Thursday, September 17, 2015

ምኞትና ተግባር ምንና ምን ናቸው? በጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ

September 17,2015

በአዲሱ አመት ዋዜማ የፖለቲካ እስረኞችን ለመጠየቅ ወደ ቂሊንጦ እስርቤት ከእህቴ ጋር ሄጄ ነበር፡፡ ስማችንን እና የምንጠይቃቸዉን እስረኞች ስም ካስመዘገብን በኋላ መታወቂያችን አሳይተን ወደዉስጥ ልንገባ ስንል መታወቂያዉን የምትመለከተዉ ፖሊስ ስማችንን ካነበበች በኋላ “ቆይ ቆይ የእናንተማ መጠየቅ አለበት” አለችንና መታወቂያችንን ይዛ ከበር መለሰችን፡፡ ከበሩ አጠገብ በሚገኝ ጎብኝዎች ወረፋ በሚጠብቁበት የእንጨት መቀመጫ ላይ አረፍ እንዳልን በሃሳብ ላይ ታቹን ማለት ጀመርኩ፡፡ እንድንገባ ይፈቅዱልን ይሆን ወይስ የቃሊቲዎቹ እንዳደረጉት “ፍቃድ የላችሁም” የሚል አስቂኝና አናዳጅ መልስ በመስጠት ይመልሱን ይሆን? ለሚለዉ ጥያቄ መልሱ እኔዉ ጋር ያለ ይመስል አጎንብሼ ማሰቤን ቀጠልኩ፡፡ ቀና ስል ከፊት ለፊቴ “ማረሚያ ቤቱ” ለእስረኛ ቤተሰቦች መልካም ምኞቱን የገለፀበት ወረቀት ተለጥፎ ተመለከትኩ፡፡ ከአራት አመታት በላይ በመኖር የእስርቤቶቹን አሰራር አዉቀዋለሁና ተመሳሳይ የመልካም ምኞት መግለጫ የያዘ ወረቀት ለእስረኛዉም ተለጥፎ እንደሚሆን አልተጠራጠርኩም፡፡
ሰላም እየነሳ ሰላም “የሚመኝ”፣ ህክምና እየከለከለ ጤንነትን “የሚመኝ”፣ የሚዋደዱ ሰዎችን ከሽቦ ወዲያና ወዲህ ሆነዉ እንኳን እንዳይተያዩ እየከለከለ ፍቅርን “የሚመኝ” . . .ተቋም ! አንድ ፖሊስ ወደኛ እየቀረበ ሲመጣ ሀሳቤ ተቋረጠ፡፡ መታወቂያዬን እየመለሰልኝ መግባት እንደማልችል ነገረኝ በኋላ ለእህቴም ተቀራራቢ መልስ በመስጠት መታወቂያዋን መለሰላት፡፡ ለምን ለሚለዉ ጥያቄያችን “አላዉቅም፡፡ የተወሰነውን ንገር ተብዬ ነው” የሚል ምላሽ ሰጠን፡፡ ምን አይነት አምባገነንነት ነው? እስር ቤት እያለሁ በሌሎች የመጎብኘት መብቴን የነፈገው ስርዐት ዛሬ ደግሞ የጠያቂነት መብቴን እየነፈገው ነው፡፡ ሙሉውን ቀን ሊባል በሚችል መልኩ ስለፖለቲካ አሳሪዎቻችን ጉዳይ እያሰብኩ ስብሰለሰል ዋልኩ፡፡ የእኔና የሌሎች በርካቶች መብሰልሰል ምክንያት የሆኑት የኢህአዴግ ባለስልጣናት ደግሞ በአሉን ምክንያት በማድረግ ፍትህ እያዛቡበተ፣ እያሰሩትና እየገደሉት ላሉት ህዝብ የመልካም ምኞት መግለጫቸዉን ሲያዥጎደጉዱለት ዋሉ፡፡ ይህንን የኢህአዴግ ምኞትና ተግባር መራራቅ እያሰብኩ እያለሁ “ኢህአዲግን ለመለወጥ የምንፈልግ ሰዎች ምኞትና ተግባርስ ምን ይመስላል? ” የሚል ጥያቄ ሽው አለብኝ፡፡ ጥያቄው በርካታ መልሶች ቢኖሩትም በዚህ ጽሁፍ ለማቅረብ የመረጥኳቸው ግን ሁለቱን ብቻ ነው፡፡
አጉል ህልመኞች
በዚህ ስርዓት ተጠቃሚ በመሆናቸው ብቻ የሌሎችን ወገኖቻቸውንና የሀገርን ጉዳት ማየት ካልቻሉ ወይም ካልፈለጉ ሆዳሞችና በህወሓት የዘረኝነት መርዝ ከተበከሉ ጥቂቶች በቀር የኢህአዴግን መሰንበት የሚፈልግ ዜጋ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች የማገኛቸዉ ሰዎች ምኞትም የስርዓት ለውጥን ማየት ነው፡፡ ነገር ግን “እነዚህ ሁሉ ሰዎች የሚፈልጉትን ለውጥ ለማየት ምን አይነት አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው?” ብለን ብንጠይቅ የምናገኘው ምላሽ አስደሳች አይደለም፡፡
አንዳንድ ለዉጥ ፈላጊዎች ቁጭ ብሎ ከመመኘት በቀር ለለዉጡ መምጣት የሚያደርጉት ምንም ነገር የለም፡፡ ለምን አንዳች ነገር እንደማያደርጉ ስትጠይቋቸው ከምታገኟቸዉ መልሶች መሃከል “እነዚህን መዥገሮች እሱ ይንቀላቸዉ እንጂ በሰው ሃይልማ የሚሆን አይደለም፤ ህዝቡን ከፋፍለውታል እኮ ምን ማድረግ ይቻላል? . . .” የሚሉት ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሰዎች ምንም እንዳይሰሩ ያደረጋቸዉ ትልቁን ምክንያት ጠጋ ብላችሁ ስትመረምሩ ግን ፍርሃት ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ፕ/ር መሳይ ከበደ “The Impasse of Fear in Ethiopia and the Necessity of Comprehensive struggle ” በተሰኘ ፅሑፋቸዉ እንዳስቀመጡት ፍርሃት የጨመደደው ህዝብ ሁሌም ምንም ላለማድረጉ የሚያቀርባቸው በርካታ ምክንያቶች ይኖሩታል፡፡
ሌሎቹ ለዉጥ ፈላጊዎች ደግሞ ለዉጥ ሊያመጡ የሚችሉ እንቅስቃሴዎቸን በማድረግ ረገድ ከላይኞቹ የተሻሉ ቢሆኑም የጀመሩትን መጨረስ ግን የማይሆንላቸው ናቸው፡፡ እያደረጉ በነበረዉ እንቅስቃሴ ሳቢያ አንዳች ችግር ሲደርስባቸው ከመንገዳቸው ይወጣሉ፡፡ “በዚህኛው አመተምህረት በተደረገው ምርጫ ሳቢያ ለእስር ተዳርጌ ነበር፤ በዛኛው ወቅት በተደረገው ሰልፍ ላይ ተገኝቼ ተደብድቤያለሁ” ማለት ይቀናቸዋል፡፡ አሁንስ? ስትሏቸው ግን መልሳቸው “ጎመን በጤና” ነው፡፡ እንደነዚህ አይነቶቹ ሰዎች መጀመሪያዉኑ እየታገሉት የነበረውን መንግስት ግፈኝነት በሚገባ ያወቁት አይመስሉም፡፡
የቆረጡ ለዉጥ ፈላጊዎች
እነዚህኞቹ አስቀድሞ ከተጠቀሱት ጋር የለዉጥ ፍላጎታቸው ቢያመሳስላቸውም ለውጥን ለማምጣት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ መኖሩና ቁርጠኝነታቸው ደግሞ የተለዩ ያደርጋቸዋል፡፡ “እሱ ያመጣዉን እሱ እስኪመልሰው” በማለት እጃቸውን አጣጥፈው አይቀመጡም፡፡ ለለውጡ እዉን መሆን የሚችሉትን ሁሉ ያዋጣሉ፡፡ ከነዚህ ሰዎች መሀከል በግንባር ቀደምትነት ሊጠቀስ የሚገባው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን መዉሰድ ይቻላል፡፡ እስክንድር ለለዉጡ ያለውን ሁሉ እየከፈለ ያለ ሰው ነው፡፡ ወደስምንት ጊዜ ያህል ሲታሰርና ሲፈታ፣ የመፃፍ መብቱን ሲገፈፍ፣ ሲደበደብ፣ ንብረቱ ሲወረስና ከሚወዳት ባለቤቱና ልጁ ጋር በአካል መለያየት ግድ ሲለዉ ሁሉ በአላማው ከመጽናት ውጭ ለአፍታ እንኳን ሸብረክ ሲል አልታየም፡፡ እስክንድርና መሰሎቹ ዲሞክራሲ እንዲሰፍንና ነፃነት እንዲገኝ ካስፈለገ ከምኞት ባለፈ ስራና መስዕዋትነት እንደሚጠይቅ ገብቷቸዋል፡፡ ለገባቸው እውነት ደግሞ እየኖሩ ነው፡፡ እነ እስክንድር ይሄን ሁሉ መስዕዋትነት ሲከፍሉ ታዲያ ሁኔታው ያማያማቸው ሆኖ አይደለም፡፡ ህመሙን ጥርሳቸውን ነክሰው እየቻሉ እንጂ!
አቶ ኤፍሬም ማዴቦ “ከዊሃ እስከ ኦምሃጀር-አንድ ሰሞን ከአርበኞች ጋር” በሚል ርዕስ በቅርቡ ባስነበቡን ጽሑፋቸዉ የአርበኞች ግንቦት 7 ጦርን ለመቀላቀል ከአሜሪካን ሀገር ከተደላደለ ኑሮዋቸው ተነስተው ሲሄዱ ይሰማቸው የነበረዉን ከሚወዱት ልጃቸው የመለየት ህመም በዉብ አገላላፅ ተርከዉልናል፡፡ አቶ ኤፍሬም አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ ሊሸኛቸው የመጣዉን የ17 አመት ልጃቸውን ሲሰናበቱ “ልጄ ይሄን ማድረግ አልፈልግም ነገር ግን ማድረግ አለብኝ” ያሉት ፊታቸው በእንባ እየታጠበ ነበር፡፡ የማይፈልጉትን ነገር ለማድረግ እራሳቸዉን ያስገደዱበትን ምክንያት የገለጹት “የምወደውን አንድ ልጄንና ጥሩ ስራዬን ደህና ሁኑ ብዬ በረሃ የገባሁት ሃገሬ ዉስጥ ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ አብቦ ለማየት ነው” በማለት ነው፡፡
ጋዜጠኛ እስክንድርና አቶ ኤፍሬም ምንም እንኳን ለውጥን ለማምጣት የሚሄዱበት መንገድ ለየቅል ቢሆንም ሁለቱም ግን ለለውጡ ያላቸውን ሁሉ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፡፡ አንደኛቸው ለውጡ ግድ ብሎአቸው ቤታቸው እስርቤት ሲሆን ሌላኛቸው ዱርቤቴ ብለዋል፡፡ ሁለቱም ከሚወዷቸው ወንዶች ልጆቻቸው ጋር ተለያይተዋል፡፡ ሁለቱም ለውጥ በምኞት ብቻ እንደማይመጣ ያውቃሉና እራሳቸው ሄደው ይገናኙት ዘንድ በተለያየ መንገድም ቢሆን በጉዞ ላይ ናቸው፡፡ በመጨረሻም . . .
በኢትዮጵያ እኩልነት ዴሞክራሲ ነፃነትና ፍትህ እንዲሰፍን የምንመኝ ሁላችን ከቀን ህልማችን መንቃትና ምኞቶቻችንን ወደ ተግባር ለመለወጥ መንቀሳቀስ ያስፈልገናል፡፡ ከመንቀሳቀስ ያገደን ፍርሃታችን ከሆነ በቀደመው ንዑስርዕስ ስር የጠቀስኩት የፕ/ር መሳይ ጽሑፍ ፍርሃትን ለመዋጋት የሚያስቀምጠው አንድ መፍትሄ አለ፡፡ ድርጊት! ራሳችንን ለፈሪነት የተመደብን አድርገን የምንቆጥርና በሌሎች ደፋርነት መንፈሳዊ ቅናት የሚያድርብን ሰዎች ካለን ፕ/ሩ የጠቀሱት የፈላስፋው አርስቶትል ሃሳብ ሳይጠቅመን አይቀርም፡፡ አርስቶትል “ጀግና ለመሆን ጀግንነትን መለማመድ ያስፈልጋል” ይለናል፡፡ ለአርስቶትል ድፍረት እንደሌሎቹ የሞራል እሴቶች ሁሉ አብሮን የሚወለድ እምቅ ሃይል ሲሆን እውን ለመሆንና ለመዳበር እንዴሎቹ እሴቶች ሁሉ ልምምድ ያስፈልገዋል፡፡ አስፈላጊዉ ጥንቃቄ እንደዳለ ሆኖ እስኪ እስከዛሬ ያላደረግነዉን አንድ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት እናድርግ፡፡ ፕ/ሩ እንደሚሉንና እኔም እንደማምነው ድርጊት ስኬትን ያመጣል፡፡ ስኬቱ የቱንም ያህል ትንሽ ቢሆን በራስ መተማመንን ይወልዳል፡፡ በራስ በተማመን ሲኖር ደግሞ ፍርሃት ይጠፋል ወይም ችግር ሊሆን በማይችልበት ደረጃ ዝቅ ይላል፡፡
ከፍርሃታችን ወጥተን እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሳለን ከኢህአዴግ በሚወረወርብን ዱላ ተሰብረን ከመንገዳችን ላለመውጣት ደግሞ የገዢዉን ፓርቲ ማንነት ጠንቅቆ ማወቅና ቢያንስ የስነልቦና ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ለማንጠብቀው ነገር አንዘጋጅም፡፡ ያልተዘጋጀንበት ነገር ደግሞ ሁሌም ይጥለናል፡፡ በመሆኑም የምንታገለው ስርዓት ስልጣኑን ላለማጣት የቱንም አይነት ጭካኔ የተሞላው እርምጃ እንደሚወስድ ማወቅና ለዛም እራስን ማዘጋጀት ግድ ይላል፡፡ ደግሞስ ኢህአዴግ ምን ሊያደርገን ይችላል? ሊያደርግብን የሚችለው ሁሉ አስቀድሞም ከአፈር በታች እንዲዉል የተወሰነበት ስጋችን ላይ አይደለምን?
መልካም አዲስ አመት!
መስከረም 3/ 2008

Tuesday, September 15, 2015

Zone 9 Bloggers Winners of the 2015 CPJ Press Freedom Award

September 15, 2015
(CPJ) – In April 2014, Ethiopian authorities arrested six bloggers affiliated with the Zone 9 collective. The bloggers–Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu–were charged with terrorism.Zone 9 Bloggers Winners of the 2015 CPJ Award
The Zone 9 blogging collective was formed in May 2012 in response to the evisceration of the independent press and the narrowing of space for free expression. The name, “Zone 9,” is derived from the zones in Kality Prison, the main jail where Ethiopia’s political prisoners, including several journalists, are held. While Kality Prison is organized into eight different zones, the bloggers refer to the entire country as “Zone 9” because of Ethiopia’s lack of democratic freedoms, one of the bloggers told CPJ.
The collective is made up of nine bloggers–the six named above, and Soleyana S Gebremichael, Endalk Chala, and Jomanex Kasaye, all of whom are in exile. Soleyana has been charged in absentia.
In July 2015, weeks before U.S. President Barack Obama visited the country, Ethiopian authorities released Mahlet and Zelalem.
The Zone 9 bloggers were arrested along with three other journalists–editor Asmamaw Hailegeorgis and freelancers Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, who were later released. The initial charges against the group included working with international human rights organizations and taking part in email encryption and digital security training. The group was subsequently charged with terrorism.
Since 2009, when Ethiopia’s anti-terror law was implemented, the government has used the sweeping legislation to imprison more than a dozen critical journalists, according to CPJ research. In 2012, bloggerEskinder Nega was sentenced to 18 years in prison and Woubshet Taye to 14 years, both on terrorism charges. CPJ’s 2014 prison census found that Ethiopia was the fourth worst jailer of journalists in the world, with at least 17 journalists behind bars. Ethiopia also ranked fourth on CPJ’s 2015 list of the 10 Most Censored Countries.
With the motto “We Blog Because We Care,” the Zone 9 collective has voiced concerns over domestic issues, including political repression, corruption, and social injustice. The collective’s posts were frequently blocked inside Ethiopia, but gained a following with Ethiopians in the diaspora, according to local reports. Their posts on Facebook solicited some 12,000 responses a week, reaching 200,000 during a four-part “campaign” they ran on Facebook.
By awarding the Zone 9 bloggers with its International Press Freedom Award, CPJ recognizes the important role that bloggers play in environments where traditional media are weak or have been all but shuttered by financial hardship and direct or indirect state attacks.
Country facts:
  • Ethiopia released at least six journalists from prison in 2015, but is still holding around a dozen journalists in jail in relation to their work.
  • In May 2015, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) won 100 percent of the vote.
  • In 2014, at least eight independent publications were shut down, according to CPJ research.
  • Between 2013 and 2014, in response to the continued government crackdown on the media, more than 40 journalists fled into exile from Ethiopia.

Monday, September 14, 2015

የሕወሓት መንግስት የአውሮፕላን አብራሪውን ኃይለመድህን አበራን መኪና ለጨረታ አቀረበ

September 14,2015
በጥር 2006 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ጣሊያን ሲበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ጠልፎ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ ንብረት የሆነች የቤት መኪና በሐራጅ ለጨረታ ቀረበች፡፡
Haile Medhin Aberaየሰሌዳ ቁጥር አአ 2-A32521 መኪና ጨረታ ያቀረበው ዘመን ባንክ ነው፡፡ ረዳት አብራሪው ለመኪና ግዢ ከዘመን ባንክ የተበደረው ብድር ስላልተከፈለው ባንኩ ተሽከርካሪዋን በጨረታ ለመሸጥ መገደዱን አስታውቋል፡፡
ባንኩ ተሽከርካሪዋን ለጨረታ ያቀረበው በሐራጅ መነሻ ዋጋ ብር 261,503.37 ነው፡፡ ጨረታው የሚካሄደው በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም. ነው፡፡ ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን መኪናዋን የገዛው ከአውሮፕላን መጥለፉ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኃይለ መድኅን ስዊዘርላንድ ውስጥ የፖለቲካ ጥገኝነት ቢጠይቅም የአገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎት ፍርድ ቤት አንድ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ጉዳዩ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ አይታወቅም፡፡ ለስዊዘርላንድ ኢሚግሬሽን ባለሥልጣን በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በግለሰቡ ላይ ክስ መሥርቶ፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሌለበት 19 ዓመት ፅኑ እስራት እንደተፈረደበት ይታወሳል፡፡

Saturday, September 12, 2015

የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ?

September 12,2013


የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ትቶ ለምን ኮበለለ ? ሊፈታ የሚገባ ጥያቄ የትህዴን መሪ አቶ ሞላ አስገዶም የተወሰኑ የትህዴን ሰራዊት ይዞ ሀገር ኢትዮጵያ ኮበለለ ይሄ ዜና ብዙዎቻችን እናዳስገረመ እና  አንዳንዶችንም እንዳሰደነገጠና፣ የተወሰኑ ግለሰቦችን እንደስደሰት እያየነው ያለ ነገርሲሆን የአቶ ሞላ  አስግዶም ከትግል ሜዳው መኮብለል እና ወደ ወያኔ ካምፕ መቀላቀል እኔን ባያስደነግጠኝ እና ባያስደስተኝም የአገር አድን ንቅናቄ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው በተሾሙ በማግስቱ ኮብልለው መጥፋታቸው   በጣም አገራሞትን ጭሮ ጥያቄ ስለፈጠረብኝ  ይችን ትንሽ ነገር ማለትን ወደድኩኝ:: በመጀመሪያ ልናውቀው የሚገባው ነገር እንደዚህ አይነት ነገር በትግል ውስጥ ሊያጋጥም እና ሊከሰት የሚችል እንደሆነ  መገንዘብ ያስፈልገናል::

እውነትና  ንጋትእያደር ይጠራል ቢሆንም ነገሩ እንደእኔ አመለካከት ግን አቶ ሞላ አስግዶም በመጀመሪያም ኤርትራ ተቀምጠው የየትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴን (ትህዴን) በሊቀመንበርለ ሲመሩት የነበሩት በእርግጥ ጸረ ወያኔ አቋምና አላማ ኖሮቸው ነበር ወይስ ሌላ ስውርና የተደበቀ አጀናዳ በጉያቸው ደብቀው አስመሳይነትን ተላብሰው ውስጥ ውስጡን የየወያኔ ፖለቲካዊ አጀንዳ ሲያስፈጽሙ የነበሩ ሰው ነበሩ ወይ የሚለውን ነገር እንድጠረጥር ቢያደርጉኝም  ምንአልባትም ማን ያውቃል እኝህ ሰው የሆነ ጊዜያዊ ጥቅም መሻት አታሏቸው ይሆን የሚልም ነገር እንዳስብ አድርጎኛል:: ምክንያቱም ለእውነት እንዳንታገል ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል አንዱ ለጊዜያዊ  ጥቅም መታለል በመሆኑ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንኮን ተዘግቦ እንደምናገኘው ኤሳው ለሆዱ ብሎ በምስር ወጥ ብኩርናውን አሳልፎ ለወንድሙ ለያዕቆብ እንደሸጠው ሁሉ ዛሬም በዚህ ዘመን ለጊዜያዊ ጥቅም ተብሎ ማንነትንና ሕሊናን በመሸጥ አስመሳይነትን ተላብሰው ለእውነት ከመቆም ይልቅ የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞችን ተቀብለው ከእውነት ጋር የተጣሉ በርካቶች ሰዎች እንዳሉ እናውቃለን።

 ሰው ለተለያዩ ጥቅሞች ሲል አስመሳይነትን ተላብሶ መኖርን የሚችል ፍጡር ነው::አስመሳይነት ዛሬ የጀመረ ብቻም ሳይሆን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አሉታዊ ተጽኖ ከፈጠሩ ጉዳዮች መካከል ትልቁን ስፍራ ይዞ እናገኘዋለን። በጥቅም ታውረው አስመሳይነትን ተላብሰው በጣሊያን ወረራ ዘመን መንገድ እየመሩ ወደ መሀል ሀገር ከማስገባት በተጨማሪም የንጉሠ ነገሥቱ የቅርብ ባልሙዋል ከነበሩ መኩዋንንቶች እና መሳፍንቶች መካከል ሳይቀሩ ለጣሊያን ያደሩ ሰዎችን እንደምሳሌ ማንሳት ይቻላል። እነዚህ በአስመሳይነት የተጠቁ ወገኖች ወይም ሹማምንቶች ህዝቡ ተቃውሞውን በማቆም መሰሪዋ ጣሊያን ይዛው የመጣችውን የይምሰል እውቀት እና ስልጣኔ በመቅሰም ሀገሩን ያለማ ዘንድ በሀሰት ለመሸንገል ሞክረዋል። መረጃ በመስጠት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ደማቸው በግፍ እንዲፈስ ያደረጉት አስመሳዮች ወይም ጥቅመኞች ናቸው።

ዛሬም አስመሳይ ጥቅመኞች ጊዜያዊ ጥቅምን እና የወያኔን ትርፍራፊ ለመልቀም ቢኮበልሉ ድሩም ከትግል ጉራው የነበሩት  ታሪክን ለመበረዝ፣ የህዝብን ለመግደል ስለነበረ የሚያስደነግጥ ነገር አይኑርም ባይ ነኝ ምክንያቱም ነገም ሌላ ነገር ልንሰማ እንችል ይሆናልና ስለሆንም ማንኛችንም ከአስመሰይነት ተላቀን ማንነትንና ሕሊናን በጥቅም ሳንሸጥ እንደ ዜጋ ለሀገር በማሰብ ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ በጽኑ መታገል ይኖርብናል በማለ  ዘመኑን የድል ያድርግልን እላለው።

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

  ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

መልካም አዲስ ዓመት – ድጋፍ ለአገር አድን ንቅናቄ

September 12, 2015
def-thumb“የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ” ምስረታ ዜና በአዲስ ዓመት መባቻ መሰማቱ ትልቅ የምሥራች ነው። ይህንን ንቅናቄ ለመመስረት ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ምስጋና ይገባቸዋል።
የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ መመስረት የህወሓት አገዛዝን ተጋግዞ ለመጣል ከማስቻሉም በላይ ድሉ የአንድ ወይም የጥቂት ድርጅቶች ድል ከመሆን ይልቅ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድል እንዲሆን ያስችላል። ከዚህም በተጨማሪ ከህወሓት አገዛዝ በኋላ የተባበረች ኢትዮጵያ እንደምትኖረን ማስተማመኛ ከሚሰጡን ነገሮች ዋነኛው ዛሬ የምናደርጋቸው ትብብሮች ናቸው። የአገር አድን ንቅናቄ ዛሬ የምናደርገውን ትብብር መዋቅራዊ ገጽታ የሚሰጠው እና ዘለቄታነት እንዲኖረው የሚያግዝ በመሆኑ ለአገራችን ለኢትዮጵያ እና ለሕዝቧ የሚሰጠው ጥቅም ዘርፈ ብዙ ነው።
የአንድን ድርጅት ጥንካሬ ከሚወስኑ ነገሮች ዋነኛው የአባላቱና ደጋፊዎቹ ጥንካሬ ነው። የአገር አድን ንቅናቄም ጥንካሬ ከሚወስኑት ነገሮች ዋነኛው አባላትና ደጋፊው ናቸው። የአገር አድን ንቅናቄ እንዲጎለብት የምንመኝ ሁሉ ለንቅናቄው መጠናከር የምናበረክተው አስተዋጽኦ አለ። ከሁሉ አስቀድሞ ኢትዮጵያ አገራችን ከግዛቷ ውስጥ የሚገኙ ማኅበረሰቦች ሁሉ አገር መሆኗን እና እያንዳንዱ ማኅበረሰብ ከሌላው ጋር እኩል መብት ያለው መሆኑን መቀበልና በተግባርም ማሳየት ይገባል። እያንዳንዱ ዜጋ እና እያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ከሌሎች ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር በጋራ አገራችን የማዳን እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆን ሁኔታዎችን ማመቻቸት ያስፈልጋል። በምናደርጋቸው ፓለቲካዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የዜጎችና የማኅበረሰቦች በእኩልነት መሳተፍ እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን ተረድተን መንቀሳቀስ ይኖርብናል። ለህወሓት “ከፋፍለህ ግዛ” ፓሊሲ መመቸት የለብንም። በዘር፣ በሃይማኖት፣ በጾታ፣ በእድሜም ሆነ በቋንቋ ሳንከፋፈል የጋራ ትኩረታችንን የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያን ማዳን ላይ እናድርግ።
በኢትዮጵያ፣ በዳር አገር እና በውጭ አገራት የሚገኙ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ከሕይወት መስዋትነት ጀምሮ በጊዜዓቸው፣ በገንዘባቸውና በእውቀታቸው ንቅናቄዓቸውን ሲረዱ ቆይተዋል። በአሁኑ ሰዓት በበርካታ የዓለም ከተሞች እየተደረጉ ያሉት የገቢ ማሰባሰቢያ ዘመቻዎች የሚያመለክቱት የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ምን ያህል የነፃነት ትግሉ የጀርባ አጥንት መሆናቸው ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 ይህ ድርጅታዊ ፍቅርና ተነሳሽነት ወደ አገር አድን ንቅናቄውም እንዲሸጋገር ይሻል።ከአሁን በኋላ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላት እና ደጋፊዎች የአገር አድን ንቅናቄውን የማጠናከር ኃላፊነት አለባቸው። በዚህም ምክንያት የአርበኞች ግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች በሚያደርጓቸው የትግል እንቅስቃሴዎች ሁሉ የሌሎች ዲሞክራሲያዊ የኢትዮጵያ ኃይሎች ተሳትፎ እንዲኖርበት ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። ሕዝብን የማስተባበር ሥራ በሁሉም ቦታዎችና በሁሉም እርከኖች መሠራት ይኖርበታል። ይህ የሁለገብ የትግል ስትራቴጂዓችን አንዱ አካል በመሆኑ አባላት ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያሳስባል።
አርበኞች ግንቦት 7 ለአባላቱና ደጋፊዎቹ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ “እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን፤ አዲሱ ዓመት የድል ዓመት እንዲሆንልን በጽናት እንታገል” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Friday, September 11, 2015

የፌስቡክ ተቃዋሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ።

September 11,2015


የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?” በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ካድሬዎችና ነዋሪዎች ውይይት በተካሄደበት ጊዜ ነው።

በመቀሌ ማዘጋጃ ቤት ማክሰኞ 3/13/2007 ዓም በአቶ ተስፋአለም ተወልደብርሃን (የመቀሌ ከንቲባ)፣ አቶ አሰፋ ተገኝ ምክትል ከንቲባ የተመራ ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን “የህወሓት ጉባኤ ምን ይመስላል?” የሚል አጀንዳ ተሰጥቶት ነበር። የትግራዩ አንጃ በጉባኤው ወቅት በፌስቡክና በተባራሪ ወሬ የአቶ አባይ ወልዱ ስም ክፉኛ ጠፍቷል በሚል እሳቤ የስም እዳሴ እያካሄዱ ነው።

1) ህወሓት ተከፋፍሏል የሚል ወሬ ውሸት ነው።

2) ዳዊት ገብረእግዚአብሔር በትግራይ የሰጠው ቃለ መጠይቆች ውሸት ናቸው።

3) በፌስቡክ የሚሰራጩ መልዕክቶች ውሸት ናቸው፤ እንዳታምኑ።

4) የጉባኤው ተሳታፊዎች ሚስጢር እንዲጠብቁ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም በቀጥታ ስርጭት ሊባል በሚችል ደረጃ የስብሰባው መረጃ በፌስቡክ ተዘግቧል።

5) በአሁኑ ሰዓት ሁለት ዓይነት ጠላቶች አሉን። ፊት ለፊት ወጥተው የሚታገሉን እንደ ዓረና የመሰሉ እና በውስጣችን ሆነው የሚታገሉን ኪራይ ሰብሳቢ ሃይሎች (ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በፌስቡክ ደረጃ ህወሓት መስለው ጀርባችን የሚወጉን ሃይሎች) ናቸው።

6) አባይ ወልዱ ሙስናን የሚጠየፍ፣ ታግሎ የሚያታግለን ጀግናና ብቁ መሪ ነው።

7) በፌስቡክ ተጠቃሚዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን።

8) ጉባኤው ፍፁም ዲሞክራሲያዊና በድል የተጠናቀቀ ነበር ወዘተ የሚል ሃሳብ ወደ ተሳታፊዎች አቅርበዋል።

ተሰብሳቢዎቹ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት በጥንቃቄ የተመረጡ ቢሆኑም ያቀረቡት ሃሳብና ተቃውሞ ግን ስብሰባው ላዘጋጀው አካል አስደንጋጭ ነበር።ከተሳታፊው የቀረቡት ጥያቄዎች፤

ሀ) አባይ ወልዱ በጉባኤተኛ በ20ኛ (የፌስቡክ ማህበረሰብ ከክፍል 20ኛ፤ ከዩኒት 1ኛ ብሎ የቀለደበት ነው) ደረጃ ተመርጦ እያለ በሊቀመንበርነት እንዴት ሊመረጥ ቻለ? እዚህ ላይ የጉባኤው ዲሞክራሲያዊነት የቱ ላይ ነው?

ለ) እነ አርከበ በድምፅ እንዲሳተፉ የተደረገበት፣ ለማዕከላዊ ኮሚቴ እንዳይወዳደሩ የተከለከሉበት አሰራር በየትኛው ደንብ ይገኛል?

ሐ) ዘመኑ ያመጣው የፌስቡክ ቴክኖሎጂ ህዝቡ እንዳይጠቀም እርምጃ እንወስዳለን ማለታችሁ ጊዜው የ21ኛ ክፍለ ዘመን መሆኑ ስላልገባችሁ ነው? የሃይል እርምጃው ቴክኖሎጂውን ምን ያህል ይቆጣጠረዋል ብላችሁ ታስባላችሁ?

መ) አቶ ዳዊትና ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚነሱት ጉዳይ በመሬት ያለና በየዕለቱ የሚያጋጥመን ሃቅ ሆኖ ሳለ አትመኑት፤ ውሸት ነው፤ ማለታችሁ ችግሮቹን ለመፍታት አቅም እንዳጠራችሁ አያመላክትም ወይ? የሚሉትና ሌሎች ፈታኝ ጥያቄዎችና ሃሳቦች የቀረቡ ሲሆኑ የመቀሌ ከንቲባና ምክትሉ የሚመልሱት አጥተው አንገታቸው አቀርቅረው በሃፍረት ከስብሰባው ወጥተዋል።

የተለያዩ የቢሮ ሃላፊዎች የመሩት የመንግስት ሰራተኞች ስብሰባዎች እየተካሄዱ ያሉ ሲሆኑ ዘመቻው አቶ አባይ ወልዱ የደረሰባቸው የይውረድልንና የስም ማጥፋት ዘመቻና የጠፋው ስም እንደገና የማደስ ስራ ተጠምደው ይገኛሉ። የዚህ ዘመቻ ትኩረት ተደርጎ ያለው ፌስቡክና የፌስቡክ ተጠቃሚዎች ናቸው። ሰብሳቢዎች በተለያዩ መድረኮች ፌስቡክ ወጣቱ ትውልድ በአሉታዊ ጎን እያበላሸው፣ የተቃውሞ መንፈስ እየበረዘውና እየበከለው በመሆኑ መንግስት እርምጃ ይወስዳል በማለት አዋጅ እያስነገሩ ይገኛሉ።

በክፍለ ከተሞች ከተካሄዱ ስብሰባዎች የሓወልቲ፣ ዓይደር፣ ሓድነትና ቀዳማይ ወያነ ተሰብሳቢዎች ከፍተኛ ውጥረት የተፈጠረ ሲሆን ባለመግባባት ሊበተን ችለዋል። ፌስቡክ አስመልክተው ከቀረቡት የአብዮታዊ እርምጃ ይወሰዳል ዛቻ ለትግራዩ አንጃ ደጋፊዎች የቀረበ ግምገማ “በቁጥር እኛ እንበዛለን፣ ለኢንቴርኔት አክሰስ እኛ እንቀርባለን፣ እነዚህን በጣት የሚቆጠሩ የፌስቡክ ተቃዋሚዎች መቃወምና ማሸነፍ ለምን አቃተን…?” የሚል ቁጭት አቅርበዋል።

እቺ ነገር መንግስቱ ሃይለማርያም “ትጥቅ አቀረብን፣ ስንቅ አቀረብን፣ አሁን የቀረን ልብ ማደል ነው። እንደ ወያነ ጠንክራችሁ አትዋጉም ወይ…!” ብሎ ያደረገው የተስፋ መቁረጥና የስርዓቱ ማብቅያ አመላካች ንግግር በእጅጉ ይመሳሰላል።
የህወሓት አንጃዎች ክፍፍል ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን በነዶ/ር ሰለሞን ዑንቋይ ለቀናት የፈጀ ሽምግልና ከመበተን እንደዳኑ ፀሓይ የሞቀ ሃቅ ለመካድ ቢሞክሩም ከህዝቡ የተሸፈነ ግን አልነበረም።

አሁን በመላ የትግራይ ወረዳዎች የአባይ ወልዱን ስም ለመገንባት ከፍተኛ ጥረት በመካሄድ ላይ ይገኛል። የአዲስ አበባው አንጃ ፊታውራሪ የሆኑት ደብረፅዮን በ12ኛ ጉባኤ ላይ በፌስቡክ የሚነሱ ሃሳቦች እንደ ትልቅ የሃሳብ ምንጭ ተቆጥረው በጉባኤው ቀርበው እንደተወያዩበትና ለጉባኤው እንደ ግብአት እንደተጠቀሙበት ለቪኦኤ መግለፃቸው ይታወሳል።

የአባይ ወልዱን ስም ለማጥፋት አገልግሎት ላይ ውለዋል የተባለው ፌስቡክና ተቃዋሚ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል። የእርምጃው ዓይነት ምን ሊሆን እንደሚችል እስካሁን በውል አልታወቀም። ሆኖም የኢንቴርኔት ማእከላት ሊዘጉ ይችላሉ። ማነው ትግራይ ሰሜን ኮርያ ያላት? ያው ውድድራችን ከሰሜን ኮርያ መሆኑ ነው። ትግራይ ለምትገኙ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች ኢትዮጵያውያን አብዮታዊ እርምጃ እንዳይወሰድባችሁ የመንፈስ ዝግጅት ብታደርጉ እንመክራለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

Tuesday, September 8, 2015

OLF and TPDM expected to join Patriotic Ginbot 7

September 8, 2015

Update: Our earlier report regarding the armed groups merger expectation confirmed with slight change. Please listen the latest ESAT News.

Four Ethiopian armed groups merged and form United Movement (ESAT)
Four Ethiopian armed groups merged and form United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy. Dr. Berhanu Nega became the leader of the United Movement. More…
——————————————————-
Eritrean Press reported Tigray Peoples Democratic Movement (TPDM) and Oromo Liberation Front (OLF) lead by Brigadier General Kemal Gelchu expected to join Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy.
Ever since the arrival of Prof. Berhanu Nega (Patriotic Ginbot 7 Chairman) and other Patriotic Ginbot 7 leaders in Eritrea, there has been a rumour that merger talks between the three major Ethiopian armed fronts are underway.
Also Patriotic Ginbot 7’s short social media update strengthen the above news:
#Ethiopia, Breaking News is on the way! Stay tuned. A major political shift into high gear to take action on the minority led TPLF.
While the united Ethiopian front against Ethiopia’s tyrannical regime Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) in progress, Asmara’s Ministry of Information statement accused TPLF’s war drums against Eritrea.
According to Agence France-Presse Eritrea’s Ministry of Information says:
War-like rhetoric from Ethiopia’s main party in the ruling coalition — the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) — had increased.
“The TPLF’s sabre-rattling has been a common staple throughout winter. And this has been ratcheted up in the past few weeks,” said the information ministry statement, released Monday.
Asmara said its progress had sparked “frustration bordering on insanity in the camp of the TPLF and its key sponsors.”
Patriotic Ginbot 7 fighters

ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ

September 8,2015
የጦርነት አታሞ እየተመታ ነው፤ “ሳንጃም ተስሎብኛል”
melesna isayas
ቀደም ሲል የአባትና ልጅ “አፈጣጠርና ግንኙነት” የነበራቸው ወዳጆች ሻዕቢያና ወያኔ ያልተጠናቀቀውን የባድመን ጦርነት ካካሄዱ በኋላ ለዳግም ግጥሚያ ዝግጅት እያደረጉ ነው። “የጦርነቱ ሁኔታ” ያሳሰበው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል ለህወሃት ማጠንቀቂያ ሰጥቷል። ከጥቂት ሳምንታ በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ እንደዘገበው በዘገበው መሠረት መግለጫው ህወሃት ኤርትራን እንዲወጋ የአሜሪካንን ይሁንታ አግኝቷል ብሏል።
የፈረንጅ የቀን አቆጣጠር የሚከተለው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤት በኩል 4 September 2015 ያወጣው መረጃ እንደጠቆመው ህወሃት የተለመደውን የጦርነት አታሞ እየመታና ሳንጃ እየሳለ እንደሆነ ጠቁሟል። የህወሃት አገዛዝ “ሌሎች ክፍሎች ከኤርትራ ጋር እንዳይወግኑ ትንኮሳ እያደረገ” መሆኑን የጠቆመው መግለጫ ወያኔ በኤርትራ ጦርነት ማካሄድ እንዲችል ከአሜሪካ ይሁንታ ማግኘቱን በገሃድ እየተናገረ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከአራት ሳምንታት በፊት “ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል፤ አሜሪካ ሃሳቡ ቀርቦላታል ተብሏል” በሚል ርዕስ ባስነበበው ዜና ላይ እንዲህ ብሎ ነበር። “አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። … አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል።”
ሻዕቢያ ይህንን ቢልም በአገር ውስጥ የሚታየው ሁኔታ ግን ጦሩን ከአንድ ስፍራ የማንቀሳቀስ ሂደት እየተደረገ እንደሆነ ይታያል። ለዚህም የሚሰጠው ምላሽ ቀለል ያለ ብወዛ እንደሆነ ቢነገርም ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለየት ባለ መልኩ በአማራው ክልል የሠራዊቱ ቁጥር እየጨረ መምጣቱ ከሥፍራው የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ዓመት በፊት የአሰብ ወደብ እንዲታደስና በአዲስ መልክ እንዲደራጅ መደረጉ ከተለያዩ ምንጮች ሲነገር የቆየ መሆኑ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በሰሞኑ የህወሃት “ጨዋታ” የአዲስ አበባው አንጃ ይመራሉ የተባለላቸው አርከበ ዕቁባይ ከጥቂት ወራት በፊት የኤርትራንና አሰብ ጉዳይ በተመለከተ “ኤርትራም ሁኔታ መቀየሩ አይቀርም፤ አሁን ያለው ሁኔታ ለዘለዓለም ይኖራል ብለን አንገምትም። በእኔ ግምት በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ውስጥ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ። የኤርትራን ወደብ እንጠቀማለን” ማለታቸው የሚጠቅሱ አስተያየት ሰጪዎች በወያኔና በሻዕቢያ መካከል የሚወራው የጦርነት ዝግጅትና አታሞ ግራ የሚያጋባ እንደሆነ ይናገራሉ።
ከጎልጉል የተወሰደ

በኤርትራ የሚገኙ አራት በትጥቅ ትግል የተሰማሩ ንቅናቄዎች የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ በሚል ስያሜ በይፋ መሰረቱ

 September 8,2015
editorial of allianceበኤርትራ የሚገኙ አራት በትጥቅ ትግል የተሰማሩ ንቅናቄዎች የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ በሚል ስያሜ  በይፋ መሰረቱ::የጋራ ንቅናቄውን የመሰረቱት ድርጅቶቹ  የጋራ ንቅናቄ ምስረታ በማስምልከት  ድርጅታዊ መግለጫ አውጥተዋል 
የኢትዮጵያ ህዝብ የኣገሩን ሉዓላዊነትና ኣንድነት ኣስከብሮ የኖረ ብቻ ሳይሆን ኣፍሪካውያን ወንድሞቹና እህቶቹ ከቀኝ ኣገዛዝ ነፃ እንዲወጡ የራሱ ኣስተዋፅኦ ያደረገ ጀግና ህዝብ ነው። ሆኖም ይህ ጀግና ህዝብ ከኣብራኩ በወጡ ገዢዎች ነፃነቱ ተገፎ፤ መብቶቹ ተረግጠው የመከራ ኑሮ እየገፋ ኣያሌ ዘመናት ኖሯል። ይህ የመከራና የሰቆቃ ኑሮ ዛሬም ኣላበቃም፤ እንዲያውም “ከጭቆና ነፃ ኣወጣንህ” እያሉ የሚሳለቁበት ግፈኛ ገዢዎች የጫኑበት የስቃይ ቀንበር ተሸክሞ የውርደት ኑሮ እየኖረ ነው። የጋራ ንቅናቄ ምስረታ በማስምልከት የወጣን ድርጅታዊ መግለጫ  ለማንበብ ይህን ይጫኑ Read more  የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ 2008

Sunday, September 6, 2015

Millions at risk as severe drought hits Ethiopia

September 6,2015
Addis Ababa - Around 4.5 million Ethiopians could be in need of food aid because of a drought in the country, the UN has said.
Hardest-hit areas are Ethiopia's eastern Afar and southern Somali regions, while pastures and water resources are also unusually low in central and eastern Oromo region, and northern Tigray and Amhara districts.
Reacting to the UN's claims that the number in need had increased by more than 55% this year, Alemayew Berhanu, spokesperson for Ministry of Agriculture, told Al Jazeera that Ethiopia had "enough surplus food at emergency depots and we're distributing it".
"When we were informed about the problem, the federal government and the regional state authorities started an outreach programme for the affected people," he said.
In August, the Ethiopian government said that it had allocated $35m to deal with the crisis that has been blamed on El Niño, a warm ocean current that develops between Indonesia and Peru. The UN says it needs $230m by the end of the year to attend to the crisis.
"The absence of rains means that the crops don’t grow, the grass doesn’t grow and people can’t feed their animals," David Del Conte, UNOCHA'S chief in Ethiopia, said.
One farmer in the town of Zway told Al Jazeera that he was selling personal belongings to stay alive.
"There is nothing we can do. We don't have enough crops to provide for our families. We are having to sell our cattle to buy food but the cattle are sick because they don't have enough to eat," Balcha, who has a family of nine, and grows corn and wheat, said.
El Niño
The onset of El Niño means the spatial distribution of rainfall from June to September has being very low. According to the UN children's agency (Unicef), the El Niño weather pattern in 2015 is being seen as the strongest of the last 20 years.
Experts say it could be a major problem for the country's economy, as agriculture generates about half of the country's income.
Climate shocks are common in Ethiopia and often lead to poor or failed harvests which result in high levels of acute food insecurity.
Approximately 44% of children under 5 years of age in Ethiopia are severely chronically malnourished, or stunted, and nearly 28% are underweight, according to the CIA World Factbook.
Unicef says that about 264 515 children will require treatment for acute severe malnutrition in 2015 while 111 076 children were treated for severe acute malnutrition between January and May 2015.
Aljazeera

Saturday, September 5, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ለ1 ሰዓት የፈጀ ውጊያ ማድረጉን አስታወቀ * ገድያለሁ፣ መሳሪያም ማርኬያለሁ ብሏል

September 5,2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የውስጥ አርበኞች በህወሓት አገዛዝ መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ለአንድ ሰዓት የዘለቀ ከባድ ውጊያ አድርገው ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን አስታወቀ::
Arebegnoch Ginbot 7

የአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች ህወሓት "ክልል አንድ" እያለ በሚጠራው በጎንደር-ወልቃይት ደጃች ሜዳ ወረዳ አቤራ ቀበሌ ስልኪ ዳግባ በተባለው ቦታ ነሃሴ 23 2007 ዓ.ም በህወሓት መከላከያ ኃይል ላይ ድንገተኛ የተኩስ ውርጅብኝ በመክፈት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ወታደሮችን ገድለውና አቁስለው ድል ተቀዳጅተዋል፡፡

በአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞችና በህወሓት የመከላከያ ሰራዊት መካከል የተካሄደው ድንገተኛ የሆነ ከባድ ፍልሚያ እኩለ ቀን ላይ ከ6፡30 ጀምሮ እስከ 7፡30 ለአንድ ሰዓት የዘለቀ ሲሆን ምሳ በመመገብ ላይ እያለ ባልገመተው ሁኔታና ባለሰበው አሳቻ ሰዓት ድንገተኛ ተኩስ ተከፍቶበት የእሳት ዝናብ በላዩ ላይ የወረደበት የህወሓት ሰራዊት አብዛኛው ተበታትኖ ከአካባቢው የሸሸ ሲሆን የአፀፋ ተኩስ ከፍቶ ለአንድ ሰዓት ለመከላከል የሞከረው ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል፡፡

የውስጥ አርበኛው ሽምቅ ተዋጊ ኃይል መትረየሶችን ጨምሮ በርካታ ክላሽን ኮቮች ከነመሰል ጥይቶቻቸው ለመማረክ ችሏል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ከሰኔ 25 2007 ዓ.ም እስከ ሀምሌ ወር መጀመሪያ በወልቃይት ቃፍታ መሲን፣ ኮርጃሙስ፤ ማይ ሰገን፣ ንኳል ሳግላ፣ በዋልና ማይ እምቧ ላይ በህወሓት መከላከያ ሰራዊት ላይ ተከታታይ ጥቃቶችን በመክፈት በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ የሆነ እልቂትና ኪሳራ በማድረስ ተደጋጋሚ ድሎችን መጎናፀፉ አይዘነጋም፡፡

Thursday, September 3, 2015

ረሀብን ለማጥፋት ህወሓትን ማስወገድ

September 3, 2015
def-thumbረሀብ በአገራችን ላይ እያንዣንበበ ነው። በአፋርና በሱማሌ ከከብቶች አልፎ ሕፃናት እየሞቱ ነው። የረሀቡ አደጋ ወደ ኦሮሚያና ሌሎች የደቡብ ገጠሮች እየተዛመተ ነው፤ ሰሜን ኢትዮጵያም ከአደጋ ውጭ አይደለም።
“ከአስር ዓመታት በላይ በተከታታይ በየዓመቱ ከአስር በመቶ በላይ የኢኮኖሚ እድገት አሳይተናል” የሚለው ዓይን ያወጣ ውሸት፤ “ድህነትን ተረት እናደርጋለን” የሚለው ጉረኛ መፈክር፤ “መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ተርታ እንደርሳለን” የሚለው ባዶ ተስፋ፤ የወያኔዎችና ጀሌዎቻቸው በፎቅና ቪላዎች መንበሽበሽ፤ የድግሶችና የስብሰባዎች መብዛት ለሕዝባችን ቁርስ፣ ምሳና እራት አልሆኑም።
አገዛዙ ጉራውና ባዶ ተስፋ መስጠቱ እንዳለ ሆኖ የረሀቡን ምክንያት በተፈጥሮ ላይ ማላከኩን ተያይዞታል። ለመሆኑ ተፈጥሮ ብቻውን እየተደጋገመ ለሚመጣ ችጋርና ቸነፈር በቂ ምክንያት ሆኖ ያውቃልን? አስከፊ የረሀብ ዜናዎች የሚሰማባቸው አገሮች በሙሉ ነፃነት የታፈነባቸው አገሮች መሆናቸው የአጋጣሚ ጉዳይ ነውን? ለምንድነው አንድ ዓይነት ችግር እየተደጋገመብን መላ መፈለግ ያቃተን? መልሱ አጭርና ቀጥተኛ ነው። “ችግር የመሳካት እናት” የምትሆነው በነፃነት ማሰብ የሚችል ጭንቅላት ሲኖር ነው። በባርነት ጨለማ ውስጥ ያለ ጭንቅላት ለችግሮች መፍትሄ የማፍለቅ አቅም የለውም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነቱ ድኩም ጭንቅላት ችግሮችን ማሸነፍ ሳይሆን ተሸናፊነትን ተቀብሎ ከችግሮች ጋር ተስማምቶና ተወዳጅቶ መኖርን ይመርጣል። ነፃነት ያለው ሕዝብ ረሀብን እንደሚያሸነፍ ተደጋግሞ የታየ ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው ረሀብን የተፈጥሮ ሚዛን መዛባት ውጤት ብቻ አድርጎ ማቅረብ እውነትን መሸፈጥ የሚሆነው። ረሀብ የብልሹ አስተዳደር ውጤት ነው።
አገራችንን የረሀብ ቀጠና ካደረጉ የ24 ዓመታት የህወሓት “ድሃን ዘርፈህ ብላ” የኢኮኖሚ ፓሊሲ ውጤቶች መካከል አንዳንዱን ለአብነት ያህል መዘርዘር ይቻላል።
1. ገበሬና መሬት ተለያይተዋል። ለም መሬቶች በኢንቨስትመንት ስም በዘመኑ የህወሓት ጉልተኞች በመያዛቸውና እነሱ ደግሞ በተራቸው ለባዕዳን እየሸጡ በመሆኑ ባለሀገሩ ጭሰኝነት እንኳን አጥቶ ለቀን ሠራተኝነትና ልመና ተዳርጓል። አዳዲሶቹ ባለሃብቶች ለፈጣን ኪስ መሙላት እንጂ ለዘለቄታ የአፈር ልማት ፍላጎቱም እውቀቱም የላቸውም። በዚህም ምክንያት ገበሬው ትንሽ የዝናብ ዝንፈት እንኳን መቋቋም እስከማይችልበት ደረጃ ተዳክሟል።
2. በዘር ላይ በተመሰረተ ክልላዊ ድንበር ሳቢያ ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች በአገራቸው ውስጥ ተዘዋውረው መሥራት አልቻሉም። ከሰሜን ወደ ደቡብ ከተሰደደ የአገራችን አርሶ አደር ይልቅ ለቻይና ገበሬ መሬት ማግኘት ይቀለዋል። እንዲያውም ኢትዮጵያዊው ድሀ ገበሬ በዱላ ሲባረር፤ ከውጭ አገር የመጣው ቱጃር ገበሬ ብድርና ማበረታቻዎች ይሰጠዋል።
3. ደኖቻችን ተጨፍጭፈው፣ ለም መሬታችን ተሸርሽሮ በማለቁ የግብርናችን ምርታማነት በእጅጉ ቀንሷል። በዘመነ ወያኔ የደን ጭፍጨፋና የመሬት መሸርሸር በአስደንጋጭ ሁኔታ ጨምሯል። አገሪቷ በፍጥነት ወደ ምድረበዳነት እየተቀየረች ነው።
4. ፋይዳ ያለው የስነ ሕዝብ ፖሊሲ ባለመኖሩ የሕዝብ ብዛት አሻቅቧል። እንደ ኢኮኖሚው ሁሉ ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ብዛት ሊቆጣጠር የሚሞክረው ቢሮ ውስጥ ቁጭ ተብሎ በሚደረግ የቁጥር ጨዋታ ነው። የስታተስቲክሱ ባለሥልጣን ቁጥራችንን በትክክል ሊነግረን ባይፈልግም እንኳን ረሀብ መብዛታችንን እየነገረን ነው።
5. የህወሓት ባለሥልጣኖችና በየክልሉ ያደራጇቸው ምስለኔዎች ራሳቸውን ባለሚሊዮኖች አድርገዋል። እነዚህ በአንድ ጀምበር የበቀሉ ቱጃሮች ከገንዘብ በተጨማሪም የጄኔራልነት፣ የሚኒስቴርነት፣ የክልል ገዢነት፣ እጅግ ቢያንስ የቢሮ ኃላፊነት ሥልጣንን ኪሳቸው ውሰጥ ከተዋል፤ ልባቸው የተመኘውን ዲግሪ ሸምተዋል። የመንግሥት ሥልጣንና ሃብት ይኸን ያህል የተቆራኙበት ሥርዓት በኢትዮጵያ ኖሮ አያውቅም። የጥቂቶች ያለአገባብና ያለቅጥ መክበር በአንፃሩ ደግሞ የብሃኑን ሕዝብ መደህየት ድህነትን መዋቅራዊ አድርጎታል።
6. በአቋራጭና በፍጥነት ለመክበር አስተማማኙ መንገድ የገዛ ራስ ጥረትና ታታሪነት ሳይሆን ቅጥፈት፣ አጭበርባሪነትና ሎሌነት መሆኑን የወያኔ ካድሬዎች በተግባር እያሳዩ ጥሮ ማደርን “ኋላ−ቀር አሠራር” አድርገውታል። በህወሓት የኢኮኖሚ ፓሊሲ የተበረታቱት አድርባይነት፣ ስንፍናና እና ልመና ችግርን የመጋፈጥ አቅማችንን ሰልበውታል።
እነዚህና የመሳሰሉት ጭብጦችን በማንሳት የረሀቡ መሠረታዊ ምክንያት የህወሓት አገዛዝ እንጂ ተፈጥሮ አለመሆኑን አስረግጠን እንናገራለን። ሕዝባችን በነፃነት ማሰብ፣ መመራመር፣ መፈተሽ ቢችል ኖሮ ረሀብን ማጥፊያ ብልሃት ማግኘት ባላቃተውም ነበር። ወደፊትም ቢሆን ተፈጥሮ እኛ እንደፈለግናት አትሆንም፤ መተማመኛችን የሰው ልጅ ወሰን የለሽ የፈጠራ ችሎታና ችግሮችን የመፍታት አቅም ነው። ለዚህ ደግሞ ችግሮችን በልጦ መገኘት ያስፈልጋል። ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከችግሮች በታች ሆኖ መፍትሄ ከአገዛዙ የሚጠብቅ ደካማ እንዲሆን አድርጎታል። በዚህም ምክንያት ነው የችግሮቻችን ቁንጮ ራሱ ወያኔ ነው የምንለው።
ህወሓትን ከመንግሥት ሥልጣን ሳናስወግድ ድህነትንና ረሀብ እናስወግዳለን ማለት ዘበት ነው:: ድህነት የህወሃት ዋነኛ የገቢ ምንጭ በመሆኑ ህወሓት ሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ በወሬ ካልሆነ በስተቀር ድህነት በተግባር ሊቀጭጭ አይችልም። ችጋርና ህወሓት እጅና ጓንት ናቸው። ረሀብ የህወሓት ባለውለታ ነው። ረሀብ የህወሓት የቁርጥ ቀን አጋሩ ነው። ህወሓት በረሃ እያለ በአሸዋ የተሞሉ ጆንያዎችን እህል አስመስሎ በመሸጥ ለእርዳታ በመጣ ገንዘብ ራሱን አደራጅቷል። ስልጣን ከያዘም በኋላ “ረሀብን እየተዋጋሁ ነው” በማለት የምዕራባዊያንን ድጋፍ ለማግኘት ጠቅሞታል። ረሀብና ችጋር የወያኔ “ጪስ አልባ” እንዱስትሪዎች ናቸው። ሕዝባችን ተራበ ማለት የወያኔ ኩባንያዎች ሥራ አገኙ ማለት ነው። ህወሓት ረሀብን ለመቀነስ ቅንጣት ታህል ፍላጎት ቢኖረው ኖሮ በዚህ ወር ውስጥ በተደረጉ ስብሰባዎች በወጣው ወጪ ብቻ በአገራችን ላይ ያንዣበበውን ረሀብ በቁጥጥር ማዋል በተቻለ ነበር።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለወገኖቻቸን መራብ ተጠያቂው የህወሓት ዘረኛ አገዛዝ ነው ይላል። ረሀብን ከኢትዮጵያ ምድር ለዘለቄታው ለማስወገድ የህወሓት አገዛዝን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ደህንነት የቆመ፣ በሕዝብ የተመረጠ እና ከሕዝብ አብራክ የወጣ መንግሥት እንዲኖረን እንታገል ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Tuesday, September 1, 2015

በጀኔራል ሳሞራ የኑስ እየተመራ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ስብሰባ ያለመፍትሄ ተበተነ

September 1,2015
samora yunus
በጀኔራል ሳሞራ የኑስ እየተመራ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የመከላከያ  ከፍተኛ አዛዦች ግምገማዊ ስብሰባ ያለመፍትሄ መበተኑን ለማወቅ ተችሏል።በመረጃው መሰረት- በአዲስ አበባ ከተማ በጀኔራል ሳሞራ የኑስ የተመራው የገዥው መንግስት ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች ከነሃሴ 12 ቀን 2007 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ እንደቆየ የገለፀው መረጃው፤ የስብሰባው አጀንዳም መንግስት አዲስ የመከላከያ ሰራዊት አሰልጥኖ ይለቃል ወደ እናንተ ሲደርስ ግን በርካታው ሰራዊት ይጠፋል ምክንያቱ ምንድንነው? ስራችሁ ምንድንነው? የሚሉና ሌሎችም በመድረክ መሪው በሳሞራ የኑስ የቀረቡ ሲሆን በርካታዎቹ በተቃውሞ ድምፅ ስለተቃወሙት በመካከላቸው ልዩነት ተፈጥሮ ስብሰባው ያለ ፍሬ ነገር እንደተበተነ ለማወቅ ተችሏል።

መረጃው ጨምሮም- ግምገማው በከፍተኛ አዛዦች ዘንድ መረዳዳት ያልነበረው ስብሰባ እስከ ታች እዞች የወረደ ሲሆን በተለይ በሰሜን እዝ ከሚገኙ ሬጂመንቶች በሚጠናቀቀው አመት ብቻ በረከት ያለ ቁጥር ያላቸው ወታደሮች በመጥፋታቸው ዋና መነጋገሪያ አጀንዳ በመሆኑ አንዳንድ አዛዦች ከስራቸው ታግደው በመቐለ ስታፍ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

Thursday, August 27, 2015

መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት !


August 27, 2015
def-thumbየግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው። በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።
በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።
“ወይን ለመኖር” የኢትዮጵያን ሕዝብ ያዋረደ፤ ለትውልድ የሚተርፍ የማኅበራዊ ስነልቦና ኪሳራ ያደረሰ እና ደካማውን ወያኔን ጠንካራ በማስመሰል በሕዝብ የትግል መንፈስ ውስጥ ፍርሃትን የረጨ መሆኑ ግንዛቤ እየዳበረ በመጣ መጠን እየቀነሰ የመጣ ክስተት ነው። በአሁኑ ሰዓት ከቀድሞው እጅግ በተሻለ ኢትዮጵያ ውስጥ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ራሳችንን ከህወሓት ባርነት እያላቀቅን ምሬታችንን በግልጽ መናገር የጀመርንበት ወቅት ነው፤ ከዚያም አልፎ የህቡዕ ተግባራዊ የትግል እንቅስቃዎችን ማድረግ ደረጃ ላይ ደርሰናል።
አገር ውስጥ እየተዋረደ የመጣው “ወይን ለመኖር” በአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካይነት በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን (ዲያስፓራ) መካከል ነፃነታቸውን በጥቅም የሚለውጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ፍለጋ ተሠማርቷል። አገዛዙ ተስፋ ያደረገው ያህል ባይሆንም ጥረቱ የተወሰነ ውጤት እያስገኘለት ነው። በጥቅማ ጥቅም እየደለለ ካመጣቸው ውስጥ በስርዓቱ ብልሹነት ያዘኑና የተሰማቸውን በግልጽ የተናገሩ መኖራቸው የሚያስደስትና የሚያበረታታ ቢሆንም ከመንደር ካድሬዎች ባነሰ ተለማማጮችና አጎብዳጆች በማየታችን ተሸማቀናል። ኢትዮጵያ ውስጥ ካለነው አብዛኛው ሕዝብ አንፃር ሲታይ በተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙት ዲያስፓራዎች መካከልም ነፃነታቸውን በጥቅም ለመለወጥ የሚፈቅዱ መገኘታቸው አሳዛኝ ነው። እነዚህ ክብራቸውን በጥቅም የለወጡ ዲያስፓራዎች ዓለም ባንክንና የዓለም የገንዘብ ድርጅትን (IMF) ተክተው ህወሓት ስላስገኘው ፈጣን እድገት በአገዛዙ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ሲነግሩን መስማት ያሳፍራል። የህወሓት አገዛዝ “ፍትህን፣ መልካም አስተዳርንና ዲሞክራሲን አስፍኗል፤ ይህንንም መጥተን በዓይኖቻችን ተመልክተናል” እያሉ የግፉን ገፈት እየቀመስን ላለነው ሲነግሩን መስማት ያማል።
እነዚህ ወገኖቻችን ህወሓትን በማሞካሸት የሚያገኙት መሬት ብዙ ድሆች የተፈናቀለቡት፤ ለእነሱ በብላሽ የተሰጠው ብድር በረሃብ ለሚጠቃ ወገን የተላከ እርዳታ መሆኑ ማሳሰብ ይገባል። ከህወሓትና አጫፋሪዎቹ ጋር ተስማምተው ባገኙት ገንዘብ የሚቆርሱት እያንዳንዱ እንጀራ የብዙ ወገኖቻችን ደምና እንባ የፈሰሰበት መሆኑ ማስገንዘብ ያሻል። ከህወሓት ጋር በማበር በወገኖቻችን ድህነትና ችጋር እየከበሩ ያሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት ከዚህ እኩይ ሥራቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቅ ይገባል። እኚህ ወገኖች የራሳቸው ክብር ማጉዳፋቸውን ብቻ ሳይሆን የልጅ ልጆቻቸውም የሚያፍሩባቸው መሆኑን ማስታወስ ይገባል። ከዚህም አልፎ የዛሬ ተግባራቸው ነገ በህግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ የአገዛዙን እድሜ በማራዘም ላይ የተሰማሩ፤ በድሆች ድህነት ለመክበር በመሯሯጥ ላይ ያሉ፤ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ለአገዛዙ ጥብቅና የቆሙ የዲያስፓራ አባላት ከዚህ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ያሳስባል።
አርበኞች ግንቦት 7 “ከህወሓት ውድቀት በኋላ ያለው ጊዜ ለእናንተም ከዛሬው የተሻለ ይሆናል። ዛሬ ከህወሓት ጋር ያላችሁን ሽርክና አቋርጡ። ለነፃነት የሚደረገውን ትግል እርዱ፤ መርዳት ባትችሉ እንቅፋት አትሁኑ፤ አለበለዚያ ግን ከተጠያቂነት የማታመልጡ መሆኑን እወቁ” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!! !

Wednesday, August 26, 2015

በዜጎች ላይ የሚፈፀመዉ ሰቆቃ አሁንም እየቀጠለ ነው!!

August 26,2015
amharic hateta
በሺዎች የሚቆጠሩ በርካታ ሰዎች በየክልሉ በተቋቋሙ እስር ቤቶች ዉስጥ ክስ ሳይመሰረትባቸዉ እንደሚታሰሩና፤ ግርፋት ሰቆቃና ድብደባ እንደሚደርስባቸዉ አልፎ ተርፎም እንደሚገደሉ ከኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወረ አይደለም።
በኢትዮጵያ የህግ አስፈፃሚ አካላት የሆኑት ፖሊሰ፤ ፍርድ ቤቶችና ወህኒ ቤቶች ኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ሙሉ በሙሉ ከመዉደቃቸዉ ሌላ የአገሪቱ የተወካዮች ምክር ቤት እንኳ ሊያዝዛቸዉ እንደማይችል በተለያየ ወቅት ተመስክሯል።
የፖሊስ ጣቢያዎች፤ የአስተዳደር ጽ/ቤቶች፤ወታደራዊ ካምፖች፡ ህጋዊ እስር ቤቶች፡ ሚስጢራዊ ስዉር እስር ቤቶች፡ በሀገረ ማርያም፤ ሁርሶ፤ ዴዴሳ፤ አጋርፋ፤ ዝዋይ፤ ጦላይ፤ቃሊቲ፤ማእከላዊ፤ በየክልል ወህኒ ቤቶችና በተለይ በአዲስ አበባ ዘመናዊ ቪላዎች በመከራየት በእስር ቤትነት ከመጠቀሙም በላይ በእስረኞች ላይ ሰቆቃ፤ ግርፋትና ድብደባ መፈፀሚያ በማድረግ እንደሚገለገልባቸዉ ይታወቃል።
የአለም አቀፍ የሰብኣዊ መብት ድንጋጌም ሆነ ህወሀት/ኢህአዴግ ያፀደቀዉ የአገሪቱ ህገ መንግሰት በማንም ሰዉ ላይ ሰቆቃ፡ ግርፋትና ድብደባ እንዲሁም ጭካኔ የተመላበት ኢ-ሰብኣዊ ድርጊትም ሆነ ስብዕናን የሚያዋርድ  ተግባር ሊፈፅምበት እንደማይገባ ይጠቅሳል። ይሁን እንጂ ይህ በእስራት ወቅትና ከእስራት ዉጭ በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች፤ የደህንነት፤ የፖሊስ፤ የድርጅቱ ካድሬዎችና ወታደሮች አማካይነት በመላዉ የአገሪቱ ክልሎች በዜጎች ላይ የሚፈፀም የየቀኑ ተግባር ነዉ። ይህን በመፈፀም ማእከላዊ የምርመራ ድርጅት በመባል የሚታወቀዉ እስር ቤትና የደህንነት ተቋም የናዚ ጀርመን ይጠቀምባቸዉ ከነበሩት የማጎሪያ ካምፖች ያልተናነሰ እንደሆነ ይነገራል።
ዜጎች በኤሌክትሪክ ገመድና በሌሎችም ነገሮች በመጠቀም እጆቻቸዉ በሰንሰለትና በካቴና ታስረዉ ግድግዳ ላይ በተመቱ ምስማርና ችካሎች እንዳይንቀሳቀሱ ተወጥረዉ፤  የዉስጥ እግራቸዉንና መላ አካላቸዉን በጠቅላላ አዕምሯቸዉን እስኪስቱ ድረስ መደብደባቸውና የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት የፀጥታ ሃይሎች ሱዳን፤ የመን፤ ኬንያ፤ ሶማሊያና ጅቡቲ ድረስ ድንበር ዘልቀዉ በመግባት የሚፈልጓቸዉን ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች አፍነዉ መዉሰዳቸዉና ሊያመጧቸዉ ያልተሳካላቸዉን እንደሚገድሉ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚገባ ያዉቀዋል።
የመንግስት የፀጥታ አስከባሪዎች ሌሎች ታጣቂዎች በቀን በአደባባይ የመንግስትን የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲ የሚቃወሙ ናቸዉ በሚሏቸዉ ላይ ግድያ እስከመፈፀም ያልተገደበ መብት አላቸዉ፤ በእያንዳንዱ የገበሬ ማህበር ቤት እየዞሩ ኢህአዴግን መምረጥ እንዳለባቸዉና ይህን ማድረግ ካልቻሉ ግን ምንም አይነት የመንግስት አቅርቦት እንደማያገኙ፤ ቤተሰቡ የመስራትም ሆነ የመማር እድል እንደማይኖረዉ በግልፅ የተነገረበት ሁኔታ እንደነበርና ኢህአዴግን ያልደገፉ ድሃ ገበሬዎች ማዳበሪያና ሌሎች የእርሻ ግብኣት ድጋፎች እንዳይደረግላቸዉ መከልከላቸዉን የሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች አጋልጠዋል።
ኢህአዴግ የፖለቲካ አላማዉን ለማስፈፀም ላለፉት 24 አመታት በመንግስት ስልጣን ላይ ተቀምጦ በደህንነትና በወታደራዊ ተቋሞቹ አማካይነት የአገሪቱን ፖለቲካ በግሉ ለመቆጣጠር፤ በጎሳና በዘር ላይ የተመሰረተ ፕሮግራም በማካሄድ፡ በፖለቲካና በሲቪክ ማህበራት ድርጅቶችና በሰላማዊ ዜጎች ላይ ይፈፅማቸዉ የነበሩትና ዛሬም የሚፈፅማቸዉ የሽብር ተግባሮች ለመሆናቸዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠንቅቆ ያዉቃል።
እናም የህወሃት/ኢህአዴግ መንግሰት “በሽብርተኝነት” “የአገርን ሰላም በማደፍረስ” “ህገ መንግስታዊዉን ስርአት በመናድ ” “በዘር ማጥፋት” “በአገር መክዳት”   ወዘተ… የሚሉትን የወንጀል ክሶች የሚጠቀምበት ለምን አላማ እንደሆነ ግልፅ በመሆኑ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሳይበረከክ በኢህ አዴግ ስርዓትና ተቋማቱ ላይ የጀመረውን ተቃውሞውን በማጠናከር ማስቀጠል ይግባል።

Tuesday, August 25, 2015

Ethiopia needs $230-million worth food aid

August 25, 2015
(Reuters) – The number of Ethiopians who will need food aid by the end of this year has surged by more than 1.5 million from earlier estimates due to failed rains, United Nations agencies said on Monday.Ethiopians needing food aid
Ethiopia needs an extra $230 million from donors to secure aid for a total of 4.5 million people now projected to require assistance this year, the Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA), the World Food Programme (WFP) and the U.N. children’s agency UNICEF said in a statement.
The country of 96 million people is one of Africa’s fastest-growing economies, but failed rains have devastating consequences for food supplies.
“The belg rains were much worse than the National Meteorology Agency predicted at the beginning of the year. Food insecurity increased and malnutrition rose as a result,” said David Del Conte, UNOCHA’s acting head of office in Ethiopia, referring to the short, seasonal rainy season that stretched from February to April.
Areas normally producing surplus food in the Horn of Africa country’s central Oromia region were also affected by shortages, the statement said, adding lack of water had decreased livestock production and caused livestock deaths in other pastoralist areas.
Meteorologists have warned that the El Nino weather phenomenon, marked by a warming of sea-surface temperatures in the Pacific Ocean, is now well established and continues to strengthen. Models indicate that sea-surface temperature anomalies in the central Pacific Ocean are set to climb to the highest in 19 years.
The El Nino can lead to scorching weather across Asia and east Africa but heavy rains and floods in South America.
The United Nations cautioned that the anomaly could further affect Ethiopia’s “kiremt” rains that stretch from June to September.
“A failed belg followed by a poor kiremt season means that challenges could continue into next year,” said John Aylieff, WFP’s Ethiopia representative.

Saturday, August 22, 2015

በሶማሊያ ሀገር ህይወታቸው እያለፈ ያሉ የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው እየጨመረ ነው

August22,2015

ethiopia millitary in somaliaእየተላኩና ህይወታቸው እያለፈ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ከቀን ወደ ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ እንደሆነ ከተለያዩ ያገራችን አካባቢዎች የደረሰን መረጃ አስታወቀ።በሶማሊያ ሃገር እየሞቱ ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሟቾቹ ቤተሰብ በየግዜው በቴለፎን መርዶ እየደረሳቸው እንደሆነ የገለፀው መረጃው በተለይም የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ለምንድነው ስልጣን ላይ ያለው ስርዓት የሞቱት ልጆቻችን የማይነግረን በመሰረቱ ልጆቻችን ወደ ሶማልያ አገር ሂደው እንዲያልቁ የሚደረገውስ ለምን ዓላማ ነው? የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው ግልፅ በሆነ መንገድ መነገር አለበት በማለት ጥያቂያቸውን እያቀረቡ መሆናቸው ተገለጸ።
ይሁን እንጂ የኢህአዴግ ባለስልጣን አልሸባብን ለማጥፋት በሚል ምክንያት ከሃያላን መንግስታት የሚያገኙትን ዶላር ለመሰብሰብ ካልሆነ ከአገሩ ውጭ እየሄደ ህይወቱን እያጣ ላለው ወጣትና ቤተሰቦቹ ግን ምንም ዓይነት ደንታ እንደሌላቸው የሟቾች ቤተሰብና አንዳንዱ የአገራችን ምሁራኖች አስተያየታቸው እየሰጡ መሆናቸው አስታውቋል።
በተመሳሳይ አንድ በትግራይ ማእከላዊ ዞን፤ ተምቤን ዓብይ ዓዲ ውስጥ የሚኖሩ ወላጅ ልጃቸው በሶማልያ ሃገር ሄዶ መሞቱ ለምን አላማ ሲባል ነው ብለው መጠየቃቸው ባለፈው የዜና እወጃችን መገለፁ ይታወቃል።

ሆዳም ቢሰበሰብ መግላሊት ኣይከፍትም

August 22, 2015
ከብርሃኑ ተስፋዬ
የሰይጣኑን ሙት ኣመት ለማክበር በሚዘጋጁበት ወቅት ወያኔዎች ሆዳም ዲያስፖራዎችን ወደ ኣዲስ ኣበባ ጋብዘው ቡራ ከረዩ የሚሉበት ሁኔታ ስለገረመኝ ነው ይህን ጽሁፍ ለንባብ የማቀርብላችሁ። በመሆኑን መልካም ንባብ።Ethiopian Diaspora
መነሻ
በመጀመሪያ የሰው ልጅ ከትውልድ ቀየው ወደ ተለያዩ ቦታ ወይም የኣለም ክፍሎች የሚሰደደው ኣንድም በሃገሩ ባለው የፖሊቲካ፣ የሶሽያልና የኢኮኖሚ ሁኔታ ኣለመመቻቸት ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። እውነቱና ሀቁም ይህ ሆኖ ሳለ የተሰደደበት ችግር በሚቀረፍበት ጊዜ ኣንድም በኣካል ኣሊያም በሃሳብ፣ ማቴሪያል፣ ወይም በገንዘብ ለሃገሩ ኣስተዋጾ ያደርጋል። ይህንን ኣይነት ሁኔታ ሊፈጠር የሚችለው ግን በተሰደደበት ወቅት የነበረው የመንግስት ስርኣት ሲቀየር የሚከተላቸው ፖሊሲዎች ዲያይስፖራውን እንደ ኣንድ ኣገር ገንቢ ኣካል ቆጥሮ በእኩልነት ማሳተፍ የቻለ እንደሆነ ነው።
በኣንድ ጥናት እንደሚያሳየው በአሜሪካ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ፣ ጋናና ዚምባዌ ዲያስፖራ አባላት(2010) በ2009 ብቻ የኣመታዊ ምርታቸውን 6.5 ፣ 7.5ና 34.4 በመቶ ወደየሃገሩ ተልኩዋል። ይህም ባንድ በኩል ከዲያስፖራው ወደ ሃገር ከሚገባው የክህሎት፣ የፖሊቲካ፣ የባህልና ሶሺያል ካፒታል በተጨማሪ የተገኘ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም።
ይህን በመነሻ ያነሳሁት ለመንደርደሪያ ይሆን እንጅ ዋናው ሃሳቤ ይህን ሃሳብ ይዤ ለመሙዋገት ኣይደለም። ሆኖም የዲያስፖራውን ሃይል ባግባቡ መጠቀም የሚፈልጉ መንግስታት ካሉ ያለውን እምቅ ሃይል ለማመላከት ብቻ ነው።
መረማመጃ
ኣሁን በኣለም ላይ ተበትኖ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ኣንድም የጉጅሌው ሰለባ የነበረ ወይም በነበረው የፖሊቲካ ኣመለካከቱ ሳይደነብር በሃገሩ መኖር ያልቻለ ስብስብ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። ይህን ስል ግን በቅርብ ጊዜ በስወር ለስለላ የተሰማሩ የጉጅሌው ኣባላት የሉም ለማለት ኣይደለም። እነዚህ ግን ኣምላክ ምስጋና ይግባዉና የጉጅሌው መሪ ተብየ በሞተ ማግስት በየድንኩዋኑ ሙሾ ሲወርዱ ስላገኘናቸው እርቃናቸውን ለማስቀረትና መስመራቸው ወዴት እንደሆነ መለየት ተችሉዋል። ከነሱ በተጨማሪ በጉጅሌው ተሳደድን ተገረፍን መብታችን ተገፈፈ ብለው ይጮሁ የነበሩ ሆኖም ትንሽ ትንፋሽ ሲያገኙ ማንነታቸው ገሃድ የወጡ የሆዳም ስብስቦች ኣደባባይ ወጥተዋል። በመሆኑም ነው ባሁኑ ጊዜ ባለም ላይ ከተበተነው ኢትዮጵያዊ ውስጥ ሆዳሞች ብቻ ተለይተው ወደ ሃገር ለበኣል የታደሙት።
ማንም ሰው ወደ ሃገሩ በመሄድ ቤተዘመዱንም ሆነ የተወለደበትን ቀየ ጉዋደኞቹንም ሆነ ሃገሩን መጎብኘት የለበትም የሚል እምነት የለኝም። ሆኖም ግን በውጭ ሃገር ኢትዮጵያዊነት ሲዋረድ ካዋራጆቹ ጋር ኣብሮ የሚጨፍረውን ወያኔን፣ (ሳውድ ኣረቢያ፥ ሊቢያ፥ የመን፥ሌሎች ኣረብ ሃገሮች) መልካም ገጽታ ኣለኝ ብሎ እንዲያናፍስበት የፖሊቲካ መጠቀሚያ ለመሆን ባህር ኣቓርጦ በጎርሻ በሚኖር እናት፣ ኣባት፣ ወንድምና እህት ላይ መሳለቅ ህሊናቢስ መሆን ነው።
ሌላው ኣስገራሚው ደግሞ ትላንት ጎረቤቱና የመንደሩ ገበሬ የተፈናቀለበትንና በረንዳ የተወረወርበትን ቦታ ለዚህ እኩይ ስራ እጅ መንሻነት ውሰድ ሲባል እሽ ብሎ ተቀብሎ የራሱን ፍላጎት ብቻ መመልከቱ ከሆዳምነት የመጨረሻው ሆዳምነቱን የሚያመላክት ነው።
ባሁኑ ወቅት ተሰባስበው የታደሙትን የዲያስፖራ ኣባላት በተናጠል ብንመለከት በውስጣቸው የተሰባሰቡት ኣንድም በወያኔ ድርጎ የራዲዮ ጣቢያ፣ የውይይት መድረክ ኣልያም ወያኔ ከህዝብ በዘረፈው ሀብት መዋእለ ንዋይ ተሰጥቶዋቸው ገበሬውን በማፈናቀል ቦታ የተረከቡ ናቸው። ኣንዳንዶቹም በሚኖሩበት ሃገር መንግስት ድጎማ የሚኖሩና የወር ገቢያቸወ እንኩዋን ድርጅት ለመመስረት ከወር ወር የሚያኖራቸው ኣለመሆኑን እያወቅን በሶስት ወር ሁለት ጊዜ ወደ ሃገር እንዲጉዋዙ የተደረጉ ናቸው።ይሁን እንጅ ይህ ሁኔታ ኣሁን ለምን ኣስፈለገ የሚለው መሰረታዊ ጥያቄን ማንሳት ያስፈልጋል።
ወያኔዎች ኣንድ ኣለመግባባት በመሃከላቸው በሚኖርበት ጊዜም ሆነ በሃገሪቱ ያለው ትግል ትንሽ ጉልበት ያወጣ ከመሰላቸው ጊዜ መግዣ የሚሉት ዘዴ ኣላቸው። ይህንን በ1997ቱም ምርጫ፣ ህዋህት በሚሰነጠቅበት ወቅት፣ ኣርዮስ መሪያቸው በማቀዝቀዣ በነበረበትም ሆነ ኦባማ ለጉብኝት ከመምጣቱ በፊት ያከናወኑዋቸውን ሸረኛ ስራዎች ማስታወስ ግድ ይላል። እነዚህን ነፍሱን ኣይማረዉና ለገሰ ዜናዊ ወጣት በነበረበት ጊዜ ይተኛበት በነበረው መኝታ ቤት ግድግዳ ላይ የዚያን ጊዜ ያስቀመጠውን “procratination is a theft of time” የሚል ኣባባል መቃብር ከመውረዱ በፊት ለወያኔዎቹ ጥሎ መሄዱን ያረጋግጥልኛል።በወቅቱ ይህ ኣባባል ያመለክት የነበረው የፊዳሉን ኣስተዳደር የመሬት ላራሹ መፈክርን ተግባራዊ ኣለማድረግን የሚያመላክት የነበረ ቢሆንም ከዚያ ትምህርት ቤት የተማረውን የከፋፍለው ግዛ ከ17 ኣመት በሁዋላ ተገባራዊ እንዳረገው ሁሉ ይህንንም መቃብር ይዞት ኣለመውረዱ ርዥራዦቹ እየተጠወሙበት ይገኛል።
ወያኔ ባሁኑ ጊዜ ይህ ዘዴ ኣሁን ያፈለገው በተላያዩ የውስጥና የውጭ ችግሮች መሆኑን በሚከተለው ለማሳየት እሞክራለሁ።
1. በሃገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ እየታገሉ ያሉትን ተቃዋሚዎች ለማስመመሰያነት እየተጠቀመበት ያለው ድራማ በምርጫ 2007 እርቃኑን እንዲወጣ ካደረጉት በሁዋላ ወያኔ ከህዝቡ ልብ ብቻ ሳይሆን ኣንዳንድ የራሱ ኣባላት ምን እየተደረገ ነው የሚል ጭምጭምታ መጀመራቸው ብሎም ኣንዳንድ የተቃዋሚ ድርጅት ኣባላት የወደፊቱ የትግል ኣቅጣጫ ምን መምሰል ኣለበት የሚለው ጥያቄ እያጫረባቸው መሆኑን በገሃድ እየተመለከተው በመሆኑ፣
2. በጎረቤት ሃገር ያሉ በሁለገብ ትግል የሚያምኑ ታጋዮች በመሃከላቸው ያለውን መለስተኛ ኣለመግባባት ወደ ጎን ትተው ኣይናቸውን በቀጥታ ወደ ኢላማቸው ለማነጣጠር በጋራ ለመስራት ኣንድ እርምጃ ወደፊት መጉዋዛቸው፣
3. ወያኔ ከኣለም የረድኤት ድርጅቶችና ኣበዳሪዎች ከሚያገኘው የውጭ ምንዛሪ ቀጥሎ ያለው የገቢ ምንጭ ዲያስፖራው ኣንድም ለቤተሰቡ ኣልያም በኢንቨስትመንት መልክ ወደ ሃገር የሚያስገባው ሲሆን ከዚህ ባሻገር ለዚህ ግንባታ ለዚህ ማስፋፊያ በሚል የልመና ኣቁማዳ ይዞ ሊሰበስበው ያቀደው የውጭ ምንዛሪ በትንታግ ታጋዮች በተለያዩ ኣካባቢዎች ሊሳካለት ባለመቻሉ፣
4. በሃገራችን በያመቱ 7.5 ሚሊዮን ገበሬዎች በበጎ ኣዳራጎት (safety net) ድጋፍ ይኖራሉ፣ ሆኖም ሃገሪቱ በምትከተለው ደካማና ያልተጠና የግብርና ፖሊሲ የተነሳ ራሱዋን በምግብ እህል ልትችል የቻለችው በሃይለ ማርያም ደሳለኝ ኣንደበት ብቻ በመሆኑ ባሁኑ ወቅት 4.5 ሚሊዮን ለረሃብ ኣደጋ የተጋለጡ መሆናቸው በኣለም መገናኛ መነገሩ፣
5. በተለያዩ ሜዲያዎች በሃገሪቱ የሚካሄደው የሰብአዊ መብት ረገጣና የህዝቦች ሰቆቃ የየእለት የመወያያ ርእስ በመሆኑና በሌሎችም ምክንያቶች የህዝባችንን የትኩረት ኣቅጣጫ ማስቀየስ በማስፈለጉ የተዘጋጀ ድራማ ነው።
ለዚህ ድራማና ዘፈን ደግሞ ኣጃቢ በማስፈለጉ በዲያስፖራው የተነገሩ መሰረታዊ ባይሆኑም ወቅታዊ ችግሮች በቅመምነት እንዲስተናገዱ ማድረግ ደግሞ ወያኔ የተካነበት መሆኑን ደደቢት ላይ ተነስታ ሳሞራን የጠየቀችው ኣርቲስትን ማጣቀስ ብቻ በቂ ይመስለኛል። በመሆኑም ወያኔ በውስጡ ያሉትን ኣለመግባባቶች ሽፋን መስጠት በመፈለጉና መቶ በመቶ ኣብላጫ ድምጽ ኣግኝቼ ኣሸነፍሁ የሚለውን የ2007 ምርጫ ተከትሎ ሊያዋቅር የሚፈልገውን የክልልና የዞን ምክር ቤት እስኪያዋቅር ድረስ ከምንሰማቸው ነጠላ ዜማዎች ኣንዱ ኣካል እንጅ ዲያስፖራው በጉቦ የተሰጠውን መሬትም ሆነ ንብረት ሸጦ ወደመጣበት እንደሚመለስ ወያኔም ያውቀዋል ዲያስፖራውም የለመደው ነው። ከዚህ ጋር ግን ኣብሮ መታሰብ ያለበት ይህች ዘለል ዘለል እቃ ለማንሳት ነው እንዲሉ የተለየ ቡድን ግን (ትክክለኛ ወያኔዎች) በልጅ ኣመካኝቶ ይበላሉ ኣንጉቶ እንደሚባለዉ ኣባላቶቻቸውን ለመጥቀም የተዘጋጀ መሆኑን ላፍታም መዘንጋት የለብንም።
ማሳረጊያ
ከላይ የጠቀስኩዋቸው መሰረት በማድረግ ሃሳቤን ለማጠቃለል ይረዳኝ ዘንድ ትናንት የሰማሁትን ባለ ፭ ሚሊዮን ባውንድ ኣጉዋጉዋዥ ኣብዛኛዎቻችን ስንሰማ ግር ያለን እንኖራለን ሆኖም በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ብዙ ሚሊዮኖች ቡልጋሪያ ሃንጋሪና ኡክሬይን ድረስ ተጭነው ሄደው የጦር መሳሪያ መገዛቱን ደግሞ እንረሳለን። በመሆኑም ኣሁን የተሰባሰበው የዲያስፖራ ጋጋታ ኣቅጣጫ ማስቀየሻ በመሆኑ እንደኔ ኣመለካከት ምን ቢሰበሰብ መግላሊት ኣይከፍትም ነውና ኣይናችንን ከኩዋሱ ላይ ማድረግ ብቻ ነው የሚጠበቅብን። በመሆኑም ያለን ባለን ሁሉ ትግሉ ኣንድ እርምጃ እንዲሄድ የየራሳችንን ኣስተዋጾ ማድረጉ ወሳኝነት ኣለው።
ኢትዮጵያ በልጆችዋ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች
chillalo@gmail.com

Monday, August 17, 2015

አምባገነንነትና የነፃነት ጥያቄ!

August 17,2015
ANBAGENEN amahric
የኢህአዴግ ስርዓት በአለፉት 24 ዐመታት ያዋቀራቸው ወታደራዊና የፀጥታ ኃይሎችን ተጠቅሞ የሰፊውን ህዝብ ነፃነት መግፈፍ፤ ውስጥ ለውስጥ የማይስማሙትን ማሰርና መግድል ካለምንም የርዕዮተ-ዓለም መሰረት የሚካሄዱ ከውጭ ኃይል ጋር በጥቅም በመተሳሰር በህዝባችን ላይ ዘመናዊ ባርነት እንዲፈጸም ሆን ብሎ እየተንቀሳቀሰ ነው።
የወያኔ ኢህአዴግ የመንግስት መከላከያ ሃይል፤ የፀጥታውና የፖሊሱ አወቃቀር ካለውጭ ዕርዳታና ምክር እንዲሁም ስልጠና በራሱ ኃይል የተደራጀ የሚል ሰው ካለ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምን እንደሚካሄድ አያውቅም ማለት ነው። ስለዚህም ለነፃነት የሚደረገው ትግል ብዙ የማይታሰቡ ጥያቄዎችን ይዞ መምጣቱ ብቻ ሳይሆን በአንድ አገዛዝ መገርሰስ ወይም መወገድ ብቻ አንድ ህዝብ ነፃነቱን ሊቀዳጅ እንደማይችል ከብዙ አገሮች ታሪክ የምንማረው ሀቅ ነው።
በተለይም ያለፈውን የሰላሳና አርባ ዐመታት የህዝቦችን የነፃነትና የዴሞክራሲ ትግል ስንመለከትና ስናጠና በአብዛኛው የሶስተኛው ዓለም አገሮች የህዝብ ነፃነት ተግባራዊ ሊሆን ያልቻለው የአብዛኛው ህዝብ ጥያቄ ሳይንሳዊና ፍልስፍናዊ በሆነ መንገድ መፈታት ስላልተቻለ ብቻ ነው።
አንደሚታወቀው  በዓለም አቀፍ ደረጃ ካፒታሊዝም ከተስፋፋና የበላይነትን ከተቀዳጀ ወዲህ ጭቆናዊ አገዛዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊስፋፋና አብዛኛዎቹ የሶስተኛው ዓለም አገሮች በወታደራዊ ሃይል ስር በመዋላቸው ምክንያት በዓለም አቀፍ የጭቆናና የአፈና ሰንሰለት ውስጥ ገብተው ለስቃይ እንዲፈረዱ ግድ ሆኗል።
የጥሬ-ሀብት ጥናቶች እንደሚያረጋግጡት አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ይህንን የተትረፈረፈ ጥሬ ሀብታቸውን እያወጡ በስርዓት ለመጠቀም፤ ህዝቦቻቸውን ከድህነት በማላቀቅ ስነ-ስርዓት ያለው ኑሮ ለመገንባትና ህዝቦቻቸውን ለማስከበር ያልቻሉት ከላይ በተዘረዘረው የወታደራዊና የስለላ የጭቆና ሰንሰለት ውስጥ ስለተካተቱና በአሜሪካንና በተቀረው የምዕራቡ ካፒታሊዝም የብዝበዛ አስተሳሰብ ውስጥ ተቀነባብረው ሀብታቸውን በስርዓት እንዳይጠቀሙ ስለተደረጉ ነው።
በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች የተዋቀረው የመንግስት አሰራር በመሰረቱ የህዝቦች አለኝታና የሀብት ፈጣሪ መሳሪያ ወይንም መንገዱን የሚቀይስ ሳይሆን ድህነት እንዲስፋፋና ሁሉም ዜጋ በስርዓቱ ስር ሆኖ እንዲገዛና አስከፊ የኑሮ ሁኔታ እንዲያሳልፍ ነው የሚደረገው።
በሳይንስና ምንም አይነት ፍልስፍና ባልተከተለ መንገድ የተዋቀሩ የመንግስታት አሰራሮች፤ ስነ-ምግባርና ሞራል የጎደላቸው ማህበራዊ ህብረተሰባዊ፤ ባህላዊና ታሪካዊ ኃላፊነት በሚያሸክም መንገድ ስላልተቀመጡ ሁሉም ነገር በተራ ታዛዥነት እንዲፈፀም ምክንያት ሁኗል።
ወደ አገራችንም ስንመጣ የስርዓቱ የአሰራርና የአወቃቀር ስርዓት ከተቀሩት የአፍሪካ አገሮች እምብዛም የሚለይ ሳይሆን የባሰ መሆኑን የሚያከራክረን አይደለም። አንድ ህዝብ ዕውነተኛ ነፃነቱን ሊቀዳጅ የሚችለው ይህ ዐይነቱ እንደሰንሰለት የተያያዘ የጭቆና አገዛዝ ለዕውነተኛ ነፃነት እጦት ዋናው ምክንያት እንደሆነና የድህነትንም አፍላቂና የተስተካከለ ዕድገት እንዳይኖር የሚያግድ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ ሲገባ ብቻ ለነፃነት የሚደረገው ትግል የተቃና ይሆናል።
በሌላ አነጋገር ለዕውነተኛ ነፃነት እታገላለሁ የሚል ሁሉ አገራችን ውስጥ ላለው ፀረ ህዝብ ስርዓትና የአብዛኛዎችን የአፍሪካ አገዛዞች አወቃቀር በሚገባ መገንዘብና ከዚህ በመነሳትም እስካሁን በተካሄደው የትግል መንገድ ዕውነተኛውን የህዝብ ነፃነት ማምጣት እንደማይቻል መረዳት ይኖርበታል።

ዴምህት