Wednesday, May 6, 2015

የኢህአዴግ መሰረተ ልማት ግንባታ ለፖለቲካ ፍጆታ እንጂ ለህዝብ ጥቅም ሲውል አልታየም!!

May 6,2015

amh editorail
በማንኛውም አገር የመሰረተ ልማት ግንባታ ወሳኝ ነው። ነገር ግን የሚሰሩት ግንባታዎች ለፖለቲካዊ ጥቅምና ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ተብሎ የሚሰሩና የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የማይለውጡ ከሆኑ ግን መሰረተ ልማት ብሎ ከመጥራት ይልቅ የሙስና እና የብልሹ አሰራር መሰረተ ተብሎ ቢገለፅ ይቀላል።
የአንድ አገር መሰረተ ልማት የህብረተሰቡን የኢኮኖሚ እድገት ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ፤ በህዝቡ ውስጥ ያለው የኑሮ ሁኔታ ልዩነት የሚያጠብና ሁሉም ዜጎች እኩል ሆነው ለመኖር የሚያስችል መሆን ይኖርበታል።
ባሁኑ ግዜ በኢህአዴግ አመራር አገራችን እየተካሄደ ያለው የመሰረተ ልማት ግንባታ። የሁሉንም ከተሞች እድገት በእኩል የማሳደግ ፋላጎት ሳይሆን ለአንዳንድ ከተሞች ብቻ ልዩ ትኩረት የሚያደርግና በቂ ዝግጅት ሳይደረግበት ግብታዊ በሆነ መንገድ ፖለቲካዊ ጥቅም ለማስገኘት ብቻ ተብሎ የሚካሄድ የግንባታ ስራ በመሆኑ እስካሁን ድረስ አመርቂ የሆነ ውጤት ማምጣት አልቻለም።
በሌላ በኩል ትኩረት ሊደረግበት የሚገባው የመሰረተ ልማት ሁኔታ። የህዝቡ ብዛት ግምት ውስጥ ያስገባ እንዲሆን ማደረግ ነው፣ የሚገነባው የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከህዝቡ ብዛት የሚመጣጠን ካልሆነ ፋይዳ ሊኖረው አይችልም ብቻ ሳይሆን የአገሪቱ ግንባታዎች በረጅም ግዜ ታይተው የሚሰሩና የሚፈጸሙ ካልሆኑ የህብረተሰቡን ፍላጎት ሟሟላትም አይችሉም። በተለይ ያገራችን ህዝብ ከ 20 እና 30 ዓመት በኋላ በእጥፍ ማደግ እንደሚችል ግምት ውስጥ በማስገባት የሚካሄድ የልማት ሁኔታ ከሌለና ከግዜው ጋር እድገት እያረጋገጠ የሚጓዝ መሰረተ ልማት መሆን ካልቻለ ችግሩ አደገኛ ነው የሚሆነው።
ከዚህ በመነሳት የኢህአዴግ ስርዓት በተለይ በከተሞቻችን ውስጥ የመኖሪያ ቤት ግንባታና የመንገድ ስራዎችን በተመለከተ ከተሰሩ በኋላ አስፈላጊውን አገልግሎት ሳይሰጡ ስለሚበላሹ የከተሞቹ ዘመናዊነት መበላሸታቸውን ሳይበቃ ያለ በቂ ጥናትና ክትትል የተሰሩትን መሰረተ ልማቶች እንደገና ለመጠገን እጅግ በርካታ ወጪ ስለሚደረግላቸው ለሌላ ግንባታ መሆን የሚገባውን ያገር ሃብት ተገቢ ባልሆነ መንገድ ሲባክን ማየት የተለመደ አሰራር ሆኗል።
ከተሞቻችን ማደግ ከሚገባቸውን እድገትና ስልጣኔ አኳያ ሲታይ ምንም እንኳን እጅግ በርካታ ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም በቂ ዝግጅት ተሰጥቶት በሰለጠነና ዘመናዊ በሆነ መንገድ መሰራት ሲገባቸው ለከተሞቹ ቀጣይ እድገት ግምት በማያስገባና በሚያበላሽ መንገድ እየተካሄደ በመሆኑ የመሰረተ ልማት ግንባታው ለወደፊቱ ትልቅ ጉዳት ማስከተል እንደሚችል የሚያጠራጥር አይደለም።
ለማጠቃለል የኢህአዴግ ስርዓት የሚያካሂደው የመሰረተ ልማት ግንባታ ባለሙያዎች የተደገፉ ባለመሆናቸውና። ሁሉም የግንባታ ስራዎች በቂ ሞያ በሌላቸው የስርዓቱ አገልጋዮች እየተመራ በመሆኑ አጥጋቢ ውጤት ማግኘት አልተቻለም እየታየ ያለው የግንባታ ሁኔታም ቢሆን የህዝቡና የአገሪቱን ጥቅም ለማስከበር ታስቦ ሳይሆን የስርዓቱን ፖለቲካዊ ስልጣን ለማቆየት ታስቦ እየተካሄደ ያለ መሆኑንና በህዝቡም ላይ የመጣ አንዳችም ለውጥ እንደሌለ ማወቅ ያስፈልጋል።
ዴምህት

የቁልቁለቱን ጉዞ እናስቁም፤ ውርደት ይብቃን!!!

May 6,2015
pg7-logoየህወሓት አገዛዝ ፋሽስታዊ ባህርያት እያደር መረን እያጣ፤ ነውረኛ እየሆነ መጥቷል። በአሳለፍነው ሣምንት ብቻ እንኳን አስነዋሪ ይዘት ያላቸው ሁለት ፋሽስታዊ ክስተቶችን አስተውለናል።
አንዱ በምርመራ ስም በታሳሪዎች ላይ የሚደረገው አሳፋሪ ሰቆቃ ነው። በገላቸው በሚያፌዙና በሚሳለቁ ተቃራኒ ፆታ መርማሪዎች ፊት ለሰዓታት ተመርማሪዎች ራቁታቸውን እንዲሆኑ የሚደረግበት እና እየተፌዘባቸው የሚደበደቡበት ሥርዓት መኖሩ የጉዳቱ ሰለባዎች ይፋ ሲያወጡ እፍረቱ ለመርማሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉድ ተሸክመን ለኖርነው ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ነው። በተለይም ደግሞ እንዲህ ዓይነት ክብረነክ ሰቆቃ በሴቶች ላይ እየተፈፀመ መሆኑን ስንሰማ አገራዊ ውርደቱ ያሸማቅቀናል። እንዲህ ዓይነቶችን በሰው ስቃይና እፍረት የሚዝናኑ ጉዶችን ተሸክመን የምኖር መሆናችን ሁላችንን ያዋርደናል። ይህንን አስነዋሪ “የምርመራ ዘዴ” ያጋለጡት የዞን 9 ብሎገሮች፣ ጋዜጠኞችና ፓለቲከኞች ክብርና ሞገስ የሚገባቸው ጀግኖች ሲሆኑ የተዋረዱት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን መሆናችን ሊሰማንና “ውርደት በቃ” ልንል ይገባናል።
ሁለተኛው አሳፋሪ ድርጊት ደግሞ ወገኖቻችንን በግፍ ባረደው አይሲስ በተሰኘው አሸባሪ ድርጅት ላይ የህወሓት አገዛዝ የተለሳለሰ አቋም ወስዷል ብለው ራሱ ህወሓት በጠራው ሰልፍ ላይ ተቃውሞዓቸውን ባሰሙ ወጣቶች ላይ አገዛዙ የወሰደው የኃይል እርምጃና ከዚያም ወዲህ እየተደረገ ያለው ነገር ነው። አገዛዙ ለፕሮፖጋንዳው ይጠቅመኛል ብሎ በጠራው ሰልፍ ወጥተው ተቃውሞዓቸውን የገለፁ ወጣቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድበዋል፤ በጅምላ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል። የአገዛዙ ካድሬዎች ወገኖቻችንን የፈጀውን አይሲስን በመቃወም ፋንታ የራሱ የህወሓትን ውል አልባ ህግ አክብረው በመንቀሳቀስ ላይ ያሉትን ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን እና አረና ፓርቲን እየወነጀሉ መሆኑ አጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። የአይሲስን አረመኔአዊ ድርጊት ከኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጋር ለማገናኘት በህወሓት የደህንነት ቢሮ አማካይነት እንቅስቃሴ መጀመሩ እየተሰማ ነው። ለወጣቱ በብዛት መሰደድ በምክንያትነት የሚያቀርቡት ደላሎችን መሆኑ አላዋቂነት ሳይሆን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ቅራኔው በኢትዮጵያዊያን መካከል እርስ በርስ እንዲሆን ያለመ መሠሪነት ነው። ከዚህም አልፎ የትግራይ ወጣቶችን ነጥሎ በመሰብሰብ “ትምክህተኞች ሊበሉህ ነውና ታጥቀህ ሳይቀድሙህ ቅደም” እያሉ መቀስቀስ በመንግሥት ደረጃ የእርስ በርስ እልቂትን ከማደራጀት ተለይቶ አይታይም። የሥርዓቱ ይሉኝታ ቢስነት የደረሰበት ዝቅጠት ገላጭ ከሆኑ ነገሮች አንዱ “እስከምርጫ መጨረሻ ድረስ ልጆቻችሁን አስረን እናቆይላችሁ” እያሉ ወላጆችን እስከመጠየቅ መድፈራቸው ነው።
ከላይ በአጭሩ የተዘረዘሩት ኩነቶች የሚያረጋግጡት ህወሓት የተማከለ አመራር አጥተው መንገድ የጠፋቸው፤ ሆኖም ግን እጃቸው ውስጥ የገባው ስልጣንና ሀብት ላለማጣት ምንም ነገር ከማድረግ የማይመለሱ አውሬዎች ስብስብ መሆኑ ነው። እንዲህ ዓይነቱን የአውሬዎች ስብስብ የሚገዛው የህግም ሆነ የሥነ-ምግባር ገደብ የለም። ህወሓት እስር በርሳችንን አባልቶ አገራችንንና ሕዝቧን ወደ ማንወጣው አዘቅት ከመክተቱ በፊት ራሱ ህወሓትን ማስወገድ እና በምትኩት ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን መገንባት የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ይህ ካላደረግን አሁን በወህኒ ቤቶች የሚደረገው ዜጎችን ልብስን አስወልቆ የማዋረድ አስነዋሪ ተግባር ነገ በአደባባዮች የማይደረግ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለንም። ይህ ትውልድ ኃላፊነቱ ካልተወጣ ህግን አክብረው ከአገዛዙ የተለየ ሀሳብ እናራምዳለን የሚሉ ወገኖቻችን በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው። በህወሓት መሠሪ ተግባራት ሳቢያ በክርስትናና እስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያን መካከል ያለው መግባባት እንዲሻክር እየተደረገ ነው። ዜጎችን በማዋረድ የሚደሰት አገዛዝና ለመዋረድ የፈቀደ ሕዝብ እስካለ ድረስ የቁልቁለቱ ጉዞ መጨረሻ የለውም። ይህንን ማስቆም ያለብን እኛ ሁላንችንም ነን። በአደባባይ መደራጀት ሲከለከል በምስጢር መደራጀትን መልመድ የኛ ኃላፊነት ነው። የኢትዮጵያ አርበኞች ድል መታሰቢያ በዓልን ስናከብር ከቀደምቶቻችን ልንወርስ ከሚገቡን እሴቶች አንዱ ለክብራችን ዋጋ መክፈል ያለብን መሆኑን ጭምር ነው። የኢትዮጵያዊያን ክብር በወያኔ ሲዋረድ እያየን ዝምታን ከመረጥን ከዚህም የባሰ እንዲመጣ መፍቀዳችንን እንወቀው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የዜጎችና የአገር ውርደት ይብቃ! በተባበረ ክንድ ህወሓት ይወገድ፤ በምትኩም ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመመሥረት መሠረት እንጣል፤ ይህንን ታላቅ ኃላፊነት ለመወጣት በኅብረት እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

የዜጎች ከፍተኛ ጭፍጨፋ በመተማ

May 6,2015
ሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት፣ የሕወሃት ታጣቂዎች ሁለት ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፈተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአምሳ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል።
በአምቦ፣ በባህር ዳር በመሳሰሉት ቦታዎች እንደታየው ዜጎች በሕወሃት ታጣቂዎች ጥይት እንደ ቅጠል እየረገፉ ነው። ህወሃት ከሕዝብ የሚነሱትን መሰረታዊ የፍትህ፣ የዴሞክራሲና የለዉጥ ጥያቄዎች፣ በሃያ አንደኛ ክፍል ዘመን እንዳሉ ድርጅቶ ዘመናዊና ስልጣኔ በተሞላበት መልኩ ማስተናገድ ሲገባው፣ በስድሳዎች ጊዜ እንደነበረው መግደል፣ ማረድና ፣ ዜጎችን እንደ እንስሳ መደብደቡን በመምረጥ የጫካን ኋላ ቀር ፖለቲካ እያራመደ መሆኑ በድጋሚ ዛሬ ደግሞ በመተማ ተመስክሯል።
ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ከደርቡሽ ጋር በተደረገ ትንቅንቅ አጼ ዮሐንስን ጨመሮ በርካቶች ደማቸውን ያፈሰሱባት መተማ፣ ዛሬ ከዉጭ ወራሪዎች ሳይሆን፣ ከሕወሃቶች በተተኮሰ ጥይት የልጆቿ ደም እየተረጨባት ይገኛል።
መተማ ዛሬ ይሄንን ትመስል ነበር።
 የሚሊዮኖች ድምጽ
metema 3
metema 2
metema

Monday, May 4, 2015

Human Rights Watch Report 2015: Ethiopia

May 3,2015


Internet café in Lalibela, Amhara Region, Ethiopia. © 2010 Hemis.fr/AFP Photo

Hopes that Ethiopia’s government would ease its crackdown on dissent ahead of the May 2015 elections were dashed in 2014.

Instead the government continued to use arbitrary arrests and prosecutions to silence journalists, bloggers, protesters, and supporters of opposition political parties; police responded to peaceful protests with excessive force; and there was no indication of any government willingness to amend repressive legislation that was increasingly condemned for violating international standards, including at Ethiopia’s Universal Periodic Review at the United Nations Human Rights Council.


Freedom of Peaceful Assembly

Security forces have harassed and detained leaders and supporters of Ethiopian opposition parties. In July, leaders of the Semawayi (“Blue”) Party, the Unity for Democracy and Justice (UDJ), and the Arena Tigray Party were arrested.  At time of writing, they had not been charged but remained in detention.

The Semawayi Party’s attempts to hold protests were regularly blocked in 2014.  Its applications to hold demonstrations were denied at least three times and organizers were arrested. Over the course of the year, authorities repeatedly harassed, threatened, and detained party leaders.

In June, Andargachew Tsige, a British citizen and secretary general of the Ginbot 7 organization, a group banned for advocating armed overthrow of the government, was deported to Ethiopia from Yemen while in transit. The transfer violated international law prohibitions against sending someone to a country where they are likely to face torture or other mistreatment. Tsige had twice been sentenced to death in absentia for his involvement with Ginbot 7.  He was detained incommunicado in Ethiopia without access to family members, legal counsel, or United Kingdom consular officials for more than six weeks. He remains in detention in an unknown location.

Protests by members of some Muslim communities against perceived government interference in their religious affairs continued in 2014, albeit with less frequency. As in 2013, these protests were met by excessive force and arbitrary arrests from security forces. The trials continue of the 29 protest leaders who were arrested and charged under the Anti-Terrorism Proclamation in July 2012.

In April and May, protests erupted in towns throughout the region of Oromia against the planned expansion of Addis Ababa’s municipal boundary into Oromia. Security personnel used excessive force, including live ammunition, against protesters in several cities. At least several dozen people were confirmed dead and hundreds were arrested. Many of them remain in custody without charge.

Restrictions on human rights monitoring and on independent media make it difficult to ascertain the precise extent of casualties and arrests. Foreign journalists who attempted to reach the demonstrations were turned away or detained by security personnel. Ethnic Oromos make up approximately 45 percent of Ethiopia’s population and are often arbitrarily arrested and accused of belonging to the banned Oromo Liberation Front (OLF).

Freedom of Association

The Charities and Societies Proclamation (CSO law), enacted in 2009, has severely curtailed the ability of independent nongovernmental organizations to work on human rights. The law bars work on human rights, good governance, conflict resolution, and advocacy on the rights of women, children and people with disabilities if organizations receive more than 10 percent of their funds from foreign sources. The law was more rigorously enforced in 2014.

In March, Ethiopia was approved for membership in the Extractive Industries Transparency Initiative (EITI), which promotes transparency on oil, gas, and mining revenues, despite the requirement for candidate countries to make a commitment to meaningful participation of independent groups in public debate on natural resource management. Ethiopia’s previous application was denied in 2010 based on concerns over the CSO law.

Freedom of Expression

Media remain under a government stranglehold, with many journalists having to choose between self-censorship, harassment and arrest, or exile. In 2014, dozens of journalists and bloggers fled the country following threats. In August 2014, the owners of six private newspapers were charged following a lengthy campaign of threats and harassment against their publications. According to the Committee to Protect Journalists, Ethiopia is one of three countries in the world with the highest number of journalists in exile.

Since 2009, the Anti-Terrorism Proclamation has been used to target political opponents, stifle dissent, and silence journalists. In July, Ethiopia charged 10 bloggers and journalists known as the Zone 9 Collective under the Anti-Terrorism Proclamation after they spent over 80 days in pre-charge detention.  The charges included having links to banned opposition groups and trying to violently overthrow the government. The bloggers regularly wrote about current events in Ethiopia. Among the evidence cited was attending a digital security training course in Kenya and the use of “security in-a-box”--a publicly available training tool used by advocates and human rights defenders. Due process concerns have marred the court proceedings.

Other journalists convicted under the Anti-Terrorism Proclamation-including Eskinder Nega, Reeyot Alemu, and Woubshet Taye-remain in prison.

The government continues to block even mildly critical web pages and blogs. The majority of opposition media websites are blocked and media outlets regularly limit their criticism of government in order to be able to work in the country.

The government regularly monitors and records telephone calls, particularly international calls, among family members and friends. Such recordings are often played during interrogations in which detainees are accused of belonging to banned organizations. Mobile networks have been shut down during peaceful protests and protesters’ locations identified using information from their mobile phones. The government has monitored digital communications using highly intrusive spyware that monitors all activity on an individual’s computer, including logging of keystrokes and recording of skype calls. The government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.

Abuses of Migrant Workers

Hundreds of thousands of Ethiopians continue to pursue economic opportunities in Saudi Arabia, Yemen, Bahrain, and other Gulf countries, risking mistreatment from human traffickers along the migration routes. In Yemen, migrants have been taken captive by traffickers in order to extort large sums of money from their family members. In late 2013 and early 2014, hundreds of thousands of migrant workers, mainly Ethiopians, were detained and deported from Saudi Arabia to Ethiopia. Saudi security forces and civilians attacked Ethiopians, prompting restrictions on migration to certain countries.

Forced Displacement

Both the government of Ethiopia and the donor community failed to adequately investigate allegations of abuses associated with Ethiopia’s “villagization program.” Under this program, 1.5 million rural people were planned to be relocated, ostensibly to improve their access to basic services. Some relocations during the program’s first year in Gambella region were accompanied by violence, including beatings, arbitrary arrests, and insufficient consultation and compensation.

A 2013 complaint to the World Bank’s Inspection Panel from Ethiopian refugees, the institution’s independent accountability mechanism, continues to be investigated. Ethiopian refugees alleged that the bank violated its own policies on indigenous people and involuntary resettlement in the manner a national program was implemented in Gambella. In July, a UK court ruled that allegations that the UK Department for International Development (DFID) did not adequately assess evidence of human rights violations in the villagization program deserved a full judicial review. The judicial review had yet to be heard at time of writing.

Ethiopia is continuing to develop sugar plantations in the Lower Omo Valley, clearing 245,000 hectares of land that is home to 200,000 indigenous people. Indigenous people continue to be displaced without appropriate consultation or compensation. Households have found their grazing land cleared to make way for state-run sugar plantations, and access to the Omo River, used for growing food, restricted. Individuals who have questioned the development plans face arrest and harassment. Local and foreign journalists have been restricted from accessing the Omo Valley to cover these issues.

LGBT Rights

Ethiopia’s criminal code punishes consensual adult same-sex relations with up to 15 years in prison. In March, Ethiopia’s lawmakers proposed legislation that would make same-sex conduct a non-pardonable offense, thereby ensuring that LGBT people convicted under the law could not be granted early leave from prison. However, in April the government dropped the proposed legislation.

Ethiopia came for Universal Periodic Review in May 2014, and they rejected all recommendations to decriminalize same-sex conduct and to take measures to combat discrimination based on sexual orientation.

Key International Actors

Ethiopia continues to enjoy unquestioned support from foreign donors and most of its regional neighbors, based on its role as host of the A frican Union (AU); its contribution to UN peacekeeping, security and aid partnerships with Western countries; and its stated progress on development indicators.

Its relations with Egypt are strained due to Ethiopia’s construction of the Grand Renaissance Dam, which will divert water from the Nile and is due to be completed in 2018. In 2014, Ethiopia negotiated between warring parties in South Sudan, and its troops maintained calm in the disputed Abyei Region. Ethiopia continues to deploy its troops inside Somalia; they were included in the AU mission as of January.

Ethiopia is one of the largest recipients of donor aid in Africa, receiving almost US$4 billion in 2014, which amounted to approximately 45 percent of its budget. Donors remain muted in their criticism of Ethiopia’s human rights record and took little meaningful action to investigate allegations of abuses. Donors, including the World Bank, have yet to take the necessary measures to ensure that their development aid does not contribute to or exacerbate human rights problems in Ethiopia.

Ethiopia rejected recommendations to amend the CSO law and the Anti-Terrorism Proclamation that several countries made during the examination of its rights record under the Universal Periodic Review in May.
SOURCE  http://www.hrw.org/world-report/2015/country-chapters/ethiopia

Sunday, May 3, 2015

በአገራችን ላይ የመልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት አልተረጋገጠም!!

May 2,2015
in our country amharic
በአገራችን የመልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት መከበር ባለመቻሉ ምክንያት ህዝባችን ከድህነት፤ ከስደትና ኋላ ቀርነት መውጣት አልቻለም ብቻ ሳይሆን እኩል የመብቱ ተጠቃሚ ሳይሆን ቀርቶ ውስን ባለስልጣናት ተንደላቅቀው የሚኖሩበት አብዛኛው ደግሞ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ተቆጥሮ በላዩ ላይ በደል እየተፈፀመበት እንዲኖር ተፈርዶበታል፣
ይህ ካለፉት ገዢዎች የጀመረውና አሁንም ቢሆን በከፋ መልኩ እየቀጠለ ያለውን የመልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት ያለመከበር ሁኔታ በህዝባችን ላይ እያደረሰው ያለው ወደር የለሽ ችግር ባሁኑ ግዜ የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ እያስከተለ መሆኑ ይታወቃል፣
የኢትዮጵያ ህዝብ አገሩ ውስጥ እንዳይኖር፤ ተምሮ እድገት እንዳያሳይና ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ተከብሮለት ነፃ ሆኖ እንዳይንቀሳቀስ፤ ነጋ ጠባ ካገሩ እየተሰደደ በሰው አገር እንዲኖርና እንዲዋረድ እያስገደደው ያለ ዋናው ምክንያት እትብቱ የተቀበረባትን ቀየውን አስጠልቶት ሳይሆን ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው መብቱ መከበር ስላልቻለና ባገሩ ውስጥ የህግ የበላይነት ተከብሮ በእኩል ተጠቃሚ ሆኖ መኖር ስላልቻለ ብቻ ነው፣
የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ስርዓት በተለይ በትረ ስልጣኑ ከተቆጣጠረበት ዕለት ጀምሮ። ሁሉም የዴሞክራሲ መብቶች እንደተሻሻሉ አድርጎ ቢናገርም። በተጨባጭ መሬት ላይ እየታየ ያለው እውነታ ግን ከሚባለው በእጅጉ የተለየ ነው፣ ይህንኑ ትልቅ አርእስት እንደ መከራከርያ ተደርጎ ባለፈው ሳምንት በተቃዋሚ ድርጅቶችና በኢህአዴግ መንግስት የተካሄደውን ክርክር ሁሉም ያገሬው ህዝብ እንደተከታተለው። በተለይ በኢህአዴግ ባለስልጣኖች የተሰጠው መልስና አስተያየት እጅግ የሚያሳፍር እንደነበር ተከታትለናል፣
  • ዛሬ በሁሉም ያገራችን ከተሞች ንፁሕ የሚጠጣ ውሃ፤ የመብራት ኃይል አገልግሎት፤ በጋና ክረምት የሚያገናኝ መንገድና ሌሎች መሰረታውያን ነገሮችን ስላልተሟላለት በተከታታይ ብሶቱን እያሰማ ይገኛል፣
  • ዛሬ ባገራችን ውስጥ የኢህአዴግ ስርዓት በፈጠረው የጎሳና የሃይማኖት ልዩነት። ህዝቡ ራስ በራሱ የሚጋጭበትና የማይተማመንበት ሁኔታ ላይ ይገኛል፤
  • ዛሬ። በማንኛቸውም መስሪያ ቤቶች የሚገኙ ባለስልጣኖች። ለስርዓቱ ባላቸው ቅርበት እንጂ በብቃታቸው ተመዝነው ስለ ማይመደቡ። ተጠያቂነት፤ ግልፅነትና ፍትሃዊነት ያለው አሰራር ባለመኖሩ ምክንያት ህዝቡ አቤቱውን እያቀረበ ይገኛል፣
  • ዛሬ። በአለማችን ከሚገኙ አገሮች። ኢትዮጵያ በብልሹ አሰራራቸው ከሚታወቁ አገሮች ከመጨረሻዎቹ በ6 ተርታ ላይ ተቐምጣ። ህዛቧ ወገናዊነት በተጠናወተው ብልሹ አሰራር እየተሰቃየ ይገኛል፣ ባገራችን ውስጥ እነዚህና የመሳሰሉት ከፍተኛ ችግሮች ከመጠን በላይ ተደቅነውና ተስፋፍተው ባሉበት ባሁኑ ግዜ። በየትኛው መመዘኛ ነው ኢህእዴግ ባገራችን ውስጥ መልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት አረጋግጫለሁ እያለ መናገር የሚችለው?
ወደደም ጠላም ይህ ስርዓት ህዝቡን ለማደናገር ብሎ በመልካም አስተዳደርና የህግ የበላይነት በማስፈን ላይ ብዙ ርቀት እንደሄደ አስመስሎ ቢገልፅም።-
  • በግብር አከፋፈል ላይ ፍትሃዊ ያለመሆን፤
  • በበጀት አመዳደብና ቁጥጥር ስርዓት ላይ ከዜሮ በታች መሆን፤
  • እስከታች ወርዶ ከህዝቡ ጋር ተመካክረሮ ያለ መስራት፤
  • ሁሉንም ያገራችን አካባቢዎች በእኩል በማሳደግና ፍትሃዊ በሆነ የተጠቃሚነት ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ያለመሆኑ፤
  • ፈጣን ውሳኔ ያለመስጠትና በወገናዊነትና በአድልዎ የሚፈጸሙ ተግባራት እጅግ የተስፋፉ መሆናቸው እንጂ። ስርኣቱ ለፖለቲካ ፍጆታ ብሎ እንደሚቀሰቅሰው እንዳልሆነና አጠቃላይ ያገራችን ሁኔታ ከኢትዮጵያ ህዝብና ከዓለም ማሀበረሰብ የተደበቀ ነገር እንዳልሆነ ይታወቃል፣
  • ከዴምህት የተወሰደ

Friday, May 1, 2015

Detail of Rights Violation on Zone9 Bloggers and Journalists

May 1, 2015
Ethiopia Human Rights Project
It is now solid one year since the arrest of Zone9 blogger and journalists. there had been 27 court hearings, 86 days of interrogation at the notorious “Meakelawi” interrogation center before they moved to their current detention place in “Kality” and “Kilinto”. during their stay they faced many rights violation. this rights violation had also been reported for the united nations working group for arbitrary detention.
On the commemoration of their arrest the summary of the rights violation was made public for readers and followers of the case of for the last one year. attached is the summary of the rights violation.
Violation on Zone9 Bloggers


የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴ የሺሻ ማጨሻ ሆነ

May 1,2015
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ያስገነባው እና ዘመናዊ ተብሎ የሚጠራቅ ቀነኒሳ ሆቴል በሺሻ ማጨስ የተለከፉ ወጣቶች መጠራቀሚያ እና ጥራቱን ያልጠበቀ ስራ በመስራት የሚታወቅ ሆቴል ሆⶈል ። በአዲስ አበባ ከተማ ወጣት ሴቶች ከተለያዩ ጓደኞቻቸው ጋር የሚቀጣጠሩበት ዋነኛ መድረክ የሆነው ሺሻ ወይንም ሁካ ማጨሻ ስፍራዎች ሲሆኑ ፣በአሁን ሰአት ግን ይህ ሆቴል የሆቴሎች አስተዳደር ድርጅት እና የአዲስ አበባ ስራ እና ከተማ ልማት ቢሮ የሰጠውን፡ሕጝ፡ጥሶ የሺሻ ማጨሻ ሱቅ ማድረጉ በጣም አሳፋሪ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል ።
ቀነኒሳ በቀለ ሆቴሉን ካሰራ በሁዋላ የፊት ለፊት ገጹን የስሙን ጽሁፍ በቻይንኛ ማሰራቱ በሃገሩ ቋንቋ እና በማንነቱ የማይኮራ ነው ሲባል የተወቀሰ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ፣በሌላም በኩል ከፍተኛውን ስራ የሰሩት ቻይናዎች ሲሆኖ ጫና አሳድረውበት ነው ሲሉ ገልጸዋል ;በሌላም በኩል በአማካሪው ግፊት ነው የቻይንኛ ቋንቋ የመሰለ ፊደል ሊጠቀም የቻለው ሲሉም 

በተለይም እንደ አትሌት ቀነኒሳ አይነት የስፖርት ቤተሰብ የሆነ ሰው እና በህዝብ ዘንድ በስራው ገናናነትን ያተረፈው ድንቅ አትሌት ወጣቶችን ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እንዲቆጠቡ መምከር ሲገባው በእራሱ ባሰራው ህንጻ ላይ ታዳጊ ወጣቶች እንዲበላሹ መጋበዙ አሳፋሪ እና ከእሱ ስራ እና ክብር የማይጠበቅ ነው ሲሉ ወርፈውታል ።
በሌላም በኩል ሆቴሉ የሚያቀርባቸው አግልግሎቶች ውስጥ ማናቸውም ከሁካ ወይንም ሺሻ ጋር የሚቀርቡ መጠጦችም፡ምግቦች ዋጋቸው የናረ ከመሆኑም በላይ መንግስት ያለቀረጥ የሚነግዱትን እንደሚያስር እና እንደሚቀጣ ሁሉ የአትሌት ቀነኒሳ ስራ ከማናቸውም ሆቴሎች ደረጃ በላይ ውድ መሆናቸው በላይም የመንግስት አስተዳደር ዝምታውን መምረጡ ተገቢ አይደለም ሲሉ አክለው ገልጸዋል ።
ሆኖም ግን በዚህ የሺሻ መሸጫ መደብር የሆነው የቀነኒሳ ሆቴል ውስጥ፡ባለ፡ስልጣናት እና የባለስልጣናት ልጆች ጊዜ ማሳለፊያቸው እና መዋያቸውንም ዘጋቢያችን ወይዘሪት ኢትዮጵያ ከስፍራው ገልጻለች ። ማለዳ ታይምስ

ሊቢያ ውስጥ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት በማለት የጠየቁ የሰራዊት አዛዦች እየታሰሩ ነው

May 1,2015
7th mekenayzid አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ግፍ የተሞላበት ግድያ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት በማለት የጠየቁ የሰራዊት አዛዦች እየታሰሩ መሆናቸውን ምንጮች ገለፁ፣የደረሰን መረጃ እንደሚያመልክተው- የምዕራብ እዝ 7ኛ ሜካናይዝድ የሬጅመንት ምክትል አዛዥ ሻለቃ ሙሉአለም የተባለ መኮነን የኢህአዴግ ገዥው መንግስት በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በየመን በኢትዮጵያውያን ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው አስቃቂ ግፍ መንግስት ፈጣን ግብረ መልስ መስጠት አለበት ብሎ ስለጠየቀ ብቻ ፀረ ሰላም ነህ ተብሎ ባህር ዳር መኮድ በተባለ ቦታ እንደታሰረ ምንጮቻችን አስታወቁ፣
ስርዓቱ በአይ ኤስ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ፍላጎት ስለሌለው የዜጎቻችንን ደም መመለስ አለብን የሚል ጥያቄ ለሚያነሱ ሰዎች እንደ ጠላት እያዬ ወደ እስር ቤት እያስገባቸው እንደሚገኝ የገለፀው ይህ መረጃ የመከላከያ ሰራዊትም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ላለው የሚያሳዝን ተግባር ዋነኛ ተጠያቂው በስልጣን ላይ ያለው የኢህአዴግ ስርዓት መሆኑን በተደጋጋሚ እየገለፁ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ያደረሱን መረጃ ገልጿል፣
ምንጭ-ዴምህት

የማዕከላዊ እዝ ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መምጣቱ ታወቀ

May 1,2015
mekononoch serawitየማዕከላዊ እዝ  ከፍተኛ ሃላፊዎች የሰራዊት ክህደት እየጨመረ መሄዱ ስላሳሰባቸው የእያንዳንዱን ወታደር ንብረት እየፈተሹ በርካታ ወታደሮችን ማሰራቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ፣በምንጮቻችን መረጃ መሰረት የማዕከላዊ እዝ አመራሮች በየዕለቱ የሚከዳው የሰራዊት ቁጥር ስላሳሰባቸው ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ/ም የእያንዳንዱን ወታደር የግል ንብረት ሲፈትሹ የዋሉ ሲሆን በፍተሻውም ከ180 በላይ የሚሆኑት የሲቪል መታወቂያ ካርድ ያላቸው ወታደሮች መገኘታቸውን አስረድቷል፣
ይህ የተገኘው የሲቪል መታወቂያ ካርድም ከትውልድ ቦታቸው በተለያዩ መንገዶች የተላከላቸው ሲሆን ሲቪል መስለው ስርዓቱን እየጣሉ ለመሸሽ እንዲያግዛቸው የተዘጋጀ መሆኑን የገለፀው መረጃው በዚህ የተነሳም አራት ነባር የሰራዊት አባላቶች ለ3 ወር እስራት ተወስኖባቸው በአዲ ኮኮብ እስር ቤት ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፣
ምንጭ -ዴምህት

Thursday, April 30, 2015

በርካታ ወጣቶችን በጨለማ እየታፈሱ ነው

April30,2015
በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ አደጋ ተከትሎ ለተቃውሞ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌደራል ፖሊሶች ተደብድበው እንዲታሰሩ በተደረገ ማግስት፣ የኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች የሚገኙ ወጣቶችን በምሽት በማፈን ወደ እስር ቤት እያጋዙ ነው።

የከተማዋ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ተወስደው ታስረዋል መጪውን ምርጫ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ረብሻ ይነሳል በሚል ፍርሃት ወጣቶችን እያፈነ በማጋዝ ላይ መሆኑን ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ሰዎች ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በወንጅ ወረዳ የገዢው ፓርቲ ኳድሬዎች እናቶችን ብቻ በመሰብሰብ ልጆቻችሁን ምከሩ በማለት እያስፈራሩ መሆናቸው ተመልክቷል። ባለፈው ረቡዕ በነበረው ተቃውሞ ላይ ተይዘው የተፈቱት ወጣቶች ለኢሳት እንደተናገሩት፣ በተያዙበት እለት ምግብና ውሃ ከመከልከላቸውም በላይ ይደበደቡ ነበር ። ወጣቶቹ ሲለቀቊ አሻራቸውን መስጠታቸውንና ከአሁን በሁዋላ በየትኛውም መንገድ ተቃውሞ ቢያደርጉ የከፋ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የአንድነት ፓርቲ አባል እና የሚሊየኖች ድምፅ አምደኛ የነበረው እስማኤል ዳውድ መታሰሩ ተዘግቧል።

ወላጅ እናቱ እንደተናገሩት ትላንት ከጠዋቱ ሁለት ሰአት ላይ ሲቪል የለበሱ ሰዎች ወደመኖሪያ ቤት መጥተው እስማኤልን ወስደው አስረውታል።
ሰዎቹ ሲወስዱት፦ ‹‹ፖሊስ ጣቢያ ቃል ሰጥተህ ትመለሰላህ›› ቢሉትም፤ አራዳ ፖሊስ ጣቢያ ቃሉን ከሰጠ በሁዋላ ግን እንደማይለቀቅ አስታውቀውት ወደ ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን ወላጅ እናቱ ገልፀዋል። በትላንትናው እለትም ከአራዳ ፖሊስ ጣቢያ ስልክ ተደውሎላቸው፤ ልጃቸው እስማኤል ችሎት መድሃኒያለም አካባቢ ወደሚገኘው ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ መዛወሩ እንደተገለፀላቸውም ተናግረዋል። እስማኤል፣ ዛሬ ሚያዚያ 21 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት ከረፋዱ 5፡30 ላይ ፒያሳ በሚገኘው አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን፤ በችሎቱ የተሰየሙት ሴት ዳኛ ‹‹በአራት ቀን ውስጥ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ ለክስ የሚያበቃ በቂ ማስረጃ ካለው ፍርድቤት እንዲያቀርበው፤ አለበለዚያ ግን በነጻ እንዲያሰናብተው›› ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡

ልጃቸው በምን ምክንያት እንደታሰረ ያውቁ እንደሆነ የተጠየቁት ወላጅ እናቱ ፦በረቡዕ ሰልፍ ላይ በመገኘቱ ምክንያት እንደሆነ በመጥቀስ፤ ከእሱም ሌላ ሁለት ጓደኞቹ ለእስር መዳረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ከስልፉ ጋር በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ ስድስት አባሎቹ እንደታሰሩ ያስታወቀ ሲሆን፤ በ አቶ በላይ ፍቃዱ ይመራ ከነበረው ከቀድሞው አንድነት ፓርቲ ውስጥ ደግሞ ለእስር የተዳረጉት ቁጥራቸው ሶስት ደርሷል፡፡

እነሱም፦እስማኤል ዳውድ፣ ስንታየሁ ቸኮልና የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ዳዊት አስራደ ናቸው። በአገር ውስጥ ያለው ውጥረት እየጨመረ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በሊቢያ፣ ሳውድ አረቢያና የመን ዜጎች ላይ የደረሰውን ግፍ ማውገዛቸውን ቀጥለዋል።

በቤልጂየም ብራሰልስ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በአውሮፓ ህብረት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ተገኝተው ሀዘናቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል። በቶሮንቶ አካባቢ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም የሻማ ማብራትና የጸሎት ምሽትት በማድረግ ብዙ ሕዝብ በተገኘበት ከፍተኛ ሃዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ በስነስርአቱ ላይ የተለያዩ እምነት ተከታይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በተገኙበት በዚህ የሃዘን ቀን ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘው በጋራ እንዲነሱ ጥያቄ ቀርቧል። በኒዮርክም እንዲሁ የሻማ ማብራትና የጸሎት ስነስርአት ተካሂዷል።
ምንጭ ኢሳት ዜና 

ኢትዮጵያ በታሠሩ ጋዜጠኞች ብዛት በአፍሪካ አንደኛ ነች!!!

April30,2015
Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.
Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.Netsanet Yibeltal's photo.

ኢትዮጵያ እሥር ላይ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙን፤ ቪየትናም ደግሞ የኢንተርኔት ፀሐፊዋን ወይም ብሎገሯን ታ ፎንግ ታንን እንዲለቅቁ ዩናይትድ ስቴትስ ጠየቀች፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ናቸው ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ይህንን የመንግሥታቸውን ማሳሰቢያ ያስተላለፉት፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በዚህ ሣምንት እያወጣቸው ባሉ ተከታታይ የፕሬስ መግለጫዎች በዓለም ዙሪያ በየእሥር ቤቱ ያሉ ጋዜጠኞችን በየቀኑ እያነሣ ይገኛል፡፡

በዚህ “FREE THE PRESS” ወይም “ፕሬስን ነፃ አውጡ” በሚለው ዘመቻው የዛሬው የመሥሪያ ቤቱ መግለጫ ካተኮረባቸው ሁለት ጋዜጠኞች አንዷና ቀዳሚዋ የቀድሞ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የእንግሊዝኛ መምህር ኢትዮጵያዊቱ ፍሪላንስ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ነች፡፡

በፀረ-ሽብር ሕጉ መሠረት በተመሠረተባት ክሥ ጥር 10/2004 ዓ.ም ተፈርዶባት እስከዛሬ ወኅኒ ቤት እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ጠቁመዋል፡፡ “… ርዕዮት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሥራቸው ጋር በተያያዘ በተመሠረቱባቸው ክሦች ምክንያት ከታሠሩ 18 ጋዜጠኞች አንዷ ስትሆን ይህ ሁኔታም ኢትዮጵያ በአህጉሩ ብዙ ጋዜጠኞችን በማሠር ቀዳሚዋ እንድትሆን አድርጓታል …” ብለዋል፡፡

ርዕዮት የመንግሥቱን ፖሊሲዎች የሚተቹ ፅሁፎችን በጋዜጣ በማውጣቷ ምክንያት በሰኔ 2003 ዓ.ም ተይዛ የሽብር ፈጠራ ክሥ ከተመሠረተባት በኋላ የ14 ዓመት እሥራት ተፈርዶባት እንደነበረ ያስታወሱት ራትካ የእሥራት ዘመኗ ወደ አምስት ዓመት ዝቅ እንዲል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በነሐሴ 2004 ዓ.ም መወሰኑን ተናግረዋል፡፡

ይሁን እንጂ ክሡ ሙሉ በሙሉ እንዲሠረዝላት በተከታታይ ያቀረበቻቸው የይግባኝ አቤቱታዎች ውድቅ መደረጋቸውንም ራትኮ አመልክተዋል፡፡

“… ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት መብቷን ተግባራዊ በማድረጓ ብቻ ታሥራ የምትገኘውን ርዕዮትን እንዲፈታ ለመንግሥቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን – ያሉት ራትኮ – መንግሥቱ ፀረ-ሽብር አዋጁን ሃሣብን በነፃነት የመለዋወጥን ተግባር ለመጠምዘዝ ጉዳይ ከመጠቀም እንዲቆጠብም እናሳስባለን …” ብለዋል፡፡

ምንጭ  ቪኦኤ

የሕወሓት ጄኔራሎች እና የደህንነት ሹሞች ዝግ ስብሰባ ተቀምጠዋል::ህዝብን ከፈሩ ስልጣን መልቀቅ::

April 30,2015
ምንሊክ ሳልሳዊ
በወያኔ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ሊድን የማይችል ድንጋጤ እና መበስበስ መከሰቱን እና የህዝብ ብሶት ገንፍሎ መውጣቱ በምርጫው ጋር ተያይዞ የሚመጣው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በህዝቡ ቁጣ ከቁጥጥር ውጪ ይወጣል የሚል ፍራቻ እንዲሁም ራስ ምታት የሆነው የሰራዊቱ እና የደህንነቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና አለመግባባት ላይ ለመነጋገር የወያኔ ጄኔራሎች እና የደህንነት ሹሞች ዝግ ስብሰባ መቀምጣቸው ታውቋል::
የሕወሓት ጄኔራሎች እና የደህንነት ሹሞች የተቀመጡት ስብሰባ የቀድሞ ታጋዮችን ብቻ የሰበሰበ ሲሆን ለስብሰባ ከተጠሩት ባለስልጣናት ውስጥ ከሶስቱ በስተቀር በሙሉ የሕወሓት ሰዎች መሆናቸው ሲታወቅ ስብሰባውን በሚያካሂዱበት ወቅት ጠባቂዎቻቸውን ይሁኑ ስብሰባ የሚያስተናግዱ ሰራተኞች በአከባቢው እንዳይደርሱ የተደረገ ሲሆን አከባቢዉን ታማኝ የሕወሓት ደህንነቶች በአይነቁራኛ እይጠበቁት ይገኛል::በአዲስ አበባ በሚገኘው እና ካሮጌው አይሮፕላን ማረፊያ በስተጀርባ ወያኔ አሻሽሎ በገነባው እና በከፍታ አጥር በተከበበው የደህንነት ቢሮ ውስጥ የተሰየመው ይህ ስብሰባ በሃገሪቱ ውስጥ የተከሰተውን ሕዝባዊ ብሶት የወለደውን እምቢተኝነት ለመቆጣጠር እቅድ ለመንደፍ መሆኑ ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::
በስብሰባው ላይ ወያኔ ባወጣው የራሱ ሕግ የውሳኔ ሰጪ የበላይ አካላት ጠቅላይ ሚኒስትር የሚባሉት ሆነ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ እንዳልተጠሩ እንዲሁም በረከት ስምኦን እና ተባባሪዎቻቸው እንዳልመጡ ታውቋል::ይህ በዝግ የተቀመጠው የማፊያ ቡድን ስብሰባ የወያኔን መደናገጥ እና መግቢያ ቀዳዳ ማጣቱን በይፋ ያሳየ እና በባለስልጣናት ፊት ላይ ከፍተኛ ድንጋጤን የፈጠረ መሆኑን ታውቋል::ወያኔ ለህዝብ ስልጣኑን አላስረክብም በማለት በከፍተኛ ደረጃ አምባገነንነቱን አስፋፍቶ የቀጠለ ሲሆን በልማት ስም ሕዝቦችን በመግደል በማሰር እና በማሳደድ ምርጫን ተገን አድርጎ ተጨማሪ አመታቶችን በሕዝብ ጫንቃ ላይ ለመቀመጥ ማቀዱን እየደሰኮረ ይገኛል::
የህዝብ ብሶት መገንፈሉ በፍራቻ ያርበደበደው ወያኔ በሰራዊቱ እና ደህንነቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና አለመግባባት ሌላኛው ራስ ምታቱ ሆኗል::በሽብርተኝነት ሽፋን ምእራባውያንን ማጭበርበሩን ለመቀጠል ቢፈልግም የተነቃበት ወያኔ አሁንም በሃሰት ዲስኩሮች ህዝብ ግብር የሚከፍልባቸውን ሚዲያዎች በመጠቀም ፕሮፓጋንዳ እየረጨ ይገኛል::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ስለሚፈልግ ህዝባዊ ብሶቱ አሁንም አደባባይ በመውጣት ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወያኔ በመደምሰስ በመቃብሩ ላይ ሕዝባዊ መንግስት መመስረት የሁላችንም የጋራ ግዴታ ነው:; የተነቃነቀ ጥርስ ይወልቃል:

Wednesday, April 29, 2015

ኢህአዴግ ሰማያዊን ለማውገዝ በየ አካባቢው የአደባባይ ስብሰባ መጥራቱ ተሰማ

April 29,2015
ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ ለነገ ሀሙስ አዲስ አበባ ውስጥ በየ ወረዳው በሚገኙ ሜዳዎች የአደባባይ ስብሰባዎችን መጥራቱን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ህዝባዊ ንቅናቄ›› የተባሉት የአደባባይ ስብሰባዎች ባለፈው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ፈጥረዋል በሚል በገዥው ፓርቲ እየተከሰሱ ያሉትን በተለይም ሰማያዊ ፓርቲን ለማውገዝ የተጠሩ ናቸው ተብሏል፡፡ በህዝባዊ ስብሰባዎቹ ከካድሬዎች ውጭ ተቃውሞ የሚያሰሙ ኢትዮጵያውያን እንዳይገኙ የኢህአዴግ አባላት ብቻ እንዲገኙ በደብዳቤ እንደተጠሩ ታውቋል፡፡
መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ እርምጃ ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ላይ ለጉዳዩ ትኩረት አልሰጠም በሚል ተቃውሞ ከገጠመው በኋላ ሰማያዊ ፓርቲ ከተቃውሞው በስተጀርባ እንዳለበት ከመክሰሱም ባሻገር በተለያዩ አካባቢዎች በጠራቸው ሰልፎች ሰማያዊን ሲያወግዝ ተስተውሏል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ ኢህአዴግና የመግንስት ተቋማት ስሙን ከማጥፋት ካልተቆጠቡ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስደውና ከዚህም ባሻገር ሌሎች ተከታታይ እርምጃዎችን እንደሚወስድ በመግለጽ ህዝብ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡

Tuesday, April 28, 2015

“መንግሥት የሌለው እዚህ ብቻ ነው!” የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መግለጫ

April 28, 2015
ባለፈው ሳምንት አይ ሲስ ባሰራጨው ቪድዮ ኢትዮጵያውያኖች በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ተከፍለው ሲገደሉ አይተናል። ስለቪድዮው ብዙ ማለት ቢቻልም ወገኖቻችን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ካገራቸው ውጥተው መከራተታቸው ለዚህ አይነቱ አሰቃቂ ሞት ዳርጓቸዋል።ከአገራቸው የወጡት እየኖሩ ከመሞት ለመትረፍ ቢሆንም በስደት ደግሞ እጅግ መራራውን የሞት ጽዋ ጠጥተዋል። ይህ የወገኖቻችን ዕልቂት በዓለማችን ሊይ በሚገኝ በምንም ዓይነት ቋንቋ፣ አገላለጽ፣ አጻጻፍ፣ እንባ፣ ወዘተ ሊገለጽ የማይችል ነው። ረዳት አልባ ሆነው የተመለከትነው ትዕይንታቸውም በውስጣችን ለዘመናት የማይሽር ቁስል  ይዞ ይቀመጣል። 
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዲይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ሁለንም ኢትዮጵያውያን ዘር፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ ቦታ፣ ወዘተ ሳይለዩ ይህ በአገር ወገን ላይ የደረሰው ሃዘን በጋራ በመሆን እርስ በርስ በመጽናናት፣ በመበረታታት እንዱወጡ፤ ላልችንም በተመሳሳይ የስቃይና የመከራ ሁኔታ ሊይ የሚገኙትን ወገኖች በመርዳት የሚችለበትን መንገድ እንዲቀይሱ አሳስበዋል። 
አቶ ኦባንግ ሲቀጥሉም፤ “በአለም ዘሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእነዚህን ለሃይማኖታቸው የቆሙ ጀግና ወገኖቻችንን ተመልክቷል፤ የሞት ከበሮ ቢደለቅባቸውም ሳይፈሩና በድፍረት ሰብዓዊነታቸውን በናቁባቸው አረመኔዎች ፊት ለእምነታቸው ቆመዋል፤ “እኔም ሆንኩ በጋራ ንቅናቄያችን ሥር የሚገኙ ቤተሰቦችና ላልች እጅግ በርካታ ወገኖች የተሰማንንን ጥልቅ ሃዘን በምንም ዓይነት ቃልት መግለጽ አንችልም፤ ይህንን ፍጹም አረመኔያዊ የሆነ፤ አንዳች ሰብዓዊነት የሌለበት ደርጊት ባሉት ቃላት ሁሉ ተጠቅመን እናወግዛለን፤ ልጃቸውን፣ ወንድማቸውን፣ አጎታቸውን፣ ወገናቸውን፣ ወዘተ ላጡት ቤተሰቦች እንደ እነርሱ እኩል ማዘን ባንችልም የአንዱት ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል እንደ መሆናችን ይህንን መራር ሃዘን የራሳችን አድርገን በመውሰደ አብረናችሁ እናዝናለን፤[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
Public outrage in Ethiopia

ሰማያዊ ፓርቲ መንግስት የከፈተበትን የጥላቻ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲያቆም አሳሰበ

April 28, 2015
መንግስት ሊቢያ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ አሰቃቂ እርምጃ የወሰደውን አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም ራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ ከህዝብ የገጠመውን ተቃውሞ ተከትሎ ሰማያዊ ላይ የጥላቻ ዘመቻ እንደከፈተበትና ይህንን የጥላቻ ዘመቻውን እንዲያቆም ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳስቧል፡፡Semayawi Parties latest press conference
መንግስት የጠራውን ሰልፍ ከማንም ተቃዋሚ ፓርቲ ቀድሞ የደገፈው ሰማያዊ እንደሆነ የገለጸው መግለጫው ‹‹የዜጎችን ስቃይ ለፖለቲካ ፍጆታ ማዋል የፈለገው ህወሓት/ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ ለሚደርሰው በደል መፍትሄ እንዲሰጥ መወትወቱ፣ የፖለቲካ ልዩነታችንን ወደ ጎን አድርገን በሰልፉ ላይ መገኘታችን እንዳላስደሰተው ከሰልፉ ቀን ጀምሮ በፓርቲያችን ላይ የተከፈተው ዘመቻ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡›› ብሏል፡፡
ከሰልፉ ማብቃት ጀምሮም ጉዳዩን ገና ፖሊስ ሳይመረምረው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን ሰማያዊ ፓርቲ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት እየጣረ ነው በሚል መወንጀላቸውን፣ የመንግስት ሚዲያዎች ሰማያዊ ፓርቲ ሁከትና ብጥብጥ ሊያስነሳ ነው ብለው ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ማሰራጨታቸውንና አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም ተብለው በተጠሩ ሰልፎችም ሁሉ መንግስት ሰማያዊ ፓርቲ ለመቃወም እየተጠቀመባቸው መሆኑን መግለጫው አትቷል፡፡
በተጨማሪም በሰልፉ ዕለት የሰማያዊ አባላት ገና ሰልፉ ሳይጀመርና መስቀል አደባባይ ሳይደርሱ እንዲሁም ሰልፉ ካበቃ በኋላ እየታደኑ ሲታሰሩ መስቀል አደባባይ ላይ የተያዙት የኢህአዴግ አባላት ከቀበሌ ደብዳቤ እያመጡ መፈታታቸው መንግስት ሰማያዊን በሀሰት ለመወንጀል መነሳቱን ያሳያል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል 6 ያህል የሰማያዊ አባላት በታሰሩበት ሁኔታ መንግስት 7 አመራሮችና 20 ያህል አባላት ታስረዋል ማለቱ ትክክል አለመሆኑንና ከመጀመሪያውም 6 አባላቱ የታሰሩበት መንገድና አሁንም በሰማያዊ ላይ የሚቀርበው ክስ መሰረተ ቢስ ነው ብሎታል፡፡
‹‹ይህ በህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት አማካኝነት እየቀረበ ያለው ክስ እና የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ህወሓት/ኢህአዴግ ለዜጎች ህይወት የማይጨነቅ እና በዜጎች ሞት የራሱን የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ እና ጠንካራ ተቃዋሚ የሆነውን ሰማያዊ ፓርቲን ለማጥቃት እየተጠቀመበት መሆኑን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው፡፡›› ሲልም የመንግስትን ተግባር ተቃውሟል፡፡ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያልተሰጠበትን ጉዳይ ተጠርጣሪ ከማለት ይልቅ ወንጀለኞች ናቸው በማለት በህገወጥ ስራ እንደተሰማራ ያሳያል ሲልም ወቅሷል፡፡
‹‹መንግስት እና የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከዚህ አኩይ ተግባራቸው የማይታቀቡ ከሆነ፣ የሰማያዊን ስም በሀሰት በማጠልሸት ስራ ላይ የተሰማሩ የመንግስት ተቋማትን እና ግለሰቦችን በህግ ፊት ለማቆም ይገደዳል›› ያለው መግለጫው ሌሎች ተከታታይነት ያላቸውን እርምጃዎችም እንደሚወስድና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያደርጋቸው ህዝባዊ ጥሪዎች በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ አባል ስንታየሁ ቸኮል በደህንነቶች ታፈነ

April 28.2015

የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው እና በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ዛሬ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም በደህንነቶች ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዱን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ አራት ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ‹‹ትፈለጋለህ!›› በማለት በመኪና አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ የወሰዱት ሲሆን ለእስሩ ምንም አይነት ምክንያት ወይንም መጥሪያ እንዳልሰጡት ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡ ቤቱን የፈተሹት አራቱ ደህንነቶች ምክንያታቸውን እንዲያስረዱት የጠየቀው አቶ ስንታየሁ ላይም ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Monday, April 27, 2015

ኢትዮጵያ ውስጥ የግብረሰዶማዊነት ትምህርት እየተሰጠ ነው – አደጋ ላይ ነን!

April 27,2015
ካስደነገጥኳችሁ አዝናለሁ ግን በጣም መደንገጥ አለባችሁ፡፡በመላው የአዲስ አበባ የመንግስት ሁለተኛ ደረጃ ትምርህት ቤቶች ማለት ይቻላል በነSave The Children ፊት አውራሪነት እየተሰጠ ያለው የግብረሰዶማዊነት ትምህርት ተጠናክሮ እየቀጠለ መሆኑን ሳረዳችሁ ከፍተኛ ሀዘን እየተሰማኝ ነው፡፡እስካሁን ከ40 በላይ የሚሆኑ የአዲስ አበባ ት/ቤቶች ውስጥ ለውስጥ በአንድ ክፍለ ጊዜ በ120 ብር በተቀጠሩ የየትምህርት ቤቱ የባዮሎጂና የአይሲቲ መምህራን አማካኝነት እየተሰጠ ነው፡፡ሁለት አይነት ነው ትምህርቱ፡፡Life Skill (ላይፍ እስኪል) እና Comprehensive Sexuality Education (ከምፕሬኤንሲቭ ሴክሽዋሊቲ ኤጁኬሽን) የሚባሉ፡፡በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያ ዙር ስልጠናው አልቋል፡፡ሁለተኛ ዙሩ የተግባር ትምህርት ነው፡፡ በቪዲዮና በተግባር እንቅስቃሴ የተደገፈ፡፡ ከሚሰጡት ትምህርቶች መካከል FREE KISSING (በፍሪ ኪሲንግ) እና MASTERBATION (ማስተርቤሽን)የሚባሉ የልቅ ወሲብ አይነቶች አሉበት፡፡ ልቅ ስል በ FREE KISSING (በፍሪ ኪሲንግ) ጊዜ ጾታ ሳይለይ የፈለጉትን ደፍሮ መሳም ሲሆን በ MASTERBATION (ማስተርቤሽን) የሚለው ደግሞ ሴቶችም ወንዶችም በቪዲዮ የታገዘ የ Pornography (የፖርኖ) ፊልሞች እያዩ እንዲተገብሩት የታሰበ ነው፡፡ ለዚህም አላማ ከየትምህርት ቤቱ ጎበዝ የተባሉ ተማሪዎች ተመርጠው ተዘጋጅተዋል፡፡

ጉዳዩ እስከ ትምህርት ሚኒስተርና ቢሮ ቢደርስም እስካሁን መልስ ሊሰጡ አልቻሉም፡፡አንዳንድ የክፍለ ከተማ ሀላፊዎች እንዳሉት እነSave The Childern (ሴቭ ዘቺልድረን) በኢትዮጵያ የተለያዩ ስራዎች ስለሚሰሩልን አቁሙ ብንላቸው ግንኙነታችን ይበላሻል፡፡በላይ አመራሩም ዘንድ ያለው እሳቤና አቋም ይሄ ነው ብለዋል፡፡የተከበራችሁ የአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ የምትገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ፤ ወላጆች ፤ቤተሰቦች ይህ የምነግራችሁ ነገር ተራ አሉባልታ አለመሆኑን በተለያየ ጊዜ ለማሳያ የተለጠፉ መረጃዎችን አይታችሁ መፍረድ ትችላላችሁ፡፡ የተከበራችሁ ተማሪዎች ወላጆች እና በዚህ ጉዳይ እንደ እኔ የተንገበገባችሁ ሁሉ አደጋ ላይ ነን፡፡በተለይ ድርጅቶቹ ነገሩን እንዲሰሩላቸው የመረጧቸውን ሰዎች ለመግዛት እያወጡት ያለው ምራቅ የሚያስውጥ ገንዘብ በየክፍሉ ከሚያስተምሩላቸው መምህራንና ከተባባሪ የትምህርት ቤት አስተዳደሮችም አልፎ እስከ ላይ ድረስ ኪስ ሳያሞቅ አልቀረም፡፡ የእናንተ እርዳታ ቆፍጠን ያለ ውሳኔ ያስፈልጋል፡፡

ተማሪዎችና ወላጆች በአዲስ አበባ በብዛት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ላይ ቢያነጣጥርም ነገሩ በኦሮሚያ፣ በአማራና በሌሎች ክልልሎች ግን እስከ ታችኛው ክፍል ድረስ በስነተዋልዶ፣በጸረኤድስና በስርአተ ጾታ ሰበብ የግብረሰዶማዊነት ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ሳረጋግጥላችሁ በአውነት ነው፡፡ ስለዚህም ተማሪዎች፣ ወላጆች የሚመለከታችሁ ሁሉ አይናችሁን ወደ ትምህርት ቤት አንሱ!! ተማሪዎች በገንዘብ በተደለሉ ግለሰቦች እተረጨባቸው ያለውን መርዝ አስቁሙ፡፡በተለይ በአሁኑ ወቅት አስረኛና አስራ ሁለተኛ ክፍሎች ትምህርት በጨረሱበት ጊዜ እየሆነ ያለው ተማሪዎችን በክረምት ትምህርትና ስልጠና ሰበብ ለዚህ ተግባር እየመዘገቡ ያሉ ትምህርት ቤቶች እንዳሉ ልነግራችሁ እችላሁ፡፡ሴቭ ዘቺልድረን በክረምት ወራት ትምህርት ቤቶችን በክረምት ትምህርት አሳቦ በመከራየት የሰዶማዊነት ትምህርት ሊሰጥ መሆኑን ስነግራችሁ ያለምንም ጥርጥር ነው፡፡አስካሁን የግብረሰዶማዊነት ትምህርት ሁለተኛ ዙር ለመስጠት ፈቃደኛ ሆነው ካሉ ትምር ቤቶች መካከል፡ ሚኒሊክ፤መድሀኒአለም፣ባልቻ አባነፍሶ፣ኤስኦኤስ፣ህዳሴ፣አፍሪካ ህብረት፣የካቲት 23 ፣መነን፣አየርጤና እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ይህ ነገር ሀሰትነው ብላችሁ የምትጠራጠሩ ከሆነ በተለይ ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተለይ ወላጆች አንደኛ በየክፍለ ከተማ የሚገኙ የስርአተ ጾታ ሀላፊዎችን ፣በአዲስ ትምህርት ቢሮ በተለይ አቶ ሀይለ ስላሴ የተባሉ የስራ ሀላፊን መጠየቅ ይቻላል፡፡በተጨማሪም በኢትዮጵያዊነት ድምጽ ላይ የተለጠፉ የመማሪያ ሰነዶችን ማየት ይቻላል፡፡ወላጆች ልጆቻችሁን አድኑ!!

የተከበራችሁ ተማሪዎች በየትኛውም አጋጣሚ በትምህርት ቤትም ሆነ ከትምህርት ቤት ውጪ በስነተዋለዋልዶና ስርአተ ጾታ ስም የሚሰጠውን ፍጹም የግብረሰዶማዊነት ትምህርት አንማርም ንድትሉ ብትሉም እራስን የማዳንና የመከላከል ተግባርና እርምጃ መሆኑን አውቃችሁ በዚህ ተግባር ላይ የተሳተፉ መምህራንም ሆኑ በገንዘብ ተደልለው ሊያስተምሩ የተዘጋጁ ተማሪዎችን አምርራችሁ እንድታገሉ ሁላችንም በፈጠረን አምላክ ስም እለምናቿለሁ!!

ኢትዮጵያ የግብረሰዶማዊነት መቀበሪያ ትሆናለች እንጂ መቼም ከግብረሰዶማዊነት ጋር አትጋባም!!
ጭንቀት ካደረበት መምህር

Thursday, April 23, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ

April 23,2015

የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም

ኢትዮጵያኖቹ በ ISIS ሲገደሉ በግድ እንዲያይ የተደረገው ታዳጊ ህፃን

April 23,2015

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2007(ኤፍ.ቢ.ሲ) የ16 ዓመቱ ኤርትራዊ ስደተኛ ናኤል ጎይቶም የኤይ ኤስ ታጣቂዎች ኢትዮጵያውያኑን እና ኤርትራውያኑን በግፍ ሲቀሉ እና ሲረሸኑ እንዲመለከት መደረጉን ይናገራል።

ታዳጊው ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ታይምስ ከተሰኘው ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ እንደተናገረው፥ ታጣቂው የአይ ኤስ ቡድን ይህን አሰቃቂ ድርጊት አስገድዶ እንዲመለከት አድርጎታል።

ይህ አሰቃቂ ድርጊት ከተከናወነ ከጥቂት ቀናት በኋላ ከሌሎች አራት ኤርትራውያን ጋር በሊቢያ ታስረውበት ከነበረው ካምፕ ማምለጣቸውንም ተናግሯል።

በእዚህ አረመኔ ቡድን ከመቀላት ለማመለጥ መሞከር አዋጭ መሆኑን የተናገረው ናኤል፥ ከቡድኑ ካምፕ ካመለጡ በኋላ እርዳታ የሚያገኙበት ስፍራ እስኪደርሱ ድረስ ለአራት ቀናት ያህል በሊቢያ በረሃ ውስጥ መጓዛቸውን ይተርካል።

ከአንድ ወር ለሚበልጥ ጊዜ በፅንፈኛው አይ ኤስ ቁጥጥር ስር በነበሩበት ወቅትም “ከመሞት እና እስልምናን ከመቀበል የቱን ትመርጣላችሁ”? የሚል ምርጫ እንደተቀመጠላቸው እና በወቅቱ ሙስሊም መሆንን እንደሚመርጡ እና እንዋጋላችኋለን ሲሉ መናገራቸውንም ያስታውሳል ታዳጊው።

ናኤል ኢትዮጵያውያኑ እና ኤርትራውያኑ በአይ ኤሴስ ከተያዙ በኋላ በአንድ ትልቅ ጉድጓድ መቀመጣቸውንም ተናግሯል ።

ከእለታት በአንዱ ቀንም 47 ያህል ኢትዮጵያውያንን እና ኤርትራውያንን ጥቋቁር እና ብርቱካናማ ልብሶችን አልብሰው ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ እንዲሁም ሊቢያ በረሃ እንደወሰዷቸው እና እሱም ይህን ይመለከት ዘንድ አብሯቸው እንደወሰዱት ከዚያም ይህን ጭካኔ የተመላበት ድርጊት እንዲመለከት መደረጉንም ይናገራል።

ታዳጊው በአይ ኤስ እንዴት ተያዘ?

ናኤል እንዴት በፅንፈኛው የአይ ኤስ እጅ እንደተያዘም ያብራራ ሲሆን፥ 10 ኤርትራውያን ሴቶችን እና 8 ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 61 ከሚሆኑ ስደተኞች ጋር ከአንድ ወር በፊት በሱዳን አድርግው ደቡብ ሊቢያን ሲያቋርጡ በአይ ኤስ ታጣቂዎች መያዛቸውን እና ሀይማኖት ነክ ጥያቄዎች መጠየቃቸውን ያስታውሳል።

ከመካከላችሁ ማን ነው ሙስሊም? ብለው እንደጠየቋቸው ነገር ግን ክርስቲያን የሆንነው መስቀል እና ክርስቲያን መሆናችንን የሚያሳዩ መንፈሳዊ ምስሎችን በመያዛችን በወቅቱ ማንነታቸንን መደበቅ አላስቻለንም ብሏል።

በአይ ኤስ ካምፕ ውስጥ ከ300 እስከ 400 የሚሆኑ የፅንፈኛው ቡድን አባላት የሚገኙ ሲሆን፥ ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን ተይዘው በካምፑ ውስጥ እንዲገቡ ሲደረግ፣ ሶማሊያውያን ግን መሄድ ወደፈለጉበት እንዲጓዙ ይፈቀድላቸው እንደነበር ይተርካል።

ናኤል ኤይ ኤስን አስቀድመው የተቀላቀሉ እና ለሽብር ቡድኑ የሚዋጉ ሶስት ኤርትራውያን የነበሩ ሲሆን፥ እነሱ ይረዱናል ብለን ስንጠብ ግን ስለኛ ምንም ስሜት አልተሰማቸውም ሲል ታሪኩን ያወጋል።

ናኤልን ጨምሮ ዮሃንስ መብራቱ፣ ቶማስ ገብረህይወት፣ አብርሃም ናይዝጊ፣ አማን ሺሻይ የተሰኙ ታዳጊ ኤርትራውያንም ከአይ ኤስ ካመለጡ እና ከአራት ቀናት አድካሚ የበረሃ ጉዞ በኋላ አንድ ሱዳናዊ አግኝቷቸው በሰሃራ በረሃ በርካታ ስደተኞች ወደሚገኙበት የስደተኞች መጠለያ እንዳደረሳቸው ገልጿል።

ታዳጊው ህይወቱን ማትረፍ ቢችልም ባየው እና በደረሰበት መከራ እና እንግልት ሳቢያ ውስጡ መጎዳቱን ነው የተናገረው።

አይ ኤስ ከ30 ደቂቃ በማያንስ የተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) በአለም ዙሪያ ባሰራጨው መልዕክቱ 30 ኢትዮጵያዊያን እና ኤርትራዊያን ንፁሃን ዜጎችን ገሚሱን በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ሲቀላ፥ ገሚሱን ደግሞ በሊቢያ በረሃ በጥይት በመተኮስ ሲገድል ማሳየቱ ይታወሳል።
ምንጭ፦ http://www.ibtimes.co.uk