Saturday, January 24, 2015

በነትግስቱ ቡድን ጠቋሚነት የአንድነት አመራሮችን ማሰር ተጀምሯል

January 24,2015
1. አቶ አስራት አብርሃ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ
2. አቶ ሰለሞን ስዩም የፍኒትና ሚሊዮኖች ድምጽ ኤዲቶሪያል ሃላፊ
3. አቶ ስንታዩ ቸኮል የአዲስ አበባ ምክር ቤት የወጣቶች ክፍል ሃላፊ
4. አቶ ንዋይ ገበየሁ የህዝብ ግንኙነት ረዳት ሃላፊ እንዲሁም ሌሎችም ወደ አልታወቀ ቦታ በፖሊስ ተይዘው ተወሰደዋል።
ወያኔ/ኢሕአዴግአወል ጋር ከምርጫ ቦርድ ጋ የኃይል የአዲስ አበባ ሰልፍ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት የኃይል እርምጃ መዉሰድ ጀምሯል። የአንድነት አመራሮች ፖሊስ እየጎተተ በማሳሰር እየሰራ ያለው፣ ከአቶ ትግስቱ ር አብሮ እየሰራ ያለው የማነ አሰፋ እንደሆነ ታወቋል።
በዚህ ሰዓት ትግሉ ወደ አንድ ምዕራፍ ተሸጋግሯል አአስራት፤ ነዋይ ፤ስንታየሁና ሰለሞን ቢታሰሩም እንኳ የሶሻል ሚዲያውን ከሀገር ውጪ ያሉ የአንድነት ምዕራፍ 2 ሶሻል ሚዲያ ቡድን አባላት እየመሩት ነው ምዕራፍ 3 እና 4 ከሰዓታት በኋላ የተጀመረው ትግል ግቡን እስኪመታ እረፍት አይኖራቸውም፡፡

የነፃነት ቀን ቀርባለችና ወደ አደባባይ ውጡ!!!

እሁድ ጥር 17 ደብርማርቆስ ንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በመገኘት
ለአንድነት ፓርቲ አጋርነታችንን እናሳይ!!!
አንድነት አንድ ነው!!!

የሰልፍ ትብብር ጥሪ ለእውነተኛ ተቃዋሚዎች በሙሉ!

አንድነት እሁድ ጥር 17 በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የሚያካሄደው ሰላማዊ ስልፍ ላይ እውነተኛ ተቀዋሚዎች ሁሉ በፈለጉት መልኩ በሰልፉ ላይ ትሳተፉ ዘንድ ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን። በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ በሚካሄደው ታላቅ ሰላማዊ ስልፍ ላይ የሰማያዊ፣ የመኢአድ፣ የመድረክ እና የዘጠኙ ፓርቲዎች አመራሮች እንድትሳተፉ በዚህ አስቸጋሪና ታሪካዊ ወቅት ከጎናችን እንደምትሆኑ እምነታቸን ነው።
የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ
udj 67
10947240_407366432761047_2187322177615197122_n
10269525_407366416094382_8678569693027599769_n


1545601_407366336094390_5858335905222877108_n

No comments: