Friday, May 1, 2015

የማዕከላዊ እዝ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መምጣቱ ታወቀ

May 1,2015
mekononoch serawitየማዕከላዊ እዝ  ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መሄዱ ስላሳሰባቸው የእያንዳንዱን ወታደር ንብረት እየፈተሹ በርካታ ወታደሮችን ማሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ፣በምንጮቻችን መረጃ መሰረት የማዕከላዊ እዝ አመራሮች በየዕለቱ የሚከዳው የሰራዊት ቁጥር ስላሳሰባቸው ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ/ም የእያንዳንዱን ወታደር የግል ንብረት ሲፈትሹ የዋሉ ሲሆን በፍተሻውም ከ180 በላይ የሚሆኑት የሲቪል መታወቂያ ካርድ ያላቸው ወታደሮች መገኘታቸውን አስረድቷል፣
ይህ የተገኘው የሲቪል መታወቂያ ካርድም ከትውልድ ቦታቸው በተለያዩ መንገዶች የተላከላቸው ሲሆን ሲቪል መስለው ስርዓቱን እየጣሉ ለመሸሽ እንዲያግዛቸው የተዘጋጀ መሆኑን የገለፀው መረጃው በዚህ የተነሳም አራት ነባር የሰራዊት አባላቶች ለ3 ወር እስራት ተወስኖባቸው በአዲ ኮኮብ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፣
ምንጭ -ዴምህት

No comments: