Saturday, May 11, 2013

የፍትህ ሚኒስትሩ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም አሉ

ግንቦት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ከብአዴን እና ከኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚነት በቅርቡ በተካሄዱት ጉባዔዎች የተነሱት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖሩን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የመብት ጥሰት የለም ሲሉ ተናገሩ።
በዛሬው ዕለት የመ/ቤታቸውን የ9 ወራት ሪፖርት ለፓርላማ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ ከብቸኛው የአንድነት ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡
...
አቶ ግርማ ባቀረቡት ጥያቄ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብቶች እየተከበሩ መሆኑን በተካሄዱ ጉብኝቶች ማረጋገጣቸውን መጥቀሳቸውን በማስታወስ በጉብኝቱ ምን እንዳገኙ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አይይዘውም ባለፈው ቅዳሜ ዕለት የታሰሩ ሰዎችን ለመጠየቅ ወደማረሚያ ቤት ሄደው ተከልክለው መመለሳቸውን በማስታወስ ይህ ፓርላማ እንኳን መጣስ የማይችለውን ሕገመንግስት ማረሚያ ቤት እየጣሰ ነው ሲሉ ምሬት አዘል አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በማረሚያ ቤቶች ጉብኝታቸው የታራሚዎች መብዛት ጋር ተያይዞ መጨናነቅ መኖሩን፣የመገልገያ ዕቃዎችና እንደንጹህ መጠጥ ውሃ ያሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውን ማስተዋላቸውን እና ይህ ችግር እንዲፈታ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

የማረሚያ ቤቶች ተጠሪነታቸው ለፍትህ ሚኒስቴር ሳይሆን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በሰብዓዊ መብት አያያዝ በኩል ችግር እንደሌለና፤ አለ እንኳን ቢባል ሕገመንግስት ተጥሶአል ለማለት እንደማይቻልና የተፈጠረ የአሰራር ችግር ካለ ሊስተካከል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡


 በማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ መሪዎች፣የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አባላትና ሌሎችም በየጊዜው በሕገመንግስቱ የተረጋገጠው የሰብዓዊ መብቶቻቸው ማለትም በቤተሰቦቻቸውና በወዳጆቻቸው የመጎብኘት፣ ከጠበቆቻቸው ጋር ያለችግር የመገናኘትና ሃሳብ የመለዋወጥ፣ ከሃይማኖት አባቶቻቸው ጋር የመገናኘት መብቶቻቸው በማረሚያ ቤት
ኃላፊዎች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተና ብዙውን ጊዜ የሚጣስ መሆኑን እየገለጹና በመግለጽ ላይ የሚገኙ ከመሆኑ አንጻር የሚኒስትሩ አባባል ግልጽ ክህደት መሆኑን አንድ ያፓርላማ አባል ተናግረዋል።


 ሚኒስትሩ ያቀረቡትን ሪፖርት ተከትሎ ከፓርላማ አባላቱ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በይቅርታ ከማረሚያ ቤት የሚለቀቁ ሰዎች መስፈርቱን ያሙዋሉት እያሉ ያላሙዋሉት ይለቀቃሉ፣ይህ ለምንድነው በሚል ለተነሳው ጥያቄ ይቅርታ የታራሚው ጉዳይ ሳይሆን መንግስት በራሱ ፍላጎት የሚያደርገው ነው፡፡እንደመብት ሊጠየቅ አይችልም ሲሉ የፓርላማ
አባላቱን ጥያቄ አጣጥለዋል፡፡

በፍትህ ሚ/ር ስር የሚገኘው የይቅርታ ቦርድ ጥያቄው ሲቀርብ የታራሚው ጠባይ፣ለመሻሻል ያለው ፍላጎት ታይቶ በማረሚያ ቤት በጎ አስተያየት ሲቀርብ እንደሚለቀቁ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡


 ይህ የሚኒስትሩ ማብራሪያ ግን በሌላ የፓርላማ አባል ተተችቶአል፡፡ አባሉ በሰጡት አስተያየት ሚኒስትሩ ሲናገሩ ይቅርታ እና አመክሮን መደበላለቃቸውን በመጥቀስ ይቅርታ ልክ እንደአመክሮ ጠባይ የሚመዘንበት አይደለም፡፡ቀደም ሲል የቅንጅት እስረኞች ጠባያቸው ታይቶ አልተፈቱም ሲሉ የሚኒስትሩን ንግግር ተችተዋል፡፡
ባለፉት 9 ወራት 2 ሺ 958 የይቅርታ ጥያቄዎች ቀርበው 2 ሺ 149 ያህሉ በይቅርታ መለቀቃቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል፡፡


የፍትሕ ሚኒስትሩ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም አሉ
ግንቦት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ከብአዴን እና ከኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚነት በቅርቡ በተካሄዱት ጉባዔዎች የተነሱት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖሩን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የመብት ጥሰት የለም ሲሉ ተናገሩ።
በዛሬው ዕለት የመ/ቤታቸውን የ9 ወራት ሪፖርት ለፓርላማ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ ከብቸኛው የአንድነት ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡

አቶ ግርማ ባቀረቡት ጥያቄ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብቶች እየተከበሩ መሆኑን በተካሄዱ ጉብኝቶች ማረጋገጣቸውን መጥቀሳቸውን በማስታወስ በጉብኝቱ ምን እንዳገኙ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አይይዘውም ባለፈው ቅዳሜ ዕለት የታሰሩ ሰዎችን ለመጠየቅ ወደማረሚያ ቤት ሄደው ተከልክለው መመለሳቸውን በማስታወስ ይህ ፓርላማ እንኳን መጣስ የማይችለውን ሕገመንግስት ማረሚያ ቤት እየጣሰ ነው ሲሉ ምሬት አዘል አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በማረሚያ ቤቶች ጉብኝታቸው የታራሚዎች መብዛት ጋር ተያይዞ መጨናነቅ መኖሩን፣የመገልገያ ዕቃዎችና እንደንጹህ መጠጥ ውሃ ያሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውን ማስተዋላቸውን እና ይህ ችግር እንዲፈታ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

የማረሚያ ቤቶች ተጠሪነታቸው ለፍትህ ሚኒስቴር ሳይሆን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በሰብዓዊ መብት አያያዝ በኩል ችግር እንደሌለና፤ አለ እንኳን ቢባል ሕገመንግስት ተጥሶአል ለማለት እንደማይቻልና የተፈጠረ የአሰራር ችግር ካለ ሊስተካከል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
በማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ መሪዎች፣የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አባላትና ሌሎችም በየጊዜው በሕገመንግስቱ የተረጋገጠው የሰብዓዊ መብቶቻቸው ማለትም በቤተሰቦቻቸውና በወዳጆቻቸው የመጎብኘት፣ ከጠበቆቻቸው ጋር ያለችግር የመገናኘትና ሃሳብ የመለዋወጥ፣ ከሃይማኖት አባቶቻቸው ጋር የመገናኘት መብቶቻቸው በማረሚያ ቤት
ኃላፊዎች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተና ብዙውን ጊዜ የሚጣስ መሆኑን እየገለጹና በመግለጽ ላይ የሚገኙ ከመሆኑ አንጻር የሚኒስትሩ አባባል ግልጽ ክህደት መሆኑን አንድ ያፓርላማ አባል ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ያቀረቡትን ሪፖርት ተከትሎ ከፓርላማ አባላቱ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በይቅርታ ከማረሚያ ቤት የሚለቀቁ ሰዎች መስፈርቱን ያሙዋሉት እያሉ ያላሙዋሉት ይለቀቃሉ፣ይህ ለምንድነው በሚል ለተነሳው ጥያቄ ይቅርታ የታራሚው ጉዳይ ሳይሆን መንግስት በራሱ ፍላጎት የሚያደርገው ነው፡፡እንደመብት ሊጠየቅ አይችልም ሲሉ የፓርላማ
አባላቱን ጥያቄ አጣጥለዋል፡፡

በፍትህ ሚ/ር ስር የሚገኘው የይቅርታ ቦርድ ጥያቄው ሲቀርብ የታራሚው ጠባይ፣ለመሻሻል ያለው ፍላጎት ታይቶ በማረሚያ ቤት በጎ አስተያየት ሲቀርብ እንደሚለቀቁ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ይህ የሚኒስትሩ ማብራሪያ ግን በሌላ የፓርላማ አባል ተተችቶአል፡፡ አባሉ በሰጡት አስተያየት ሚኒስትሩ ሲናገሩ ይቅርታ እና አመክሮን መደበላለቃቸውን በመጥቀስ ይቅርታ ልክ እንደአመክሮ ጠባይ የሚመዘንበት አይደለም፡፡ቀደም ሲል የቅንጅት እስረኞች ጠባያቸው ታይቶ አልተፈቱም ሲሉ የሚኒስትሩን ንግግር ተችተዋል፡፡
ባለፉት 9 ወራት 2 ሺ 958 የይቅርታ ጥያቄዎች ቀርበው 2 ሺ 149 ያህሉ በይቅርታ መለቀቃቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል፡፡

No comments: