Wednesday, May 6, 2015

የዜጎች ከፍተኛ ጭፍጨፋ በመተማ

May 6,2015
ሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት፣ የሕወሃት ታጣቂዎች ሁለት ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፈተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአምሳ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል።
በአምቦ፣ በባህር ዳር በመሳሰሉት ቦታዎች እንደታየው ዜጎች በሕወሃት ታጣቂዎች ጥይት እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው። ህወሃት ከሕዝብ የሚነሱትን መሰረታዊ የፍትህ፣ የዴሞክራሲና የለዉጥ ጥያቄዎች፣ በሃያ አንደኛ ክፍል ዘመን እንዳሉ ድርጅቶ ዘመናዊና ስልጣኔ በተሞላበት መልኩ ማስተናገድ ሲገባው፣ በስድሳዎች ጊዜ እንደነበረው መግደል፣ ማረድና ፣ ዜጎችን እንደ እንስሳ መደብደቡን በመምረጥ የጫካን ኋላ ቀር ፖለቲካ እያራመደ መሆኑ በድጋሚ ዛሬ ደግሞ በመተማ ተመስክሯል።
ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ከደርቡሽ ጋር በተደረገ ትንቅንቅ አጼ ዮሐንስን ጨመሮ በርካቶች ደማቸውን ያፈሰሱባት መተማ፣ ዛሬ ከዉጭ ወራሪዎች ሳይሆን፣ ከሕወሃቶች በተተኮሰ ጥይት የልጆቿ ደም እየተረጨባት ይገኛል።
መተማ ዛሬ ይሄንን ትመስል ነበር።
 የሚሊዮኖች ድምጽ
metema 3
metema 2
metema

No comments: