Saturday, December 6, 2014

ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?

December 6,2014
ከክንፈ አሰፋ
teddy-afro1
ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ጋባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.።
የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል።
ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ አገቱት። በውድቅት ሌሊት ፓስፖርቱን ነጥቀው ወደ ቤቱ አሰናበቱትም። ይህንን ያደረጉበትን ምክንያትም አልነገሩትም።  አስቀድመው ገና ከበሩ ላይ መከልከል ይችሉ ነበር።… ግን ማንገላታት ነበረባቸው። ስሜቱን ለመጉዳት መሞከር ነበረባቸው። ጉልበት እንዳላቸው ማሳየት ነበረባቸው። ፈላጭ፤ ቆራጭ መሆናቸውን ማሳወቅ ነበረባቸው። ቂመኞችና ተበቃዮችም መሆናቸውን መናገር ነበረባቸው። ….
ነገሩ ያልተጠበቀ ባይሆንም፤ ለቴዲ ጠበቆች ግራ ማጋባቱ አልቀረም።  በነጋታው ጠበቆቹ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፍርድ ቤት መሄድ ነበረባቸው። ከፍርድ ቤት ያገኙት ምላሽ በቴዲ አፍሮ ላይ ምንም አይነት የማገጃ ትዕዛዝ ያለመኖሩን ነው። ከዚያም ወደ ኢሚግሬሽን ጉምሩክ እና ሌሎች ጉዳዩን የሚመለከቱ ቢሮዎች ሁሉ አመሩ። እዚያም የጉዞ ማገጃ አልተገኘም። ታዲያ ማን ይሆን ያዘዘው? የካዛንችዙ ስውር መንግስት ስራውን እንደገና ጀምሮ ይሆን?
ጉዳዩ ግራ ያጋባል። እርግጥ ነው። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አንድ ተራ ካድሬ እንዲህ አይነት ተራ ወንጀል የሚፈጽምባት ሃገር ሆናለች። አንዳንድ ቦታዎች ላይ “መንግስት የለም እንዴ?” የሚያስብሉ ወንጀሎች እንደሚፈጽሙ ይሰማል።  የቀድሞው የኮሚኒኬሽን ሚንስትር ዴዔታ የነበረው ኤርምያስ ለገሰ፤ በቅርቡ ባሳተመው “የመለስ ትሩፋቶች” የተሰኘ መጽሃፉ አዲስ አበባን ባለቤት አልባ ከተማ ብሏታል።
በልማታዊ አርቲስቶች እለት-ተለት የሚወደሰው ጸሃዩ መንግስት፤ ለልማት የተጋው መንግስት፣ ጭቆናን ያቆመው መንግስት፤ ለዜጎች መብትና ነጻነት የቆመ መንግስት፣ ሃገሪቱን ወደ እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ጎዳና ላይ ያስኬደ መንግስት፣ የመቻቻል ባህልን ያመጣ መንግስት…. እንዴት ሆኖ የጥላቻ፣ የቂም እና የበቀል እርምጃ ሊወስድ ቻለ?
ልማታዊ አርቲስቶቻችን ይቅርታ አድርጉልኝና የአስተሳሰብና የአመለካከት ለውጥ ሳይኖር ቁሳዊ ለውጥ ይመጣል ብሎ የነገራችሁ ማን ይሆን? አመለካከታችን ካላደገ፣ እድገት ይታሰብ ይሆን?
ወደ ጉዳዩ ስንመለስ፣ ከፊንላንድ በኋላ ሌሎች ስድስት የአውሮፓ ከተሞች ላይ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። ፕሮሞተሮች ለመሰናዶው ብዙ ወጪ አውጥተዋል። የአርቲስቱ አድናቂዎችም አስቀድመው ትኬት ቆርጠዋል። ይህንን ካድሬዎቹ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ሁሉንም ማጉላላቱ፤ ከተቻለም ማደናቀፉ ደስታን ይሰጣቸዋል። እንዲህ አይነት የድፍረት ስሜት የሚመነጨው አርቲስቱን ሳይሆን ይልቁንም ሕዝብን በጅምላ ከማናቅ ነው። ሕዝብን ከመጥላት። እየገዙት ያሉትን ህዝብ መናቅና መጥላት የት ድረስ ሊያደርሳቸው እንደሚችል የምናየው ይሆናል። እንደ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን እንደ እንስሳ የሚያስቡ እነዚህ የዘመናችን ጉዶች ሕዝብ የሚወደውን ነገር በሙሉ በመጥላት፤ የህዝብ አካል እንዳልሆኑ እይረጋገጡልን ነው። ከጫካ ከወጡ 21 አመታትን አስቆጥረዋል። አካላቸው ከጫካ ወጣ እንጂ አመለካከታቸው ግን እዛው እንደሆነ ድርጊታቸው ይነግረናል።  ከሁለት ዓስርተ-ዓመት በኋላም ጥንት ከሚያስቡበት ከጫካው ህግ አልተላቀቁም።
ይህንን ትልቅ ሃገር እና ይህንን ትልቅ ሕዝብ እየመሩ ለምን እንደመንገስት ሊያስቡ እንደማይችሉ አይገባኝም። መንግስት ሆነው እንደግለሰብ ቂም ይይዛሉ። ቂም ይዘው እንደ ክፉ ሰው ይበቀላሉ። ሀገር ደግሞ በጥበብ እና በማስተዋል እንጂ፤ ከቶውንም በቂም እና በበቀል አትመራም። ይህንን የሚያደርጉ ሁሉ መጨረሻቸው ውድቀት፤ አወዳደቃቸውም የውርደት እንደሆነ ለደቂቃ አስተውለውት የሚያውቁ አይመስለኝም።
እንግዲህ ይህ ተራ ወንጀል በዚህ ድንቅ አርቲስት ላይ ሲፈጸም የመጀመርያ አይደለም። ከወራት በፊትም ወደ አሜሪካ ሊጓዝ ሲል የአየር መንገዱ ካድሬዎች ይዘው ብዙ አጉላልተውት ነበር። እርግጥ ነው ቴዲ አፍሮ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰውበታል። ኤርምያስ ለገሰ፤ በ”መለስ ትሩፋቶች” መጽሃፉ ላይ የቴዲን ጉዳይ አንስቶ የገዢው ፓርቲ ሰዎች ይህንን አርቲስት እንዴት በክፉ አይን እንደሚመለከቱት ዳስሷል። ይህ አርቲስት ምናልባት በአንዲት ዜማ ተችቷቸው ይሆናል። እነሱም አላለፉትም። በፍትህ ስም የበቀል ዱላቸውን አሳርፈውበታል። ወህኒ ወርዷል። እስኪበቃቸውም ቀጥተውታል።
ቴዲ አፍሮ ግን ቂም አልቋጠረባቸውም። አሁንም የሚያቀነቅነው ስለ ፍቅር ነው። አሁንም የሚለው እንዲህ ነው። “ፍቅር ያሸንፋል!”
እነዚህ ሰዎች ሃያ ሁለት አመታት ሙሉ ከጥፋት አለመማራቸው ብቻ አይደለም የሚደንቀው። በአንድ ግለሰብ ምክንያት ከሚሊዮኖች ጋር እንደሚላተሙ አለማሰተዋላቸውም የሚገርም ነው።  ለሟቹ ፓትሪያርክ ሲሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኦርቶዶክስ ምዕመናን ጋር ተቃርነው ነበር። አንድ የሙስሊም መጅሊስ መሪን ለመያዝ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ጋር ጠፋጥተዋል።
ዛሬ አንድ ቴዲን ቢያንገላትቱት፣ ቢያግቱትም ሆነ ፓስፖርቱን ቢነጥቁት ለግዜውም ቢሆን የአድናቂዎቹን ስሜት ሊጎዱት ይችሉ ይሆናል። ይህ ድርጊታቸው ቴዲ አፍሮን ቅንጣት ያህል አይጎዳውም።  ይልቁንም የበለጠ ተወዳጅ እና የበለጠ ጀግና ያደርገዋል።  ከዚህ የፖለቲካ ንግድ እነሱ የሚያተርፉት ነገር ቢኖር የህዝብ ጥላቻን ነው። የቴዲን መታገት የሰሙ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ሳይቀሩ እንዲህ ሲሉ ተደመጡ፤ “አሁንስ አበዙት… ሃገራችንን እንድንጠላ አደረጉን….” ካድሬዎቹ ማህበራዊ ድረ-ገጾችን ቢጎበኙ የህዝቡን ስሜት ያነብቡ ነበር።
በሕዝብ አመኔታ ሳይሆን ይልቁንም በጆሮ ጠቢዎችና በመሳርያ በመተማመን እስካሁን ስልጣን ላይ ላላችሁት ገዢዎች ግን አንድ የምለው አለኝ።  የፈረንሳዩ አንባገነን ናፖሊዮን ቦናፓርት የነበረውን ሰራዊት እስተውሉ። ይህ ግዙፍ እና የሰለጠነ ሰራዊት በህዝብ እንደ አሸዋ ተበተነ። የግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ያልታሰበ እና ያልታለመ ውድቀት የመጣው እንዲሁ በመሳርያ ከመተማመን እና ህዝብን ከመናቅ ነበር። ይህ አስደንጋጭ ትዕይንት ለእናንተ ትምህርት ካልሰጣቸሁ የሱ እጣ ፈንታ ይጠብቃችኋል። መቶ አመት የቆየ አንባገነን ገዢ በታሪክ አላየንም።
Breaking News from Helsinki: 

‹‹የከተማ ጦርነት አውጃችኋል!የተዘጋጀ ኃይል አለን ልካችሁን ያሳያችኋል›› ኮሎኔል ዘውዴ የየካ/ክ/ከ/ፖ/መ/ኃ

December 6, 2014
ሳሙኤል አበበ (በፖሊስ ታግቶ የነበረ)

ትናንት ከቀኑ 10 ሰአት አካባቢ ልክ እንደ ሰሞኑ ሌሎች ጓዶቻችን ላይ ይደረግ እንደነበረው የፖሊስና የደህንነት አፈና ሁሉ ፍቅረማርያም አስማማውን የህወሓት ቅልብ ደህንነትና ፖሊሶች አፍነው ወሰዱት፡፡ እኛም ቢያንስ ያለበትን ቦታ ለማወቅ ከትንታጉ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ጋር በመሆን ፖሊስ ጣቢያዎችን ማሰስ ጀመርን፡፡ የመጀመሪያ መዳረሻ የሆነን የየካ ክ/ከተማ አድዋ ድልድይ ፖሊስ ጣቢያ ሆነ፡፡ እንደደረስንም በር ላይ የነበሩትን ሁለት ፖሊሶች ጓደኛችን በፖሊስ ተይዞ ወዳልታወቀ ቦታ ስለተወሰደ እዚህ መኖሩን ለማረጋገጥ ነው ስንላቸው ‹‹ልጁ እዚህ ገብቷል፡፡ ግን ምርመራ ላይ በመሆኑ ትንሽ ቆይታችሁ ኑ!›› ተባልን፡፡

እኛም ‹‹ምን አልባት ሊያድር ስለሚችል እራት እናስገባለት›› አልናቸው፡፡ አሁን እኛን አላናገረንም፡፡ በቀጥታ ውስጥ የቆሙት ሁለት ፖሊሶች ጋር ሄዶ አነጋገራቸውና ተመለሰ፡፡ ‹‹አሁን አይቻልም፡፡ ሂዱና ቆይታችሁ ተመለሱ፡፡›› የሚል ትዕዛዝም ሰጠን፡፡ በትዕዛዙ መሰረት ፊታችንን ከማዞራች ሰከንድ እንኳ ሳይሞላ ከውስጥ በጎርናና ድምጽ ‹‹ኑ ተመለሱ! እናንተም ትፈለጋላችሁ፡፡›› በማለት አምባረቀብን፡፡ እኛም ሳናቅማማ ገባን፡፡ ሁለቱም ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት ይነበብባቸዋል፡፡ የማስፈራሪያና ማሸማቀቂያ ቃላትን በተደጋጋሚ ይናገራሉ፡፡

እኛ ደገሞ ውስጣችን ያለው እውነት ነውና እንዳሰቡት ልንደናገጥላቸው አልቻልንም፡፡ ጓደኛዬ በላይ ማናዬን ‹‹ስትገባ ስቀሃልና ምን እንዳሳቀህ ንገረን!›› አለው አንደኛው ፖሊስ! በላይም ‹‹ይህ የአኔ የግል ጉዳይ ነውና ልትጠይቀኝም፣ ልነግርህም አልችልም›› ብሎ በልበ­ሙሉነት መለሰለት፡፡ ቀጥሎም‹‹ተፈተሹ!›› ተባልን፡፡ እኛም ‹‹ፍ/ቤት ትዕዛዝ ካልተሰጠ በስተቀር ምንም ሰው ሊፈተሸ አይገባምና እኛም አንፈተሸም›› አልን፡፡ እነሱም አስገድደው ፈተሹን! እንዲያውም ‹‹እኛምኮ ህግ እናውቃለን፡፡ እንድፈትሽም የለበስነው የፖሊስ ልብስ መብት ሰጥቶናል፡፡.ወዘተ..›› በማለት ህጉን ሳይሆን ፍላጎታቸውን ነገሩን፡፡

በዚህም ንትርክ መሃል የክፍለ ከተማው ኃላፊ ኮሎኔል ዘውዴ የተባሉ ሰው ግቢውን ዘልቀው እኛ ጋር ደረሱ፡፡ እንደደረሱም ‹‹እነኚህን ልጆች አውቃቸዋለሁ፡፡ ከአንተ ጋር በተደጋጋሚ ቁጭ ብለን አውርተናል፡፡ ግን ሁሌም ያው ናችሁ፡፡ ሊገባችሁ አልቻለም፡፡›› አሉን፡፡ በእርግጥ እኚህ ሰውዬ ጋር ለሚያዚያ 19/06 ዓ.ም የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ የወጡትን የፓርቲውን አባላት ከመንገድ ለቅመው ያሰሯቸውን ልጆች ለመጠየቅ በሄድኩ ጊዜ ከሁለት ሰዓት በላይ የፈጀ እልህ አስጨራሽ ክርክር አይሉት ውይይት ብቻ ቅጥ የሌለው ንግግር እንዳደረግን አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ ያሉኝ ‹‹እናንተ ምን ፈልጋችሁ ነው? ልማቱ ተፋጥኗል፡፡ መንገዱ ኮንዶሚኒየሙ፣ ግድቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ወዘተ ተገንብተዋል›› በማለት የተሞሉትን ዘከዘኩልኝ፡፡

እኔም ባይሰሙኝም ‹‹እዚህ አገር ያለው ስርዓት የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቀውስ መውጣት ወደማንችልበት አዘቅት ውስጥ እየከተተን እንደሆነ ስነግራቸው etv እንደሚለው ጸረ­ልማት ብለው ከመፈረጅ አልተቆጠቡም፡፡ ዛሬም ከ8 ወር በኋላ ስንገናኝ በአቋማቸው ጸንተው እንዲያውም ከሬድዋን ሁሴን በልጠው አገኘኋቸው፡፡ ከላይ እስከታች እየገላመጡ ‹‹ከእናንተ ጋር እንተዋወቃለን፡፡ የከተማ ጦርነት አውጃችኋል፡፡ ይህ ደግሞ አይቻልም፡፡ ጫካ ግቡና ጦርነት ክፈቱ፡፡ ያኔ የተዘጋጀ ኃይል አለን፡፡ ልካችሁን ያሳያችኋል፡፡›› በማለት የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት ነገሩን፡፡ እነሱም እንዳሰቡት ልንሸማቀቅና ልንሰግድላቸው አልቻልንም፡፡ ረዥም ጊዜ ካቆዩን በኋላ ተጠራን፡፡ ስልካችንና መታወቂያችን መንግስቱ የተባለ መጀመሪያ ያገተን ፖሊሲ ይዞት መጣ፡፡ በማዝተዛዘንም ‹‹የያዝናችሁ በአመለካከታችሁ ወይንም እኛ ለአንድ ወገን በመቆም አይደለም፡፡ የያዝናችሁ ለሁላችንም ደህንነት ስንል ነው፡፡ ግን ላንግባባ እንችላለን፡፡›› በማለት አስረዳን፡፡ እኛም መጀመሪያ ዱላ ቀረሽ ንግግር፣ ክብር የሚነኩ ቃላትን ሲተፋ የነበረ ሰው አሁን ይህን ቢለን እንዴትስ ሊገባን ይችላል? ግቢውንም በእኩለ­ሌሊት ለቀን ወጣን፡፡ በመጨረሻም እንዲህ ልላቸው ወደድኩ፤ በእያንዳንዷ ቀን የምትፈጽሙብን ግፍ ለእኛ ብርታት፣ ትግላችንም አስፈላጊ መሆኑን የበለጠ ያስረዳናል እንጅ እናንተ እንደምታስቡት ይህ ግፍ መቀጣጫ ሆኖን ወደየ ቤታችን ፈጽሞ ልንመለስ አንችልም፡፡ ትግላችን እስከ መስዋዕትነት ደረስ ነው!!

Friday, December 5, 2014

ከመተባበርና አንድ ከመሆን በላይ ታላቅነት የለም – የሰማያዊ ከፍተኛ አመራር

December 5,2014
ፍኖተ ነፃነት
“አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብጭ፡፡”
“በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።”
ወ/ሮ ሃና ዋልለልኝ ይባላሉ። የሰማያዊ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ናቸው። ፍኖተ ነጻነት ባወጣው 86ኛ እትሙ ቃለ መጠይቃ ካደረገላቸው የተወሰደ ነበር። ከቅአለ መጠይቅቁ የተወሰነዉን እንደሚከተለው አቅርበናል።
ፍኖተ ነፃነት፡- በመጪው ምርጫ ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንድን ነው የሚጠበቀው?
10344785_738568506228086_275256779448546603_n

ወይዘሮ ሀና፡ – ከተቃዋሚዎች የሚጠበቀው እርስበርሳችን በመስማማትና ትንንሽ ልዩነቶቻችንን በማስተካከል ባለችው ቀዳዳ፣ ጠባብ ቀዳዳ ማለት እችላለሁ ሾልከን ለውጥ ለማምጣት መትጋት ነው፡፡ የረጅም ጊዜ ልምድ አለ፤ ከዛ ውስጥ ደግሞ ነጥረው የሚወጡ ሰዎች ይኖራሉ፤ የሚታዩም አሉ። ጥሩ ጥሩ ወጣቶችም እያደጉና እያበቡ ነው። እነዚህን ነገሮች ወደ ተግባር ወይም ወደ ውጤት በመቀየር ለምርጫ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል። ምክንያቱም ሀገሪቷ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በምርጫ የሚመጣ ስልጣን ብናገኝ በእውነት ይህቺ ሀገር ታላቅ ትሆናለች። ጥሩ ነገርም ይታይባታል፡፡ስለዚህም እርስ በእርሳችን በብዙ ፍትጊያ ውስጥ አልፈን በብዙ ዘረኝነት ውስጥ አልፈን እዚህ ደረጃ መድረስ ራሱ ትልቅነት ስለሆነ ይሄን ብናደርግ ደግሞ የተሻለ ትልቅ ሰው እንሆናለን ብዬ አምናለሁ። እርስ በርሳችንም እንከባበራለን፤ እንቻቻላለን፤ መቻቻሉ ግን በመተማመን ውስጥ መሆን አለበት ብዬም አምናለሁ።
ፍኖተ ነፃነት፡- በፖለቲካ ፓርቲዎች አብሮ በመስራት ላይ ሁለት አይነት አስተሳሰቦች በአደባባይ ሲራመዱ እናስተውላለን። ፓርቲዎች አንድ ላይ ተባብረው መስራት አለባቸው የሚል ወገን አለ፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ብቻቸውን ነጥረው መውጣት አለባቸው ይላል፡፡ባንቺ አመለካከት አሁን ካለው የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አውድ አንጻር የትኛው ያዋጣል
ወይዘሮ ሀና፡- ፓርቲዎች ነጥረው ይወጣሉ የሚለው ነገር የእኔም ሀሳብ ነበረ። ጥረቱ ጥሩ ነው። ባልተሄደበት መንገድ መሄድ የአስተዋይነት ምልክት ነው። ባለንበት እንቁምና ባለንበት እንርገጥ የሚል አስተሳሰብ መኖር የለበትም። ሁልጊዜ የሰው ልጅ አዲስ ነገርን ይፈልጋል። አዳዲስ ነገሮችን ማምጣት ይፈልጋል። ስለዚህ ያልተደረጉ ነገሮችን መሞከርና ማድረግ ጤናማነት ነው። ያ ደግሞ የማይሳካበትን ሁኔታ ካወቅን ወይም ደግሞ በፊት አብሮ መስራቱ አይጠቅምም ብለን ከነበረ አሁን ይጠቅማል ወደሚለው ነገር ላይ አስተሳሰባችን ከመጣ ደግሞ ያንን ተቀብሎ ማራመድ ምንም የሚጎዳ ነገር አይደለም።
ሁለቱም ሀገርን ለመጥቀም ለውጥን ለማየት ከመፈለግ የመነጨ እስከሆነ ድረስ ጤናማ ናቸው፡፡ ለየብቻ መስራት የሚያዋጣ ነው ብለን እርግጠኛ ስንሆን ብቻችንን መስራት ይኖርብናል። እኔ አሁን ያለኝ እምነት አብሮ መስራት ታላቅ ያደርጋል ነው። ሁለተኛው ነገር ደግሞ ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሃኒቱ የሚለው ተረት ቀላል አይደለም። በሶስት የተገመደ ገመድም ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ እናውቃለን። ከዚህ በፊት ለብቻችን ነጥረን እንውጣ የሚለውን ሀሳብ ከሚያራምዱት ውስጥ ነበርኩኝ። ያም የተደረገበት ምክንያትም ከመገፋት ወይም ደግሞ አቅምንና ያለንን እውቀት ለማውጣትእንዳንችል ከመደረግ አንፃር ነው።ሆኖም ግን ያንን ነገር ለውጠን የአብሮመስራታችንን ብቃታችንን ክህሎታችንን አሳድገን አብሮ በመስራት ለውጥ ማምጣት፣ ራሱን የቻለ ስኬት ነው ብዬ አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብም፡፡ ራስን ለሀገር መሰዋት ማድረግ ያስፈልጋል። በነገራችን ላይ እኔ መስዋዕት የምለው የመሞት የመታሰርን ብቻ አይደለም፡፡ ትልቁ መስዋዕትነት ማለት ፍላጎትን ሁላ ማሸነፍ መቻልን ራስ ወዳድነትን ማሸነፍ መቻልንና ለሌሎች መኖር መቻልን ነው፡፡ ለሌሎች መኖርን መልመድ መቻል አለብን። በአፍ ሳይሆን በተግባር ይሄን ካደረግን የማይፈነቅል ድንጋይ አይኖርም።
ፍኖተ ነፃነት፡- የፓርቲዎች የውስጥ ዴሞክራሲ ምን መሆን አለበት ትያለሽ? በየፓርቲዎቹ ውስጥ ያሉ አስቸጋሪ ባህርያቶችስ ምንድን ናቸው?
ወይዘሮ ሀና፡- ብዙ ጊዜ ችግራችን መደማመጥ አለመቻል ነው ብዬ አስባለሁ። እንደገና ደግሞ እኔ አውቃለሁ የሚሉ ሰዎች ካሉ የሌላውን ሀሳብ የሚገፉ ከሆነ የመናገር መብትን የሚገድቡ ከሆነ ሁልጊዜ ችግር መፈጠሩ አይቀርም፡፡ ከዛ ይልቅ ግን መደማመጥ ቢኖር በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ቢኖር ስህተት ያለበትም ሰው ስህተቱን እንዲያምን በሀይል በጠብና በቁጣ ሳይሆን በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።
በሀሳብ ላይ መፋጨት በጣም ጠቃሚ ነው። የተሻለና የነጠረ ሀሳብ እንድናመጣም ያደርጋል። ያ ሰው ምንም ቢሆን ሀሳቡንም ማዳመጥ ማክበር ያስፈልጋል። እንደዚህ አይነት ነገሮችን አዳብረን ብንሄድ አሁንም ደግመዋለሁ የማንፈነቅለው ድንጋይ ይኖራል ብዬ አላምንም።
ፍኖተ ነፃነት፡- በመጨረሻ ማስተላለፍ የምትፈልጊው መልዕክት ካለ
ወይዘሮ ሀና፡- ማስተላለፍ የምፈልገው አንደኛ ለፓርቲዬ ማለትም ለሰማያዊ ፓርቲ ነው። ሰማያዊ ፓርቲ በውስጡ ምርጥ ምርጥ ወጣቶች አሉ፡፡ ብዛትም ባይሆን አንድ ሰው ለውጥ ያመጣል ብዬ አስባለሁ። ያንን ሰው ግን በአግባቡ መጠቀም መቻል አለብን ጓደኞቼን በጣም አከብራቸዋለሁ እወዳቸዋለሁ የአስተሳሰብ ልዩነታችንን በጣም አደንቃለሁ፤ በአስተሳሰብ ልዮነታችን ውስጥ ብዙ የተደበቁ ነገሮች ይወጣሉ ብዬ ስለማምን ስላየሁም ማለት ነው። ጥሩ ነገሮች ብቻ ሳይሆን የተደበቁ ስህተቶችም ይወጣሉ። ይህንን በደንብ አይቻለሁ፡፡ ይሄንን ነገር በደንብ አከብራለሁ። በውስጥ የሚሰራውንም ስራ በርቱ ግፉበት እላለሁ፡፡በተለይ በማንም ፓርቲ ውስጥ ያላየነውን የኦዲትና የኢንስፔክሽን ስራ አከብራለሁ ለዚህም በእውነት አድናቆቴን ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ጥሩ እየሰራ ነው። ፓርቲ ውስጥ ላሉ ችግሮች እስከ ቅጣት ድረስ በመሄድ ለማስተካከል የተሞከረውን ነገር ሳላደንቅ አላልፍም።
በሁለተኛ ደረጃ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችንም አከብራለሁ አደንቃለሁ ብዙ ትምህርቶችን እንድማር አድርገውኛል አሁን ለደረስኩበት ብስለት እንድደርስ የእነዚህ ፓርቲዎች መፈጠር ጥሩ አጋጣሚና እድል ፈጥሮልኛል። ሀቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጭቆናውን አመት ለመቀነስና በጭንቅ ላይ ያለችን ሀገር ለመታደግ መፍጠን አለባቸው። አሁን የዕንቅልፍ ጊዜ አይደለም፡፡የምንፈጥንበትን የሩጫ ሂደትና ቀስ የምንልበትን እንደገና ደግሞ አሯሯጭ የምንሆንበትን መለየት መቻል አለብን።
የኢትዮጲያ ህዝብንም የምለው ነገር ይኖራል፡፡ የኢትዮጲያ ህዝብ ሆይ! ተስፋ አትቁረጥ፤ ተስፋ የሚቆርጥ የሞተ ብቻ ነው። በቁም ያለ ሰው የሚፈልገውን ነገር እጁ ውስጥ እስካላስገባ ድረስ ተስፋ አይቆርጥም። እስከ መጨረሻ ህልፈተ ህይወቱ ድረስ ማድረግ ያለበትን በሙላ ያደርጋል። ሰው እንሁን፤ ስብእናችንን እንጠብቅ፤ እርስ በእርሳችን እንከባበር፤ እንተማመን፤ መተማመን አንድነትን ያመጣል፤ አንድ ከሆንን ደግሞ የማንሰራው ነገር አይኖርም። ከዓለም በታች ጭራ የሆነችውን ሀገር ከፍ እናደርጋታለን፡፡ለዚህ ደግሞ እግዚአብሔር
ይርዳን ማለት እፈልጋለሁ። አመሰግናለሁ።

በአዳር ሰልፉ ኢህአዴግ “ተሸብሯል”

December 5,2014
በስውርና በግልጽ አፈናው ተጧጡፏል
police 11
* የከምባታ ጠንባሮ ዞን ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለጸ
* የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በፖሊስ ተከብቦ አደረ
የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በፖሊስ ተከብቦ ማደሩንና አባላት ከውጭ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለአዳር ሰልፉ ቅስቀሳ ዝግጅት ቢሮ ያደሩ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አመራሮችና አባላቱ እራት በልተው ወደ ፓርቲው ጽ/ቤት ሲመለሱ ቢሮው በፖሊስ ተከብቦ እንዳገኙትና ወደ ውስጥ እንዳይገቡ እንደተከለከሉ በቦታው የነበሩት የፓርቲው አመራሮችና አባላት ገልጸዋል፡፡
police 14አመራሮችና አባላቱ ፖሊስ ከ200 ሜትር ርቀት ውጭ ወደ ፖለቲካ ፓርቲ ጽ/ቤት መጠጋት እንደማይችል ቢከራከሩም ፖሊሶቹ “መመሪያ ተሰጥቶናል፤ አንሄድም!” ማለታቸው ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ከፖሊስ ጋር ሲከራከሩ የአካባቢው ህዝብ በመውጣቱ ፖሊሶቹ ፓርቲው ጽ/ቤት እንደራቁ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ከውጭ ወደ ቢሮ ከሚመጡበት ወቅት የፓርቲው ቢሮ አካባቢ ምንነቱ ያልታወቀ ወረቀት ተበትኖ እንዳገኙና እነሱ ሲደርሱ ፖሊሶቹ እንዳነሱት የፓርቲው የምክር ቤት አባል ወጣት እየሩስ ተስፋው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡
*********************
በነገረ ኢትዮጵያ የፌስቡክ ገጽ ላይ የታተመው መረጃ እንደሚያመለክተው ፖሊስና ደህንነቶች ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት የሚገቡና የሚወጡ አባላትንና አመራሮችን እያዋከቡ ይገኛሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንና አባላትን “እንፈልጋችኋለን!” በሚል እየያዙ ሲሆን በተለይ ደህንነቶቹ መታወቂያ አሳዩ ሲባሉ ፈቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡
ሰማያዊ ቢሮ ጽ/ቤት የሚገኙ ደህንነቶች የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን እያፈኑ እየወሰዱ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ የሆነውን ፍቅረ ማሪያም አስማማውን አፍነው ወስደውታል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የገዥው ፓርቲ ደህንነቶች ተጨማሪ ሰዎችን አፍነዋል፡፡ የነገረ ኢትዮጵያ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ እና የሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ እንዲሁም የብሄራዊ ምክር ቤት ፀኃፊ ወጣት ሳሙኤል አበበ በደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸውን ነገረ ኢትዮጵያ በዚሁ የፌስቡክ ገጹ ዘግቧል፡፡volunteers of 9 parties
ከጥቂት ሰዓታት በፊት የተሰራጨው መረጃ እንደሚያመለክተው የአዳር ሰልፉን የጠሩት የ9ኙ ፓርቲዎች ቢሮ በፌደራል ፖሊስ ተከብቧል፡፡ እንዲሁም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አባል የሆነው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቸርቺል የሚገኘው ጽ/ቤት በፌደራል ፖሊስ ተከቧል፡፡ ከሰማያዊ ጽ/ቤት መውጣትም ሆነ መግባት የማይቻል ሲሆን በርካታ አመራርና አባላት ታፍነው ታስረዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የትብብሩ አመራሮች ስልክ እንዳይሰራ እየተደረገ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር የኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ስልክ እንዳይሰራ ተደርጓል፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በተሰራጨ መረጃ መሠረት የሰማያዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ስራ አስፈጻሚ ፀኃፊ የሆነው ወጣት አወቀ ተዘራ ወደ ቤቱ በሚገባበት ወቅት በስርዓቱ የደህንነት ኃይሎች ተይዞ ታስሯል፡፡ ፍቅረማሪያም አስማማው፣ አወቀ ተዘራና ተስፋሁን አለምነህን ጨምሮ በደህንነቶች የታፈኑት ወጣቶች የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
በተያያዘ ዜና የከምባታ ጠንባሮ ዞን ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ በገዥው ፓርቲ አድሏዊ አሰራር ምክንያት ልማትና መልካም አስተዳደር ባለመኖሩ የከንባታ ጠንባሮ ነዋሪዎች ዛሬ ህዳር 26/2007 ዓ.ም ዱራሜ ከተማ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የከምባታ ህዝብ ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዲሎ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ህዝብ ያለ ማንም ቀስቃሽና አስተባባሪ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣቱን የገለጹት አቶ ኤርጫፎ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት አከብራለሁ በሚል ለፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ ከማድረጉ ውጭ በተግባር ግን በህዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እየፈጸመ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የከንባታና ጠንባሮ ህዝብ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ተቃዋሚዎችን በተለይም የከምባታ ህዝብ ኮንግረንስን ትደግፋላችሁ በሚል በደል እንደሚደርስበት የገለጹት አቶ ኤርጫፎ “ህዝቡ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት በደል እየደረሰበት ነው፡፡ ምርጫ ሲደርስ መንገድ፣ ዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ይሰራልሃል ይባላል፡፡ ምርጫው ሲያልፍ ለማታለያነት ይሰራሉ የተባሉ ነገሮች ተግባራዊ አይሆኑም፡፡ እስካሁን ከ1993 ዓ.ም አንስቶ ይሰራል የተባለ መንገድ አልተሰራም፡፡ በምርጫ ወቅት አርሶ አደሮችን እያፈናቀሉ ኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ እንሰራለን ይላሉ፡፡ ከምርጫ በኋላ ግን ይህ መሬት የሚሰጠው ለሹመኞች ነው፡፡ ሁለቱም ጠቅላይ ሚኒስትሮች የምርጫ ሰሞን በየቦታው የመሰረት ድንጋይ ተክለዋል፡፡ ከምርጫ በኋላ ግን ለሹመኞች ይሰጣል፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ የወጣውም ከዚህ አንጻር ነው” ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የከንባታ ጠንባሮ ህዝብ ባለፉት ምርጫዎች ተቃዋሚዎችን በመምረጥ ከገዥው ፓርቲ ጋር ያለውን ልዩነት በግልጽ እንዳሳየ የገለጹት አቶ ኤርጫፎ “ወጣቶች ልማትና የትምህርት እድል ስለማያገኙ ወደ ደቡብ አፍሪካና አረብ አገራት እየተሰደዱ መንገድ ላይ እየሞቱ ነው፡፡ በቀን 11 አስከሬን የመጣበት ጊዜ አለ፡፡ በስርዓቱ አድሏዊ አሰራር ምክንያት ከንባታ ጠንባሮ ወጣቱ ከቀየው እየተፈናቀለ የሚሰደድበት ትልቁ ዞን ነው ማለት ይቻላል” በማለት አስረድተዋል፡፡
በዛሬው እለት አርሶ አደሩ፣ ተማሪውና ነጋዴው የዞኑ ጽፈት ቤት ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ከማድረጉም ባሻገር በቀጣይነት በየወረዳዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚየደርግ ገልጾአል ሲሉ ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ (ለመረጃ ጥንቅሩና ለፎቶዎቹ፡ ነገረ ኢትዮጵያ)
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, December 4, 2014

ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ አመክሮ ተከለከለች

December 4,2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ “ሽብርተኛ” ተብላ በእስር ላይ የምትገኝ ሲሆን እንደማንኛውም እስረኛ ልታገኝ የሚገባውን አመክሮ ሳታገኝ ቀርታለች:: በመሰረቱ አመክሮ የሚሰጠው አንድ እስረኛ በ እስር ቤት ቆይታው ወቅት የሚያሳየው መልካም ባህሪ ተገምግሞ ለአንድ እስረኛ ከተፈረደበት አመት ተቀንሶ እንዲወጣ ይደረጋል:: ከቤተሰብ ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው ከሆነ ለርዕዮት አለሙ ሊሰጣት የነበረው የአመክሮ ቅፅ “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚል ነው::
ከዚህ በፊትም “አጥፍቻለሁ ይቅርታ ይደረግልኝ” ተብሎ በፕሬዘዳንቱ አማካኝነት የሚደረገውን ሂደት ሳትቀበለው ቀርታ የይቅርታ ደብዳቤ አለማገባቷ ይታወሳል:: አሁን በቅርቡ ማድረግ የሚቻለውን “አመክሮ” ተቀብላ ቢሆን ኖሮ አሁን ከ እስር የምትወጣበት ወቅት እንደነበር ከቤተሰብ አካባቢ ያገኘነው ምንጭ አረጋግጧል::ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን በዚህ ጉዳይ ያነጋገራት ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣ ሰው ነበር:: በውይይታቸው ወቅት “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚለውን አባባል ለመቀበል አልቻለችም:: ምክንያቱም ሃሳቧን በጽሁፍ ስለገለጸች ነው “አሸባሪ” ተብላ የታሰረችው:: ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣውም ሰው “እንግዲያው አንቺ ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” ብለሽ የማትፈርሚ ከሆነ እኛም አመክሮ አንሰጥሽም ብሏታል::

የሃና ላላንጎ ጉዳይ በዝግ ችሎት ታየ

December 4,2014
ቤተሰቦቿ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቀሱ
Hana-lalango

* “አሸባሪዎችን” ለይቶ የመያዝ ልዩ ችሎታና ብቃት ያለው ፖሊስ ያልያዘው ተጠርጣሪ አለ
ሃና ላላንጎ የተባለችውን ተማሪ በሚኒባስ ታክሲ አፍነው በመውሰድ፣ በቡድን በመድፈርና ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙትን አምስት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ጉዳይ በዝግ ችሎት መታየት ጀመረ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ቀደም ባለው ቀጠሮ እንደሚሠራቸው ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት፣ ለችሎቱ ያስረዳበትና ተጠርጣሪዎቹን ያቀረበበት ሰዓት፣ ከሌሎች ቀናት የተለየ ነበር፡፡
ሟች ሃና ላላንጎ በቡድን ተደፍራ ሕይወቷ ማለፉ በመገናኛ ብዙኃን ከተሰራጨበት ጊዜ አንስቶ እያነጋገረ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት የሚገኘው ታዳሚ ቁጥር ጨምሯል፡፡ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደተለመደው ፖሊስ ዘግየት ብሎ ከ4፡30 ሰዓት በኋላ እንደሚመጣ በማሰብ፣ ሕዝቡ ወደ ፍርድ ቤት መድረስ የጀመረው በአብዛኛው ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ጀምሮ ነበር፡፡
የጠዋቱ ጊዜ ወደ እኩለ ቀን እየተቃረበ በመሄዱ፣ ሕዝቡ እርስ በራሱ “አራዳ አቅርበዋቸዋል አሉ፤ አይ አይደለም ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ መሥርተዋልና ፖሊስ እንጂ ተጠርጣሪዎቹ አይቀርቡም፤” የሚሉና ሌሎች መላምቶችን በመነጋገር ላይ እያለ፣ ፖሊስ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ላይ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ቀርቦ፣ ማንም ወደ ችሎት ሳይገባ በዝግ ችሎት፣ የሠራውን የምርመራ ሒደት ለፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ፣ ለሚቀረው ተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናትን ጠይቆ እንደተፈቀደለት ተሰማ፡፡ ለታኅሣሥ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. መቀጠሩም ታወቀ፡፡
የተነገረውን ለማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃ ለመስማት ቀጠሮውን ወደሰጡት ዳኛ የሟች ዘመዶችና የመገናኛ ብዙኃን በመሄድ ሲጠይቁ፣ ጠዋት በሥራ ሰዓት ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ በመቅረብ፣ ችሎቱ በዝግ እንዲታይለት ባመለከተው መሠረት ፍርድ ቤቱም ስላመነበት በዝግ ችሎት መታየቱ ተረጋገጠ፡፡
በሕገ መንግሥቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች አሠራር በዝግ መታየት ያለባቸው የወንጀል ድርጊቶች መኖራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ተማሪ ሃና ላላንጎን ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ጉዳይ፣ ለሁለት ጊዜያት በግልጽ ችሎት ከታየ በኋላ፣ በየትኛው የሕግ መሠረት ሦስተኛው ቀጠሮ በዝግ ሊታይ እንደቻለ ማብራሪያ እንዲሰጡ ዳኛው ተጠይቀው ነበር፡፡
የሃና ጉዳይ በዝግ ችሎት እንዲታይ የተወሰነው፣ ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና ድረ ገጾች፣ የሆነውንና ያልሆነውን ዘገባ በማሰራጨት ለምርመራው እንቅፋት እየፈጠሩበት መሆኑን አስረድቶ፣ ምርመራውን እስከሚያጠናቅቅ ድረስ በዝግ ችሎት እንዲታይለት መጠየቁ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ በዝግ ችሎት እንዲታይ መፈቀዱን አስረድተዋል፡፡
hana 2ፖሊስ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹን በችሎት አቅርቦ ቀደም ባለው ችሎት ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት ምን ያህሉን እንደሠራና ምን ያህሉ እንደቀረው ማወቅ ባይቻልም፣ ቀደም ባለው ቀጠሮ ተጨማሪ 14 ቀናትን ጠይቆ፣ ፍርድ ቤቱ ‹‹10 ቀናት ይበቃሃል›› በማለት ከጠየቀው ቀናት ላይ አራት ቀናትን የቀነሰ ከመሆኑ አንፃር፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. የጠየቀውን 14 ቀናት ሙሉውን መፍቀዱ፣ ሌላ ተጨማሪ ተጠርጣሪ የመያዝና በርካታ ቀሪ ምርመራ ሳይኖረው እንዳልቀረ ጥርጣሬ አሳድሯል፡፡
የሟች ተማሪ ሃና ወላጅ አባት አቶ ላላንጎ አይሶ ኅዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በየሳምንቱ እሑድ ምሽት ላይ በኢቢኤስ በሚቀርበው “ሰይፉ ፋንታሁን ሾው” ላይ ቀርበው ፖሊስ አንድ ተጠርጣሪን መያዝ እንደሚቀረው በመናገራቸው፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉዳዩ በዝግ መታየቱንና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን ተከትሎ ጥርጣሬውን አጠናክሮታል፡፡
አቶ ላላንጎ ሟች ልጃቸው መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ታፍና መወሰዷንና ለ20 ቀናት አስታመዋት፣ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ልትተርፍ አለመቻሏን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ላላንጎ ገለጻ፣ ልጃቸው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተጥላ ከተገኘች በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ አለርት ሆስፒታል ወስደዋታል፡፡ የአለርት ሆስፒታል ዶክተሮች ተመልክተዋት በስለት በመወጋቷና በደረሰባት የመደፈር አደጋ ሕይወቷን ልታጣ እንደምትችል በመናገር፣ ሕይወቷ ከማለፉ በፊት ቃሏን ለፖሊስ እንድትሰጥ በመናገራቸው ቃሏን እንድትሰጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የሃና ላላንጎ ወላጅ አባት ስለልጃቸው ስቃይ እንዳብራሩት፣ አለርት ሆስፒታል ከአቅሙ በላይ መሆኑን ገልጾ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ሲወስዷት፣ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ደግሞ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሪፈር እንዲወስዷት እንደነገራቸው አስረድተዋል፡፡ ያለምንም ሕክምና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ መልሶ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሲልካቸው ተስፋ የቆረጡት አቶ ላላንጎ፣ ልጃቸውን በቀጥታ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል መውሰዳቸውን ትተው፣ ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ አንድ ቀን አድራና ቤተሰቦቿን ተሰናብታ፣ በማግስቱ ወደ ጋንዲ ሆስፒታል እንደወሰዷት ገልጸዋል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ጋንዲ ሆስፒታል በሪፈር የሄደችው ሟች ሃና፣ ይኸ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲደረግ ደም እየፈሰሳትና ቁስሏም ወደ ሌላ ሕመም እየተቀየረ መሆኑን የገለጹት አባቷ፣ ሙሉቀን በጋንዲ ሆስፒታል ከቆየች በኋላ፣ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶላት መተኛት መቻሏን ተናግረዋል፡፡
የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሐኪሞች የሃናን ጉዳትና ሕመም ሲመለከቱ፣ በከፍተኛ ሐዘንና እንባ ታጅበው ለማትረፍ የተረባረቡ ቢሆንም፣ ችግሩ ወደ ሌላ ነገር ተቀይሮ የነበረ በመሆኑ ሕይወቷ ሊተርፍ አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡
አቶ ላላንጎ የልጃቸውን ስቃይ በሐዘን ሲገልጹ፣ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቅሰዋል፡፡ “ሁሉንም ሐኪምና ሁሉንም ፖሊስ በጅምላ መውቀስ አልፈልግም፤” ብለው፣ መልካምና ሥራቸውን የሚወዱ፣ ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ሐኪሞችና ፖሊሶች ስላሉ እነሱን ማመስገን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ ልጃቸው ደም እየፈሰሳት በሄዱበት ሆስፒታሎች “አልጋ የለም፣ ውጭ አስመርምሯት” ማለትና ችላ ማለት ተገቢና የገቡለትም ቃል ኪዳን ባለመሆኑ፣ ተገቢ አለመሆኑን በመናገር፣ መንግሥትም ሊከታተለው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ፖሊሶችም ቢሆኑ፣ ጉዳዩን በትጋት ተከታትለውና ራሳቸው የሚሆነውን እንደማድረግ “እዚያ ውሰድ እኛ ጋ አይደለም” በማለት እንዲንገላቱ ማድረጋቸው ተገቢ ባለመሆኑ መንግሥትም ሊያየው የሚገባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ ሪፖርተር)

Wednesday, December 3, 2014

TPLF shockingly admits failures in Ethiopia

December 3,2014
By Admasu Belay
TPLFSince it came to power over 20 years ago, the TPLF regime has always declared its achievements in Ethiopia’s political and economic sectors. Everybody knows the state media ETV and its daily nonstop propaganda of how much better Ethiopia has become over the years. Not only that, TPLF has been telling the international community about how it changed and transformed Ethiopia. So much so that it had even deceived some Bush and Obama adminstration officials to believe its lies.
But after over 20 years, the London-based Financial Times (FT) reported today that TPLF has finally admitted its massive failures in Ethiopia.
Shockingly, the TPLF admitted its disasterous policy of landlocking Ethiopia and its economic impact as well as the risk of another famine in Ethiopia.

Lessons for those who harp on TPLF’s non-existing “Economic Growth” and other “achievements”

“The document, seen by the Financial Times, is a sobering reminder of the risk of investing in one of Africa’s less developed nations. With gross domestic product per capita at less than $550 per year, Ethiopia is the poorest country yet to issue global bonds.
In the 108-page prospectus, issued ahead of its expected $1bn bond, Ethiopia tells investors they need to consider the potential resumption of the Eritrea-Ethiopia war, which ended in 2000, although it “does not anticipate future conflict”.
There is also the risk of famine, the “high level of poverty” and strained public finances, as well as the possible, if unlikely, blocking of the country’s only access to the sea through neighbouring Djibouti should relations between the two countries sour.
Addis Ababa, Ethiopia’s capital, also warns that it is ranked close to the bottom of the UN Human Development Index – 173rd out of 187 nations – and cautions about the possibility of political turmoil. “The next general election is due to take place in May 2015 and while the government expects these elections to be peaceful, there is a risk that political tension and unrest?.?.?.?may occur.” “
For the last two decades, this “F word,” was banned by Meles and all his TPLF disciples. In the past, If any foreign officials dared to use the words “famine” and “Ethiopia” in the same sentence, the wrath of TPLF’s “ministry of foreign affairs (mfa)” would attack and humiliate them with endless MFA press releases. Meles himself told Ethiopians to forget about famine and promised that even our poorer people “will eat three times a day very soon.” That promise was made in 1994! Ironically today, the TPLF government sent a document to international investors, admitting another ” risk of famine, the high level of poverty” in Ethiopia, according to the Financial Times.
Not only has Ethiopia lost most of its hard currency reserves but the “steadily depreciating exchange rate may adversely affect Ethiopia’s economy?,” according to the TPLF document
That is not all. TPLF also admitted the chance of “resumption” of the war with Eritrea and more unrest from “political turmoil” as well as bad relations with Djibouti causing the “blocking of the country’s only access to the sea.”
It is about time TPLF accepted its failures!

Regarding the 5th TPLF policy, everybody knows TPLF has failed. Soon it will admit this failure too.
In 1995, TPLF claimed its “ethnic federalism” system will empower tribes without dividing Ethiopians. But today, Ethiopia is the most ethnically divided country in the world. Ethnic hatred, propaganda and tensions today are the highest ever in history. Just like the 1990s Rwanda, tribalism has destroyed Ethiopian nationalism and humanity. Sooner or later, TPLF will be forced to admit its last and final failure.
Regardless, Today will go down in history as the day TPLF admitted that it has achieved almost nothing (other that a few tall buildings) since it removed the DERG regime in 1991. It has failed Ethiopia in every way possible. The only reason TPLF is still in power is because Ethiopians are peaceful people, unlike the warmongering and hate-filled TPLF.
For all those EPRDF ruling party supporters and TPLF footsoldiers worldwide, this must be the most embarasssing day. One single TPLF document has virtually dismissed over 20 years of ETV propaganda

አሶሳ በከፍተኛ የመከላከያ ጥበቃ ስር መውደቁዋ ተሰማ፡፡

December 3,3014

9ነኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል የሚያስተናግደው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዝግጅት ማጠናቀቁን ቢገልጽም፣ በአካባቢው መንግስትን የሚቃወሙ ኃይሎች በተለያየ ጊዜያት በደፈጣ ውጊያ ጥቃት ማድረሳቸው ያሰጋው መንግስት በአካባቢው ከፍተና ወታደራዊ ሃይል አሰማርቷል።

ህዳር 29 ከሚካሄደውን በዓል ጋር ተያይዞ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ብዙዎች የሚሰጉ ሲሆን፣ ጥቂት የማይባሉ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች በተለያዪ ሰበቦች የጉዞ እቅዳቸውን የሰረዙ መሆኑ ታውቆአል፡፡

በቤንሻንጉል ክልል የተመሠረተው የአባይ ግድብ ጨምሮ በዋና ከተማዋ አሶሳ ከወትሮው በተለየ መልክ በኮንቮይ የታገዘ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን ለጸጥታ ሲባል እንደልብ መዘዋወር መከልከሉ ተሰምቷል፡፡

የፌዴሬሽን ምክርቤት የዘንድሮው በዓል የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሕገመንግስቱን ያጸደቁበትን 20ኛ ዓመት ጭምር የሚያከብሩበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን በመጥቀስ በተደጋጋሚ መግለጫ የሰጠ ሲሆን ይህንን በዓል ለማክበርም ከ2ሺ500 በላይ እንግዶች ወደስፍራው ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቅ እንደነበር ታውቆአል፡፡


ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተውጣጣ ቡድን ነገ ሐሙስ ወደስፍራው የሚያቀና ሲሆን ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (የቀድሞ ኢቲቪ) ብቻ ከ100 በላይ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች አሶሳ መግባታቸው ታውቆአል፡፡


በስተሰሜን ምዕራብ ሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሁኑ ሰዓት የህዝብ ቁጥሩ 964 ሺ 647 ደርሷል፡፡ በክልሉ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ማለትም በርታ ፤ ጉሙዝ ፤ ሽናሻ ፤ ማኦ፣ ኮሞ ኦሮሞና አማራ የሚገኙ ሲሆን እነዚህ ብሔር ብሔረሰቦች ከዚህ ሥርዓት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ካለመሆናቸውም በላይ መሬታቸው ለውጪ ባለሃብቶች ጭምር ያለፈቃዳቸው በገፍ የሚሰጥ በመሆኑ በጅምላ የመፈናቀል አደጋና በሰፈራ ስም ከቀዩአቸው እንዲሰደዱ በመደረጋቸው በሕዝቡ ውስጥ ከፍተኛ ቅሬታ መኖሩን ዘጋቢያችን ገልጻለች።


ምንጭ ኢሳት ዜና

በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

December 3,2014
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ዛሬ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

በጠቦቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡

ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡
Photo: በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ዛሬ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

በጠቦቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡

Tuesday, December 2, 2014

The Zone9 Defense: Limits of International Law

December 2, 2014
by Ivan Sigal (World Policy Blog)
The international human rights system is broken – or perhaps it never worked at all.An Ethiopian court granted police 10 more days to investigate six bloggers and journalists
In case after case, citizens’ human rights are violated under the national laws of their respective countries, despite the existence of international human rights commitments in the United Nations’ Universal Declaration, and by The Organization for Security and Cooperation in Europe, the Organization of American States, the African Commission, and others. The International Criminal Court has little say concerning any but the most egregious of international human rights violations, and member states have wide latitude to dispense justice as they see fit.
For those who live in countries that fail to provide or enforce their own laws protecting freedom of expression, international principles have rarely provided actual recourse. This is the case, today, with the independent Ethiopian blogger collective known as Zone9.
In April of this year, the government of Ethiopia arrested six members of Zone9 and affiliated journalists in Addis Ababa. They were held for months without a formal charge and were denied the ability to communicate. Testimony from Befeqadu Hailu, one of the accused bloggers who was smuggled out of prison in August, as well as statements in court, allege mistreatment and frequent beatings. Informally, the nine were held on accusations of “working with foreign organizations that claim to be human rights activists and…receiving finance to incite public violence through social media.”
In July, the Zone9 prisoners were charged under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation of 2009 for receiving support from political opposition organizations, defined formally by the government as terrorists, and receiving training from international activists in email encryption and data security from the Tactical Technology Collective, a group that helps journalists and activists protect themselves from digital surveillance.
The Zone9 bloggers joined other media outlets targeted under similar laws, including Eskinder Nega, who had reported on recent Arab uprisings and the possibility of similar uprisings in Ethiopia. He was arrested and charged with the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt” of terrorism and sentenced to 18 years in prison.
International appeals from human rights advocacy organizations have had little effect on the case. In May, UN High Commissioner for Human Rights Navi Pillay issued a statementexplaining, “The fight against terrorism cannot serve as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, human rights activists and members of civil society organizations. And working with foreign human rights organizations cannot be considered a crime.” Additionally, seven international human rights and press freedom organizations pressed the African Commission and the United-Nations in an urgent appeal to intervene in the case against Zone9. The appeal focused on the lack of clear charges and failure to allow the defendants adequate legal representation.
Nani Jansen, a lawyer for the Media Legal Defence Initiative and the lead signatory in the appeal, writes in an email that both the African Commission and the UN “operate under the cover of confidentiality in the early stages of these matters: when they follow up with a Government, this is done without informing the outside world. Only months and months (often over a year) later, these exchanges with a Government get published in the mechanism’s report to its supervisory body.” Thus any intervention joins the rest of those in the cone of silence that is Zone9—hidden from public scrutiny or participation.
Even if these bodies do follow up with the Ethiopian government, their recourse is limited. In an article on the urgent appeal, Jansen notes that the African Commission can condemn the arrests in a resolution, that both organizations’ rapporteurs can request official visits to Ethiopia to investigate, and that Ethiopia, as a member of the UN Human Rights Council, would be obligated to honor such a request. But even should such requests be made, and investigations conducted, there is little chance of enforcement of hypothetical findings on the Ethiopian government.
Since the appeal, the Ethiopian government has proceeded with charges against the accused. The latest details on the trial can be found on the website trialtrackerblog, run by people close to the defendants.
Public attempts to highlight the Ethiopian governments’ transgressions against human rights such as the #Freezone9bloggers social media campaign have an indirect effect. They aim to shame the Ethiopian government to ensure better treatment for the prisoners. They also seek to pressure international organizations and Ethiopia’s allies such as the United States, for whom Ethiopia is a critical military and security partner. The hope is that those organizations will in turn employ political pressure on Ethiopia to free the Zone9 defendants.
The implementation of international commitments seems to rest primarily upon a negotiated process of politics, not a functioning and enforceable system of law. Considering the ease with which national law in Ethiopia is employed or ignored for political ends, it is a grim irony that only political pressure can hope to resolve the case in their favor.
*****
To read more about the Zone9 bloggers, read our Fall 2014 article Joining Zone Nine.
Ivan Sigal is the executive director of Global Voices, a non-profit online global citizen media initiative. He is also a fellow at the Berkman Center for Internet & Society at Harvard University, where he studies digital storytelling and online communities. 

ለኢትዮጵያ መምህራን የቀረበ ጥሪ

December 2,2014
ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር

አንዲት አገር ካለባት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ወጥታ በስልጣኔ ጎዳና እንድትጓዝ፣ ከሌሎች አገራት ጋር ተወዳድራ እንድታሸንፍ ትምህርት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ ያለ መምህር ትምህርት ለውድድርና ለእድገት የሚያስችል አይሆንም፡፡ የዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ አስቀድሞ ሀይማኖት ለሚያስተምሩት መምህራን ከፍተኛ ክብር ይሰጥ እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ የዘመናዊ ትምህርት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶም ለመምህራን ከፍተኛ ክብር ይሰጥ እንደነበር በቂ ማስረጃዎች አሉ፡፡ በዚህም ምክንያት አገራችን በርካታ ምሁራንን ማፍራት ችላለች፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ውስጥ በተደረጉት የለውጥ እንቅስቃሴዎች መምህራንና የቀረጹዋቸው ተማሪዎች ቀዳሚውን ሚና ሲወጡ ታይተዋል፡፡

በአንጻሩ በዚህ ትምህርት ቁልፍ መሳሪያ በመሆነበት የሉላዊነት ዘመን አገራችን በትምህርት ዘርፍ ከፍተኛ ውድቀት ደርሶባታል፡፡ ይህም የሆነው ለመምህራን የሚገባቸውን ትኩረትና ክብር ባለማግኘታቸው ነው፡፡ ባለፉት 24 አመታት ከመምህራን ይልቅ ካድሬዎች የህጻናትን አዕምሮ በፕሮፖጋንዳ እንዲበርዙ ሆን ተብሎ ተሰርቶበታል፡፡ መምህራን በነጻነት እንዳያስተምሩ በካድሬዎች ጣልቃ ገብነት ተማርረዋል፡፡ የመምህራን ማህበራት በገዥው ፓርቲ እጅ በመውደቃቸው መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸው ሊከበር አልቻለም፡፡ በየ መድረኩ በሚያነሱዋቸው ጥያቄዎች ከስራቸው ይፈናቀላሉ፡፡ ኑሯቸው የምትሸንፈውን አነስተኛ ደሞዛቸውን ይቀጣሉ፡፡ ይታሰራሉ፡፡ የገዥው ፓርቲ አባል ባለመሆናቸው ሁሌም በጥርጣሬ አይን ከመታየታቸው ባለፈ የተለያዩ እርምጃዎች ይወሰድባቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ቀጣዩን ትውልድ ለመቅረጽ ከመጣርና በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰው በደል ላይ ቀዳሚነቱን ወስዶ የትግሉ አካል እንዳይሆን ስርዓቱ ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ይገኛል፡፡ ይህም ሆኖ የራሱንና የሌሎቹን ድምጽ በማሰማት የቻለውን ያህል እያደረገ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ በየ ዕለቱ ከሚታሰሩት፣ ከስራቸው ከሚባረሩትና ሌሎች የስርዓቱ አፈናዎች ከሚደርስባቸው ባሻገር አድማጭ ሲያጣ ራሱን መስዋዕት ያደረገው መምህር የኔሰው ገብሬን መጥቀስ በቂ ነው፡፡ ስርዓቱ በመምህራን ላይ ከሚያደርገው ከፍተኛ አፈና አንጻር ያልተነገረላቸው በርካታ መስዋዕቶች እንዳሉም መገመት ይቻላል፡፡

በአሁኑ ወቅት በመምህራን ላይ የተጫነው ጭቆና የአጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ያለው ጭቆና አንድ አካል ነው፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ነጻ ካልወጡ መምህራን ብቻቸውን ነጻ መሆን አይቻላቸውም፡፡ ነገር ግን ትግሉን በቀዳሚነት የመምራት የሙያና የሞራል ግዴታ እንዲሁም አጋጣሚ እንዳላቸው ግልጽ ነው፡፡ በመምህራን ላይ የተጫነውን ጭቆና ከድሮው የተለየ የሚያደርገው መምህራን ህዝብ ላይ እየደረሰ ለሚገኘው መከራ ይቅርና ለራሳቸውም እንዳይጮሁ፣ በራሳቸው የእለት ተእለት ችግሮችና ፍርሃት ተጠምደው እጥፍ ድርብ ጫና የሚፈጸምባቸው መሆኑ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት መምህራን የሚገባቸውን ሚና እንዳይወጡ ተደርገዋል፡፡

መምህራን ያልቀረጹት ትውልድ ለራሱም ሆነ ለአገሩ ነጻነትና ክብር ሊቆም አይችልም፡፡ ባለፉት 24 አመታት በመምህራንና ትምህርት ላይ የተፈጸመው በደልም አሁን ላለንበት ጭቆና የራሱን ሚና ተጫውቷል፡፡ በመሆኑም ለራሱም ሆነ በቀሪው ማህበረሰብ በግንባር ቀደምነት የሚታገል ትውልድ ለመፍጠር የመምህራን ሚና ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በአሁኑ ወቅት የ9ኙ ፓርቲዎች የአንድ ወር መርሃ ግብር ቀርጸው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ ምንም እንኳ አፈናው እየበረታ ቢሆንም መምህራን ቀዳሚ ሚና ሊወጡ እንደሚችሉ እናምናለን፡፡ በመሆኑም ራሳቸውን ነጻ አውጥተው ለህዝብ መብትና ለአገር ክብር ለመቆም ትግሉን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ መምህራን የአንድ አገር ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን በደል ለማጋለጥና ህዝቡንም ለማንቃት ካላቸው ተደራሽነት እንዲሁም የሙያ ግዴታ ግንባር ቀደም ሚና በመጫወት ታሪካዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ በተለይ ህዳር 27/28 በተጠራው የአዳር ሰልፍ በመሳተፍና በሙያም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች የምታገኙዋቸውን ኢትዮጵያውያን በመቀስቀስ ጥሪውን እንዲቀላቀለሉ በማድረግ ግንባር ቀደሙን ሚና እንድትወጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ ይህ ቀን ኢትጵያውያን ከፍርሃት ወጥተን ድምጻችን በጋራ የምናሰማበት እንዲሆን ቀዳሚ ሚና እንድምትወጡም እምነታችን ነው፡፡

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ ዕለታዊ መግለጫ

December 2,2014
ዝግጅታችን ተጠናክሮ ቀጥሏል! እርስዎም ይዘጋጁ!


‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል የአንድ ወር መርሃ ግብር ከጀመርንበት ጊዜ አንስቶ ስርዓቱ መርሃግብሮቻችን በማጨናገፍ ለነጻነት የምናደርገውን የትግል ጉዞ ለማደናቀፍ ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል፡፡ ሆኖም የነጻነት ትግሉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍል መሆኑን የተረዳው ትብብሩ ለገዥው ፓርቲ አፈና ሳይንበረከክ ስራውን ቀጥሏል፡፡ በተለይ ከመርሃ ግብሮቻችን መካከል ስርዓቱን ያስፈራውን የ24 ሰዓት የአደር ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅታችን አጠናክረን ቀጥለናል፡፡ ለዚህ የአዳር ሰልፍ የትብብሩ አባል ፓርቲዎች ሰው በሰው በመቀስቀስ፣ ወረቀት በመበተን እንዲሁም በየ ፓርቲዎቻችን ስም የታተሙ ቲሸርቶችን በመልበስ ህዝቡን እያነቃቃን እንገኛለን፡፡ ሰልፉ እስከሚደረግበት ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም ድረስም ዝግጅታችን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡

ይህን መርሃ ግብር ስንነድፍ ለነጻነት የሚከፈለው መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንና የቀድሞ አባቶቻችን ካሳዩት ቆራጥነት ተምረን ነው፡፡ በዚህ ለቀጣይ የትግል ጉዞአችን ጭላንጭል ለምናይበት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናችን እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን፡፡ በውጭም ሆነ አገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት ለምናደርገው ጉዞ የጀመርነውን የሰው በሰው ቅስቀሳ በመደገፍ፣ በገንዘብ፣ በሞራልና በሌሎች ለመርሃ ግብሩና ለአጠቃላይ ትግሉ ይጠቅማል ባሉት መንገድ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ መርሃ ግብሩ ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በሞራልና በተለያየ መንገድ መልዕክቶቻችን ለህዝብ እንዲደርሱ ድጋፍ ያደረጋችሁልን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ልባዊ ምስጋናችን ማቅረብ እንፈልጋለን፡፡ አሁንም ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ በመቀጠል ታሪካዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡

በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በኩል ለሰላማዊ ሰልፉ የሚያስፈልገው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ህዝቡ በዝግጅቱ ከሚያደርገው ድጋፍ ባሻገር በመስቀል አደባባይ በሚኖረን ቆይታ የሚያስልጉት ቁሳቁሶች በተለይም ደረቅ ምግብና ውሃ ከአሁኑ እንዲያዘጋጅ ማስታወስ እንፈልጋለን፡፡ ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚደረገው የ24 (አዳር) ሰልፍ ኢትዮጵያውያን ላይ የተጫነውን የፍርሃት ድባብ በመስበር ለነጻነት የምናደርገው ወሳኝ ጉዞ ጅማሬ በመሆኑ በሁሉም የማህረሰብ ክፍል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ራሳቸውንና አገራቸውን ነጻ ለማውጣት የትግሉ አካል እንዲሆኑ ጥሪያችን እያቀርባለን፡፡

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

ህዳር 23/2007 ዓ.ም

አዲስ አበባ

Monday, December 1, 2014

ፍርደ ገምድሉ የወያኔ ፍርድ ቤት ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ለተከሰሱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ

December 1,2014
አሸባሪው የወያኔ አገዛዝ ትንታግ የሆኑትን ወጣት ፖለቲከኞች በሽብር ወንጀል ተካፍለዋል፣ ድርጊቱን ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ ህዝብን ለአመጽ ቀስቅሰዋል በሚል የፈጠራ ክስ አጎሮ ስቃይ እየፈጸመባቸው ሲሆን የካንጋሮው ፍርድ ቤት አራቱ ወጣት ፓለቲከኞችን እና በተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱት ሌሎች 6 ተከሳሾች ለቀረበባቸው የፈጠራ ክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ለታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች አገዛዙ በወጣት ፖለቲከኞች ላይ ያቀረበውን የፈጠራ ክስ እያወገዙ መቀጠላቸው ታውቋል። ወጣት ፖለቲከኞቹን ጨምሮ በአገዛዙ የፈጠራ ክስ ሰለባ ሆነው በእስር እየተሰቃዩ የሚገኙትን የህሊና እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አገዛዙ በአስቸኳይ እንዲፈቱ የሚጠይቅ የበይነ መረብ ዘመቻ መከፈቱም የታወቀ ሲሆን በርካታ ኢትዮጵያውያን ዘመቻውን በመደገፍ ፋሽስታዊው አገዛዝ ሁሉንም የህሊና እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈታ አበክረው እየጠየቁ እንደሚገኙ ዘጋቢያች አመልክቷል።
በሌላ ዜና የፋሽስቱ ወያኔ አገዛዝ እያደረሰባቸው ያለው ወከባ፤ አፈናና እስር ትግሉ እንደማይቆም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አስታወቀ። “ነጻነታችን በእጃችን” ነው የሚለው ትብብሩ፣ ፋሺስታዊው አገዛዝ እየወሰዳቸው ባሉት እርምጃዎች ፈጽሞ ወደኋላ እንደማይል በማሳሰብ እቅዱን በህጋዊ መንገድ ለማስቀጠል እስከ ህይወት መስዋትነት ለመክፈል ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
በመጨረሻም አገዛዙ ከአፈና ድርጊቱ እንዲገታና ለቀረበው ህጋዊ የዕውቅና ጥያቄ በአስቸኳይ መልስ እንዲሰጥ የጠየቀው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የትግሉ አላማ የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሆኑን በማመልከት በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ለቀጣዩ ትግል የሚቀርበውን ጥሪ በንቃት እንዲከታተሉና ከፓርቲዎች ጎን እንዲቆሙ፣ ትብብሩን ያልተቀላቀሉ ፓርቲዎችም እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።

ለሀገር ነጻነት የወጣቱ ተሳትፎ ቀጣይነት ይኑረው!

December 1,2014
ከ1997 ምርጫ ማግስት ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጣቶችና በሁሉም የእድሜ ክልል የሚገኙ ዜጎች ለሀገራቸው የዲሞክራሲ መብት መከበር እያደረጉት ያለው አስተዋጽኦ ላቅ እያለ መምጣቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። ይህን ተከትሎ ዛሬ ወጣቱ የወላጆቻችን ደምጽ ይከበር፣ ኢትዮጵያዊነት በዘረኝነት አይፈተንም! ነጻነት ዳቦ አይደለም! እስራትና ግድያ በኢትዮጵያ ይቁም! የወያኔ አገዛዝ በቃን! በሚሉ በበርካታ ወጣቶች ጩኸት የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮቹ ላይ የፈጠረው ድንጋጤ ወጣቱን ሽብርተኛ አስደርጎታል።
ወጣቶች ህዝብን አስተባብረው ለተቃውሞ በማሳደም የወያኔን ዘረኝነት በመቃወም ረገድ የተለያዩ ዘዴዎችን ከሌሎች የነጻነት አቢዎት እንቅስቃሴ በመማር እምቢተኝነትን በማሳየት ጅማሮ ላይ ናቸው። ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ የተጀመረው የእምቢተኝነት ዘመቻ በሚቀጥለው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ይቀጣጠል ዘንድ ወጣቱ ሃላፊነት አለበት። ሀገራችን መስቀለኛ መንገድ ላይ ነች። ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው መራራ ትግል ውስጥ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ ይኖርበታል። አባቶቻችን የውጪ ሀገራትን ወራሪዎች ወራራ ለመመከት ሁሉም ሰው የሚችለውን ሁሉ እንዲያደርግ ያደረጉት ጥሪ አሁንም ላይ ይሰራል።
ለራሳችን ክብር፣ አንድነት፣ ለሀገር ነጻነትና ህልውና መከበር ኢትዮጵያዊ እምቢተኝነት የሚጀምረው ከትንሽ ነው። ህወሃት በጠላትነት የፈረጃችሁ የዛሬ ወጣቶች የሆናችሁ ዘመን በሚፈቅድላችሁ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በመላው ሀገሪቱ ወረቀት ከመበትን አንስቶ ሌሎች ይትግል ስልቶችን ተጠቀሙ። ኢትዮጵያ ሀገራችሁ በአንድ ጠባብ ዘረኛ ቡድን መዳፍ ውስጥ ማልቀስ ከጀመረች ሰነባብታለች። ዜጎቿ የግለሰብም ሆነ የቡድን መብታቸው ተረግጦ በባርነት እየተገዙ ነው። ጉልበታቸውና ሀብታቸው እየተመዘበረ ሲሆን፤ ለነጻነት፣ ለዲምክራሲና ለፍትህ የጮኹ ሁሉ ሽብርተኛ ተብለው ወደ ማጎሪያ እየተወረወሩ ነው።
ስለዚህ ስለ ሀገራችን፣ ስለራሳችን የግልም ሆነ የቡድን ጥቅም ስንል በሀገሪቱ የትኛውም ከፍል የተጀመረውን የእምቢ አልገዛም ባይነት እንቅስቃሴ እንደግፍ፣ እንሳተፍ! በባህርዳር የተጀመረውን የወጣቶች እንቅስቃሴን አድንቀን ይህ ተነሳሽነት በሌላውም የሀገሪቱ ክፍል መቀጠል ያለበት ነው።
ይህን በማድረግ ወደ ትግሉ በመቀላቀል ካልተሳተፍን በስተቀር ትግላችን አንድ እርምጃ ወደፊት ፈቀቅ ማድረግ እንደማንችል ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ሁሉም አካላት በያለበት በየሚኖርበት፣ በሚችለው አቅሙ ሁሉ ወደትግሉ በንቃት ተሳተፍ! አብረን ታግለን ነጻነታችንን እናረጋግጥ! ለኢትዮጵያ ትንሳኤ፣ የነጻነት አዋጆች ነጋሪ፣ አብሳሪ ትውልዶች እንሆን ዘንድ ሳንታክት እንታገል ዘንድ ወቅቱ የሚጠይቀው ጥሪ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

December 1,2014
ኑ- ለነጻነታችንና ክብራችን ድምጻችንን በጋራ እናሰማ!

ከባርነትና ውርደት ለመላቀቅ ነውና በፍጹም አይቀርም፣ አይቀርም!

የ9ኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ ››በሚል መርህ የመጀመሪያ ዙር ዕቅዱን ለህዳር ወር አዘጋጅቶ ወደ እንቅስቃሴ ከገባ ሦስት ሣምንታትን አሳልፏል፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባራትና የተጓዝንበትን መንገድ ለጉዳዩ ቀዳሚ ባለቤትና ለባለ ድርሻ አካላት ስናሳውቅ የነበረ በመሆኑ ያጋጠሙንን ችግሮች በመደጋገም ማሰልቸት አንሻም፡፡

ስለሆነም የዛሬው መግለጫችን በቀጣይ ለቀሩን ተግባራት የደረስንበትን ድምዳሜና ያወጣነው ዕቅድ በሚመለከት ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በእስከዛሬው እንቅስቃሴያችን ይዘን የተነሳነው ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› የሚለው መርህ ትክክልና ወቅታዊ፣ ያነሳናቸው ጥያቄዎችም አግባብ መሆናቸውን ያረጋገጥንበትና ገዢው ፓርቲ መድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ማለት ፍጻሜዬ ነው በሚል ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜትና ሥጋት ለተቃውሞ ጎራው እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ማለት በሚያስችል ሁኔታ በሩን ለመዝጋት የተዘጋጀ መሆኑን አገር ለ23 ዓመታት በላይ ካስተዳደረ መንግስታዊ ሥርዓት የማይጠበቅ መረን የለቀቀ የውንብድና ተግባራት ያረጋገጥንበት ነው፡፡ በመሆኑም ጥያቄዎቻችንን በህገ መንግስቱና በአገሪቱ ህጎች መሠረት ለመመለስ ቀርቶ ለመስማትና ለማንበብ ፍቃደኝነቱና የኃላፊነት ስሜቱ እየተሟጠጠ በመሆኑ የአፈናና ማስፈራራት መንገድን ብቸኛ አማራጭ አድርጎታል፡፡ ይህ በመሆኑም የራሱን መንግሥታዊ መዋቅር አሰራር ሥርዓት እንኳ በአደባባይ ለመቀበል እምቢተኛ መሆኑን በአደባባይ አረጋግጧል፡፡ ባለሥልጣናቱ በግንባር ያቀረብነውን ደብዳቤ ካለመቀበል አልፈው በመንግሥታዊው ፖስታ ቤት የተላከ ደብዳቤ ያለመቀበላቸው የሚያመለክተው ይህንና የደረስንበትን የመልካም አስተዳደር አዘቅት ነው፡፡

በተቃራኒው አበረታችና መልካም ዜናም አለ፡፡ ይህም ይህን የአፈናና ማስፈራትት አካሄድ አንቀበልም ያሉ ለነጻነታቸውና ክብራቸው፣የራሳቸው ብቻ ሣይሆን የመንግሥት መዋቅሮችና ባለሥልጣናትም ነጻነት መረጋገጥ አለበት ብለው የቱንም መስዋዕትነት ለመክፈል በቁርጠኝነት የተዘጋጁ በትብብሩ የታቀፉ ፓርቲዎች፣ አመራርና አባላት መኖራቸውና በትግሉ ለመቀጠል መወሰናቸው ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ትብብሩ ለመጀመሪያ ዙር ዕቅዱ ማጠቃለያ የህዳር 27/28 የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤ አመራሩ በግንባር ቢያቀርቡም አሻፈረኝ አንቀበልም ያሉት አሰራርና ባለሥልጣናት ከፖስታ ቤት እንዲቀበሉ ተደርጓል፡፡ለዚሁ ደብዳቤ መስተዳድሩ ከህገመንግስቱና ከአዋጁ (ቁጥር 3/1983) ተቃራኒ የሆኑ ምክንያቶችን በመደርደር ለሠላማዊ ሠልፉ ዕውቅና አልሰጠሁም ሲል በዛሬው ቀን (22/03/07) መልስ አድርሶናል፡፡ በመሠረቱ መስተዳድሩ ጊዜና ቦታ እንዲቀየር አስተያየት ከማቅረብ ያለፈ ዕውቅና የመንፈግ መብት የሌለው በመሆኑ ትብብሩ የደብዳቤውን መልዕክት ያልተቀበለ መሆኑንና ሠልፉም በታቀደው ጊዜና ቦታ እንደሚደረግ ወስኖ የመልስ ደብዳቤ አስገብቷል፡፡ በመሆኑም ለተግባራዊነቱ ዝግጅቱን በሙሉ አቅም ጀምሯል፤ ለዚህም የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከአገር ውስጥና ከውጪ አጋርነታቸውን ገልጸዋል፤ አበረታተውናል፡፡ ይህም የያዝነው የትብብር የጋራ ዓላማችን ተቀባይነት፤ የኅብረትና አንድነትን ዋጋ አመላካች፣ ለማይቀረው ሠላማዊ ትግላችን ሥንቅ ነውና በታላቅ አክብሮት ተቀብለነዋል፡፡

ስለሆነም ይህ መግለጫ ትግላችን ነጻነታችንና ክብራችን የማስመለስ መንገዱም ፍጹም ሠላማዊ፣ ህጋዊና ህገ- መንግሥታዊ ስለሆነ የህዳር 27/28 ሠላማዊ ሰልፍ የማይቀርና የማይቀርበት መሆኑን ለመግለጽና ነጻነትና ክብርን ወዳድ ኢትዮጵዊያንና የፖለቲካ ኃይሎች በሙሉ ለዚህ ታሪካዊ ዕለትና ሠላማዊ ትግል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ነጻነታችንና ክብራችን ለማስመለስ ዋጋ ለመክፈል እንዘጋጅ፣ ያለመስዋዕትነት ድል የለምና!!

Sunday, November 30, 2014

ምርጫ መሳተፍ በመርዕ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ወይስ ኢህአዴግን ማጀብ? – ከግርማ ሰይፉ ማሩ

November 30,2014
ሰዎች በማንኛውም መንገድ ሸብረክ ሸብረክ የሚሉ ከሆነ መርህ አልባ መሆናቸውን ከማሳየት ውጭ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ ባለፈው ሳምነት ፍኖተ ነፃነት ላይ ወጣቱ ፀሃፊ ኢዮኤል ፍስሃ ዳምጤ ለምን እንደምንፈራ ቁልጭ አድርጎ አሳይቶን ነበር፡፡ የገዢዎቻችን በትር የበረታብን በእነርሱ ጥንካሬ ሳይሆን ከፍርሃት በመጣ ዝምታችን እንደሆነ አስምሮበታል፡፡ መፍትሔውም ከፍርሃት መላቀቅና ዝምታውን ማፍረስ ነው፡፡ በዛሬው ፅሁፌ ማንሳት የፈለኩት ደግሞ ለምን ሸብረክ ሸብረክ እንደምንል ነው፡፡
ለምንድነው ኮሽ ሲል ደንግጠን ከቆምንበት “መርዕ” ከምንለው አስተሳሰብ የምንሸራተት? እንዲህ ከሆነ ቀድሞውንም መርዕ አልነበረንም ማለት ነው፡፡ መርዕ ብለን የምንይዘው አሰተሳሰብ በእኔ እምነት ለምናደርገው እንቅስቃሴ የማዕዘን ድንጋይ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ መርዕ ሸርተት ስንል ቀጥሎ የምናገኝው ሌላ የተሻለ ማዕዘን የሚሆን ድንጋይ ሳይሆን ድጥ ወይመ ማጥ ነው የሚሆነው፡፡ ብዙዎች መርዕ የሚመስላቸው በአቋራጭ የሚፈልጉትን ግብ የሚያሳካ አጭር መንገድ አድርገው ይወስዱታል፡፡ ይህ አቋራጭ መንገድ ግን ብዙን ጊዜ ወደ ሌላ ውጥንቅጥ ከመውሰድ አልፎ ለስኬት ሲያበቃ አይታይም፡፡
Girma Siefu
ግልፅ ያልሆነ የህይወት ግብ ያለን ሰዎች የምንሄድበትን ስለማናውቅ ሌሎች በሄዱበት ተከትለን እንነጉዳለን፣ ሌሎች ግባቸውን ሲያሳኩ እኛ የበይ ተመልካች መሆናችን አይቀርም፡፡ ግባችን ግልፅ ያለመሆኑ መድረሻችንን ብቻ ሳይሆን መነሻችንንም ስሚያዛባው ከየት ተነስተን የት እንደምንደርስ፣ እንዴት እንደምንደርስ እንዳናውቅ ያደርገናል፡፡ መርዕ ማለት አሁን ካለንብት ቦታ ተነስተን ወደምንፈልገው ቦታ ለመድረስ የምንጓዝበት ፍኖተ ካርታ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በአሰተሳሰብ ብቻ ሳይሆን በተግባርም ልክ መሆን ያለበት ነው፡፡ አንድ አንድ ሰዎች የምንፈልገውን ግብ ለማሳካት ማነኛውንም መንገድ መጠቀም ችግር የለውም ይላሉ፡፡ ይህ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው /the end justify the means/ የሚባለው ዓይነት መሆኑ ሲሆን፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ ሌሎች የምንሄድበት መንገድ እንደ ወጤቱ ሁሉ መርዕ ላይ መመስረት አለበት የሚሉ ናቸው /The means is equally important as the end/:: በግሌ የማምነውም የምከተለውም የኋለኛውን አማራጭ ነው፡፡ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭው የስግብግቦች መንገድ ነው ብዬ በፅኑ ስለማምን፡፡
ሰሞነኛ ወደ ሆነው የምርጫ አጀንዳ እና በመርዕ ላይ የተመሰረተው የአንድነት ፓርቲ ምርጫ እሳተፋለሁ ውሳኔ እንዴት መታየት እንዳለበት በአጭሩ ይህን አቋም ለደገፉም ሆነ ለተቃወሙ ማሰረዳት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ አንድነት ፓርቲ ስልጣን የሚገኘው በህዝብ ድምፅ ነው የሚል መርዕ አለው፡፡ የህዝብ ድምፅ የሚገኘው ደግሞ በምርጫ ወቅት መራጩ ህዝብ በሚሰጠው ካርድ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ በምርጫ የህዝብ ድምፅ ይገኛል ማለት ነው፡፡ ብዙዎች ምርጫ ለመሳተፍ እኩል ሜዳ ያሰፈልጋል ይላሉ፡፡ ትክክል ነው እኔም አምንበታለሁ፡፡ ሜዳውን ትክክል ከሚያደርገው አንዱ ጉዳይ የምርጫ ቦርድ ገለልተኝነት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የምርጫ ቦርድ ገለልተኛ ካልሆነ ማለትም ሜዳው ትክክል ካልሆነ ስልጣን በሌላም መንገድ መያዝ ተቀባይነት አለው የሚል መከራከሪያ ለማቅረብም ሰበብ ይሆናል፡፡
ስልጣን በተለያየ መንገድ ለመያዝ እንደሚቻል አማራጭ ማሳየት አንድ ጉዳይ ሆኖ እኛ የመረጥነው ብቻ ልክ ነው ማለትም ተገቢ አይደለም፡፡ በተገኘው መንገድ ለመያዝ መሞከር ግን መርዕ አልባ ያደርገናል፡፡ ሰላማዊ ትግል እከተላለሁ ብሎ በሰላማዊ ትግል መርዕዎች አምናለሁ የሚል ማታ-ማታ ወይም ቅዳሜና-እሁድ በሌላ መንገድ ልሞክር የሚል ከሆነ መርዕ አልባነት ነው፡፡ በእኔ እምነት ችግር ያለው የምርጫ ሜዳ ላይ ከሆነ የምርጫው ሜዳው ለማስተካከል ምን አድርገናል? ከሚለው መነሳት አለበት፡፡ ስልጣን የመያዣው መንግድ ኮሮኮንች በዝቶበታል ማለት ኮሮኮንቹን እንዴት እናሻሽል ወደሚል ሊገፋን ይገባል፡፡
ሁሉም ሰው መረዳት ያለበት ገዢው ፓርቲ የምርጫ ሜዳውን ያጠበበው ወይም ኮሮኮንች እንዲበዛበት ያደረገው አውቆ ነው፡፡ ሜዳው ደግሞ የጠበበን ደግሞ አማራጭ አለን የምንል ፓርቲዎች ነን፡፡ አማርጭ ለማቅረብ እድል ስንነፈግ መጠየቅ ያለብን አንድ መስረታዊ ጥያቄ አማራጭ የተከለከለው ህዝብ ምንም ማድረግ አለበት የሚለው ነው? አማራጭ የሚፈልግ ህዝብ ድንጋይ ወይም ጠብመንጃ ይዞ አማራጭ አትከልክሉን ቢል ነው የሚሻለው ወይስ የምርጫ ካርድ ይዞ? አንድነት የመረጠው መስመር የምርጫ ካርድ ይዞ ቢሆን ይሻላል የሚለውን ነው፡፡ ይህ በምንም ዓይነት ሌሎች የመረጡት መስመር አይሰራም ማለት አይደለም፡፡ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጭውን እንደ መርዕ የተቀበለ ብዙ ሌላ አማራጭ ሊያስብ፣ ሊተገብር ይችላል፡፡ ችግሩ የእኛ ካልሆነ ብሎ የሌሎችን ምርጫ ለማክበር አለመፈለጉ ላይ ነው፡፡
ETHIOPIA ELECTIONSበሀገራችን ኢትዮጵያ በ1997 ከተደረገው ምርጫ ውጭ ህዝቡ በምርጫ እንዲሳተፍ የምርጫ ካርድ እንዲወስድ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በተገቢው መልኩና ደረጃ ተቀስቅሶዋል የሚል እምነት የለኝ፡፡ ከ1997 በፊት ምርጫ መወዳድር ወያኔን ማጀብ ነው እያልን ምርጫ የሚወዳደሩትን ብቻ ሳይሆን መራጩንም ተሰፋ እያስቆረጥን ኖረናል፡፡ ይህን ምርጫ የማጣጣል ስትራቴጂያችንን በደንብ የተረዳው ገዢው ፓርቲ የራሱን መራጮችና ተመራጮች እያዘጋጀ ውድድር ሲያድርግ ነበር፡፡ እንደዚያም ሆኖ ህዝቡ በምርጫ ካርዱ ቅሬታውን ሲገልፅ እንደ ነበር የገዢው ፓርቲ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዴእታ የነበሩት አቶ ኤርሚያስ ለገሠ “የመለስ ትሩፋቶች” በሚለው መፅሃፍ አስነብቦናል፡፡ ስለዚህ የአንድነት ቤተሰቦች ምርጫ እንሳተፋለን ስንል መራጮቻችን እንዲመዘገቡ እናደርጋለን ማለት ነው፡፡ የእኛ መራጮች ሲመዘገቡ፣ ገዢው ፓርቲ የእኔ ብሎ ያስመዘገባቸውም ቢሆኑ እኛን ለመምረጥ እንዲችሉ መሸሸጊያ እንሰጣቸዋለን፡፡
ብዙ ሰው መረዳት ያለበት የምርጫ ቅስቀሳ የሚጀመርበት ወቅት መራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሳምንት ሲቀረው ነው (በ1997 ቀድሞ የምርጫ ቅስቀሳ ተጀምሮ ነበር)፡፡ ለዚህ ነው ገዢው ፓርቲ ሁል ጊዜ የሚጮሁት ካርድ ያልያዙ ናቸው የሚለው፡፡ ያስመዘገባቸውን ስለሚያውቅ ነው፡፡ የእኛ መራጮች ካርድ ባልያዙበት ሁኔታ የፈለገ አማላይ የሆነ ለሀገር የሚጠቅም አማራጭ ብናቀርብ ለማሸነፍ ያለን እድል አነስተኛ ነው፡፡
ማስተላለፍ የፈለኩት ነጥብ ምርጫ እገባለሁ-አልገባም በሚል ዥዋዝዌ ስንጫወት ደጋፊዎቻችን በመራጭነት ሳይመዘገቡ እንዳይቀሩ በአንድነት በኩል የተወሰደው እርምጃ ትልቅ ፖለቲካ ውሳኔ ነው፡፡ የምርጫ ፓርቲ መሆናችን የሚታወቅ ቢሆንም እስከ አሁን በተቃዋሚ ፓርቲዎች መስመር ምርጫ መግባትና አለመግባት በቁርጥ ቀድሞ ስለማይወሰን መራጮች ሁለት ልብ እየሆኑ ከጫወታ ውጭ ሲደረጉ ከርመዋል፡፡ ይህ እንዳይደግም መራጮች እንዲመዘገቡ እና በምርጫው ሙሉ ሂደት በንቃት እንዲሳተፉ ይህን አቋም መያዝ እጅግ አስፈላጊ እና ጠቃሚ ነበር፡፡ ሁሉም እንደሚረዳው ያልተመዘገበ ደግሞ አይመርጥም፣ ያልመረጠ ደግሞ ድምፁ እንዲከበር ዘብ ሊቆም አይችለም፡፡ ድምፃችን ይከበር የሚለው እንቅስቃሴ የሚጀምረው ከህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እሰከ ድምፅ ቆጠራ ድረስ ይዘልቃል፡፡
ጎበዝ ሰላማዊና ህጋዊ ትግል እናደርጋልን ስንል የሰላማዊና ህጋዊ ትግል መርዖዎችን ጠንቅቀን መረዳት የግድ ይለናል፡፡ በስላማዊ ትግል ዋናው ግብ የህዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ ሲሆን፣ ስልጣን መያዝ የሚፈልግ ፓርቲ የህዝብ ይሁንታ ማግኘት የግድ ይለዋል፡፡ ይህ ደግሞ በምርጫ የሚገኝ ነው፡፡ ምርጫውን የህዝብ ፖለቲካ ተሳትፎ መለኪያ አድርገን ለመውስድ ቁርጠኞች መሆን የግድ ይለናል፡፡
ቸር ይግጠመን

የብሄር ነጻነት እስከ መጨፈር — ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

November 30,2014
ማስታወሻ፡ ይህች ጽሁፍ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከተከሰሰባቸው ሁለት መጣጥፎች አንደኛዋ ናት። በመጭው ወር በአሶሳ የሚደረገውን የብሄር ቀን ድራማ እሳቤ በማድረግ – በርካታ አንባብያን በጠየቁት መሰረት እነሆ በድጋሚ ለንባብ አቅርበናል።
— ክን
ፉ አሰፋ –
“እኛ ጭቁን ብሄረሰቦች ከዚህ ቀደም በየሰው ቤት ተቀጥረን የምንሰራ፣ አሽከሮች እየተባልን ነበር የኖርነው። አሁን ግን ይኸውና ህገ-መንግስታችን መብታችንን ሰጥቶናል… ኑሯችንም ተሻሽሎ ዛሬ ዘመናዊ ኑሮ እየኖርን ነው።”

እያለ የሚናገርን አንድ ጎልማሳ የቴሌቪዥኑ መስኮት ያሳያል። የደቡብ ቅላጼና ዘዬ ባለው አማርኛ ከደቡብ የመጣ ጎልማሳ ነው በቴሌቪዥን ቀርቦ መግለጫ እየሰጠ ያለው። ከአነጋገሩ በቀን ሶስቴ የሚበላ፣ የባቡር ሃዲድ እና የኤሌክትሪክ መስመር ገብቶለት፣ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም… ይመስላል።

  የዚህ ምስኪን ሰው ገጽታ እና አለባበሱ የሚነግረን ግን ሌላ ነው። በኢህአዴግ ዘመን መብቱ እንደተከበረና ኑሮው እንደተሻሻለ የሚነግረን ይህ ሰው፣ መሰረታዊ የሆነውን የሰው ልጆችን የኑሮ ፍላጎት እንኳን አላሟላም። ለእግሩ ጫማ የለውም።  በባዶ እግሩ ነው የቆመው። ሃፍረተ ስጋውን ከሸፈነለት ብጣቂ ጨርቅ በስተቀር ሰውነቱም እርቃኑን ነበር።

ለመገናኛ ብዙሃን ፍጆታ አነጋገሩ እንዲያሳምር ተነግሮት ሊሆን ይችላል – ንግግሩ ልክ መካከለኛ ገቢ ካላቸው የምዕራብ አውሮፓ ሃገሮች ተርታ የተሰለፈ ይመስላል። ይህ ደግሞ ገና የ’ትራንስፎርሜሽኑ’ ተስፋ እንጂ፤ ለውጡ በብሄር ብሄረሰቦቹ ላይ እንደማይታይ የቪድዮ ምስሎቹ ፍንትው አድርገው ነው የሚያሳዩት። ኢትዮጵያ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ላይ እንደምትደርስ ኢህአዴግ ቃል ገብቷል። በአሁኑ ግዜ ሰባት በመቶ ብቻ የሆነው የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ብሄር ብሄረሰብ እና ሕዝብ በአምስት አመቱ እቅድ 80 በመቶ ይደርሳል ብለውናል። በእስር ያለው ጠንቋይ ታምራት ገለቴ ነግሯቸው ካልሆነ በስተቀር መቼም ይህንን ተረት ተረት በማህበራዊውም ሆነ በተፈጥሮ ሳይንስ ሊያረጋግጡልን እንደማይችሉ እርግጥ ነው። ከፈረሱ ጋሪው… እንዲሉ ከተግባሩ ወሬው፣ ከ’ህዳሴው ግድብ’ ስራም ሽልማቱ ቀድሞ መያዣ – መጨበጫው የጠፋ ነው የሚመስለው። ከገጠር እየታፈሱ ለሚመጡት ለነዚህ ምስኪን ወገኖች የ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ መብት ማለት በአመት አንዴ በጎዳና ላይ እየወጡ መጨፈር እና ያለፈውን ስርዓት ማውገዝ ብቻ ነው የሚመስለው። ጭፈራውና ውግዘቱ እንደ ጥምቀት በዓል ስለተለመደ የግድ መደረግ እንዳለበት ያመኑበትም ይመስላል።

የደርግ ስርዓት ሰዎች በባህላቸውና በቋንቋቸው እንዳይዘፍኑ ከልክሎ እንደነበር የሚጠቁም መረጃ የለም። ደርግ አስራ ሰባት አመት ገዛ፣ 20 አመት ሙሉ በብሄር ጭቆናው ሲወገዝ ኖረ። በባንዲራ ቀን ውግዘት፣ በከተሞች ቀን ውግዘት፣ በብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ውግዘት፣ በግንቦት ሃያ ቀን ውግዘት…. በየሽልማቱ ስነ ስርዓት እና በየበዓላቱ ቀን ውግዘት….። የደርግ ሃጢያት መብዛት የነሱን ግፍ ይሸፍን ይመስል የኢህአዴግ በዓላት እና ውግዘቱ ከለት-ተለት ሲጨምር ብቻ ነው የምናየው – እንደ 11 በመቶው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያ እድገት።

የዚህ ሳምንት ወሬ ደግሞ በመቀሌ ስለተካሄደው ስድስተኛው የ ‘ብሄር – ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን’ ነው። የመከር ወቅት ስራቸውን እንዲያቆሙት ተደርገው፣ ከየክልሉ እየተጫኑ ለጭፈራ መቀሌ የገቡ አርሶአደሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። በዲያጎን እየተፈለጉ የተለቀሙ ልማታዊ አርቲስቶች እና የመድረክ አስተዋዋቂዎችም በስፍራው ተገኝተዋል። የእውቁ ኪነጥበብ ሰው – የኪሮስ አለማየሁ ልጅ ዛፉ ኪሮስ ‘አንበሳ ገዳይ’ በሚለው የትግርኛ ዘፈንዋ መድረኩን ይዛዋለች። በርከት ያለ ሰው መድረኩን ከቦት ይጨፍራል። አዳራሹም በ ‘ብሄር – ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ ተሞልቷል። መቀሌ፣ ኅዳር 27 ቀን 2004 ዓ.ም.።
የእለቱ የመድረክ አስተዋዋቂ ‘አንበሳ ገዳይ’ የሚለው የዛፉ ኪሮስ ዘፈን የተስማማው አይመስልም፤ አልተዋጠለትም። አልያም ዘፈኑን እዚያው መድረክ ላይ እንዲያስተባብል ተነግሮታል። ተራውን ጠብቆ ማይክራፎኑን ያዘ። “ህገ መንግስታችን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ብቻ ሳይሆን ለዱር እንስሶችም…” ብሎ እየተናገረ እያለ እንደተለመደው መብራት ተቋረጠ።
  በዚህ ‘ታላቅ’ ቀን መብራት መቆራረጡ ቢያበሳጭም፣ በእንግድነት ወደ መቀሌ የተጓዙት ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ ኤሌክትሪክ ምን እንደሆነ ስለማያውቁ አልደነቃቸውም – የሚያውቁት ደግሞ የለመዱት ስለሆነ – ለእነሱ እንግዳ ነገር አይደለም።  ከቆይታ በኋላ ግን መብራት መጣ። ልማታዊው አርቲስትም ንግግሩን ቀጠለ።

“…ህገ መንግስታችን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ብቻ ሳይሆን የዱር አራዊቶችንም መብት ስላስከበረ አንበሶች አሁን አይገደሉም።…” በማለት የዘፈኑን መልእክት ለማስተባበል እና ጭብጡን ለብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ለማስረዳት ሞከረ። እዚህ ላይ የመድረክ አስተዋዋቂው እና ዘፋኝዋ እንዳልተግባቡ መገመት ይቻላል። ዛፉ ኪሮስ ዘፈንዋን በዚህ መድረክ ታቅርበው እንጂ መልእክቱ ላሁኑ ትውልድ ሳይሆን ምናልባት ‘ተራራ ላንቀጠቀጠው’ ለዚያኛው ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ የተሳነው ይመስላል። ያ ቡድን የትኛውን ተራራ እንዳንቀጠቀጠ ባይገለጽልንም አሁን ያጠለለበት የለውጥ ደመና ግን በተራው እያንቀጠቀጠው ለመሆኑ ከሚያደርጋቸው ግራ ገብ ድርጊቶቹ መረዳት ይቻላል።

የሆነው ሆኖ በአሉ ለመቀሌ ህዝብ ልዩ ስሜት እንደሰጠው ይታያል። ይህ ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ተለይቶ፣ በእነ መለስ እና በረከት ካድሬዎች ታጥሮና ታፍኖ የሚገኝ ህዝብ ስለመሆኑ በርካታ መረጃዎች ይመሰክራሉ። ከስፍራው የሚደርሱን መረጃዎች እንደሚተቁሙት ከመንግስት ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ውጭ ያሉ የመገናኛ ብዙሃንን በዚያ ክልል መጠቀም ራሱ እስከ ስድስት ወር የሚያሳስር ወንጀል ነው። ለ20 አመታት የታፈነ ህዝብ ከሌላው ወገኑ ጋር ተቀላቅሎ ፣ አብሮ ሲጨፍር የሚፈጥርበትን ስሜት መገመት አያደግትም። የደርግ ስርዓት የአሜሪካ እና የጀርመን ድምጽ ራዲዮን የትግራይ ህዝብ እንዳይሰማ አልከለከለም ነበር። ወያኔ ግን የትግራይ ህዝብን የመናገር ብቻ ሳይሆን የመስማት መብቱንም ጭምር ነው የነፈገው።

የሳተላይት ዲሽ ቴሌቪዥን ክልክል በሆነበት በዚያ ክልል የኢቲቪ አኬልዳማ ድራማ ይደገምልን ብሎ የትግራይ ህዝብ ቢጠይቅ ሊደንቀን አይገባም። ጆሮ ካሰለቸው የ’ህዳሴው ግድብ’ ወሬ እና እጅ እጅ ካሉት ከነ ሰራዊት ፍቅሬ አኬልዳማ ትንሽም ቢሆን ዘና ሳያደርጋቸው አልቀረም። የቴሌቪዥኑ መግቢያ ላይ ታዲያ ‘እንደምን አመሻችሁ ዲሽ የሌላችሁ” ብሎ ነው የሚጀምረው እየተባለም ይቀለዳል። ይህ ህዝብ በስሙ ሲነገድበት እና ከሌላው ወገኑ ጋር እንዲቃቃር ሲደረግ የትግራይ ኢሊቶች ዝም ማለታቸው እጅግ የሚያሳዝን ጉዳይ ነው። ስለ ዱር አራዊት መብት እና ስለ አንበሳ መግደል ሲነሳ ትዝ ያለኝ የ1983ቱ የአምባሳደር ተስፋዬ ሃቢሶ ንግግር ነበር። ቻርተሩ ሲጸድቅ በነበረበት ጊዜ የከምባታና ሃድያን ጎሳ እወክላለሁ ብለው ወንበር ይዘው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ሃቢሶ በወቅቱ ሲናገሩ። “እኛ አናሳ ብሄር ብሄረሰቦች ዲሞክራሲ ብቻ ሳይሆን የሚያስፈልገን፣ እንደብርቅዬ እንስሣ እንክብካቤም ይገባናል።” ብለው ነበር።

ኢህዴግም በወቅቱ ለእነኚህ ‘አናሳ ጎሳዎች’ ልዩ እንክብካቤ እንደሚያደርግ ነበር ቃል የገባው። አቶ ተስፋዬ ይህንን በተናገሩ ከአመታት በኋላ ታዲያ በሃዲያ እና ወላይታ ወገኖቻችን ላይ ጥይት እና ቦምብ እንደዝናብ ወረደባቸው። የ1993ቱ ብሄራዊ ምርጫ ተጭበርብሯል፣ ‘ድምጻችን ይከበር’ ብሎ የጮኸው የደቡብ ወገናችን በመለስ ወታደሮች ያለ ርህራሄ ነበር የተጨፈጨፈው። ልዩ እንክብካቤው እና ዴሞክራሲው ቀርቶ ይልቁንም የቆሙለት፣ በስሙም ስልጣን ያገኙበት፣ የራሳቸው ጎሳ በጥይት ሲቆላ አቶ ተስፋዬ ሃቢሶ ሹመታቸውን ላለማጣት ሲሉ ትንፍሽ አላሉም። እንዲያውም ዛሬም ስለ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች’ መብት መከበር ከሚነግሩን እና የሌሎችን ጽሁፎች እየሰረቁ ከሚጽፉት ሰዎች አንዱ ናቸው።

  ማሌሊቶቹ የሃገሪቱ የዘመናት ችግር የብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች መብት መነፈግ ነው ሲሉ ሰበኩ። የዚህ ችግር መፍቻ ቁልፍም በእጃቸው እንዳለ ነገሩን። በለስ ቀንቷቸው ምኒሊክ ቤተ መንግስት ሲገቡም ጫካ ውስጥ የጻፉትን ያንን የስታሊን ፍልስፍና ወደ ህገ-መንግስትነት ቀየሩት። መፍትሄ ያሉት የጎሳ ፖለቲካም በጥላቻና በበቀል ተተካ። የማሌሊት ፍልስፍና ሲተገበር ታዲያ የመጀመርያ ሰለባ የሆነው አማራው ወገናችን ነበር። ለፖለቲካ ትርፍ ሲሉ እነ አቶ መለስ ዜናዊ ይዘውት የመጡት የጥላቻና የብቀላ ፖለቲካ እንደስካር ቶሎ በረደ እንጂ አካሄዱ እጅግ ዘግናኝ ነበር። በምስራቅ እና በምእራብ ኢትዮጵያ የአማራ ዘር ጨርሶ እንዲጠፋ ተዘምቶበት ነበር። የአማራን ዘር ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ከተበቀሉት በኋላም ጽዋው ወደ አኙዋክ – ጋምቤላ ሄደ ፣ ከአኙዋክ ጭፍጨፋ በኋላ ደግሞ ዘመቻው በኦሮሞ ወገናችን ላይ ቀጠለ። በወላይታ ተከተለ፣ በኦጋዴን… ተዛመተ። የብሄር መብት እስከመገንጠልን ያስከበረው ህገ-መንግስት ጸድቆ በወረቀት ላይ ተቀምጧል። ይህንን መብት እየጠየቁ ያሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችንን ግን በዘራቸው ብቻ እየተመረጡ ማጥፋቱ ዛሬም በሚያሳዝን ሁኔታ እንደቀጠለ ነው።

እነ መለስ እነ በረከት ለዘመናት ተዋልዶና አብሮ ሲኖር የነበረን ህዝብ እንደ እንግሊዝ ከፋፍለህ ግዛው ቅኝ ስርዓት ለአገዛዝ እንዲያመቻቸው ህዝቡን እርስበርስ እያጋጩት ላለፉት 20 አመታት ለመቆየት ችለዋል። የዘር ፖለቲካው ምስጢር ይኸው ነው። ህንን ባያደርጉ ኖሮ እስካሁን እንደ ጉም ተበትነው በጠፉ ነበር።

  ወደመቀሌው በዓል እንመለስ። ብሄር ብሄረሰቦቹ በመቀሌ ከተማ በቡድን በቡድን እየዘፈኑና እየጨፈሩ ይጓዛሉ። በተለይ ከደቡብ የመጡት ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸው ተከብሮላቸው ወደ እድገት ጎዳና ከተጓዙ ከሃያ አመት በኋላም – ጥንታዊው የጋርዮሽ ስርዓት ከሚመስለው አለባበሳቸው እንኳን አልተቀየሩም። መር ከሃያ አመት በፊት ቅጠል ለብሶ ይጨፍራል፣ ዛሬም ቅጠሉን አልቀየረም። ዳውሮ ድሮ ለእግሩ ጫማ አያደርግም ነበር አሁንም ጫማ የለውም። ከፊቾ ከ20 አመታት በፊት ከቀንድ የተሰራ የሙዚቃ መሳርያ ነበር የሚጠቀመው፣ አሁንም እሱኑ ይዞ ነው መቀሌ የመጣው…። ሁሉም አንዳች ለውጥ አይታይባቸውም። ታድያ የዚህ ሕዝብ ነጻነቱ፣ ለውጡ እና እድገቱ የቱ ላይ እንደሆነ ማን ይሆን የሚያስረዳን?

ህገ መንግስታዊ መብቴ ይከበርልኝ ባለ ብቻ ምላሹ የጥይት እና ቦንብ የሆነ ሕዝብ ቅጠል ለብሶ መጨፈሩ ምን ትርጉም ይሰጠናል? ይህ ነጻነቱን ያሳየናል እንዴ? ወይንስ ዛሬም የእግር ጫማ እንኳን አለማድረጉ እንደ ባህል ተቆጠረለት?  ጎንደሬው ሁመራ ላይ ለማረስ ፈቃድ ከመቀሌ መጠየቁ ነው የመብቱ መከበር? ወይንስ መቀሌ ላይ ሄዶ እስክስታ መምታት? አፋርና ኢሳ – ጉርጉራ ላይ ካላረሰ – አማራው ኦሮሞ ምድር ላይ እንዳይሰራ ከታገደ መብቱ ምኑ ላይ ነው?

ተረስቶ ይሆን ይሆናል እንጂ “የአክሱም ሃውልት ለወላይታው ምኑ ነው?…” ብለው ነበር አቶ መለስ። ታዲያ ዛሬ ምን አዲስ ነገር ተገኘ? በመቀሌ እየተደረገ ያለው የወላይታ ጭፈራስ ለአድዋው ምኑ ሊሆን ነው? ‘የኢትዮጵያ ጥንታዊ ስልጣኔ አንተን አይመለከትህም’ ተብሎ የነበረ የወላይታ ህዝብ ዛሬ የመለስን ፎቶ እና ‘ለልማት የተጋ ብቸኛው መሪ’ የሚል መፈክር ይዞ በመቀሌ እንዲሰለፍ ተደርጓል። ደቡቡ የየራሱን የአፍ መፍቻ ቋንቋ እርግፍ አድርጎ ትቶ ኢህአዴግ በፈጠረለት ‘ወጋ ጎዳ’ እንዲናገር አቶ መለስ፡ ሲያስገድዱት እነሱ ግን ልጆቻቸውን በአለም አቀፍ ቋንቋ ብቻ እንዲማሩ ነው ያደረጉዋቸው። ዛሬ አቶ መለስ የነዚህን ጎሳዎች መብት መከበር ነው በመቀሌ እያበሰሩ ያሉት።

ይህ ህዝብ እንዲሁ ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች እየተባለ ሲቀለድበት እንደዋዛ ሃያ አመታት አለፉ። በኢህአዴግ ዘመን ተወልዳ፣ ተምራ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀች ወጣት አንድ አፍሪካ ሃገር አግኝቼ አወራኋት። ሜሮን ትባላለች። ስለ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች መብት እና ነጻነት ልትነግረኝ ሞከረች። ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ ውጤት ሳይኖራት ይልቁንም ኢህአዴግ በሰጣት እድል ዩኒቨርሲቲ ገብታ እንደተማረች ስለተነገራት የመለስ ዜናዊ አድናቂ ናት።

በወሬያችን መሃል በድንገት ‘ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ማለት ምን ማለት ነው?’ ብዬ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ዱብዳ ነገር ሆነባት። ለሚለኒየም ግብ ሲባል ከተከፈቱት ዩኒቨርሲቲዎች ለስታስቲክስ ማሟያ የተመረቀች ስለመሆንዋ አመለካከትዋ፣ አስተሳሰብዋ እና ንግግርዋ ይገልጸዋል። ጥያቄዬን ለመመለስ እንደከበዳት ተረዳሁ። ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች የሚለውን ቃል የሜሮን ትውልድ ለሃያ አመታት ያለማቋረጥ ሲሰማው የነበረው ጉዳይ ነው። ለዚህ ትውልድ የብሄር መብት ማለት ግን በየአመቱ በጎዳና ላይ ከሚደረግ ጭፈራ ውጭ የሚሰጠው ሌላ ትርጉም ያለ አይመስለኝም። ማን ነው ብሄር? ብሄረሰሰቦችስ የትኞቹ ናቸው? ህዝቦች የሚባሉትስ? ለዚህ ጥያቄ እንኳንና ሜሮን – ወያኔም መልሱ እንደሚቸግረው ይገባኛል። ሜሮን ግን ኮስተር ብላ “ህገ መንግስቱ ነዋ!” አለችኝ።

ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች ወጣት ቀርቶ ከአንደኛ ደረጃ ተማሪ እንኳን የማልጠብቀውን መልስ በማግኘቴ ባዝንም – በመልስዋ ግን ትንሽ ፈገግ ማለቴ አልቀረም። ከአፍታ ቆይታ በኋላ – ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ማለት ራሱ መለስ ዜናዊ ይመስለኛል ስትል ቀለደች ሜሮን። እዚህ ላይ ልብ በሉ! ‘የህዳሴው ግድብ’ ሽልማት ስነ ስርዓት እየተደረገ በነበረበት ግዜ የግድቡ “ወደር የሌለው ተሸላሚ”ን ሰራዊት ፍቅሬ በቴሌቭዥን ሲያስተዋውቅ የሆነው ነገር ታወስውኝ። ነገሩ ጤነኛ አእምሮ ላለው ሰው እንግዳ ነበር።
ሰራዊት እና ሙሉአለም እየተቀባበሉ – እየደጋገሙም ‘የህዳሴው ግድብ ወደር የሌለው ተሸላሚ’ ይላሉ። ከብዙ ደቀቃ በኋላም የህዳሴው ግድብ ወደር የሌለው ተሸላሚ ይፋ ሆነ።

“ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች!” ሲል ሰራዊት ፍቅሬ በሚለኒየም አዳራሽ ለተሰበሰበው ህዝብ አበሰረ። ሸልማቱን የሚሰጠው አቶ መለስ ዜናዊ ፣ ሽልማቱን የሚቀበለው የኢህዴግ ተወካይ ሲሆን ፣ ይህም በተዘዋዋሪ አቶ መለስ ዜናዊ መሆኑ ነው። ሜሮን ይህንን ማለትዋ ከሆነ – ጥያቄዬን በትክክል እንደመለሰችልኝ ተረዳሁ። ሽልማቱ መጣም አልመጣ ለብሄር ብሄረሰቦቹ የሚፈይደው ነገር አይኖርም። በየአመቱ የሚደረገው የጎዳና ላይ ጭፈራ ግን የብሄረሰቦች መብት ብቻ ሳይሆን ግዴታቸውም ሆኗል ብለን እንደምድም።

የብሄር ነጻነት እስከ መጨፈር! ከዛ ካለፈ ግን የህይወት ዋጋም ያስከፍላል። ኦጋዴንን ያስተውሏል?

Saturday, November 29, 2014

የሕወሓት ሰዎች በብአዴን እና በኦሕዴድ ባለስልጣናት ላይ በአዲስ መልክ ሽብር እየፈጠሩ ነው::

November 29,2014
ምንሊክ ሳልሳዊ 
- ክፍተኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን በሚል ተከፍለው እየተሰለሉ ስልካቸው እየተጠለፈ መሆኑ ታውቋል::
- የሕወሓት ስጋት ውስጥ ውስጡን ክሻእቢያ ጋር ግንኙነቱን እንዲያጠናክር አድርጎታል::

- የኢትዮጵያ ሕዝብ ውስኝ የለውጥ ወቅት ላይ መሆኑን አውቆ አደባባይ በመውጣትወያኔን ሊያስወግድ ይገባል::
ከፊታችን አደጋ አለ በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የገቡት እና በመፍትሄፍለጋ ስብሰባዎች የተወጠሩት የሕወሃት ሰዎች ክከፍተኛ ባለስልጣናት ጀምሮ እንከ በታች ሹሞች ድረስ በብአዴንና በኦህዴድ ባለስልጣናት ላይ ክፍተኛ የማስፈራራት እና የማዋከብ ሽብር እየፈጸሙ መሆኑን አንድ ከፍተኛ የኢሚግሬሽን እና ደህንነት ባለስልጣን ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::
በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ የሚገኙ የብአዴን እና የኦሕዴድ አባላት በግል እንዳይገናኙ እንዲሁም ከመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች ጋር እንዳይገናኙ ከፍተኛ የሆነ ክትትል እየተደረገባቸው ሲሆን በባለስልጣናት ደረጃ እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የሚያጠና የደህንነት ቡድን የተመደበባቸው ሲሆን ስልኮቻቸውም እየተጠለፉ መሆኑን እኚሁ ባለስልጣን ተናግረዋል::
የብአዴንና የኦሕዴድ ሰዎችን ከፍተኛ አነስተኛ እና ጥቃቅን በሚል ተከፍለው በሕወሓት እየተሰለሉ ስልካቸው እየተጠለፈ ሲሆን እንደ በግ የሚታዘዝላቸው የደቡብ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ውስጥ ዘልቀው እንዳይገቡ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::ከዚህ ቀደም ከፍተኛ የሆኑ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት መቀራረብ እና አብሮ መዋል የሕወሓት ሰዎችን ማሳሰቡን እና የደህንነት ክትትል እያደረጉባቸው እንደነበረና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከደመቀ መኮንን እና ከሙክታር ከድር ጀምሮ እስከ በታች የፌዴራል ባለስልጣኖች ላይ ከፍተኛ ስለላ እየተካሄደ ምንጮች መረጃ ሰተው እንደነበር ሲታወቅ ይህ በአሁኑ ወቅት በእጥፍ ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል::
ሁኔታዎች መልካም አይደሉም ከፊታችን አደጋ ተደቅኗል::ለውጥ ያስፈልጋል::የሚሉ የተቆጡ ድምጾች በስፋት በኢሕኣዴግ አባላት እየተሰሙ ያለበት አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ሕወሓት በግል እና በጋራ ባለስልጣናቱ ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት እና ዛቻ እያደረገባቸው መሆኑን የተናገሩት ምንጮቹ ኢሕአዴግን ለመናድ ብትሞክሩ ሃገሪቷ ትበታተናለች::እንደ ሱማሊያ መንግስት አልባ ሆና እንደ ሩዋንዳ ትበጠበጣለች እያሉ ከማስፈራራትም አልፎ በግል የተነከራችሁበት ሙስና አደባባይ እናወጣዋለን:: እኛን ማንም ሊጠይቀን አይችልም ቁልፉ እኛ ጋር ነው የሚሉ በኣደገኛ መርዞች የተሞሉ ማስፈራሪያዎች መሰንዘር ክጀመሩ እንደቆዩ ተገልጿል::
የኢትዮጵያን ህዝብ እንደ ሶማሌ እና ሩዋንዳ ማስብ ጅልነት ነው::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ እንጂ ፍጅት ስለማይፈልግ ኢሕ አዴግ ሲፈርስ ሕወሓት እንደሚያስበው ሳይሆን ትልቅ ሰላም በሃገሪቱ ላይ ይሰፍናል ያሉት ምንጩ የብኣዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት የየቀን ሪፖርት እና ግንኙነት በተመለከተ ማን ከማን ጋር እንደዋለ ማን እነማን ቤት እንደሄደ በመከታተል እየቀረበ ሲሆን የሃገሪቱን የደህንነት ቢሮ በጋራ የሚመሩት ጸጋዬ:ጌታቸውና ደብረጺሆን በየቀኑ ለትግሪኛ ተናጋሪ ደህንነቶች በአጫጭር ስብሰባዎች መመሪያ እያወረዱ ከመሆኑም በላይ አደጋ ውስጥ መሆናቸውን እየደጋገሙ እንደሚናገሩ ምንጮቹ አክለዋል::
በአሁን ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ ወሳኝ የትግል ወቅት ላይ መሆኑን በማወቅ የበሰበሰውን የወያኔ አምባገነን ስርአት ለመጣል በጋራ አደባባይ በመውጣት የሚያካሂደውን አብዮት የመከላከያ ሰራዊት የፖሊሱ እና የብአዴን እንዲሁም የኦሕዴድ ፓርቲ ለውጡን እንደሚደግፉት የህዝቡን መነሳሳት እየጠበቁ መሆኑን እና ሕወሓት ከመስጋቱ የመጣ ከሻእቢያ ጋር በውስጥ ግንኙነቱን አጠናክሮ መቀጠሉን እንዲሁም ለተመረጡ የኤርትራ ስደተኞች የደህንነት ትምህርት የተሰጠ እንደሚገኝ እኚሁ ባለስልጣን መረጃ አድርሰውኛል: