Friday, July 4, 2014

የአፍሪቃ መሪዎች ያለመከሰስ መብት

June4/2014
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ

የአፍሪቃ መሪዎች ባለፈዉ ሳምንት ባካሄዱት ጉባኤ አንድ መሪ በስልጣን ላይ እያለ ክስ እንዳይመሠረትበት መስማማታቸዉ ትችት አስከትሏል። የአፍሪቃ የፍትህና የሰብዓዊ መብቶች ፍርድ ቤት የተሰኘዉ መድረክ ስልጣን ላይ የሚገኙ መሪዎችና ባለስልጣናትን መክሰስ እንዳይችል የታገደ ነዉ።

የመብት ተሟጋቾች ከወዲሁ የተጣለዉ እገዳ ወንጀል ፈፃሚዎች ሳይጠየቁ በነፃ እንዲኖሩ ያደርጋል እያሉ ነዉ። የአፍሪቃ መሪዎች ይህን ዉሳኔ ያሳለፉት ባለፈዉ ሳምንት ዓርብ ዕለት ኢኳቶሪያል ጊኒ ላይ ባካሄዱት ጉባኤ ነዉ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደሚለዉ የመሪዎቹ ስብሰባ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ ተደርጎ በዝግ ነዉ የተካሄደዉ። የዝግ ስብሰባዉ ዉሳኔም ሰኞ ዕለት ማምሻዉ ላይ በመግለጫ መልክ በድርጅቱ ይፋ ሆነ። መሪዎቹ አፍሪቃዊ መሪም ሆነ የመንግስት ባለስልጣን ስልጣን ላይ እያለ ክስ ሊመሠረትበት አይገባም ማለታቸዉን 42 የአፍሪቃ እና ዓለም ዓቀፍ ሲቪል ማኅበራትና የመብት ተሟጋች ቡድኖች ተቃዉመዋል።
በሎንዶን የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የህግ አማካሪ ኮላዋሊ ኦላኒያ( kolawole Olaniyan) የመብት ተሟጋቻቾች የተቃወሙበትን ምክንያት ያስረዳሉ፤
“የተደረገዉ ማሻሻያ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ያሳስበዋል፤ ምክንያቱም ለአፍሪቃ ሃገራት መሪዎች፣ የመንግስት ከፍተኛ ባልስልጣናትና መራሄ መንግስታት በጅምላ ጭፍጨፋ፣ በጦር ወንጀልና በሰብዓዊነት ላይ በሚፈፀሙ ወንጀሎች ያለመከሰስን ከለላ ይሰጣል። ያለመከሰስ መብት ደግሞ እንደሚታወቀዉ ወንጀል ፈፅሞ በነፃነት መንቀሳቀስን ያስከትላል። ይህም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰለባዎችን ይጎዳል። ለዚህ ነዉ እኛ የተቃዉምነዉ።»
እንደአምነስቲ እምነትም ስልጣን ላይ የሚገኙት ፖለቲከኞች የማይከሰሱ ከሆነ የመብት ጥሰቶችና የጦር ወንጀሎች ቢፈፀሙም ተጠያቂዉ በነፃነት እንዲኖር ያስችላል። አፍሪቃ ለከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂነት እንዲኖር ለማስቻል ጥረት እያደረገች በምትገኝበት በዚህ ወቅትም መሪዎቿ ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ መስማማታቸዉ ትርጉም እንደሚያጣ ነዉ የተገለፀዉ። የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የህግ አማካሪ ኮላዋሊ ኦላኒያ እንደሚሉት የአፍሪቃ መሪዎች ይህን ማሻሻያ ያደረጉበት ወቅት አነጋጋሪ ነዉ፤
0,,17403235_404,00
“ይህ ነገር የመጣዉ የአፍሪቃ መሪዎች ዓለም ዓቀፉን የወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ላይ ከፍተኛ ተቃዉሞ ባሰሙበት ወቅት ነዉ። ፖለቲካዊ ስሌት እንዳለዉ አናዉቅም። ነገር ግን ቀደም ብዬ እንዳልኩት ይህ ፍርድ ቤት የአፍሪቃ መሪዎች በስልጣን ላይ እስካሉና እስከቆዩ ድረስ ከሶ ከችሎት ማቆም አይችልም።»
የአፍሪቃ ኅብረት ICC በኬንያ ፕሬዝደንት ዑሁሩ ኬንያታና በምክትላቸዉ ላይ የመሠረተዉን ክስ እንዲያስነሳ የተመድ ላይ ያደረገዉ ግፊት ዉጤት አላመጣም። ሁለቱም በጎርጎሪዮሳዊዉ 2007ዓ,ም በሀገራቸዉ ከተካሄደዉ ምርጫ በኋላ በተፈጠረዉ ግጭት በሰብዓዊነት ላይ ከተፈፀሙ ወንጀሎች ጋ በተገናኘ ICC ክስ መስርቶባቸዋል።ሁለቱም ግን የቀረበባቸዉን ክስ ያስተባብላሉ። የአፍሪቃ መሪዎችም አፍሪቃ ላይ ብቻ ያተኩራል ያሉት ICC በመንበረ ስልጣናቸዉ ላይ የሚገኙ መሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን በአንድ ድምፅ እየተቃወሙ ነዉ። ችሎቱ ከተመሠረተበት የሮማ ዉል ፈራሚ የአፍሪቃ ሃገራት ቦትስዋና ብቻ ይህን ተቃዉማለች።ተቺዎችም እንዲሁ የICC አባል ያልሆነችዉ ዩናይትድ ስቴትስ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በፍርድ ቤቱ አሰራር እጇን እንደምትከት በማመልከት የአፍሪቃ መሪዎች በራሳቸዉ ላይ ያነጣጠረ ነዉ የሚሉትን ፍርድ ቤት አሠራር መቃወማቸዉ አይደንቅም ይላሉ። ኮላዋሊ ኦላኒያ በዚህ ላይ አስተያየታቸዉን እንዲሰጥተዋል፤
0,,17399307_404,00
“እዉነታዉ አብዛኞቹ የአፍሪቃ መንግስታት ዓለም ዓቀፉ የወንጀል ችሎት የተመሠረተበት የሮም ዉል ፈራሚዎች ናቸዉ። እናም ይህን ተጠቅመዉ ለራሳቸዉ ያለመከሰስ መብት ማጎናጸም መሞከራቸዉ ስህተት ነዉ። ምክንያቱም ይህ ከመተዳደሪያ ደንባቸዉ የሚጻረር ነዉ። የኅብረቱን የመተዳደሪያ ደንቡን ብትመለከቺ የአፍሪቃ መንግስታት ወንጀል ፈጽሞ ሳይጠየቁ መኖርን ለመዋጋት ዝግጁና ፈቃደኛ ናቸዉ ይላል። ምክንያቱም ቀደም ብዬ እንዳልኩት ያለመከሰስ መብት መኖር ማለት ወንጀል ፈፅሞ በነፃ የመንቀሳቀስ መብት ያጎናፅፋል። ይህ ነዉ እየኛ አቋም፣ ለዚህም ነዉ የአፍሪቃ ኅብረትና የአፍሪቃ መሪዎች በዚህ ላይ ያደረጉትን ማሻሻያ እንዲያጤኑት የምንጠይቀዉ።»
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የICC አካል ባለመሆኑ የክስ አቀራረብ ሂደትና አሠራሩን እንደማያዉቅ ያመለከቱት የድርጅቱ የሕግ አማካሪ ፍርድ ቤቱ ምንም ቢያደርግ በሰብዓዊነት ላይ ወንጀል የሚፈፅሙ መሪዎች ግን ስልጣን ላይ እስካሉ ድረስ አይከሰሱ የሚለዉን አጥብቆ እንደሚቃወም ገልጸዋል። ICC ከኬንያንያ መሪዎች በተጨማሪ በሱዳኑ ፕሬዝደንት ኦማር አልበሽር ላይ የቆረጠዉ የእስር ማዘዣ እስካሁን እልባት ያልተገኘለት መከራከሪያ እንደሆነ ነዉ።
Source: dw

በወያኔ የተቀነባበረ ሴራ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታገትና ለወያኔዎች ተላልፎ መሰጠት ለተቀዋሚዎች የማንቂያ ደውል ነው (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌ)

June4/2014
Gezahegn Abebe

Photo: የግንቦት7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው በየመን መታፈን ሁላችንንም ኢትዮጵያኖችን የወያኔን መሰሪነት አውቀን በቁጣ በወያኔ መንግስት ላይ መነሳት ይገባናል ::የወያኔ መንግስት እሱን በሚቃወሙ ባሉ ሰዎች ላይ ሁሉ እየወሰዳቸው ያለው በግፍ የተሞሉ እርምጃዎች ምን ያህል አንባገነን መንግስት እንደሆነ አመላካች ሲሆን የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታፈንም አመላካች ሲሆን በወያኔ ሴራ የተቀነባበረ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለኝም :: የወያኔ መንግስት ማወቅ ያለበት ነገር ቢኖር በነፃነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ላይ የሆነው ነገር የኢትዮጵያን ሕዝብና ተቃወሚዎችን ይበልጥ የሚያጠነክርና ለትግል ይበልጥኑ እንዲነሳሱ የሚያደርግ መሆኑ ነው:: የእንዳርጋቸው በየመን መታሰር ለተቃዋሚ መሪዎች ሊያነቃቸው ያለ ትልቅ ደውል የተደወለ ነው የሚመስለኝ :: በሀገርም ውስጥ በውጭም ያሉ የተቀዋሚ ድርጅቶች አንድ በመሆንና በመተባበር ልዮነታችንን ወደ ጎን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብንም 
በማስተባበር በጋራ ጠላታችን ላይ በመዝመት ይሄን አረመኔ መንግስት ለማስወገድ በጋራ እንናሳ:: 

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ውድቀት ለወያኔ!!
የግንቦት7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው በየመን መታፈንን ከሰማን ጊዜ ጀምሮ አብዛኛው ሀገር ወዳድና የኢትዮጵያን የነጻነት ቀን ናፋቂ ወገኖችን ያሳሰበና እረፍት የነሳ ጉዳይ እንደሆነ በየቀኑ በየማህበራዊ ድህረ ገጽ ከሚወጡት ነገሮች መረዳት እንችላለን :: በርግጥ ወያኔ በስልጣን በቆየባቸው በእነዚህ ሃያ ሶስት አመታቶች ብዙ የተማሩ ኢትዮጵያን ሙህሮች፣ ብዙ የፖለቲካ ሰዎች በወያኔ የተቀነባበረ ሴራ ለብዙ ነገር ሰላባ ሲሆኑና ህይወታቸውን እስከሚያጡ ድረስ ሆነዋል :: ሰሞኑን ግን በነጻነት ታጋያችን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ በወያኔ የተቀነባበረ ሴራ በየመን የደረሰው እገታና ለነብሰ በላው የወያኔ መንግስት ተላልፎ መሰጠቱ እውን እንደሆነ ስሰማ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ በእኔም ላይ በጣም ከባድ የሆነ የሀዘን መንፈስ የፈጠረብኝ ሲሆን በወያኔ መንግስት ላይ ያለኝን ጥላቻ ይበልጥኑ ከፍ እንዲል ያደረገ ክስተት ሆኖል  እንዳርጋቸው ወደ ትግል ሲገባ እራሱን ለሞት በማዘጋጀት ሊደርስበት ያለውን ማንኛውንም መሰዋትነት ለመክፈልና ሁሉንም መከራ ለመቀበል ዝግጅነቱን በማሳየት እንደሆነ ከሚሰራቸው ስራዎች መረዳት ይቻላል ::በርግጥ እውነተኛ ትግል መስዋህትነትን እንደሚያስከፍል ባውቅም የእኝህ እድሜያቸውን በሙሉ ለነጻነት ሲታገሉ የኖሩ የነጻነት ታጋይ ላይ የደረሰው ነገር ግን በውስጤ ሁለት ነገሮችን ጭሮብኛል ያለፈ ሲሆን አንድን ነገር ግን እንዳውቅ ረድቶኛል:: አንዱ እንዳርጋቸው ቢታሰርና  የፈለገው ነገር በእሱ ላይ ቢደርስ እንኮን  ለወያኔዎች የእግር እሳት የሆኑ እንዳርጋቸው የወለዳቸው ብዙ ሚሊዩኖች የነጻነት ታጋዮች ኢትዮጵያኖች በየስፍራው ተወልደዋልና ደስ ይለኛል::

አሁን ላይ ነገሮች ሁሉ የተቀየሩ ነው የሚመስለው የአቶ እንዳርጋቸው ጉዳይ  የአንድ የፖለቲካ ድርጅት ከመሆን  አልፏል :: በአሁኑ ሰአት አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ እና የአመለካከት ልዩነቱን ወደ ኋላ በመተው እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በሚል ቃል ጉዳዮን በንቃት እየተከታተለው ሲሆን የታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መያዝና በወያኔ እጅ ላይ መውደቅ ለአንዳንድ ሆድ አደር ወያኔዎች ብቻ ፈንጠዝያ የፈጠረና ያስደሰተ ቢመስልም ብዙ ኢትዮጵያ ወገኖችን ግን ከሌላዉ ጊዜ በተለየ መልኩ በእልህና በቁጭት ለትግል እንዲነሳሱ ያደረገ ክስተት እንደሆነ በፊስ ቡክ በውስጥ መልክት ከሚደርሰኝ ደስ የሚልና የሚያበረታታ ጽሁፍ ለመረዳት ችያለው::

ድርጊቱ ለተቃዋሚዎች የማንቂያ ደውል መሆን ይገበዋል ለነጸነት እንታገላለን የሚሉ ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆኑ ለነጻነት እየታገልን ያለን  ኢትዮጵያኖች የወያኔን መሰሪነት አውቀን ከመቼውም ጊዜ በተለየ መልኩ በቁጣ በወያኔ መንግስት ላይ መነሳትና በወያኔ ላይ ያለንን የከረረ ጥላቻ በእንቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ ልንገልጽ ይገባናል ::የወያኔ መንግስት ስልጣኑን በሀይልና በጉልበት ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ  እሱን በሚቃወሙ ባሉ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ ሁሉ  ይኼው አረመኔው የወንበዴ ስብስብ  እየወሰዳቸው ያለው በግፍ የተሞሉ እርምጃዎች ምን ያህል አንባገነን መንግስት እንደሆነ አመላካች ሲሆን የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታፈንም የዚሁ አመላካች ነው::ዛሬ ላይ የአንዳርጋቸው መታፈን በርግጥ የወንበዴዎችን ቡድን ጮቤ እያስረገጣቸው እንደሆነ አስባለው  የወያኔ መንግስት ማወቅ ያለበት ነገር ቢኖር በነፃነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ላይ የሆነው ነገር የኢትዮጵያን ሕዝብና ተቃወሚዎችን ይበልጥ የሚያጠነክርና ለትግል በጥንካሬ እንዲነሳሱ የሚያደርግ መሆኑ ነው:: የእንዳርጋቸው በየመን መታገትና በወያኔዎች የተቀነባበረ ሴራ ለወያኔዎች ተላልፎ መሰጠት የየመንን መንግስት ባደረገው ከህግ ውጭ የሆነ አሳፋሪ ድርጊት ለወደፊት የታሪክ ተወቃሽ የሚያደርገው ቢሆንም የመኖች በሰሩት ስራ ወደ ፊት ተጠያቂ እንደሚሆኑበት ምንም ጥርጥር የለኝም::ዋናው መታወቅ ያለበት ግን ድርጊቱ  ለተቃዋሚ መሪዎች ትልቅ የቤት ስራ የሰጠና ሊያነቃቸው ያለ ደውል የተደወለ ነው የሚመስለኝ ::

በሀገርም ውስጥ በውጭም ያሉ የተቀዋሚ ድርጅቶች በስሜትና፣ በደመነብስ የምንጓዝበት ዘመን ያብቃ፣ እየሰራን ያለውንም ስራ እንመርምር ፣እንንቃ የወያኔን መሰሪ ሴራ ለማክሸፍ አንድ በመሆንና በመተባበር ልዮነታችንን ወደ ጎን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብንም በማስተባበር ነጻነታችንን ህውን ለማድረግ  በጋራ ጠላታችን ላይ በመዝመት ይሄን አረመኔ መንግስት ለማስወገድ በጋራ መነሳት ይጠበቅብናል::

በመጨረሻም ለወያኔዎች የማስተላልፈው መልእክት ቢኖር እውነተኛ ታጋይ ሊታሰር ሊሞትም ይችላል የተጀመረውን ትግል ግን ልታስሩትም ሆነ ልትገሉት ከቱ አትችሉም ::ኢትዮጵያ አንድ እንዳርጋቸው ብቻ ሳይሆን ሚሊዮን እንዳርጋቸው ፈጥራለችና  በከንቱ አትደከሙ:: ወደዳችሁም ጠላችሁም የእንዳርጋቸውን ፈለግ በመከተል  ሁላችንም  የነጻነት ታጋዮች ነን!!!

አቶ አንዳርጋቸው አምላክ ከአንተ ጋር ይሁን

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
gezapower@gmail.com

Thursday, July 3, 2014

በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ… ኤርትራ እና የመን ተፋጠዋል (መልእክተ ዜና – በዳዊት ከበደ ወየሳ)

July3/2014
ኤርትራ የየመንን አየር መንገድ እንደምትዘጋ አሳወቀች (ምክንያቱ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታሰር ነው)
(ኢ.ኤም.ኤፍ) አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰና፣ የመን ውስጥ በየመን የጸጥታ ሃይሎች ታፍኖ መታሰሩ ብሎም አሁን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አለመታወቁ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ላይ ትራንዚት እያደረገ በነበረበት ወቅት ነበር በየመን ታጣቂዎች ታፍኖ የተወሰደው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን በየቦታው ድምጻቸውን ለማሰማት ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው። ከ’ነዚያ ሁሉ ድምጾች ግን ጎልቶ የወጣው በኤርትራ በኩል የተላለፈው መግለጫ ነው። ይህን የኤርትራን መግለጫ መሰረት በማድረግ፤ ሌሎች ምን ማድረግ እንዳለባቸው የራሳችንን ሃሳብ እንሰጣለን።
ኤርትራ ለየመን በላከችው መልዕክት መሰረት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ካልተፈታ፤ በኤርትራ አየር ላይ የሚሄዱትንም ሆነ፤ ምድር ላይ የሚያርፉት የየመን አውሮፕላኖች የሚታገዱ መሆኑን ገልጿል። ይህ ደግሞ እያደገ ለመጣው የየመን አየር መንገድ ትልቅ ኪሳራን የሚያስከትል ነው። ኤርትራ የጀርመኑን ሉፍታንዛ ካገደች ወዲህ፤ የየመን አየር መንገድ ሉፍታንዛን ተክቶ፤ አስመራ ውስጥ በመስራት ላይ ይገኛል። በዚህም መሰረት ወደ አውሮፓ የሚሄዱም ሆኑ የሚመጡ አውሮፕላኖች በየመን በኩል አድርገው ማለፍ ከጀመሩ ሰነባብተዋል። አሁን ኤርትራ የየመን አየር መንገድን እንደሉፍታንዛ የምታገድ ከሆነ፤ የየመን መንግስት የሚያገኘው ከፍተኛ ገቢ ሊቀንስበት ይችላል።
ከዚህ በፊት ባቀረብነው ዘገባ ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእንግሊዝ አገር ዜግነት ያለው እና የእንግሊዝን ፓስፖርት ይዞ የሚንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ስለአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ስናወራ፤ የ እንግሊዝንም መንግስት የጉዳዩ ባለቤት ማድረግ ያስፈልጋል። እንግሊዝ ዜጋዋ በየመን ታስሮ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይላክ በአውሮፓ ዲፕሎማሲያዊ ስራ መስራት ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ እና የመን እስረኛን አሳልፎ የመስጠት ስምምነት ቢኖራቸውም፤ የመን የ እንግሊዝ ዜግነት ያለውን ሰው አሳልፋ እንዳትሰጥ በዛቻ ሳይሆን፤ በህጋዊ መንገድ የመንን መሞገት ያስፈልጋል።
ከ እንግሊዝ በተጨማሪ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችም በጉዳዩ ጣልቃ እንዲገቡ ማድረግ ሌላው ብልሃት ነው። አሜሪካ ከየመን ጋር ያላትን መልካም ግንኙነት በመጠቀም አቶ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲፈታ በየመን የአሜሪካ ኢምባሲ ጥረት እንዲያደርግ ጫና መፍጠር ያስፈልጋል። በአሁኑ ወቅት ግንቦት ሰባት የሚያወጣቸው የማስፈራሪያ መግለጫዎች ድምጸታቸውን በማስተካከል እንደአንድ በሳል የፖለቲካ ድርጅት የሚታይ ዲፕሎማሲያዊ ስራ በመስራት ለውጤት መብቃት አለባቸው። በመሆኑም ከማስፈራሪያ መግለጫዎች ይልቅ፤ ከዲፕሎማሲያዊው ዘመቻ ጎን ለጎን… ህጋዊ ጠበቃ በየመን አዘጋጅቶ፤ ጉዳዩ በኢሚግሬሽን እና በዋናው ፍርድ ቤት እንዲታይ በማድረግ፤ ቢያንስ አቶ አንዳርጋቸው ወደ ኢትዮጵያ እንዳይላክ ጊዜ መግዛት ይቻላል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእንግሊዝ ዜግነት ያለው እንደመሆኑ መጠን ዲፕሎማሲያዊው ዘመቻ በእንግሊዛውያን ጭምር እንዲሰራ፤ ቢቢሲን ጨምሮ ሌሎች የአገሪቱ ሚዲያዎች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ ማድረግ ተገቢ ነው። የምናወጣቸውም መግለጫዎች በአማርኛ ሳይሆን ሁሉም አገራት በሚረዱት እንግሊዘኛ ቋንቋ ሊሆን ይገባዋል። ከዚያ ውጪ ግን “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባስቸኳይ ካልተፈታ በኢትዮጵያ እና በየመን ባለስልጣናት ላይ እርምጃ እንወስዳለን” አይነት መግለጫዎች፤ ወያኔ ኢህአዴግ “ግንቦት ሰባት የአሸባሪዎች ድርጅት ነው” የሚለውን አባባል ከማጠናከር ውጪ ብዙም ፋይዳ ላይሰጥ ይችላል።
ይህ ብቻም አይደለም። በማህበራዊ ድረ ገጾች እና ሌሎች ሚዲያዎች ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከዚህ በፊት ያደረጓቸው ንግግሮች እየተለጠፉ መሆኑን ታዝበናል። እንዲህ አይነቶቹ… ቀደም ሲል የተደረጉ ንግግሮችን አሁን ለእይታ ማቅረቡ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እስሩ እንዲጸናባቸው እንጂ፤ እንዲፈቱ ስለማይረዳቸው፤ በዚህ ረገድ ሌላ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በድጋሚ ለማሳሰብ ያህል… ግንቦት ሰባትም የማስፈራሪያ መግለጫዎችን ከማውጣት ይልቅ፤ በሌሎች ዜጎች እየተደረጉ ያለውን ጥረት ማስተባበር እና ዲፕሎማሲያዊ ይዘት እንዲኖራቸው ማድረግ አለበት። ኤርትራ ያደረገችውን ውሳኔ በማድነቅ፤ ሌሎች አገሮችም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ማበረታታት ከግንቦት ሰባት አመራሮች የሚጠበቅ ነው።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሌሉበት ሞት የተፈረደባቸው መሆኑን፣ ንብረታቸው በወያኔ ኢህአዴግ መወረሱን፣ ወላጅ አባታቸው እና ቤተሰባቸው በእስር መንገላታቱን አጉልቶ በማውጣት የወያኔ ኢህአዴግን አስከፊ ገጽታ ማሳየት ይቻላል። አሁንም የየመን መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ወደ ኢትዮጵያ ብትመልስ በወያኔ ኢህአዴግ ሊደርስባቸው የሚችለውን የግድያ ወንጀል ማሳወቅ እንጂ፤ “አቶ አንዳርጋቸው ካልተፈታ ወዮላቹህ!” የሚለው አይነት ማስፈራሪያ ህሊና ለሌላቸው የሁለቱም አገራት አምባገነን መሪዎች ላይሰራ ይችላል። ህዝብ እና አገር የሚመሩት በእውቀት እና በጥበብ ጭምር በመሆኑ፤ ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ በመከተል… ነገር ግን በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ አቶ አንዳርጋቸውን የማስፈታቱን ሂደት እንቀጥል – የዛሬው ዜና መልእክታችን ነው።

የአማራ ጉዳይ፤ አለ? ወይስ የለም?

July 2/2014
መስፍን ወልደ ማርያም
ግንቦት 2006
mesfinተናግሬ ነበር ማለት ዋጋ የሌለው የወሬ ማጌጫ ነው፤ እስቲ ፍቀዱልኝና ልጠቀምበት፤ ከወያኔ ዋና ምሁር፣ ከመለስ ጋር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ፊት-ለፊት በቴሌቪዥን በተገኛኘን ጊዜ ‹‹አማራ የሚባል ጎሣ የለም፡›› በማለቴ መለስ ዜናዊና ጭፍሮቹ ብቻ ሳይሆኑ ‹‹አማራ-ነን ባዮች›› በቃልም፣ በጽሑፍም፣ በቴሌፎንም ልክ-ልኬን እየነገሩኝ አንጀታቸውን ቅቤ አጠጥተው ነበር፤ ‹አንዲት ሴት ደውለው እብድና ዘበናይ የልቡን ይናገራል፤› ብለውኛል፤ አንድ ሰው የተናገረው ስሕተት ከሆነ ስሕተቱን በማስረጃ ማጋለጥና የራስን ሀሳብ በማስረጃ መትከል ነው፤ እውቀት የሚዳብረው፣ ሰዎች የሚማሩትና በእድገት ጎዳና የሚጓዙት በተጨባጭ ማስረጃ መነጋገር ሲችሉ ብቻ ነው፤ እኔ አማራ የለም፣ ዜሮ (0) ነው፤ አልሁ፤ አማራ አለ፣ አንድ አለ፤ (1) ነው ያለ ሰው የአንድን ዋጋ ማሳየት አለበት፤ አማራ የለም የሚል ዜሮ ነው ማለቱ ስለሆነ ከሌለ ነገር ምንም አይጠብቅም፤ ከአለ ነገር (ከ1) ብዙ ነገሮችን መጠበቅ ይቻላል።
ዱሮ በልጅነታችን ጭራቅ የሚሉት ማስፈራሪያ ነበረ፤ በአለፉት ሃያ ሦስት ዓመታት አማራ የሚባል ጭራቅ ማስፈራሪያ፣ የኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ ቋት እንደሆነ ሲነገር ቆየ፤ መለስ ዜናዊም እየደጋገመ ‹አከርካሪቱን ሰብረን ሁለተኛ እንዳያንሰራራ› እናደርገዋለን እያለ እንደዛተ የተሰበረውን አከርካሪት ሳያይ ሞተ፤ በሕይወትም እያለ ቢሆን መለስ ዜናዊ አከርካሪቱን እሰብረዋለሁ የሚለውን አማራ የተባለ ስያሜ እንደሹመት ለነበረከት ስምዖንና ለነተፈራ ዋልዋ ይሰጥ ነበር፤ የክብር ጎሣ እንበለው! ራሱም ቢሆን ከዚህ የክብር ጎሣ ቤተሰብነት አልራቀም፤ አከርካሪቱ እንኳን ሊሰበር አልተገኘም!
ስንት ሺህ ሰዎች አማራ ናችሁ እየተባሉ ከስንት ስፍራ ተፈናቀሉ? አማራ ማለት እነዚሁ የተፈናቀሉት፣ በየጫካው የተገደሉትና የተሰደዱት ብቻ ናቸው? ሌሎችም ካሉ የጎሣ ዝምድና ሳይስባቸውና ከተፈናቀሉት ጋር አብሮ ለመቆም ለምን አልቻሉም? በጋምቤላ በደረገው ጭፍጨፋ የተጨፈጨፉት ጎሣዎች በጣም ትንሽም ቢሆኑ ከካናዳ እስከ አውስትራልያ ዓለምን ያዳራሱት የጎሣ ዝምድና ስሜት ለምን ለእነዚህ አማራ ለተባሉት ተፈናቃዮች አልሠራም? እንግዲህ አማራ እየተባሉ የሚፈናቀሉት፣ የሚገደሉትና የሚሰቃዩት ዘመድና ደጋፊ የሌላቸው ሰዎች ናቸው ማለት ነው፤ ሰውነታቸውም ቢሆን በሕግ ያልተረጋገጠላቸው፣ ሕግ የማይመክትላቸው ናቸው ማለት ነው፤ ይህንን ክርክር ከገፋንበት ዜግነታቸውንም የምንጠራጠርበት ደረጃ ላይ እንደርሳለን፤ ደርግ በጎሣ ላይ የተመሠረተ የውትድርና ሥልጠና ያደረገ ይመስለኛልና በዚህ ጉዳይ ላይ የደርግ ባለሥልጣኖች፣ በተለይም ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አንድ ቀን የሚነግሩን ይኖራል የሚል ግምት አለኝ።
አጥቂና ጨቋኝ ነፍጠኛ የሚባለው ሕዝብ ሲጠቃና ሲበደል ከኡኡታ በቀር ድምጹ የማይሰማው ትርጉሙ የህልውና ነው? ወይስ የወኔ? በሌላ አነጋገር አማራ የሚባል ጎሣ በእርግጥ አለ? ወይስ የለም? ከአለ የሚወራለትን ነፍጠኛነትና ወኔ ምን ዓይነት ብል በላው? ይህ ክርክር ከሃያ ሦስት ዓመታት በፊት አማራ የሚባል ጎሣ አለ ብለው የሞገቱኝን ሰዎች (የሞተውን መለስንና ያሉትን ጓደኞቹን ጭምር)፣ የመላው አማራ ይባል የነበረውን ድርጅት፣ ብአዴን የሚባለውን የወያኔ ድርጅት መሠረተ-አልባነት ለማሳየት እንጂ የሌለውንና ከዚህ በፊት ተቆስቁሶ ያልተነሣውን ጎሣ ለማነሣሣት አይደለም፤ የሌለ ነገር ቢቆሰቁሱት አይነሣም,
በአለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ውስጥ እነዚህን አማራ እየተባሉ የሚፈናቀሉትን፣ የሚገደሉትን፣ የሚሰቃዩትን ሁሉ ‹‹ሰዎች›› ብናደርጋቸውና ሰዎች ብንላቸውስ? ሰው መሆን የተፈጥሮ ነው፤ ልለውጥህ ቢሉት አይለወጥም፤ ሰው ሆኖ ተወልዶ ሰው ሆኖ ይሞታል፤ ሰው መሆናቸውን ወንጀል የማድረግ ዝንባሌ የሚኖረው ሰይጣን ብቻ ይመስለኛል።
ወይም አማራ የክርስቲያን ሃይማኖትን ተከታይነት የሚገልጽ ስያሜ አድርገን ብንወስደው የእነዚህ ሰዎች መፈናቀል፣ መገደል፣ መሰቃየትና መሰደድ ክርስቲያኖች እንዲጠፉ ለማድረግ ነው? ይህ ከሆነ አንድ ጸረ-ክርስቲያን ኃይል አለ ማለት ይመስለኛል፤ ይህ መደምደሚያ ችግር አለበት፤ ፓትርያርክና ሊቃነ ጳጳሳት ሰይሞ ጸረ-ክርስቲያን ተግባር ነጋ-ጠባ ማከሄድ አታላዩንና ተታላዩን ለመለየት ያስቸግራል።
እነዚህን አማራ እየተባሉ የሚፈናቀሉትን ‹‹ኢትዮጵያውያን›› ብንላቸውስ? ኢትዮጵያዊነት ታሪካዊ ዜግነት ነው፤ ዜግነት አንድ ሕዝብ በደሙና በአጥንቱ የሚገነባው ነው፤ ዜግነት የሕግ ከለላ አለው፤ ይህንን የሕግ ከላላ ተነፍገው በኢትዮጵያ ምድር ከያለበት የሚፈናቀሉት፣ የሚገደሉት፣ የሚሰቃዩትና የሚሰደዱት ኢትዮጵያዊ ዜግነትን ለማጥፋት የተደራጀ ኃይል አለ ማለት ነው።
አንግዲህ አማራ የሚባሉት ነፍጥ የሌላቸው ነፍጠኞች በምድረ ኢትዮጵያ ሰዎችም ሆነው፣ ክርስቲያኖችም ሆነው፣ ኢትዮጵያውያንም ሆነው መኖር አይፈቀድላቸውም ማለት ነው ወደሚል መደምደሚያ በግድ መድረሳችን ነው፤ ያዋጣል ወይ?
ግራም ነፈሰ ቀኝ አማራ የሚባል ጎሣ እንደሌላ በስያሜው ላይ የሚደርስበትን ጥቃት ለመመከት እንኳን ባለመቻሉ አስመስክሯል፤ በሕይወት ላለ በህልውና ላይ የሚደርስበትን ጥቃት መመከትና መከላከል የተፈጥሮ ነው፤ ይህ ሳይሆን ሲቀር ህልውና የለም።

Wednesday, July 2, 2014

ሎሚ መጽሄት ከአብርሃ ደስታ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ

July2/2014
“ሕወሓት በ2007 ምርጫ እንደማይመረጥ አውቋል”
“ዓረናን ለማፍረስ ቢሞከርም አልተሳካም”
“ዓረና ሕወሓትን ያስደነገጠ እንቅስቃሴ አድርጓል”
===============================
አቶ አብረሃ ደስታ (የዓረና የፖሊት ቢሮ አባል)
የአረና ፖሊት ቢሮ አባል የሆነው አቶ አብረሃ ደስታ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሎሚ መጽሔት ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ቶማስ አያሌው ጋር እንደሚከተለው አውግቷል፡፡
ሎሚ መጽሄት የፊት ገጽ
ሎሚ መጽሄት የፊት ገጽ
ሎሚ፡- በአሁኑ ወቅት የአረና እንቅስቃሴ ምን ይመስላል?
አብረሃ፡- ዓረና ሦስተኛ መደበኛ ጉባኤውን ካካሄደ በኋላ ከህዝብ ጋር ለመገናኘት፣ ህዝብን ለመሰብሰብ፣ ለማስተማርና ለማደራጀት እንዲሁም ለነፃነቱ እንዲነሳ ለመቀስቀስ ባቀደው መሰረት በተሳካ ሁኔታ ተግባሩን እያከናወነ ይገኛል። እስካሁን ድረስ በአስራ አምስት ከተሞች ህዝባዊ ስብሰባ ጠርተናል። በአስራ አንዱ የተሳካ ስብሰባ ሲደረግ በሽረ እንዳስላሴ፣ ዓዲግራት፣ ሑመራና ሐውዜን ግን በካድሬዎች ሴራ ተስተጓጉሏል። በሰባ አንድ የትግራይ ከተሞችና የገጠር መንደሮች የተሳካ ቅሰቀሳ ተደርጓል። የዓረናን አማራጭ ፖሊሲ የያዘ በራሪ ወረቀት ታድሏል። ዓረና ከምንም ግዜ በላይ በጥሩ ሁኔታ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፤ ተስፋም ተጥሎበታል። የህወሓት አባላትም ዓረናን ወደ መደገፍ የሚሸጋገሩበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። ባጠቃላይ ዓረና ያደረገው እንቅስቃሴና እያገኘ ያለው የህዝብ ድጋፍ ህወሓትን አስደንግጦታል።
ሎሚ፡- በፓርቲያችሁ ውስጥ ልዩነት ስለመኖሩ ይነገራል፤ ካለስ ምክንያቱ ምንድነው?
አብረሃ፡- በዓረና ውስጥ ልዩነት አልተፈጠረም። ቅሬታ የሚያነሱ ግለሰቦች ግን አሉ። ቅሬታውም ከዓረና ዕቅድና ህወሓት በዓረና አባላት ላይ እያሳረፈው ካለው ጫና ይመነጫል። ዓረና ሰፊ እንቅስቃሴ ለማድረግ ሲወስን ገና ከጅምሩ ያልተዋጠለት አንድ አባል ነበር። ዕቅዱ የአብዛኛውን ድምፅ አገኘና ፀደቀ። የዓረና አመራር አባላት ወደ ህዝብ ወርደው መንቀሳቀስ እንዳለባቸው ተስማማን። በዚሁ መሰረት ሁሉም የማእከላዊ ኮሚቴና የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት የየራሳቸው የስራ ድርሻ ተሰጣቸው።
ሁሉም የዓረና አመራር አባላት በተሰጣቸው የስራ መስክ ሲሰማሩ ሁለት አመራሮች ግን የተሰጣቸውን የስራ ድርሻ ሳይቀበሉ ቀሩ። ከሃያ አምስት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ወደ ህዝብ ወርዶ የፓርቲ ስራ ለመስራት ፍቃደኛ ሳይሆን ሲቀር ከሰባቱ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትም አንድ አባል ላለመስራት ወሰነ። ስለዚህ ከሰላሳ ሁለት ሰዎች ሁለት ብቻ የፓርቲ ስራ ለመስራት ፍቃደኞች ሳይሆኑ ቀሩ። ሰላሳዎቹ ግን በየተመደቡበት የስራ ዘርፍ ተሰማርተው እነሆ ህወሓትን ያንቀጠቀጠ ዉጤት አስመዝግበዋል።
በዓረና ፓርቲ እንቅስቃሴ ለመሳተፍና የበኩሉን ለመወጣት ፍቃደኛ ያልሆነ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ሺሻይ አዘናው ሲሆን፤ የቁጥጥር ኮሚሽኑ አባል ደግሞ ገብሩ ሳሙኤል ነው። እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ከዓረና ጉባኤ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በማንኛውም የፓርቲ እንቅስቃሴ፣ ስልጠና፣ ስብሰባ ወይ የፓርቲ ስራ አልተሳተፉም። እንደ አባላት የፓርቲ ወርሃዊ ክፍያም አላደረጉም። በዚህ ምክንያት በጉባኤ ተመርጠው ሓላፊነት ተሸክመው የተሰጣቸውን ሓላፊነት በአግባቡ ባለመወጣታቸው በማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ሊገመገሙና ለያዙት አፍራሽ ተልእኮ ሊከሰሱ ዕቅድ ተይዟል።
ሌላ ለችግሩ ምንጭ ነው ብለን የምንወስደው የህወሓትን ጫና መቋቋምህ አለመቻል ነው። ህወሓት በዓረና እንቅስቃሴ በመሸበሩ ምክንያት ዓረናን ለማዳከም፣ ከህዝብ ጋር እንዳይገናኝ ለማድረግ እንዲሁም ለማፍረስ ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው። የህወሓት ዋነኛ ጠላት ዓረና ሆኗል። በዚህ ምክንያት በመከላከያ ደህንነት አማካኝነት በዓረና አባላት ላይ ጫና ለመፍጠር እያንዳንዱ የዓረና አባል ተጠንቷል። ጥናቱ ምን ይፈልጋል? በምን ሊደለል ይችላል? ይፈራል ወይ? ቢታሰር ነው የሚሻለው ወይስ ቢመከር? ወይስ ቢደበደብ? ወዘተ በሚሉ ነጥቦች ላይ ያተኩራል።
እንደ ውጤቱም ብዙ የዓረና አባላት አባልነታቸውን ከለቀቁ ገንዘብና መሬት እንደሚሰጣቸው፣ ስልጣን እንደሚሰጣቸው ወዘተ ተነግሯቸዋል። ሌሎችም አባልነታቸውን ካላቆሙ እንደሚደበደቡ፣ እንደሚታሰሩ፣ እንደሚገረፉ፣ ከስራ እንደሚባረሩ፣ ንብረታቸውን እንደሚነጠቁ፣ እንደሚገለሉ፣ እንደሚገደሉ ተነግሯቸዋል። በተነገራቸው መሰረት ጥቅም ያገኙ አሉ። ከስራቸው የተባረሩ አሉ። የታሰሩና የተገረፉ አሉ። ሃብት ንብረታቸውን የተነጠቁ አሉ። ሲቀሰቅሱ በድንጋይ የተወገሩ አሉ። አሁን ብዙ የዓረና አባላት በእስር ላይ ይገኛሉ፤ ቃላቸውን በመጠበቃቸው እና በህወሓት ሊደለሉ ባለመቻላቸው።
ስለዚህ ጥቂቶች ህወሓት በሚፈጥረው ጫና ሲደናገጡ ብዙዎች ግን በቆራጥነት እየታገሉ ነው። አቶ ሺሻይ አዘናውና ገብሩ ሳሙኤል በዓረና እንቅስቃሴ ለመሳተፍ ያልፈለጉበት ምክንያት ምናልባት በዓዲግራት በድንጋይ ስንወገር ስላዩ ይሆናል። ፍርሓትም አንድ ምክንያት ሊሆን ይችላል። በዓረና መርህ መሰረት አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል ግንባር ቀደም ሁኖ መሳተፍ ይጠበቅበታል። መፍራት የለበትም። በጥቅም ሊደለል አይገባም። ከህወሓት ጎን ተሰልፎ ዓረናን ለማፍረስ ጥረት ማድረግ የለበትም።
በፓርቲ ውስጥ ችግር ካለ በፓርቲ ስብሰባ ይገመገማል፤ ይጣራል፤ ይፈታል። በዓረና ፓርቲ የተፈጠረው የነ ሺሻይና ገብሩ በስራ ምክንያት አለመገኘት ችግር በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እንዲነሳ ተወስኗል። ማንኛውም የውስጥ ችግር በውስጠ ደንብ ነው የሚታየው። ዓረና የነኚህ ሁለት የአመራር አባላት እምቢተኝነት በማዕከላዊ ስብሰባ አጀንዳ እንደሚሆን ሲነገራቸው ግን “ጉባኤ መጥራት እንፈልጋለን” የሚል ደብዳቤ ለዓረና ፅህፈት ቤት አስገቡ፡፡ ራሳቸው የፈጠሩትን ችግር ላማድበስበስ በፓርቲው ውስጥ ችግር እንዳለ አስመስለው አቀረቡ። “ጉባኤ እንጠራለን” የሚል ጥያቄያቸውም በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እንደሚታይ ተነገራቸው።
እነሱ ደብዳቤ ሲያስገቡ ህወሓትም ዓረና እየፈረሰ ነው የሚል ወሬ መንዛት ጀመረ። በተመሳሳይ ግዜ አቶ ሺሻይ አዘናው፣ አቶ ገብሩ ሳሙኤልና አቶ አስገደ ገብረስላሴ “ፓርቲው እየፈረሰ ነው፣ አንባገነንነት እየሰፈነ ነው፣ የዓረና አባላት እየወጡ ነው፣ አስቸኳይ ጉባኤ እንድንጠራ ይፈቀድልን” የሚል መልእክት ያለው ቅሬታ ለዓረና ፅህፈት ቤት አስገቡ። “ጉዳያችሁን በስብሰባ እናየዋለን። እስከዛ ድረስ ግን እንደ አባላት በፓርቲው ስራ ተሳተፉ፣ መብታችሁን ለመጠየቅ ግዴታችሁን ተወጡ” የሚል መልስ ተሰጣቸው። አቶ አስገደ በፓርቲው ስራ ሲሳተፍ አቶ ሺሻይና አቶ ገብሩ ግን አሻፈረን አሉ።
ቀጥለውም ዓረና በተለያዩ ከተሞች ህዝባዊ ስብሰባዎችና ቅስቀሳዎች በሚያደርግበት ግዜ፣ የዓረና አመራር አባላት በስራ በተጠመዱበት ግዜ በስራ ከመሰማራት ይልቅ “ፓርቲው እየፈረሰ ነው፣ አስቸኳይ ጉባኤ እንጠራለን” የሚል ፅሑፍ ድጋሚ አስገቡ። ህወሓትም ተመሳሳይ አጀንዳ ፈጠረ። ዓረና እየፈረሰ ነው እያለ ፕሮፓጋንዳ መንዛት ጀመረ። ጉዳዩ ሌላ ተልእኮ እንዳይኖረው በመጠርጠር መቐለ የሚገኙ የዓረና የስራ አስፈፃሚ አባላት ተሰብስበው “የአስቸኳይ ጉባኤ” ጥያቄ ለመመለስ ያህል ጥያቄው ፕሮሲጀሩን (Procedure) ጠብቆ መምጣት እንዳለበት ወሰኑ።
በዚሁ መሰረት ሦስቱ ቅሬታ አቅራቢዎች የዓረናን ህገ ደንብ አክብረው ህገ-ደንቡ በሚፈቅደው መሰረት ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ ተነገራቸው። አቶ አስገደ ገብረስላሴ ተራ አባል እንደመሆኑ መጠን ማንኛውም ጥያቄ ለመሰረታዊ አደረጃጀት ያቀርባል። መሰረታዊ አደረጃጀቱ ጥያቄውን መርምሮ ከተቀበለው ለክልል ፅህፈት ቤት ያስገባል። ስለዚህ አስገደ በዓረና ህገ-ደንብ መሰረት ጥያቄውን በመሰረታዊ አደረጃጀቱ በኩል እንዲያስገባ ተጠየቀ፤ ህገ ደንቡ የሚፈቅደው ይሄ ነውና። አስገደ ያለበት መሰረታዊ አደረጃጀት አባላትና ሐላፊዎች ግን የአስገደን ጥያቄ እንደማያውቁ፣ ቅሬታም እንዳላስገባላቸው መሰከሩ። ስለዚህ አስገደ ለሚመለከታቸው አካላት ቅሬታውን አለማቅረቡ ታወቀ። በህገ-ደንቡ መሰረት አንድ ተራ አባል መሰረታዊ አደረጃጀትን ሳያሳውቅ ዘው ብሎ ወደ ክልል ፅሕፈት ቤት አያስገባም። አንድ ተራ አባል አስቸኳይ ጉባኤ ለመጥራት የመሰረታዊ አደረጃጀቱ አባላት ሊቀበሉትና ሊያፀድቁት ይገባል።
አቶ ሺሻይ አዘናው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆኑ ጥያቄውን ለማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲያቀርብ ተነገረው። የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል “አስቸኳይ ጉባኤ” ለመጥራት ከማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ቢያንስ አንድ ሦስተኛ ሊቀበሉት ይገባል። ከሃያ አምስቱ የዓረና ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሺሻይ አዘናው አንድ ነው። አንድ የማእከላዊ ኮሚቴ አባል አስቸኳይ ጉባኤ የመጥራት ስልጣን የለውም፤ በህገ-ደንቡ መሰረት። የሺሻይ ጥያቄ በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እንደሚታይ ግን ተነግሮታል። የዓረና ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በሁለት ሳምንታት ግዜ ውስጥ እንደሚካሄድም ተነግሮታል። የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጥያቄ በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ይፈታል።
ሦስተኛው ቅሬታ አቅራቢ አቶ ገብሩ ሳሙኤል ደግሞ የቁጥጥር ኮሚሽን አባል በመሆኑ ቅሬታው ይሁን የአስቸኳይ ጉባኤ ጥያቄ ለሚሰራበት የቁጥጥር ኮሚቴ ማቅረብ ይጠበቅበታል። ጥያቄው ለኮሚሽኑ ካቀረበ በኋላ የኮሚሽኑ አንድ አራተኛ አባላት ከተቀበሉት ጥያቄው ተቀባይነት ይኖረዋል። አቶ ገብሩ ሳሙኤል ግን ለቁጥጥር ኮሚሽን ያቀረበው ጥያቄ የለም። በመሆኑም የገብሩ ጥያቄ ወደ ቁጥጥር ኮሚሽን መሆን እንዳለበት ተነግሮታል።
የሦስቱም ጥያቄዎች በዓረና ህገ-ደንብ መሰረት procedure ጠብቀው መምጣት እንዳለባቸው ሲነገራቸው አቶ ሺሻይና አቶ ገብሩ “ጥያቄያችን ታፍኗል” ብለው የዓረናን ስም የሚያጠፋ ፅሑፍ በተኑ። “በፓርቲው ህገደንብ መሰረት አስገደ ወደ መሰረታዊ አደራጃጀትህ አስገባ፣ ሺሻይ ወደ ማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አቅርበው፣ ገብሩ ሳሙኤል ደግሞ ወደ ቁጥጥር ኮሚሽን አቅርብ። ከዛ ጥያቄያቹ መስመራቸውን ጠብቀው ይፈታሉ” የሚል መልስ ሲሰጣቸው “ታፈንን” አሉ። በፓርቲው ብዙ ችግሮች እንዳሉ ተናገሩ። “ፕሮሲጀር (procedure) ተከተሉ” ማለት ጥያቄን ማፈን አልነበረም። ግን አደረጉት። ፓርቲ የፈረሰ አስመስለው ደጋፊዎቻችንን ለማደናገር ሞከሩ። ይህ ተግባር ህወሓት ከሚሰራው ጋር ይመሳሰላል። የዓረና ፓርቲ ችግሮች ያሏቸውን ዘረዘሩ። ግን እንዴት ማወቅ ቻሉ? ከፓርቲው እንቅስቃሴ ከተሰናበቱ ኮ ዘጠኝ ወራት አስቆጥረዋል። በምናደርገው ስብሰባም ይሁን ስልጠና ወይ ሌላ እንቅስቃሴ አይሳተፉምኮ። የፓርቲውን ውስጣዊ አሰራር ለመገምገም ኮ በፓርቲው እንቅስቃሴ መሳተፍ ግድ ይላል።
እንግዲህ ጥያቄያችሁን በአግባቡ አቅርቡ ስለተባሉ ነው “ታፍነናል” ብለው ፀረ ዓረና እንቅስቃሴ ያደረጉት። ዓረና ቢሆኑ ኑሮ ዓረናን ለማስተካከል ጥረት ባደረጉ ነበር። “በአስቸኳይ ጉባኤ ጥሪ” ስም ባለፈውም ዓረናን ለማፍረስ ተሞክሮ እንደነበር አውቃለሁ። አልተሳካም፤ አሁንም አይሳካም። ጉዳያቸው ግን በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ይታያል።
ሎሚ፡- የፓርቲያችሁ ፀሐፊ ፓርቲውን ለቅቋል፤ ምክንያቱ ምንድነው?
አብረሃ፡- አዎ! የፓርቲያችን የአደረጃጀት ጉዳዮች ሓላፊ የነበረው አቶ ስልጣኑ ሕሸ ከፓርቲው ለመልቀቅ ደብዳቤ አስገብቷል። እንደ ዓረና መርህ ማንኛውም ሰው ፖሊሲያችንና የፖለቲካ አቅጣጫችን እስከተስማማው ድረስ ወደ ፓርቲያችን የመግባት መብት አለው። በፈለገው ግዜም ከፓርቲያችን መልቀቅ ይችላል። መብቱ ነው። ያለ ፍላጎቱ ተጨቁኖ የሚኖር አባል መኖር የለበትም። አቶ ስልጣኑም መልቀቅ ፈልጓል። ለመልቀቅ ያቀረበው ምክንያት አሳማኝ ሆኖ አላገኘሁትም። ግን መልቀቅ መፈለጉ በራሱ በቂ ምክንያት ነው። ፖለቲካ የህሊና ስራ ነውና።
አቶ ስልጣኑ ሕሸ በመልቀቁ ምክንያት ዓረና ብዙ ነገር አጥቷል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም አቶ ስልጣኑ ጠንካራና ጀግና ከሚባሉ የዓረና መሪዎች አንዱ ነበረ። ዓረናን ይመራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ወጣት ነበር። የስልጣኑን ጥንካሬ ግምት ውስጥ በማስገባት ያቀረበው የመልቀቅያ ምክንያት አሳማኝ ሊሆን አይችልም። በፓርቲው ስብሰባ ወይ ግምገማ ማቅረብ ይችል ነበር። እንደግፈው ነበር። የምናምነውና የምንኮራበት ጓዳችን ነበርና ነው። ስለዚህ መውጣት ፈልጓል። ምክንያቱን በግልፅ ስላልነገረን የመውጣት ፍላጎቱን መከልከል አልፈለግንም፤ አንችልምም። ግን እስካሁን ብዙ ነገር ሰርቷል፤ ብዙ አባል አፍርቷል፤ ብዙ አስተዋፅዖ አበርክቷል። የፓርቲውን ግዴታ በአግባቡ የተወጣ ጀግና ነው። ላበረከተው አስተዋፅዖ የምስጋና ደብዳቤም ያስፈልገዋል።
ሎሚ፡- አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች አረና ውስጥ የሕወሓት ሰርጎ ገቦች ገብተዋል ይላሉ፤
አብረሃ፡- አዎ! ዓረና ውስጥ የህወሓት አባላት ሳይገቡ አልቀረም። የሚናገሩትና የሚሰሩት ዓረናን ለማፍረስ ያለመ ይመስላል። ግን አጣርተናል ብለን ነው የምናምነው። ህወሓት ሆነው ወደ ዓረና የገቡ፣ ዓረና ሆነው በጥቅም ተደልለው ለህወሓት የሚሰልሉ ቅጥረኞችም ይኖራሉ። መረጃው ቶሎ ይደርሰናል። አፋጣኝ መፍትሄ እናደርጋለን። ስለዚህ የህወሓት በዓረና መግባት ብዙ ችግር አይፈጥርብንም። ችግር እየፈጠረብን ያለው ጠንካራ አባሎቻችን መታሰራቸው ነው። ጉዳት እየደረሰባቸው ነው። አሁን ያለውን የህዝብ መነሳሳት በአግባቡ ለመምራት ብዙ ቋሚ ሰራተኞች መቅጠር ይጠበቅብናል።
ሎሚ፡- ከአንድነት ጋር ልትዋሃዱ ነው የሚባለው ነገር ምን ያህል እውነት ነው?
አብረሃ፡- ለመዋሃድ ያሰብነው ከመድረክ አባላት ጋር ነው። በመድረክ ውስጥ ደግሞ አንድነት፣ ኦፌኮና ደቡብ ሕብረት ኢሦዴፓ እንዲሁም ሲአን አሉ። ስለዚህ ከተቻለ እነዚህ ፓርቲዎች በሙሉ ከዓረና ጋር ቢወሃዱ ምርጫችን ነው። ምክንያቱም አንድ ጠንካራ ሀገራዊ ፓርቲ መመስረት ነው የምንፈልገው። ይህ ካልተቻለ ግን ከኦፌኮ ወይ ከአንድነት ወይ ከደቡብ ሕብረት ወይ ከሲአን ጋር እንወሃዳለን። አንድነቶች ከመኢአድ ጋር ለመወሃድ ጥረት እያደረጉ ነው። ውህደቱ ከተሳካ ጥሩ ነው። ዓረናም ተመሳሳይ አጀንዳ ከሚያራምዱ ፓርቲዎች ጋር የመወሃድ ዕቅዱ ይተገብራል። ባጭሩ ባሁኑ ግዜ አንድነት ከዓረና ሳይሆን ከመኢአድ ጋር ለመዋሃድ ነው ጥረት እያደረገ ያለው። ዓረናም የአንድነትና የመኢአድ ውህደት ይደግፋል። ምክንያቱም ዓረና ጠንካራ ውሁድ ሀገራዊ የተቃውሞ ፓርቲ የማየት ራዕይ አለው።
ሎሚ፡- ፓርቲያችሁ በስፋት በሚንቀሳቀስበት ትግራይ ያለው ተቀባይነት ምን ይመስላል?
አብረሃ፡- ዓረና በትግራይ ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ነው። ሰፊ ድጋፍ እንዳለውም አረጋግጠናል። የትግራይ ህዝብ ሙሉ በሙሉ ለውጥ እንደሚፈልግ ለማወቅ ችለናል። ህወሓትም ይህንን ጉዳይ በሚገባ ተረድቶታል። እናም ብዙ እንቅፋቶች ለመፍጠር እየሞከረ ነው። “ዓረና አያድናችሁም፣ ከፈለግኩ አስራቸዋለሁ ከፈለግኩ እለቃችዋለሁ” እያለ ህዝብን እያስፈራራ ነው። “ዓረና እየፈረሰ ነው። ዓረና አስፓልት መንገድ፣ ባቡር ሃዲድ፣ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤት ወዘተ ሰርቶ አያውቅም” እያሉ ህዝብን እያጭበረበረ ይገኛል። ስም የማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብናል። የህወሓት የደህንነት ሰዎች ራሳቸው አሳስረው ራሳቸው “እናስፈታችኋለን” እያሉ ህዝብን እያስደነገጡ ነው። ፍትሕ ግን ሊሰጡ አልቻሉም።
ሎሚ፡- አሁን ላይ ሆነህ ቀጣዩን የ2007 ምርጫ እንዴት ትመለከተዋለህ?
አብረሃ፡- የ2007 ምርጫ ከባድ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ህወሓት ምንም የህዝብ ድጋፍ እንደሌለው ከወዲሁ አረጋግጧል። ስለዚህ ፍትሓዊ ምርጫ ከተደረገ፣ የህዝብ ድምፅ ከተከበረ መሸነፉ አይቀርም። ህወሓት ግን ሽንፈቱን ለመቀበል ዝግጁ አይሆንም፤ ስልጣን መልቀቅ አይፈልግምና። ስለዚህ ጥሩ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላትን ማሰሩ አይቀርም። የምርጫ ታዛቢዎችን መከልከሉ አይቀርም። የምርጫ ኮሮጆውን በጠመንጃ መጠበቁ አይቀርም። ህዝቡ ግን ለውጥ ይፈልጋል። እኛ ለለውጥ ቀስቅሰን፣ አነሳስተን የህዝብ ድምፅ ሲታፈን ህዝቡ ምን ሊያደርግ እንደሚችል ስለማይታወቅ ህወሓት ተጨናንቋል። ስለዚህ የህወሓት ጭንቀት ላልመረጥ እችላለሁ የሚል አይደለም፤ እንደማይመረጥማ አውቋል። የህወሓት ጭንቀት ህዝቡን እንዴት መቆጣጠር ይቻላል የሚል ነው።
ዓረና እስከ 2007 ምርጫ አሁን ባለው መንፈስና ጥንካሬ መንቀሳቀስ ከቻለ ግን አብዛኞቹ የህወሓት ካድሬዎችም ጭምር የማሳመን ከፍተኛ ዕድል አለው። የምርጫን ውጤት ሊያጭበረብሩና ሊሰርቁ የሚችሉ ካድሬዎች በለውጥ ማዕበሉ ሰጥመው ለፓርቲ ሳይሆን ለሀገርና ህዝብ እንዲሰሩ የማድረግ አቅም አለን። በተንቀሳቀስንባቸው አካባቢዎች ያገኘናቸው ካድሬዎች ፈጣን የሆነ የአመለካከት ለውጥ ታይቶባቸዋል። ስለዚህ የጨዋታ ካርዱ በህዝቡ አይደለም ያለው፤ በካድሬዎቹ ነው። ምክንያቱም ህዝቡማ ህወሓትን እንደማይመርጥ ተረጋግጧል። ጥያቄው የህዝቡ ድምፅ ይጭበረበራል ወይ የሚል ነው። ህወሓት የራሱ ካድሬዎች እንኳን የዓረናን እንቅስቃሴ አይተው እየካዱት ነው። ስለዚህ የ2007 ምርጫ ወሳኝ ነው።

Letter to Yemeni Presidnt on the Detention of Andargachew Tsege, Secretary General of Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy


July2, 2014
H.E. Field Marshall Abdu Rabu Mansour Hadi
President,
Republic of Yemen
Sana’a, Yemen
Your Excellency:
Re: Yemeni: Detention of Andargachew Tsege, Secretary General of Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy
We are writing to express our grave concerns regarding the unlawful and unwarranted detention of Andargachew Tsege, Secretary General of Ginbot 7 Movement for Justice Freedom and Democracy while in transit at Sanaa International Airport on June 23, 2014.
We are particularly concerned that the continued illegal detention of Mr. Tsege, a renowned critic of the Ethiopian government is politically motivated and against international law.
We urge the Government of Yemen to release him immediately and unconditionally.
Mr. Tsege a well-known pro-democracy and human rights advocate in his ancestral homeland, Ethiopia, presents no threat to Yemen or to the Yemeni authorities.
Mr. Tsege was imprisoned in Ethiopia for his political activities during the ill-fated election of 2005 and has escaped assassination attempts by the dictatorship whose brutality, is well documented even by the United States State Department.
It is now universally recognized that the Ethiopian regime subjects political opposition, human rights defenders, journalists and critics of the government in general, to persecution including threats, intimidation, arbitrary arrests and detentions, politically motivated trials, enforced disappearances and extra-judicial killings.
It’s unconscionable that the Government of Yemen would hand Mr. Tsege over summarily to the security forces of the country whose persecution of its critics at home and abroad is well documented.
We would like to call your Excellency’s attention to the doctrine of non-refoulement, now recognized as a norm of customary international law. As such all persons are protected under international human rights law from return to any country where they would be in danger of being subjected to torture and extra-judicial killings. Such is the case of Mr. Tsege and we urge your government to adhere to these recognized principles aimed at protecting human rights.
We respectfully write this letter:
  • To convey our profound concerns for the security of Mr. Tsege and to request his immediate and unconditional release.
  • To call upon the Government of Yemen to respect its solemn obligations under international law to protect Mr. Tsege from arbitrary detention
  • To request your Excellency to use the powers vested in your office to stop any illegal renditions the government of Ethiopia may have requested
We would like to impress upon you the long and historical ties between the Yemeni and Ethiopian people and we urge you to protect the security of our compatriot and to release him immediately.
We also trust that Yemeni authorities would not engage in any harmful acts that would endanger the well-being, safety and security of Mr. Tsege. It should be self-evident that such acts would only bring about adverse consequences for the future relations between the peoples of Yemen and Ethiopia.
Please accept, Your Excellency, the assurance of our highest considerations.
Sincerely,

Berhanu Nega, Ph.D.
Chairman
Ginbot 7 Movement for Justice Freedom and Democracy

አቶ አንዳርጋቸው በየመን መንግስት ከታገቱ በሁዋላ የኢትዮጵያ ትምባሆ ድርጅት ለየመን ኩባንያ ተሰጠ

June2/2014
የግንቦት 7 አመራር አባል በየመን መንግስት ታግተው ከተያዙ ከአንድ ሳምንት ወዲህ የፕራይቬታይዜይሽንና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ውሳኔ መስጠት በተቸገረበት የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት ሽያጭ ጉዳይ ላይ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ውሳኔ በመስጠት ለየመን ኩባንያዎች ከፍተኛ የአክሲዮን ድርሻ እንዲወስዱ ተደረገ::
andargachew
በአሁኑ ወቅት የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግታ ባለችበት ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የየመኑ ኩባንያ ሼባ ኢንቨስትመንት የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት 60 በመቶ ባለቤት እንዲሆን መወሰኑ በርካታ ፖለቲከኞችን እያነጋገረ ይገኛል;:
ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው የ70 ዓመት ዕድሜ ባለቤት የሆነው ብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት 22 በመቶ የሚሆነው አክሲዮን ከ1991 ዓ.ም. ጀምሮ በየመኑ ሼባ ኢንቨስትመንት ሲያዝ፣ ቀሪው 78 በመቶ አክሲዮን ደግሞ በመንግሥት የተያዘ ነበር፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በወሰነው አዲስ ውሳኔ ሼባ ኢንቨስትመንት ተጨማሪ 38 በመቶ አክሲዮን ከመንግሥት ላይ እንዲገዛ የሚፈቅድ በመሆኑ፣ ሼባ ኢንቨስትመንት በብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት አክሲዮን ላይ አንበሳውን ድርሻ 60 በመቶ ሲይዝ፣ መንግሥት ደግሞ 40 በመቶ ድርሻ ይዞ ይቀጥላል፡፡
ሼባ ኢንቨስትመንት እንዲገዛ ለተፈቀደለት 38 በመቶ አክሲዮን 1.3 ቢሊዮን ብር መክፈል እንደሚጠበቅበት የፕራይቬታይዜሽንና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ወንዳፍራሽ አሰፋ ለሪፖርተር ገልጸው፣ ኩባንያው ይህንኑ ገንዘብ እንደከፈለ የስም ዝውውር እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡
ብዙም ባልተመለመደ ሁኔታ የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት አክሲዮን ሽያጭ ላይ የፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ የሥራ አመራር ቦርድ ውሳኔ ለመስጠት የተቸገረው በሁለት ምክንያቶች መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ የመጀመርያው ድርጅቱ በሲጋራ ላይ ብቸኛ መብት (ሞኖፖሊ ራይት) ያለው በመሆኑ፣ ይህ የብቸኝነት መብት የየመኑ ኩባንያ ከፍተኛ ድርሻ በሚይዝበት ወቅት ምን መሆን አለበት? የሚለው ጉዳይ ላይ አቋም መያዝ ባለመቻሉ ነው፡፡ ሁለተኛው ጉዳይ ደግሞ ትምባሆ ድርጅት በተለያዩ የታክስ ዓይነቶች በየዓመቱ ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ ለመንግሥት የሚያስገባ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ትርፋማ ከሆኑ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መካከል አንዱ በመሆኑ፣ ለመንግሥት ግምጃ ቤት ከፍተኛ ገንዘብ ፈሰስ የሚያደርግ ነው የሚለው ጉዳይ ቦርዱ በአክሲዮኑ ሽያጭ ላይ ለመወሰን እንዲቸገር ማድረጉ ነው፡፡
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስና የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር በሆኑት ወ/ሮ አስቴር ማሞ የሚመራው የፕራይቬታይዜሽን ቦርድ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ የመንግሥትን አቅጣጫ በግልጽ ባለመረዳቱ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አቅጣጫ እንዲሰጠው መጠየቁን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ነገር ግን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሁለቱም ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው የአክሲዮን ሽያጩ እንዲከናወን በማዘዙ፣ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የተሰበሰበው የፕራይቬይታዜሽን ቦርድ የየመኑ ኩባንያ ከፍተኛ ባለድርሻ መሆን የሚያስችለውን ውሳኔ እንዲወስን ማድረጉን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ትምባሆ ድርጅት በተለያዩ አካባቢዎች የትምባሆ ልማት የሚያካሂድባቸው የእርሻ መሬቶች ባለቤት ነው፡፡ የድርጅቱ መሥርያ ቤት ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ሳር ቤት በሚወስደው መንገድ ከአፍሪካ ኅብረት ፊት ለፊት የሚገኝ ሲሆን፣ ለፀጥታ አመቺ አይደለም በሚል መሥርያ ቤቱ ከዚህ ቦታ ተነስቶ ወደ አቃቂ አካባቢ እንዲዛወር ተወስኗል፡፡ ምንጮቹ እንደገለጹት ድርጅቱ ቃሊቲ አካባቢ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተረከበው ቦታ ላይ የሚያካሂደውን ግንባታ ሲያጠናቅቅ፣ ለበርካታ ዓመታት ከነበረበት ቦታ ይነሳል ሲል ሪፖርተር ዘገባውን አጠናቁአል::
ውድ አንባቢያን በኢትዮጵያ አትራፊና ከፍተኛ ታክስ ከፋይ ከሆኑ ትላልቅ የመንግስ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የሆነው የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት አቶ አንዳርጋቸው ከታሰሩ ወዲህ ለየመኑ ኩባንያ በጠቅላይ ሚኒስተር መስሪያ ቤት ትዕዛዝ ሙሉ በሙሉ እንዲተላለፍ መደረጉ ዙሪያ ምን ትላላችሁ?

አንዳርጋቸውን ፍለጋ በየመን…ወዳጄ የሀገር ሰው የት ይሆን የታሰርከው?

July 1/2014
በግሩም ተ/ሀይማኖት

ትላንት ነው አስደንጋጭ ዜና የሰማሁት፡፡ ስለ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታሰር፡፡ ከምር በጣም ደንግጫለሁ፡፡ የመን ያለውን ሁኔታ ስለምኖርበት በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ የመን አሁን ያሉም በፊት የኖሩም በትክክል ያውቁታል፡፡ ድንጋጤዬን እንደያዝኩ በተለያየ ሀሳብ እና መላምት ስታትር፣ ነግቶ የት እንዳለ ለመፈለግ የት የት ሄጄ መፈለግ እንዳለብኝ ውስጤ በእቅድ ስነድፍ ቆየሁ፡፡ እቅዴ ተወስኖ ሳያልቅ ከተለያየ አቅጣጫ የሚያውቁኝ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ሰዎች ተንቀሳቃሽ ስልኬ(ሞባይሌ) ላይ እየደወሉ ስለሁኔታው ይጠይቁኛል፡፡ የማውቀው እንደሌለ እና ምን ማድረግ እንደምችል ግራ እንደገባኝ ከመንገር ውጭ መልስ አጣሁ፡፡ ከተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ለሚደወልልኝም መልስ አጠረኝ፡፡ ሌሊቱ እስኪጋመስ ድንጋጤዬ አለቀቀኝም፡፡ የድንጋጤዬ መንስኤ ሶስት ነገር ነበር፡፡

1ኛ፡- የመን እንደገባሁ ተይዤ እስር ቤቶቹን ስላየኋቸው፡፡ እኔን አንድ ጋዜጠኛ ወደ ሀገሬ ለመመለስ ‹‹ወኪል ኒያባ›› የሚባለው ፍርድ ቤት እስከማቆም የወያኔ ካድሬዎች ያደረጉትን በማሰብ…


2ኛ፡- ከኢትዮጵያ ውጭ የወያኔ ካድሬዎች እንደልብ ከሚንቀሳቀሱባቸው ሀገሮች የመን የመጀመሪያዋ እና በሺህ የሚቆጠሩ ካድሬዎች ያሉባት በመሆንዋ…


3ኛ፡- የመንና ኢትዮጵያ እ.አ.አቆጣር ከ2004 ጀምሮ በየአመቱ የሚታደስ ወንጀለኛ የመለዋወጥ የሁለትዮሽ ስምምነት ያላቸው በመሆኑ ነው ድንጋጤዬ ልክ ያጣው፡፡


ባሰብኩት መሰረት ፍለጋዬን ለመቀጠል በዛሬው እለት ጠዋት…የኢሳቱ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም ጋር በመደወል መታሰሩን ሲሰሙ የታሰረበትን እስር ቤት ሰምተው እንደሆነ ጠየኩኝ፡፡ ምንም ፍንጭ የለም ትራንዚት ሲያደርግ መያዙን ብቻ ነው የሚያውቁት፡፡ ፍለጋዬን ከሚግሬሽን እስር ቤት ጀመርኩ፡፡ ሞባይል ስልኬ ግን በሁኔታው የተጨነቁ ሰዎች ሲደውሉ ተጨናንቆ ዋለ፡፡ ኢሚግሬሽን እስር ቤት አስፈልጌ የለም፡፡ ወደ ኤርፖርት በመሄድ እዛው ባለው ጊዜያዊ እስር ቤት ታስሮ ከሆነ አስጠየኩ፡፡ የለም፡፡ በመቀጠል የደህንነት ቢሮ በእነሱ አጠራር ‹‹አምንስቲያሲ..›› ሄጄ የሚታወቅ ነገር እንዳለ ጠየኩ፡፡ የረመዳን ጾም በመሆኑ የፍጡር ሰዓት ደርሷል እና ከፈለክ ክፍጡር በኋላ ካልሆነም ነገ ጠዋት መተህ ጠይቅ አሉኝ፡፡ ምን አስችሎኝ ነገ ድረስ ልቆይ…ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ ሄጄ ባስፈልግም የለም ሆነ ያገኘሁት ምላሽ፡፡


‹‹..ወዳጄ የሀገሬ ሰው የት ይሆን የታሰርከው?..›› የሚል እሳቤ ውስጤ ተላወሰ፡፡ ለነገሩ የታሰረበትን ባውቅስ ምን ማድረግ እችል ይሆን? የሚል እሳቤም ሰቅዞ ያዘኝ፡፡ በእርግጥ የመን ከታሰረ ያለው ሁኔታ በጥሩ መንፈስ አይሸትም እና ሁላችንም ተላልፎ እንዳይሰጥ ድምጽ እንድናሰማ ለራሴ አሳሰብኩኝ፡፡…ፍለጋው አያልቅም ነገ ቸር ያሰማኝ ይሆን?...ፍለጋው አያልቅም ነገ ቸር ይገመኝ ይሆን?

Tuesday, July 1, 2014

የአቶ አንዳርጋቸውን ጽጌን በየመን መታፈን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን የተለያዩ አስተያየቶችን እያሰጡ ነው

July 1/2014
ሰኔ ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን የጸጥታ ሃይሎች የግንቦት7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸውን ማፈናቸውን ተከትሎ በፌስቡክ፣ በቲውቲርና በድረገጾች ላይ የተለያዩ አስተያየቶች ተሰጥተዋል።

አክቲቪስት አበበ ገላው በበኩሉ የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማገቷ   ሌላአደገኛና በጣም አሳሳቢ ክስተት ነው።የአንባገነኑየህወሃትስርወመንግስትተቃዋሚዎችንማንምአገርበምንምአይነትሁኔታማፈን፣ማሰርናማንገገላታትአለምአቀፍህግንየሚጥስህገወጥድርጊትነው።የመንአቶአንዳርጋቸውንለወያኔአሳልፋእንዳትሰጥናያለምንምቅድመሁኔታእንድትለቅሁሉምነጻነትናፋቂኢትዮጵያዊሁሉበጋራጥረትሊያደርግይገባል።የየመንኤምባሲዎችንበያሉበትበተቃውሞማጨናነቅናእንቅልፍመንሳትእንዲሁምአለምአቀፍጫናማድረግያስፈልጋል።ግዜሳይረፍድይህንንየቁርጥቀንኢትዮጵያዊለመታደግበያለንበትበጋራእንረባረብ።” ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ፕራይድ ዲ ባሰፈረው ጽሁፍ ደግሞ ” እውነተኛ ታጋይ ሊታሰር ሊሞት ይችላል፣ የተጀመረውን ትግል ግን ሊያስሩትም ሆነ ሊገሉት ከቶ አይቻላቸውም። ኢትዮጵያም አንድ አንዳርጋቸውን ብቻ ሳይሆን ሚሊዮን አንዳርጋቸውን ፈጥራለችና በከንቱ አትድከሙ፣ ወደዳችሁም ጠላችሁም ሁላችንም ግንቦት 7 ነን።” ብሎአል።

የአረና ፓርቲ አመራር አባል የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና መምህር አብራሀ ደስታ ከመቀሌ ባሰፈረው ጽሁፍ ደግሞ ” በርካታኢትዮጵያውያንስደተኞች በየመን ሲሰቃዩ የኢህአዴግ መንግስት ዝምታመምረጡይገርመኝ ነበር።ኢትዮጵያውያን በየመንይታሰራሉ፣ይገረፋሉ፣ይገደላሉ።መንግስትናሀገርየሌላቸውይመስልማንምየሚደርስላቸውየለም።ይህንነገርእንቆቅልሽሆኖብኝነበር።ለካኢትዮጵያውያንስደተኞችበየመንሲሰቃዩየኢትዮጵያመንግስትሰምቶእንዳልሰማየሆነውየየመንመንግስትየግንቦት 7ንአመራርአባላትበመያዝእንዲተባበረውለማግባባትነው።ይሄው ኢህአዴግለዜጎች ደህንነት ሳይሆን ለስልጣኑ የቆመ   የማፍያዎችድርጅትመሆኑአስመሰከረ።መንግስትየሚመሰረተውየህዝብናሀገርደህንነትለመጠበቅነው።ኢህአዴግግንየስደተኞችንደህንነትወደጎንትቶለስልጣኑየሚፈታተኑትንግለሰቦችበመያዝስራተጠምዷል።ለስልጣንጥበቃየሚውልንያህልለዜጎችደህንነትምየሚውልቢኖርመልካምነውእላለሁ።” ብሎአል።

ዘላለም ጸጋየ በበኩሉ ” በሀገራችንመኖርሲያቅተንእንሰደዳለን፡፡
ተሰደንእንኳንእንታደናለን፡፡ኦአምላክሆይምነውእረሳኸን፡፡ኢትዮጵያውያንልጆችህእንደራሄልእንባቸውጸባዖትየሚደርሰውመቸነው፡፡ ጃያስተሰርያ” ያለ ሲሆን፣ ነጻነት ይበልጣል ደግሞ”የመንበኢትዮጵያህዝብየነፃነትትግልላይጣልቃመግባቷንእንድታቆምለጫትናለርካሽለሆነጥቅምየወንበዴስብስብየሆነውወያኔኢህአዴግጋርበማበርታጋዮቿላይእየደረሰላለውአፍናመከራእንግልትተባበሪበመሆንየሀገራችንታሪካዊጠላትእየሆነችእንደምትገኝሊገነዘቡትይገባል:፡” ብሎአል።

የነፃነት ትግል ሁሉንም መራራ መከራ ለመቀበል መፍቀድ ነው በሚል ርእስ ሥርጉተሥላሴ ባወጣችው ጽሁፍ ደግሞ ” የነፃነትትግልመከራንለመቀበልተፈቅዶናተወዶየሚወሰድእርምጃነው።የነፃነትትግልየጫጉላጊዜሽርሽርአይደለም።ሊሆንምከቶውንምአይችልም።ስለዚህ ዛሬ በግንቦት 7ጸሐፊ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የደረሰው እግታ ከትግልመስምር አንዱ በመሆ ኑ ሊያደናግጥ የሚገባው የዓለም ፍጻሜ አይደለም። ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን እራሳቸውን ሰጥተው ነው ኢትዮጵያሀገራችንከክብሯጋርያቆዩን።” ብላለች።

ሙላት ሃይሉ ለየመኑ ፕሬዚዳንት በጻፈው ደብዳቤ ደግሞ ” የየመን መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር የሚኖረውን የረጅም ጊዜ የጥቅም ግንኙነት በመመርመር አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፎ እንዳይሰጥ ጠይቋል። ሙላት አቶ አንዳርጋቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲሰፍን እራሱን አሳልፎ የሰጠ ሰው መሆኑን ገልጿል።

ለኢሳት በኢሜል ከደረሱት መልእከቶች መካከል ፣ አዱኛ የተባሉ ሰው “ለነጻነት በሚደረግ ትግል  ውስጥ መሪ ወይም ታጋይ ቢሞት፣ ቢታሰር ወይም ቢሰደድ ትግል አይቆምም፣ ትግል የሚቆመው ወይም ቅርጹ የሚቀየረው የተፈለገው ነጻነት ሲመጣ ብቻ ነው። አንድ መሪ በመታሰሩ ወይም በመሞቱ ትግል የሚቆም ቢሆን ኖሮ የጆን ጋራንግ ደቡብ ሱዳን ወይም የማንዴላዋ ደቡብ አፍሪካ እስከዛሬም አይወለዱም ነበር። አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ጀግና የነጻነት ታጋዮች መካካል በመጀመሪያው ረድፍ የሚሰለፍ ነው። አንድም ቀን ለልጆቹና ለኑሮው ሳያስብ በረሃ ለበረሃ የሚንከራተት፣ ለአገሩ ነጻነት ሲል ውድ ህይወቱን ለመስጠት ቆርጦ የተነሳ እውነተኛና ጀግና መሪ ነው።  አንዳርጋቸው ቆራጥና ጀግና ሰው ነው። የአገሩ ጉዳይ ሁሌም ስለሚያንገበግበው እረፍት የለውም። የየመን መንግስት አንዳርጋቸውን ለወያኔ ጅቦች አሳልፎ እንደማይሰጠው ተስፋ አደርጋለሁ፣  ቢያደርገው እንኳን ለነጻነት የሚደረገው ትግል መልኩን ቀይሮ፣ እስካሁን ከታየውም በበለጠ ቆራጥነትና አንዳንዴም ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ይካሄዳል እንጅ አይደበዝዝም።  ” ብሎአል።


የኢትዮጵያ ህዝብ በዝምታ እየተቀበላቸው የሚገኙት በደሎች

July 1/2014
የኢትዮጵያ ህዝብ በዝምታ እየተቀበላቸው የሚገኙት በደሎች
ከአንድነት ሃይሌ
በየመን የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መታገትን በመስማቴ አዘንኩ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ በዝምታ እየተቀበላቸው የሚገኙትን በደሎችም መለስ አድርጌ ባጭሩ እንድቃኝ አስገደደኝ።
ያሳዝናል! በአመት ከ70 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ህፃናት በማደጎነት ሲሸጡ እያየን፣ እየሰማን፤ ከ45 ሺህ በላይ ሴቶቻችን ለሳውዲ አረቢያ በቤት ሰራተኝነት ሲቸረቸሩና፤ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ዜጎቻችን በተመሳሳይ መልኩ ለሌሎች አረብ ሃገራት በሃራጭ ሲሸጡ እያየን፣ እየሰማን፤ ሴቶቻችን በየ አረብ ሃገሩ ለመስማት እጅግ በሚያዳግት ሁኔታ አሰቃቂ በደሎች ባደባባይ ሲፈፀምባቸው እያየን፣ እየሰማን፤ አያሌ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ህይወታቸውን ለማትረፍና ለማሻሻል ወደተለያዩ ሃገራት ተሰደው ስቃይ ውስጥ እንደሚገኙ እያየን፣ እየሰማን፤ ከዚህም በላይ ደግሞ ይህ ሁሉ በደል በዜጎች ላይ ሲፈፀም ቢያንስ ተቃውሞውን ሊያሰማ ፈፅሞ ፍላጎት የሌለው፤ ይባስ ብሎ በደሉን በተቃወሙ ዜጎች ላይ ከበዳዮቹ ሃገራት ጋር በማበር ንፁሃን ዜጎችን የሚደበድብ፣ የሚያስር ጭካኝ ስርዓት በጫንቃችን ተሸክመን፤ አንጀታችን እያረረ፣ ልባችን በሃዘን እየተጎዳ፣ ሞራላችን በውድቀት እየተሰበረ፣ አንገታችንን ደፍተን በዝምታ እየኖርን እንገኛለን።
ሁላችንም እንደምናቀው የኬኒያ፣ የሱዳን፣ የጅቡቲና፣ ሌሎች የጎረቤት ሃገራት በወያኔ በደል ምክንያት ሳይወዱ ተገደው ህይወታቸውን ለማዳን ከሃገራቸው በተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ላይ በተደጋጋሚ አፈና እየፈፀሙ ይገኛሉ። በቅርቡ በኬኒያ መንግስት ታፍኖ ለወያኔ ከተሰጠ በኋላ ህይወቱ እስክታልፍ ድረስ ለአመታት በወያኔ እስር ቤት በተሰቃየው በወንድማችን ወጣት ተስፋሁን ጨመዳ ላይ የተፈፀመውን አሳዛኝ በደልና በኦብነግ አመራር አባላት ላይ የተደረገው አፈና፤ በደቡብ ሱዳን በአቶ ኦኬሎ አኩአይና ሌሎች የጋምቤላ ንቅናቄ አባላት ላይ በተመሳሳይ መልኩ የተደረገው አፈና ያለምንም ተጨባጭ እርምጃ በዝምታ ታልፈዋል። ዛሬ ደግሞ የየመን መንግስት በአሳዛኝ ሁኔታ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ማገቱ በመገናኛ ብዙሃን ተነግሯል።
በዜጎቻችን ላይ እየደረሱ ለሚገኙት አሰቃቂ በደሎች በዋነኝነት ተጠያቂው የወያኔ መንግስት ቢሆንም፤ በስደት የሚኖሩ ዜጎቻችን ላይ ከወያኔ መንግስት ጋር በመተባበር በተደጋጋሚ አፈና እየፈፀሙና አጋልጠው እየሰጡ የሚገኙ የጎረቤት ሃገራት ወደፊት በኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ተጠያቂ እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር የለኝም። ነገር ግን ወገኖቼ ይህ አፈና እስከመቼ ይቀጥላል!? ዜጎች ጭቆናን በመቃወማቸው ብቻ በስደት ከሚደርስባቸው ስቃይ በላይ ለምን በየ ጎረቤት ሃገሩ ይታፈናሉ!? እኛ ኢትዮጵያውያን እስከመቼ እየተናቅን እንኖራለን!? ጎበዝ ዝምታውና መነጣጠሉ ይብቃ! የሚደርስብንን አፈና ለማስቆምና ራሳችንን ለመከላከል ሁላችንም በአንድነት ጫና መፍጠርና ማስገደድ ግድ ስለሚለን፤ በምንችለው ሁሉ መረባረብና መተባበር ይኖርብናል እላለሁ።
አፈናው ይብቃ!

Open Letter to President of Yemen

July 1, 2014

Open letter to Abd Rabbuh Mansur Hadi: President of Yemen Arab Republic

by Mulat Hailu
yemen-andargachew
The people of Ethiopia are Shocked and disappointed over the illegal detention of Andargachew Tsige, Secretary General of Ginbot7 Movement for Justice, Freedom and Democracy by Yemen security forces during his transit flight in Yemen.
Mr. Andargachew is an Ethiopian origin and British citizen who has been struggling for prevalence of democracy in Ethiopia. He has devoted himself to the true cause of Ethiopian people, the inevitable desire for democracy. Though foiled successfully, the criminal dictatorial regime in Ethiopia has attempted to assassinate the leader Andargachew in November 2013. Mr. Andargachew is hero for Ethiopian people and is one of the icons of democracy in the nation.
The Senna Security forum that has been signed under former president of Yemen, Ali Abdullah Saleh and former dictator of Ethiopia Melse Zenawi which lead TPLF to establish surveillance base in Yemen for surveillance and phone tapping on Ethiopian opposition has been serious concern for Ethiopian people. The illegal detention of Mr. Andargachew, by Yemen Security forces since June 23, 2014 has no ground and is grave concern for the people of Ethiopia. We urge the government of Yemen to immediately free Mr. Andargachew and the Yemen security forces not to transfer him to the criminal regime in Addis under any circumstance. Yemen has no ground to detain Mr. Andargachew who has been tirelessly working for prevalence of democracy in Ethiopia. We request the government of Yemen to carefully evaluate its long term interest and lasting cooperation with the people of Ethiopia and avoid short termism in dealing with dictatorial regime in Ethiopia. The long historical relationship between the people of the two sisterly nations has endured, in spite of changing regimes, on the basis of mutual cooperation. The people of Ethiopia considers the act of transferring Mr. Andargachew to the dictatorial regime in Ethiopia as direct attack on its long aspiration and struggle for genuine democracy in the nation. We hereby request President Hadi not to take any steps that will jeopardies the long lasting relationship between the people of the two sisterly nations and to order the immediate release of Mr. Andargachew. Thank you in advance for your serious consideration.

የሽብር - ዘፍጥረት (ተመስገን ደሳለኝ)

July1/2014

በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ዋዜማ፣ በመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ንቅናቄ መፈጠሩን ያስተዋለ  አልነበረም፤ …ከሺህ ዓመታት በፊት በአገር አልባነት፣ በተለያዩ የዓለም አህጉራት የተበታተኑት አይሁዳውያን ይደርስባቸው ከነበረው መገለልና ጭቆና (ፀረ-ጽዮናዊነት) ነፃ ለመውጣት በፈረንጆች አቆጣጠር በ1896 ዓ.ም. ቴዎድሮ ሄርዘል በተባለ ሰው መሪነት የጽዮናዊ ንቅናቄን መሰረቱ፤ ዋነኛ ዓላማውም ለዘመናት ሲናፍቋት ወደቆየችው ‹‹ተስፋይቱ ምድር›› መመለስን እውን ማድረግ ሲሆን፤ ይች ዕለት ትቀርብ ዘንዳም ገና ከልጅነት ዕድሜው ጀምሮ ‹‹ሃ-ቲካያ›› (ተስፋችን) የተሰኘውን ዝነኛ መዝሙር ሲዘምር የኖረው እያንዳንዱ አይሁዳዊ፣ ተደራጅቶ ለመታገል መወሰኑ ደስታውን ሰማይ ጥግ አደረሰው፤ ንቅናቄው ከተመሰረተ ከሁለት አስርታት በኋላም ባካሄደው የመጀመሪያው ኮንግረስ ታሪካዊ ሊባል የሚችል ውሳኔ ላይ ደረሰ፤ በአውሮፓ አገራት ተበታትነው ይኖሩ ከነበሩ ጽዮናውያን መካከል የተወሰኑት በግል ገንዘባቸውም ሆነ ቡድናቸው በሚያደርግላቸው ድጎማ ወደ ፍልስጤም በተናጠል ሄደው መሬት እየገዙ እንዲሰፍሩ የሚል ነበር፤ ይህንንም ሂደት አካባቢውን ከአውቶማን ቱርክ ነጥቃ የምታስተዳድረው ታላቋ ብሪታኒያ እ.ኤ.አ. በ1917 ዓ.ም ባወጣችው ‹‹ባልፎር ዲክላሬሽን›› (Balfour Declaration) በመደገፏ፣ መንገዱን አልጋ በአልጋ አደረገው፡፡ ይሁንና ዕቅዱ ሙሉ ለሙሉ ከመሳካቱ በፊት ሁለተኛው የዓለም ጦርነት መቀስቀሱ እንደማይቀር እርግጠኛ የሆኑት አዶልፍ ሂትለር እና ዱቼ ሞሶሎኒ፣ በጦርነቱ ወቅት አረቦቹን ከጎናቸው ለማሰለፍ ሲሉ፣ ብሪታኒያ ለሰፈራው የምታደርገውን እገዛ በአሉታዊ ጎኑ እያጋነኑ ቅስቀሳ ማድረግ መጀመራቸው ከባድ ስጋት ውስጥ ጣላት፤ እናም ‹‹ኋይት ፔፐር›› (White Paper) በተሰኘ አዲስ ድንጋጌ አይሁዳውያን መሬት እንዳይገዙ ከለከለች፡፡ እነርሱም በውሳኔው እጅግ ከመበሳጨታቸው የተነሳ ‹‹ሃጋና›› (Hagana) የሚባል ህቡዕ ቡድን መስርተው የእንግሊዝ ንብረትና ጥቅም የሆኑትን በሙሉ በፈንጅ ማጋየት፣ ሰላማዊ ዜጎችን መግደልና መጥለፍን የቀን ተቀን ሥራቸው አደረጉት፡፡ …እነሆም የፖለቲካ ተንታኞች ይህን ሁነት ነው ‹በዘመናዊው ዓለም የሽብርተኝነት ጅማሮ› ሲሉ የሚጠሩት፡፡ በአናቱም የአሸባሪው ‹‹ሃጋና›› የአመራር አባል ከነበሩት መካከል ዳቪድ ቤንጎሪኦን እና ሌቪ ሸኮል በተለያየ ጊዜ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሲመረጡ፤ የድርጅቱ ታጣቂዎችም እ.ኤ.አ. በ1948 ዓ.ም. ለተመሰረተችው አዲሲቷ እስራኤል የመከላከያ ሠራዊት እርሾ ሆነው ማገልገላቸውን የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡

 የሽብር መግፍኤ

ሽብርተኝነት ሰይጣናዊ ድርጊት መሆኑ ባይካድም፤ የአንድ ሐይማኖት አሊያም ብሔር መለያ አለመሆኑ መዘንጋት የለበትም፤ እንዲያውም አብዛኛውን ጊዜ የጭቆና ውጤት መገለጫ ተደርጎ ሲበየን ይስተዋላል፡፡ ከዓለም አቀፉ አል-ቃይዳ እስከ አፍሪካ ቀንዱ አልሸባብ፤ ከናይጄሪያው ቦኮ ሐራም እስከ ማሊው አሳር ዲን፤ ከማግሪቡ ሙጃአን አቢዒ እስከ ሰሀል በረሀው አዘዋድ… የሚጠቀሱ ድርጅቶችም የመጀመሪያ አነሳስ መገለል፣ ጭቆና እና ወረራን የመሳሰሉ ገፊ-ምክንያቶች ስለመሆኑ ጉዳዩን ያጠኑ ምሁራን ያስረግጣሉ፡፡ ከቀዳሚው ‹‹ሃጋና››ን እስከ ዛሬዎቹ ድረስ ያሉ በአሸባሪነት የተፈረጁ ቡድኖች የሚከተሉት ስልት ከወታደራዊ ተቋማት ይልቅ፣ ሰላማዊ ዜጐችና የሕዝብ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ደግሞ፣ ዘግናኝ የጭካኔ ገፅታን አላብሶ እጅግ አስፈሪ ፍጡር አድርጓቸዋል፤ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የጃፓን አየር ኃይል አባላት ፈንጅ የጫኑ የጦር አውሮፕላኖችን ቁልቁል አምዘግዝገው ከአሜሪካን የውጊያ መርከቦች ጋር በማላተም ይፈፅሙት የነበረው፤ በእነሱ አጠራር ‹‹መለኮታዊው የንፋስ ጥቃት›› ተብሎ የሚታወቀው የአጥፍቶ መጥፋት ተግባር፣ ከ1980ዎቹ መጨረሻ ወዲህ ለተመሰረቱ አሸባሪ ድርጅቶች ተመራጭ ሆኗል፡፡ በርግጥ ይህን መሰሉ ድርጊት በዓለም ማሕበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት ያሌለው በመሆኑ፣ ቡድኖቹ ከየትኛውም አገራትም ሆነ ሕጋዊ ተቋማት ይፋዊ ድጋፍ እንዳያገኙ እንቅፋት መፈጠሩ በገሃድ የሚታይ እውነታ ነው፡፡ እንዲሁም የሽብርተኝነት መነሾና አንድምታ ዛሬም ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚያስማማ ብያኔ ባያገኝም፣ የፖለቲካ ውሳኔን ጨምሮ ከማሕበራዊና ኃይማኖታዊ ጭቆና ጋር መያያዙ አያከራክርም፡፡ ጥቂት የማይባሉ የወቅቱ ቡድኖችም አመሰራረታቸው የእስልምና ሕግጋትን በሥርዓተ-መንግስት ውስጥ በኃይል ማንበር መሆኑ፣ በብዙሃኑ ዘንድ የተዛባ ትርጉም ፈጥሮ፣ ድርጊቱን የኃይማኖት መገለጫ እንዲመስል እየገፋው ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

 …የሽብርተኝነትን ታሪካዊ ዳራ ከእስልምና ይልቅ፤ ከአይሁዳውያን ጋር የሚጋመድ መሆኑን በደምሳሳው ከቃኘን ዘንዳ፣ ለኢትዮጵያችን አስጊ እየሆነ ወደመጣው አልሸባብ አፈጣጠር እና ኢህአዴግ መራሹ-መንግስት ሽብርን የሚመለከትበትን መነፅር ወደ መፈተሹ አቢይ አጀንዳችን እንለፍ፡፡

 ወረራ-ሶማሊያ 
 የ1998ቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሥራ ዓመቱን ከማጠናቀቁ በፊት ከባድ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሶማሊያ ራሱን ‹‹የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ሕብረት›› ብሎ የሚጠራው ስብስብ፣ ኢትዮጵያ ላይ ጅሀድ በማወጁ ምክንያት መከላከያ ሠራዊታችን ሞቃዲሾ ድረስ ገብቶ እንዲደመስሰው የሚጠይቅ አጀንዳ አቀረበ፡፡ ይሁንና በምክር ቤቱ ቅንጅትን እና ሕብረትን ወክለው የገቡት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት፣ ይህ ሁኔታ ለብሔራዊ ጥቅም ሳይሆን የአሜሪካንን ተልዕኮ ለማስፈፀም እንደሆነ በማጋለጥ እና ለወደፊቱም ሀገሪቷን ከባድ ዋጋ ሊያስከፍላት እንደሚችል በማስጠንቀቅ በብርቱ ቢወተውቱም፤ ገዥው-ግንባር፣ ከአጋር ፓርቲዎች እና ከአቶ ልደቱ ኢዴፓ ጋ ተባብሮ በማፅደቁ (ባያፀድቁትም በመለስ የቀረበ አጀንዳ ከመፈፀም የሚያግደው ኃይል አልነበረም) የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ ሶማሊያ ዘልቆ ይገባ ዘንድ ግድ ሆነ፡፡ የህወሓት መስራች የነበረው አውዓሎም ወልዱ ከጋዜጠኛ ዮናስ በላይ ጋር ቃለ-መጠየቅ ባደረገበት ወቅት ከኤርትራ ጋር በማያያዝ በተረት አስደግፎ የገለፀበት መንገድ ይህንን ሁነት ፍንትው አድርጎ ስለሚያሳይ እዚህ ጋ ልጥቀሰው፡-

 ‹‹አንዲት ተረት ልንገርህ፡፡ በአንዲት ሀገር ውስጥ ሀገሪቷን ለመጠበቅ የተሰማሩ ውሾች ነበሩ፡፡ ሰዉ ደግሞ ይህን በጎ ምግባራቸውን እያየ ያቀርባቸው ነበር፡፡ ከጊዜ በኋላ ግን ሰዉ ምን ብሎ ይወስናል፤ ‹ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ስላልሆነ እናባራቸው፡፡› ውሾችም ይህንን ሰሙ እና ስብሰባ ተቀመጡ፡፡ ‹ሰዉ ሁሉ እንዲህ ብሎ ወስኖብናልና ምን እናድርግ?› ሲሉም መከሩ፡፡ መጨረሻ ላይ ‹አንድም መኖር ነው፣ አንድም መሞት ነውና ሕጎቻቸውን አክብረን እንሰናበት› ብለው ወሰኑ፡፡ ትክክለኛዋ ስነ-ሐሳብ እቺ ነች፡፡ ቢሆንም ግን አንዱ እጁን አውጥቶ ምን ይላል? ‹ክፍት የተተወ ነገር ካገኘንስ ምን እናድርገው?› አለ፡፡ ‹ይህማ የራሱ የሰዉ ስህተት ነውና እንክት አድርገን መብላት ነው እንጂ› ብለው ወሰኑ ይባላል፡፡ እኛም፣ ወደ ኤርትራ ዘልቀን ስንገባ ‹ልዑላዊት ሀገር ናትና፣ በቃ ተመለሱ› ተባለ፤ እንደ ውሾቹ ውሳኔ ክፍት የሆነች ሶማሊያን ያገኘን እንደሆነስ? ክፍት የሆነች ሶማሊያን ካገኘንማ እንክት አድርገን እንበላታለን እንጂ ነው የተባለው፡፡›› 
(የትግራይ ሕዝብ፣ ወያኔዎቹና ሽፍቶቹ›› ገፅ 208)

 በዚህ መልኩ በቅጥረኝነት በዘመቻው እንዲሰማራ የተደረገው መከላከያ ሠራዊታችን መዳረሻው የሕብረቱ ጠንካራ ይዞታ ወደነበረው ሞቃዲሾ ሆኖ፣ በሶስት ግንባር የተከፋፈለ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በነገራችን ላይ ኢትዮጵያን ለታሪካዊ ስህተት ከዳረገ ከዚህ ዘመቻ 30 ቀናት ቀደም ብሎ (ሰኔ 4/ 1998 ዓ.ም.) መንግስት አንድም ከኋላው አደገኛ ጠላቱን ኦብነግን አስቀምጦ ወደፊት መገስገሱ ያልታሰበ ችግር የሚያመጣ በመሆኑ፤ ሁለትም ‹በሚሊኒየሙ ሽብርተኛ ድርጅቶችን በሙሉ እንደመስሳለን› በሚለው ዕቅዱ፤ ሶስትም ‹የኦብነግ የተወሰኑ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሶማሊያ በኩል ወደ ሀገር ቤት ገብተዋል› የሚል መረጃ በመድረሱ፤ የዘመቻ ሠራዊቱ አባል የሆነው አግአዚ 6ኛ አሉላ ሻለቃ ‹‹ሀጂ ተራራ›› በተባለው ስፍራ የመሸገው ኦብነግን እንዲደመስስ ይታዘዝና፣ ገርብ ከሚገኘው የጦር ሰፈሩ ተንቀሳቅሶ ድንገተኛ ጥቃት ይሰነዘራል፤ እነርሱም ለመከላከል ባደረጉት ከፍተኛ ትንቅንቅ ውጊያው እየበረታ መጣ፤ የማታ ማታም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ግንባር ጥቂት ጣቶቹን ቢያጣም፣ ‹‹ቃታ ለመሳብ አንድ ጣት እስኪቀረኝ ድረስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር መዋጋቴን አላቋርጥም›› እያለ ሲዝት ይሰማ የነበረው፣ ‹‹ዱብኬ›› በሚል ቅፅል ስሙ የሚታወቀው የኦብነግ ተዋጊዎች አዛዥ ከመገደሉ በተጨማሪ፣ በአጠቃላይ የግንባሩ ታጣቂ ላይ ከባድ ጉዳት በመድረሱ፣ ገሚሱ ድንበር አቋርጦ ወደ ሶማሊያ ሲሸሽ፤ የተቀረው ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በመቀላቀል ሰላማዊ ዜጋ መስሎ መሸሸጉን የ‹‹ፋክት›› ወታደራዊ የመረጃ ምንጮች ይስረዳሉ፡፡

 በኦጋዴን ‹‹የኢትዮጵያ መንግስት ጅምላ ጭፍጨፋ ፈፅሟል›› በሚል በዓለም አቀፍ መድረክ ውግዘት የቀረበበትም በዚሁ ውጊያ ሰሞን ከተከሰተ አንድ ጉዳይ ጋ ይያያዛል፡፡ ይኸውም ከላይ የተጠቀሰው የሻለቃ ጦር አባል የሆነ አንድ ሻምበል መንገድ ስቶ ይጠፋና በኦብነግ ሰዎች እጅ ይወድቃል፤ እነርሱም ህይወቱን በመንጠቅ ብቻ ባለመርካታቸው ነውረኛነት   በተጠናወተው ሁኔታ ምላሱን ጎልጉለው ካወጡ በኋላ አስክሬኑን ጎዳና ላይ ይጥሉታል፤ ይህም ሠራዊቱን ክፉኛ በማስቆጣቱ፣ ቀድሞውንም ‹‹ከአሸባሪዎቹ ጋር ትተባበራላችሁ!›› በሚል የሚወነጅለውን የአካባቢው ነዋሪ መኖሪያ ቤቶች በእሳት ከማቃጠሉም በላይ፣ በርካታ ሰላማዊ ዜጎችን ሲገድል፣ ጥቂት የማይባሉ እንስቶችን ደግሞ አስገድዶ ደፍሯል መባሉ ነው የክሱ ጭብጥ ሆኖ የቀረበው፡፡

 በክልሉ ለሰፈረው ሠራዊት ከ15 ዓመት በላይ በመረጃ መኮንንነት ያገለገለው ሁንዴ ከበደ (ስሙ የተቀየረ)፣ መንግስት ነዋሪውን ከማሰቃየት አልፎ ኦብነግን ከሕዝብ ለመነጠል ያደረገው የረባ ጥረት አለመኖሩን ይናገራል፡፡ እንደመኮንኑ ትንተና የአካባቢው ነዋሪዎች አብዛኛዎቹ ዘላን በመሆናቸው ተበታትነው (ተራርቀው) እንጂ አንድ ቦታ በቋሚነት ሰፍረው መኖር አይችሉም፤ ነገር ግን መንግስት አንድ ቦታ ላይ ሰብሰብ ብለው እንዲሰፍሩ ለማድረግ ጫና ሲፈጥር ይስተዋላል፤ ይሁንና እነርሱ ጥያቄውን ለመቀበል የሚያስችል መሰረተ ልማት (ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያ፣ የእርሻ መሬትና የመሳሰሉት) ባለመሟላቱ ፍቃደኛ አልሆኑም፤ ይህ እምቢተኝነታቸውም ወታደሩ ጎጆአቸውን በእሳት እንዲያጋይ፣ በርሃብ አለንጋ ይረግፉ ዘንድ ሩዛቸውን በትኖ ከአፈር ጋር እንዲደባልቅ፣ ሴቶቻቸውን አስገድዶ እንዲደፍርና መሰል ስቅየቶችን ወደማድረሱ ጭካኔ ገፍቶታል፤ በዚህም የአብላጫው ነዋሪ ልብ ወደ ኦብነግ መሸፈቱን ያምናል፤ ይህ ደግሞ ለድርጅቱ በእጅጉ አስፈላጊ የሆነው የሰው ሀይል፣ መሸሸጊያ፣ ቀለብ እና የሀገሪቱን ሠራዊት የተመለከተ መረጃ በቀላሉ እንዲያገኝ ያስችለዋል (ኦጋዴንና አካባቢውን፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሠራዊት ሚናን እና ኦብነግን በተመለከተ ሌላ ጊዜ በስፋት መመለሴ ስለማይቀር፣ ይህን ሀተታ እዚሁ ጋ ገታ አድርገን የጀመርነውን እንቀጥል)

 …ወደ ሶማሊያ የተደረገው ዘመቻ በሶስት የተከፈለ ነበር፤ በመጀመሪያው ግንባር አግአዚ 6ኛ አሉላ ሻለቃ ኮማንዶ እና ከ44ኛ ክፍለ ጦር የወጡ ሁለት ኃይሎች፣ ከሰሜን ዕዝ እና ከአዋሽ አርባ ማሰልጠኛ ከተወጣጣ አንድ ሜካናይዝድ ጋር ተጣምረው በፍርፍር በኩል በለደወይኔን፣ ብሉ በርግን፣ ጀዋሀርን አልፈው ሞቋዲሾ መግቢያ አፋፍን ተቆጣጥረው እንዲቆዩ ሲታዘዙ፤ በሁለተኛው ግንባር ከ44ኛው ክፍለ ጦር የወጣ አንድ ሻለቃ እና አግአዚ ወጋገን ክፍለ ጦር የተመደቡ ሲሆን፤ ግዳጃቸውም ‹በጊልካ ሀዩ፣ ባይደዋን ተሻግራችሁ ሞቋዲሾ ግቡ› የሚል ነው፤ በሶስተኛው ግንባር ደግሞ ጉና ክፍለ ጦር እና ኡመር 5ኛ ሻለቃ በፑንትላንድ በኩል በለበልን አልፈው ሞቋዲሾ እንዲደርሱ ታዝዘዋል፤ በዚህ መልክ የተንቀሳቀሰው የኢትዮጵያ ሠራዊት፣ ሞቋዲሾ አፋፍ ላይ ከደረሰ በኋላ የነበረውን ሁኔታ ከሰሜን ዕዝ ሜካናይዝዱን የተቀላቀለ የአስር አለቃ እንደሚከተለው ይተርከዋል፡-

‹‹መጀመሪያ ከአገራችን ስንነሳ አዲስ የተመሰረተው የሶማሊያ የሽግግር መንግስት ወታደር ከፊት እንደሚመራ፣ የእኛ ግዴታ ከኋላ ሆኖ ድጋፍ መስጠት ብቻ እንደሆነ የተነገረን ቢሆንም፤ እቦታው ስንደርስ የገጠመን እውነታ ግን በተገላቢጦሽ፣ እኛ ከፊት እነርሱ ከኋላ መሰለፋቸው ነው፤ በዚያ ላይ ቁጥራቸው እዚህ ግባ የሚባል አልነበረም፡፡ ሌላው አስቂኙ ጉዳይ ደግሞ ሞቋዲሾ አፋፍ ደርሰን ደፈጣ ባደረግንበት ወቅት በእኛ መንግስት ተመድበው እንደቀረቡ የምጠረጥራቸው የሀገር ‹ሽማግሌ› ተብየዎች በአስተርጓሚ በኩል አክራሪውን ኃይል ወደከተማው ገብተን እንድንደመስሰው እንዲማፀኑ የተደረገበት ድራማ ነው፤ ለማንኛውም እኛም ወደ ከተማው ዘልቀን የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ሕብረትን በውጊያ ድባቅ መትተን ከይዞታው አባረርነው ስናበቃ፣ በ‹ባሌ ባይደዋ› ፈራርሶ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ ተቆጣጠርን፤ ቀጥሎም ቤተ-መንግስቱን ይዘን ባንዲራችንን ሰቀልን፤ በዚህ ግዳጅ ከእኛ በኩል ከ44ኛ ክፍለ ጦር የመጣ አንድ ሻለቃ ሙሉ በሙሉ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ከዋናው ውጊያ በፊት (በጉዞ ላይ ሳለን) ደግሞ ‹‹ብሉ በርግ›› በተባለ ቦታ ባደፈጡ የአክራሪው ኃይል አባላት ድንገተኛ ጥቃት ተሰንዝሮብን አንድ ወታደር ሲሰዋ፤ አንድ ቆስሎብናል፡፡››

የሆነው ሆኖ ኢትዮጵያ ሠራዊቷን ወደ ሶማሊያ የማስገባቷ ክሽፈት ዓብይ ማሳያ በደካማው የእስላማዊ ፍርድቤቶች ሽንፈት ላይ እጅግ የበረታው አልሸባብ መፈጠሩ ብቻ አይደለም፤ ዘመቻው ሀገራዊ ተልእኮ የሰነቀ አለመሆኑም እንጂ፡፡ ለዚህም እንደማስረጃ ከሚጠቀሱት መካከል፣ የአሜሪካን የጦር መኮንኖች ሞቃዶሾና ኪስማዩ ድረስ መጥተው ከሳተላይት የሚቀበሉትን መረጃ ተንተርሰው፣ ሠራዊቱን ‹በዚህ ቦታ አሸባሪዎች መሽገዋልና፣ ወደዚያ ተንቀሳቀስ›፣ ‹በዚህ ቦታ ጥቃት ሰንዝር› እያሉ ትዕዛዛት ከመስጠታቸው ባሻገር፣ በውጊያ መሀል የጦር አውሮፕላኖቻቸው ድንገት ደርሰው በአጋዥነትየመሳተፋቸው ምስጢር ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ መቶ አለቃ ዘላለም እጅጉ (ስሙ የተቀየረ) እንዲህ ሲል ያጠናክረዋል፡-

‹‹በ1999 ዓ.ም አጋማሽ ላይ በኪስማዩ ጫካ ከመሸጉ የአልሸባብ አባላት ጋር ከባድ ውጊያ እያካሄድን ሳለ፣ ዘግይተን የአሜሪካን እንደሆነ ያወቅነው የጦር አውሮፕላን ሳይታሰብ ብቅ ብሎ በሰከንድ ውስጥ ሺ ጥይቶችን በሚተፋ ዘመናዊ  መሳሪያ አልሸባቦችን እንደቅጠል ያረግፉቸው ጀመር፤ ስለጉዳዩ አስቀድሞ የደረሰን መረጃ ባለመኖሩ አዛዣችንን ጨምሮ ሁላችንም ክፉኛ ደንግጠን፣ ‹ምን መጣ?› ብለንም መሬት ላይ ‹ፓንች› እስከማድረግ ደርሰን ነበር፤ ሁኔታው የመብረቅ ስብርባሪዎች ከሰማይ እምብርት ውስጥ እየተምዘገዘጉ ምድርን የሚያደባዩ እንጂ ከአንድ የጦር መሳሪያ አፈ-ሙዝ ውስጥ የሚንጣጣ የጥይት እርምታ በፍፁም አይመስልም ነበር፡፡››

 ‹‹ማሃ ሚገለገሌ?›› 

 መከላከያ ሠራዊታችን የእስላማዊው ፍርድ ቤቶች ሕብረት የተሰኘውን ስብስብ ኪስማዩ ድረስ ተከታትሎ አከርካሪውን ቢሰብረውም፤ ዘመቻው ከተጀመረ አንድ ወር እንኳ ሳይሞላው ከሕብረቱ ኃይል ፍፁም የላቀ፣ በቁጣ የነደዱ ወጣቶችን ማሰለፍ የሚችል ንቅናቄ ይነሳል ብሎ ያሰበ ሰው አልነበረም፤ የሆነው ግን እንዲያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሞቋዲሾን ጨምሮ የሶማሊያ ዋና ዋና ከተሞችን መቆጣጠሩ፣ በአርበኝነት መንፈስና አገር ነፃ በማውጣት ስም ‹‹አልሸባብ›› መመስረቱን፣ የቡድኑን ስነ-ተፈጥሮ ያጠኑ ምሁራን ያስረግጣሉ፡፡ መጀመሪያውኑም ‹‹ዘመቻው የአሜሪካንን ተልዕኮ ለማስፈፀም ያለመ ቅጥረኝነት ነው›› በሚል ከሀገር ውስጥ እስከ አለም አቀፍ መድረኮች ድረስ የተቀጣጠሉ ተቃውሞዎችን መስማት ያልፈቀደው የኢትዮጵያ መንግስት ጦር ሠራዊት፣ በሶማሊያም የተደረገለት አቀባበል ‹‹ማሃ ሚገለገሌ?›› (ምን አገባችሁ?) በሚል ብርቱ የቁጣ ድምፅ የታጀበ ነበር፡፡

 ቆይታው ለሁለት አመት ያህል የተራዘመው ይህ ሠራዊት በሰላማዊ ዜጎች ላይ ካደረሰው ሰቆቃ በተጨማሪ፣ የዓለም አቀፍ ስምምነትን ተፃራሪ ድርጊቶች ፈፅሟል ተብሎ ተደጋጋሚ ወቀሳ ይቀርብበት እንደነበረ አይዘነጋም፡፡ በወቅቱ የአንዱ ሻለቃ አስተባባሪ ሆኖ የተመደበው ኃይላይ ገ/መድህን (ስሙ የተቀየረ) ኩነቱን እንዲህ ይገልፀዋል፡-

 ‹‹በሶማሊያ በርካታ ተግዳሮቶች ያጋጠሙን ቢሆንም፣ ግዳጃችንን ከባድ ካደረጉብን መሀል ዋነኛውን ልጥቀስልህ፣ አብዛኛው የሞቋዲሾ ቤቶች ከድንጋይ የታነፁ ናቸው፤ ለከተማ ውጊያ በብላቴን ስልጠና የወሰደው የእኛ ሠራዊት ደግሞ፣ ልምምዱን ያካሄደው ከጭቃ በተሰሩ ቤቶች ውስጥ ነው፤ በዚህም ምክንያት ከአንዱ ሕንፃ ወይም መኖሪያ ቤት በክላሽንኮቭ ለሚሰነዘርብን ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ በታንክ አሊያም በሞርታር የተደገፈ በመሆኑ፤ ድርጊቱ ለከተማ ውጊያ ከባድ መሳሪያ መጠቀምን የሚያግደውን ዓለም አቀፍ ሕግ ከመጣሱም በላይ፣ ከሞቋዲሾ ነዋሪ ሀዘን ያልገባበት አንድም ቤት ተፈልጎ እንዳይገኝ ሰበብ ሆኗል፡፡››

  ኃይላይ ገ/መድህን እንደሚያስረዳው በርካታ መኖሪያ ቤቶች፣ ሕንፃዎች፣ መስጊዶች… በከባድ መሳሪያ ሲፈራርሱ የተመለከቱ አያሌ ወጣቶች፣ በአርበኝነት ስሜት በገፍ ወደ አልሸባብ መጉረፋቸውን ነው፤ አያይዞም ‹‹በዚህ አይነቱ ሰላማዊ ዜጎችን አብሮ በሚደመስስ ጅምላ ጥቃት የተማረሩ ሶማሊያውያን አልሸባብን ቢቀላቀሉ ምን ይደንቃል?›› ሲል ይጠይቅና፣ ሁኔታው ለድርጅቱ ጥንካሬ ገፊ-ምክንያት እንደሆነው አጽንኦተ በመስጠት ይከራከራል፡፡ በተጨማሪም ከምሽቱ እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ድረስ የተጣለው ሰዓት እላፊን ተከትሎ ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ማንኛውም ሶማሊያዊ እርምጃ እንዲወሰድበት የተላለፈው ትዕዛዝ ሕዝቡን ለምሬት ዳርጎት ነበር፡፡ ለዚህም እንደማሳያ የሚጠቀሰው ‹‹ሆርሞድ›› እየተባለ በሚጠራው የቴሌ አገልግሎት ሰጪ መስሪያ ቤት ግቢ የሰፈረው የኢትዮጵያ ሠራዊት ከቆይታው በአንዱ ዕለት፣ ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አንድ አውቶብስና አንድ ሚኒባስን ኦርሴዶ ፓስታ ፋብሪካ አጠገብ በላውንቸር መትቶ ሲጋያቸው፤ ከተሳፋሪዎቹ መካከል በፅኑ ቆስለው ከተረፉት አራት ሰዎች በቀር፣ አንዲት እርጉዝ ሴትን ጨምሮ ሁሉም ማለቃቸው ነው፡፡ …ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ አልሸባብ ካላፈ ታሪክ ጋር በማዛመድ ‹‹ኢትዮጵያውያን በአፄ ኃይለስላሴ ዘመን ጓሮአችንን ይኮተኩቱ ነበር፤ በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ጊዜ ጓዳችን ድረስ ገቡ፤ ዛሬ በኢህአዴግ ደግሞ ሚስቶቻችንን እስከመንጠቅ ደረሱ›› እያለ የሚነዛው ፕሮፓጋንዳ የሕዝቡን ስሜት እንዲያሸንፍ ከማገዙ በዘለለ፣ ትውልድ ተሻጋሪ አደጋን የተሸከመ ይመስለኛል፡፡
 ቀሪውን ሳምንት እመለስበታለሁ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

June 30/2014
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።
ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።
መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።
በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

አንጋፋው የነጻነት ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ግንቦት 7 ዛሬ አስታውቋል::

June 30/2014

Breaking News: አንጋፋው የነጻነት ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ግንቦት 7 ዛሬ አስታውቋል
ግንቦት 7 ዛሬ ለጋዜጠኞች እና ለአባላቶቹ በላከው መግለጫ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ሰአት ትራንዚት በአደረጉበት በየመን አውሮፕላን ጣቢያ ውስጥ በፀጥታ ሃይሎች መወሰዳቸውን አስታውቋል።
ንቅናቄው የየመን መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን ለወያኔ አሳልፎ እንዳይሰጥ ከፍተኛ የሆነ ማስጠንቀቂያ የላከ ሲሆን ለሳምንት ያህል ውስጥ ለውስጥ ሲደረግ የነበረው ውይይትም በሁለቱ ወገኖች ሳይሳካ መቅረቱን በመግለጽ የመን ይህን ታሪካዊ ስህተት ብትፈጽም በወደፊቱ የሁለተዮሽ ሀገራት ግንኙነት ላይ የማይጠፋ ጠባሳ እና አስቸጋሪ ሁኔታ እንደሚፈጠር አስታውቋል፡፡
ድርጅታችን የሚያደርገውን የነጻነትና የዲሞክራሲ ትግል ከቶ ለአንዳፍታም ቢሆን አያቆምም ያለው ድርጅቱ፤ አቶ አንዳርጋቸው ራሳቸውን አሳልፈው ለሚወዷት ሀገራቸው እማማ ኢትዮጵያ መሰዋእት ለመሆን የተዘጋጁ የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጅ መሆናቸውን እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ከጎናችን ሆኖ ትግሉን እንዲያጠናክርና  በየመን መንግስት ላይ ህዝቡ በያለበት ጫና እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
ginbot 7እንደሚታወቀው በአለፉት ወራቶች የኢትዮጵያ መንግስት በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ የመግደል ሙከራ ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ሙሉ መግለጫውን በሚቀጥለው  እናወጣለን።
በዚህ አጋጣሚ አባይ ሚዲያ በየመን መንግስት ያደረበትን ከፍተኛ ቅሬታ እየገለጸ ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ለዚህ አንጋፋ የነጻነት ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ተላልፎ እንዳይሰጥ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በየመን እና በአለም አቀፍ የተባበሩት ቢሮዎች የተቃውሞ ድምጻችን እንድናሰማ ጥሪያችን እናቀርባለን፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የሚደርሱንን ማናቸውም መልእክትና ጽሁፍ ቅድሚያ በመስጠት ድህረገጻችን ላይ እንለጥፋለን።
አባይ ሜዲያ

Yemen detained Ethiopian Opposition Ginbot 7 Secretary Andargachew Tsige

June30/2014
Andargachew Tsege
Andargachew Tsige
(borkena) Yemen detained Andargachew Tsige, Ginbot 7 Secretary, ESAT reported in a breaking news coverage.
Citing official statement issued by Ginbot 7, ESAT indicated that Andargachew was detained by Yemen Security on June 23,2014. Effort by Ginbot 7 to secure the release of Andargachew Tsige was not a success.
Also, the report indicated that Ato Andargachew was on transit to a third country,unnamed, via Yemen.
Ginbot 7 asserted that there is no legal basis for Yemen authorities to detain Andargachew and has requested Yemen not to handover Andargachew Tsige to Ethiopian government.
Ginbot 7 Movement for Justice, Democracy and Freedom was formed in 2005 , following the release of opposition party leaders from many months of imprisonment after government crackdown on registered opposition parties in Ethiopia.
The ruling party in Ethiopia legislated law to outlaw the movement and the movement is considered as a “terrorist” organization. if Yemen hands over Andargachew to Ethiopian government, there is no question that Andargachew’s life would be in danger.
There are indications that Ethiopian government spends millions of dollars in security operations overseas. And it is possible that it might have corrupted Yemen security forces for this particular arrest.
A few months ago Ethiopian government apparently employed some members of Kenyan security forces to kidnap two members of delegation of ONLF who were in Nairobi to negotiate with Ethiopian government delegates with the invitation of Kenyan government.