Saturday, June 13, 2015

ቴድሮስ አድሐኖም በጆሐንስበርግና በፕሪቶሪያ ዙሪያ እንዳይዘዋወሩ ጥብቅ መልእክት እንደደረሳቸው ተነገረ

June 13,2015

በደቡብ አፍሪካ የሚደረገዉን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመካፈል ወደዚያዉ ያመራዉ የወያነኔ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቴድሮስ አድሐኖም በጆሐንስበርግና በፕሪቶሪያ ዙሪያ እንዳይዘዋወሩ ጥብቅ መልእክት ከወያኔ መረጃ ቢሮ በፕሪቶሪያ ለሚገኘዉ የወያኔ ኢንባሲ መተላለፉን ከዉስጥ የወጣ መረጃ አመለከተ::

ተላላኪዉ ቴድሮስ አድሐኖም በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ የወያኔ ደጋፊዎችን ሰብስቦ ሊያነጋግር በሞባይል ስልክ መልክት (text)እያደረገ ሳንድተን ሪክሬሽን ሴንተር ቀጠሮ እያስያዘ መሆኑን የደረሱበት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ተቃዋሚዎች በንቃት እየተጠባበቁት ሲገኙ ተላላኪዉ ቴድሮስ በማንኛዉም ስፍራዎች ለመዟዟር እንዳይችል ተደርጓል።

በተጨማሪ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ሚኒስተሩን በመቃወም በተገኘበት ስፍራና ቦታ ሁሉ መረጃ ለመስጠት በተጠንቀቅ መቆማቸዉን አሳዉቀዋል። ወያኔና ወያኔይያዊያን በሙሉ በደረሱበት ሁሉ ከመዋረዳቸዉንና ከመሸማቀቃቸዉን በዘለለ መልኩ ህዝብን በመፍራት መደበቃቸዉ በራሱ አንድ ታላቅ ድል ነዉ ሲሉ ከወደ ሳንድተን አንድ ግለሰብ ተናግረዋል፤

መርጋ ደጀኔ እንደዘገበው

No comments: