Friday, March 8, 2013

ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ሀገራችን ወደማትወጣው አደጋ እየተገፋች ነው።

    

ባለፉት 21 የወያኔ የግዛት አመታት አይነቱና መጠኑ ይለያይ እንደሆነ እንጅ ጥቃት፣ ግፍ፣ በደልና እብሪታዊ የመብት ገፈፋ ያልደረሰበት ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ክፍል የለም። ገበሬው፣ የመንግስት ሰራተኛው፣ የፋብሪካ ሰራተኛና በየዘርፉ የእለት ጉርሱን አሳዶ የሚኖረው ሁሉ የወያኔን የሰቆቃ ግፍ በትር በየተራ አይቶታል፣ እያየውም ይገኛል። የኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት አንጀቱ ለፍቶ ያቋቋማቸው ተቋሞቹ እየፈራረሱ ለወያኔ አገዛዝ እንዲመቹ ሆነው ሲጨፈላለቁም አይተናል።
ወያኔ ይህን ሁሉ ያደረገው “አንዱን በአንዴ” በሚል ስልት ነው። መምህራንን ሲያጠቃ የፋብሪካውን ሰራተኛ ተመልካች ያደርገዋል፤ ገበሬውን ሲያጠቃ ከተሜውን ዝም ይለዋል፤ ከተሜው ላይ ሲዘምት ገበሬው ተመልካች ይሆናል፤ ቤተክርሰቲያን ላይ ሲዘምት ቤተ ሙስሊሙ ይመለከተዋል፤ የቤተ ሙስሊሙ የበደል ተራ ጊዜ ቤተክርስቲያን ተመልካች ትሆናለች። ይህ ወያኔን እስከዛሬ ያደረሰው ስልት ነው።
አራዊታዊው የወያኔ አገዛዝ በተመቸውና ይጠቅመኛል ብሎ በአሰበ ሰአት ሁሉ የውብ ህዝብነት ምልክታችን የሆነውን የባህልና የቋንቋ ስብጥርነታችንን እርስ በርስ ለማናከሻነት ሊጠቀምበትም ሞክሯል፤ በተወሰነ ደረጃ አልሰራላቸውም ማለት ያስቸግራል፡፡
ወያኔዎች ከፋፍሎ መግዛትንና በየተራ ማጥቃትን በኪነ ጥበብ ደረጃ አሳድገነዋል ብለው ያምናሉ። በህዝብ ወገን ያለነውም የዲሞክራሲና የነጻነት ሃይሎች ለዚህ አልተመቸንም ማለት ያስቸግራል፡፡ ይህንን ከፋፍሎ የማጥቃት ግፍ በጋራ ለመመከት ያደረግነው ጥረት ህዝባችን ላይ እየደረሰ ካለው ጥቃት ጋር ቢያንስ የሚመጣጠን አይደለም።
የወያኔ መሪዎች ዛሬ ስልታቸውን በማሻሻል አደገኛ ጭዋታ በቤተ እምነቶቻችን ዙሪያ መጫዎት ጀምረዋል። የቤተክርስቲያን እና የአቢያተ መስጊዶችን አስተዳደር በካድሬዎቻቸው ለመቆጣጠር ከሚያደርጉት ሳይጣናዊ ተግባር በተጨማሪ ህዝቡ ሃይማኖት ለይቶ እንዲባላ ለማድረግ በእጅጉ የሚቀፍ ፕሮፖጋንዳ እያካሄዱ ነው። ፍጹም ምሳሌያዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሲቪል መብት ጥያቄ እንደባዕድ መሳሪያነትና እንደ ሽብርተኝነት ለማሳየት እየሞከረ ይገኛል። በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሙሉ እጁን በማስገባት የተጀመረውን እርቀ ሰላም በማፍረስ የራሱን እንደራሴ ሰይሟል። ይህም አልበቃ ብሎት ለዘመናት በመከባበር የኖረውን ሙስሊሙንና ክርስቲያኑን እርስ በርስ ለማጋጨት ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል።
ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ሀገራችን ወደማትወጣው አደጋ እየተገፋች ነው። ይህንን ወያኔ ያዘጋጀልንን የክፍፍልና ግጭት ድግስ ለመመከት ይበልጥ በአንድነት የምንቆምበት እና የምንታገልበት ግዜ ዛሬ ነው፡፡
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለወያኔ የ”ከፋፍለህ በየተራ ቀጥቀጥ” ፖሊሲ መድሃኒቱ አንድ ሆኖ በአንድነት አሻፈረኝ ብሎ መነሳት መሆኑን ያምናል፡፡ ወያኔ ጉልበቱ የኛ መከፋፈልና ለክፍፍሉ መመቸት መሆኑን ያምናል፡፡ እኛ ስንተባበርና ልዩነታችንን ለመጠቀም የሚያደረገውን ሙከራ ስናከሽፍና አንዱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የሁላችንም ነው ብለን የተነሳን እለት ወያኔ የለም።
ግንቦት 7 ንቅናቄ ወያኔ በፈቃዱ የማይታረም ፋሺስታዊ አምባገነን መሆኑን ከተረዳ ሰንብቷል። በመሆኑም ወያኔን በማስገደድ ወይም በማስወገድ ነጻነታችንን መቀዳጀትና ነጻ ሀገር እንዲኖረን ማድረግ አለብን ብለን እናምናለን። ለዚህ ትግልም ማንኛውንም መሰዋእትነት ለመክፈል ተነስተናል። ነጻነትና ኮርተህ በነጻነት የምትኖርባት ሀገር እንድትኖርህ የምትወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተቀላቀለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ጋምቤላ አሁንም በወያኔ ወራሪ ሠራዊት እየታመሰች መሆኗ ተሰማ

በ1996 ዓም ከ400 በላይ አኝዋኮችን በግፍ የጨፈጨፈዉ የወያኔ ወራሪ ሠራዊትና ልዩ ኃይል ከሰሞኑ በብዛት ወደ ጋምቤላ በመዝመት ሠላማዊ ዜጎችን በተለይ የአካባቢዉን አርሶ አደሮች እየያዘ ማሰርና መግደል መጀመሩን ከአካባቢዉን እየሸሹ ጫካ የገቡ ዜጎች ለኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን ስልክ እየደወሉ በሚልኩት ዜና ገለጹ። በተለይ ካለፈዉ አርብ ጀምሮ ፌዴራል ፖሊስ፤ መከላከያ ሠራዊትና የደህንነት ልዩ ሀይሎች ተቀናጅተዉ በጋራ በወሰዱት የማጥቃት እርምጃ ከቤት ቤት እየተዘዋወሩ ተቃዋሚዎችን ይረዳሉ ወይም ታጣቂዎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ ብለዉ የጠረጠሯቸዉን ሠላማዊ ዜጎች ማሰራቸዉንና እራሳቸዉን ለማዳን የሞከሩ ሰዎችን ተኩሰዉ መግደላቸዉን ከአካባባዉ የደረሰን ዜና ጨምሮ ያስረዳል። በአሁኑ ወቅት የወያኔ ወራሪ ሠራዊት በብዛት ወደ ጋምቤላና አካባቢዉ እየዘመተ ሲሆን የአካባቢዉ ህዝብም እራሱን ለማዳን ጫካ እየገባ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የወያኔ ወራሪ ሠራዊት ካለፈዉ ዐርብ ጀምሮ በወሰደዉ የማጥቃት አርምጃ ከአስራ ሁለት በላይ ሠላማዊ ዜጎችን የገደለ ሲሆን ከሟቾቹ ዉስጥ አንድ የአካባቢዉ ተወላጅ የሆነ የአሜሪካ ዜጋ ይገኝበታል። የግንቦት ሰባት ድምጽ ዝግጅት ክፍል የወያኔ ጦር በአካባቢዉ ያደረገዉ ጭፍጨፋ እንደተሰማ በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ ባለስልጣናትን ሰልክ ደዉሎ ሁኔታዉን ለማጣራት ሞክሮ ነበር ፤ ሆኖም የዝግጅት ክፍላችን ያናገረዉ ከፍተኛ የክልሉ ባለስልጣን በአካባቢዉ ምንም አይነት ግጭት የለም በማለት በአለም ዙሪያ የተሰራጨዉን እዉነት ለመካድ ሞክሯል። በሌላ በኩል አዲስ አበባ ዉስጥ የሚገኙ ከፍተኛ የወያኔ አገዛዝ ባለስልጣኖች የጸጥታ ሀይሎች ጋምቤላ አካባቢ የአማጽያንን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር በሚል በወሰዱት እርምጃ አንድ የአሜሪካ ዜግነት ያለዉ ሰዉ መገደሉን ለአሜሪካ ኤምባሲ ተናግረዋል።
የአዲስቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሪ የሆኑት አቶ አባንግ ሜቶ ከኢሳት ሬድዮ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በጋምቤላና በአካባቢዉ ያለዉን ወታደራዊ ዉጥረት ድርጅታቸዉ በቅርብ እንደሚከታተለዉ ተናግረዉ ከሰሞኑ በወያኔ ወታደሮች ተገደለ ስለተባለዉ የአሜሪካ ዜጋ አስፈለገዉን የክትትል መረጃዎች ለአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መስጠጣቸዉን ተናግዋል። ዜጎችዋ በዉጭ አገር በሚደረጉ ወታደራዊ ግጭቶችና አመጾች ሲገደሉ ወይም ደብዛቸዉ ሲጠፋ ክፍተኛ ክትትል የምታደርገዉ ዩ ኤስ አሜሪካ አሁንም ጋምቤላ ዉስጥ በወያኔ ወታደሮች ተገደለ የተባለዉን ዜጋዋን ጉዳይ መከታተል መጀመሯን ለማወቅ ተችሏል። በቅርቡ የኦባማ አስተዳደር ከአሸባሪዎች ጎን ተሰልፈዉ በሚዋጉ የአሜሪካ ዜጎች ላይ የሚወስደዉን አርምጃ በተመለከት ሾልኮ የወጣዉ መረጃ ኮንግሬሱን ጨምሮ አያሌ አሜሪካኖችን እንዳስቆጣ የሚታወቅ ሲሆን፤ ይህ ከሰሞኑ ጋምቤላ ዉስጥ የተገደለዉ አሜሪካዊ ጉዳይ ይበልጥ በተሰማና በታወቀ ቁጥር ወያኔ ላይ መዘዝ ይዞ ሊመጣ እንደሚችል ብዙዎች በመናገር ላይ ናቸዉ።

ጥቃት በየተራ እስከመቼ?

 

ባለፉት 21 የወያኔ የግዛት አመታት አይነቱና መጠኑ ይለያይ እንደሆነ እንጅ ጥቃት፣ ግፍ፣ በደልና እብሪታዊ የመብት ገፈፋ ያልደረሰበት ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ክፍል የለም። ገበሬው፣ የመንግስት ሰራተኛው፣ የፋብሪካ ሰራተኛና በየዘርፉ የእለት ጉርሱን አሳዶ የሚኖረው ሁሉ የወያኔን የሰቆቃ ግፍ በትር በየተራ አይቶታል፣ እያየውም ይገኛል። የኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት አንጀቱ ለፍቶ ያቋቋማቸው ተቋሞቹ እየፈራረሱ ለወያኔ አገዛዝ እንዲመቹ ሆነው ሲጨፈላለቁም አይተናል።
ወያኔ ይህን ሁሉ ያደረገው “አንዱን በአንዴ” በሚል ስልት ነው። መምህራንን ሲያጠቃ የፋብሪካውን ሰራተኛ ተመልካች ያደርገዋል፤ ገበሬውን ሲያጠቃ ከተሜውን ዝም ይለዋል፤ ከተሜው ላይ ሲዘምት ገበሬው ተመልካች ይሆናል፤ ቤተክርሰቲያን ላይ ሲዘምት ቤተ ሙስሊሙ ይመለከተዋል፤ የቤተ ሙስሊሙ የበደል ተራ ጊዜ ቤተክርስቲያን ተመልካች ትሆናለች። ይህ ወያኔን እስከዛሬ ያደረሰው ስልት ነው።
አራዊታዊው የወያኔ አገዛዝ በተመቸውና ይጠቅመኛል ብሎ በአሰበ ሰአት ሁሉ የውብ ህዝብነት ምልክታችን የሆነውን የባህልና የቋንቋ ስብጥርነታችንን እርስ በርስ ለማናከሻነት ሊጠቀምበትም ሞክሯል፤ በተወሰነ ደረጃ አልሰራላቸውም ማለት ያስቸግራል፡፡
ወያኔዎች ከፋፍሎ መግዛትንና በየተራ ማጥቃትን በኪነ ጥበብ ደረጃ አሳድገነዋል ብለው ያምናሉ። በህዝብ ወገን ያለነውም የዲሞክራሲና የነጻነት ሃይሎች ለዚህ አልተመቸንም ማለት ያስቸግራል፡፡ ይህንን ከፋፍሎ የማጥቃት ግፍ በጋራ ለመመከት ያደረግነው ጥረት ህዝባችን ላይ እየደረሰ ካለው ጥቃት ጋር ቢያንስ የሚመጣጠን አይደለም።
የወያኔ መሪዎች ዛሬ ስልታቸውን በማሻሻል አደገኛ ጭዋታ በቤተ እምነቶቻችን ዙሪያ መጫዎት ጀምረዋል። የቤተክርስቲያን እና የአቢያተ መስጊዶችን አስተዳደር በካድሬዎቻቸው ለመቆጣጠር ከሚያደርጉት ሳይጣናዊ ተግባር በተጨማሪ ህዝቡ ሃይማኖት ለይቶ እንዲባላ ለማድረግ በእጅጉ የሚቀፍ ፕሮፖጋንዳ እያካሄዱ ነው። ፍጹም ምሳሌያዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የሲቪል መብት ጥያቄ እንደባዕድ መሳሪያነትና እንደ ሽብርተኝነት ለማሳየት እየሞከረ ይገኛል። በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሙሉ እጁን በማስገባት የተጀመረውን እርቀ ሰላም በማፍረስ የራሱን እንደራሴ ሰይሟል። ይህም አልበቃ ብሎት ለዘመናት በመከባበር የኖረውን ሙስሊሙንና ክርስቲያኑን እርስ በርስ ለማጋጨት ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል።
ዛሬ ከመቸውም በበለጠ ሀገራችን ወደማትወጣው አደጋ እየተገፋች ነው። ይህንን ወያኔ ያዘጋጀልንን የክፍፍልና ግጭት ድግስ ለመመከት ይበልጥ በአንድነት የምንቆምበት እና የምንታገልበት ግዜ ዛሬ ነው፡፡
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለወያኔ የ”ከፋፍለህ በየተራ ቀጥቀጥ” ፖሊሲ መድሃኒቱ አንድ ሆኖ በአንድነት አሻፈረኝ ብሎ መነሳት መሆኑን ያምናል፡፡ ወያኔ ጉልበቱ የኛ መከፋፈልና ለክፍፍሉ መመቸት መሆኑን ያምናል፡፡ እኛ ስንተባበርና ልዩነታችንን ለመጠቀም የሚያደረገውን ሙከራ ስናከሽፍና አንዱ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የሁላችንም ነው ብለን የተነሳን እለት ወያኔ የለም።
ግንቦት 7 ንቅናቄ ወያኔ በፈቃዱ የማይታረም ፋሺስታዊ አምባገነን መሆኑን ከተረዳ ሰንብቷል። በመሆኑም ወያኔን በማስገደድ ወይም በማስወገድ ነጻነታችንን መቀዳጀትና ነጻ ሀገር እንዲኖረን ማድረግ አለብን ብለን እናምናለን። ለዚህ ትግልም ማንኛውንም መሰዋእትነት ለመክፈል ተነስተናል። ነጻነትና ኮርተህ በነጻነት የምትኖርባት ሀገር እንድትኖርህ የምትወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተቀላቀለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
 

Thursday, March 7, 2013

እኛም እንድገመዋ… ርዕዮትን እያሰሩ … ቐሽ ገብሩን ቢዘክሩ… “ሼም” የለም በአገሩ…!? ከአቤ ቶኪቻው

እኛም እንድገመዋ… ርዕዮትን እያሰሩ … ቐሽ ገብሩን ቢዘክሩ… “ሼም” የለም በአገሩ…!?

ተዓምረኛው ኢቲቪ ለማርች ስምንት የሴቶች ቀን መታሰቢያ አንድ ዶክመንተሪ ፊልም አሳይቶናል። ፊልሙ የዛሬ አመት ተላልፎ እኛም የአቅማችንን አስተያየት ሰጥተንበት ነበር። ታድያ ዛሬም ኢቲቪዬ ፊልሙን ደግሞ አሳይቶናል። ታድያ መድገም ብርቅ ነው እንዴ… እኛም አስተያየታችንን እንድገመዋ!
በመጀመሪያ አበሻ እንደመሆኔ መጠን ጭቆናን “እምቢ” ብለው ፋኖን ለዘመሩ ታጋዮች ትልቅ አክብሮት እንዳለኝ ያለ ሽሙጥ እገልፃለሁ።
ተስፋዬ ገብረ አብ ከተረካቸው ትረካዎች በሙሉ “የቁንድዶ ፈረስ” ትረካ በጣም የመሰጠችኝ ናት። እስቲ ለማስታወስ ልሞክር…
ሐረር አካባቢ፤ የጋሪ ፈረሶች የሚደርስባቸው የስራ ጫና እጅግ በጣም ከባድ ነበር። ከስራ ጫናው እኩል ደግሞ ዱላም አለው። ልክ አሁን አሁን ደሞዛችን አነሰ ብለን “ኡኡ” ስንል “ለአባይ እና ለሌሎች ልማቶች ደግሞ መዋጮ አዋጡ” ተብለን መከራችንን እንደምናየው ማለት ነው። በዚህ ላይ እነዚህ የጋሪ ፈረሶች ስራውና ዱላ የሚደራረብባቸው አንሶ ጌታቸው (አባ ፈርዳው) ቀለባቸውንም በአግባቡ አይሰፍርላቸውም ነበርና ከሰውነት ጎዳና ወጥተው ክስት ጉስቁል አሉ።
ይሄን ግዜ “እምቢኝ” አሉና “ቁንድዶ” ወደተባለ ጫካ ገቡ። ከዛም ባህሪያቸው ተለውጦ እንደፈረስ ሳይሆን እንደ እንደ አውሬ ሆኑ። ማን ወንድ መጥቶ ዳግም ወደዛ የጋሪ ባርነት ይመልሳቸው? ማንም።
ታድያ ፈረሶቹ እዛው ጫካ ውስጥ መሽገው እንዳሻቸው እየበሉ እንዳሻቸው እየቦረቁ አማረባቸው። ወዘናቸውም “ጢም” አለ።
“በአሁኑ ግዜ የሀረር አካባቢ ነዋሪዎች የኦህዴድ አባላትን እስከ መቼ የጋሪ ፈረስ ትሆናላችሁ? አንዳንዴ እንኳን የቁንድዶ ፈረስ ሁኑ እንጂ…! እያሉ ያሽሟጥጧቸዋል።” ብሎናል ተስፋዬ። (ልክ ነኝ አይደል ተስፋዬ…? “ይሄንን እኔ አላልኩም” ካልክ እኔ ለማለት እገደዳለሁ…!(ፈገግታ))
እናም እኔ በበኩሌ የቁንድዶ ፈረስነትን አደንቃለሁ። አላማው ልክ ነው አይደለም የሚለው ጥያቄ በይደር ይቆይ። ነገር ግን በደል ሲበዛ “እምቢ” ማለት ከአባት የወረስነው ነው። ዛሬ የሽብረተኝነት አዋጅ ወጥቶ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ አንድ ዘፈን ትዝ ይለኛል…
“ደብቆታል መሰል ሶማ በረሃው
“እምቢ” ያለው ጎበዝ የታል ሽፈራው” የሚል ዘፈን።
በአሁኑ ወቅት፤ ይህንን ዘፈን በይፋ መዝፈን የሚቻል አይመስለኝም። ምክንያቱም በሽብርተኝነት አዋጁ አንድ ግለሰብ፤ በዘፈን በፅሁፍ እና በተለያዩ መንገዶች “ሽብርተኛን” እንኳንስ ሲያበረታታ ተገኝቶ ይቅርና፤ “አበረታቷል” ተብሎ ሲታሰብም “ጉዱ ይፈላል” ይላል። በተጨባጭ እንደምናየው ደግሞ እንኳንስ እምቢ ብለው ሶማ ጫካ ገብተው ይቅርና በከተማው ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች ራሳቸው “አሸባሪ” ስለመሆናቸው መረጃው አለ። ማስረጃው ጠፍቶ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩም እኛም የጨነቀን…! ስለዚህ “ደብቆታል መሰል ሶማ በረሃው እምቢ ያለው ጎበዝ የታል ሽፈራው…” ብሎ ማዜም አይቻልም ማለት ነው።
ለማንኛውም፤ ዘፈኑ ግን “እምቢ” ባይነትን እኔ ብቻ ሳልሆን ብዙሃን የሀገሬ ሰው እንደሚያደንቅ ያስረዳልኛል። አዎ አንዳንዴም እምቢ ማለት ጥሩ ነው። “እምቢ… እምቢ ለሀገሬ! እምቢ… እምቢ ለክብሪ! እምቢ… ታታታታ” ፉከራው ራሱ ማማሩ።
ስለዚህ ቐሽ ገብሩ፤ አሞራውና ሌሎችም “እምቢ” ባይ ታጋዮች “እምቢ” በማለታቸው አደንቃቸዋለሁ። እንኳንም እምቢ አላችሁ!
ወደ ቐሽ ገብሩ ስንመጣ የዶክመንተሪው አዘጋጆች ልብ ያላሉት ወይም ደግሞ “ምን ታመጣላችሁ” ብለው ችላ ያሉት አንድ ስህተት የፌስ ቡክ ወዳጆቼ አግኝተው ነበር። ልብ በሉልኝ ህውሃት ሆዬ ቐሽ ገብሩን መትረየስ ሲያሸክማት ገና የአስራ ሶስት አመት ልጅ ነበረች። ከፈለጋችሁ አስሉት በአስራ ዘጠኝ ስድሳ አንድ ተወለደች። በአስራ ዘጠኝ ሰባ አራት ወደ ትግል ገባች። ማነው ሂሳብ የሚችል…? በሉ እስቲ አስሉልኝ። ሰባ አራት ሲቀነስ ስድሳ አንድ እኩል ይሆናል፤ አስራ ሶስት። ዘጋቢው ፊልም ሲቀጥልም “…ትግሉን በተቀላቀለች በጥቂት ወራት ውስጥ እጇን ተመታች። እንደዛም ሆና መትረየስ ትሸከም ነበር።” ይላል። ጉድ በል ህውሃት…! አይሉኝም?
በዛ ሰሞን አለም ሲነጋገርበት ከሰነበተባቸው ነገሮች ውስጥ በኡጋንዳ የሚገኘው የሎርድ ሬዚስታንት አርሚ መሪ፤ ጆሴፍ ኮኒ ህፃናትን ጦርነት ውስጥ እየማገደ ነው በሚል ታድኖ ይከሰስ ዘንድ የተጀመረው “ኮኒ ሁለት ሺህ አስራ ሁለት” የሚል እንቅስቃሴ ነው። በአለም አቀፍ ህግ፣ አረ በኢትዮጵያ ህገ መንግስትም ቢሆን ህፃናትን ለጦርነት ማሳተፍ የለየለት ወንጀል ነው። በእግዜሩ ዘንድም ያስጠይቃል።
እና ህውሃት የአስራ ሶስት አመቷን ህፃን ሙሉ “ቐሽ ገብሩ” ን በጦርነት ማሳተፉ ሳያንስ የግፉ ግፍ ደግሞ ለማርች ስምንት የሴቶች መብት ክብረ በዓል ላይ ታሪኳን እንደ ጥሩ ነገር ዘገበልን። እውነቱን ለመናገር ይሄ ትልቅ የወንጀል መረጃ ነው። እንደኔ እምነት ይህንን መረጃ ያጠናከሩ ሰዎች የውስጥ አርበኝነት ስራ እየሰሩ ነው። ይሄ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ገና በርካታ መረጃዎችን ያወጣል። እዝችው ላይ ሙሉ ወይም ቐሽ ገብሩ ገና አስራ ስምንት አመት እንኳ ሳይሞላት አንድ ጎረምሳ በፍቅር ስም አስረግዞ እስከማስወረድ እንድትደርስ እንዳደረጋትም ዶክመንተሪው ይዘግባል። ሰውየው ከሷ ጋር ያሳለፈውን ፍቅርም ሲናገርም በኩራት ነው። እንዴት ነው ነገሩ… እኛ መሀሙድ አህመድ በአንድ ዘፈኑ ላይ “ሸግየዋ ጉብሊቷ… የአስራ አምስት አመቷ እንዴት ነሽ በሉልኝ የምታውቁ ቤቷን” ብሎ ስለዘፈነ አይደል እንዴ ከህፃናት መብት አንፃር ወንጀል ነውና ይቅርታ መጠየቅ አለበት እያልን የምንሟገተው? እንዲህ የባሰውን ነውር በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አየነው። ለዚህ ነው አይናችን የተርገበገው…?
ወዳጄ እንዴት ሰነበቱ አይገርምዎትም ይሄ ሁሉ መንደርርደሪያ መሆኑ… ይበሉ ወደ ዋናው ጉዳይ ተያይዘን እናምራ
እናልዎ… ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተለያየ ግዜ የተለያየ ዘጋቢም አወዛጋቢም ፊልሞችን ያቀርብልናል።
በዛ ሳምትን ያየነውም የቐሽ ገብሩ ዶክመንተሪም የዚሁ አካል ነው። እንግዲህ ከላይ ያነሳነውን በቐሽ ገብሩ የተጋለጠውን ህፃናትን ወደ ጦርነት የማሰማራት እና ለአቅመ ህይዋን ያልደረሱ ሴቶችን የማማገጥ ወንጀል እንዲህ ያለውን ጉዳይ ለሚከታተሉ አካሎች እንተወው እና የፈረደባትን ይቺን ህፃን “እምቢ” እንዳለች ጀግና እንቁጠራት። ቆጠርናት…!
ኢህአዴግ ደርግን ብዙ ግዜ ደርግ በጦርነት የማረካቸውን ታጋዮቼን የማያምኑበትን እንዲናገሩ ያሰቃያቸው ነበር፤ ከዛም እምቢ ሲሉት ያስራቸዋል፤ ይገድላቸዋል። ብሎ ይወቅሳል። ይቀጥልናም ቢሆንም ግን፤ “እንደ አሞራው ሁኑ እንደ ቐሽ ገብሩ ሁኑ ብሎ ይመክረናል። እኛም ምክር የምንሰማ ልባሞች ነንና እሺ ብለን እንደ አሞራው፤ እንደ ቐሽ ገብሩም ለመሆን እንታትራለን ከዛ ውጤቱ ምን ይሆናል አይሉኝም…? ለምን እጠይቅሀለው እያወቅሁት…? አሉኝ እንዴ!?
ሰሞኑን አቶ አንዷለም አራጌ ላይ የሆነውን ነገር ሰምተዋል። አንዷለም አራጌ እንደ አሞራው ሁኑ ከመባሉ በፊትም እንደ አሞራው “እምቢ” ባይ ነበር። ለዛውም ጫካ ሳይገባ ፊት ለፊት እምቢ ብሎ የተጋፈጠ ደፋር የተቃማዊ ፓርቲ አመራር ነው። ምን ዋጋ አለው አንዷለም እንደ አሞራው “እምቢ” ቢልም ኢህአዴግ ደግሞ እንደ ደርግ “እምቢ” ማለት አይቻልም ብሎ አሰረው። ማሰር ብቻ ቢሆን በስንት ጣዕሙ ጎረምሳ አስገብቶ አስደበደበው እንጂ!
ማርች ስምንት የአለም ሴቶች ቀን ነው። በአለም ላይ ያሉ ሴቶች ቀደም ሲል ሲደርስባቸው የነበረ ጭቆና ይብቃ የተባለበት ቀን። ይህ ቀን፤ የህውሃት ሴቶች ቀንም የአንድነት ሴቶች ቀንም፤ የጋዜጠኛ ሴቶች ቀንም፣ የሁሉም ሴቶች ቀን ነው።
ርዕዮት አለሙ አሳሪዎቿ የጠላነውን አብረሽን ከጠላሽ ትለቀቂያለሽ ብለዋት ነበር። ቃል በቃል ሲነገር “ኤልያስ ክፍሌ የተባለው ጋዜጠኛን አሸባሪ ነው መሰስክሪበት እና ትለቀቂያለሽ” ተባለች። እርሷም እኔ “በወንጀለኝነት አላውቀውም” ብላ ድርቅ አለች። እንግዲያስ ብሎ ኢህአዴግም አስራ አራት አመት ፈረደባት። ቐሽ ገብሩን ደርግ የያዛት ግዜ “የህውሃት ሰዎችን ወንጀለኛ ናቸው ብለሽ መስክሪባቸው” አላት እምቢኝ ብላ ድርቅ አለች ሞት ፈረደባት። እንግዲህ ቐሽ ገብሩ እና ርዮት አለሙ አንድ ናቸው “እምቢኝ” ብለዋልና። ደርግ እና ኢህአዴግስ…? የመጣው ይምጣ ደፍሬ ልናገር ነው..! አዎ ደርግ እና ኢህአዴግም አንድ ናቸው። እምቢ ያላቸው ላይ ሁሉ ይፈርዳሉና። በነገራችን ላይ የደርግ ፕሮፖጋንዳ ሰራተኞች ቐሽ ገብሩን ለማናገር መከራቸውን ሲያዩ የነበረውን ያህል የኢህአዴግ ጋዜጠኞችም በተደበቀ ካሜራ ሳይቀር ርዮትን ለማናገር አበሳቸውን ሲያዩ ነበር። ነገር ግን ቐሽ ገብሩም ርዮትም አለሙም ፍንክች የአባ ቢላው ልጅ ብለዋል። ወይ መገጣጠም…! አይሉልኝም?
እና ታድያ የሴቶች ቀን ክብረ በዓል ሲዘከር መንግስት ርዕዮትን አስሮ ስለ ቐሽ ገብሩ ሲተርክ የአራዳ ልጆች ሰሙ። ሰምተውም ጠየቁ “ሼም የለም እንዴ በአገሩ!?” አሉ ዝርዝር ያለው የስራ ሂደት ካለ መልስ ያምጣ…!
በጥቅሉ መንግስት እነ ርዕዮትን፣ እነ እስክንድርን፣ እነ ውብሸትን፣ እነ ሂሩትን፣ እነ አንዷለምን እነ ናትናኤልን፤ ስንቱን ጠርቼ እዘልቀዋለሁ? በጅምላው እምቢ ያሉትን ሁሉ እያሰረ እና እየገረፈ “ደርግ ታጋዮቼን አሰረ፣ ገረፈ፣ ገደለ” ብሎ ዋይ ዋይ ማለት ውሃ የማያነሳ ወቀሳ ነው። መፅሐፉም ይላል “የሌሎችን ጉድፍ ከማየትህ በፊት በአንተ አይን ውስጥ ያለውን ቆሻሻ ተመልከት…”
በመጨረሻም
ያወጋነውን ለፍሬ ይበልልን
አማን ያሰንብተን!

ለትግራይ መገንጠል እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች

    

ዛሬ ትግራይ ከማናቸውም የኢትዮጵያ ጠ/ግዛቶች በበለጠና በተለየ የስስት አይን ስለምትታይ መፈክሩ “ ሁሉም ነገር ወደ ትግራይ” ሆኗል ። በትግራይ የሚሰሩት የአየር ማረፊያዎች ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሞች ፤ የመገናኛ መንገዶች ፤ የውሃ ግድቦች ፤ ከመሃል አገር እየተነቀሉ ወደ ትግራይ የተጓዙት የጨርቃ ጨርቅ ፤ የሲሚንቶ፤ የመድሃኒት ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ግንባታዎች ፤ የአውቶሞቢል መገጣጠሚያዎች ፤ ከብዙ በጥቂቱ ለአብነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ ፤ በአንፃሩ ለተቀሩት ጠ/ግዛቶች የሚደረግ ግንባታ አይታይም ፤ ካለም ከትግራይ ልማት ጋር ሲነፃፀር እጅግ በጣም ያነሰ በመሆኑ ልማት ተደርጓል ለማለት አያስደፍርም ። ትግራይን እንደ ወለዱት ልጅ ሲንከባከቡ የተቀረውን ግን በገዛ ሀብቱ እየተንደላቀቁና እየተጠቀሙ እንደ እንጀራ ልጅ ማየታቸው አሳዛኝ ትርኢት ሆኖ አግኝቼዋለሁ ።
በእርግጥ አሁን ያለው አገዛዝ ለግንጠላው መሰናዶ የተቀረውን የኢትዮጵያ ክፍል አለ ሃፍረት እንደ ጥገት ማለቡን እንደቀጠለ ይገኛል ፤ በአንዲት ትልቅ አገር አንጡራ ሀብት ያለ ከልካይ እየተዘረፈ አንዲት ትንሽ ጠ/ግዛት መገንባቱ ፤ አንድን ክፍል እያስተማሩ ሌላውን በድንቁርና ማስቀመጡ ፤ አንዱን እያበሉ ሌላውን ማስራቡና ያልተመጣጠነ አድሎአዊ የሆነ አሰራር የሚካሄደው አገሬ ብሎ ተቆርቁሮ ተደራጅቶ የተነሳ ተቃዋሚ እንደሌለ በማወቃቸው ፤ ጊዜና ሁኔታዎችም ስለተመቻቹላቸው ጭምር እንደሆነ ይታወቃል ፤ ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም ህልማቸውን እውን ለማድረግ እንደ መዥገር ተጣብቀው መመጥመጡን በሰፊው ተያይዘውት እናያለን ።
እንደዚህ ያለ ወርቃማ አጋጣሚ በሚሊዮን ዓመት አንድ ጊዜ እንኳን የማይከሰተውን በነሱ ጫማ ሆኖ ለሚመለከት አጥፊ ህሊና ላለው እንዴት የሚያጓጓና የሚያስመረቅን ሊሆን እንደሚችል በገመትም አያዳግትም ።
እንግዲህ ወያኔዎች ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ጀምሮ ምኞታቸው ኤርትራን ከማስገንጠል ባሻገር እነሱም ትግራይን ገንጥሎ ለመሄድ ስለሆነ ፤ እኛ ታላቋ ኢትዮጵያ ፤ አንድ ኢትዮጵያ እያልን ስለምናለቅስላት አገር ፍቅርም ፤ ደንታም እንደማይኖራቸው ማወቅና መረዳት የግድ ይላል ።
ባጋጣሚ ኢትዮጵያ አገራችን ዛሬ ጠባቂና ዘበኛ ባጣችበት ወቅት ስለመጡ ሀብት ንብረቷን ፤ ቅሪቷን ፤ ዘርፎ አገሪቷን በጎሳ ፤ በሃይማኖትና በመሳሰሉት ከፋፍሎ በለስ ቀንቷቸው እነሱ ወደሚሄዱበት በሚሄዱበት ወቅት ላላማቸው መሳካት የተቀረው ኢትዮጵያዊ እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ፤ ማለትም የሚያስገነጥሉትን የትግራይ ጠ/ግዛት አለ አንዳች ስጋት መገንባትና ማጠናከር ያስችላቸው ዘንድ ቀደም ብለው ስልጣኑ ላይ እንደተፈናጠጡ ሲሰሩበት የቆዩበት የረጅም ጊዜ ውጥን እንደሆነ ይታወቃል ። ይህንን ዓላማቸውን እንኳን የማስተዋያ አይምሮ ያለው የሰው ልጅ ቀርቶ ፤ ሳር የሚግጡት እንሰሳትም በውል የሚያውቁት ተግባር ነው ብል ነገሩን ማጋነን አይመስለኝም ።
ወያኔዎች ዛሬ ኢትዮጵያዊው የደከመ ኃይል መሆኑን በመረዳታቸው ከጎንደርና ከወሎ ሰፊና ለም የሆኑ ቦታዎችን ቆርሰው ወደ ትግራይ ጠ/ግዛት ቀላቅለዋል ። ከነዚህም ከጎንደርና ከወሎ የተወሰዱ ቦታዎች ላይ ነዋሪ የነበሩትን ዜጎቻችንን በማፈናቀል ፤ ሴቶችና ልጃገረዶችም ከትግራይ ወንዶች በግድ እንዲወልዱ በማስገደድ ፤ በመድፈር ፤ የአካባቢውን ነዋሪ ሕዝብ በትግሪኛ ተናጋሪው ለመተካት የተደረገው የቅኝ ገዢዎችን መርሆ የተመረኮዘ ፋሽስታዊ አሰራር ስንመለከት ለግንጠላውና ድብቅ ላልሆነው አላማቸው ምን ያክል ጠንክረው እየሰሩ እንደሆነ ይመሰክራል ።
እነዚህ የጥፋት መልዕክተኞች ለኢትዮጵያ ካላቸው ጥላቻ በመነሳት ፤ ለወደፊትም ሕዝብ ከተባበረ ለምኞታቸው እንቅፋት እንደሚሆንባቸው አስቀድመው ስላወቁ ከፈጠሩት የጎሳና የሀይማኖት ቅራኔ ባሻገር ፤ የጎረቤት አገርም እነሱ በሚሄዱበት ወቅት በቀሪው የኢትዮጵያ ክፍል ላይ ቂም በቀል ይዞ በሕዝባችን ላይ እንዲነሳ ፤ በአረጋችን ላይ መረጋጋት እንዳይኖር ለማድረግ ፤ ዛሬ ሱማሊያ ውስጥ በኢትዮጵያ ሥም በመግባት የሚያደርሱት ኢሰብአዊ ጭፍጨፋ ነገ ሱማሌ እራሷን ስትችል ይህንን ቂም በማዘል በሐገራችን ላይ የሚኖራት አመለካከትና በሐገራችንም ሰላም እንዳይኖር ልታደርግ የምትችለውን ጥፋት ከወዲሁ ለመስራት ታቅዶ የታወጀ ጦርነት እንደሆነ ማወቁ ተገቢ ነው ።
ይህ ለወደፊት ግንጠላውን እውን አረጋለሁ ለሚለው ወያኔ የጊዜ መግዣና የመጠናከሪያ ስልት መሆኑ ታምኖበት በጥናትና በዘዴ የተፈጸመ ወረራ መሆኑን ለመረዳት ነብይነትን አይጠይቅም ።
ወያኔዎች በዚህ ተንኮል ብቻ አላበቁም : ባራቱም ማዕዘን ለኢትዮጵያ ጠላት መሸመቱን በሰፊው ተያይዘውታል ፤ በምዕራብ ኢትዮጵያ ከጎንደር እስከ ጋምቤላ ድረስ እርዝመቱ 1600 ኪ/ሜትር የሆነና ጥልቀቱ ደግሞ ከ 30 እስከ 50 ኪ/ሜትር የሚደርስ ለምና በተፈጥሮ ማዕድናት የዳበረ መሬታችንን በማናለብኝነት ለሱዳን መንግሥት አሳልፎ ሰጥቷል ። የሱዳን መንግሥትም ለተደረገለት መልካም ስጦታ አጸፋውን ለመመለስ ለወደፊት በወያኔ ሂሳብ ትግራይ እራሷን ከኢትዮጵያ ገንጥላ እንደ አንድ አገር ትቆማለች ብሎ ለሚያስባት እንደ ዋና የንግድ በር ሆኖ የሚያገለግል ከፖርት ሱዳን ተነስቶ አዲግራት የሚደርስ የባቡር ሀዲድና በተጨማሪም ሱዳንና ትግራይን የሚያገናኝ ትልቅ የአውራ መንገድ ለመዘርጋት የሱዳን መንግሥት ቃል እንደገባላቸው ተዘግቧል ።
ይህን ሁሉ ወንጀል በአገራችን ላይ የፈጸመው ወያኔ እስካሁን የሰራው ጥፋት ሁሉ አላረካ ብሎት ፤ ዛሬ የሐገራችን አርሶ አደር ገበሬ እራሱንና ቤተሰቡን ከመመገብ አልፎ ለህብረተሰቡ ይተርፍ የነበረውን ፤ በማዳበሪያ እዳና በጥላቻ ፖለቲካ የተነሳ ገበሬው በየምክንያቱ አርሶ መብላት እንዳይችል አድርጎት ለረሃብ እንደዳረገው እያየን ነው ።
በሌላው ወገን ደግሞ ይህ ገበሬ እንዳያርሰው የተደረገውን መሬት ለጅቡቲና ለሳውዲ አረቢያ መንግሥታት አልምተው ሕዝባቸውን መመገብ ይችሉ ዘንድ በማለት ከሐገራችን ገበሬ ቀምቶ ለባዕዳን መንግሥታት በብዙ ሺህ ሄክታር የሚቆጠር ለም ቦታዎችን እየቸበቸበው ይገኛል ። “የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች” ይሏል ይሄ ነው ።
እንግዲህ ኢትዮጵያ በመሃል አገር በጎሳና በሃይማኖት ልዩነት እንዲጨራረስ ሆን ተብሎ በገዢው ክፍል እየተቆሰቆሰና እየተበረታታ ባለበት ሁኔታ ፤ በሌላው ወገን ከጎረቤት አገሮች ጋር በሰላም መኖር እንዳይቻል በምስራቁም በምዕራቡም የጠላት አይነት እየመለመለልን ባለበት ወቅት ፤ ዛሬ ደግሞ ከኤርትራ ጋር የጦር ፍልሚያ ለማድረግ ደፋ ቀና ማለት አላማው ለምን ይሆን?
በእውነት ኢትዮጵያዊነት የማይሰማቸው ወያኔዎች ዛሬም ለባድሜና ለዛላምበሳ በምናደርገው ጦርነት ኑና ሙቱልን ብለው የኢትዮጵያን ሕዝብ በድፍረት ይጥሩት? “ያሁኑ ይባስ” ይላል ያገሬ ሰው ነገር አልጥም ሲለው ፤ የሚሉን እኮ “ከባልሽ ባሌ ይበልጣልና ሽሮ አበድሪኝ” ነው ጎበዝ? እጅግ ተንቀናል የሚሉን ከገባን ።
እውነት ሻቢያና ወያኔ እኛ እንድንቀበላቸው እንደሚፈልጉት በጠላትነት አይን የሚተያዩ ናቸው ? ወይስ ለኛ ግልጽ ያልሆነልን ድራማ እየሰሩብን ነው?
የኢትዮጵያ የሆነው ለም መሬት ተቆርሶ ለሱዳን ሲሸጥ ፤ ለሳውዲ አረቢያና ለጅቡቲ ሲለገስ ፤ ታዲያ ለኤርትራስ ለምን እንደ ሌሎቹ ድርሻዋ አይሰጣትም?
ወያኔዎቹ የሚሉን የመሬት ስጦታው ከኢትዮጵያ ተቆርሶ እንጂ ከትግራይማ እንዴትስ ተሞክሮ ! መታሰቡስ ! ነው የሚሉን ? “ኢትዮጵያ የጋራችን ትግራይ የግላችን” አይገርምም ? ይሄ አድራጎታቸው እራሱ ወያኔዎች ኢትዮጵያን እንደ አንድ የባዕድ አገር የሚመለከቱና ስለ ኢትዮጵያ ግድ እንደሌላቸው መሆናቸውን ነው ። አገራችን የሚሉት ትግሬን እንጂ ኢትዮጵያን እንዳልሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መስታወት ነው ።
የሻቢያ የመሬት ጥያቄው ከትግራይ ጠ/ግዛት ባይሆንና ጥያቄው ከባሌ ወይም ከጅማ መሬት ማግኘት ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ ጅቡቲና ሳውዲ አረቢያ መንግሥታት አይንህ እስካየ ፈረስህ እስከጋለበ ያንተው ነው ተብሎ ተመርቆ ይሰጠው እንደነበረ ለማንም የተሰወረ አይደለም ። ችግሩን የፈጠረው ከትግራይ መሬት የመጠየቁ ጉዳይ ነው ።
ታዲያ ዛሬ በምዕራቡ ኢትዮጵያ ያለው ሕዝባችን አገሬንና ዳር ድንበሬን አላስነካም ፤ አላስደፍርም ፤ ብሎ ከድርቡሽ ጦር ጋር በሚዋደቅበት ባሁኑ ጊዜ ፤ ከፊቱ የድርቡሽ ጦር ከኋላው የወያኔ ጦር መሃል አስገብተው እየቆሉት ባናቱ ላይ እንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች እሳት ሲያነዱበት እንዴትና በምን ሂሳብ ቢታሰብ ነው ታዲያ ዛሬ ለባድሜና ለዛላምበሳ ሕዝባችን መስዋዕት እንዲከፍል የሚጠየቀው?
እንግዲህ ይህ በኢትዮጵያ ሥም የተቋቋመው የጦር ሠራዊት ባንድ ወገን ዳር ድንበሬን አላስደፍርም በማለት የሠራዊቱ ተግባር የነበረውን ሥራ እየሰራ ያለውን ዜጋችንን ከድርቡሹች ጋር አብሮ እየወጋ ፤ በሌላ በኩል ባድሜን ከወራሪ ለመጠበቅ ጥሪ አለብኝና ተባበሩኝ ብሎ ለሕዝብ ጥሪ ማቅረብ ኢትዮጵያዊውን ከመናቅ የመጣ ነው? ወይንስ ለቀልድ የተሰነዘረ ማላገጥ?
በወያኔ ጭንቅላት ስሌት ሳይሆን በንጹህ ኢትዮጵያዊ አይምሮ ቢታሰብ በአንድ ወገን አገር ቆርሰው ያውም ለሙን መሬት እየሰጡ ፤ በሌላ ወገን ድንበሬ ተገፋ እያሉ ለሱዳን ከሰጡት መሬት በለምነትም ሆነ በስፋቱ እምኑም የማይደርስ ቁራሽ መሬት ከሻቢያ አስጥላልሁ ብሎ ያገር አድን ጥሪ እያሉ ሆያ ሆዬ መጨፈር ሚስጥሩ ሊገባኝ አልቻለም ።
ለጎረቤት አገሮችም ሆነ ባሕርና ውቅያኖስ አቋርጠው ለመጡ የውጭ መንግሥታት አገር እየተሸነሸነ በሚሰጥበትና በሚቸበቸብበት በወያኔ አገዛዝ ዛሬ በድንበሬ ተገፋ ሳቢያ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም ለምን አስፈለገ? ኢትዮጵያዊው በርግጥ ጦርነት ማድረግ ካስፈለገው ጦርነቱን ማድረግ ያለበት ከወያኔ ከራሱ ጋርና ከድርቡሾች ጋር እንደሆነ ሕዝባችን ጠንቅቆ ያውቀዋል ።
ባገር ተወረረ ሳቢያ ፤ በውዴታ የመጣን ጦርነት አንተርሶ ዛሬም ወያኔ እራሱን እንዳንታገለው ለኢትዮጲያ አንድነትና ዳር ድንበር አሳቢና ተቆርቋሪ በመምሰል ጦርነቱን ደጋፊና ፤ ጦርነቱን ተቃዋሚ በሚል ውዥንብር በሕብረተሰቡ ውስጥ በመንዛት ወደሱ የተነጣጠረውን ትግላችንን ለማዳከሚያና ትግሉን ለመከፋፈያ ሊጠቀምበት እንደሚፈልግ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ልብ ሊሉት ይገባል ።
ይህንን የማዘናጊያ ጦርነት አላማውን ተገንዝበን ወያኔ ከሕዝብ ሊያገኝ የፈለገውን ድጋፍ እንዳያገኝ ጠንክሮ በመስራት በጸረ ወያኔነት የተሰለፈ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ግዴታ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል ።
ነገሮች በየ ቀኑ እየተለዋወጡና መልካቸውን እየቀየሩ በመምጣታቸው እኛም በየጊዜው ወያኔ አጀንዳ እያቀረበልን ትኩረታችንን በመሳት የወያኔ ሰለባ ከመሆን እራሳችንን መጠበቅ ይኖርብናል ።
ይህ ጸረ ሕዝብና ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ አገዛዝ ስር እየሰደደ ፤ ኢትዮጵያዊነት ደብዛው እየጠፋ መጥቷልና የምንሰራውንና የምንቃወመውን በሰከነ አይምሮ መርምረን መንገዳችንን ማስተካከል ተገቢ ነው ። አገሬ ብለን የምንጠራት ፤ ለልጆቻችንና ለልጅ ልጆቻችን የምናስተላልፋት ፤ ኢትዮጵያ የምትባል አገር የመኖር አለመኖር ህልውናዋ ከምን ጊዜም በላይ አሳሳቢ እየሆነ ስለመጣ ፤ ነገ ሳይሆን ዛሬ ፤ ሳይመሽብን ስለ ሐገራችን መምከር ፤ መወያየት ጊዜ ልንሰጠው የማይገባ አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑን አምነንበት ከምን ጊዜውም በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘን ጠንክረን መስራት ይጠበቅብናል እላለሁ ።
ድል ለሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ !

በኦህዴድ ውስጥ ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ የታየው ክፍተት እየሰፋ ነው።

     

በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የውስጥ ሽኩቻ መበራከት የተነሳ ኢህአዴግ እንደ ድርጅት አንድ ሆኖ መውጣት እንደተሳነው የሚያመለክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው።
በህወሀት ውስጥ ሁለት ቡድኖች ድርጅቱን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ መጀመራቸው ከተዘገባ ከወራት በሁዋላ ችግሩ ከመቃለል ይልቅ እየጨመረ መምጣቱን አንድ የቀድሞ የህወሀት ነባር ታጋይ ለኢሳት ዘጋቢ ገልጸዋል።
ነባር ታጋዩ፤ በአቶ ስብሀት ነጋ በኩል ባሉ ሰዎች ወደ ድርጅቱ እንዲመለሱ ጥሪ ቀርቦላቸው እንደነበር ጠቅሰው፤ እርሳቸው ግን አሻፈረኝ ማለታቸውን ገልጸዋል።
በድርጅቱ ውስጥ የሚታየው ክፍተት ለአደባባይ ባይበቃም፣ ህዝቡ የሚያየውና እየተነጋገረበት ያለ ጉዳይ መሆኑን ነባር ታጋዩ ገልጸዋል።
በኦህዴድ በኩል ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ የታየው ክፍተትም እየሰፋ እንጅ እየጠበበ ሲሄድ አለመታየቱ ነው የተገለጸው።
ከአንድ ወር በፊት የጨፌ ኦሮሚያ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት በድርጅቱ ውስጥ የሚታየው ሙስና እና ጎሳዊነት እንደጨመረና ድርጅቱንም አደጋ ላይ እንደጣለ አንዳንድ የምክር ቤቱ ተወካዮች ቢናገሩም፣ ምክር ቤቱ በስፋት እንዳይወያይበት መደረጉን በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።
በተለይም በከፍተኛ ህመም የሚሰቃዩትን ፕሬዚዳንቱን አቶ አለማየሁ አቶምሳን ለመተካት ቢፈለግም፣ በእርሳቸውና በአፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ ደጋፊዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ሌላ ፕሬዚዳንት ለመሾም ሳይቻል በመቅረቱ አቶ አለማየሁ በስልጣን ላይ እንዲቆዩ ተደርጓል።
በኦህአዴድ ስራ አስፈጻሚዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ተባብሶ በዞን ደረጃ ያሉ ስራ አስፈጻሚዎች ሳይቀሩ እንደተከፋፈሉና አጠቃላይ ድርጅቱ ወደ ሞት እያመራ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም።
ሪፖርተር ዛሬ ባወጣው ዘገባ ደግሞ ኦህዴድ የካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔውን ለማድረግ የተሰበሰበ ቢሆንም ፤ያልተጠበቁ አጀንዳዎች በመቅረባቸው ፤ ለኢሕአዴግ በሚቀርበው የሁለት ዓመታት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ብቻ በመወያየት ጉባዔውን ለሚቀጥለው ሳምንት አስተላልፎአል።
የ ኦህዴድ አባላት፤ ድርጅታቸው የተለያዩ ችግሮች ስላሉበት ጉዳዩ በአጀንዳ ተይዞ ውይይት እንዲደረግበት ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ ሰብሳቢዎች በድጋሚ ሌላ ስብሰባ እንደሚደረግና በዚያ ስብሰባ ላይ <<አሉ>> የተባሉ ችግሮችን በማንሳት መወያየትና መፍታት እንደሚቻል ቢናገሩም፣ ስምምነት ላይ አልተደረሰም ብሎአል- ጋዜጣው።
አባለቱ፤ ችግሩ የሕልውና ጉዳይ መሆኑን ደጋግመው በመግለጽ ራሱን የቻለ አጀንዳ ተይዞለት ውይይት እንዲደረግበት ቢጠይቁም፣ እንዲሁም የተወሰኑ አባላት ድርጅቱ በሁለት ዓመታት ውስጥ ባከናወናቸው ሪፖርት ውስጥ የተነሳው ጥያቄ ተካቶ አንድ ላይ እንዲታይ ሐሳብ ቢያቀርቡም ፤ስምምነት ላይ ስላልተደረሰ ነው ጉባዔው እንዲተላለፍ የተደረገው።
ሥራ አስፈጻሚው፤ ለኢሕአዴግ በሚያቀርበው የሁለት ዓመታት ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሲወያይ በዋናነት ያነሳቸው ችግሮች፣ በድርጅቱ ውስጥ የአመራር ችግር መኖሩን፣ እንደ ድርጅቱ ሳይሆን በግል የመጠቃቀም ሁኔታ መባባሱን፣ ለሥልጣን መሯሯጥ መስተዋሉን፣ ድርጅት ሳይመክርበት የፍርድ ቤት ሹማምንት ከኃላፊነት እንደሚነሱ መደረጋቸውን እና የግለሰቦች አምባገነንነት መንገሱን የሚመለከቱ ናቸው።
አባላቱ በችግሮቹ ዙሪያ ከተወያዩ በኋላ፣ የተፈፀሙት ድርጊቶች ተገቢ እንዳልሆኑ መተማመናቸውን ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።
ከዚህም ባሻገር የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ከድርጅት ተባረው አገር ጥለው መጥፋታቸው እንዲሁም በድርጅቱ ውስጥ በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮች መንግስት የሚከተለውን ፖሊሲ መቃወም መጀመራቸው በኦህዴድ ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግም ውስጥ ትልቅ ራስ ምታት ፈጥሯል ተብሏል።
ለኢሳት ቅርበት ያላቸው የኢህአዴግ ሰዎች እንደገለጡት፣ በርካታ የኢህአዴግ በተለይም የኦህዴድ አባላት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የጀመሩትን እንቅስቃሴ ከመደገፍ አልፈው በተለያዩ መንገዶች አስተዋጽኦ እያደረጉ ነው።
በኢህአዴግ ውስጥ የሚታየው ልዩነት ያሳሰበው ሪፖርተር ጋዜጣ ዛሬ በርእሰ አንቀጹ ድርጅቱ በመጪው ጉባኤ አንድ ሆኖ በመውጣት ለአገሪቱ የተጠናከረ አመራር እንዲሰጥ ተማጽኗል።
ጋዜጣው ” ሁኔታዎች እየከበዱና እየተካበዱ ናቸው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም በአገር ደረጃም የኢኮኖሚው ሁኔታ አሳሳቢ እየሆነ ነው፡፡ ምንም እንኳ አሁንም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ዕድገት ለማስመዝገብ የሚያስችል አመቺ ሁኔታ ቢኖርም፤የውጭ ምንዛሪ እጥረትን፣ ግሽበትንና የኑሮ ውድነት ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም፤ ለተጀመሩና ለታቀዱ ዓበይት ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ በቂ ገንዘብ አግኝቶ መተግበር ትልቅ ፈተና ነው” ብሏል።
የመልካም አስተዳደር መጥፋት፣ የአቤቱታ ብዛትና የሰሚ እጦት እጅግ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱንም አልሸሸገም።
ጋዜጣው አያይዞም፦ ” መጪው የኢህአዴግ ጉባኤ ጠንካራ ኢሕአዴግና ጠንካራ መንግሥት ፈጥሮ፤ ጠንካራ መፍትሔ በመስጠት እንደ አንድ ኩሩ ሕዝብ እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንቀጥል ማድረግ ይጠበቅበታል ፣ህዝብም ጠንካራ ኢሕአዴግ ከጉባዔው እውን እንዲሆን ይጠብቃል” ብሎአል።
በሌላ በኩል ደግሞ በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች የኢህአዴግን መዳከም በመጠቀም ወደ አንድነት ጎዳና በማምራት ለለውጥ መስራት እንዳለባቸው ከተለያዩ ወገኖች ጥሪ እየቀረበ ነው።
በቅርቡ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች በተካሄደ የኢሳት ገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት ላይ የተገኙ ኢትዮጵያውያን፤ ኢሳት ሁሉንም ተቃዋሚዎች በአንድ ጉባኤ በመጥራት አብረው እንዲሰሩ ግፊት እንዲያደርግ ተማጽነዋል።
ኢሳት ዜና:

Wednesday, March 6, 2013

በባለፈው አመት የአሳሳ ግርግር የታሰሩ ከ45 በላይ ሙስሊሞች ተፈረደባቸው፡፡


ድምፃችን ይሰማ
ፍርዱ ከሁለት አመት እስከ አስራ አንድ አመት ይዘልቃል፡፡
ባለፈው ዓመት በኦሮሚያዋ አርሲ ዞን አሳሳ ከተማ ፖሊስ በመስጊድ ውስጥ ባስነሳው ግርግር ታስረው የነበሩ ወደ 48 የሚደርሱ የከተማዋ ሙስሊሞች ከፍተኛ ፍርድ ተፈረደባቸው፡፡ ውሳኔው የመንግስትን ጸረ ሙስሊም እንቅስቃሴ ገላጭ ተብሎለታል፡፡ በወቅቱ በተነሳው ግርግር የአራት ንጹሀን ሰዎች ሕይወት በፖሊስ ጥይት መጥፋቱ የሚታወስ ሲሆን በግርግሩ ሰበብም የታሰሩ ሴቶችን ጨምሮ ወደ 53 የሚጠጉ ሙስሊሞችም በሻሸመኔ ወህኒ ቤት የይስሙላውን ፍ/ቤት ጉዳይ ሲከታተሉ ቆተው ዛሬ የመጨረሻ ፍርድ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በዚህም መሰረት ከ53 ታሳሪዎች 2 ሴት እና 3 ወንዶች በጥቅሉ 5 ሰዎች ከአንድ አመት እስር በኋላ በነጻ ሲሰናበቱ የጠቀሩት 48 ሙስሊሞች ከሁለት አመት እስከ አስራ አንድ አመት በሚዘልቅ እስር ብይን ተሰጥቶባቸዋል፡፡በባለፈው አመት የአሳሳ ግርግር የታሰሩ ከ45 በላይ ሙስሊሞች ተፈረደባቸው፡፡
ፖሊስ ግርግሩ እንዲነሳ ምክንያት አድርጎ የጠቀሳቸውና የህጻናት የቁርአን አስተማሪ የሆኑት ሼኸ ስኡድ ይህ ነው በማይባል ማስረጃ አስራ አንድ አመት ከሦስት ወር የተፈረደባቸው ሲሆን፣ ሼኸ አብደላ ኪኒሶ ሶስት አመት ከስድስት ወር፣ ሼኸ ሁሴን ሶስት አመት ከስድስት ወር የተፈረደባቸው ሲሆን የተቀሩት 45 ሙስሊሞች እያንዳንዳቸው የሁለት አመት ከሶስት ወር እስር ተበይኖባቸዋል፡፡ የዛሬውን ችሎት ለመታደም በሻሸመኔና ዙሪያዋ የሚገኙ በርካታ ሰዎች የተገኙ ሲሆን የፍ/ቤቱ ውሳኔ ሲሰማም በአካባቢው ከፍተኛ የሀዘን ድባብ ተፈጥሮ እንደነበር ተሰምቷል፡፡
በፎቶው ላይ የሚታዩት በዛሬው እለት ብይን የተሰጠባቸው የአሳሳ ሙስሊሞች ናቸው፡፡
አላሁ አክበር!

የህወሓት/ኢህአዴግ የውስጥ ፍጥጫ፣ ዴሞክራሲን አይወልድም የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

    
የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) በአገራችን ውስጥ ተንሰራፍቶ ያለው አምባገነን አገዛዝ ሕዝባችንን ከዕለት ወደ ዕለት ለከፋ ስቃይ እየዳረገው እንደሆነ በተደጋጋሚ አስገንዝቧል። አሁን ደግሞ አምባገነኑ አገዛዝ እራሱ ሊወጣ ወደማይችልበት ከፍተኛ ችግር ውስጥ እየተዘፈቀ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ሆኗል።የመለስ ዜናዊን ህልፈት ተከትሎ በህወሓት/ ኢህአዴግ ውስጥ የሚታየው ግልፅ ሽኩቻና ፍትጊያ እጅግ እየተፋጠነ መሄዱ ይህንኑ ሃቅ ያረጋግጣል።
ይህንን ፉክክር የሚያካሂዱት የድርጂቱ አባላት በተወሰነ ደረጃ ይቀያየሩ እንጂ፣ በመሠረታዊነት ቢያንስ ሁለት ቦታ ተፋጠው የሚገኙ ቡድኖች መከሰታቸውን መገንዘብ ይቻላል።
አንዱ ቡድን ሌላውን በሙስና፣ በጎታችነት ወይም ደግሞ ህወሓትን በመክዳት… ወዘተ ይከሳል። የተወሰኑት ደግሞ በሁለቱ ካምፕ ውስጥ የተፈጠረውን ቀውስ ከህዝብ ደብቆ ለመጓዝ እየጣሩ ቢሆንም፣ ችግሩ ግን ወደ ሕዝብ ጆሮ ደርሶ ፀሐይ ከሞቀው ውሎ አድሯል።
የዚህ ከፍፍል አንዱና ዋና ተዋናኝ የሆነው ስብሀት ነጋ ለመገናኛ ብዙሀን በቅርቡ በሰጠው መግለጫ በህወሓት/ ኢህአዴግ ውሰጥ ምንም ዓይነት ልዩነት እንደሌለና ልዩነት ቢኖርም “በዴሞክራሲያዊ መንገድ” እንደሚፈታ ለመግለጽ ሞክሯል። ይሁን እንጂ ወዲያውኑ “መለስን የሚተካ የህወሓት ሰው ለምን አልተገኘም? ለምን ሃይለማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚኒስተር ሆኖ ተመረጠ?” የሚል ከፍተኛ ጥያቄ በህዝቡ ውስጥ እንዳስነሳ ከትግራይ የሚተላለፈው ሬዲዮ በድንገት ሳያስበው አሰራጭቷል።
ይህ የሚያሳየው የህወሀት/ ኢህአዴግ መሪዎች አሁንም እንደ ልማዳቸው በውሰጣችው ያለውን ቀውስ ከህዝብ ደብቀው ለመቀጠል ቢፍጨረጨሩም ከቶውንም እንዳልሆነላቸውና ሽኩቻውን አጠናክረው እንደቀጠሉ መሆኑን ነው። ፍጥጫው እጅግ የከረረ ሲሆን ልዩነት መኖሩን በግልፅ የሚያምኑት ግን እንደተለመደው ጠንካራው ወገን ሌላውን የማባረር፣ የማሰርና ካስፈለገም የማጥፋት ዕቅዱን ይፋ ማድረግ ሲጀምር ነው።
በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች (ህወሓት፣ ኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴን) ውስጥ የሚገኙ ሁሉ ድርጅቶቻቸውን ለረጅም ጊዜ ከተዘፈቁበት አረንቋ ውስጥ በማውጣት የሀገራችን ክብርና የህዝባችን መብት ያረጋገጠ መሠረታዊ ለውጥ እንዲመጣ እንዲታገሉ በዚህ አጋጣሚ ሸንጎው ጥሪውን ያቀርባል።
ሸንጎው የሚሻው መሠረታዊ ለውጥን እውን በማድረግ ቂም በቀል የሌለባት፥ ሁሉንም ዜጎች እኩል የምታሰተናግድ፥ አድልዖ የሌለባት የሁሉም ዜጋ መብት የተረጋገጠባት፥ የህግ የበላይነት የሰፈነባት አንድነቷ የተጠበቀባትና ዜጎቿን ሁሉ የምታኮራ ኢትዮጵያን በጋራ እውን ማድረግ ነው። በዚህ ተጠቃሚ የሚሆነው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው።
ይህን ዓይነት ሀገርንና ህዝብን የሚጠቅም ለውጥ ለማምጣት የሚቻለው ደግሞ የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ሲቻል ብቻ መሆኑንም ሸንጎው ለማሳሰብ ይወዳል። እነዚህም፦
  1. ስብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የሚያግዱ አፋኝ ህጎች ሲሰረዙ፥
  2. ሁሉም የኅሊና እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሲፈቱ፥
  3. ፍርድ ቤቶች ከፖለቲካ ቁጥጥር ነፃ ሲሆኑና ፍትህ እንዲሰፍን ሲደረግ፥
  4. ሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያሳትፍ በሀገራዊ መግባባት ላይ የተመሠረተ የሽግግር ሂደት እንዲኖር ሲደረግ ነው ።
በህወሓት/ኢህአዴግ ውስጥ የሚካሄደው የርስበርስ ትርምስ የትኛውም ቡድን አሸናፊ ሆኖ ቢወጣ ከላይ የተዘረዘሩት ሁኔታዎች እስካልተሟሉ ድረስ አገሪቷ ላይ የሚደርሰውን የቀውስ አደጋ ሊቀለብስ አይችልም። የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሻው መሠረታዊ ለውጥን ነው። ከዚህ ሌላ ግን የአበው ብሂል እንደሚያሰተምረን “ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም” ከሚለው የዘለለ ሊሆን አይችልም።
ስለሆነም ወገናችን የናፈቀውን መሠረታዊ ለውጥ በአጭር ጊዜ ውስጥ እውን ለማድረግ የተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ መታገል የግድ ነው። ከዚህ ሌላ አማራጭ እንደሌለ በመገንዘብ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) ትግላችንን በጋራ እንድናካሂድ በተደጋጋሚ ላቀረበው ጥሪ ተቃዋሚ ኃይሎች አወንታዊ ምላሽ እንድትሰጡ በዚህ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳልን።
የሕዝብ ድምፅ የማይሰሙ አምባገነኖች መጨረሻቸው ውድቀት ነው!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Let the evidence speak: Three-Decade TPLF’s Deception and Disinformation Strategy


by Ewnetu Sime
Tigrai People’s Liberation Front (TPLF) is “celebrating” thirty eight years birth of their mob rule style at Mekele town.ethiopian national flag The on going discussions of the issues are not known to general public, at least to my knowledge. But it is expected that they will be confined to dogmatic ethnic politics and then viciously slandered one another to win the power struggle among themselves. TPLF survived all these years through deception or coercion and frequently by brutal force. They had political and ideological differences within their guerrilla warfare years. Through violent internal purges or dissention, execution and finally the current ethno-centric TPLF’s leaders came out as winner. The present leaders continued the ethnic based authoritarian rule and eroded Ethiopian nationalist identity. A long Ethiopian history of cultural awareness is weakening through deception and disinformation strategy. They are attempting to rewrite history based on lies and political propaganda ploy.
As we witnessed and observed when the Derg dictatorship nears its terminal stage, TPLF realized a symbolic strategy is needed to seize power. They formed a ridicule united front with Oromo Liberation Front (OLF), EPDM the defector group from Ethiopian People Revolutionary Party (EPRP) called Ethiopian People’s Democratic Movement, OPDO a group of Derg’s troop prisoners of TPLF and EPLF known as Oromo People’s Democratic Organization, and with others smaller ethnic
Groups. They then formed Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Party (EPRDF). Within EPRDF, TPLF is by far dominant and have a monopoly over everything, including policy formulation, politics, economics, etc…
After 38 years of their existence, TPLF leaders remain extremely corrupt and not able to break out their ethnic and regional enclaves. But sadly, TPLF_ EPRDF has squandered multiple opportunities for building a free society. The 1974 Ethiopia revolution that promised to bring about genuine peace, freedom, justice, to all Ethiopians has been hijacked and prolonged. Unless the opposition democratic forces are willing to collaborate among themselves and to step up effective indigenous discipline movement as seen in Arab Spring movements. Arab Spring movement leads the complete defeat of African tyrants. TPLF’s regime resembles with many African dictators. If the discontents continue unanswered, the consequence will be the inevitable collapse of dictatorial rule with all out uprising. Does this lead to anarchy and possible to another civil war? Just by looking the countries that went through Arab Spring movement, the answer is no. One hope the opposition groups by focusing on common causes and shared values will do smart move and will take steps now to unite.
It is not a secret EPRDF is a just mask for TPLF to fragment or destroy the sovereignty of unitary state of Ethiopia. The goal of this alliance from its very inception has been to promote ethnic rights over national priority. As it stated above from this alliance TPLF has an enormous power. We already witnessed that they can and has done anything they want. As stated above, one of the alliances in EPRDF was the OLF. They have been reflected similar political aim to have one ethnic dominance and to destroy Ethiopian unity. As we recall in 1991, the OLF leaders was given special treatment, and made to feel as though they are on the winning team.
However, before they get too comfortable in new position, TPLF’s leaders saw them as a threat to their power. Immediately, OLF’s leaders and supporters were attacked until TPLF is assured that they were no longer a threat.
Soon after, TPLF’s action has been revealed to rest of the Ethiopian people too, the Opposition and the patriotic people has been attacked, killed, jailed, tortured and destroyed without mercy. Ethnic rights concept is used as a shield for atrocity TPLF committed. As we know, to advance ethnic rights TPLF/EPRDF retained the kebele peasant associations from past Derg’s regime structure, which they used to control the people same way as the Derg did. At same time, TPLF cadres penetrated in every corner of the associations. Then the cadres implemented TPLF’s ethnic policy in full.
They introduced a system of identity cards through kebele specifying to which ethnic a card holder belonged. Ethnic division’s official instituted and discrimination by ethnic line become as norm for ruling TPLF aristocracy. Ethnic violence orchestrated by TPLF later erupted in Harare, Anwak in Gambella and on other several regions. Although they are so obsessed and entrenched on this barbaric style, ethnicity has not resonated to most of ordinary Ethiopians to date. This was proven in 2005 where the Opposition parties mobilized undivided mass and win election.
The history of Ethiopia revolution that ignited in 1974 largely about to be free from yoke of oppression and exploitation of all Ethiopians. The fight always against Oligarchs and tyrants since the day of Ethiopian Students Movement commenced in 1960. Liberation by revolution would entail fundamentally to bring about equality and justice for all. Unfortunately, TPLF’s leaders have refused to listen or ask what everyone else thinks. The effect is alienating more Ethiopian patriots and ordinary fair minded people from political process. TPLF’s deception and disinformation strategy hindering all forms democratic rights and become also a path for the continuation of a toxic single ethnic-based rule tyranny.
It is evident that ethnic based of political structure is incapable of providing any solution to the country political, social and economic problems. In multinational state all ethnic deserve to be treated equally. For several years TPLF’s deception and self-aggrandizing propaganda attempted nearly every method imaginable to paint the Oppositions are against respecting ethnic rights. In contrary, the Oppositions are standing for diversity, equality, political democracy, social justice, unity, etc… In the past decades, we can enumerate several evidences that that the country is ravaged by a TPLF leaders to weaken Ethiopian solidarity. In the absences of oppositions, free media, check and balance system they proven to be corrupt, and continue to loot the country wealth and natural resources at broad day light, and made it easy for cronies to do the same. In summary we all aware of the dire situation in the country and we shall speak out in any way we can. As seen in the past in Tunisia or Ethiopia, if we brought unbearable pressure on the dictators, they tend to flee the country and the supports also will change with the tide.

ኢህአዴግ በርካታ የመረጃ ሰዎችን በሆቴል ቤት ሰራተኝነት ስም ቀጥሮ አሰማራ

    
 
ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ሻሂ ቤቶች፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች ውስጥ የ ኢህአዴግ መንግስት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ወጣት ሴቶችን በማሰልጠን እና አንድ ለአምስት በመጠርነፍ መረጃ እንዲያቀርቡ እያሰማራ እንደሚገኝ ታውቋል። መንግስት ከሻሂ ቤቶችና ሆቴሎች ስራ አስኪያጆች ጋር በሚስጢር በመነጋገር ደሞዝ የሚከፍላቸውን አስተናጋጆች አሰማርቶ ከህዝቡ መረጃ እየሰበሰበ ነው።
ቀደም ሲል መንግስት ሰዎችን በማስረግ ብቻ የመረጃ ማሰባሰቡን ስራ ይሰራ እንደነበር ለዘጋቢያችን የገለጡ አንድ ስማቸው እንዳይነገር የፈለጉ የድርጅቱ ሰው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በተጠናከረ ሁኔታ እራሱ ደሞዝ የሚከፍላቸውን ሰዎች በተመረጡ የመስተንግዶ ቤቶች መድቧል። ወጣት ሴቶች በትምህርት ደረጃቸው ዲፕሎማ ሳይቀር ያላቸው ሲሆን፣ ድርጅቱ ለረጅም ጊዜ በመረጃ አሰባሰብ ስራ በደህንነት ሰራተኞች እንዳሰለጠናቸውም ታውቋል።
የመረጃ ሰዎች የሰበሰቡትን መረጃ ለተወካያቸው የደህንነት ሰራተኞች በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ የሚገልጹ ሲሆን፣ መስሪያ ቤቱም መረጃዎችን በመተንተን ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን አስቀድሞ ለመከላከል ይጠቀምበታል ።
ከመረጃ ሰዎች የሚሰበሰቡትን መረጃዎች በመንተራስ ስርአቱን ይጠላሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰዎች ውሎአቸው እየታየ የተግባር ግሳጼ መስጠት መጀመሩ ታውቋል።
በተለይ ከተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ከግል ጋዜጠኞች ጋር የሚገናኙ ሰዎች ከግሳጼው በሁዋላ ግንኙነታቸውን ከላቋረጡ፣ በገንዘብ ለመደለል፣ ንብረታቸው ሊወሰድባቸው እንደሚችል በማስፋራራት፣ በመንግስት ቤት ውስጥ የሚኖሩ ከሆነም ቤታቸውን እንደሚቀሙ በማስጠንቀቅ በፖለቲከኞችና በህዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት ለመበጠስ እቅድ መያዙን ጉዳዩን ሲከታተለው የቆየው አዲስ አበባው ዘጋቢያችን ገልጿል።
ዘጋቢያችን ፒያሳ በሚገኝ አንድ ሻሂ ቤት ውስጥ በመሄድ ስላጋጠመው ገጠመኝ ሲገልጽ ” ከአንድ ባልንጀራየ ጋር ድምጼን ከፍ በማድረግ ስለወቅቱ ፖለቲካ እወያይ ነበር። አንዲት ወጣት መልከመልካም ቀይ ሴት የማስተናገዱን ስራ ትታ ጆሮዋን ወደ እኛ ቀስራ የምንናገረውን ለመስማት ትጥራለች ፤ ጉዳዩን ያልተረዳው የቅርብ ዘመዴ የሆነው የሻሂ ቤቱ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ የሚያስተናግደን መስሎ በመምጣት፣ በለሆሳስ ‘የምታወሩትን አቁሙ ልጂቱ እኛ የቀጠርናት ሳይሆን መንግስት የቀጠራት አስተናጋጅ ነች አለን።” ብሎአል።
የሆቴሉ ስራ አስኪያጅ አስተናጋጁዋ ከመንግስት በመጣ ትእዛዝ እንድትቀጠር መደረጉን፣ አብዛኛው ስራዋም ሰዎች የሚነጋገሩትን መቅዳት መሆኑን እና ድርጅቱ ምንም አይነት ደሞዝ እንደማይከፍላት ለዘጋቢአችን አረጋግጠውለታል። የስለላ ሰራተኞች በብዛት ይገኙባቸዋል ተብለው በተጠቆሙት ሆቴል ቤቶች በመዘዋወር ከአንዳንድ ስራ አስኪያጆች ጋር በመነጋገር መረጃውን ያረጋገጠው ዘጋቢያችን፣ አስተናጋጆቹ ሆቴሎች ደሞዝ ባይከፍሉዋቸውም ያለምንም ማንገራገር የተሰጣቸውን መስተንግዶ ስራ ይሰራሉ። የድርጅቶቹ ባለቤቶች ሰላይ አስተናጋጆች እነሱንም የሚሰልሉዋቸው ስለሚመስሉዋቸው ብዙ እንደማይናገሩዋቸው ለማወቅ ተችሎአል።
የደህንነት መስሪያ ቤት ቀጥሮ ካሰማራቸው ሴት አስተናጋጆች በተጨማሪ በኮሚኒኬሽንና ጆርናሊዝም ትምህርት የተመረቁ በርካታ ተማሪዎችን በአሁኑ ጊዜ በአዋሳ የደህንነት ጽህፈት ቤት መረጃ ስለመሰብሰብ፣ መረጃ ስለማስተላለፍ እና መረጃ ስለመተንተን ስልጣና እየተሰጠ ነው።
በኢትዮጵያ የሚታየው አፈና እየጨመረ መምጣት በተለይም የሙስሊሞ እንቅስቃሴ መጠናከር እና ተቃዋሚዎች ይህን እንቅስቃሴ ለራሳቸው ግብ ሊጠቀሙበት ይችላል የሚለው ስጋት እያየለ መሄድ መንግስት በርካታ የደህንነት ሰራተኞችን አሰልጥኖ ለማሰማራት መገደዱ ይገመታል።
የደህንነት ክትትሉ ቢጨምርም፣ ህዝቡ ግን አሁንም ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ስሜቱን ከመግለጽ ወደ ሁዋላ አይልም።
በቅርቡ በአዳማ ከተማ ይፋ የሆነ አንድ የኢህአዴግ ሪፖርት እንዳመለከተው የአንድ ለአምስት አደረጃጀት የታሰበውን ያክል ውጤት ሊያስገኝ አልቻለም። በብዙ መስሪያ ቤቶች እና ቀበሌዎች ተግባራዊ የተደረገው የአንድ ለአምስት አደረጃጀት ባለመሳካቱ ኢህአዴግ ሌሎች የመረጃ ማሰባሰብ ዘዴዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ግድ ብሎታል።

Tuesday, March 5, 2013

Moral Equivalent of an Anti -Apartheid Movement in Ethiopia?


by Alemayehu G. Mariam
Ethiopian Muslims engaged in the moral equivalent of an anti-Apartheid movement?
In her recent commentary in the New York Times Book Review, “Obama: Failing the African Spring?”, Dr. Helen EpsteinEthiopian Muslims Continue Protests questioned the Obama Administration for turning a blind eye to human rights violations in Africa, and particularly the persecution of Muslims in Ethiopia. She argued that “After more than four years in office… Obama has done little to advance the idealistic goals of his Ghana speech.” In fact, she finds the Administration playing peekaboo with Paul Kagame, the Rwandan dictator and puppet master of M23 (the rebel group led by Bosco Ntganda under indictment by the International Criminal Court) which has been wreaking havoc in Goma, (city in eastern Democratic Republic of the Congo) and Youweri Museveni, the overlord of the corruptocracy in Uganda. Dr. Epstein is perplexed by President Obama’s lofty rhetoric and his paralysis when it comes to walking the talk in Ethiopia:
Perhaps most worrying of all is the unwillingness of Obama and other Western leaders to say or do anything to support the hundreds of thousands of Muslim Ethiopians who have been demonstrating peacefully against government interference in their religious affairs for more than a year. (The Ethiopian government claims the country has a Christian majority, but Muslims may account for up to one half of the population.) You’d think a nonviolent Islamic movement would be just the kind of thing the Obama administration would want to showcase to the world. It has no hint of terrorist influence, and its leaders are calling for a secular government under the slogan ‘We have a cause worth dying for, but not worth killing for.’ Indeed, the Ethiopian protesters may be leading Africa’s most promising and important nonviolent human rights campaign since the anti-apartheid struggle.
Is Dr. Epstein correct in her profound observation that the Ethiopian Muslim “protesters may be leading Africa’s most promising and important nonviolent human rights campaign since the anti-apartheid struggle.” Are the Muslim protests that have been going on for nearly two years the moral equivalent of an anti-Apartheid movement in Ethiopia? Is Obama failing an Ethiopian Spring?
The importance of religious freedom to Americans and in U.S. foreign policy
Religious freedom is arguably the most important cornerstone of all American liberties. Promoting religious freedom worldwide is so important that the U.S. Congress passed the International Religious Freedom Act of 1998 (IRFA) affirming religious freedom enshrined in the U.S. Constitution and in various international instruments, including Article 18 of the Universal Declaration of Human Rights.
The Obama Administration’s record on international religious freedom in general has been deplorable. In 2010, Leonard Leo, chairman of the U.S. Commission on International Religious Freedom Commission openly complained that the Administration is ignoring religious persecution throughout the world to the potential detriment of U.S. national security. “We’re completely neglecting religious freedom in countries that tend to be Petri dishes for extremism. This invariably leads to trouble for us… Regrettably, this point seems to shrink year after year for the White House and State Department.”
The Obama Administration’s disregard for religious freedom and tolerance of religious intolerance and persecution throughout the world is incomprehensible given the centrality of religious freedom and separation of religion and government in the scheme of American liberties. The First Amendment to the U.S. Constitution, the foundation of all American liberties, first and foremost prohibits government involvement in religion in sweeping and uncompromising language: “Congress shall make no law respecting an establishment of religion, or prohibiting the free exercise thereof…” The “establishment” clause guarantees government neutrality by preventing government establishment of religious institutions or support for religion in general. The “free exercise” clause protects against religious persecution by government.
In the 1796 “Treaty of Peace and Friendship between the United States of America and the Bey and Subjects of Tripoli of Barbary”, the U.S. formally affirmed to the world the sanctity of religious freedom in America without regard to doctrine or denomination: “As the government of the United States of America is not in any sense founded on the Christian Religion, — as it has in itself no character of enmity against the laws, religion or tranquility of Musselmen, — and as the said States never have entered into any war or act of hostility against any Mehomitan nation, it is declared by the parties that no pretext arising from religious opinions shall ever produce an interruption of the harmony existing between the two countries.” (Art. 11.)
Many of the American Founding Fathers including George Washington, Thomas Jefferson, James Madison, John Adams and Benjamin Franklin were deeply suspicious of government involvement in religion, which they believed corrupted religion itself. George Washington championed separation of religion and state when he wrote, “I beg you be persuaded that no one would be more zealous than myself to establish effectual barriers against the horrors of spiritual tyranny, and every species of religious persecution.” Thomas Jefferson believed religion was a personal matter which invited no government involvement and argued for the “building a wall of separation between Church & State”. Jefferson wrote, “Among the most inestimable of our blessings is that … of liberty to worship our Creator… a liberty deemed in other countries incompatible with good government and yet proved by our experience to be its best support.” James Madison, the “father of the U.S. Constitution” was a staunch defender of religious diversity: “Freedom arises from the multiplicity of sects, which pervades America and which is the best and only security for religious liberty in any society.” President John Adams minced no words when he wrote, “Nothing is more dreaded than the national government meddling with religion.”
President Barack Obama himself made it crystal clear that he personally disapproves of government’s involvement in religion or government imposition of religious orthodoxy on citizens. “I am suspicious of using government to impose anybody’s religious beliefs -including my own- on nonbelievers.” In his first inauguration speech, President Obama declared, “Our Founding Fathers, faced with perils we can scarcely imagine, drafted a charter to assure the rule of law and the rights of man, a charter expanded by the blood of generations. Those ideals still light the world, and we will not give them up for expedience’s sake.”
The right of freedom of religion is the quintessential “rights of man” and an “ideal that still lights the world”. Yet, neither President Obama personally nor his Administration collectively have made any statements or taken any action concerning religious persecution in Ethiopia. It seems President Obama has given up the “ideal” of religious freedom for “expedience’s sake”. Such facile expedience is difficult to comprehend because President Obama was a constitutional lawyer before he became president.
It seems the President Obama now prefers a foreign policy based not on principle and the ideals of the Constitution but rather one based on expediency. It is more expedient for President Obama to have drone bases in Ethiopia than to have bastions of religious freedom. It is more expedient to sacrifice human rights at the altar of realpolitik than to uphold the right of Ethiopians to worship at the altar of their faiths. It is more expedient to chase after terrorists in the name of counterterrorism while sharing a bed with state terrorists. It is more expedient to tolerate dictatorship than to uphold the fundamental rights of citizenship. It is more expedient to support a benighted police state that to use American “ideals that still light the world” to enlighten it.
Why is the Obama Administration tone-deaf and bat-blind about religious freedom in Ethiopia given the established fact that the ruling regime in that country has engaged in egregious religious persecution with reckless abandon. The U.S. Commission on International Religious Freedom, an independent body constituted by the Congress and the President of the United States to monitor religious freedom worldwide, recently reported:
Since July 2011, the Ethiopian government has sought to impose the al-Ahbash Islamic sect on the country’s Muslim community, a community that traditionally has practiced the Sufi form of Islam. The government also has manipulated the election of the new leaders of the Ethiopia Islamic Affairs Supreme Council (EIASC). Previously viewed as an independent body, EIASC is now viewed as a government-controlled institution. The arrests, terrorism charges and takeover of EIASC signify a troubling escalation in the government’s attempts to control Ethiopia’s Muslim community and provide further evidence of a decline in religious freedom in Ethiopia. Muslims throughout Ethiopia have been arrested during peaceful protests: On October 29, the Ethiopia government charged 29 protestors with terrorism and attempting to establish an Islamic state.
U.S. foreign policy of expediency in Africa
Expediency has been a guiding principle in American foreign policy in Africa for quite a while. “Expediency” emphasizes “pragmatism” or “realpolitik” over principles and ideals. It is an approach that dictates consideration of each case in light of prevailing circumstances. Expediency subordinates values, ideals and principles to particular political or strategic objectives. Expediency justifies full support for blood thirsty African thugs just to advance the national interest in global “war on terror”. Expediency sacrifices principles and ideals on the altar of hypocrisy. Expediency has allowed the Obama Administration to pump billions of America taxpayer dollars to strengthen the iron fist of Meles Zenawi and his cronies in the name of fighting the so-called war on terror while preaching a hollow sermon of human rights to ordinary Africans.
What is most disconcerting is the fact that President Obama speaks with forked tongue. In Accra and Cairo, he hectored African dictators and made promises and affirmations to the people of Africa: “Development depends on good governance… We must support strong and sustainable democratic governments… Repression can take many forms, and too many nations, even those that have elections, are plagued by problems that condemn their people to poverty… That is not democracy, that is tyranny, even if occasionally you sprinkle an election in there…” He spoke of a “new partnership” with Africa, but his Watusi dance partners were Kagame, Museveni, Zenawi and their ilk.
As a strong supporter of President Obama and one who sought to exhort and mobilize Ethiopian Americans to support his election and re-election, I feel pangs of conscience when I say the President has been a poor advocate of American ideals in U.S. foreign policy in Africa. He has hectored ordinary Africans and African dictators about the need to be “on the right side of history”. For four years, President Obama has talked a good talk to Africans that America symbolizes freedom, liberty and democracy. But when it comes to walking the talk, we see him sitting in a wooden wheel chair that ain’t going nowhere fast. This paralysis has created a monumental crises of credibility for the President personally. Few Africans believe he is on their side and even fewer believe he is on the right side of history. But they do see him standing side by side with African dictators.
But could there really be expediency in dealing with blood thirsty African dictators? President Obama knows Ethiopia is a virtual police state. He knows elections are stolen there in broad daylight as those in power claim victory by a margin of 99.6 percent. He knows thousands of political prisoners languish in Ethiopian jails considered by international human rights organizations to be among the most inhumane in the world. He knows civil society institutions in that country have been wiped out of existence. He knows opposition parties, the press and dissidents have been crushed. He knows of the crimes against humanity that have been and continue to be committed in the Ogaden region, in Gambella, the Omo region and many other parts of the country. He knows about religious persecution. President Obama personally knows that 193 unarmed protesters were massacred and 763 wounded following the 2005 elections and that no one has been brought to justice for those crimes against humanity. That crime against humanity is on par with the Sharpeville Massacre of March 21, 1960 in South Africa in which South African police slaughtered 69 unarmed black protesters in the township of Sharpeville and wounded 180.
It is said that politics makes for strange bedfellows. But must the Obama Administration get in bed with those who have committed the most heinous crimes against humanity in the 21st Century? Is it worth sacrificing American ideals to coddle and consort with brutal African dictators just to get drone bases?
Can Ethiopian Americans hold the Obama Administration accountable?
Yes, we can! The International Religious Freedom Act of 1998 (Public Law 105-292) [IRFA] was enacted to promote religious freedom as a foreign policy of the United States, and to advocate on behalf of persons and groups facing religious persecution throughout the world. Very few people are aware that IFRA came into being as a result of the religious persecution of a Christian Ethiopian man named Getanah Metafriah who was “imprisoned and tortured by the Communist rulers of Ethiopia for talking about Jesus.” Getanah’s cause “manage[d] to help start a grassroots movement to publicize religious persecution abroad” eventually leading to the passage of IRFA.
IFRA requires that the United States designate as “country of particular concern” (CPC) those countries whose governments have engaged in or tolerated systematic and egregious and “particularly severe violations of religious freedom” and prescribes sanctions against such countries. IRFA provides the President 15 options ( 22 U.S.C. § 6445(a)(1)-(15)) to consider against states violating religious freedom including demarches (diplomatic protest) , private or public condemnation, denial, delay or cancellation of scientific or cultural exchanges, cancellation of a state visit, withdrawal or limitation of humanitarian or security assistance, restriction of credit or loans from United States and multilateral organizations, denial of licenses to export goods or technologies, prohibition against the U.S. government entering into any agreement to procure goods or services from that country, or “any other action authorized by law” so long as it “is commensurate in effect to the action substituted.” Once a state is designated a CPC, the President is required by law to conduct an annual review, no later than September 1 of each year, and to take one or more of the actions specified in IRFA.
Based on the USCRIF (a body auhtorized by IFRA) report cited above, there is no question that the regime in Ethiopia meets the IRFA criteria of engaging in “systematic, ongoing, and egregious” violations of the religious liberty of Ethiopian Muslims. It is noteworthy that the 2012 Annual Report of the United States Commission on International Religious Freedom March 2012 (covering April 1, 2011 – February 29, 2012)) documenting serious abuses of freedom of thought, conscience, religion, and belief around the world does not include religious persecution of Muslims in Ethiopia (which was reported by USCRIF in Novemeber 2012).
The first action Ethiopian Americans who believe in religious freedom in Ethiopia should take in an organized and collective manner is to file a request, (and if necessary a demand) that USCRIF amend or append to its 2012 report religious persecution and government interference in the profession and practice of the Islamic and Christian faiths in Ethiopia and make recommendations to the Secretary of State (SoS) for sanctions or alternative actions. In the alternative, they should insure that the violation is reported in the 2012-2013 USCRIF report with recommendations to the SoS for appropriate action. The SoS is required by IRFA to take “into consideration the recommendations of the Commission [USCRIF]” in formulating subsequent action.
By having USCRIF amend or append to its report and submit appropriate recommendations, Ethiopian Americans concerned about religious freedom in Ethiopia will have a legal basis to demand that the President “take all appropriate and feasible actions authorized by law to obtain the cessation of violations” (22 U.S.C. § 6445(a)(1)-(15)) or make Presidential certification and issue a waiver. In other words, the President would be in a position to take action or not to take action because taking action would be against U.S. “national security”. Either way, the Obama Administration could be held accountable under IFRA. No doubt, any such organized effort by Ethiopian Americans will stir the hornet’s nest of the K Street lobbyists who will rub their palms with glee and grin ear to ear as they come to feast at the trough of poor Ethiopian taxpayers.
The second action Ethiopian Americans who believe in religious freedom in Ethiopia should take is to establish an interfaith council to work on broader issues of religious freedom in Ethiopia. In my July 2012 commentary “Unity in Divinity”, I argued that a threat to the religious liberty of Muslims is a threat to the religious freedom of Christians. I urged Ethiopian “Christian and Muslim religious leaders [to] play a critical role in preventing conflict and in building bridges of understanding, mutual respect and collaborative working relations…” I suggested the establishment of “interfaith councils” patterned after those in the U.S. “These [interfaith] councils bring diverse faith communities to work together to foster greater understanding and respect among people of different faiths and to address basic needs in the community. Many such councils go beyond dialogue and reflection to cooperative work in social services and implementing projects to meet community needs. They stand together to protect religious freedom by opposing discrimination and condemning debasement of religious institutions and faiths. There is no reason why Ethiopians could not establish interfaith councils of their own.”
I reiterate my call for interfaith councils to bring together members of the two faith communities in the United States, and possibly elsewhere, for collective action. Religious freedom in Ethiopia is not an issue that concerns only Muslims. It is of equal concern and importance for Christian Ethiopians who have undergone similar egregious interference in the selection of their religious leadership just recently.
What is needed is sincere and open dialogue and interaction between Ethiopian Americans who are Christians and Muslims to advance the cause of religious liberty and equality for all in unity. Members of these two faith communities must come together in a historic meeting and develop a joint agenda to guarantee and safeguard their religious freedom, overcome any traces of sectarianism and reaffirm their long coexistence, diversity and harmony in a unified country based on the rule of law. They must jointly develop principles of cooperation and coordination. They must develop solidarity which can withstand narrow sectarian interests and the whims and personalities of those in leadership positions. They must relate with each other in the spirit of mutual respect, trust and co-operation and find ways to deepen and strengthen their relations.
Perhaps such dialogue may not come so easily in the absence of existing institutions. It may be necessary for leaders of both faiths to join together and establish a task force to study the issues and make recommendations for the broadest possible dialogue between Ethiopian American Muslims and Christians in America. Christian and Islamic spiritual authorities and laymen should be encouraged to work together not only to defend each other on matters of religious liberty but also to propose long term solutions to reduce the dangers of sectarianism, fanaticism, conflict and misunderstanding and institute a permanent dialogue between members of both faiths. There is no reason why an interfaith council cannot organize joint conferences, meetings, workshops, seminars, press conferences and informational campaigns in the media in both faith communities. The Ethiopia of tomorrow can be built on a strong foundation of dialogue of Muslims and Christians today. Dialogue is a precursor to national reconciliation.

Monday, March 4, 2013

"ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያልተሳተፉበት የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ስብሰባ"

አስገራሚ መረጃ

የኢህአዴግ ጉዳ ይ ዘመኑ የፈጠራቸውን አባላት አይመለከትም::
"ድርጅታችንን ከመበታተን እና ከውድቀት ማዳን " እንዴት??
ከቀናት በፊት ለሊቱን የኢሕኣዴግ ነባር ታጋይ ባለስልጣናት እና ጄኔራሎቻቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የታሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞችን የሚፈቱበትን ብልሃት እና ድርጅታቸው የገባበትን አጣብቂኝ እንዲሁ ከመበታተን እና ከመፍረስ ለመዳን በሚል ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሩ እንቅልፍ አስተኝተው እስከንጋት መዳረሻ ሃይለማርያምን ያላሳተፈ ዉይይት አድርገዋል::

እነዚህ በሙስና የተዘፈቁ እና የነገ ህይወታቸው ያሳሰባቸው የወያኔ ቀደምት ታጋዮች የመጀመሪያ አጀንዳ ብለው የያዙት ድርጅታቸውን ከመፈራረስ እንደት ሊያድኑት እንደሚችሉ ነው :: በአሁን ሰኣት እየተጠቀሙበት ያለ አይነት የፖለቲካ አካሄድ ከደርግ እንደማይለይ እና የደርግንም ውድቀት ያፋጠነ እንደዚህ አይነቱ አፈጻጸም የጎደለው የፖለቲካ ስልት ነው በሚለው ሃሳብ ዙሪያ መነሾነት ከቀበሌ ጀምሮ የተደራጁት የፖለቲካ ህዋሶች መረጃ እየሸጡ ነው ለግል ጥቅም ባገኙበት ሁሉ ይገባሉ አዳዲስ አባላትንም ብንመለምል ለስለላ እንጂ ሊያገለግሉ አልቻሉም ስለዚህ መፍትሄ ያስፈልጋል ብለዋል :: ለዚህ የሚያስፈልጉ ድርጅታዊ ጉዳዮች ሳይሰሩ ስብሰባውን ለመጋቢት ያስተላለፍነውም ለዚህ ነው እና ስብሰባው ከመድረሱ በፊት የተሰሩ ስራዎች እንደሌሉ እና ፉርሽ እንደሆኑ እየታየ ነው በሚለው ተስማምተዋል::

ኦህዲድን እና ደሕኣዴግን ያላሳተፈው ይህ የህወሓት እና የብኣዴን ታጋዮች ስብሰባ በነባር የትግራይ ተወላጅ ታጋዮች መካከል የተነሳውን የመከፋፈል አደጋ አንስቶ ለቀሪዎችም አባል ድርጅቶች መጥፎ ገደል እየሆነ መሆኑ ተጠቁሟል::ስለዚህ ከኣሁ ሰአት ጀምሮ ሁለቱ አንጃዎች መስማማት አለባቸው በማለት አቶ ስብሃት ነጋ ቢያንገራግሩም በሕወሃት መካከል በመርህ ደረጃ ስምምነት ተደርሷል:: ወይዘሮ አዜብ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት ባይሰጡም ሆኖም የኢህኣዴግ ለዚህ ችግር መብቃት ተጠያቂ ያደረጉት ሳይመዘኑ ዘለው ማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ የገቡት አዳዲስ አባላት ናቸው ብለዋል::

በስብሰባው ላይ ተሳታፊ የነበሩት ስብሃት ነጋ ኣርከበ ዕቁባይ ፀጋይ በርሀ በረከት ስምዖን ኣዜብ መስፍን ትርፉ ኪዳነማርያም ተክለወይኒ ኣሰፋ ሳሞራ ዮኑስ ብርሃነ ገብረክርስቶስ ኣዲሱ ለገሰ ዓለም ገብረዋህድ አዲስአለም ባሌማ ሕላዊ ዮሴፍ ስዩም መስፍን ጌታቸው አሰፋ ኣባይ ፀሃዬ እንዲሁም ለጊዜው ስማቸው ያልተጠቀሰ 5 ጄኔራሎች ነበሩ::እነዚህ ተሰብሳቢዎች በተደጋጋሚ ያነሱት ድርጅታችንን እንዴት እናድን ነው::
በዚህም መሰረት ድርጅታቸውን ማዳን የሚችሉበት አዳዲስ ታማኝ ትውልዶችን ሰብስቦ ስልጣን በመስጠት በማስተማር አላማቸውን እንዲያስፈጽሙ ማድረግ ድርጅታቸውን ብቻ ሳይሆን ራሳቸውንም ማዳን እንደሚችሉ ...የደርግ እጣ እንዳይገጥማቸው ሰራዊቱ ውስጥ ያሉትን አስቸጋሪ የተባሉ ከፍተኛ መኮንኖችን ጠቀም ያለ እና አፋቸውን የሚያዘጋ ገንዘብ እና ንብረት እየሰጡ ማሰናበት ...ከትግራይ ክልል እና አከባቢው ታማኝ አባሎችን አምጥቶ አዲስ አበባ ውስጥ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ላይኛው እርከን መሾም:...እስረኞችን መፍታት :አስፈላጊ የሚባሉ የቀድሞ አባላትን ወደ ድርጅቱ ጋብዞ ስለተሃድሶ መነጋገር እና ለውጦችን ማድረግ ማስፈጸም:: እንዲሁም ታማኝ የሰራዊት አባላትን እና የፖሊስ ሃይሎችንእና የደህንነትአባላት በማስታጠቅ አስፈላጊውን ጥቅማጥቅም በመስጠት በመንግስት (በግለኝነታቸው መባሉ ነው) ላይ የሚከሰተውን ማንኛውንም ችግር ፈጥነው እንዲያመክኑት ሲሉ በቅርቡ ሰልጥኖ የተመረቀው የኮማንዶ ሃይል በአዲስ አበባ ዙሪያ እንዲሰፍር በማለት ተነጋግረዋል:: በተጨማሪም በሃገሪቱ የተማረ የሰውሃይል በሚበዛባቸው ከተሞች ደህንነቶች እንዲሰማሩ ብለዋል::

የሃገሪቱን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ያልተነጋገረው የሀው የታጋዮች ስብሰባ እስረኞችን በተመለከተ አለማቀፍ ጫና እየበረታ መምጣቱን እና በእነዚህ እስረኞች የመጣ ዲያስፖራው ወዳጆቻችን እንኳን ፊታቸውን እያዞሩ ነው የሚለውን ሃሳብ አንስተው ተወያይተዋል::
በዚህም መሰረት እስረኞቹን መፍታት እንደሽንፈት የሚያዩት አቶ በረከት ስምኦን እንዳሉት እስረኞቹን ለመፍታት እንዲያመች ሽማግሌዎች ብንልክም ማንም የሚቀበላቸው የለም :: በሌላ በኩል እየሞከርን ብንገኝም እንዲሞክሩልን የጠየቅናቸው ከየክልሉ የሰበሰብናቸው ሽማግሌዎች በቀጥታ ፍቷቸው እኛ ከ ህዝብ ጋር መጣላት አንፈልግም ብለዋል :: አኩርፈውም ሄደዋል:: እንዲሁም ከአፋር የመጡት ሽማግሌዎች የይቅርታ ቅድመ ሁኔታዎች ብናቀርብ ሊቀበሉን አልቻሉም ትተውን ሄደዋል:: ዲያስፖራው እና አጋሮቻችንንም ቢሆን በየምናገኛቸው ወቅት የሚያነሱልን የእስረኞችን አጀንዳ ነው ብለዋል:: ማድረግ ያለብን ምንድነው ታዲያ? ....ሲሉ ተደምጠዋል::

ሁነታዎችን እያዩ እና ሰበብ እየፈለጉ መፍታት አሁን ከአውሮፓ ህብረት ጋር የተጀመረው ዉይይት ጥሩ ነው ችግሩ ሰዎቹ የይቅርታ ፎርም ፈርሙ ሲባሉ አሻፈረኝ ማለት ጀምረዋል::(ለማስታወስ ከዚህ ወራት በፊት እንዳስታወቅነው ፎርም የሚሞሉ እንደሚፈቱ ተነግሮ ነበር) ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ የተጀመረው ስራ በእንጥልጥል መተው የለበትም ለእኛም ያሰጋናል:;አስቸኳይ መፍትሄ ይፈለግ ብለዋል::በየጊዜው እየተወያየን አዲስ የተለየ ሃሳብ ላይ ወስነን የተወሰኑ እስረኞች መፈታት አለባቸው ዋናው ዲያስፖራው የሚያራግብባቸው ስማቸው በብዛት የሚነሳ ሰዎች መለቀቅ አለባቸው:: ይህ በንዲህ እንዳለ አንዳንድ ነባር አባላት መረጃዎች እየሸጡ ስለሆነ የት እንደሚውሉ ከማን ጋር እንደሚገናኙ ከነቤተሰቦቻቸው መሰለል አለባቸው ሲሉ ወስነዋል::

በዚህ ስብሰባ ላይ የአቶ መለስ ዜናዊ ራእይ የሚባል ነገር አልተነሳም:: እንዲሁም የኢህአዴግ ጉዳ ይ ዘመኑ የፈጠራቸውን አባላት አይመለከትም:: ያሉት አና የተስማሙት ነባር አባላቱ አቶ ሃይለማርያም ለምን አልተሳተፉም የሚል ጥያቄ አልተነሳም:: ኦሆዲዶች የታሉ ያለም አልነበረም:;አብዮት ማለት እንዲህ ነው::አስገራሚ መረጃ

"ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያልተሳተፉበት የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ስብሰባ"

የኢህአዴግ ጉዳ ይ ዘመኑ የፈጠራቸውን አባላት አይመለከትም::
"ድርጅታችንን ከመበታተን እና ከውድቀት ማዳን " እንዴት??
ከቀናት በፊት ለሊቱን የኢሕኣዴግ ነባር ታጋይ ባለስልጣናት እና ጄኔራሎቻቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የታሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞችን የሚፈቱበትን ብልሃት እና ድርጅታቸው የገባበትን አጣብቂኝ እንዲሁ ከመበታተን እና ከመፍረስ ለመዳን በሚል ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሩ እንቅልፍ አስተኝተው እስከንጋት መዳረሻ ሃይለማርያምን ያላሳተፈ ዉይይት አድርገዋል::

እነዚህ በሙስና የተዘፈቁ እና የነገ ህይወታቸው ያሳሰባቸው የወያኔ ቀደምት ታጋዮች የመጀመሪያ አጀንዳ ብለው የያዙት ድርጅታቸውን ከመፈራረስ እንደት ሊያድኑት እንደሚችሉ ነው :: በአሁን ሰኣት እየተጠቀሙበት ያለ አይነት የፖለቲካ አካሄድ ከደርግ እንደማይለይ እና የደርግንም ውድቀት ያፋጠነ እንደዚህ አይነቱ አፈጻጸም የጎደለው የፖለቲካ ስልት ነው በሚለው ሃሳብ ዙሪያ መነሾነት ከቀበሌ ጀምሮ የተደራጁት የፖለቲካ ህዋሶች መረጃ እየሸጡ ነው ለግል ጥቅም ባገኙበት ሁሉ ይገባሉ አዳዲስ አባላትንም ብንመለምል ለስለላ እንጂ ሊያገለግሉ አልቻሉም ስለዚህ መፍትሄ ያስፈልጋል ብለዋል :: ለዚህ የሚያስፈልጉ ድርጅታዊ ጉዳዮች ሳይሰሩ ስብሰባውን ለመጋቢት ያስተላለፍነውም ለዚህ ነው እና ስብሰባው ከመድረሱ በፊት የተሰሩ ስራዎች እንደሌሉ እና ፉርሽ እንደሆኑ እየታየ ነው በሚለው ተስማምተዋል::

ኦህዲድን እና ደሕኣዴግን ያላሳተፈው ይህ የህወሓት እና የብኣዴን ታጋዮች ስብሰባ በነባር የትግራይ ተወላጅ ታጋዮች መካከል የተነሳውን የመከፋፈል አደጋ አንስቶ ለቀሪዎችም አባል ድርጅቶች መጥፎ ገደል እየሆነ መሆኑ ተጠቁሟል::ስለዚህ ከኣሁ ሰአት ጀምሮ ሁለቱ አንጃዎች መስማማት አለባቸው በማለት አቶ ስብሃት ነጋ ቢያንገራግሩም በሕወሃት መካከል በመርህ ደረጃ ስምምነት ተደርሷል:: ወይዘሮ አዜብ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት ባይሰጡም ሆኖም የኢህኣዴግ ለዚህ ችግር መብቃት ተጠያቂ ያደረጉት ሳይመዘኑ ዘለው ማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ የገቡት አዳዲስ አባላት ናቸው ብለዋል::

በስብሰባው ላይ ተሳታፊ የነበሩት ስብሃት ነጋ ኣርከበ ዕቁባይ ፀጋይ በርሀ በረከት ስምዖን ኣዜብ መስፍን ትርፉ ኪዳነማርያም ተክለወይኒ ኣሰፋ ሳሞራ ዮኑስ ብርሃነ ገብረክርስቶስ ኣዲሱ ለገሰ ዓለም ገብረዋህድ አዲስአለም ባሌማ ሕላዊ ዮሴፍ ስዩም መስፍን ጌታቸው አሰፋ ኣባይ ፀሃዬ እንዲሁም ለጊዜው ስማቸው ያልተጠቀሰ 5 ጄኔራሎች ነበሩ::እነዚህ ተሰብሳቢዎች በተደጋጋሚ ያነሱት ድርጅታችንን እንዴት እናድን ነው::
በዚህም መሰረት ድርጅታቸውን ማዳን የሚችሉበት አዳዲስ ታማኝ ትውልዶችን ሰብስቦ ስልጣን በመስጠት በማስተማር አላማቸውን እንዲያስፈጽሙ ማድረግ ድርጅታቸውን ብቻ ሳይሆን ራሳቸውንም ማዳን እንደሚችሉ ...የደርግ እጣ እንዳይገጥማቸው ሰራዊቱ ውስጥ ያሉትን አስቸጋሪ የተባሉ ከፍተኛ መኮንኖችን ጠቀም ያለ እና አፋቸውን የሚያዘጋ ገንዘብ እና ንብረት እየሰጡ ማሰናበት ...ከትግራይ ክልል እና አከባቢው ታማኝ አባሎችን አምጥቶ አዲስ አበባ ውስጥ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ላይኛው እርከን መሾም:...እስረኞችን መፍታት :አስፈላጊ የሚባሉ የቀድሞ አባላትን ወደ ድርጅቱ ጋብዞ ስለተሃድሶ መነጋገር እና ለውጦችን ማድረግ ማስፈጸም:: እንዲሁም ታማኝ የሰራዊት አባላትን እና የፖሊስ ሃይሎችንእና የደህንነትአባላት በማስታጠቅ አስፈላጊውን ጥቅማጥቅም በመስጠት በመንግስት (በግለኝነታቸው መባሉ ነው) ላይ የሚከሰተውን ማንኛውንም ችግር ፈጥነው እንዲያመክኑት ሲሉ በቅርቡ ሰልጥኖ የተመረቀው የኮማንዶ ሃይል በአዲስ አበባ ዙሪያ እንዲሰፍር በማለት ተነጋግረዋል:: በተጨማሪም በሃገሪቱ የተማረ የሰውሃይል በሚበዛባቸው ከተሞች ደህንነቶች እንዲሰማሩ ብለዋል::

የሃገሪቱን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ላይ ምንም ያልተነጋገረው የሀው የታጋዮች ስብሰባ እስረኞችን በተመለከተ አለማቀፍ ጫና እየበረታ መምጣቱን እና በእነዚህ እስረኞች የመጣ ዲያስፖራው ወዳጆቻችን እንኳን ፊታቸውን እያዞሩ ነው የሚለውን ሃሳብ አንስተው ተወያይተዋል::
በዚህም መሰረት እስረኞቹን መፍታት እንደሽንፈት የሚያዩት አቶ በረከት ስምኦን እንዳሉት እስረኞቹን ለመፍታት እንዲያመች ሽማግሌዎች ብንልክም ማንም የሚቀበላቸው የለም :: በሌላ በኩል እየሞከርን ብንገኝም እንዲሞክሩልን የጠየቅናቸው ከየክልሉ የሰበሰብናቸው ሽማግሌዎች በቀጥታ ፍቷቸው እኛ ከ ህዝብ ጋር መጣላት አንፈልግም ብለዋል :: አኩርፈውም ሄደዋል:: እንዲሁም ከአፋር የመጡት ሽማግሌዎች የይቅርታ ቅድመ ሁኔታዎች ብናቀርብ ሊቀበሉን አልቻሉም ትተውን ሄደዋል:: ዲያስፖራው እና አጋሮቻችንንም ቢሆን በየምናገኛቸው ወቅት የሚያነሱልን የእስረኞችን አጀንዳ ነው ብለዋል:: ማድረግ ያለብን ምንድነው ታዲያ? ....ሲሉ ተደምጠዋል::

ሁነታዎችን እያዩ እና ሰበብ እየፈለጉ መፍታት አሁን ከአውሮፓ ህብረት ጋር የተጀመረው ዉይይት ጥሩ ነው ችግሩ ሰዎቹ የይቅርታ ፎርም ፈርሙ ሲባሉ አሻፈረኝ ማለት ጀምረዋል::(ለማስታወስ ከዚህ ወራት በፊት እንዳስታወቅነው ፎርም የሚሞሉ እንደሚፈቱ ተነግሮ ነበር) ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ የተጀመረው ስራ በእንጥልጥል መተው የለበትም ለእኛም ያሰጋናል:;አስቸኳይ መፍትሄ ይፈለግ ብለዋል::በየጊዜው እየተወያየን አዲስ የተለየ ሃሳብ ላይ ወስነን የተወሰኑ እስረኞች መፈታት አለባቸው ዋናው ዲያስፖራው የሚያራግብባቸው ስማቸው በብዛት የሚነሳ ሰዎች መለቀቅ አለባቸው:: ይህ በንዲህ እንዳለ አንዳንድ ነባር አባላት መረጃዎች እየሸጡ ስለሆነ የት እንደሚውሉ ከማን ጋር እንደሚገናኙ ከነቤተሰቦቻቸው መሰለል አለባቸው ሲሉ ወስነዋል::

በዚህ ስብሰባ ላይ የአቶ መለስ ዜናዊ ራእይ የሚባል ነገር አልተነሳም:: እንዲሁም የኢህአዴግ ጉዳ ይ ዘመኑ የፈጠራቸውን አባላት አይመለከትም:: ያሉት አና የተስማሙት ነባር አባላቱ አቶ ሃይለማርያም ለምን አልተሳተፉም የሚል ጥያቄ አልተነሳም:: ኦሆዲዶች የታሉ ያለም አልነበረም:;አብዮት ማለት እንዲህ ነው::

ኢህአዴግ አሣ አስጋሪዎችን ጨፈጨፈ

 

የአሜሪካዊው አስከሬንና አሟሟት ሊመረመር ነው
fisherman
የመከላከያ ሰራዊት በድንገተኛ ከበባ ከገደላቸው ንጹሃን ዜጎች መካከል የአሜሪካ ዜግነት ያላቸውን የአቶ ኡሞት ኡዶል ግድያ አስመልክቶ የአሜሪካ መንግስት አስፈላጊውን ሁሉ ምርመራ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ግድያው ከተፈጸመ በኋላ የሰራዊቱ አባላት አስከሬን አደባባይ በማውጣት ለህዝብ እያሳዩ ደስታቸውን ሲገልጹ የተመለከቱ የጋምቤላ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ክፉኛ መበሳጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በጋምቤላ የደረቁን ወቅት ወይም በጋውን በወንዞች ዳር ውሃ ተንተርሶ መኖር የተለመደ ነው። ከቋሚ የመኖሪያ ቀዬ ወደ ወንዝ ዳርቻ በመሄድ አድኖ መመገብና አሳ አስግሮ ዕለትን ማሳለፍ የባህል ያህል ነው። በአገሬው ልምድ መሰረት ከቋሚ መኖሪያቸው ወደ ውሃ ዳር የሚሄዱት ወንዶች ሲሆኑ ጉዞውም የሚደረገው በቡድን ነው።
በዚሁ መሰረት በጋምቤላ ክልል የጎክዲፓች ነዋሪዎች የደረቁን ወቅት ለማሳለፍ በጊሎ ወንዝ ዳርቻ ወደምትገኘው አብሌን ያመራሉ። በቡድን ወደ አብሌን ያመሩት ሰዎች ከወንዝ አሳ በማስገርና ያገኙትን በማደን ቀን እየገፉ ሳለ የካቲት 21፤2005ዓም (28/2/13) በድንገት የመከላከያ ሰራዊት ከበባቸው። ተኩስ ተከፈተ። ለጊዜው ስድስት ሰዎች ህይወታቸው ማለፉንና የቆሰሉ እንዳሉ ለተጎጂዎቹ ቅርበት ያላቸው ያስረዳሉ።
ሰዎቹ ከጋምቤላ ከተማ 120 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው አብሌን ተቀምጠው ኑሯቸውን እየገፉ ሳለ በድንገት የተከበቡት በጥቆማ እንደሆነ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል። “አቶ ኡሞት ኡዶል እና ሌሎች መሳሪያ የታጠቁ አብሌን ታይተዋል” የሚል ጥቆማ የደረሰው ኢህአዴግ፤ ሰራዊቱን ሰዎቹ በቋሚነት ወደሚኖሩበት ጎክዲፓች በመላክ ቤተሰቦቻቸውን በመያዝ፣ በማሰርና፣ በመግረፍ ሰዎቹ ያሉበትን ቦታ እንዲያሳዩ አስገደዱ።
ኡሞት ኡዶል (ፎቶ: ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ)
አቶ ኡሞት በዋሽንግተን ዲሲ ነዋሪ የነበሩ ሲሆን የአሜሪካ ዜግነትም አላቸው። ኢህአዴግ ከመሬት ነጠቃ ጋር በተያያዘ በክልሉ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍ አጥብቀው በግልጽ የሚቃወሙ ሰው መሆናቸውን የሚያውቋቸው ይናገራሉ። አቶ ኡሞት ከመሬት ነጠቃ ጋር በተያያዘ ህዝብን የሚያስተባብሩና ለዓመጽ የሚያነሳሱ ናቸው በሚል ኢህአዴግ ቢወነጅላቸውም ውንጀላውን በማስረጃ ማቅረብ እንደማይችል እነዚሁ ክፍሎች ይገልጻሉ። ስለተፈጸመው ግፍ የተሞላበት ግድያና ከግድያው በኋላ ስለተከናወነው “አረመኔያዊ የእንስሳ ተግባር” ሲያስረዱ በቁጣ ነው።
በተጠቀሰው ቀን ቤተሰቦቻቸውን ቀበሌያቸው ድረስ በመሄድ በመግረፍና በማስፈራራት ወደ አብሌን ለከበባ በጠቋሚ የመጡት የመከላከያ አባላት ሰዎቹን እንደተመለከቱ ተኩስ ከፈቱ። በድንገት የተከበቡትና ዛፍ ሥር ተቀምጠው የነበሩት አንዳችም ጥያቄ ሳይቀርብላቸው በጥይት የተደበደቡት ሰዎች የአልሞት ባይ ተጋዳይ ትግል ቢያደርጉም አልሆነም። ተደራጅቶ በሶስት የወታደር ካሚዮን ከባድ መሳሪያ ታጥቆ የመጣው ሰራዊት ጨፈጨፋቸው። ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ እንደተናገሩት ወዲያው ህይወታቸው ካለፈው ስድስት ንጹሃን መካከል አቶ ኡሞት መሞታቸው ሲታወቅ የሰራዊቱ አባላት አውካኩ፤ በደስታ ጨፈሩ። አስከሬኑንን ጭነው ፉኙዶ ወደሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ካምፕ በመሄድ ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን ደስታቸውን አበሰሩ።
አስከሬን በመኪና በመጫን ከተማ እየዞሩ ደስታቸውን ገለጹ። በማግስቱ በጋምቤላ ከተማ ስታዲየም አስከሬኑን ህዝብ እንዲመለከተው ታዘዘ። ህዝብ ስታዲየም ተገኝቶ የአቶ ኡሞትን አስከሬን እንዲሳለም፣ ኢንቨስተሮችም ያለስጋት የመሬት ነጠቃቸውንና “ልማታቸውን እንዲቀጥሉ”፣ መሞታቸውን አይቶ ሕዝቡ እንዲያምንና ሞራሉ እንዲጎዳ የተላለፈው ውሳኔ ባልተጠበቀ ሁኔታ ተስተጓጎለ። ለጎልጉል መረጃውን ያስተላለፉ እንዳሉት አቶ ኡሞት አሜሪካዊ መሆናቸው ሲታወቅ ማዕከላዊ መንግስት ከአዲስ አበባ አስቸኳይ ትዕዛዝ አስተላለፈ። አስከሬኑን ባስቸኳይ እንዲቀብሩ መመሪያ ሰጡ። ሁሉም ነገር በመመሪያው መሰረት ተጠናቀቀ። የአቶ ኡሞት አስከሬን ባልታወቀ ቦታ ተቀበረ። አስከሬኑንን ለማየት በግዳጅ ተሰባሰበው ህዝብም ምንም ነገር ሳይመለከት ወደ ቤቱ ተመለሰ። ሁኔታውን ተከትሎ በተፈጠረ አለመረጋጋት የኢህአዴግ ሠራዊት በጎክ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ የጋምቤላ ተወላጆች በተለይም ወንዶችን እያሠሩና እያሰቃዩ እንደሆነ ከሥፍራው የደረሰን ዜና ያረጋግጣል፡፡
የአኙዋክ የፍትሕ ምክርቤት ጉዳዩን ለአሜሪካ መንግስት እንዳሳወቀና የአሜሪካ መንግስት ጉዳዩን ከስር መሰረቱ ጀምሮ እንደሚመረምረውና እስከ መጨረሻው የመንግሥት አካል እንደሚደርሱ ማረጋገጡ ታውቋል። ኢህአዴግ አቶ ኡሞትን የገደለበትን ምክንያት በማስረጃ ማቅረብ እንደሚጠበቅበትም አስታውቀዋል። አቶ ኡሞት የሚጠረጠሩበት ድርጊት እንኳን ቢኖር በቁጥጥር ስር አውሎ በህግ መጠየቅ እየተቻለ እንዲገደሉ መደረጋቸው ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ የሚከራከሩላቸውና ጉዳያቸውን ይፋ ያደረጉት ክፍሎች ይናገራሉ።
በወቅቱ ህይወታቸው ያለፈው ንጹሃንና የደረሱበት ያልታወቀው ሰዎች ስም ዝርዝር ከስፍራው የደረሰን ሲሆን እንደሚከተለው አቅርበነዋል።
  1. ጎጎ ኦቻላ
  2. ቻም ኦቻላ
  3. ዑከች አቻው
  4. አኳይ ኦሞት
  5. ኦሞት ኦባንግ
  6. አጂባ አኳይ
  7. ኦሞት ኡጁሉ ኦጎታ
  8. አንበሳው ኡጁሉ
  9. ቱወል ኦሎክ
  10. ኦችዋል ኦባንግ
  11. ኦዋር ቻም
  12. ኒሙሉ አጎሌ
  13. አብራች ኒሙሉ
  14. አኩኔ ኦሞት
  15. አግዋ ቻም
  16. ኦዋር ኒግዎ አጋክ
  17. ኦሞት ኡዶል (አሜሪካዊው)

http://www.goolgule.com/massacre-in-gambella/

የሙስሊሙ እንቅስቃሴ ከመንግስት እጅ እየወጣ ነው



የሙስሊሙ ጥያቄ ከመንግስት እጅ እየወጣ ስለመሆኑ የሚያመላክት ሁኔታ መታየቱን ኢሳት የካቲት 22 ቀን 2005 ዓ ም ዘገበ። ኢሳት እንዳለው የድምጻችን ይሰማ አስተባባሪዎች በነደፉት መርሐግብር መሰረት በአገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች ተቃውሞዎች ተደርገዋል።
በመቀሌ፣ በመቱ፣ በጅጅጋ፣ በአፋር፣ በጅማ፣ ወልቂጤ፣ ጎንደር፣ በአዲስ አ...በባ እና በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ተቃውሞዎች ተነስተዋል። በአዲስ አበባ ሙስሊሙ ማህበረሰብ “መሪዎቻችን ይፈቱ ድምጻችን ይሰማ በቤታችን ሰላም ስጡን” የሚሉ መፈክሮችን ማሰማታቸውን ያስታወቀው ኢሳት አሁን ባለው ሁኔታ የሙስሊሙ ጥያቄ ከመንግስት እጅ እየወጣ ለመሆኑ አመላካች እንደሆነ ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ለመከፋፈል መንግስት በእየለቱ የሚያሰራጨው ፕሮፓጋንዳ ሙስሊሙን በቁጭት እንዲነሳ እያደረገው መሆኑን ታዛቢዎች እንደሚናገሩ ያመለከተው ኢሳት፤ “በመላው አገሪቱ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች እጅግ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚያሰሙት ተቃውሞ ብዙዎችን እንዳስደመመ ቀጥሎአል” በማለት ዘገባውን ቋጭቷል።

Fights near Awash kill 60, injure many


 Severe "ethnic and resource" fights among the Afar, Oromo and Somali ethnic groups, near the Awash River, Eastern Ethiopia, have left around sixty people dead and many injured the weekend before (Febr...uary 23-24, 2013), sources told De Birhan. The fights had also renewed over the week between the Afars and Somalis.
According to our source, so far 6 from the Somali, 18 from Afar and 36 from the Oromo ethnic groups are recorded dead due to the week long fights. Residents of the area state that they don't know who and how the clash started.
The region has been prone to clashes over resources such water and grazing land and also ethnic conflicts by pastoralists of the three ethnic groups.
Some studies, such as this one by Asknake K. Adegehe (2009), indicate that the cause of these conflicts has been the wrong federalism policy of the current regime,
The federal restructuring carried out by dismantling the old unitary structure of the country led to territorial and boundary disputes. Unlike the older federations created by the union of independent units, which among other things have stable boundaries, creating a federation through federal restructuring leads to controversies and in some cases to violent conflicts. In the Ethiopian case, violent conflicts accompany the process of intra-federal boundary making.
Similarly, De Birhan had reported that there has been an inter-ethnic clash in the Benishangul Gumz Region of Ethiopia this weekend.
By De Birhan Staffer Addis Abeba 04 March 2013
 

የሸሪያ ፍርድ ቤት” በጅጅጋ የአማራ ተወላጆችን ሰለባ አደረገ



ካለፉት አርባ ዓመታት ጀምሮ በሶማሊ ክልል በጅጅጋ ከተማ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ቤቶቻቸውን እያስረከቡ ለጎዳና ህይወት እየተዳረጉ መሆናቸውን ኢሳት አስታወቀ።
 እስካሁን ድረስ በከተማዋ ውስጥ ዋና ዋና የንግድ ቦታዎች የነበሩዋቸው የአማራ ብሔረሰብ ተወላጆች፣ ንብረታቸውን ...ለክልሉ ተወላጆች እንዲያስረክቡ በመዳረጋቸው ብዙዎች ድርጅቶቻቸውን አስረክበው ወደ መሀል አገር ሄደዋል በማለት ኢሳት የዘገበው የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ ም ነው። ተወልደው ያደጉበትን ቦታ አንለቅም በማለት እስካሁን የቆዩትም በተለያዩ አስተዳዳራዊ ጫናዎች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ በደብዳቤ እና በቃል ተነግሯቸዋል።
በጅጅጋ ከተማ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ለኢሳት በጻፉት ደብዳቤ “የአንድ ብሄር የበላይነት በሰፈነበት መልኩ አማራ ወይም ሀበሻ የሚል መጠሪያ ተደርጎልን እነሆ ከህጻናት እስከ ትልቅ በመንገድም በቢሮም እየተሰደብንና እየተተፋብን መኖራችን ሳያንስ፣ አሁን ደግሞ ያለምንም ልዋጭ ቤታችን ተቀምቶ ጎዳና ላይ ተጥለን እንገኛለን” ብለዋል። ነዋሪዎቹ አክለውም “የእኛ ልጆች እንደልብ በመንገድ ላይ መሄድ አይችሉም፣ ሱሪ የለበሰች ሴት በፖሊስ ዱላ ትደበደባለች፣ ማን ፖሊስ ማን ሀላፊ እንደሆነ በማናውቀው ሁኔታ፣ የሸሪያ ፍርድ ቤት የሚል ተቋቁሞ ቤታችንን እንድንለቅ እያስገደደን ነው። ተወልደን ባደግንበት አገር እንደ ሁለተኛ ዜጋ እንደቆሻሻ እየታየን ነው” ብለዋል።
አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የከተማው ነዋሪ በክልሉ የመኖር ተስፋቸው መሟጠጡን ተናግረዋል። ኢሳት በጅጅጋ ከተማ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰውን በደል በተደጋጋሚ መዘገቡንና መንግስትም ዝምታ መምረጡን አስታውቃል።

Sunday, March 3, 2013

Ethiopian Muslims protest: a rise of sociopolitical consciousness


by Mubarak Keder
The relationship between the Ethiopian Muslim community and the government has always been on a delicate balance reached by a compromise made by the Muslim community. For the most part, given the authoritarian rule the country is under, the Muslim community tolerated the government’s unconstitutional involvement in their religious affair and institutions. In particular, the Muslim community has, for long time, been unsettled by the government’s heavy-handed involvement in the supposedly independent Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council commonly known as Majlis. Consequently, the Majlis have been as ineffective in executing the tasks entrusted by the community. However, it was not this specific circumstance that gave way for the growing protest in the country that has been going on for more than a year.
Tension between the two start to grow when the government decided to import followers of Islamic sect from Lebanon,Ethiopian Muslims rallying all over Ethiopia known as Ahbash, on a bold and ambitious move – that disrupted the long wrestled balance between the two – to implement a Nationwide plan to introduce and impose Al Ahbash ideologies, which is completely alien to Ethiopian Muslims. Al Ahbash, is an organization based in Lebanon, formally known as Association of Islamic charitable project, which describes itself as a charitable organization promoting Islamic culture. Despite the group’s claim, some have hard time understanding the true objective of the group, one of the reasons for this being the fact that the group was in the center of the UN probe into the murder of the former Lebanese Prime Minister Rafik Hariri, following the UN inquiry naming two of its active members as key suspects.
In July 2011, the Ethiopian government has aggressively mobilized to change the country’s Muslim belief for that of ‘Ahbashism’. To this effect, it launched a nationwide training of imams and Islamic scholars in Ahbash ideologies side by side with ‘revolutionary democracy’, which is essentially an indoctrination of EPRDF’s political ideology as the only and perfect fit to govern the country. Those imams and Islamic scholars who have either refused to take part in the program or teach it in their respective mosques have been removed from their mosques otherwise arrested; mosques and Islamic institutions that turned down the government’s demand have been closed.
The Muslim community came to find out about the government’s plan before it hardly take full effect; they understood this to be a grave aggression against their constitutionally bestowed right to freedom of religion and action that farther endangered a secular form of governance, which the government have been insisting on having. So, started the protest which spread from Awolia and Anwar mosques in Addis Ababa to different part of the country, and have been growing throughout it’s more than one year period. The disorganized Muslim community started to readjust; and the first important advance they made were to form an arbitration committee of 17 Islamic leaders to negotiate with the government regarding four issues: “1) respecting the Ethiopian constitution’s guarantees of religious freedom; 2) ending government imposition of al-Ahbash on Ethiopian Muslims, while allowing al-Ahbash to operate equally with other religious communities; 3) re-opening and returning schools and mosques to their original imams and administrators; and 4) holding new elections for the EIASC, and having these elections take place in mosques, rather than in neighborhood government community centers, to ensure that the community’s selections would be honored.” as noted on the November 8, 2012 statement released by the United States commission on international religious freedom ( USCIRF).
However, the negotiation between the government and the arbitration committee failed to bring any result and the protest continued to grow in size and frequency. The same month the government arrested all 17 members of the committee along with other hundreds of protesters. Since July 13, Ethiopian police and security services have harassed, assaulted, and arbitrarily arrested hundreds of Muslims at Addis Ababa’s Awalia and Anwar mosques who were protesting government interference in religious affairs, Human Rights Watch said.
While the protest continued to gain the overwhelming support of the Muslim population, instead of dealing with the grievance of the people, the government rather got invested in campaigning to characterize the movement as a question of the few propagated by ‘extremist elements’ in the country, belittling the legitimate constitutional demand of the people. The EPRDF government attempted to justify it’s unconstitutional action as a measure that needed to be taken to eliminate terrorist cells – allegedly are trying to establish Islamic state – threatening the secular form of government. The Muslim community rejected linking the protest with terrorism as a misrepresentation of the legitimate concerns raised in a desperate attempt to scare away the support the movement is gaining. Ironically enough, the protesters demand is, for the government to uphold the laws that are entrenched in the constitution to maintain a secular state, on the contrary to that asserted by the government. This position by the protesters transcended the movement from being a theological one to that of a struggle to protect constitutional rights which the government is defying.
The statement issued by the USCIRF backed the protesters’ claim that, “Since July 2011, the Ethiopian government has sought to force a change in the sect of Islam practiced nationwide and has punished clergy and laity who have resisted.” And, when the negotiation between the committee and the government had failed in July 2011, and as the protest start to grow, “the Ethiopian government started to crack down on and intimidate the demonstrators, surrounding them with armed guards and conducting house-to-house searches.” The report further stated, “The government also has manipulated the election of the new leaders of the Ethiopia Islamic Affairs Supreme Council (EIASC). Previously viewed as an independent body, EIASC is now viewed as a government-controlled institution. The arrests, terrorism charges and takeover of EIASC signify a troubling escalation in the government’s attempts to control Ethiopia’s Muslim community and provide further evidence of a decline in religious freedom in Ethiopia.”
Regarding those people arrested during the protest the statement issued by the Amnesty international, on November 2, 2012 rebuked the government’s allegation, stating “These individuals appear to have been arrested and charged solely because they exercised their human rights to freedom of expression and to participate in a peaceful protest movement.” The report also expressed concern regarding the country’s vague anti-terrorism law and its application saying, “Since its introduction in 2009 the excessively broad Anti-Terrorism Proclamation has predominantly been used to prosecute dissenters and critics of the government, including journalists and members of political opposition parties.”
Given the level of very little, if any, freedom of expression in the country, the protest is being met with great difficulty. The people have been well aware of the risk in assembling or staging a protest. The last time the people held a demonstration, in 2005 opposing the ruling party; more than 200 people got killed. Taking this experience into account, the Muslim community was forced to come up with a way to avoid any violent incidents from happening. To this effect, instead of holding a big mass demonstration in the cities’ squares, the Muslim community have been holding the protests in separate mosques after the Friday (Jumah) prayer, where large congregation gather; and to avoid any circumstance that might give a chance for the police to turn the peaceful protest into chaos, the protesters come up with an innovative means to circumvent the challenges that are set and to get their messages across. The protesters used white and yellow placard and papers, and hold silent demonstration as a sign of peaceful intention, and as way of refuting the government’s assertion of the protest as provocative. Even though holding a mass protest in a single location might have been effective in putting the spotlight on the issues the people raised and pressuring the government for a quick measure to deal with the grievance of the community, however, with the current political environment in the country it were deemed impractical. Besides, having the protest in separate smaller group has its own perks: one of which is the fact the protest have been able to continue for more than a year, which would have been unattainable as the cost of continuing the protests would have been impossible to bear and the movement would have been long suppressed or weakened shortly. The most important thing for the community have been to keep the movement alive until their questions are being answered, fortunately enough for the community, the weekly Friday prayer offered convenient enough platform to attain this objective. The people were also able to overcome the challenge of weak communication infrastructure and managed to unify their voices. Most importantly of all, the protesters have been able to keep an impeccable record of staying peaceful, despite the provocation, depriving the government any opportunity to misconstrued the movement as a violent one and easily squash it.
Throughout the protest, the other main challenge the movement faced has been the apparent absence of free press, which left protesters to be a victim of smear campaign by the state media and no independent media outlet to have an independent investigation and coverage of events. While the EPRDF government used the state media as a propaganda tool to portray the protest as violent, terrorist-related and orchestrated by the few, it has been as much invested in cracking down the few independent newspapers for covering the protest. Journalists who published article regarding the protest were imprisoned on charges of treason and incitement to violence; police, even, raided the printing company which published the newspapers. “Ethiopia has reached a high level of harassment of the press by attempting to censor coverage of the protests,” said CPJ(committee to protect journalists) East Africa Consultant Tom Rhodes.
International human rights and other related organization have been fast to condemn the government’s action and call for a rapid judicial process. While the idea of bringing those arrested swiftly to judicial authorities and have a due process is sound and reasonable, one important fact that is being overlooked is the apparent absence of the rule of law and independent judiciary in the country. In spite of what is stated in the constitution there is no practical distinction between the executive and judicial branch of government on the ground, making it impossible for the people to see the obscure line that differentiate being charged of a crime to that of being convicted of one. One manifestation of this is the ‘documentary’ that aired on February 6, 2013 on the state controlled Ethiopian Television, which basically,’ investigated ‘ the allegation , ‘charged’ those suspected and ‘convicted’ them of a crime, all these while court hearing is far from being half way, and throwing the basic principle of ‘innocent till proven guilty’ to the side.
while the mark the movement will have on the history of the country is something to be seen, the course the protest will take and the roll it will play in the sociopolitical sphere will largely depend on the level of sociopolitical consciousness the society possess, by which the people in general, stand to defend the common principles regardless of the groups being involved. This level of consciousness by which the general public is well informed about their country’s affair and, as much importantly, are actively involved in dictating and further safeguarding the principles and values they want their country to be governed a complex development to bring given the current sociopolitical structure in the country. However, the unprecedented persistency and solidarity the people that have been exhibited by this movement for more than one year just might be an indication to the changing course.

Saturday, March 2, 2013

የስዑዲ ማስጠንቀቂያና የኢትዮጵያ ምላሽ

    
ሰሞኑን አንድ ከፍተኛ የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣን ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ የተነሳ በግብጽና በሱዳን የአባይ ወንዝ አጠቃቀም መብት ላይ አደጋ እየጣለች ነው ማለታቸውን ሱዳን ትሪብዩን የተሰኘው ድረ ገጽ ዘግቧል። ባለስልጣኑ የተናገሩት የሳውዲ አረቢያ መንግስት
አቋም መሆን አለመሆኑን አጣርቶ የኢትዮጵያ መንግስት ሰሞኑን መግለጫ እንደሚያወጣ ተዘግቧል። ሱዳን ትሪብዩን የተሰኘው ድረ ገጽ ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ምክትል የመከላከያ ምክትል ሚኒስትር ካሊድ ቢን ሱልታን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለው ፕሮጀክት፣ ግብጽና ሱዳን በወንዙ ላይ ያለቸውን መብት አደጋ ላይ እንደሚጥል መናገራቸው ተሰምቷል። ከሱዳን ድንበር 12 ኪሎሜትር ርቆ እየተሰራ ያለው የህዳሴ ግድብ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ይልቅ ለፖሊቲካ አሻጥር የሚያገለግል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃለ አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የተባለው ዜና የሳውዲ አረቢያ መንግስት አቋም መሆኑን አጣርቶ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ መግለጫ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፣
ይህ በሰባ አራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር በመሰራት ላይ ያለው ግዙፍ የግድብ ፕሮጀክት ተፋጥኖ እየጨመረ ያለውን የኢትዮጵያን ህዝብ ለመመገብና በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የምግብ እጥረት ለመቋቋም እንደሚረዳ የኢትዮጵያ መንግስት ይናገራል።
ኢትዮጵያና ሳውዲ አረቢያ ጥሩ የኦኮኖሚ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው። በርካታ የሳውዲ አረቢያ ባለጸጋዎች መዋለ ነዋያቸውን በኢትዮጵያ ውስጥ ያፈሳሉ። ታዋቂው የኢትዮጵያ ባለሐብት ሼ ሞሐመድ አል-አህሙዲም የሳውዲ አረቢያ ዜግነት አላቸው።

ኢትዮጵያ በአብዛኛው ለቤት ውስጥ ሥራዎች ብዙ ሰራተኞችን በየዓመቱ ወደ ሳውዲ አረቢያ ትልካለች። የምክትል መከላከያ ሚኒስትር ካሊድ ቢን ሱልጣን መግለጫ ኢትዮጵያ ከሳውዲ አረቢያ ጋር ካላት ከዚህ ትስስር ጋር የማይሄድ ነው ይላሉ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤

በግብጽ የፕሬዞዳንት ሙርሲ መንግስት ስልጣን ላይ ከወጣ ወዲህ በሳውዲ አረቢያና ግብጽ ግንኙነት እያደገ መምጣቱ ይነገራል። የብሪታኒያውያኑ የፖሊቲካ ጥናት ተቋም ቻተም ሃውስ የአፍሪቃ ቀንድ የፖሊቲካ አዋቂ ጃተም ሞስሊ እንዳሉት የሳውዲ አረቢያ መንግስት የአባይ ወንዝ ጉዳይ አይመለከተውም ማለት ይከብዳል፤


«የግብጽ የውሃ ጉዳይ ለግብጽ ብሔራዊ ጸጥታ በጣም አስፈላጊ ነው። የአሁኑ የግብጽ መንግስት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ግብጽና ሳውዲ አረቢያ ግንኙነታቸውን አሳድገዋል። ግብጽ ለሳውድ አረብያ ቅርብ ሀገር ናት። ስለዚህ በግልጽ እንዲህ ነው ባይባልም፣ በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ የሳውድ አረቢያ ፍላጎት የለበትም ማለት አይቻልም።»

ግብጽ የአረቡን አቢዮት ተከትሎ በተከሰተው የውስጥ አለመረጋጋት ምክንያት በምስራቅ አፍሪቃ ያላት የፖሊቲካ ተጽዕኖ ቀንሷል። ሱዳንም የደቡብ ሱዳንና የዳርፉር ችግሮች ፊቷን ከአከባቢው ፖሊቲካ እንድታርቅ አድርጓታል። በሌላ ኢትዮጵያም የአባይ ወንዝ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም በብርቱ እየገፋች ነው።
በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ ንትርክ ከተጀመረ ከሃምሳ ዓመታት በላይ ሆኖታል። ግብጽ የአባይ ወንዝ አጠቃቀምን በተመለከተ እአአ በ1929 የተፈረመው የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ትፈልጋለች።


ኢትዮጵያና የላይኛው አባይ ተፋሰስ ሀገራት ግን ሁሉን ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምንነት እንዲፈረም ይሻሉ። እአአ በ2010 ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች አራት የአባይ ተፋሰስ ሀገራት በአባይን ውሃ ክፍፍል ላይ በዩጋንሳ ኢንቴቤ ከስምምነት ደርሰዋል። ከአንድ ዓመት በኋላም ጎራውን ተቀላቅላለች።

Friday, March 1, 2013

በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ሲሆን ፣ የወያኔ ካድሬዎችም ድርጊቱን ለማስቆም የተጠናከረ አሰሳ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።


በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ሲሆን ፣ የወያኔ ካድሬዎችም ድርጊቱን ለማስቆም የተጠናከረ አሰሳ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለው የሕዝብ መነሳሳት ስሜትና ተጋድሎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከለውጥ ፈላጊው ሕዝብ ጎን የቆመ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያቶች በጠላት ላይ በሚያደርሰው ጥቃት የሀገርና የወገን ደራሽነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ከወታደራዊ ትግሉ ጎን ለጎን የአካባቢውን ህብረተሰብ የማስተማር፣ የመቀስቀስ፣ የማደራጀትና የማስታጠቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገለፀ።
በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኛች ግንባር ደጋፊዎች አማካኝነት የድርጅቱ ወቅታዊ የሀገር አድን ጥሪ በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ በመገኘቱ ስጋት የገባው አሸባሪው የወያኔ ገዥ ቡድን የቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ወከባና እንግልት እያደረሰ እንደሚገኝ ከስፍራው የደረሰን የመረጃ ምንጭ ያስረዳል።
በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለው የሕዝብ መነሳሳት ስሜት በተደራጀ መልኩ እንዲቀጥልና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀጣጠለ የመጣው ሕዝባዊ ተቃውሞ ለፍሬ ይበቃ ዘንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ተነስ! ታጠቅ! ዝመት! የሚለውን ወቅታዊ የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት በሃገሪቱ በተለያዩ ከተሞች በብዛት እንዲሰራጩ በድርጅቱ ደጋፊ አባሎች አማካኝነት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረግን ሲሆን ይህ የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀትም በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነትን ከማግኘቱም በተጨማሪ ለስርዓት ለውጥ በሚደረገው የትጥቅ ትግል መላውን ህብረተሰብም መነሳሳትን እንደፈጠ...ረለትና የተጀመረውም ሕዝባዊ አመፅ ግፊቱ እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።
በመተማና አካባቢው እየተሰራጨ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት ዋና አላማ የኢትዮጵያ ሕዝብ በወያኔ ላይ ያለው ጥላቻ ግልፅ ማድረግ ቢሆንም ሕዝብ እንደ ሕዝብ እጅ ለእጅ በመያያዝና በመደጋገፍ በአምባገነኑና አሸባሪው ገዥ ቡድን አፋኝና ቀፍዳጅ ስርዓት ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር መነሳት፣ መታጠቅና መዝመት የወቅቱ አንገብጋቢ ጉዳይ በመሆኑ ህብረተሰቡ የጀመረውን ሕዝባዊ ተቃውሞ አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ የታለመ ሲሆን በዚህ የተደናገጠው ወያኔና ተላላኪዎቹ በአካባቢው ነዋሪ ህብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር የቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ ህብረተሰቡን በማስፈራራትና በማዋከብ ስራ ላይ ተጠምደው እንደሚገኙ ከስፍራው የደረሰን የመረጃ ምንጭ ያስረዳል።
አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳትና ተጨባጭ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ ህብረተሰቡን ለበለጠ የፀረ- ወያኔ የሚያነሳሱ በራሪ ወረቀቶችን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በሰፊው በማሰራጨት ትግሉ የደረሰበትን የእድገት አቅጣጫ እንዲሁም አናሳው የወያኔ ቡድን በሕዝብና በሃገር ላይ እየፈፀመ ያለውን ስውር ደባ በማጋለጥ ክፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልፀው፣ የጀመሩትን ፀረ- ወያኔ አመፅና ተቃዎሞ አጠናክረው እንደሚገፉበትና የድርጅቱን ወቅታዊና የሀገር አድን የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት በተለያዩ ቦታዎች በሰፊው የሚሰራጭበትን ስልት ቀይሰው እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል።
 
    ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!