Tuesday, November 18, 2014

‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

November18,2014
ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››
Photo: ‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››

Hearing On the Human Rights Dilemmas in Ethiopia

November 18, 2014

Tom Lantos Human Rights Commission – Hearing On the Human Rights Dilemmas in Ethiopia – Testimony of Felix Horne, Researcher, Africa Division

Press Release

Mr. Chairman and members of the committee, thank you for providing me the opportunity to speak today about the human rights situation in Ethiopia.

The other panelists have articulated some of the critical issues that are facing Ethiopia ahead of the May 2015 elections. I would like to elaborate on human rights concerns associated with Ethiopia’s many development challenges.

Ethiopia is the one of the largest recipients of development assistance in the world, including more than $800 million in 2014 from the US government. Many of Ethiopia’s 94 million people live in extreme poverty, and poverty reduction is rightly one of both the US and Ethiopian government’s core goals. Improving economic and human development is fundamental to ensuring that Ethiopians are able to enjoy their rights to health care, education, shelter, food and water, and Ethiopia’s government, civil society, international donors and private investors all have important roles contributing to the realization of these rights.

But sustainable development also requires a commitment to the full range of human rights, not just higher incomes, access to education and health care, but the ability for people to express their views freely, participate in public policy decision-making, join associations of their choice, have recourse to a fair and accessible justice system, and live free of abuse and discrimination.

Moreover, development that is not rooted in respect for human rights can be counter-productive, associated with abusive practices and further impoverishment of people already living in situations of extreme poverty. In Ethiopia, over the past few years Human Rights Watch has documented disturbing cases where international donors providing development assistance are turning a blind eye to government practices that fail to respect the rights of all beneficiaries. Instead of improving life in local communities, these projects are proving harmful to them. And given the repression of independent voices, media and associations, there are no realistic mechanisms for many local communities to express their views to their government. Instead, those who object or critique the government’s approach to development projects face the prospect of intimidation, harassment and even serious abuse.

In 2011 in Ethiopia’s western region, Gambella, Human Rights Watch documented such abuses during the implementation of the first year of the government’s “villagization” program. Gambella is a region populated by indigenous groups who have suffered from political marginalization and lack of development for decades. In theory the villagization program aimed to address some of these concerns. This program required all indigenous households in the region to move from their widely separated homes into larger villages – ostensibly to provide improved basic services including much-needed schools, health clinics and roads.

I was in Gambella for several weeks in 2011 and travelled to 16 different villages in five different districts. I met with people who had not yet moved from their homes and others who had been resettled. I interviewed dozens of people who said they did not wish to move but were forced by the government, by police, and by Ethiopia’s army if necessary. People described widespread human rights violations, including forced displacement, arbitrary arrest and detention, beatings, and rape and other sexual violence. Thousands of villagers fled into neighboring countries where they became refugees. At the same time, in the new villages, many of the promised services were not available and the food security situation was dire.

The villagization program has also been implemented in other marginalized regions in Ethiopia. These regions are the same areas where government is leasing large pieces of land to foreign investors, often from India, China and the Gulf states, without meaningful consultation with local communities, without any compensation being paid to local communities, and with no benefits for local communities other than low-paying labor jobs on the plantations.

In the Omo valley in southern Ethiopia, Human Rights Watch found that the combination of sugar and cotton plantations and hydroelectric development is causing the displacement of up to 200,000 indigenous people from their lands. Massive amounts of water are being used for these projects which will have devastating impacts for Lake Turkana across the border in Kenya and the 300,000 indigenous people who live in the vicinity of the lake and depend upon it. The displacement of communities in the Omo valley is well underway. As in Gambella, communities in the Omo valley told Human Rights Watch about coercion, beatings, arrests and threats from military and police to force people to move to new settlements.

Human Rights Watch also found politically motivated abuse in development programs. In 2010, we documented discrimination and “political capture” in the distribution of the benefits of development programs especially prior to the 2010 elections. Opposition party supporters and others who did not support the ruling party were denied access to some of resources provided by donor-funded programs, including food aid, micro credit, seeds, fertilizers, and other critical agricultural inputs needed for food security, and even employment opportunities. Schools, funded as part of education programs by the US and other development partners, were used to indoctrinate school children in ruling party ideology and teachers were required to report youth perceived to support the opposition to the local authorities. These government practices, many of which continue today, show the intense pressure put on Ethiopian citizens to support the ruling party, and the way in which development aid is manipulated to discriminate against certain communities.

All of these cases have several common features. First, the Ethiopian government routinely denies the allegations without investigation, claiming they are politically motivated, while simultaneously restricting access for independent media and investigators. Second, these programs are directly and indirectly funded by Western donors, who seem unwilling to acknowledge, much less address human rights concerns in Ethiopia.

Monitoring and evaluation of these programs for human rights abuses is inadequate. Even when donors carry out assessments to look into the allegations, as has happened in Gambella, they are not conducted rigorously and do not ensure victims of abuses can speak freely and safely. In the current environment in Ethiopia, it is essential for anyone seeking to investigate human rights violations to go to locations where victims can speak openly, to understand the dynamics of the local communities, and recognize the depths of the fear they are experiencing.

All of these problems are exacerbated by the ongoing government crackdown on the media and civil society. The independent press has been ravaged since the 2010 election, with the vast majority of journalists terrified to report anything that is remotely critical of the government. In October I was in a country neighboring Ethiopia where over 30 journalists have fled in the past few months alone. I spoke to many of them: their papers were closed, their families were threatened, and many had been charged under repressive laws merely because they criticized and questioned the Ethiopian government’s policies on development and other issues. I spoke with someone who was forced to seek asylum abroad because he had questioned in writing whether the development of Africa’s largest dam on the Nile River was the best use of money in a country where poverty is pervasive.

As for Ethiopian civil society, it has been decimated by another law, the Charities and Societies Proclamation. It has made obtaining foreign funding nearly impossible for groups working on human rights, good governance, and advocacy. Leading members of the human rights movement have been forced to flee abroad.

Some people take to the streets to peacefully protest. Throughout 2014 there were various protests throughout Ethiopia. In many of these protests, including during the student protests in the Oromia region in April and May of this year, the security forces used excessive force, including the use of live ammunition against the students. We don’t even know how many Oromo students are still detained because the government publicizes no information, there is no comprehensive human rights monitoring and reporting, and family members are terrified of reporting the cases. Members of the Muslim community who organized protests in 2012 against what they saw as government interference in religious affairs have also paid an enormous price for those demonstrations, with many beaten or arrested and most of the protest organizers now imprisoned on terrorism charges.

Finally, bringing about change through the ballot box is not really an option. Given that 99.6 percent of the parliamentary seats in the 2010 election went to the ruling party and that the political space has shrunk dramatically since then, there is little in the way of a viable opposition that can raise questions about government policy, including development plans, or other sensitive topics.

This situation leaves Ethiopians no real means to express concerns over the policies and development strategies imposed by the government. They either accept it, they face threats and imprisonment for speaking out, or they flee their country as thousands have done. The refugee communities in countries neighboring Ethiopia are full of individuals who have tried to raise concerns in all of these ways, and are now in exile.

To conclude, we all recognize that Ethiopia needs and requires development. The problem is how development is being undertaken. Development projects need to respect the rights of the local communities and improve their quality of life, regardless of ethnicity or political perspective. The United States and Ethiopia’s other major partners can and should play a leading role in supporting sustainable, rights-respecting development. The US should not accept arguments that protecting human rights is in contradiction to development goals and implementation.

In 2014, the appropriations bill required the US to scrutinize and suspend funding for development programs in Ethiopia that might contribute to forced evictions in Ethiopia, including in Gambella and Omo. This was an important signal that the abuses taking place were unacceptable, and this should be maintained in the upcoming FY15 appropriations bill, whether it is a stand-alone bill or a continuing resolution.

As one of Ethiopia’s key partners and supporters of Ethiopia’s development, the US needs to do more to ensure it is rigorously monitoring and consistently responding to human rights abuses in Ethiopia, both bilaterally and multilaterally. The US should be pressing the Ethiopian government to ensure that there is genuine consultation on development initiatives with affected communities, that more robust monitoring is put in place to monitor for potential abuses within programs, and that independent civil society, both domestic and foreign, are able to monitor and report on rights abuses. Respect for human rights is first and foremost a concern of all Ethiopians, but it is also central to all US interests in Ethiopia, from security to good governance to sustainable development.

Monday, November 17, 2014

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

November 17,2014
በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም!!

ዘጠኝ /9/ ህጋዊ ሰውነት ያለን ፓርቲዎች በትብብር ለመሥራት በተስማማነው መሠረት የአጭር ጊዜ የጋራ ዓላማችንን ማስፈጸሚያ ተግባራት የመጀመሪያ ዙር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የአንድ ወር ዕቅድ አውጥተን ወደ ሥራ መግባታችን ይታወሳል፡፡ የዚሁ የአንድ ወር ዕቅድ አካል ከሆኑት ተግባራት ቅዳሜ በ6/03/07ዓ.ም ‹‹ዲሞክራሲያዊ ምርጫና የአፈጻጸም መርሆዎች›› በሚል ርዕስ የአዳራሽ ውይይት በተሳካ ሁኔታ አከናውነን በትናንትናው ዕለት በ07/03/07ዓ.ም ደግሞ ከአዲስ አበባ ሰሜን ምስራቅ /ከአራት ኪሎና አካባቢው / ህዝብ ጋር በአደባባይ በቤልኤር ሜዳ ተገናኝተን በምርጫ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የትብብራችን አባል የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባውን እንዲያስተባብር በሰጠነው ኃላፊነት- የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1983 የምጠይቀውን ሁኔታ አሟልቶ ለከንቲባ ጽ/ቤቱ የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በ02/03/07 ደብዳቤ ማስገባቱ፣ የጽ/ቤቱ ክፍልም ለደብዳቤው በ04/03/07 ዓ.ም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ከክፍሉ የተጻፈለት ደብዳቤ፡-

1. የተሰጠው መልስ ዕውቅናውን በተመለከተ ግልጽ ያለመሆኑን፤

2. ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ መሰረት አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ የተገለጸውን የሚጻረር መሆኑን፣

3. በአዋጁ አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ ከተደነገገው ጋር የሚቃረን፤
በጥቅሉ በክፍሉ የተጻፈው ደብዳቤ በአዋጁ መሰረት በ12 ሰዓት ውስጥ የተሰጠ ምላሽ ካለመሆኑም፣ ጊዜና ቦታውን ለመቀየር እንኳ አማራጭ ያልቀረበበት፣ ለስብሰባው ዕውቅና ለመንፈግ እንደ ምክንያት የቀረበውም ግልጽ ሆኖ ባለመቅረቡ ፓርቲው የተጻፈውን ደብዳቤ አሳማኝ ሆኖ እንዳላገኘውና እንዳልተቀበለው፣ በመሆኑም ስብሰባው አስቀድሞ በተገለጸው ቦታና ጊዜ እንደሚካሄድ በ05/03/07 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ መልስ በመጻፍ ለክፍሉ ገቢ አድርጎ ዝግጅቱን ቀጥለናል፡፡ ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ ክፍሉ በደብዳቤም ሆነ በአካልና ስልክ ሳያገኘን ዝግጅታችንን አጠናቀን በዕለቱ በተገጸው ሰዓት ወደ ቦታው ስንሄድ ያጋጠመን ሁኔታ ፡-

1ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 9 የተቀመጠውን ‹‹የህገመንግስት የበላይነት›› ያልተከተለ፤

2ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 10(2) የተቀመጠውን የዜጎች መብት በመዳፈርና ለማፈን፤

3ኛ/በህገ መንግስቱ አንቀጽ 12 የተቀመጠውን ‹‹የመንግስት አሠራር ተጠያቂነት›› በጣሰ
ሁኔታ፤

4ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 13 የተቀመጠውን የህገ መንግስት ‹‹ተፈጻሚነትና አተረጓጎም›› በመተላለፍ፤

የተፈጸመ ኢህገመንግሥታዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ፤ በሠላማዊ ዜጎችና በፖሊስ መካከል ግጭት የሚፈጠርበትን ሁኔታ የሚጋብዝ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ይህ ሁኔታ በወቅቱ በቦታው የተገኙት
የአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ ባልደረባና የተልዕኮው ቡድን መሪ ከመሆናቸው ውጪ የራሳቸውን ማንነት/ሥምና ኃላፊነት ለመግለጽ ድፍረት በማጣታቸው፣ በአንድ በኩል ‹‹የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባቸው የታዘዙትን የማስፈጸም ግዳጅ›› በሌላ በኩል ከስብሰባው አስተባባሪዎችና የትብብሩ አመራሮች ለቀረቡላቸው አዋጁን ያጣቀሱ ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄዎች ‹‹አሳማኝ መልስ ለመስጠት በመቸገራቸው ›› በጭንቀት ውስጥ መውደቃቸውን አረጋግጠናል፡፡ በቦታው የነበረን ቆይታ በተራዘመና ጥያቄኣችንም በተደጋገመ መጠን በአንድ በኩል ‹‹የቡድን መሪው›› ጭንቀት ወደ ኃፍረት፣ ብስጭትና የግጭት ስሜት የፖሊስ አባላቱ መንፈስ ደግሞ ወደ ሥጋት ሲሸጋገር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የስብሰባውን ጥሪ ተቀብለው የመጡ ዜጎች ‹‹ስብሰባው ይጀመር፤ እዚህ የመጣነው በመብታችን ልንደራደር አይደለምና የሚያመጡትን እናያለን ›› ግፊት እያየለ በተሰብሳቢውና በፖሊስ መካከል እሰጥ አገባውና ፍጥጫው እየተጠናከረ ሄዷል፡፡

የትብብራችን አመራር መስተዳድሩ በደብዳቤው የገለጸውን ማለትም ‹‹ጥያቄ በቀረበበት ቀን ቀድም ብሎ ዕውቅና የተሰጣቸው ፕሮግራሞች ስላሉ በዕለቱ የፀጥታ አስከባሪዎች የኃይል እጥረት ሊያጋጥም ስለሚችል›› የተባለውን በወቅቱ በህዝቡ ውስጥ ፈሶ ከነበረው ከ100 በላይ የአዲስ አበባና ፌዴራል ፖሊስ ቁጥርና በተጠባባቂነት በአንድ ማክ መኪና ተጭኖ በጋራዥ ውስጥ ተደብቆ ይጠባበቅ ከነበረ የፖሊስ ኃይል ጋር በማገናዘብ በሂደቱ ሴራ እንዳለበት ማረጋገጥ ችሏል፡፡ በመሆኑም አመራሩ ሂደቱን ከትግሉ ዓላማና መርህ ፣ለዓላማው ማስፈጸሚያ በተከታታይና በቀጣይነት በታቀደው ሰላማዊ ትግል ላይ ከሚያስከትለው አሉታዊ ተጽዕኖ፣ ለእንዲህ ዓይነቱ ሴራ ከተደረገው ዝግጅትና በፖሊስ በኩል ከታየው የ‹‹ጭንቅ›› ስሜትና ተደጋጋሚ ውትወታ ካለበት ኃላፊነት ጋር በማገናዘብ የዕለቱ ፕሮግራም በሰላም እንዲጠናቀቅ የማረጋጋት ተግባር በማከናወን ህዝቡን በሠላም አሰናብቷል፡፡ ከዕለቱ ውሎ በመነሳት አመራሩ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የሚከተሉትን የጋራ ግንዛቤዎች ጨብጧል፡፡

1ኛ/ ትብብሩ በመርሃ ግብሩ መሰረት በዕለቱ የተሞከረው ህዝባዊ ስብሰባ ለታሰበለት የድምር ውጤትና የትግሉን ቀጣይነት የማረጋገጥ ፋይዳ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤

2ኛ/ የዕለቱ ውሎ ገዢው ፓርቲ የደረሰበትን የፍርኃት እርከን የሚመለክት ነው፤ ደፍሮ ባይናገረውም በተግባር በሠላማዊ ህዝባዊ ንቅናቄዎች የቱን ያህል እንደሚሸበር በተግባር ያረጋገጠበት ነው፤

3ኛ/በስብሰባው ላይ የተገኙ ኢትዮጵያዊያን ያሳዩት ቆራጥነትና ለመብታቸው ለመቆም ያላቸው ጽናትና የቱንም ዋጋ ለመክፈል ያላቸው ዝግጁነት ለቀጣዩ ትግል ከፍተኛ ሥንቅ ነው፡፡ይህም ለተያያዝነው የጋራ ትግል በእጅጉ አበረታች ነው ፤

4ኛ/ገዢው ፓርቲ/መንግሥት ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜት ለመውጣት ያስቀመጠው የሴራ መፍትሄ መስዋዕትነቱን ይጨምር እንደሆን እንጂ፣ ትግሉን አያቆመውም፡፡

ከእነዚህ ግንዛቤዎች በመነሳት-

1. በተለይ ፡-

1.1.ከገዢው ፓርቲ የማስፈራሪያ ፕሮፖጋንዳ ራሳችሁን ነጻ አውጥታችሁ በተጠራው ስብሰባ ላይ ተገኝታችሁ ለነጻነታችሁና መብታችሁ ያላችሁን ቀናኢነት የገለጻችሁ፣ የቱንም መስዋዕትነት የመክፈል ዝግጁነታችሁን ላረጋገጣችሁ ኢትዮጵያዊያን ያለንን አድናቆት እየገለጽን ትግላችን ጥያቄዎቻችን እስኪመለሱና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አውን እስከሚሆን ተከታታይና ቀጣይ ስለሆነ የተጽዕኖ አድማሳችሁን አስፍታችሁ የበለጠ ተሳታፊ ይዛችሁ በትግሉ እንድትቀጥሉ፤

1.2. በህዝብ ኃይል የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን ሙሉ በሙሉ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ውለው ገዢውን ፓርቲ ከማገልገል አልፈው በሠላማዊ ትግል የፖለቲካ ኃይሎች ላይ አፍራሽ ፕሮፖጋንዳ በሚነዙበት ወቅት የህዝብ ዓይንና ጆሮ ሆናችሁ የምታገለግሉ በአገር ቤትና በውጪ የምትገኙ የመገናኛ ብዙኃን ሁሉ ስላደረጋችሁልን ድጋፍ እያመሰገንን፣ በቀጣይም በህዝብ ወገናዊነታችሁ በመቀጠል ከጎናችን እንድትቆሙ፤

1.3.ገዢው ፓርቲ ከገባበት ከፍተኛ ሥጋትና ፍርኃት ለመውጣት እየተከተለ ካለው የሴራ ፖለቲካ ወጥቶ የህዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ ራሱን ለለውጥ እንዲያዘጋጅ፤

1.4. እንደ ፖሊስ ኃይል ያላችሁ የመንግሥት አስፈጻሚ አካሎች ለገዢው ፓርቲ ሴራ ራሳቸውን በማጋለጥ ከሠላማዊ የመብት ታጋዮች ጋር አላስፈላጊ ግጭት ውስጥ እንዳይገቡና ከህገ መንግሥቱና ከህዝብ ጎን ቆመው ከህግና ታሪክ ተጠያቂነት ራሳቸውን ነጻ እንዲያወጡ፤

2. በአጠቃላይ፡-

2.1. የትግሉ ዓላማ የአገርና የህዝብ፣ቀዳሚ ባለቤቱም እኛው - ነጻነታችንም በእጃችን ነውና በጋራ ‹‹በቃን›› በማለት ለነጻነት በምናደርገው ትግል በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ አገራችንን ከወረደችበት አዘቅት እኛም ከሚደርስብን ጭቆናና ሥቃይ ለመውጣትና የዜግነት ክብራችን ለማስመለስ በሚደረገው ቀጣይና ተከታታይ ሠላማዊ ትግል ለምናቀርበው ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ፤

2.2. የትግሉ ባለቤት ሁላችንም በመሆናችን ብቻ ሣይሆን ‹‹አገራችን ላለችበት ምስቅልቅል ሁኔታ በተናጠል ተመጣጣኝና ዘላቂ መፍትሄ መስጠት ከአንድ ፓርቲ አቅም በላይ ነው›› ከሚለው የጋራ ድምዳሜያችን አንጻር በትብብሩ ያልታቀፋችሁ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋችሁ የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረማችሁና እስከዛሬም ያልተመለሳችሁ እንዲሁም ሌሎች ሠላማዊ ዲሞክራቲክ የተቃውሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ እንድትቀላቀሉ፤
2.3. የዓለም አቀፉና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት መንግስታት ተለዋዋጭና አላፊ፣ አገርና ህዝብ ግን ቋሚ ናቸውና በግንኙነታችሁ የህዝብ ለህዝብ ዘላቂ ጥቅምንና የአገራትን ታሪካዊና ፖለቲካ ግንኙነት ከግምት በማስገባት ሰልፋችሁን ከህዝቡ ጎን እንድታደርጉ፤

ጥሪያችንን ስናስተላልፍ በእኛ በኩል ለአገራችንንና ህዝቧ የምናደርገው የጋራ የተባበረ ትግል የሚጠይቀንን መሥዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል ያለንን ዝግጁነትና ቁርጠኝነት በድጋሚ እናረጋግጣለን!

የተቀናጀና የተባበረ ህዝባዊ ሠላማዊ ትግልን አሸንፎ በሥልጣኑ የዘለቀ አንድም አምባገነናዊ መንግሥት ዓለማችን አታውቅም!!

ስለሆነም እናሸንፋለን!!

ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም

አዲስ አበባ

Sunday, November 16, 2014

የተወሰደው እርምጃ የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃ እንደሚያሳይ ኢ/ር ይልቃል ገለጹ

November 16,2014
9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩትን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል መበተኑ የስርዓቱ የፍርሃት ደረጃ ጫፍ መድረሱን ያሳያል ሲሉ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

ኢንጅነር ይልቃል በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም እንደሚያደርገው ለምን እስከመጨረሻው አንበተንምአላላችሁም? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥተናል፡፡ ምርጫው ነጻና ፍትሓዊ እስኪሆን ድረስ የነጻነት ትግሉ የሚቀጥል ነው፡፡ በአራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ጠርተን ልናነጋግር በሞከርንበት ወቅት ብዙ እስርና ደብደባ ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ የስርዓቱ ፍርሃት አንጻር ገና በመጀመሪያው ስራችን ወደኃይል እንዲገባ አልፈለግንም፡፡ ለሚቀጥሉት ስራዎቻችን ስንል ነው፡፡ ለሚቀጥለው ያንን በሚመጥን ደረጃ መዘጋጀት አለብን፡፡›› ብለዋል፡፡

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እኛ ዛሬ የአራት ኪሎን አካባቢ ሰዎች ነው የጠራነው፡፡ በዚህ ደረጃ ፈርተው ይህን ስብሰባ ያግዳሉ ብሎ ለመገመት ይከብዳል፡፡ ድሮውንም የሌላቸው የህዝብ ድጋፍ ጭራሹን እንደተሟጠ ነው የሚያሳየው፡፡ ትንሹም ነገር ለስልጣናቸው አስጊ ነው ብለው ማሰባቸው የፍርሃት ደረጃቸው ጫፍ እንደደረሰ ያሳያል፡፡›› ብለዋል፡፡
Photo: የተወሰደው እርምጃ የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃ እንደሚያሳይ ኢ/ር ይልቃል ገለጹ

9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩትን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል መበተኑ የስርዓቱ የፍርሃት ደረጃ ጫፍ መድረሱን ያሳያል ሲሉ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ 

ኢንጅነር ይልቃል በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም እንደሚያደርገው ለምን እስከመጨረሻው አንበተንም አላላችሁም? ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥተናል፡፡ ምርጫው ነጻና ፍትሓዊ እስኪሆን ድረስ የነጻነት ትግሉ የሚቀጥል ነው፡፡ በአራት ኪሎ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎችን ጠርተን ልናነጋግር በሞከርንበት ወቅት ብዙ እስርና ደብደባ ተፈጽሟል፡፡ ከዚህ የስርዓቱ ፍርሃት አንጻር ገና በመጀመሪያው ስራችን ወደኃይል እንዲገባ አልፈለግንም፡፡ ለሚቀጥሉት ስራዎቻችን ስንል ነው፡፡ ለሚቀጥለው ያንን በሚመጥን ደረጃ መዘጋጀት አለብን፡፡›› ብለዋል፡፡  

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት አክለውም ‹‹እኛ ዛሬ የአራት ኪሎን አካባቢ ሰዎች ነው የጠራነው፡፡ በዚህ ደረጃ ፈርተው ይህን ስብሰባ ያግዳሉ ብሎ ለመገመት ይከብዳል፡፡ ድሮውንም የሌላቸው የህዝብ ድጋፍ ጭራሹን እንደተሟጠ ነው የሚያሳየው፡፡ ትንሹም ነገር ለስልጣናቸው አስጊ ነው ብለው ማሰባቸው የፍርሃት ደረጃቸው ጫፍ እንደደረሰ ያሳያል፡፡›› ብለዋል፡፡

እንግሊዝ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በተመለከተ ደብዳቤ መጻፏን ወያኔ አረጋገጠ

November 15,2014
የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በተመለከተ ለወያኔዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውንና ወያኔም አቋሙን ግልጽ ማድረጓን የወያኔዉ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን ተናገረ። ሬድዋን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባለፈዉ ማክሰኞ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ዴቪድ ካሜሩን ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደብዳቤ መጻፋቸውን የተለያዩ የውጭ ሚዲያዎች መዘገባቸውን ሰምቻለሁ ካለ በኋለ “ለምን ጻፉ ማለት አይቻልም፤ ጥያቄዉ መሆን ያለበት ምን መለሳችሁ ነው፤” በማለት የተለመደ የማጭበርበሪያ ቃላት ደርድሯል።
የተለያዩ የእንግሊዝ ሚዲያዎች ኢትዮጵያ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ ቀደም ሲል የተፈረደውን የሞት ቅጣት እንዳትተገብር እንዲሁም ኢትዮጵያ ለሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ አቶ አንዳርጋቸውን የመጐብኘት ቋሚ ፈቃድ እንዲሰጥ በደብዳቤያቸው መጠየቃቸውንም ሬድዋን ሁሴን ተናግሯል።
ለዴቪድ ካሜሮን ደብዳቤ መልስ መሰጠቱን ያረጋገጠዉ ሬድዋን፣ “በተጨባጭ የተፈረደበትን ግለሰብ ነው የያዝነው፤ እንዲህ ብታደርጉት ባታደርጉት ብሎ ማንሳት ይቻላል። ምክንያቱም እነሱም የሚመለከታቸው በመሆኑ። በዚህ ምክንያት ግን የእኛ መልስ በራሳችን ሕግ መሠረት ዓለም አቀፍ ሕጉም በሚለው መሠረት የምናደርገውን እናደርጋለን፤” ብሏል። ኢትዮጵያ የምትተገብረው የራሷን ሕግ መሆኑን የገለጹት አቶ ሬድዋን፣ “ከነጭም ከጥቁርም የሚመጣን ደብዳቤ ተንተርሰን ምንም አንተገብርም፤” ብሏል። ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን ደብዳቤ ጽፈው፣ በኢትዮጵያ በኩልም መልስ ተስጥቷል ያለዉ ሬድዋን ሁሴን በደብዳቤው የቀረቡ ጥያቄዎች ቅሬታ እንዳላስነሱ ሁሉ መልሱም ቅሬታ አያስነሳም የሚል ተስፋ በኢትዮጵያ በኩል መኖሩን ተናግረዋል።
“እነሱ ዜጋዬ ነው ብለዋል፤ የእነሱ ዜጋ እንደ ቼ ጉቬራ ነፃ አውጣ ተብሎ ኢትዮጵያ ውስጥ አልተላከም። የእነሱ ዜጋ ከነበረ የእንግሊዝን ዴሞክራሲ ይበልጥ ለመጨመር መታገል ይችል ነበር። ነገር ግን በኢትዮጵያ በቅጥር ነብሰ ገዳይነት ካልተሰማራ በስተቀር ሌላ ሚና አልነበረውም፤” ብለዋል።

የሰንደቅ አላማችን ጠላት ወያኔና ወያኔ ብቻ ነዉ!

November 15,2014
ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ የኩራት፤ የአልበገር ባይነት፤ የአንድነትና የታሪክ ተከታታይነት ምልክት ነዉ። ሰንደቅ አላማ በአንድ በኩል የወደፊቱን ብሩህ ተስፋ ክወዲሁ እያሳየን እየዟችሁ የሚለን፤ በሌላ በኩል ደግሞ በምናብ ወደኋላ እየወሰደን የድልና የመስዋዕትነት ታሪላችንን የሚያስታዉሰን የነጻነት፤ የሠላምና የብሩህ ተስፋ ማህደር ነዉ። የአገራቸን የኢትዮጵያ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማ ትናንትናና ከትናንት ወዲያ በተስፋፊዎች አለመደፈራችንን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ዘረኞች የጫኑብንን የመከራ ቀንበር በቆራጥነት ሰብረን ነገና ከነገ ወዲያ የነፃነት አየር እንድንተነፍስ አስረግጦ የሚነግረን የአንድነታችን፤ የተገጋድሏችንና የድላችን ልዩ ምልክት ነዉ። አንድን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ አላማ ላንተ ምንህ ነዉ ብለን ብንጠይቀዉ ጥያቄዉን ዕድሜህ ስንት ነዉ ተብሎ እንደሚጠየቅ አንድና ሁለት ቃል ብቻ ተናግሮ አይመልስም። ሰንደቅ አላማም በአንድና በሁለት ቃላት ምንነቱ የሚገለጽ ተራ ቃል አይደለም። ኢትዮጵያዉያን ተማሩ አልተማሩ፤ ደሃ ሆኑ ኃብታም ፤ወንጀለኛ ሆኑ ወይም ሠላማዊ ለአገራቸዉ ሰንደቅ አላማ የተለየ ቦታ አላቸዉ። ሰዎች የአገራቸዉን ሰንደቅ አላማ የሚወዱትና ለሰንደቅ አላማዉ በክብር መዉለብለብ የህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉት ስለታዘዙ ወይም ስለ ሰንደቅ አላማዉ ተነግሯቸዉ አይደለም። በእርግጥም የሰንደቅ አላማ ክብርና የአገር ፍቅር ለሰዎች ሰንደቅ አላማዉን አክብሩ፤ አገራችሁን አፍቅሩ እየተባለ የሚነገር ነገር አይደለም። አገርንና ወገንን ማክበርና መዉደድ ሰንደቅ አላማን ከማክበርና ከማፍቀር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነዉ።የሰንደቅ አላማ ልዪ ክብርና የአገር ፍቅር ሰዎች ተወልደዉ ከሚያድጉበት ማህበረሰብ፤ ከቤተሰብ፤ ከጎረቤትና ከጓደኛ እንደ ምግብና እንደ ዉኃ እየበሉና እየጠጡ የሚያገኙት የሰዉነትና የዜግነት መገለጫ ታላቅ እሴት ነዉ።
ለዚህም ነዉ የማንም አገር ዜጋ አገሩ ዉስጥ ቢኖር ወይም ካገሩ ዉጭ፤ ቢታሰር ባይታሰር፤ ሀብታም ቢሆን ወይም ደሃ፤ የኔ ነዉ የሚለዉን የእናት አገሩን ሰንደቅ አላማ በፍጹም የማይረሳዉ። ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ሰዎች ደግሞ በተለይም ኢትዮጵያዉያን በተለያዩ ምክንያቶች የሚኖሩባቸዉን አገር ዜግነት ቢወስዱ እንኳን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩና ባስታወሱ ቁጥር የሚሰማቸዉ አገራዊ ስሜት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ – እንዲያዉም ከአገራቸዉ ተሰድደዉም ሆነ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከአገራቸዉ ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ሰንደቅ አላማቸዉን ባዩ ቁጥር የአገራቸዉ፤ የወንዛቸዉ ፤ ተወልደዉ ያደጉበት መንደርና የልጅነት ትዝታቸዉ ባአይናቸዉ ላይ እየመጣ ዕንባ በዕንባ ይተናነቃሉ። ሰንደቅ አላማ ለአንድ አገር ህዝብ አንድ ነገር ነዉ፤ ብዙ ነገር ነዉ፤ ሁሉም ነገር ነዉ። ሰንደቅ አላማ ህዝብን ያስተባብራል፤ ያከባብራል፤ ያዋድዳል፤ መስዋዕትነትን፤ ፍቅርንና ብልፅግናን ያመለክታል።
ዛሬ የሰንደቅ አላማችንን ጉዳይ አቢይ የመወያያ አርዕት አድርገን የወሰድነዉ አለምክንያት አይደለም። በአገር ጥላቻቸዉና በስንደቅ አላማ ንቀታቸዉ የሚታወቁት የወያኔ ዘረኞች “የአብዬን ወደ እምዩ” እንዲሉ ሰንደቅ አላማቸዉ ተዋርዶ ከሚያዪ የቁም ሞታቸዉን የሚመር ትን ዉድ የኢትዮጵያ ልጆች ባንዲራዉን አዋረዱበለዉ መናገራቸዉን ስለማን ነዉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ አገሮች ተስማምተዉ የሚያከብሩት አለም አቀፉ የሰንደቅ አላማ አያያዝ ፕሮቶኮል በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ የሁሉም አገሮች ሰንደቅ አላማ በእኩል ደረጃ መቀመጥና መሰቀል አለበት፤ አንድ ላይ መሰቀልና አንድ ላይ መዉረድ አለበት ይላል። ይህንን ፕሮቶኮል ረስቶና ሰንደቅ አላማችንን ንቆ በአለም አቀፍ መድረክ ላይ ከሌሎች አገሮች መሪዎች ጋር የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እንደ አለባሌ ዕቃ ዘቅዝቆ ይዞ ያዋረደዉ ወያኔዎች “ታላቁ መሪ” ብለዉ የሚጠሩት ነገር ግን የለየለት የአገርና የህዝብ ጠላት የሆነዉ ዘረኛዉ መለስ ዜናዊ ነዉ። የህወሓትን ባንዲራ በየቦታዉ እየሰቀሉ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ተራ ጨርቅ ነዉ ብለዉ የሸቀጥ መጠቅለያ ያደረጉትም መለስ ዜናዊና ጓደኞቹ ናቸዉ። ዛሬ ደማቅ ሰንደቅ አላማዉን አስመልክቶ በወያኔና በኢትዮጵያ ህዝብ መካከል ያለዉ ትልቅ ልዩነት ትክክለኛዉና ህዝብ የኔ ነዉ ብሎ የተቀበለዉ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የትኛዉ ነዉ የሚለዉ ጥያቄ ላይ ነዉ አንጂ ባንዲራዉን ማክበር አለማክበር ወይም ማዋረድ ላይ አይደለም።
የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የእናት አገራችንን የኢትዮጵያንና የህዝቦቿን ታሪካዊ ተከታታይነትና ዘለዓለማዊነት አጉልቶ የሚያሳየን ከሁላችንም በላይ የገዘፈ ግዙፍ አርማ ነዉ፤ ይህ ማለት ደግሞ ሰንደቅ አላማችን ያቻትና ብሎ እንደሚያሳየን አገር አንደ ኢትዮጵያ ሙሉ ህልዉና ያለዉ ህያዉ አካል ነዉ ማለት ነዉ። ሰንደቅ አላማችንን የምንወደዉና የምናከብረዉም ህያዉ አገራችንን የሚወክል ህያዉ አካል በመሆኑ ነዉ። መለስ ዜናዊንና ስብሀት ነጋን የመሳሰሉ በጣት የሚቆጠሩ የትዉልድ ጭንጋፎች ለራሳቸዉ አገር ሰንደቅ አላማ ደንታ ላይኖራቸዉ ይችላል። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዳለ ግን የህልዉናዉና የአንድንቱ መገለጫ የሆነዉን ሰንደቅ አላማ አይንቅም ወይም አያዋርድም፤ አንድ ህዝብ ባንዲራዉን የማይቀበልና የማያከብር ከሆነ ባንዲራዉ አይወክለዉም ማለት ነዉ፡ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዛሬ ያለዉ እዉነታም ይሄዉ ነዉ፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ባዕድ አካል የለጠፈበትን ባንዲራ የኔ ነዉ ብሎ አልተቀበለዉም ወይም ባንዲራዉ ይወክለኛል ብሎ አያምንም።
ዘርዓይ ደረስ በ1937 ዓም ሮም ዉስጥ የፋሺስት ጣሊያኖችን ጭንቅላት በገዛ አገራቸዉ እንደ ቅጠል እየጨረገደ ከጣለ በኋላ በጣሊያኖች ጥይት ቆስሎ ሲያዝ የተናገዉ የመጨረሻ ቃል ይህ የጣሊያኖች ባንዲራ ይዉረድና የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ይሰቀል የሚል የጀግንነትና የአገር ፍቅር ቃል ነበር። ጀግናዉ አብዲሳ አጋ በጣሊያን በረሃዎች ጣሊያኖችን እያሳደደ ሲገድል የኢትዮጵያ ባንዲራ ከአጠገቡ አልተለየችም። በቀዳማዊ ኃ/ስላሤና በደርግ ዘመነ መንግስት ተማሪዎች ጧት ወደ ክፍል ከመግባታቸዉ በፊት ተሰልፈዉ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ በክብር ይሰቅሉ ነበር፤ ማታም ወደ ቤታቸዉ ከመሄዳቸዉ በፊት ጧት በክብር የሰቀሉትን ባንዲራ በክብር አዉርደዉ ነበር ወደየቤታቸዉ የሚሄዱት። ዛሬ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ጨርቅ ነዉ ብለዉ የተሳደቡና በዚህ ሰንደቅ አላማ ከገበያ የገዙትን ሸቀጥ እየጠቀለሉ አስራ ሰባት አመት የከረሙ ምናምንቴዎች ናቸዉ በሰንደቅ አላማ ክብርና በአገር ፍቅር ታንጾ ያደገዉን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ አላማዉን አዋረደ እያሉ የአዞ እምባ የሚያነቡት።
ሰንደቅ አላማ በዜጎች ልብ ዉስጥ አንደ እሳት የሚቀጣጠል የአገር፤ የህዝብና የዜግነት መገለጫ የሆነ ታላቅ አርማ ነዉ። ይህ አርማ ደግሞ ከእኛነታችንና ከህልዉናችን ጋር የተጣበቀ አርማ ነዉና መንግስት በተለዋወጠ ቁጥር አይለዋወጥም። ዛሬ ወያኔ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የገባዉ የማይታረቅ ቅራኔም የሚመነጨዉ ከዚሁ ከወያኔ ግራ የተጋባ እዉነታ ነዉ። የዚህ ዘመን ትዉልድም ሆነ ለዚህ ዘመን ትዉልድ አገርና ሰንደቅ አላማ አስረክቦ ያለፈዉ የቀድሞዉ ትዉልድ ሰንደቅ አላማዬ ብሎ የሚጠራዉና ወያኔ የኢትዮጵያ ባንዲራ እያለ የሚጠራዉ ነገር የተለያዩ ናቸዉ።
ባለፉት 75 አመታት አራት ኪሎ ቤ/መንግስትን የተቆጣጠሩት ሦስት ኃይሎች ማለትም የቀኃስ፤ የደርግና የወያኔ አገዛዞች ሁሉም የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ከራሳቸዉ ጋር ለማያያዝ ሞክረዋል። በንጉሡና በደርግ ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የይሁዳ አንበሳና የወታደራዊዉ መንግስት አርማ ነበረበት፤ ሆኖም እነዚህ ሁለት አርማዎች ያረፈበት የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ በቤተመንግስትና ንጉሡና ፕሬዚዳንቱ በሚጓዙባቸዉ ኦቶሞቢሎች ላይ እንጂ ሌላ ቦታ አይታዩም ነበር። በመላዉ አገሪቱ በየቀኑ ጧት እየወጣ ማታ ሲመሽ የሚወርደዉና በየግለሰቦች ቤት የሚገኛዉ ሌጣዉ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀዩ ሰንደቅ አላማ ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብም ሰንደቅ አላማዬ ነዉ ብሎ የሚያምነዉና የሚቀበለዉ ይህንኑ ምንም አይነት ባዕድ አካላ የሌለበትን አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማ ነዉ።
ወያኔዎች ጫካ ዉስጥ ሆነዉ የትጥቅ ትግል በሚያካሄዱበት ወቅት ያነገቡትና ነጻ አወጣን ባሉበት ቦታ ሁሉ የሰቀሉት የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ሳይሆን የህወሓትን ባንዲራ ነበር። ከብዙ መረጃዎች እንደተረዳነዉ ወያኔዎች የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አንደ ተራ ጨርቅ ቆጥረዉ ዕቃ መጠቅለያ አድርገዉት ነበር፤ ይህ ደግሞ የለየለት የጥላቻና የንቀት ምልክት ነዉ።
በአርግጥም ዋና ዋናዎቹ የወያኔ መሪዎች እነ ነመለስ ዜናዊና እነ ስብሐት ነጋ ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ህዝብ ይጠሉ ስለነበር ለነሱ ትልቁ ቁም ነገር ህወሐትና የዘረኝነት ምልክት የሆነዉ የህወሓት ባንዲራ ነዉ እንጂ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አልነበረም። ይህ ፀረ ህዝብና ፀረ አገር ባህሪያቸዉ ደግሞ ጫካ ዉስጥ ብቻ ተወስኖ የቆየ ባህሪ ሳይሆን አዲስ አበባ ገብተዉ ክህዝብ ጋር ሲቀላቀሉም በግልጽ የታየና ምን ግዜም ሊደበቅ የማይችል ባህሪይ ነዉ። የወያኔዉ ቁንጮ መለስ ዜናዊ እኛ ኢትዮጵያዉያን የምናከብዉንና የምንወደዉን ሰንደቅ አላማ “ጨርቅ” ብሎ መጥራቱ አዲስ የጀመረዉ ነገር ሳይሆን ከጫካ ይዞት የመጣዉ የተለመደ አባባል ነዉ። መለስ ዜናዊ ይህንን ጸያፍ ድፍረቱንና ፀረ ሰንደቅ አላማነቱን ለማረሳሳት የባንዲራ ቀን ብሎ ቢያዉጅም የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ልጆቹ፤ አባቶቹ፤ አያቶቹና ቅድም አያቶቹ የተሰዉለት ሰንደቅ አላማ በአለባሌ ሰዉ አንደበት “ጨርቅ” ተብሎ የተጠራበትን ቀን ምን ግዜም አይረሳም።
ከቅርብ ግዜ ወዲህ የወያኔ ዘረኞች ኢትዮጵያዉያንን በተለይም በዉጭ አገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን ባንዲራቸዉን አያከብሩም ወይም ባንዲራዉን አዋረዱ እያሉ መክስስ ጀምረዋል። በነገራችን ላይ ከወያኔዎችና ከጥቂት ሆዳም ተከታዮቻቸዉ ዉጭ የኢትዮጵያ ህዝብ አገር ዉስጥም በዉጭ አገሮችም በሰንደቅ አላማዉ ላይ ያለዉ አቋም ተመሳሳይ ነዉ። ወያኔ ሰንደቅ አላማዉ ላይ ባዕድ አካል ለጥፎ ከዛሬ ጀምሮ ሰንደቅ አላማችሁ ይህ ነዉ ብሎ አዋጅ ሲያወጣ አዋጁን የሰማለት አንድም ሰዉ አልነበረም። እንዲያዉም ህዘብ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ፤ ሰርግ ሲደግስ፤ ኳስ ጨዋታ ሲሄድና በተለያዪ ቦታዎች ደስታዉንና ኃዘኑን ሲገልጽ አንግቦ የሚወጣዉ የወያኔን ባንዲራ ሳይሆን አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀዩን ሰንደቅ አላማ ነበር። ወያኔ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ የቀየረዉ በጠመንጃ ሀይል እንደሆነ ሁሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን የማይወደዉንና በሀይል የተጫነበትን ባንዲራ ተቀብሎ እንዲኖር ያደረገዉም በጠመንጃ ሀይል ነዉ።
ለመሆኑ እነሱ እራሳቸዉ የለየላቸዉ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ጠላት የሆኑት የወያኔ መሪዎች በዉጭ አገሮች የሚኖሩና አክርረዉ የሚቃወሟቸዉን የኢትዮጵያ ልጆች ባንዲራዉን አዋረዱ እያሉ ተደጋጋሚ ክስ የሚያሰሙት ለምንድነዉ? አንዳንድ ከህልዉናቸዉ ይልቅ ለማይጠረቃዉ ሆዳቸዉ ያደሩ ደካማ ግለሰቦችስ ይህንን የወያኔ መሠረተ ቢስ ክስ እየሰሙ አንደ ገደል ማሚቶ ደግመዉ ደጋግመዉ የሚያስተጋቡት ለምንድነዉ? አገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የተለያዩ ባንዲራዎች ሊኖራት እንደማይችል ሁላችንም እናዉቃለን። ለመሆኑ ይህ እኛ ሰንደቅ አላማ እነሱ ባንዲራ እያልን የምንጠራዉ ነገር አንድና ተመሳሳይ ነዉ? ወያኔና በየቦታዉ ያስቀመጣቸዉ የገደል ማሚቶዎች ከሁሉም ነገር አስቀድመዉ መመለስ ያለባቸዉ ይህንን ጥያቄ ነዉ። እኛ ኢትዮጵያዉያን ከህጻንነታችን ጀምሮ የኛ ነዉ እያልን ያሳደገንን፤ የመራንን፤ አቅጣጫ ያሳየንነና በተለይ በልጅነታችን ት/ቤት እያለን ጧት በክብር ሰቅለን ማታ ላይ በክብር እያወርድን በክብር እናስቀምጥ የነበረዉን አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ሰንደቅ አላማችንን ማክበርና መዉደድ ብቻ ሳይሆን ለዚህ ሰንደቅ አላማ ዘለዓለማዊነት አንድ ህይወታችንን እንሰጣለን። ሰንደቅ አላማዉን የማያከብር ህዝብ የለም፤ እኛም ኢትዮጵያዉያን ሰንደቅ አላማችንን እንወዳለን፤ እናከብራለንም፤ የምንወደዉና የምናከብረዉ ሰንደቅ አላማ ግን ባዕድ አካል የተለጠፈበትን የወያኔን ባንዲራ ሳይሆን የነፃነታችን፤ የእንድነታችን፤ የሰላማችንና የመዋዕትነታችን ምልክት የሆነዉን አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀዩን ሰንደቅ አላማ ነዉ። ይህንን ሰንደቅ አላማ ደግሞ እኛ ኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳንሆን ይህንን የጥቁር ህዝብ የነጻነትና የመስዋዕትነት ታሪክ ምልክት የሆነ ደማቅ ሰንደቅ አላማ አያሌ አፍሪካዉያንም ያከብሩታል። ለምሳሌ የስምንት የአፍሪካ አገሮች ባንዲራ አቀማመጡ ይለያያል አንጂ ቀለሙ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ነዉ፤ ከዚህ በተጨማሪ የሌሎች 23 አፍሪካ አገሮች ባንዲራ ደግሞ ቀዩና አረንጓዴዉ ቀለም አለበት። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ሰንደቅ አላማችን የፓን አፍሪካ ባንዲራ እየተባለ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮችም የሚከበርና የብዙ አፍሪካ አገሮች ሰንደቅ አላማ መሰረት መሆኑን ነዉ።
የወያኔ ዘረኞች ኢትዮጵያ ዉስጥ የነበሩትንና በዉጭ አገሮች የሚገኙ አማራጭ የመረጃ ምንጮች ሁሉ ጥርቅም አድርገዉ ዘግተዉ እንደቤት ዉስጥ ዕቃቸዉ በሚቆጣጠሩት ቴሌቪዥን፤ ሬዲዮና ጋዜጣ “በሬ ወለደ” አይነት ዉሸታቸዉን ጧትና ማታ በተደጋጋሚ አየተናገሩ ለግዜዉም ቢሆን ህዝብን ማደናገር ይችሉ ይሆናል። ሰንደቅ አላማዉን የሚወደዉንና የሚያከብረዉን ኢትዮጵያዊም እነሱን ስለተቃወመ ብቻ ባንዲራዉን አዋረደ እያሉ ህዝብን ሊያታልሉ አንዳንድ ወደ ገባዎችንና ጥቂት የዋሆችን ሊያሳምኑ ይችሉ ይሆናል። ሆኖም የኢትዮጵያን ህዝብ እንወዳለን ፤ ለኢትዮጵያ አንድነት እንቆማለን፤ የዚህ አንድነት ምልክት የሆነዉን ሰንደቅ አላማም እናከብራለን አያሉ ታቦት ተሸክመዉ ቢምሉም የሚያምናቸዉ ቀርቶ ከጉዳይ ቆጥሮ የሚሰማቸዉ አንድም ዜጋ የለም። የወያኔ ዘረኞችና ቡችሎቻቸዉ የሚባቸዉ ቢሆን ኖሮ ዉስጣችን ያለዉን ከፍተኛ የአገር፤ የወገን፤ የባንዲራና የሉዓላዊነት ስሜት ደግመን ደጋግመን እንነግራቸዉ ነበር፡ ሀኖም እነሱን ከማስወገድ ጀምሮ አገራችንን እስከማረጋጋት ድረስ ብዙ አስቸኳይ የሆነ አገራዊ አደራና አገራዊ ስራ ይጠብቀናልና ለዛሬዉ እዚህ ላይ እናብቃ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ያሸንፋል!

ሰበር ዜና – የቅ/ሲኖዶሱን ልዕልናና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን መፃረራቸውን የቀጠሉት አቡነ ማትያስ ማኅበረ ቅዱሳንን ‹‹የቤተ ክርስቲያን ቅኝ ገዥ›› አሉት – ‹‹አባ ማትያስ አላበደም፤ በዚኽ መግለጫ እንድትሠሩበት ነው የምነግራችኹ›› ሲሉም በማኅበሩ ላይ የጥፋት መልእክታቸውን ዐዋጁበት!

November 16,2014
  • ጥቂት አማሳኞች በማንጨብጨብ ሲከተሏቸው፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱን ጨምሮ ብዙኃን ጉባኤተኞች በድንጋጤና በተደምሞ አዳምጠዋቸዋል፡፡ ፓትርያርኩ በቀቢጸ ተስፋ ውስጥ እንዳሉም አመላካች ኾኗል፡፡
  • ማኅበረ ቅዱሳን÷ በጉባኤያት፣ በኅትመትና በኤሌክትሮኒክስ የስብከተ ወንጌል ስርጭት፣ በቅዱሳት መካናት ልማት፣ በአብነት ት/ቤቶችና በካህናት ማሠልጠኛዎች ድጎማና ሞያዊ እገዛዎች ያከናወናቸው ተግባራት በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ሪፖርት በስፋት ተዳስሰዋል፤ ጉባኤተኞች ማኅበሩ ላስመዘገባቸው የሥራ ፍሬዎች ደማቅ ድጋፋቸውን ገልጸዋል፡፡
his-hholiness00ዛሬ፣ ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብሰባ አዳራሽ በተጀመረው ፴፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ላይ የጉባኤ መክፈቻ ቃለ በረከት እንዲሰጡ የተጋበዙት ፓትርያርክ አባ ማትያስ፣ ማኅበረ ቅዱሳንን ‹‹የቤተ ክርስቲያን ቅኝ ገዥ›› በማለት ‹‹በቁጥጥር ሥር እንዲውል›› ቅስቀሳ እንዳካሔዱበት ተሰማ፡፡
ፓትርያርኩ የጉባኤ መክፈቻ ‹ቃለ በረከታቸው› ማሳረጊያ ላደረጉት ቅስቀሳ መሰል ንግግራቸው መግቢያ ያደረጉት፣ ‹‹ስለ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ኹኔታ ልገልጽ እፈልጋለኹ፤ ይህ ጉባኤ በዓመት አንዴ የሚገኝ ነው፤ ዕድሉ እንዲያመልጠኝ አልፈልግም፤›› በሚል ቃለ አጽንዖት ነበር፡፡
ከዚያም ‹‹ቤተ ክርስቲያናችን በቅኝ ገዥዎች ተይዛለች›› ካሉ በኋላ ‹‹ቅኝ ገዥው ማን ነው?››ሲሉ ጠይቁ፡፡ ምላሹን ራሳቸው ሲሰጡ፣ ‹‹ኹላችኁም የምታውቁት አንድ ማኅበር ነው›› ሲሉ ጠቆሙ፡፡ ‹‹በምን?›› ሲሉ ዳግመኛ ጠየቁና ‹‹በገንዘብ፤ በራስዋ ገንዘብ፤ ይኼን እንድታውቁ እፈልጋለኹ›› ሲሉ መለሱ፤ ‹‹እኔ ይኽን ጉዳይ ከራሴ አወርዳለኹ፤ የቤተ ክርስቲያናችን ገንዘቧ፣ ክብሯ ተወስዷል፤›› በማለትም አስረገጡ፡፡
በአምናው ዓመታዊ ስብሰባ፣ ‹‹ማኅበሩ በቁጥጥር ሥር እንዲውል›› አጠቃላይ ጉባኤው ውሳኔ አሳልፎ ነበር ያሉት ፓትርያርክ አባ ማትያስ፣ ‹‹ገንዘቡ፣ ንብረቱ በቁጥጥር ሥር እንዲውል የወሰናችኁት አንድም አልተፈጸመም፤ እነርሱም ፈቃደኛ አልኾኑም፤ ማን ጠይቆ?›› ሲሉ ኹኔታው ከአቅማቸው በላይ እንደኾነ ገልጸዋል፡፡
አስከትለውም ‹‹ቤተ ክርስቲያን ከቅኝ ተገዥነት ትውጣ፤ ካህናቱ ከመከራ ይውጡ›› በማለት መልእክታቸውን በማንኛውም ቦታ እንደሚያስተላልፉ ከተናገሩ በኋላ፣ በሓላፊነት የተቀመጡት ‹‹ይህችን ቤተ ክርስቲያን ለመጠበቅ፤ አንዷን ቅድስት፣ ኦርቶዶክሳዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን ልመራ እንጂ ኹለት ቤተ ክርስቲያን የለችም፤›› ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ‹‹የቤተ ክርስቲያን ቅኝ ገዥ ነው፤›› ባሉት ማኅበረ ቅዱሳን ላይ የጥፋት መልእክታቸውን ያስተላለፉት በሚከተለው መልክ ነበር፡-
‹‹እኔ ብቻዬን የምሠራው ነገር የለም፤ በዚኽ መግለጫ እንድትሠሩበት ነው የምነግራችኹ፤ አባ ማትያስ አላበደም፤ መልእክቴን እያስተላለፍኹ ነው ያለኹት፤ መልእክቴን ተቀበሉ ብዬ እማፀናችኋለኹ፡፡››
የፓትርያርኩ አቋም ብዙም ያልተጠበቀ አልነበረም፡፡ ይኹንና የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ከተቀመጡበት አካባቢ ጥቂት አማሳኞች ቢያንጨበጭቡላቸውም በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱና በጉባኤተኞች ላይ ሰፍኖ ይታይ በነበረው መደመምና ድንጋጤ የተዋጠ እንደነበር ተገልጧል፡፡ ‹‹የመልካም አስተዳደር አስተሳሰብን ማበልጸግ›› በሚል ሰበብ መስከረም ፳፯ ቀን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ፣ መስከረም ፳፱ ቀን በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በማኅበረ ቅዱሳንና በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ላይ ከርእሱ በመውጣት በከፈቱት ዘመቻ፤ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁንና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱን ጨምሮ ከቤተ ክርስቲያናችን ከፍተኛ ሓላፊዎችና በብዙኃን መገናኛ አውታሮች ከተስተጋባው የብዙኃን አገልጋዮችና ምእመናን ብርቱ ተቃውሞ የተነሣ በቀቢጸ ተስፋ ውስጥ እንዳሉ አመላካች ተደርጎም ተወስዷል፡፡
የጉባኤተኞችን ቀልብና ስሜት ለመግዛት የተጠቀሙበት ቅስቀሳ ‹‹ከልጆቹ ጋራ እልክ መጋባታቸውን›› ያሳያል ያሉ አንዳንድ ተሳታፊዎች፣ አባ ማትያስ በፕትርክና በተሾሙበት ቀን አበ ብዙኃን ለመኾን ቃል የገቡበትን መሐላ በግላጭና በተደጋጋሚ ከመጣስ በላይ እብደት ባለመኖሩ በተጣለባቸው ታላቅ የቤተ ክርስቲያን ሓላፊነትና አባትነት ጉዳዩን በጥሞናና በተረጋጋ መንፈስ ሊመለከቱት እንደሚገባ ያሳስባሉ፡፡ የአጠቃላይ ጉባኤው መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ካህናት በጸሎተ ወንጌል ሲከፈት ፓትርያርኩ በንባብ ያሰሙት ቃልም‹‹ወንድምኽ ቢበድልኽ ምከረው፣ ይቅር በለው›› (ማቴ. ፲፰÷፲፭) የሚል ነበር – የማኅበረ አመራር ከፓትርያርኩ ጋራ የውይይት መርሐ ግብር እንዲያዝለት በተደጋጋሚ ባመለከተበት ኹኔታ ቀርቦ የተጠየቀበትና ምላሹ ተሰምቶ ጥፋተኝነቱ የተረጋገጠበት በደሉ ባይታወቅም!
MK on the 33rd gen assembly of Sebeka Gubae
(ፎቶ: ማኅበረ ቅዱሳን)
አባ ማትያስ የጠቀሱት ‹‹ገንዘብና የንብረት ቁጥጥር›› ጉዳይ በተመለከተ አጠቃላይ ጉባኤው ባለፈው ዓመታዊ ስብሰባው ያወጣው የጋራ ያአቋም መግለጫው፣ ‹‹እየተሠራበት ያለውን የገቢና የወጪ ሒሳብ በቤቱ የቁጥጥር አገልግሎት እያስመረመረ፣ በቤቱ ሞዴላሞዴሎች እየተገለገለ ማእከልንም በመጠበቅ አገልግሎቱን እንዲቀጥል›› ያስገነዘበበት ነበር፡፡
ማእከላዊነትን ጠብቆ ከማገልገል አንጻር፣ ማኅበሩ በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. ለሦስተኛ ጊዜ በቅዱስ ሲኖዶስ ተሻሽሎ በጸደቀለት መተዳደርያ ደንቡ መሠረት ከዋናው ማእከል አንሥቶ በየአህጉረ ስብከቱ በዘረጋው መዋቅሩ ከየአህጉረ ስብከቱ ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ በመመካከርና መመሪያ በመቀበል የቤተ ክርስቲያንን ኹለንተናዊ አገልግሎት የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ እንዳለ ገልጧል፡፡ በየጊዜው የአገልግሎት ዕቅዱን በማሳወቅ በየስድስት ወሩ የአገልግሎት የሥራ ዕቅድ አፈጻጸምና የሒሳብ ሪፖርት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ያቀርባል፤ ተገቢውን መመሪያም ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ይቀበላል፡፡
የገቢና የወጪ ሒሳብ እንቅስቃሴውን ስለመቆጣጠርም፣ ሒሳቡን በየጊዜው በውስጥ ኦዲተር እያስመረመረ ቆይቶ በየዓመቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ባለው ሕጋዊ የውጭ ኦዲተር አስመርምሮ ለሚመለከታቸው የቤተ ክህነት አካላት እያቀረበ የሚሰጠውን መመሪያ ተከትሎ አገልግሎቱን በማከናወን ፳፫ ዓመታትን ማስቆጠሩን ገልጧል፡፡
የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የቁጥጥር አገልግሎት የማኅበሩን የገቢና ወጪ እንቅስቃሴ መቆጣጠር በፈለገበት ጊዜ ኹሉ ማኅበሩ በውስጥ ይኹን በውጭ ኦዲተር ያስመረመረውን ሒሳብ ማየት አልያም በማንኛውም ጊዜ በራሱ ኦዲተሮች ወይም የውጭ ኦዲተሮች አወዳድሮ በመመደብ ማስመርመር እንደሚችል አበክሮ የገለጸው ማኅበረ ቅዱሳን፣ ስንኳን የራሱን የሒሳብ አያያዝ ቀርቶ የቤተ ክርስቲያናችን የሒሳብ አሠራር በሙሉ ዘመናዊና ለኦዲት የሚመች እንዲኾን የሚያግዝ ማኅበር መኾኑን አረጋግጧል፡፡
ይኹንና የማኅበሩ የሒሳብ አሠራር ዘመናዊና በሕግ ተቀባይነት ያለው የኹለትዮሽ የሒሳብ አመዘጋገብ ሥርዐት(double entry accounting system) የሚከተል በመኾኑ፤ እጅግ ኋላ ቀር፣ በዘመናዊ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ሥርዐትም ተቀባይነት እንደሌለው ቋሚ ሲኖዶስና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት ሰሞኑን በቀረበላቸው የሦስት የበጀት ዓመታት የውጭ ኦዲት ምርመራ ሪፖርት አጋጣሚ ያመኑበትን የቤተ ክህነቱን የነጠላ የሒሳብ አመዘጋገብ ሥርዐት(single entry accounting system) ለመከተል እንደሚቸግረው በተደጋጋሚ አስተያየቱን አቅርቧል፡
በተመሳሳይ አኳኋን የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የገንዘብና ንብረት ገቢና ወጪ መመዝገቢያ ሰነዶች (ሞዴላሞዴሎች) ሥራ ላይ ማዋል የማኅበሩን የሒሳብ አሠራር ወደ ኋላ የሚጎትት እንደኾነ ነው የገለጸው፡፡ ማንኛውም ሕጋዊና ዘመናዊ የሒሳብ ምርመራ(ኦዲት) አሠራር በተለይም የውጭ ኦዲት የኹለትዮሽ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ሥርዐትን ተግባራዊነት በተሻሻለ ደረጃ የሚጠይቅ በመኾኑና በዚኽ የኦዲት ሥርዐት የቤተ ክህነቱ ሞዴላሞዴሎች ተቀባይነት እንደሌላቸው ሞያዊ አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡
እስከ አኹን ባለው አሠራርና እውነታ ሞዴላሞዴሎቹን መጠቀም የቤተ ክርስቲያናችንን ገንዘብ፣ ሀብትና ንብረት ከብኩንነት፣ ከመዘረፍና ከመጭበርበር ማዳን እንዳልተቻለ ጥናታዊ ሪፖርቶች ያመለክታሉ፡፡ የሞዴላሞዴል አሠራር (የነጠላ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ) ማንኛውንም ወጪ(ቋሚ ዕቃም ቢኾን) በወጪነት የሚመዘግብ እንጂ አንድ ተቋም ስላለው ሀብት በአግባቡ የሚያሳይ አይደለም፡፡ የፓትርያርኩንም ኾነ የቱኪና ጯኺ አማሳኞች የ‹‹ተቆጣጠሩት›› ዐዋጅ የሚረዳና ጥያቄያቸውን የሚመልስም አይደለም፡፡
በርግጥም ጥያቄው የማኅበሩን የገንዘብና ንብረት እንቅስቃሴ በአግባቡ ለመቆጣጠርና ተቋማዊ ለውጡን እንደ ጥርስና ከንፈር ተደጋግፎ የማራመድ ከኾነ፣ በማንኛውም የዘርፉን ሞያ በሚረዳ ወገን ዘንድ ተቀባይነት ያለው የመፍትሔ ሐሳብ በማኅበሩ ቀርቧል፡፡ ይኸውም ቁጥጥሩ፡-የማኅበር ሕገ ተፈጥሮን የተገነዘበ፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሕግንና የቁጥጥር መርሕን የጠበቀ፣ ለቁጥጥር አመቺ የኾነና በሕግም ተቀባይነት ያላቸውን ዘመናዊ መንገዶች በመከተል ላይ ያተኩራል፡፡
ከማኅበር ሕገ ተፈጥሮ አኳያ፣ ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክህነት በሚመደብ በጀት እንደሚተዳደሩት መምሪያዎች ወይም ድርጅቶች ሳይኾን በበጎ ፈቃድ ክፍተቶችን ለመሙላት፣ አባቶችን በፍቅር ለመታዘዝና ለማገዝ የተሰባሰቡ አባላቱ ያቋቋሙት ራሱን የቻለ የቤተ ክርስቲያን አጋዥና ድጋፍ ሰጭ አካል በመኾኑ በአባላቱ መዋጮና በበጎ አድራጊዎች ርዳታ/ድጋፍ ነው የሚንቀሳቀሰው፡፡ የማኅበሩን ሒሳብ ሊያንቀሳቅስና ንብረቱን ሊያስተዳድር የሚችለው ጠቅላላ ጉባኤው የመረጠው የማኅበሩ አባልና አካል የኾነ ብቻ ነው፡፡
ተቆጣጣሪው አካል በዕለት ተዕለት የሥራ እንቅስቃሴው ውስጥ ከገባ ዓለም አቀፍ የቁጥጥር መርሕን ይጥሳል፡፡ ይኹንና ተቆጣጣሪው አካልቁጥጥሩን ሊያጠብቁለት የሚችሉ ሥርዐቶችን መዘርጋትና ተግባራቱን በአግባቡ መከታተል ብቻ የማኅበሩን አገልግሎት፣ የገንዘብና ንብረት እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ያስችለዋል፡፡
በአግባቡ ከተደራጀ ተቆጣጣሪ አካል የሚጠበቁት እኒኽ የሥርዐት ዝርጋታዎችና ክትትሎችም፡-
  • የኦዲት ሥራን ማሠራትና ከውጤቱ ተነሥቶ ተገቢውን አስተያየትና መመሪያ መስጠት፤
  • ዕቅዶችንና ሪፖርቶችን በመገምገም አስተያየት መስጠት፤
  • የገንዘብና ንብረት የገቢና የወጪ ሰነዶች ኅትመት በተቆጣጣሪነት መፍቀድ፤
  • የባንክ ሒሳብ እንዲከፈት ማኅበሩ ሲጠይቅ ለባንክ ማሳወቅ፤
  • የባንክ ፈራሚዎችን ስም ማኅበሩ ሲያቀርብ ለባንክ ማሳወቅ፤
  • በማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤያት ላይ እየተገኙ ሐሳብን መስጠት… የመሳሰሉት ናቸው፡፡
በማኅበሩ መተዳደርያ ደንብ መሠረት ማኅበሩ አገልግሎቱን የሚያቆመው፣ ትክክለኛነቱ በቅ/ሲኖዶስ በተረጋገጠ የጠቅላላ አባላቱ ውሳኔ አልያም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ ሲኾን ያፈራው የማይንቀሳቀስ፣ ተንቀሳቃሽ የኾነና ጥሬ ገንዘብ በሙሉ ንብረትነቱና ሀብትነቱ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደኾነ ሰፍሯል፡፡ ማኅበሩ ከሚከተለው የሒሳብ አያያዝ ሥርዐት አኳያ የንብረት መሸጥና መለወጥ፣ ቱኪዎቹ እንደሚሉት ‹‹ማሸሽ›› ሳይኾን፤ በአጠቃላይ ንብረቱ ላይ የሚያመጣው ለውጥም የለም፤ የሚጨምረውና የሚቀንሰው ነገር በግልጽ በሚረዳ መንገድ በአሠራሩ የሚታይ ነውና፡፡፡፡
በአጠቃላይ የማኅበረ ቅዱሳን የማገልገል አቅም ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ በቤተ ክርስቲያናችን ከፍተኛ አካል በታመነበትና የሚገኝበትን የዕድገት ደረጃ የሚመጥን፣ ለቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ዕድገት የሚጠቅም፣ የላቀና የተሻለ መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለማበርከት የሚያስችለው መዋቅራዊ አደረጃጀትና ምቹ ኹኔታ እንዲፈጠርለት እየተጠየቀ ባለበት ወቅት፣ የፓትርያርክ አባ ማትያስ ቅኝ ገዥ ነው፤ አጥፉትቅስቀሳ በእጅጉ አሳዛኝና በብርቱ ሊታሰብበት የሚያስፈልግ ነው፡፡
ደጉ ነገር! በዛሬው የአጠቃላይ ጉባኤው ዓመታዊ ስብሰባ በስፋት የተደመጠው የጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አጠቃላይ ሪፖርት፣ ይህን በአማሳኞች፣ ጎጠኞች፣ አድርብዬ ፖሊቲከኞችና የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ግንባር ቀደም መሪዎች ክፉ ምክር የተፈጠረ እልከኝነትና ምናልባትም የውጭ ኃይልን አጀንዳ በሌላ ገጽታ የሚገፋ የውክልና ጫና የወለደው ክሥ ከንቱ የሚያደርግ መኾኑ ነው፡፡
ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በጥቅልና በዝርዝር ያቀረቧቸው የማኅበሩ የሥራ ፍሬዎች፣ አባ ማትያስ ማኅበሩን በቅኝ ገዥነት እንደወረፉት ሳይኾን፤ለታሪካዊት፣ ብሔራዊትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን ክብርና መብት መጠበቅ፤ ለትምህርተ ሃይማኖቷ፣ ሥርዐተ እምነቷና ክርስቲያናዊ ትውፊቷ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሳይበረዝና ሳይከለስ መተላለፍ ትጉህ ዘኢይነውም ኾኖ ጥብቅና መቆሙን ነው፡፡
ከአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እስከ ልዩ ጽ/ቤት በተዘረጋው የአማሳኞች፣ ጎጠኞችና አድርብዬ ፖሊቲከኞች የሙስና ኤምፓየር የቤተ ክርስቲያንን‹‹ክብሯንና ገንዘቧን በቅኝ ገዥነት የወሰደ›› ሳይኾን፤ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ማእምራን ፋንታኹን ሙጬ የዘንድሮውን የአህጉረ ስብከት ውጤታማነት በገለጹበት ቋንቋ ‹‹የቤተ ክርስቲያናችን ምጣኔ ሀብት በዓለት ላይ የተመሠረተ ይኾን ዘንድ›› የአባላቱንና የበጎ አድራጊ ምእመናንን ጉልበት፣ ሞያና ገንዘብ አስተባብሮ ስኬታማ የልማት ሥራ የሠራ መኾኑን ነው፡፡
‹‹ካህናቱን ለጭቆናና ለመከራ ቀንበር የዳረገ›› ሳይኾን ከማንኛውም ክፍያ ነፃ በኾነና ያለስስት በልግስና በሚናኘው ሞያዊ አበርክቶው፣ ለተቀደሰው የክህነት ሞያቸው መከበርና ለኑሯቸው መመቻቸት የተጠበበና ከአማሳኞች፣ ጎጠኞችና ዐምባገነኖች ጋራ በየመድረኩ ፊት ለፊት የተሟገተ መኾኑን ነው፡፡
ፓትርያርኩም ኾነ መላው ኦርቶዶክሳዊ የሚጨነቅለት የኦርቶዶክሳውያን ቁጥር መቀነስ አሳስቦት፣ በንግግር ብዛት ሳይኾን በተግባር፣ ሚልዮኖችና መቶ ሺሕዎች የቃለ እግዚአብሔርን ማዕድ በሚቋደሱባቸው ሐዋርያዊ ጉዞዎችና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዙ አውታሮች ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋቱንና ማጠናከሩን ነው፡፡

Friday, November 14, 2014

ፌደራል ፖሊሶች ለሚፈጽሟቸው ግድያዎች ተጠያቂው ማን ነው?

November 14,2014
ከዳዊት ሰለሞን
dawitይህ ጥያቄ በቀጥታ በመንግስት ትዕዛዝ የተፈጸሙ ግድያዎችን አይመለከትም፡፡እንደውም በፓርላማ ከቀረበው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ‹‹በግዳጅ ላይ ያለ የመንግስት ታጣቂ ለሚፈጽመው ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆን ››የሚሞግት ነው፡፡
ፓርላማው 446 ለ 1 የሚመራ በመሆኑም ገዢው ፓርቲ የፈለገውን አዋጅ የማውጣት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡በዚህ ገጽ ግን ለማንሳት የወደድኩት ታጣቂዎች ከስራ ገበታቸው ውጪ እየፈጸሟቸው የሚገኙ ግድያዎች ሀላፊ ማን ይሆናል የሚለውን ነው፡፡
ንፋስ ስልክ አካባቢ የመንግስት የሰላም አስከባሪ አባል የነበረ አንድ መቶ አለቃ ጎረቤቶቹን በ35 የክላሽ ጥይት መግደሉና ህጻናቱን ያለ ወላጅ ማስቀረቱ አይዘነጋም፡፡
መቶ አለቃው ከታሰረ በኋላ በልዩ እንክብካቤ ተይዞ ወላጆቻቸውን ባጡ ህጻናት ላይ ይዘት እንደነበርና በኋላም አመለጠ ተባለ፡፡መቶ አለቃው መጨረሻ ላይ ስለመያዙ ተነገረ፡፡
ባህርዳር የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አንዘነጋውም፡፡አፍቅሪያታለሁ ያለ ፌደራል ፖሊስ የ18 ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሞተ የሚል ወሬ ተናፈሰ፡፡
ቂርቆስ መንደር በምትገኝ የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር እንዲሁ የእኔ የሚላትን ሴተኛ አዳሪ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ በማግኘቱ ፌደራሉ በሁለት ጥይት ደረቷን መትቶ ለህልፈት ዳረጋት ፣ከሴትየዋ ጋር የነበረው ጎልማሳም እግሩን በጥይት ለመቆረጥ በቅቷል፡፡
ይህ ፎቶ ግራፍም በተመሳሳይ መንገድ በፌደራል ፖሊስ ህይወቱን በግፍ ስለ ተነጠቀ ወጣት የሚጮህ ነው፡፡
ጅማን በእንባ፣በድንጋጤና በተቃውሞ የሞላ ክስተት የተስተናገደው በፌደራል ፖሊስ ነው፡፡በምሽት ሰው ቤት ሰብሮ የገባው ፖሊሱ አንዲት አይነ ስውር እናትና ልጃቸውን ቀጥፏል፡፡
ግለሰቡ ስለ መያዙም ተነግሯል፡፡ግን ይህ ነገር በገዳዮቹ መያዝ ብቻ የሚያበቃ መሆን የለበትም፡፡ተጠያቂነቱ ወደ ላይም መውጣት አለበት፡፡መሳሪያ መያዝ የማይገባቸው፣ሰብዓዊነት ምን ማለት እንደሆነ የማይረዱ፣ግደሉ ሲባሉ ከመግደል የማያመነቱ፣መሳሪያ ሲጨብጡ ጭንቅላታቸውን ቃታው ጋር የሚያደርጉ ሰዎችን መለዮ እያለበሱ ስልጣናቸውን ለማራዘም እስከጠቀሟቸው ድረስ ስለሚፈጽሙት ዘግናኝ ድርጊት ደንታ የሌላቸው አካላትም መጠየቅ ግድ ይላቸዋል፡፡
የሟቾቹ ደምም በተኳሾቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ ባሸከሟቸው ሀይሎች ላይም ይጮሃል፡፡

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ፖሊስ ጣቢያዎችን እንዲሰሩ ተጠየቁ

November 14,2014
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በየ አካባቢያቸው ለሚሰሩት አዳዲስ ፖሊስ ጣቢያዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ መጠየቃቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በየ አካባቢው የሚገኙት የፖሊስ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ በየ ቤታቸው ደብዳቤና የገንዘብ መክፈያ ቅጽ እየሰጡ ሲሆን ነዋሪዎቹ ገንዘብ እንዲከፍሉ የተጠየቁበትን ቅጽ ሳይሞሉ መመለስ አይችሉም ተብሏል፡፡

ደብዳቤው ላይ ባለው የፖሊስ ጣቢያው ስልክ ቁጥር ደውለን ያነጋገርናቸውና ስማቸውን ለመግለጽ ፈቃደኛ ያልሆኑ አንድ የፖሊስ አባል ‹‹ህዝቡን ለምን ፖሊስ ጣቢያ እንዲሰራ ታስገድዳላችሁ?›› በሚል ላነሳነላቸው ጥያቄ ‹‹ህዝቡኮ ራሱ ነው ሴት ልጆቻችን በሰላም መግባት አልቻሉም እያለ ያለው፡፡ ፖሊስ የህዝብ እስከሆነ ድረስ ህዝብ ፖሊስ ጣቢያ ቢያሰራ ምን ችግር አለው? ህዝቡ አልከፍልም ካለ ሊቀር ይችላል፡፡ እናንተ ግን ይህን እንደጥያቄ የምታነሱት ስብሰባው ላይ ስላልነበራችሁ ነው፡፡›› ብለውናል፡፡

ከወራት በፊት ‹‹ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ›› በሚል አደረጃጀት ህዝቡ በየቤቱና ከጎረቤት ጋር 1ለ5 በመደራጀት ከፖሊስ ጋር ግንኙነት እንዲኖረው የሚያዝ ህግ መውጣቱና ነዋሪዎቹንም ማደራጀት መጀመሩን ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወቃል፡፡


የሶዶ ከተማ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ካምፕ እንዲገቡ ተደረገ

November 13,2014
ከህዳር 6/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 10/2007 ዓ.ም በሶዶ ከተማ የሚደረገውን የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክቶ ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ወደ ካምፕ እንዲገቡ መደረጋቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ 

በመቶዎቹ የሚቆጠሩ ሴት፣ አዛውንትና ህጻናት ጎዳና ተዳዳሪዎች ሶዶ ውስጥ አራዳ ክፍለ ከተማ ተብሎ በሚጠራውና አዲስ እየተሰራ በሚገኘው ገለሜ የተባለ እስር ቤት ውስጥ በግዳጅ እንዲገቡ መደረጉን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ካምፕ ውስጥ የገቡትን የጎዳና ተዳዳሪዎችም የቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለሳምንት ቀለብ እንደሚያቀርብላቸውና ጉባዔው ካለቀ በኋላ ወደነበሩበት እንደሚመለሱም ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ለጉባኤው ሲባል ዜጎችን በግዳጅ ወደ ካምፕ ማስገባቱ ደኢህዴን በከተማዋ ልማት እንደተመዘገበና ህዝቡን ከድህነት እንዳላቀቀ ለማስመሰል ያደረገው አስነዋሪ ተግባር ነው›› ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ የወላይታ ዞን የአደረጃጀት ኃላፊ አቶ ታደመ ፈቃዱ ‹‹እስካሁን ሶዶ ከተማ ውስጥ መብራት ስለማይኖር በርካቶች ተዘርፈዋል፡፡ የተገደሉም አሉ፡፡ የከተማዋ ውበትም እምብዛም የተጠበቀ አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን ለማጽዳት እየተሯሯጡ ነው፡፡ መብራት ባልነበረበት ከተማ መንገዱ ሁሉ ባውዛ ሆኗል›› ሲሉ ስለሁኔታው አስረድተዋል፡፡

ለደኢህአዴን ጉባዔ ተብሎ የከተማዋ ውበት እንዲጠበቅና የጠፉት አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲስተካከሉ መደረጉም በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል ተብሏል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው አንድ የከተማዋ ነዋሪም ‹‹ህዝቡ በአገልግሎቶች መጥፋት ተማሯል፡፡ የከተማው ውበት ለሚኒስትሮቹ እንጅ ለእኛ አይደለም፡፡ እንዲህ ከሆነ ደኢህዴን በየ15 ቀኑ ጉባዔ ቢያደርግ ጥሩ ነበር›› ሲሉ ስለሁኔታው ገልጸውልናል፡፡

ለጉባዔው ሲባልም በጸጥታ ስም በተቃዋሚዎች ላይ ክትትል እየተጠናከረ ይገኛል ያሉት አቶ ታደመ ‹‹ከተማዋ በፖሊስ ተጥለቅልቃለች፡፡ ፖሊሶች በየ 10 ሜትሩ ቆመው ነው የሚታዩት፡፡›› ብለዋል፡፡

Thursday, November 13, 2014

ጊዜው የሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው!!!

November 13,2014
በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።
በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።
በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ … በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ …. እጦት።
እነዚህ ሁለት ተፃራሪ እውነታዎች ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች ለወሳኝ ፍልሚያ ፊት ለፊት መፋጠጣቸዉን በግልጽ ያሳያሉ። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነትና ባርነት፣ ፍትህና ጭቆና፣ ደስታና ሀዘን፣ ተስፋና ተስፋ መቁረጥ፣ ብልጽግናና ድህነት፣ እውቀትና ድንቁርና፣ ብርሃንና ጨለማ፣ ለወሳኝ ግጥሚያ ተፋጠዋል። ይህ ፍጥጫ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታን በመወሰን ረገድ አቢይ ሚና የሚኖረው ወሳኙ ግጥሚያ – ሕዝባዊ እምቢተኝነት – መጀመሩን አብሳሪ ነው። የነፃነት፣ የፍትህ፣ የተስፋ፣ የብልጽግና፣ የእውቀትና የብርሃን ወገኖች ነን የምንል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይህንን ፍልሚያ በድል መወጣት ግዴታችን ነው።
ወያኔ ታጋዮችን ቢያስር ትግሉን አያስርም። በእጦት ኑሮዓችን በማመሰቃቀል በድህነት ሊያንበረክከን ቢሻም፣ በፍጹም አንበረከክለትም። በተዘረፈ የድሆች ድካም ህንፃዎችን ቢገነቡም የራስ ባልሆነ ጌጥ አንኮራም። የወያኔ የሆነ የኛ አይደለም፤ የእነሱ መክበር የኛ መክበር አይደለም። ወያኔ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ገዢና ተገዢ፤ በዳይና ተበዳይ፣ ገፊና ተገፊ ናቸው።
ተበዳይና ተገፊ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘረኞች፣ ሙሰኞችና ከፋፋዮች የህወሓት ባለሥልጣኖቻቸውና ሎሌዎቻቸው ላይ ይነሳሉ። የተጀመረው ሕዝባዊ እምቢተኝነት አመቺ በሆኑ መንገዶች ሁሉ ይጧጧፋል።
የወያኔ ትዕዛዛትን መሻር፤ በሥራ ላይ መለገም፤ ግብር አለመክፈል፤ አድማ መምታት፤ የወያኔ ካድሬዎችን ማግለልና ማዋረድ፤ የነፃነት ኃይሎችን መደገፍ፤ የፓሊስና የጦር ሠራዊት አባላትን ማቅረብ እና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ እነሱም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማበረታታት፤ ህሊና ያላቸው የኢሕአዴግ አባላት የሕዝቡን ትግል እንዲያግዙ ማበረታታት … – እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ በርካታ የትግል ስልቶች ከአሁን ጀምሮ በተከታታይ በሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። የወያኔን የጭቆና ምሽግ ከውስጥ መሸርሸር፤ ከውጭ መደርመስ ይኖርበታል። የመሸርሸርና የመደርመስ ሥራዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል። ጊዜው የእምቢተኝነት ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የነፃነት ንቅናቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ አጠገቡ ባሉት መሪዎቹ አስተባባሪነት በአንድነት እንዲነሳ ጥሪ ያቀርባል፤ በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገው ሁለገብ ትግል በጽናት እንዲደግፉ ያሳስባል። ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው፤ እንወጣዋለንም!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Wednesday, November 12, 2014

የዞን 9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች አስራአንደኛ የፍርድ ቤት ውሎ

November 12,2014
በዛሬው እለት በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ 10 ተከሳሾቸን ጉዳይ ሊያይ የተሰየመው ችሎት በጦማርያኑ እና በጋዜጠኞቹ ላይ የቀረበውን ክስ አቃቤ ህግ አንዲያሻሽል ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡
ባለፈው ሳምንት የክስ ፋይሉን አስመልክቶ የህግ እና የፍሬ ነገር ችግር አለበት በሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ያቀረቡትን የተከሳሾች ጠበቆች አንዲሁም መሻሻል የሚገባው ነገር የለውም ያለውን የአቃቤ ህግን መልስ ተከትሎ ብይን ለመስጠት ተቀጥሮ በዳኞች ለውጥ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ የነበረው ችሎት ዛሬ ክሱ ላይ መሰረታዊ ማሻሻያ እንዲደረግ ብይን ሰጥቷል፡፡
ብይኑም በአጠቃላይ ሲታይ
1. በመጀመሪያው ክስ የጸረ ሽብር ህጉን አንቀጽ አራት በመጥቀስ በደፈናው የሽብር ስራ ተብሎ ቀርቦ ነበረውን ክስ አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ ክሱ ፈጸሙትን ወይም ሊፈጽሙ ያሰቡትን የሽብር ተግባር በአንቀጽ ሶስት መሰረት አቃቤ ህግ በዝርዝር አንዲያስቀምጥ መቼ እና እንዴት አንደፈጸሙት ተግባሩም ምን እነደሆነ አንዲገለጽ
2. የሽብር ቡድን ፣ ግንቦት ሰባት አንዲሁም ኦነግ በማለት በተለያየ ቦታ የተጠቀሱ ስሞች ከመኖራቸው ባሻገር ግልጽ የሆነ ነገር ባለመኖሩ የተባለው የሽብር ቡድን ማን እነደሆነ በግልጽ አንዲቀመጥ ( አቃቤ ህግ በክሱ አንድም ቦታ ላይ ዞን 9 የሚል ቃል አለመጠቀሙን ያስታውሷል)
3. ስትራቴጂ እና ተልእኮ በመቀበል የሚለው ክስ ምን አይነት ስትራቴጂ እና ምን አይነት ተልእኮ ከማን ለእነማን ተከሳሾች አንደሆነ በግልጽ እንዲቀመጥ
4. የገንዘብ ድጋፍን አስመልክቶ ለሽብር ተግባር ተቀበሉት የተባለው ገንዘብ ከማን እነደተላከና ለምን ሽብር ተግባር አንደዋለ በዝርዝር አንዲገለጽ
5. የተከሳሾችን የስራ ክፍፍል አስልመልክቶ አቃቤ ህግ አቃቤ ህግ ለይቶ እነማን ምን የሽብር ስራ ክፍፍል አንደነበራቸው ለይቶ እንዲያቀርብ
6. ህገ መንግስቱን በሃይል መናድ የሚለው ክስ በአንደኛ ክስ ላይ ከተጠቀሱ ተግባራት ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አንዲሆን እና ጉዳዩ በጸረ ሽብር ህጉ ብቻ አንዲታይ ብይን ሰጥቷል፡፡
በተመሳሳይ ፍርድ ቤቱ ሁለቱ ሴት ተከሳሾች ማህሌት ፋንታሁን እና ኤዶም ካሳዬን የማረሚያ ቤት አያያዝን አስመልክቶ ማረሚያ ቤት ሃላፌ ቀርበው መልስ አንዲሰጡ ባዘዘው መሰረት የማረሚያ ቤት ተወካይ መጥተው የእስረኞቹ አያያዝ እንደማንኛውም እስረኛ ነው ብለው የካዱ ሲሆን በተጨማሪም ማንኛውንም አይነት ችግር ካለ ከተከሳሾች ጋር በመነጋገር ለመፍታት ፍቃደኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የፍርድ ሂደቱን ላለማጓተት የተከሳሽ ጠበቆች ከማረሚያ ቤቱ ጋር አንዲነጋገሩ እና መፍትሄ ላይ እነዲደርሱ አንዲሁም ለውጥ ከሌላው ግን የተከሳሽ ቤተሰቦችን ምስክርነት ለመስማት የሚገደድ መሆኑን ገልጿል። አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ ተከሳሾች አንደተለመደው በሙሉ የስሜትና የአካል ደህንነት ላይ ሆነው ወዳጆቸን ሰላም ሲሉ እና እርስ በርሳቸው ሲወያዩ ተስተውለዋል፡።
ማስታወሻ - ዞን 9 የጦማርያን ቡድን ፍርድ ቤቱ የክስ ማሻሻል ትእዛዝ በበጎ ጎን የምንመለከተው ሲሆን የፍትህ ስርአቱ የሚታማበትን የተለመደውን ገለልተኛነት የማጣት ችግር አስወግዶ ጦማሪ ጓደኞቻችንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን ከክሱ በነጻ በማሰናበት ታሪካዊ ሃላፌነቱን አንደሚወጣም ተስፋ አናደርጋለን፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ምንም አይነት የሽብር ተግባር ላይ ተሰማርተን የማናውቅ መሆኑን ክሱም ሃሳባችንን በነጻነት ከመግለጽ ተግባራችንን ጋር ተያያዘ መሆኑን አጥብቀን እንደምናምን እያስታወስን መንግሰት ክሱን ሙሉለሙሉ ውድቅ በማድረግ የጉዳዩን ፓለቲካዊ አለመሆን አንዲያረጋግጥልን ጥሪ እናስተላለፍለን ፡፡
አሁንም ስለሚያገባን እንጦምራለን!

Tuesday, November 11, 2014

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ።

ImageNovember 11,2014

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።

ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ''የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ''

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

''የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ''''

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

''አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።''

 source http://www.dw.de/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1% ... a-18051929