. ገብሩ አስራት
3. መለስ ዜናዊ 10. አርከበ እቁባይ
4. አባይ ፀሃየ 11. ጻድቃን ገብረተንሳይ
5. ሥዩም መስፍን 12. ዘርአይ አስገዶም
6. አውአሎም ወልዱ 13. ግደይ ዘርአጽዮን
7. ስየ አብርሃ

ከነዚህ በተጨማሪ ከዚህ አለም በሞት የተለየው አታክለት ቀጸላ፣ በስብሃት ነጋ የተገደለ፤ አስፍሃ ሃገኦስ፣ ታሞ የሞተ፤ ግደይ ዘርአጽዮን ከ1969 ጀምሮ ህ.ወ.ሓ.ትን በጸረ- ዲሞክራሲነቱና በሽብርተኝነቱ ያወገዘ፤ ራሱን ከማንኛውም አስከፊ ተግባር ያገለለ፣ በታጋዩ ተከብሮና ታቅፎ የቆየና በ1977 ከህ.ወ.ሓ.ት. በመለስና በስብሃት ተባሮ የወጣው ኢትዮጵያዊ ይገኝበታል።

በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም በገጽ 16 ተጽፋ የምትገኘው ደርግንም የአማራ መንግሥት በማለት በመፈረጅ ታወግዛለች። ደርግ ግን የአማራ አልነበረም። ከዘረኝነት የጸዳ ነበር። የደርግ ስርዓት ሁሉንም ኢትዮጵያውያንን ያቀፈ ነበር። ህ.ወ.ሓ.ት. ይህን ሁሉ ውሸት የሚደረደረው ዋናው ምክንያት አማራውን ለማጥቃት የተቀነባበረ “ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ” ነው። በገጽ 16 መጨረሻ ላይ ጽሑፉ እንዲህ በማለት ያጠቃልላል፣ “ጨቋኟ አማራም ህብረተሰብአዊ እረፍትና ሰላም አታገኝም” ይላል።

“ወይን” የሚባለው የህ.ወ.ሓ.ት. ልሳን መጽሔት ከ1969 መጀመሪያ በአማራው ላይ እንዲፈጸሙ በመሬት ላይ ተግባራዊ መሆን አለባቸው ተብለው በአጭርና በረጅም የትግል ጉዞ የተግባር ዝርዝር ሃታታ በስፋት በመዘርዘር አውጥተዋል። ከተዘረዘሩትም አንዱ የአማራው ሕዝብ እረፍትና ሰላም አያገኝም ለመኖርም አይችልም የምትለው የህ.ወ.ሓ.ት. አቋምና ፖሊሲ ይዛለች። ህ.ወ.ሓ.ት. በአማራው ላይ አጸፋዊ እርምጃ ይወስዳል። እርምጃውም አማራው ከመኖር ወደ አለመኖር ይለወጣል። በዚህ መሰረት በወይን መጽሔት የተዘረዘረው በጥር 1969 ወደ ተግባር ተለውጦ አማራው በተገኘበት መግደል ተጀምሮ ከዛም ወደ ወልቃይት ፀገዴ ተሸጋግሮ የዘር ማጥፋት ተካሂዷል።
1. ማንኛውም በህ.ወ.ሓ.ት. ነፃ መሬት የሚኖር አማራ ከትግራይ ለቆ በአስቸኳይ ይውጣ። በሕዝብ ግንኙነት ከያሉበት እየተለቀሙ በርካታ በጡረታ የተገለሉ ጦር ሰራዊት፣ ፖሊስ፣ ፊናንስ ፖሊስ፣ በሌላ የመንግሥት ሥራ ሲሰሩ የነበሩ በተለያዩ ቦታ ይኖሩ የነበሩ፤ ከትግራይ ሚስት አግብተው፤ ልጆች ወልደው ብዙዎቹም ልጆቻቸው ለትዳር የበቁ የልጅ ልጅ ያዩ ናቸው። ይህ ድንገተኛ ዘረኛ የህ.ወ.ሓ.ት. ፖሊሲ እንደተላለፈ አማራውም ከየቦታው እየተያዘ ሃለዋ ወያነ 06 ገብቶ ይጠፋል፣ ንብረቱም ይወረሳል። የትግራይ መሬት ለትግራይ ሰዎች ብቻ በማለት ከሃገራችን ልቀቁልን ይላል። በትግራይ በ1969 የተጀመረው አሁን አማራው ከተለያየ ቦታ እየተጠረገ ተገፍቶ፣ ተፈናቅሎ በረሃ ላይ ወድቆ ይገኛል። ስለዚህ ከመሬታችን ውጡልን የተጀመረው በ1969 በህ.ወ.ሓ.ት. ሲሆን አሁንም ይህንን ክልል ተብለው የሚጠሩ የረጅም ጊዜ ውጥን ህ.ወ.ሓ.ት. በተግባር እፈጸመው ይገኛል። ከህ.ወ.ሓ.ት. ትግል መነሻ ጀምሮ እስከ ዛሬ አማራ ዘሩ እየጠፋ ነው።

2. ኢ.ህ.አ.ፓ. አባይ ኢትዮጵያ ከትግራይ ውጣ ሲባል፣ ትግራይ ኢትዮጵያ እኛም ኢትዮጵያውያን ነን ብለው አንወጣም በማለታቸው ለጥቃት ተዳረጉ።

“ወይን” መጽሔት ከ1969 ጀምሮ በተከታታይ የሚያወጣው ጽሑፍ በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራም ላይ የተቀመጡ የረጅም ጊዜ እቅድ በመተንተን እና በማብራራት ለታጋዩ ለውይይት በማቅራብ ሲያብራራ፣ ኢትዮጵያ ወይም ሞት ብሎ የሚናገረውን አማራ ማጥፋት ከሱም ጋር አብሮ የሚቀበረው አማርኛ ቋንቋ ይሆናል ይላል።

በህ.ወ.ሓ.ት. ፕሮግራምና በወይን መጽሔት እንደተዘገበው፣ አማራው የትግራይ ሕዝብ ጠላት እንደመሆኑ በግንባር ቀደምትነት ህ.ወ.ሓ.ት. አማራውን ማጥፋት ግዴታው ነው ይላል። ኢትዮጵያን ለማጥፋትና ከዓለም ካርታ ፍቆ ለማስወጣት አማራው ሲጠፋ ብቻ ነው በማለት ወይን መጽሔት ይዘረዝራል። ከጎንደር ጠ/ግዛት ከወሎ ለምና ሰፊ መሬት የነጠቀው ወያኔ በፕሮግርራሙ መቅድም V ላይ እንደዘረዘረው እውን ሆኖለታል። በሰፊና ለም መሬት የተከበበች ትግራይ “የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ሪፓብሊክ” ነፃ ሃገር ማቋቋም ግብ አማራው ከጠፋ ተቀናቃኝ አይገጥመኝም በማለት የታቀደ የረጅም ጊዜ የስትራተጂ እቅድ ቀስ በቀስ ወደ ተግባር የሚለወጥ ነው።

የህ.ወ.ሓ.ት. አመራር ኢትዮጵያን እገዛለሁ የሚል ተስፋም ህልምም አልነበረውም። ደርግ ተዳክሞ በራሱ ጉዞ እንደጠፋ ህ.ወ.ሓ.ት. በለስ ቀንቶት ግንቦት 1983 ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ እንደ ዋናው የፖሊሲ ፕሮጀክትና እቅድ በ1984 መጀመሪያ በተግባር ላይ ዋለ። አማራውን ለብዙ ዓመታት ከኖረበት ቦታ ያፈራውን ሃብትና ንብረቱን፤ በትዳር ከኦሮሞው፣ ከሲዳማው፤ ከወላይታው ጋር ከተሳሰረበት ለአማራው “ነፍጠኛ፣ ተስፋፊ” የሚል ተለጣፊ ስም በመስጠት የአማራው ዘር እየተፈለገ በሁሉም እድሜ የሚገኙትን እየሰበሰበ በጥይት በመደብደብ፤ በገደል በመወርወር ፈጅቷል። ይህንን ተግባሩን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በመቀጠል በቤንች ማጂና ጉራ ፈርዳ ተመሳሳይ ድርጊት ፈጽሟል። ሊገድላቸው ያልቻለውን ደግሞ የማንገላታት ተባሩን ቀጥሎ የአማራውን ብሄረሰብ እየነጠለ ከጉራ ፈርዳ፤ ከቤኒሻንጉል እንዲባረሩ በማድረግ ለክፉ ሰቆቃ ተዳርገዋል። ህ.ወ.ሓ.ት. ይህንን ሁሉ የሚያደርገው ከመመስረቱ ጀምሮ የወጠነውን እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ነው።

ይህንን ለመተግበር ወያኔ አስቀድሞ ያዘጋጀው እቅድ የአማራውን ቦታ ማጥበብ ነው። ትግራይ ከበጌምድርና ከወሎ ሰፊና ለም መሬት ወስዳለች። ከወሎ ሰፊ መረት ወደ አፋር ተከልሏል፤ የጎጃም መሬት ለአፋርና ለሌሎች ተሰጥቷል፤ ሸዋ እንዳለ የኦሮሞ ሆኗል። በዚህ አይነት የአማራው መሬት ተከፋፍሎ የቀረችው መሬት የበሬ ግንባርም አታክልም። አንድ ነገር ካልተደረገ በስተቀር ነገ ደግሞ ከዚችው ከቀረችው መሬት ውጣ ሊባል ይችላል። ህ.ወ.ሓ.ት. ይህንን አማራውን የማጥፋት “Systematic elimination and genocide” ዋናው ፖሊሲ አድርጎ የተነሳው ገና ትግራይ በረሃ እዳለ ነው። አማራውን መግደል፤ ካልተቻለም በዘዴ ማጥፋት ብሎ ያቀደውን አሁን በግልጽ እያስፈጸመው ነው። አማራው ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በመሆን እኩል መስዋእትነት ከፍሎ ሃገራችንን ዳር ድንበሯን በማስከበር ለብዙ ሺህ አመታት በነጻነት ያቆየን የሕዝብ አካል ነው።
ህ.ወ.ሓ.ት. አማራውን ለምን በጠላትነ ፈርጆ ያጠቃዋል? ለዚህ ብዙ ምክንያቶች መስጠት ቢቻልም ዋና ዋንዎቹን አንድ ሁለት ልበል፤

1. አማራውም ሆነ ቀሪው የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ነው። ኢትዮጵያዊነቱን አምርሮ የሚወድና የሚያፈቅር አማራ ነው ብሎ ስለሚያስብ አማራ ካልጠፋ ኢትዮጵያን ማጣፋትም ሆነ ማፍረስ ቀላ አይሆንም የሚል ግምት አለው። ስለዚህ አስቀድሞ የአማራውን አከርካሬ መስበር ከተቻለ ኢትዮጵያዊነትም አብሮ ይሰበራል የሚል ሕልም ስለአለው ነው።
2. ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ሃገሪቱን በቋንቋና በሃይማኖት ከፋፍሎ እርስ በርሱ በማፋጨት ቂም በቀል እንዲይዝና አዳክሞ አገዛዙን ማቅለል ከበረሃ ይዞት የመጣው ውስጣዊና ድብቅ ፖሊሲው ነው።

3. በዚች ዓለም ብዙ የተለያዩ ቋንቋዎች ይነገራሉ። ቢሆንም ብሄራዊ ቋንቋ የሌላቸው ሃገሮች የሉም ማለት ይቻላል። ኢትዮጵያ ሃገራችንም ከ85 በላይ የተለያዩ ቋንቋዎች የሚነገርባት ሃገር ናት። ይሁን እና ለብዙ ዘመናት እንደብሄራዊ ቋንቋ ሲያገለግል የቆየው ግን በአማርኛ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የትኛውም ቦታ ቢኬድ አማርኛ ተናጋሪ አይጠፋም። የአማርኛ ቋንቋ መግባቢያ፣ መወያያና ሃሳብ ለሃሳብ መለዋወጫ ከሆነ በሺህ የሞቆጥር ዘመን አልፏል።
ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. የአማርኛ ቋንቋ የጠላት ቋንቋ ስለሆነ መጥፋት አለበት ብሎ በፖሊሲ ደርጃ ይዞ የተነሳው ከ1967 ጀምሮ ነው። ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ስርዓቱ ስር እንደወደቀች፤ ክልል ብሎ ከፋፍሎ እንዲያመቸው በከፋፈላቸው ግዛቶቹ በት/ቤቶች፤ በፍርድ ቤቶች፣ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች አማርኛ ጥቅም ላይ እንዳይውል አገደ። ወያኔ ሥልጣኑን ከያዘ ወዲህ የተወለዱ ሕፃናት በትግራይ፣ ኦሮም፣ አፋር፣ ሲዳሞ፣ ጋምቤላ ወዘተ አማርኛ የማይናገረውና የማይሰማው በርክቷል። ይዞት በመጠው የጫካው ፖሊሲ አማካኝነት አማርኛን እያዳከመ በመቅበር ላይ ይገኛል። ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. የአማርኛ ቋንቋን በማዳከሙ ምን ትርፍ ያገኛል? የሚሉ አይጠፉም። በጥቂቱ ላስረዳ፤

1. የኢትዮጵያዊነት ብሄራዊ እምነትን ያዳክማል፤ ቀስ በቀስም ኢትዮጵያዊነትን ይደመሰስላል፤ ሃገር አልባና ባይተዋር ያደርጋል። የግል መገለጫና ማንነትን ያጠፋል።

2. ብሄራዊ ቋንቋ ስለማይኖር ከተወለድክበት ክልል መውጣት አትችልም። በማንኛውም የኢትዮጵያ ግዛት ተዘዋውሮ መሥራት አይቻልም። ይህ ሁሉንም የኢትዮጵያ ዜጋ የሚመለከት ነው። ይህ የወያኔ ፖሊሲ ወጣቱን ኢትዮጵያዊ አይኑን እና አእምሮውን ሸፍኖ ዜግነቱን እንዲረሳ የታቀደ ተንኮል ነው።

3. ብሄራዊ ቋንቋ እንዳይኖር እየተገበረ ስለሆነ፤ አመለካከትና አስተሳሰብ ከመንደር የዘለለ አይሆንም። ኢትዮጵያዊ ታሪክ፣ ባህልና ማንነት አብሮ ይጠፋሉ።

4. ብሄራዊ ቋንቋ ካልኖረ እድገትና ልማት በምንም ተአምር በሃገሪቱ አይታይም። ይህም አንዱ የህ.ወ.ሓ.ት. ጸረ-ልማት ፖሊሲ ነው።

ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. ክልል ብሎ ያስቀመጣቅቸው የኢትዮጵያ ሕዝብና ብሄራዊ የሆነውን የአማርኛ ቋንቋ በማዳከምና በማጥፋት ነው። አንዱን ክልል በሌላው ላይ መጠራጠርና ጥላቻ እንዲፈጥር ቢጥርም የፈለጉትን ያህል አልተሳካላቸውም። በሕዝቡ ብርታትና አልበገር ባይነት በተቻለው ሁሉ ኢትዮጵያዊነቱን ጠብቆ የሚኖር ኩሩ ሕዝብ እንደሆነ ይገኛል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የህ.ወ.ሓ.ትን ማንነት አውቆ ድርጊቱን በተለያየ መንገድ መግለጽ ከጀመረ ከራርሟል።

ስለዚህ ህ.ወ.ሓ.ት. ይህንን የአማራውን የዘር ማጥፋት (Genocide)የረጅም ጊዜ እቅድና ፖሊሲ በማውጣትና በመተግበር በዋናነት የሚጠየቁት፤ ከነዘር ሃረጋቸው፤ እነማን ናቸው የሚለውን እንመልከት፤

1. መለስ ዜናዊ፣ በአባቱም በእናቱም ሕዝብና ሃገር ያጠፋ የባንዳ ዘር ኤርትራዊ
2. ስብሃት ነጋ፣ በእናቱ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ (በናቱ በኩል)
3. አባይ ፀሃየ፣ የባንድ ልጅ አክሱም
4. ሥዩም መስፍን የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ
5. አርከበ እቁባይ፣ የባንዳ ልጅ አድዋ
6. ዶ/ር ሰሎሞን እንቋይ፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ (በአባቱ በኩል)
7. ጸጋይ በርሄ፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ
8. ጻድቃን ገብረተንሳይ፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ
9. ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ
10. አባይ ወልዱ፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ (በአባቱ በኩል)
11. ቴዎድሮስ አድሃኖም፣ የባንዳ ልጅ ኤርትራዊ
12. ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል፣ የባንዳ ልጅ (የሻእቢያ ፈዳያን የነበረ) ኤርትራዊ
13. አዜብ መስፍን፣ እድገቷ ኤርትራና ሱዳን ፀገዴ (ጸረ-አማራ)

ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉም ወላጆቻቸው የጣልያን ወራሪን በባንዳነት አሽከር ሆነው እያገለገሉ፣ ኢትዮጵያን የወጉና ሕዝቧን ያስፈጁ የጠላት ልጆች ናቸው። የወላጆቻቸውን ፈለግ በመከተል ወላጆቻቸው የሰጧቸውን አደራ በመከተል አሁንም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጥቃትና በደል እየፈጸሙ ነው። ኢትዮጵያን በማፍረስ፣ ሃብትና ንብረቷን በመመዝበርና በዘር ማጥፋት ወንጀል በመሰማራት በሕግ የሚያስጠይቃቸውን ድርጊት እየፈጸሙ ናቸው። ብ.አ.ዴ.ን. እና ኦ.ህ.ዴ.ድ. እንዲሁም የደቡብ ህዝቦች ንቅናቄም በዘር ማጥፋት አስፈጻሚነታቸው በወንጀል ተጠያዊ ናቸው።

ይህንን የወያኔ ህ.ወ.ሓ.ትን እና የግብረአበሮቹን ሃገርና ሕዝብን የማጥፋት ተግባራቸው የመግቻው መፍትሄ ምንድን ነው? ለሚለው፤ እከሌ ከእከሌ፤ ፓርቲ ከፓርቲ፤ ግንባር ከግንባር፣ ወገን ከወገን ሳይለያይ ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዞ አሻፋረኝ፣ አልገዛም፣ በቃኝ ብሎ በአጠቃላይ አንድ ሆኖ የሕዝብ አመጽ ማስነሳት ብቻ መፍትሄ ያመጣል እላለሁ።
ኢትዮጵያና ሕዝቧን እናድን
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር

የኢትዮጵያ አደገኛ የፖከቲካና ማህባዊ ጉዞ ያሳሰባቸዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እራሰቸዉን በህቡዕ እያደራጁ መሆኑ ተነገረ


ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ባለፉት ሃያ አንድ አመታት የተከተላቸዉ የፖለቲካ፤የኤኮኖሚና ማህበራዊ ፖሊሲዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ያደረሰዉ ጥፋትና አሁንም አገሪቱ የምትጓዝበት አደገኛ አቅጣጫ ያሳሰባቸዉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት እራሳቸዉን በህቡዕ እያደራጁ መሆኑን አንድ ምስራቅ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኘዉ የዚሁ የህቡዕ ድርጅት ህዋስ መሪ ከግንቦት ሰባት ድምጽ ጋር ባደረጉት የስልክ ምልልስ ገለጹ። እኚህ ለደህንነታቸዉ በመስጋት ቃለምልልሳቸዉ በሬድዮ እንዳይደተላለፍ የጠየቁን ከፈተኛ የጦር መኮንን በህቡዕ የመደራጀቱ እንቅስቃሴ ሠራዊቱ በብዛት በሚገኝባቸዉ ቦታዎች ሁሉ እየተካሄደ ሲሆን በቅርብ ግዜ ዉስጥ ከሌሎች ለለዉጥ ከሚታገሉ ሀይሎች ጋር በመሆን ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንደሚጅምሩ ተናግረዋል።

የዚህ “አገርህን አድን” በሚል ስያሜ የሚጠራዉ አገር ወዳድ ቡድን አባላት የወያኔ ደህንነት የሚያደርግባቻዉን የሃያ አራት ሰአት ክትትል ጥሰዉ ለመጀመሪያ ግዜ የተሰባሰቡት ከአራት አመታት በፊት ሲሆን ያሰባሰባቸዉም ወያኔ ሠራዊቱ ዉስጥ የሚከተለዉን ጭፍን የዘረኝነት ፖሊሲ ለመቋቋም እንደሆነ ታዉቋል። ሆኖም ይህ በ“አገርህን አድን” ቡድን ስር በመደራጀት ላይ የሚገኘዉ ሠራዊት አላማ የሠራዊቱን መብትና ነጻነት አስጠብቆ ወደ ሠፈሩ መመለስ ሳይሆን የቡድኑ ተቀዳሚ አላማ ለህዝብ በገባዉ ቃል መሠረት ኢትጵያንና ህዝቧን ከወያኔ ዘረኝነትና ከፋፍለህ ግዛዉ ፓሊሱ ማዳን ነዉ ሲሉ የቡድኑ ቃል አቀባይ ተናግረዋል።

የወያኔ አገዛዝ በአማራዉ ወገናችን ላይ የሚያደርሰዉን ጥቃት በቅርብ እየተከታሉት እንደሆነ የተናገሩት እኚሁ ቃል አቀባይ እንደዚህ አይነቱን የማን አለብኝነት ወንጀልና ባጠቃላይ የወያኔ ዘረኞች በግልጽ የሚያካሄዱት መብት ረገጣ፤ግድያ፤ዝርፍያና የአገርን ብሔራዊ ጥቅም ለባዕዳን አሳልፎ መስጠት ወያኔ አስካልተወገደ ድረስ የማይቆም በመሆኑ ያለን አማራጭ በቻልነዉና በምናዉቀዉ መንገድ ሁሉ ወያኔን ለማስወገድ መታገል ዋናዉ አላማችን ነዉ ብለዋል።

በመጫረሻም ከነማን ጋር ትሰራላችሁ ተብሎ የተጠየቁትን ጥያቄ ሲመልሱ ዛሬ አገራችን ለመዉደቅ በመንገዳገድ ላይ በምትገኝበት ወቅት ያለን አማራጭ አልገዛም ካለና የእኩሎች አገር የምትሆን ኢትዮጵያን ለመገንባት ፍላጎቱና ቆራጥነቱ ካላቸዉ ወገኖች ጋር ሁሉ አብረን እንታገላለን ብለዋል። በአሁኑ ወቅት አያሌ ኢትዮጵአዉያን ወያኔን ለመታገል መሳሪያ ካነሱ ወገኖች ጋር በየቀኑ እየተቀላቀሉ ስለሆነ የኛም አላማ የትግል ስልትና የተለየ የትግል ቦታ ሳንመርጥ ወያኔን ያዋጣናል ባልነዉ ስልትና ይመቸናል ባልነዉ ቦታ ሁሉ እስከእለተ ሞቱ እንታገለዋለን ብለዋል።

Saturday, April 13, 2013

Jailed Ethiopian female journalist Reeyot Alemu in critical condition

The Horn Times Newsletter 13 April 2013
by Getahune Bekele, South Africa
*spare Reeyot, CPJ pleads with Berhan Hailu
Her predicament touched millions of hearts around the world in 2012 when it was established that she had a malignantReeyot Alemu is one of those journalists – she has been sentenced to five years in jail. tumor in her breast which prompted her lawyer father and others to plead with the late Ethiopian despot Meles Zenawi for clemency on humanitarian grounds.
However, the fiend fuehrer refused to pardon Reeyot, an iconic figure in Ethiopian free media fraternity and she went under the knife, and rushed back to jail in most brutal show of barbarity by the hateful prison authorities.
But against all odds, even after being forced to recuperate in filthy cell, the courageous Reeyot survived.
Held since 2011 on trumped up terrorism charge alongside blogger Eskinder Nega and young politicians Andualem Aragie and Natinael Mekonnen, in the past two weeks there were reports of heated exchanges between Reeyot and the extremely rigid wardens who threatened to put her in solitary confinement for two months.
Then those reports were followed by yesterday’s disturbing news of her illness, appeared on moonofthesouth BlogSpot written by renowned African journalist Issa Sikiti Da Silva.
According to Da Silva who lamented the terrible state of journalism in countries like Djibouti, Somalia and Ethiopia; CPJ, a New York based media watchdog has written an open letter to Ethiopian justice minister Berhan Hailu, pleading with him to spare the already ailing Reeyot and relax her tight prison condition.
“Prison authorities have threatened Reeyot with two months of solitary confinement as punishment for alleged bad behavior toward them and threatening to publicize human rights violations by prison guards, according to sources close to the journalist who spoke to the international women’s media foundation on condition of anonymity. CPJ has independently verified the information. Reeyot has also been denied access to adequate medical treatment after she was diagnosed with a tumor in her breast” CPJ’s letter sent to Birhan Hailu by its executive director Joel Simon reads.
“We would like to draw your attention to 2011 report by Juan E Mendez, the United Nations special rapporture on torture, in which he urged the prohibition of ‘the imposition of solitary confinement as punishment- either as judicially imposed sentence or a disciplinary measure.’ We would also remind you that Ethiopia is a signatory to the United Nations convention against Torture and other cruel, Inhuman or Degrading Treatment or punishment and is legally bound to uphold these principles.” The letter which was distributed to diplomats and various human rights institutions says.
Nevertheless, it remains to be seen how warlord Berhan Hailu, a Meles Zenawi loyalist who is well aware of the plight of more than 56,000 political prisoners would respond to CPJ’s plea.

ECADF

የአማራ ህዝብ ስቃይ እንዲያበቃ ወያኔን መቅበር ይኖርብናል

          
   ቀን ሚያዝያ 5 2005/ጋዜጣዊ መግለጫ 0002

ዛሬ ወያኔ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ያፈናቀላቸው አማሮች የመጀመሪያዎቹ የወያኔዎች የጥቃት ሰለባዎች አይደሉም። የመጨረሻዎቹም አይሆኑም። ወያኔ ከነ ጸረ አማራ ፖሊሲው በስልጣን እስካለ ድረስና በአማራ ስም አማራውን እያፈኑ፣ እየሰለሉ ከወያኔ ፍርፋሪ እየለቀሙ ለመኖር የቆረጡ ከአማራው መሃል የወጡ ከሃዲዎች አማራውን መቆጠጠር እስከቻሉ ድረስ የአማራ ህዝብ መራቆት፣ ስደት፣ ውርደት፣ ሰቆቃና ሞት የማይለዩት ህዝብ እንደሆነ ይቀጥላል።





 
  
የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል ይህን በእብሪትና በጥላቻ የተሞላ በወያኔ የሚፈጸም በአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ የባላጌዎች ጥቃት ማስቆም የሚቻለው የወያኔን እብሪት በጠመንጃ እና በተባበረ የህዝብ አመጽ ማስተንፈስ እስከተቻለ ብቻ ነው ብሎ ያምናል። እስካሁን ወያኔ በከንቱ ያፈሰሰውን የንጹሃን አማሮች ደም መፋረድ የሚቻለው ከጠምንጃ አፈሙዝ በሚወጣ እሳት ብቻ ነው ብሎ በጽኑ ያምናል። ከንፈር መምጠጥ፣ ዋይታ፣ ኡኡታ፣ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሰላማዊ ሰልፍና በየፈረንጅ በር ደጅ መጽናት ወያኔ የአማራ
ህዝብ ቅስም ለመስበር የወያኔ እንጨት ሰባሪና ውሃ ተሸካሚ አድርጎ፣ ነጻነቱንና ክብሩን ገፎ አዋርዶ ለመግዛት የዘረጋውን መርሃ ግብ
ግብር እንዲያጥፍ አያደርገውም።

ወያኔ ይሉኝታ ያልዘራበት፣ ትእግስትን እንደፍራቻ፣ አርቆ ሳቢነትን እንደሞኝነት የሚቆጥር በአማራው ላይ ቂምና ጥላቻን ሰንቆ የተነሳ ጨካኝ ድርጅት ነው። ይህን ድርጅት ስለጀግንነቱና ስለወርቅ ዘርነቱ እጅግ የተሳሳተና የተጋነነ ግምት ያለው፣ ማንም ምንም አያደርገኝም በሚል ትምክህት ተወጥሮ የሚኖር ድርጅት ነው። ከእንዲህ አይነቱ በራሱ ፕሮፓጋንዳና ከንቱ ውዳሴ ከሰከረ ድርጅት ጋር የሚደረግ ትግል ያለምንም መወላወል በከፍተኛ እልህና ጭካኔ የሚካሄድ ብቻ ነው። የአማራውን ሰቆቃ ለማስቆም ወያኔ “እዩኝ እዩኝ” እንዳለለ “ደብቁኝ ደብቁኝ” እስከሚል የሚዘምቱበት እና ክንዳቸውን የሚያሳዩት ጀግኖችን ይሻል። ከወያኔ ጋር ፊት ለፊት ተጋፍጠው ገድለው ለመሞ ት የቆረጡ የወገን ደምመላሾችን ይጠይቃል። ቤታቸውን ዱርና ገደሉን አድርገው፣ “ወተት ይሸፍታል እንኳን ሰው ሲበደል” የሚሉ ቁጡዎችን ይፈልጋል። የአማራውን ህዝብ እልቂት ለማቆም፣ የወንድ ልጅ እናት በገመድ የምትታጠቅበት፣ ልጇን አሞራ እንጂ ሰው የማይቀብርበት ሌላ ታሪካዊ ዘመን መምጣቱን ሁላችንም መቀበል ይኖርብናል።

የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሃይል አባላት ወያኔ በአማራ ህዝብ ላይ በሚያሳየው እብሪት ተቃጥለናል። በግነናል። የእዚህ እብሪት ማርከሻ ጠመንጃ ነው፡ እሳትና አርር ብቻ ነው ብለናል። ሌላው ሁሉ አማራጭ ተፈትሿል፣ተሞክሯል፣ታይቷል ሌላ አማራጭ የለም ብለናል። የቀረው አንድ ምርጫ ነው፦:መሞ ት ወይም መግደል ። እኛ ይህን አውቀን ከያለንበት ተጠራርተን የአማራን ህዝብ በቀላሉ ልንደርስበት በምንችልበት ምድር እየተሰባሰብን ነው። የከፋህ፣ የመረረህ፣የተበደልክ በቃኝ ያልክ ና ተቀላቀለን፣ የወገናችንን የአሳርና የመከራ ዘመን ማብቃት በወያኔ ቀብር ላይ እናረጋግጥ ።

ውድመት ለአማራ ህዝብ ጠላት ለዘረኛው ወያኔ!!!!!!!!!
ድል በወያኔ ለሚረገጡ ኢትዮጵያውያን በሙሉ!!!!!!!!!!!!!

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ የአማራ ተወላጆችን አሁንም ለተጨማሪ ጥፋት እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ

GINBOT 7 Movementለረጂም ዘመናት ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር ተዋደውና ተግባብተው ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆችን ኢሰብዊ በሆነ መንገድ እንዲፈናቀሉና በሰላምም ይኖሩበት ከነበረው ህበረተስብ ጋር ግጭት እንዲፈጥሩ ያደረገው ዘረኛ አገዛዝ እነኝህን ተፈናቃዮች እንደገና በመመለሱ ለሌላ ጥፋት እየተዘጋጀ መሆኑን ዘጋቢያችን ከባህር ዳር በላከልን ዘገባ አመለከተ።

ቁጥራቸው ከ5 ሺ በላይ የሚጠጉ ከፍኖተሰላም ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እንዲመለሱ የተደረጉት የአማራ ተወላጆች በሚመለሱበት ቦታ የደህንነት ዋስትና እንደሌላቸው እየገለጡ ሲሆን መሰሪው አገዛዝ በበኩሉ ስህተት መፈጠሩን በማመን ችግሩን የፈጠሩት ታች ያሉ ባለስልጣናት ናቸው። የሚል አሳፋሪ መልስ በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተያይዞ የደረሰን ዘገባ አመልክቷል።

ከትናንት በስቲያና፣ በትናንትናው እለት መኪኖች ተፈናቃዮችን ከአቅማቸው በላይ በመጫን ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ማቅናታቸውን የገለፀው ዘጋቢያችን የክልሉ ሆድ አደር ባለስልጣናት ተፈናቃዮች እንዲወጡ የተደረገው በስህተት መሆኑን ተናግረው ይቅርታ ጠይቀዋል ብሏል። የአማራ ክልል ፕሬዘዳንት ተብየውም የዞንና የወረዳ አመራሮችን ተጠያቂ ያደረጉ ሲሆን፣ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም መዛቱ ታውቋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት እንደዘገበው “እርምጃ ይወሰድባቸዋል የተባሉት የከማሸ ዞን አስተዳዳሪ እና የያሶ ወረዳ አስተዳዳሪ” መሸፈታቸውን የሚገልጥ መረጃ የደረሰው መሆኑን አመልክቷል።

 ባለስልጣኖቹ “የአካባቢውን ተወላጆች አማራ ወረራችሁ ተነሱ እያሉና እየሰበኩ ወደጫካ መግባታቸውን የደረሰው መረጃ ያመለክታል ያለው ኢሳት የፌደራል ፖሊሶችም የሸፈቱትን ባለስልጣናት በመፈለግ ላይ መሆናቸውን አክሎ ገልጧል።

በከማሺ ዞን በአንድ የግብርና ኢንቨስትመንት ስራ ውስጥ ተቀጥረው እስካሁን ያልተፈናቀሉ የአማራ ተወላጅ እንደገለጹት በክልሉ እየተነዛ ያለው ወሬ አደገኛ በመሆኑ ተፈናቃዮች ሲመለሱ ችግር ሊደርስባቸው እንደሚችል ስጋታቸውን መግለጻቸውን ኢሳት አክሎ ዘግቧል።

Friday, April 12, 2013

ወደ ቤንቺ ማጅ ዞን የተመለሱ የአማራ ተወላጆች ጫካ ውስጥ ወድቀናል ይላሉ

ሚያዚያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ወደ ቤንቺ ማጅ ዞን የተመለሱ የአማራ ተወላጆች ጫካ ውስጥ ወድቀናል ይላሉ
ሚያዚያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ከቤንሻነጉል ጉሙዝ ከከማሺ ዞን ከያሶ ወረዳ ተፈናቅለው ፍኖተሰላም ከተማ ሰፍረው የነበሩት የአማራ ተወላጆች ወደ መጡበት ቦታ እንዲመለሱ ቢደረጉም፣ መጠለያ እና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ነገሮች ባልተሟሉበት ጫካ ውስጥ እንዲሰፍሩ መደረጋቸውን በቦታው ደርሰው ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል።
ተፈናቃዮቹ ህጻናቱም ሆኑ አዋቂዎች ምግብ ሳይመገቡ መዋላቸውን፣ ከአንድ ቀን በሁዋላ ዱቄት ተሰፍሮ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል። የቀይ መስቀል ሰራተኞች አብረዋቸው እንደመጡ የሚገልጹት ተፈናቃዮች ፣ የተቅማጥ በሽታ በመከሰቱም ሀኪሞቹ ከአቅማችን በላይ ነው እያሉ መሆኑን ገልጸዋል።
ተፋናቃዮች አንድም ባለስልጣን መጥቶ እንዳልጎበኛቸው ተናግረው የአማራ ክልል ባለስልጣናት መልሰው እንዲወስዷቸው ጥያቄ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል። vvvv አሁንም የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ባለስልጣናት በቦታው ተገኝተው ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ስጋታቸውን እንደጨመረው ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ክልል በመተከል ዞን በቡለን ወረዳ ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ የሚገኙ ከ2 ሺ በላይ አርሶአደሮች አንድም ባለስልጣን እንዳላናገራቸው ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ ከሶስት ቀናት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ 7 አመራሮቻቸው ተይዘው ለ24 ሰአታት ከታሰሩ በሁዋላ በይቅርታ እንዲፈቱ መደረጋቸውን ታስረው የተፈቱ አንድ ተፈናቃይ ገልጸዋል።
ተፈናቃዩ ” የተዘረፍነው ንብረት ይመለስልን፣ ወደ ቀያችንም እንመለስ” በማለት በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ የወረዳው ባለስልጣናትም የቻግኒን ከተማ ህዝብ ጸጥታ ታደፈርሳላችሁ በሚል ሰልፉን እንዲበተን እንዳደረጉና መሪ ናቸው የተባሉትን ሰዎች አስረው እንደለቀቁዋቸው ገልጸዋል። ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች እንታሰራለን በሚል ከከተማዋ መውጣታቸውን የገለጡት ተፈናቃዮ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ1600 በላይ ሰዎች መፍትሄ አጥተው መቀመጣቸውን ገልጸዋል።
ከከማሺ ዞን የተፈናቀሉት እንደተመለሱ ብንሰማም ከመተከል ዞን ለተፈናቀሉት ግን አሁንም መልስ አልተሰጠንም በማለት ተፈናቃዩ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በመተከል ዞን እንዲፈናቀሉ ሲደረጉ ድብደባ የተፈጸመባቸው አንድ የአማራ ተወላጅ፣ የደረሰባቸውን ጉዳት ዘርዝረው አቅርበዋል። ተፈናቃዩ እንዳሉት ድብደባው የደረሰባቸው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተጠይቀው ፣ አልወጣም የሚል መልስ ከሰጡ በሁዋላ ነው ።
የክልሉ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ተገቢውን ካሳ እንደሚያገኙ ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።

ኢሳት ዜና:-ከቤንሻነጉል ጉሙዝ ከከማሺ ዞን ከያሶ ወረዳ ተፈናቅለው ፍኖተሰላም ከተማ ሰፍረው የነበሩት የአማራ ተወላጆች ወደ መጡበት ቦታ እንዲመለሱ ቢደረጉም፣ መጠለያ እና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ነገሮች ባልተሟሉበት ጫካ ውስጥ እንዲሰፍሩ መደረጋቸውን በቦታው ደርሰው ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል።

 ተፈናቃዮቹ ህጻናቱም ሆኑ አዋቂዎች ምግብ ሳይመገቡ መዋላቸውን፣ ከአንድ ቀን በሁዋላ ዱቄት ተሰፍሮ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል። የቀይ መስቀል ሰራተኞች አብረዋቸው እንደመጡ የሚገልጹት ተፈናቃዮች ፣ የተቅማጥ በሽታ በመከሰቱም ሀኪሞቹ ከአቅማችን በላይ ነው እያሉ መሆኑን ገልጸዋል።

 ተፋናቃዮች አንድም ባለስልጣን መጥቶ እንዳልጎበኛቸው ተናግረው የአማራ ክልል ባለስልጣናት መልሰው እንዲወስዷቸው ጥያቄ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል። vvvv አሁንም የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ባለስልጣናት በቦታው ተገኝተው ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ስጋታቸውን እንደጨመረው ገልጸዋል።

... ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ክልል በመተከል ዞን በቡለን ወረዳ ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ የሚገኙ ከ2 ሺ በላይ አርሶአደሮች አንድም ባለስልጣን እንዳላናገራቸው ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ ከሶስት ቀናት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ 7 አመራሮቻቸው ተይዘው ለ24 ሰአታት ከታሰሩ በሁዋላ በይቅርታ እንዲፈቱ መደረጋቸውን ታስረው የተፈቱ አንድ ተፈናቃይ ገልጸዋል።

 ተፈናቃዩ ” የተዘረፍነው ንብረት ይመለስልን፣ ወደ ቀያችንም እንመለስ” በማለት በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ የወረዳው ባለስልጣናትም የቻግኒን ከተማ ህዝብ ጸጥታ ታደፈርሳላችሁ በሚል ሰልፉን እንዲበተን እንዳደረጉና መሪ ናቸው የተባሉትን ሰዎች አስረው እንደለቀቁዋቸው ገልጸዋል። ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች እንታሰራለን በሚል ከከተማዋ መውጣታቸውን የገለጡት ተፈናቃዮ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ1600 በላይ ሰዎች መፍትሄ አጥተው መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

 ከከማሺ ዞን የተፈናቀሉት እንደተመለሱ ብንሰማም ከመተከል ዞን ለተፈናቀሉት ግን አሁንም መልስ አልተሰጠንም በማለት ተፈናቃዩ ገልጸዋል።

 በሌላ በኩል ደግሞ በመተከል ዞን እንዲፈናቀሉ ሲደረጉ ድብደባ የተፈጸመባቸው አንድ የአማራ ተወላጅ፣ የደረሰባቸውን ጉዳት ዘርዝረው አቅርበዋል። ተፈናቃዩ እንዳሉት ድብደባው የደረሰባቸው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተጠይቀው ፣ አልወጣም የሚል መልስ ከሰጡ በሁዋላ ነው ።

 የክልሉ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ተገቢውን ካሳ እንደሚያገኙ ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።

የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት መግለጫ አነጋጋሪ ሆኗል

ሚያዚያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ናስር የአማራ ተወላጆችን ለመመለስ የክልላቸው ካቢኔ መወሰኑን በሚመለከት በአገር ቤት ለሚታተ...ሙ ጋዜጦች እና ለኢሳት የሰጡት መግለጫ በተለይ በአዲስአበባ ከተማ አነጋጋሪነቱን ቀጥሎአል፡፡

 “የተፈጠረ ስህተት አምኖ ይቅርታ በመጠየቅ ለማረም መንቀሳቀስ ተገቢ እርምጃ ነው” በሚል ሒደቱን አንዳንድ ምሁራን ያደነቁ ሲሆን ሌሎች ደግሞ “እርምጃው የጭንቅት ውጤት ነው” በማለት አጣጥለውታል፡፡

 እነዚሁ ምሁራን ለአዲስ አበባው ዘጋቢ እንደተናገሩት “በሕገወጥ መንገድ ሰፍረዋል፣ደን ጨፍጭፈዋል” በሚል ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ የአንድ ብሔር ተወላጆች ብቻ ተመርጠው እንዲባረሩ የሚደረግበት መንገድ ከአፓርታይድ የዘር መድልኦ ተለይቶ የማይታይና አደገኛ ጅምር መሆኑን ጠቁመው ይህን ሁኔታ የመንግስት አመራሮች ተረድተው ስህተቱን አምነው ችግሩን ለመፍታት ፍላጎት ማሳየታቸው በበጎ መልኩ ሊታይ ይገባል ብለዋል፡፡

 በጅማ ዪኒቨርሲቲ የሕግ መምህር የሆኑት አንድ አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው መንግስት የእሳት ማጥፋት ስራ በማከናወን ችግሩን ከመሰረቱ መፍታት እንደማይችል ተናግረዋል፡፡ ዋናው ነገር ከላይ እስከታች ያለው አመራር የፌዴሬሽን አወቃቀር ጉዳይ አጣሞ በመረዳት አንድ ክልል በራሱ ተወላጆች ብቻ መያዝ አለበት የሚል የተሳሳተ አመለካከት በሰረጸበት ሁኔታ ነገሩ ዓለም አቀፍ ቁጣ በማስከተሉ ብቻ “የተባረሩት ይመለሱ” ማለት ችግሩን ከመሰረቱ የሚፈታ እርምጃ አይሆንም ብለዋል፡፡

 በአንድ በኩል ሰዎቹን ሕገወጥ ሰፋሪዎች ናቸው እየተባለ በሌላ በኩል ስህተት ተሰርቶአል ይመለሱ ማለት እርስበርሱ የተምታታና ጭንቀት የወለደው ምላሽ ይመስላል ሲሉ
አስረድተዋል፡፡

 አይይዘውም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሁኔታ ከደቡብ ክልል፣ከሶማሌ ክልል አማሮች እየተመረጡ ተባረዋል ያሉት ምሁሩ በነዚያ ጥፋቶች ምንም የማስተካከያ እርምጃ ሳይወሰድ ዛሬ ብድግ ተብሎ ስህተት መፈጸሙን በአደባባይ መናገሩ ብቻውን ስህተቱን አያርመውም ሲሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡

 በግሌ የቤንሻንጉሉ ፕሬዚዳንት መግለጫ አሳዝኖኛል ያሉት ምሁሩ “እንዲመለሱ ተፈቅዶአል፣ተወስኗል፣…ከአማራ ክልል ጋር ተስማምተናል፣ተፈራርመናል..”ሲሉ ምን ማለታቸው ነው፡፡የሰዎችን ተዘዋውሮ የመስራት መብት በኢትዮጵያ ሕገመንግስት ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎች ጭምር ተቀባይነት ያገኘ ሆኖ ሳለ እነሱን ማን ፈቃጅ ፣ማን ከልካይ እንዳደረጋቸው የሚያስገርም ነው፡፡ አንድ በአዲስአበባ የሚኖር ዜጋ ብድግ ብሎ በቤንሻንጉል ለመኖር ቢወስን ቤንሻንጉሎች ከሰውየው ብሔር ክልል ጋር ተነጋግረው መስማማት አለባቸው እያሉን ነውን?…ትልልቆቹ አመራሮች ነገሮችን በዚህ ደረጃ የሚገነዘቡ መሆናቸው በራሱ አስደንጋጭ ነው ብለዋል፡፡

 መንግስት ከደቡብ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ ባለፈው ዓመት በመጋቢት ወር የተባረሩትን የአማራ ተወላጆች በተመሳሳይ ሁኔታ ወደተፈናቀሉበት በመመለስ መልሶ የማቋቋም ተግባር መስራት ካልቻለና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮቹ ስለፌዴራሊዝም ጽንሰ ኀሳብ ማስተማር እስካልቻለ ድረስ አሁንም በዘላቂነት ችግሩ ይፈታል ብለው እንደማያምኑ የሕግ ባለሙያው ተናግረዋል፡፡
ሌላ አስተያየት ሰጪ ደግሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስለተፈናቀሉት ሰዎች ምንም አለማለቱ እንዳስገረው ገልጿል። “ይህ ትልቅ አገራዊ ጉዳይ ነው፤ ይህ ካልተዘገበ ሌላ ምን ሊዘገብ ነው?’ በማለት አክሏል።
ወጣቱ ፖለቲከኛ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ በበኩሉ የሰዎቹ መመለስ ተገቢ ቢሆንም የደረሰው ቀውስ ግን በምንም ነገር የሚተካ አለመሆኑን ገልጿል።

 “እንኳንስ ቤትን የሚያክል ነገር ቀርቶ አንድ ሰው ጓዳውንና ምኝታ ቤቱን ለመቀየር ቢነሳ ብዙ ችግሮች ይገጥሙታል ” በማለት የተናገረው ኢንጂነር ዘለቀ፣ ሰዎቹ ያጡት ነገር ብዙ በመሆኑ ቢመለሱም እንኳን የደረሰባቸውን ቀውስ በቀላሉ ለመተካት አይቻልም ብሎአል።

 የፌደራል መንግስቱን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚደረገው ጥረት ተገቢ አለመሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ገለጹ
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ናስር በአማራ ተወላጆች ላይ ተገቢ ያልሆነ ድርጊት የፈጸሙት የወረዳ ባለስልጣናት ናቸው በማለት የክልሉን ባለስልጣናት እና የፌደራል መንግስቱን ከተጠያቂነት ለማዳን ያደረጉት ሙከራ በማስረጃ ላይ ያልተደገፈ ነው በማለት አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የህግ ባለሙያ ተናግረዋል።

 ባለሙያው ” በሚያዚያ ወር ውስጥ በ 2004 ዓም ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ የሚፈናቀሉ ሰዎችን በተመለከተ በወቅቱ ጠ/ሚ ለነበሩት ለአቶ መለስ ዜናዊ ጥያቄ ባቀረቡበት ወቅት፣ አቶ መለስ ዜናዊ የሰጡት መልስ የፌደራል መንግስት እጅ እንዳለበት የሚያመለክት ነው ብለዋል።

 የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ጉዳዩ የክልሉ ችግር ነው በማለት የሚሰጡት መልስ ተገቢ አይደለም የሚሉት ባላሙያው፣ ምናልባትም ዋናው ተጠያቂ የፌደራል መንግስቱ ሊሆን ይችላል ሲሉ አክለዋል።

Thursday, April 11, 2013

ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ የ አማራ ተወላጆችን አሁንም ለተጨማሪ ጥፋት እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ

ለረጂም ዘመናት ከ አካባቢው ህብረተሰብ ጋር ተዋደውና ተግባብተው ይኖሩ የነበሩ የ አማራ ተወላጆችን ኢ ሰብ ዊ በሆነ መንገድ እንዲፈናቀሉና በሰላምም ይኖሩበት ከነበረው ህበተስብ ጋር ግጭትና እንዲፈጥሩ ያደረገው ዘረኛ አገዛዝ እነኝህን ተፈናቃዮች እንደገና በመመለሱ ለሌላ ጥፋት እየተዘጋጀ መሆኑን ዘጋቢያችን ከባህር ዳር በላከልን ዘገባ አመለከተ።
ቁጥራቸው ከ5 ሺ በላይ የሚጠጉ ከፍኖተሰላም ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እንዲመለሱ የተደረጉት የአማራ ተወላጆች በሚመለሱበት ቦታ የደህንነት ዋስትና እንደሌላቸው እየገለጡ ሲሆን መሰሪው አገዛዝ በበኩሉ ስህተት መፈጠሩን በማመን ችግሩን የፈጠሩት ታች ያሉ ባለስልጣናት ነው የሚል አሳፋሪ መልስ በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተያይዞ የደረሰን ዘገባ አመልክቷል ።
ከትናንት በስቲያና፣ በትናንትናው እለት መኪኖች ተፈናቃዮችን ከአቅማቸው በላይ በመጫን ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ማቅናታቸውን የገለተው ዘጋቢያችን የክልሉ ሆድ አደር ባለስልጣናት ተፈናቃዮች እንዲወጡ የተደረገው በስህተት መሆኑን ተናግረው ይቅርታ ጠይቀዋል ብሏል። የአማራ ክልል ፕሬዘዳንት ተብየውም የዞንና የወረዳ አመራሮችን ተጠያቂ ያደረጉ ሲሆን፣ እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም መዛቱ ታውቋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት እንደዘገበው “እርምጃ ይወሰድባቸዋል የተባሉት የከማሸ ዞን አስተዳዳሪ እና የያሶ ወረዳ አስተዳዳሪ” መሸፈታቸውን የሚገልጥ መረጃ የደረሰው መሆኑን አመልክቷል። ባለስልጣኖቹ ” የአካባቢውን ተወላጆች አማራ ወረራችሁ ተነሱ እያሉና እየሰበኩ ወደጫካ መግባታቸውን የደረሰው መረጃ ያመለክታል ያለው ኢ ሳት የፌደራል ፖሊሶችም የሸፈቱትን ባለስልጣናት በመፈለግ ላይ መሆናቸውን አክሎ ገልጧል።
በከማሺ ዞን በአንድ የግብርና ኢንቨስትመንት ስራ ውስጥ ተቀጥረው እስካሁን ያልተፈናቀሉ የአማራ ተወላጅ እንደገለጹት በክልሉ እየተነዛ ያለው ወሬ አደገኛ በመሆኑ ተፈናቃዮች ሲመለሱ ችግር ሊደርስባቸው እንደሚችል ስጋታቸውን መግለጻቸውን ኢሳት አክሎ ዘግቧል።

የአቶ መለስ ዜናዊን ስም፣ ምስልና ሥራዎቻቸውን መጠቀምን የሚከለክልና የሚፈቅድ የመመርያ ረቂቅ ቀረበ

ሚያዚያ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ሪፖርተር እንደዘገበው የአቶ መለስ ዜናዊን ማንኛውም ከመንግሥትና ከፓርቲ ሥራዎች ጋር ያልተያያዙ ምስሎች ወይም ፎቶግራፎች ባለቤትነት የቤተሰቦቻቸው ብቻ ነው።

ረቂቅ መመርያው፣ ማንኛውም ሰው ገንዘብ ለማሰባሰብ፣ ለሽያጭ፣ ለባዛር፣ ለጨረታ ወይም ለማንኛውም ዓይነት ጥቅም ማስገኛነት ሊሰቅል፣ ሊለጥፍ፣ ሊቀርጽ ወይም ሊያስቀምጥ እንደማይችል ይከለክላል፡፡

የአቶ መለስን ፍቅርና ክብር ለመግለጽ የሚፈልጉ ምስላቸውን በመኖሪያ ቤታቸው ግድግዳ ላይ ሊሰቅሉ፣ በአልበም ውስጥ፣ በቦርሳቸው፣ በኪሳቸው፣ በተሽከርካሪያቸው ወይም በሌላ የግል መጠቀሚያቸው ሊይዙ እንደሚችሉ ደግሞ መመርያው ይፈቅዳል እንደ ጋዜጣው ዘገባ።

ከፋውንዴሽኑ ቦርድና ከቤተሰቡ በቅድሚያ ፈቃድ በመጠየቅ ስማቸውን ለአርዓያነት፣ ለማስተማሪያነትና ለመታሰቢያነት ማንኛውም ሰው መጠቀም እንደሚችሉ የመመርያው ረቂቅ የሚያስረዳ ሲሆን፣ በተለየ ሁኔታ ለሕዝባዊ ዓላማም ከሆነ ፈቃድ ጠይቆ ገንዘብ ማሰባሰብም እንደሚቻል በረቂቁ ተጠቁሟል፡፡

በአቶ መለስ ስም የታተሙም ሆነ ያልታተሙ ሥራዎች ለቤተሰባቸው እንደሚሆኑ የሚገልጸው ረቂቅ መመርያው፣ በመንግሥት ወይም በፓርቲ ኃላፊነታቸው የሠሯቸው ማናቸውም ሥራዎች ባለመብት መንግሥት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብና አባል ድርጅቶች መሆናቸውን ገልጿል፡፡

አንዳንድ ወገኖች አቶ መለስ ዜናዊ እንደጣኦት መመለክ ጀመሩ በማለት በማህበራዊ ድረገጾች አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል።