Friday, November 14, 2014

ፌደራል ፖሊሶች ለሚፈጽሟቸው ግድያዎች ተጠያቂው ማን ነው?

November 14,2014
ከዳዊት ሰለሞን
dawitይህ ጥያቄ በቀጥታ በመንግስት ትዕዛዝ የተፈጸሙ ግድያዎችን አይመለከትም፡፡እንደውም በፓርላማ ከቀረበው ረቂቅ አዋጅ አንዱ ‹‹በግዳጅ ላይ ያለ የመንግስት ታጣቂ ለሚፈጽመው ጥፋት ተጠያቂ እንዳይሆን ››የሚሞግት ነው፡፡
ፓርላማው 446 ለ 1 የሚመራ በመሆኑም ገዢው ፓርቲ የፈለገውን አዋጅ የማውጣት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡በዚህ ገጽ ግን ለማንሳት የወደድኩት ታጣቂዎች ከስራ ገበታቸው ውጪ እየፈጸሟቸው የሚገኙ ግድያዎች ሀላፊ ማን ይሆናል የሚለውን ነው፡፡
ንፋስ ስልክ አካባቢ የመንግስት የሰላም አስከባሪ አባል የነበረ አንድ መቶ አለቃ ጎረቤቶቹን በ35 የክላሽ ጥይት መግደሉና ህጻናቱን ያለ ወላጅ ማስቀረቱ አይዘነጋም፡፡
መቶ አለቃው ከታሰረ በኋላ በልዩ እንክብካቤ ተይዞ ወላጆቻቸውን ባጡ ህጻናት ላይ ይዘት እንደነበርና በኋላም አመለጠ ተባለ፡፡መቶ አለቃው መጨረሻ ላይ ስለመያዙ ተነገረ፡፡
ባህርዳር የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አንዘነጋውም፡፡አፍቅሪያታለሁ ያለ ፌደራል ፖሊስ የ18 ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ወንዝ ውስጥ ገብቶ ሞተ የሚል ወሬ ተናፈሰ፡፡
ቂርቆስ መንደር በምትገኝ የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር እንዲሁ የእኔ የሚላትን ሴተኛ አዳሪ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ በማግኘቱ ፌደራሉ በሁለት ጥይት ደረቷን መትቶ ለህልፈት ዳረጋት ፣ከሴትየዋ ጋር የነበረው ጎልማሳም እግሩን በጥይት ለመቆረጥ በቅቷል፡፡
ይህ ፎቶ ግራፍም በተመሳሳይ መንገድ በፌደራል ፖሊስ ህይወቱን በግፍ ስለ ተነጠቀ ወጣት የሚጮህ ነው፡፡
ጅማን በእንባ፣በድንጋጤና በተቃውሞ የሞላ ክስተት የተስተናገደው በፌደራል ፖሊስ ነው፡፡በምሽት ሰው ቤት ሰብሮ የገባው ፖሊሱ አንዲት አይነ ስውር እናትና ልጃቸውን ቀጥፏል፡፡
ግለሰቡ ስለ መያዙም ተነግሯል፡፡ግን ይህ ነገር በገዳዮቹ መያዝ ብቻ የሚያበቃ መሆን የለበትም፡፡ተጠያቂነቱ ወደ ላይም መውጣት አለበት፡፡መሳሪያ መያዝ የማይገባቸው፣ሰብዓዊነት ምን ማለት እንደሆነ የማይረዱ፣ግደሉ ሲባሉ ከመግደል የማያመነቱ፣መሳሪያ ሲጨብጡ ጭንቅላታቸውን ቃታው ጋር የሚያደርጉ ሰዎችን መለዮ እያለበሱ ስልጣናቸውን ለማራዘም እስከጠቀሟቸው ድረስ ስለሚፈጽሙት ዘግናኝ ድርጊት ደንታ የሌላቸው አካላትም መጠየቅ ግድ ይላቸዋል፡፡
የሟቾቹ ደምም በተኳሾቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ነፍጥ ባሸከሟቸው ሀይሎች ላይም ይጮሃል፡፡

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ፖሊስ ጣቢያዎችን እንዲሰሩ ተጠየቁ

November 14,2014
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በየ አካባቢያቸው ለሚሰሩት አዳዲስ ፖሊስ ጣቢያዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ መጠየቃቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በየ አካባቢው የሚገኙት የፖሊስ ጣቢያዎች ነዋሪዎች ገንዘብ እንዲያዋጡ በየ ቤታቸው ደብዳቤና የገንዘብ መክፈያ ቅጽ እየሰጡ ሲሆን ነዋሪዎቹ ገንዘብ እንዲከፍሉ የተጠየቁበትን ቅጽ ሳይሞሉ መመለስ አይችሉም ተብሏል፡፡

ደብዳቤው ላይ ባለው የፖሊስ ጣቢያው ስልክ ቁጥር ደውለን ያነጋገርናቸውና ስማቸውን ለመግለጽ ፈቃደኛ ያልሆኑ አንድ የፖሊስ አባል ‹‹ህዝቡን ለምን ፖሊስ ጣቢያ እንዲሰራ ታስገድዳላችሁ?›› በሚል ላነሳነላቸው ጥያቄ ‹‹ህዝቡኮ ራሱ ነው ሴት ልጆቻችን በሰላም መግባት አልቻሉም እያለ ያለው፡፡ ፖሊስ የህዝብ እስከሆነ ድረስ ህዝብ ፖሊስ ጣቢያ ቢያሰራ ምን ችግር አለው? ህዝቡ አልከፍልም ካለ ሊቀር ይችላል፡፡ እናንተ ግን ይህን እንደጥያቄ የምታነሱት ስብሰባው ላይ ስላልነበራችሁ ነው፡፡›› ብለውናል፡፡

ከወራት በፊት ‹‹ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ›› በሚል አደረጃጀት ህዝቡ በየቤቱና ከጎረቤት ጋር 1ለ5 በመደራጀት ከፖሊስ ጋር ግንኙነት እንዲኖረው የሚያዝ ህግ መውጣቱና ነዋሪዎቹንም ማደራጀት መጀመሩን ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወቃል፡፡


የሶዶ ከተማ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ካምፕ እንዲገቡ ተደረገ

November 13,2014
ከህዳር 6/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 10/2007 ዓ.ም በሶዶ ከተማ የሚደረገውን የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክቶ ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጎዳና ተዳዳሪዎች በግዳጅ ወደ ካምፕ እንዲገቡ መደረጋቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ 

በመቶዎቹ የሚቆጠሩ ሴት፣ አዛውንትና ህጻናት ጎዳና ተዳዳሪዎች ሶዶ ውስጥ አራዳ ክፍለ ከተማ ተብሎ በሚጠራውና አዲስ እየተሰራ በሚገኘው ገለሜ የተባለ እስር ቤት ውስጥ በግዳጅ እንዲገቡ መደረጉን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ካምፕ ውስጥ የገቡትን የጎዳና ተዳዳሪዎችም የቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ለሳምንት ቀለብ እንደሚያቀርብላቸውና ጉባዔው ካለቀ በኋላ ወደነበሩበት እንደሚመለሱም ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ለጉባኤው ሲባል ዜጎችን በግዳጅ ወደ ካምፕ ማስገባቱ ደኢህዴን በከተማዋ ልማት እንደተመዘገበና ህዝቡን ከድህነት እንዳላቀቀ ለማስመሰል ያደረገው አስነዋሪ ተግባር ነው›› ያሉት የሰማያዊ ፓርቲ የወላይታ ዞን የአደረጃጀት ኃላፊ አቶ ታደመ ፈቃዱ ‹‹እስካሁን ሶዶ ከተማ ውስጥ መብራት ስለማይኖር በርካቶች ተዘርፈዋል፡፡ የተገደሉም አሉ፡፡ የከተማዋ ውበትም እምብዛም የተጠበቀ አልነበረም፡፡ አሁን ግን ከተማዋን ለማጽዳት እየተሯሯጡ ነው፡፡ መብራት ባልነበረበት ከተማ መንገዱ ሁሉ ባውዛ ሆኗል›› ሲሉ ስለሁኔታው አስረድተዋል፡፡

ለደኢህአዴን ጉባዔ ተብሎ የከተማዋ ውበት እንዲጠበቅና የጠፉት አገልግሎቶች ለጊዜው እንዲስተካከሉ መደረጉም በህዝቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል ተብሏል፡፡ ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው አንድ የከተማዋ ነዋሪም ‹‹ህዝቡ በአገልግሎቶች መጥፋት ተማሯል፡፡ የከተማው ውበት ለሚኒስትሮቹ እንጅ ለእኛ አይደለም፡፡ እንዲህ ከሆነ ደኢህዴን በየ15 ቀኑ ጉባዔ ቢያደርግ ጥሩ ነበር›› ሲሉ ስለሁኔታው ገልጸውልናል፡፡

ለጉባዔው ሲባልም በጸጥታ ስም በተቃዋሚዎች ላይ ክትትል እየተጠናከረ ይገኛል ያሉት አቶ ታደመ ‹‹ከተማዋ በፖሊስ ተጥለቅልቃለች፡፡ ፖሊሶች በየ 10 ሜትሩ ቆመው ነው የሚታዩት፡፡›› ብለዋል፡፡

Thursday, November 13, 2014

ጊዜው የሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው!!!

November 13,2014
በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።
በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።
በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ … በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ …. እጦት።
እነዚህ ሁለት ተፃራሪ እውነታዎች ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች ለወሳኝ ፍልሚያ ፊት ለፊት መፋጠጣቸዉን በግልጽ ያሳያሉ። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነትና ባርነት፣ ፍትህና ጭቆና፣ ደስታና ሀዘን፣ ተስፋና ተስፋ መቁረጥ፣ ብልጽግናና ድህነት፣ እውቀትና ድንቁርና፣ ብርሃንና ጨለማ፣ ለወሳኝ ግጥሚያ ተፋጠዋል። ይህ ፍጥጫ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታን በመወሰን ረገድ አቢይ ሚና የሚኖረው ወሳኙ ግጥሚያ – ሕዝባዊ እምቢተኝነት – መጀመሩን አብሳሪ ነው። የነፃነት፣ የፍትህ፣ የተስፋ፣ የብልጽግና፣ የእውቀትና የብርሃን ወገኖች ነን የምንል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይህንን ፍልሚያ በድል መወጣት ግዴታችን ነው።
ወያኔ ታጋዮችን ቢያስር ትግሉን አያስርም። በእጦት ኑሮዓችን በማመሰቃቀል በድህነት ሊያንበረክከን ቢሻም፣ በፍጹም አንበረከክለትም። በተዘረፈ የድሆች ድካም ህንፃዎችን ቢገነቡም የራስ ባልሆነ ጌጥ አንኮራም። የወያኔ የሆነ የኛ አይደለም፤ የእነሱ መክበር የኛ መክበር አይደለም። ወያኔ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ገዢና ተገዢ፤ በዳይና ተበዳይ፣ ገፊና ተገፊ ናቸው።
ተበዳይና ተገፊ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘረኞች፣ ሙሰኞችና ከፋፋዮች የህወሓት ባለሥልጣኖቻቸውና ሎሌዎቻቸው ላይ ይነሳሉ። የተጀመረው ሕዝባዊ እምቢተኝነት አመቺ በሆኑ መንገዶች ሁሉ ይጧጧፋል።
የወያኔ ትዕዛዛትን መሻር፤ በሥራ ላይ መለገም፤ ግብር አለመክፈል፤ አድማ መምታት፤ የወያኔ ካድሬዎችን ማግለልና ማዋረድ፤ የነፃነት ኃይሎችን መደገፍ፤ የፓሊስና የጦር ሠራዊት አባላትን ማቅረብ እና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ እነሱም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማበረታታት፤ ህሊና ያላቸው የኢሕአዴግ አባላት የሕዝቡን ትግል እንዲያግዙ ማበረታታት … – እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ በርካታ የትግል ስልቶች ከአሁን ጀምሮ በተከታታይ በሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። የወያኔን የጭቆና ምሽግ ከውስጥ መሸርሸር፤ ከውጭ መደርመስ ይኖርበታል። የመሸርሸርና የመደርመስ ሥራዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል። ጊዜው የእምቢተኝነት ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የነፃነት ንቅናቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ አጠገቡ ባሉት መሪዎቹ አስተባባሪነት በአንድነት እንዲነሳ ጥሪ ያቀርባል፤ በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገው ሁለገብ ትግል በጽናት እንዲደግፉ ያሳስባል። ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው፤ እንወጣዋለንም!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Wednesday, November 12, 2014

የዞን 9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች አስራአንደኛ የፍርድ ቤት ውሎ

November 12,2014
በዛሬው እለት በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ 10 ተከሳሾቸን ጉዳይ ሊያይ የተሰየመው ችሎት በጦማርያኑ እና በጋዜጠኞቹ ላይ የቀረበውን ክስ አቃቤ ህግ አንዲያሻሽል ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡
ባለፈው ሳምንት የክስ ፋይሉን አስመልክቶ የህግ እና የፍሬ ነገር ችግር አለበት በሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ያቀረቡትን የተከሳሾች ጠበቆች አንዲሁም መሻሻል የሚገባው ነገር የለውም ያለውን የአቃቤ ህግን መልስ ተከትሎ ብይን ለመስጠት ተቀጥሮ በዳኞች ለውጥ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ የነበረው ችሎት ዛሬ ክሱ ላይ መሰረታዊ ማሻሻያ እንዲደረግ ብይን ሰጥቷል፡፡
ብይኑም በአጠቃላይ ሲታይ
1. በመጀመሪያው ክስ የጸረ ሽብር ህጉን አንቀጽ አራት በመጥቀስ በደፈናው የሽብር ስራ ተብሎ ቀርቦ ነበረውን ክስ አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ ክሱ ፈጸሙትን ወይም ሊፈጽሙ ያሰቡትን የሽብር ተግባር በአንቀጽ ሶስት መሰረት አቃቤ ህግ በዝርዝር አንዲያስቀምጥ መቼ እና እንዴት አንደፈጸሙት ተግባሩም ምን እነደሆነ አንዲገለጽ
2. የሽብር ቡድን ፣ ግንቦት ሰባት አንዲሁም ኦነግ በማለት በተለያየ ቦታ የተጠቀሱ ስሞች ከመኖራቸው ባሻገር ግልጽ የሆነ ነገር ባለመኖሩ የተባለው የሽብር ቡድን ማን እነደሆነ በግልጽ አንዲቀመጥ ( አቃቤ ህግ በክሱ አንድም ቦታ ላይ ዞን 9 የሚል ቃል አለመጠቀሙን ያስታውሷል)
3. ስትራቴጂ እና ተልእኮ በመቀበል የሚለው ክስ ምን አይነት ስትራቴጂ እና ምን አይነት ተልእኮ ከማን ለእነማን ተከሳሾች አንደሆነ በግልጽ እንዲቀመጥ
4. የገንዘብ ድጋፍን አስመልክቶ ለሽብር ተግባር ተቀበሉት የተባለው ገንዘብ ከማን እነደተላከና ለምን ሽብር ተግባር አንደዋለ በዝርዝር አንዲገለጽ
5. የተከሳሾችን የስራ ክፍፍል አስልመልክቶ አቃቤ ህግ አቃቤ ህግ ለይቶ እነማን ምን የሽብር ስራ ክፍፍል አንደነበራቸው ለይቶ እንዲያቀርብ
6. ህገ መንግስቱን በሃይል መናድ የሚለው ክስ በአንደኛ ክስ ላይ ከተጠቀሱ ተግባራት ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አንዲሆን እና ጉዳዩ በጸረ ሽብር ህጉ ብቻ አንዲታይ ብይን ሰጥቷል፡፡
በተመሳሳይ ፍርድ ቤቱ ሁለቱ ሴት ተከሳሾች ማህሌት ፋንታሁን እና ኤዶም ካሳዬን የማረሚያ ቤት አያያዝን አስመልክቶ ማረሚያ ቤት ሃላፌ ቀርበው መልስ አንዲሰጡ ባዘዘው መሰረት የማረሚያ ቤት ተወካይ መጥተው የእስረኞቹ አያያዝ እንደማንኛውም እስረኛ ነው ብለው የካዱ ሲሆን በተጨማሪም ማንኛውንም አይነት ችግር ካለ ከተከሳሾች ጋር በመነጋገር ለመፍታት ፍቃደኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የፍርድ ሂደቱን ላለማጓተት የተከሳሽ ጠበቆች ከማረሚያ ቤቱ ጋር አንዲነጋገሩ እና መፍትሄ ላይ እነዲደርሱ አንዲሁም ለውጥ ከሌላው ግን የተከሳሽ ቤተሰቦችን ምስክርነት ለመስማት የሚገደድ መሆኑን ገልጿል። አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ ተከሳሾች አንደተለመደው በሙሉ የስሜትና የአካል ደህንነት ላይ ሆነው ወዳጆቸን ሰላም ሲሉ እና እርስ በርሳቸው ሲወያዩ ተስተውለዋል፡።
ማስታወሻ - ዞን 9 የጦማርያን ቡድን ፍርድ ቤቱ የክስ ማሻሻል ትእዛዝ በበጎ ጎን የምንመለከተው ሲሆን የፍትህ ስርአቱ የሚታማበትን የተለመደውን ገለልተኛነት የማጣት ችግር አስወግዶ ጦማሪ ጓደኞቻችንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን ከክሱ በነጻ በማሰናበት ታሪካዊ ሃላፌነቱን አንደሚወጣም ተስፋ አናደርጋለን፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ምንም አይነት የሽብር ተግባር ላይ ተሰማርተን የማናውቅ መሆኑን ክሱም ሃሳባችንን በነጻነት ከመግለጽ ተግባራችንን ጋር ተያያዘ መሆኑን አጥብቀን እንደምናምን እያስታወስን መንግሰት ክሱን ሙሉለሙሉ ውድቅ በማድረግ የጉዳዩን ፓለቲካዊ አለመሆን አንዲያረጋግጥልን ጥሪ እናስተላለፍለን ፡፡
አሁንም ስለሚያገባን እንጦምራለን!

Tuesday, November 11, 2014

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ።

ImageNovember 11,2014

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።

ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ''የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ''

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

''የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ''''

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

''አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።''

 source http://www.dw.de/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1% ... a-18051929

ግልጽ ደብዳቤ ”ለጠቅላይ ሚኒስትር” ኃይለማርያም ደሳለኝ : ከታሳሪ ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

November 10,2014
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!
ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች  ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’
“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” በማለት አንዲት አጭር ደብዳቤ ፅፈንልዎት ነበር፡፡
zone9ድንገት በተለያዩ ምክንያቶች የጻፍንልዎትን ደብዳቤ ካላነበቡት ወይም ማስታወስ ካልቻሉ ዛሬ ይሄን ማስታወሻ ስለምንፅፍልዎት ግለሰቦች አንድ ሌላ ማስታወሻ እንስጥዎ፡ ከ6ወራት በፊት /በሚያዚያ 2006 ዓ.ም/ ሶስት  ጋዜጠኞችንና ስድስት ጦማሪያንን ‘ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ በመሞከር ወንጀል ጠርጥሬያችኋለሁ’ በማለት መንግስትዎ ልማታዊ ርምጃ (አብዮታዊ ርምጃ እንደሚባለው) ወስዶ ነበር፡፡
እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6 ወራትበፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ  ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡
በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡
ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት ከታሰርን ከ 200 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፣ነገር ግንጉዳያችን ገና በቅድመ ክስ (Pre Trial) የክርክር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ይሄ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም መንግስትዎ እንኳን ለእኛ ለተከሳሾች ለከሳሽ አካልም ግልፅ ያልሆነ ክስ በማቅረቡ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል ልትፈፅሙት ነበር የተባለው ‘የሽብርተኝነት ድርጊት’ ሳይጠቀስ ‘በቃ የሽብርተኝነት ድርጊት ልትፈፅሙ ነበር’ በማለት በጨበጣ ስለመጣብን ነው፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንግዲህ የብዙ ድብደባ፣ ዛቻ እና ስድብ ሰለባዎች ከሆንን በኋላምየቀረበው ይሄ  ክስ ነው ከ6 ወራት በኋላም ተከሳሾች ከሳሾቻችንምሳንረዳው በየቀጠሮው እየታሸ ነው የሚገኘው፡፡ ‘የተፋጠነ ፍትህ’ ሕገ መንግስትዊ መብት ነውና የተፋጠነ ፍትህ ይሰጠን፣ እርስዎምይሄን ሕገ መንግስታዊ መብት ያክብሩ እያልንዎት አይደለም ‘ሕገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ሕገ መንግስቱ ይከበር በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ’በማለት ‘ጥፋት የሚያሳምን’ ( አንዱ የዚህ ደብዳቤ ጸሃፌ ጦማሪ ጥፋት ብሎ አንዲፈርም የተገደደው ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለህገመንግስቱ ይከበር ማለቴ ጥፋት ነው ብሎ መሆኑ መንግስትዎን መልክ ግልጽ አድርጎ ያሳያል) መንግስት አለዎትና ይህ ጥያቄ አንደሚበዛብዎትእናውቃለን፡፡
ይልቁንም ቀላልና ግልፅ ቅሬታን ነው ይዘን የመጣነው፡፡ ይሄውም የኢፌድሪ ሕገ መንግስትበአንቀፅ 20/3/ ላይ
‘የተከሠሡ ሰዎች[…]  በፍርድ ሂደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደ ጥፋተኛ ያለመቆጠር[…]መብት አላቸው::’
በማለት የደነገገ ሲሆን፣ ይሄንን ሕገ መንግስታዊ መብትም ማንኛውም የመንግስት አካል እንዲሁም ግለሰብ የማክበር ግዴታ አለበት፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እርስዎና መንግስትዎም በተደጋጋሚ ‘ሕገ መንግስቱ ሳይሸራረፍ እናስከብራለን’ ይላሉና ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ የምታውቁት ይመስለናል፡፡ ነገር ግን ከታሰርን ወዲህ ስለእኛ የእስር ጉዳይ በተጠየቁባቸውጊዜያት ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ በመጣስ ‘ፍርድዎትን’ በተደጋጋሚ ሲሰጡ ታዝበናል፡፡ እናስረዳዎ፡- ሐምሌ 12/2006 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣሚ መግለጫ ላይ ስለእኛ እስር ጉዳይ ለቀረበልዎት ጥያቄ ሲመልሱ፡-

‘ከአስመራ እስከ ሞቃዲሾ የተዘረጋው የሽብር ሰንሰለት ውስጥ አንዴከገቡ በኋላ ብሎገር ነኝ፣ ጋዜጠኛ ነኝ ማለት ዋጋ የለውም’
በማለት ብዙ ነገሮችን ተናገሩ፡፡ ይሔውልዎት ስህተትዎ፡-
1.     የክሳችን ዋነኛ ጭብጥ በሃገርውስጥ ‘የሽብርተኛ ድርጅት በማቋቋም ‘የሽብርተኝነት’ ተግባራትን ለመፈጸም አሲረዋል፡ አቅደዋል… የሚል እንጂ፣ እርስዎም እንደሚሉት ‘ሰንሰለት’ ምናምን አይደለም፣
2.    እሺ አሸባሪዎችም ይበሉን፣ነገር ግን ሕገ መንግስቱ እንደሚደነግገው በፍርድ ቤት ‘ጥፋተኝነታችን’ እስሚረጋገጥ ቢጠብቁስ ምናለበት? ይህ የሚያመለክተው እርስዎም እንደ ማእከላዊ መርማሪዎች ነፃ ሆኖ የመገመት (presumption of innocence) መብታችንን እያከበሩልን እንዳይደለ ነው፡፡
ይሄ ነገር የሆነው በድንገት ሊሆን ይችላል ብለንዝም ብንልም እርስዎ ግን በድጋሚ ጥቅምት 6/2007 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ከምክር ቤቱ አባል ለቀረበልዎ ጥያቄሲመልሱ፡-

“የብሎገር ጭምብልአጥልቆና በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ ተሸሽጎ ከተከሳሽነት ማምለጥ አይቻልም፡፡ ሽብርተኝነትን መዋጋታችን ይቀጥላል…” እያሉ እርስዎ ያሉትን የብሎገር ጭምብል አውልቀውና ተሸሸጉበት ያሉትን የጋዜጠኝነት ሙያመሸሸጊያ አፍርሰው ባንዴ ‘የአሸባሪነት’ ካባ ደረቡልን፡፡
ክቡር ጥቅላይ ሚኒስቴር፣ እያልን ያለነው የአንድ ሰው ‘አሸባሪነት/ወንጀለኝነት’ የሚረጋገጠው በፍርድ ቤት እንደሆነ ሕገ መንግስቱ ደንግጎ እያለ፣ እርስዎ ግን ነፃ ሆኖ የመገመት መብታችን ወደ ጎን ብለው እንደ ከሳሽም እንደፈራጅም በመሆን ‘አሸባሪዎች’… እያሉን ይገኛሉ ነው፡፡
ምናልባት ‘ስራ አስፈጻሚው ከሳሽ ነውና እኔም የስራ አስፈጻሚው አካል መሪ ስለሆንኩ የፈለኩትን አስተያየት የመስጠት መብት አለኝ’ ብለው ከሆነ፣ ሕገ መንግስቱን የማክበር ጉዳይ ‘ርስዎን ጨምሮ ሁሉም ዜጎች ላይ የተጣለ ግዴታነው፡፡ እርስዎ ‘L’e’tat, c’est moi’ ይሉት አይነት የራስ ግምት ውስጥዎ ከሌለ በስተቀር እንዲህ በግልፅ እየጠየቅንዎት ‘ሕገ መንግስትቱን  አላከብርም’ በማለት ገና ዋነኛ ክርክሩ እንኳንያ ልተጀመረ ክስን (ዋነኛ ክርክር ካለው) መሠረት በማድረግ ከዚህ በኋላ እኛን ‘አሸባሪዎች’ አይሉንም ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ይህን ተመሳሳይ ምላሽ “በእርግጠኝነት አሸባሪ ናቸው” በሚል ቃና ለቢቢሲ ለኢንቢሲ ለመሳሰሉት አለም አቀፍ ሚዲያ  ተቋማትም መስጠትዎን ሰምተናል፡፡
ሌላው ልናስታውስዎ የምንፈልገው ጉዳይ እንደኛ አይነት የተራገበ( በሰፊው በታወቀ የአደባባይ)የፍርድ ጉዳይ ([un] popular case) ላይ የመንግስት አካላት አስተያየት (say) ያለውን ተፅእኖ እንዲያስቡት ነው፡፡እርስዎ በምክር ቤት ቀርበው የአሸባሪነት ፍርድ ከበየኑብን (አሁን እያደረጉት እንዳሉት) ፍርድ ቤትም ሆነ ሌሎች የመንግስትዎ አካላትምን ሊያስቡ እንደሚችሉ አስተውለውታልን?!
ይሄን ሁሉ ስንልዎ እንዲያው ሕጉን ያክብሩልን ለማለት ያክል ነው እንጅ፣ ከሽብርተኝነትጋር የሚያገናኘን ቅንጣት ያክል እውነት /A segment of fact/ እንደሌለና የሰው ልጆች መልካምና ደስተኛ ሕይወት እንዲኖራቸውከመመኘትና ለአገራችን ያገባናል ከማለት ያለፈ ሕይወትም ፍላጎትም እንደሌለን እኛም እናውቀዋለን እርስዎና መንግስትዎም ያውቁታል፡፡ነገር ግን ካለፉት ስድስት ወራት አንስቶ ጨዋታውን በግድ ካልተጫወታችሁ ተብለናልና እየተጫወትን ነው፡፡ የአሁኑ ጥያቄያችን ግን በጣም ቀላል ነው፣ ጨዋታው ገና በደንብ እንኳን ሳይጀመር ውጤቱን እይወስኑት ነው፡፡
እርስዎ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት የስልጣን ደረጃ በወጡ ሰሞን አብዛኞች የዚህ ማስታወሻፀሃፊዎች መጠነኛ ለውጥና ማሻሻዎች ያደርጋሉ የሚል ተስፋ ሰንቀን “The First 100 Days” ወዘተ እያልን ብዙ ጠብቀንዎት ነበር፡፡ ከሁለት ዓመት በሚበልጥ ግዜ እንደተመለከትንዎ ግን ተስፋችን ፍሬ ሊያፈራልን አልቻለም፡፡ አሁንም አዲስ ተስፋ ሰንቀን ግን ፡-“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እባክዎትን ሕገ መንግስቱን ያክብሩ! የእኛንም መብት ያክብሩልን” እንላለን፡፡

‘’የብሎገር ካልሲ አድርጎ፣ የጋዜጠኝነት ጫማ ተጫምቶ የሽብረተኝነት ሰንሰለት ውስጥ ከገቡ በኋላ ሕገ መንግስቱን ያክብሩልኝ ማለት ዋጋ የለውም!’’በማለት ተስፋችን ዋጋ እንደማያሳጡት ተስፋ አለን፡፡

ከአክብሮት ጋር

 ጦማርያን                    ጋዜጠኞች
ዘላለም ክብረት                 ኤዶም ካሳዬ
ናትናኤል ፈለቀ                ተስፋለው ወ/የስ
በፍቃዱ ሃይሉ                አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ
አጥናፍ ብርሃኔ
አቤል ዋበላ
ማህሌት ፋንታሁን

ታላቁ ረኃብ፡ ህወሀት አሁንም ቢሆን ለመስረቅ እና ለመዝረፍ ፈቃድ አለው ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

November 10,2014
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
TPLF Cash.. 1984 የተከሰተውየኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ክፍል 2
ባለፈው ሳምንት ባቀረብኩት ትችቴ (እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ ክፍል1)፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት ረኃብን በማስመልከት ሳቀርባቸው በነበሩት ትችቶች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት ረኃብ የለም በማለት ሙልጭ አድርገው በመካድ ሲያደርጉት የነበረውን ተራ ቅጥፈት በማጋለጥ በተጨባጭ መረጃዎች ላይ በመመስረት ስሞግት የቆየሁባቸውን ዋና ዋና ጭብጦች በማካተት ክለሳ ማድረጌ ይታወሳል፡፡ መለስ እና ጓደኞቹ ከዓለም አቀፍ ለጋሾች እና አበዳሪ ድርጅቶች ጋር በመሞዳሞድ ለረኃብ ስያሜ የተለያዩ የማስመሰያ እና የማደናገሪያ ስሞችን በመስጠት በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ተንሰራፍቶ ህዝብን ሲፈጅ እና ሲያሰቃይ የቆየውን ረኃብ በመደበቅ በሀገሪቱ ውስጥ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንደሌለ አድርገው በረኃብ ሲሰቃዩ በቆዩት እና በረኃቡ ምክንያት ባለቁት ወገኖቻችን ላይ ሸፍጥ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚህም አጽንኦ በመስጠት በኢትዮጵያ ያለው ረኃብ የፈለገውን ያህል በማስመሰያ እና በማደናገሪያ ቃላት እና ሀረጎች ተሸፋፍኖ እና ታጅቦ ቢቀርብም ያው አሁንም ቢሆን ረኃብ ነው! በማለት ማጠቃለያ መስጠቴ የሚታወስ ነው፡፡
በዚህ በክፍል ሁለት ትችቴ ደግሞ እ.ኤ.አ ከ1984 – 85 ድረስ ህወሀት በተከሰተው በታላቁ ረኃብ ምክንያት የረኃብ ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ነብስ ማዳኛ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣውን እርዳታ ለጦር መሳሪያ ግዥ እና ለግል ጥቅም ለማዋል ሲያደርገው የነበረውን የዥዋዥዌ ጨዋታ ለመዳሰስ ሞክሪያለሁ፡፡ በመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ ሜይ 2011 በሁፊንግተን ፖስት “ለመስረቅ ፈቃድ ማግኘት” በሚል ርዕስ ባቀረብኩት የመጀመሪያ ትችት ህወሀት የሰረቀ መሆኑን ከሁለት የቀድሞ የህወሀት የአመራር አባላት ጋር የተደረገን ቃለ መጠይቅ ዋቢ በማድረግ ለሰብአዊ እርዳታ ተብሎ የመጣን የእርዳታ እህል ከታለመለት ዓላማ ውጭ ህወሀት ለመሳሪያ መግዣ እና ለሌላ ለግል ጥቅሙ ያዋለ መሆኑን በማጋለጥ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ ይህ ቡድን እ.ኤ.አ በ1984 ጫካ በነበረበት ጊዜ የጀመረው የዓለም አቀፍ የእርዳታ ስርቆት፣ ዘረፋ እና ሙስና የማይላቀቁት መናጢ አመል ሆኖበት አሁንም እስካለንበት ጊዜ እስከ 2014 ድረስ በተለያየ እና በተወሳሰበ መልኩ ቀጥሎ ይገኛል፡፡
“አሊ ባባ”፣ መለስ እና 40 የህወሀት/ማረት (TPLF/REST) የ1984- 85 የእርዳታ እህል እና ዶላር ሌቦች እና ዘራፊዎች፣
እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ በነበረው አስከፊ እና አሰቃቂ ረኃብ ምክንያት የረኃቡ ሰለባ ለሆኑ ህዝቦች በሚል ከዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ሩብ ሚሊዮን ዶላር ተሰብስቦ ነበር፡፡ ያ ረኃብ እጅግ በጣም አስከፊ ገጽታ ያለው እና ባልተጠበቀ መልኩ የተከሰተ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 የትግራይን አካባቢ የጎበኘው የቢቢሲው ጋዜጠኛ ሚካኤል ቡርክ የረኃቡን አስከፊነት እንደሚከተለው ገልጾት ነበር፣ “የ20ኛው ክፍለ ዘመን የመጽሐፍ ቅዱስ ረኃብ“ እና “በመሬት ላይ ለሲኦል የቀረበ ነገር“፡፡
እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በአማጺያን ኃይሎች እንቅስቃሴ እና በደርግ ወታደራዊ አምባገነን መንግስት የአውሮፕላን ድብደባ ምክንያት በትግራይ ክልል እና በሌሎች የሰሜን ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታን በተለመደው የእርዳታ አሰጣጥ ሁኔታ ማቅረብ እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነበር፡፡ በርካታ የዓለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታውን አማጺያን ቡድኖች በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች በአስከፊው ረኃብ የጥቃት ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ፈጣን በሆነ መልኩ የህይወት አድን እርዳታውን ለማድረስ ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እና ዘዴዎችን ማግኘት ነበረባቸው፡፡
እንደ አማራጭ በመውሰድ በርካታዎቹ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ለረኃብ ጥቃት ሰለባ ለሆኑ ወገኖች በቀላሉ ምግብ ማድረስ እንዲቻል በማሰብ በምስራቃዊ የሱዳን ጠረፍ በትግራይ ወሰን አካባቢ የማከፋፈያ ጣቢያ ከፈቱ፡፡ በሱዳን ወሰን አካባቢ በርካታ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በብዛት መከማቸት እና ገንዘብ በማዋጣት እረገድ ይደረጉ በነበሩት የህዝብ ግንኙነት ጥረቶች ምክንያት ለህወሀት አመራሮች እና ለአማጺያኑ ወታደሮቻቸው ትርፋማ የሆነ የንግድ አጋጣሚ ፈጠረላቸው፡፡ አማጺያኑ እነርሱ በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች ጥሩ የእርዳታ ማስተላለፊያ መንገዶች እንዳሉ በማሳወቅ እና የእርዳታ እህሉንም ሆነ ሌላ ማንኛውንም ዓይነት ቁሳቁስ እነርሱ ማከፋፈል ቢችሉ ስራው የተሳካ እንደሚሆን እና ለዘለቄታው ውጤታማ እንደሚሆኑ መንግስታዊ ላልሆኑ ለጋሽ ድርጅቶች ሀሳብ አቀረቡ፡፡
የቀድሞው የህወሀት የገንዘብ ግምጃ ቤት ኃላፊ የነበሩት እንደ ገብረመድህን አርአያ እና የአማጺያኑ መስራች የነበሩት እንደ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ ገለጻ ከሆነ የህወሀት ቁልፍ መሪዎች መለስ ዜናዊን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የረኃብ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች አማካይነት በረኃቡ ሰለባ ለሆኑት ተብሎ የተመደበውን በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር የእርዳታ እህል የማጭበርበሪያ ስልት ነድፈው ከተያዘለት ዓላማ ውጭ ለጦር መሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅማቸው አዋሉ፡፡ ገብረ መድህን እና አረጋዊ ግልጽ እንዳደረጉት መለስ እና ቁንጮ ካድሬዎቹ አንድ የማጭበርበሪያ ዕቅድ በመንደፍ የሰብአዊ እርዳታ የሚያቀርብ ድርጅት በሚል ማህበረ ረዲኤት ትግራይ/ማረት (Relief Society of Tigray/REST) ተብሎ የሚጠራ የማስመሰያ እርዳታ ሰጭ ድርጅት አቋቋሙ፡፡ ውስጡ ለቄስ ነው እና በአንድ ወቅት አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ እንዳለው የዚህ ድርጅት ልብ እንደ ፈጣን ሎተሪ ተፍቆ ቢታይ እንደ ስሙ እርዳታ ሰጭ ድርጅት እንዲሁም ለሰው ልጆች ክብር በፍቅር ተቃጥሎ ህይወትን ለማዳን ከልቡ የሚሰራ ርህራሄን የተላበሰ እውነተኛ ሰብአዊ ድርጅት ሳይሆን ሌባ፣ ዘራፊ እና በቅጥፈት የተሞላ የማፊያ ድርጅት ሆኖ ይገኛል፡፡ በዚያን ወቅት የህወሀት አመራሮች ማረት ከህወሀት ወታደራዊ ክንፍ ጋር ፈጽሞ ግንኙነት የሌለው እና የተለዬ ሀቀኛ የእርዳታ ሰጭ/አከፋፋይ ለጋሽ ድርጅት እንደሆነ በማስመሰል የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶችን ለማሳመን ሌት ከቀን ጥረት አደረጉ፡፡ እውነታው እንደሚያሳየው በእርግጥ ማረት እና ህወሀት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡
በአሁኑ ጊዜ በስደት በውጭ ሀገር የሚኖሩት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የህወሀትን የረቀቀ የእርዳታ ማጭበርበር ባህሪ ለቢቢሲ ጋዜጠኛ ለማርቲን ፕላውት እንዲህ በማለት ገልጸው ነበር፣
“… አንዳንድ ጊዜ የእርዳታን ገንዘብ እንደ ሁለተኛ አማራጭ በመውሰድ የጦር መሳሪያ እንገዛበት ነበር፡፡ ገንዘቡ ካለህ መካከለኛው ምስራቅ በመምጣት መሳሪያ መግዛት ትችላለህ፡፡ ስለሆነም የተወሰነውን ገንዘብ ለመሳሪያ ግዥ በማዋል እንጠቀምበት ነበር፡፡ ይህንን ማረት እየተባለ በአህጽሮ ቃል የሚጠራውን ድርጅት ታውቀዋለህ፣ ሲተነተን ማህበረ ረድኤት ትግራይ ማለት ነው፡፡ የህወሀት የሰብአዊ እርዳታ ክንፍ ነው፣ እና በማረት ስም የእርዳታ ገንዘብ ወደ ህወሀት ይመጣ ነበር፡፡ ከዚያ ይህንን የእርዳታ ገንዘብ ካገኘህ በኋላ ለእርዳታ፣ ለጦር ግንባር ወይም ደግሞ ለጦር መሳሪያ ግዥ፣ ለመድኃኒት፣ ወዘተ በሚል በጀት ታዘጋጃለህ፡፡ የእርዳታን ገንዘብ ትግሉን ለማስቀጠል እንጠቀምበት ነበር ለማለት እችላለሁ፡፡
ከዚህም በላይ በብዙ ሚሊዮን ስለሚቆጠር ዶላር ጉዳይ እንነጋገር ነበር፡፡ ለዚህ አንድ ተጨባጭነት ያለው ምሳሌ ልነግርህ እችላለሁ፡፡ እ.ኤ.አ በ1985 ትግራይ አሰቃቂ በሆነ ረኃብ በተጠቃች ጊዜ የእርዳታ ገንዘብ በማረት በኩል አድርጎ ወደ ህወሀት ይጎርፍ ነበር፡፡ ስለሆነም ከሞላ ጎደል አንድ ዓይነት ዓላማ ያላቸው እና ምንም ዓይነት ልዩነት የሌላቸው ማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ትግራይ/ ማሌሊት/Marxist Leninist League of Tigrai (MLLT) እና የህወሀት አመራሮች 100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለተለያዩ ተግባራት እንዲውል መመደብ ነበረባቸው፡፡ በዚህም መሰረት መለስ ዜናዊ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ 50 በመቶ የሚሆነው ለህወሀት እንቅስቃሴዎች፣ 45 በመቶ የሚሆነው ለማሌሊት ማደራጃ እና 5 በመቶ የሚሆነው ብቻ በረኃብ ሰለባ ለወደቁት ተረጅዎች መዋል አለበት የሚል ሀሳብ አቅርቦ እንደነበር አስታውሳለሁ…እነዚህን ሁለት ሰዎች (አርዓያ ገብረመድህን እና ተክለወይነ አሰፋ) አውቃቸዋለሁ፡፡ የህወሀት ተዋጊዎች ናቸው፡፡ አንዱ እራሱን ነጋዴ በማስመሰል ይቀርባል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ከነጋዴው ማሽላ የሚገዛ በመምሰል ይቀርባል፡፡ ሁለቱም የህወሀት ነባር ካድሬዎች ናቸው፣ እናም ነጋዴ ለመምሰል ትወና በመተወን ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሚተወኑት ገንዘቡን ለማግኘት ሲባል ነው፡፡ [በፎቶግራፉ ላይ ከላይ የሚታዩት የመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካይ የነበረው ፔርቤዲ ከመካከል ሆኖ የታሰረ ረብጣ ብር ለተወካይ ተብዬዎች ሲያስታቅፍ ነበር] እናም ይህ ዜጋ መቶ በመቶ ተታሏል፡፡”
ገብረ መድህን የዓረጋዊንን ሀሳብ ትክክለኛነት አረጋግጠዋል፡፡ ገብረ መድህን (ከላይ በስዕሉ ላይ በስተግራ በኩል ሆነው ገንዘብ ሲቆጥሩ የሚታዩት) እራሳቸው በግንባር በመቅረብ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠር ዶላር ለመለስ ዜናዊ እና እንደ እባብ ተስለክላኪው እና የህወሀት የክርስትና አባት ለሆነው ለስብሀት ነጋ በወቅቱ በእጃቸው ያስረከቡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሁለቱ የህወሀት አድራጊ ፈጣሪዎች መለስ እና ስብሀት የህወሀትን የገንዘብ ፍሰት ይቆጣጠሩ ነበር፡፡ ገብረመድህን የህወሀት ዋና የገንዘብ ኃላፊ ሹም የነበረ ቢሆንም መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በእርዳታ ስም የሚመጣውን ገንዘብ ለመለስ እና ለስብሀት ካስረከበ በኋላ ስለገንዘቡ አወጣጥ እና ከጥቅም ላይ እንዴት ሆኖ እንደሚውል እንዲያውቅ አይደረግም ነበር፡፡ ያም ሆነ ይህ ገብረመድህን ገንዘቡ በትክክል ለታለመለት ዓላማ ጉዳይ ስለመዋሉ እና አለመዋሉ ጥርጣሬ ነበረው፡፡ ሆኖም ግን የጥፋተኝነት ማስረጃው (ሁለቱን የህወሀት ካድሬዎች እና ማክስ ፔርቤዲ የተባለውን ከእንግሊዝ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች መካከል ታላቅ ከሆነው የክርስቲያን እርዳታ/Christian Aid ተብሎ ከሚጠራው ተወካይ እጅ እየቆጠሩ በመረከብ በወለሉ ላይ በትልቅ ቦርሳ ውስጥ በርካታ ገንዘብ ሲያጭቁ የሚያሳየው ፎቶግራፍ) በምንም ዓይነት መልኩ ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል አስደንጋጭ ነገር ነው፡፡
የችግሩን ስፋት እና ጥልቀት እንዲሁም የረኃቡን አስከፊነት እና አሳሳቢነት መንግስታዊ ላልሆኑት እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በውሸት በትወና መልክ ለማሳየት ሲባል የህወሀት አመራሮች እጅግ ብዛት ያለውን የረኃብ ሰለባ ህዝብ ከትግራይ ወደ ሱዳን በማምጣት በኢትዮ-ሱዳን ሰሜናዊ የድንበር አካባቢዎች ላይ በአንድ ጀንበር ምሽት እንደ አሸን የፈሉ የእርዳታ መስጫ ጣቢያዎችን በማዘጋጀት የተረጅዎችን ቁጥር ከመጠን በላይ አበዙት፡፡ የተለያዩ ዘዴዎችን እና ስልቶችን በመጠቀም የህወሀት አመራሮች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በትግራይ ውስጥ በረኃብ ለተጠቃው ህዝብ የእርዳታ እጃቸውን እንዲሰነዝሩ ለማስቻል ዝርዝር የሆነ የገበያ ተውኔት በማዘጋጀት ለመድረክ እይታ አበቁ፡፡ ይህ የተደረገው ለእነርሱ በጣም ታማኝ የሆኑ የድርጅቱን ጥቂት የውስጥ አባላት በመምረጥ እና በማደራጀት የእህል ነጋዴ ሆነው እንዲቀርቡ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እርዳታ የማሰባሰብ ንግድን ማጧጧፍ ነበር፡፡
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የማታለሉ ጨዋታዎች ወይም ደግሞ የበለጠ ግልጽ ለማድረግ የምዕራቡን ዓለም መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የረኃብ እርዳታ የማታለል ዕቅድ የተለያዩ መገለጫዎችን ያካተተ ነበር፡፡ በማጭበርበሩ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ የህወሀት አመራሮች ሶስት ደረጃዎችን ያካተተ ሂደትን ተጠቅመዋል፡፡ በመጀመሪያው ደረጃ አንድ የህወሀት/ማረት የባለስልጣኖች ቡድን ህጋዊ የእህል ነጋዴዎች በመምሰል በርካታ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ይቀርባሉ፣ እናም በረኃብ ለተጠቃው ህዝብ እርዳታ በፍጥነት እንዲደርስ በርካታ ብዛት ያለው እህል እንዲሸጥላቸው ይጠይቃሉ፡፡ በዚያን ጊዜ የህወሀት አታላዮች በመቶዎች የሚቆጠሩ ከባድ የጭነት ማምላለሻ መኪናዎች ያገኙ እና በጣም ሚስጥራዊ በሆነ መልኩ ከመሬት ውስጥ በተዘጋጀ ሰፊ ማጠራቀሚያ ከተለያዩ ምንጮች ያገኗቸውን የእርዳታ እህሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ጨምሮ ለእራሳቸው ተዋጊዎች መጠቀሚያ በሚል ያጭቁታል፡፡ እነዚህ በከባድ ሚስጥር ከመሬት ውስጥ ታጭቀው የሚገኙ የእህል ቁልሎች በእርግጠኝነት ዓላማው መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ለመሸጥ ነው፡፡ የህወሀት/ማረት እህል አዳዮች መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እህልን ለመሸጥ ይደራደራሉ፣ ከዚያም ሽያጩን ያጠናቅቁ እና ከሽያጩ ያገኙትን በርካታ ገንዘብ ተሸክመው እህሉን ወደ ደበቁበት ቦታ ይመለሳሉ፡፡ ገብረመድህን እራሳቸው በዚህ እህል የመግዛት እና የመሸጥ ትወና ላይ የእህል ማደል ቀጥተኛ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ ከዚህ አንጻር የእርሳቸውን ሚና እንዲህ በማለት በግልጽ አስቀምተውታል፣
የሙስሊም ነጋዴ እንድመስል የሙስልም ልብሶች እንድለብስ ይሰጡኝ ነበር፡፡ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እኔን አያውቁኝም ምክንያቱም የእኔ ስም መሀመድ ነበር፡፡ ይኸ ስም የመቀየር የማጭበርበር ስራ የተደረገው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለማታለል በህወሀት የበላይ አመራሮች የተዘየደ የማጭበርበሪያ ስልት ነበር፡፡ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በርካታ የሆነ ገንዘብ እቀበል ነበር፣ እናም የተቀበልኩት ገንዘብ ወዲያውኑ በህወሀት መሪዎች ይወሰድ ነበር፡፡ ከወሰዱት ገንዘብ ውስጥ በርካታውን የህወሀት አመራሮች በግል የሂሳብ ቁጥራቸው በምዕራብ አውሮፓ ባንኮች ያስቀምጡ ነበር፡፡ ከዚህ ገንዘብ ጥቂቱ ደግሞ ለመሳሪያ መግዣ ያውሉት ነበር፡፡ የአስከፊው ረኃብ የጥቃት ሰለባ የሆነው ተረጅው ህዝብ ግማሽ ኪሎ ግራም ያህል በቆሎ እንኳ አያገኝም ነበር፡፡ አንድ ጊዜ የእህል መግዛቱ ስራ ከተከናወነ በኋላ ሌላው የህወሀት/ማረት ቡድን ደግሞ የተገኘውን የእርዳታ እህል በትግራይ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች በመሄድ የማከፋፈሉን ስራ ይሰራል፡፡
በሁለተኛው ደረጃ የተዋቀረው የህወሀት/ማረት ባለስልጣኖች በሚስጥር ከመሬት ውስጥ ያከማቹትን የእህል ክምችት ድንገተኛ ፍተሻ በማድረግ ስራውን ያቀላጥፋሉ፡፡ ሆኖም ግን የእህል ማስቀመጫ መጋዘኑ በሌላ ማሳሳቻ ነገር ተሞልቶ ይቀመጣል፡፡ ገብረመድህን እንዲህ ብለው ነበር፣ “እዚያ ብትሄድ ግማሽ የሚሆነው የመጋዘኑ የእህል መያዣ ጆንያ በአሸዋ ተሞልቶ ነው የሚገኘው“ ገብረመድህን እንዳሉት ከሆነ የመንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ተወካይ ወደ መጋዘኑ ከመጣ በኋላ በችኮላ እና በዓይን ውጫዊ የገረፍ ገረፍ እይታ ብቻ በመመልከት የእራሱን መተማመኛ ይሰጣል፣ ከዚያም ክፍያ ፈጽሞ ወደ ሱዳን ተመልሶ በመሄድ ሌላ ተጨማሪ እህል ለመግዛት ዝግጅቱን ያደርጋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ የተመደበው አንድ ዓይነት ወይም ደግሞ ሌላ የህወሀት/ማረት ቡድን ወደ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ይሄድ እና ወደተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች በመውሰድ ለህዝቡ ማደል እንድንችል ሌላ ተጨማሪ እህል እንዲሸጥልን በማለት ሌላ የውሸት ማታለያ መጫወቻ ሜዳ በማዘጋጀት ጥያቄውን ለእርዳታ ሰጭ ደርጅቶቹ ያቀርባል፡፡ በዚህን ጊዜ ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተገኘው አዲስ የእርዳታ እህል ወደተባለው ህዝብ እንዲሄድ አይደረግም፡፡ ይልቁንም ከመሬት ውስጥ ባለው መጋዘን ውስጥ ታጭቆ የሚገኘው እህል ወደ ሌሎች የትግራይ የተለያዩ ክፍሎች እንዲሄድ በማድረግ መንግስታዊ ላልሆኑት የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ግን አዲሱ እና ከዚያ ተገዝቶ እንዲሰጥ የተባለውን እህል ያሰራጩ እና ያከፋፈሉ በማስመሰል የማታለል ስራቸውን በስፋት ይቀጥላሉ፡፡ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ነጻ በሆነ መልኩ የተሰጠው እርዳታ ወደ እርዳታ ፈላጊው ህዝብ ሄዶ በትክክል መከፋፈሉን የሚያረጋግጡበት ምንም ዓይነት መንገድ ስለሌላቸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለሚጓጓዘው  ተመሳሳይ የማደናገሪያ እህል ሁሉ ይከፍላሉ፡፡ በዚያ መልኩ የረቀቀ የማታለል ዘዴን በመጠቀም ህወሀት/ማረት ቀደም ሲል የነበራቸውን የእህል እና የአሸዋ ክምችት ብዙ ጊዜ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ደጋግመው በመሸጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በገቢነት ይሰበስባሉ፡፡
ማርቲን ፕላውት ከቢቢሲ በሰሜን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ1970ዎቹ ተከስቶ የነበረውን ረኃብ እ.ኤ.አ ማርች 2010 ባወጣው ዘገባው እ.ኤ.አ በ1985 የሲአይኤ መረጃ ያወጣውን ዋቢ በማድረግ እንዲህ የሚል መደምደሚያ ሰጥቶ ነበር፣ “ለተራቡት ወገኖች እርዳታ በሚል የሽምቅ ተዋጊዎች የሚያሰባስቡትን እርዳታ ዓለም በስፋት እያወቀው ሲመጣ እና የእርዳታው መጠንም እየጨመረ ሲመጣ ለእርዳታው ተብሎ የሚመጣው ሁሉ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ለጦር መሳሪያ መግዣ ይውል ጀመር፡፡“ በ1980ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ሮበርት ሁደክ የተባሉ በኢትዮጵያ የዩኤስ አሜሪካ ነባር ዲፕሎማት የህወሀት አባላት በዚያን ወቅት ለእርዳታ የሚሰጣቸውን እህል ለመሳሪያ መግዣ ያውሉ ነበር በማለት የተናገሩትን ቢቢሲ እንዳለ ቃላቸውን ወስዶ እንዲህ በማለት ዘግቦ ነበር፡፡ “አንድ ማክስ ፔቤርዲ የሚባል የእርዳታ ሰራተኛ በግንባር በመገኘት ለህወሀት/ማረት ባለስልጣኖች 500,000 ዶላር በኢትዮጵያ ገንዘብ ተቀይሮ እህል እንዲገዙበት በእጃቸው የሰጣቸው መሆኑን ተናግሯል“ በማለት ገልጸው ነበር፡፡
ገብረመድህን በጽሁፋቸው በዝርዝር ግልጽ እንዳደረጉት እ.ኤ.አ በ1984 – 85 ተከስቶ የነበረውን ታላቁን ረኃብ ሰበብ በማድረግ ህወሀት አብዛኛውን እርዳታ ለመሳሪያ መግዣ እና ለአመራሩ አባላት የግል ጥቅም አውለውታል የሚለው የመጀመሪያ ማስረጃ አሳማኝ ይመስላል (የገብረመድህንን ክፍል አንድ የአማርኛ ጽሁፍ እዚህ ጋ ይጫኑ፡፡ ለክፍል ሁለት ደግሞ እዚህ ይጫኑ)
የህወሀት የእርዳታ ስርቆት እና እርዳታውን ለሌላ ዓላማ ማዋል የሚለውን ፕሮፌሰር ሀሰን ሰይድ “መንግስታዊ ጥቃት በኢትዮጵያ፡ ሰብአዊ እርዳታ እና ሙስና“ (መነበብ ያለበት ጽሁፍ) በሚል ርዕስ ባዘጋጁት ዝርዝር እና ጥልቀት ባለው ጥናታዊ ጽሁፋቸው ውስጥ እንዲህ የሚል ማጠቃለያ ሰጥተዋል፣ “በጥናቴ ውስጥ የመረመርኳቸው ሰነዶች እና ያደርግኋቸው ቃለ መጠይቆች እንዲሁም የሰበሰብኳቸው የምስክርነት ማስረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ለጋሽ እና እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት ከህወሀት ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን እንደሚያውቁ የሚጠቁሙ መሆናቸው፣ እንደዚሁም ደግሞ የህወሀት እና የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ሰራተኛ ለሰብአዊ እርዳታ ተብሎ የሚመጣ እርዳታ ለመሳሪያ ግዥ እና ለጦር ግንባር ዓላማ ይውል እንደነበር ያውቁ ነበር…“
በዚህ አሳፋሪ እና የወረደ ድርጊት ስህተት ውስጥ ተሳትፈው የነበሩት መቅንየለሾች ማስረጃዎችን ቆሻሻ በማለት ዘለፋ ከማቅረብ ውጭ በእውነተኛ መረጃ ላይ በተመሰረተ መልኩ አጣሪ እና እውነታ አፈላላጊ ኮሚቴ በማቋቋም ማስተባበል እና እራሳቸውን ከዚህ ከባድ እና ጠንካራ ክስ ነጻ ማድረግ ተስኗቸው ቀርቷል፡፡ እውነት በሀሰት ተቀብራ አትቀርማ! እንደዚህ ያለ ምርመራ እስከሚካሄድ ድረስ የእርዳታ ምንተፋ ስግብግብነት እና ሌብነት የማይደፈር እና ሊስተባበል የማይችል መደበኛ ዘረፋ ሆኖ የቆያል፡፡ ቦብ ጌልዶፍ እ.ኤ.አ በ1984 የሙዚቃ ባንድ በማስተባበር በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ለእርዳታው እንዲሰበሰብ አድርጓል፣ የረኃብ እርዳታው በተሳሳተ መልኩ ለጦር መሳሪያ መግዣ ውሏል እየተባለ የሚሰማውን ውንጀላ ምክንያት በማድረግ እንዲህ ብሎ ነበር፣ “ምንም ዓይነት ገንዘብ ያለአግባብ የጠፋ ካለ የኢትዮጵያን መንግስት በህግ እጠይቃለሁ፡፡“
እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ አጋማሽ (እንዲሁም ባለፉት 23 ዓመታት) መንግስታዊ ካልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በአስር ሚሊዮኖች የሚሆን ለእርዳታ የተመደበ ዶላር የህወሀት አታላዮች ለራሳቸው ተራ ተስፈኝነት፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር በብልጣብልጥነት እየዘረፉ ለግል ጥቅማቸው እና ለመሳሪያ መግዣ ያዋሉትን ሰው ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሊያደንቅ ይችላል፡፡ እውነት ለመናገር አሊ ባባ እና የእርሱ 40 የወያኔ ሌቦች እንደዚህ ዓይነት ብልጣብልጥነት የተሞላበት የማጭበርበር ዕቅድ በመጠቀም መንግስታዊ ላልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች እራሳቸው እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የለገሱትን እህል እና አሸዋ የተሞላባቸውን ጆንያዎች እየደጋገሙ መሸጥ አልነበረባቸውም፡፡ የግሪክ የሌቦች አምላክ የነበረው ሄርምስ እንኳ እንደዚህ ያለ በጣም የሚያስገርም ዕንከንየለሽ የሸፍጥ ዕቅድ በማውጣት በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ለመውሰድ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለማታለል እና በቀላሉ ለማሞኘት አልቻለም ነበር፡፡ የህወሀት አመራሮች “አዲስ የአፍሪካ የሌቦች ዝርያ” የሚለው ስም የሚገባቸው ነው፡፡
ማረት የህወሀት ባተሌ ፍጹም አያውቅ እረፍት፣
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ የምግብ እርዳታ በሶስት የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በብቸኝነት ይተዳደራል፡፡ እነርሱም ምግብ ለተራቡ/Food for the Hungry (FH) (እራሱን የክርስቲያን ድርጅት/Christian Organization እያለ የሚጠራ እና እ.ኤ.አ ከ1971 ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ድሆችን በመርዳት ላይ ያለ)፣ የህጻናት አድን ድርጅት/Save the Children (እራሱን የዓለም የተቸገሩ ህጻናት ቁንጮ እርዳታ ሰጭ ድርጅት እያለ የሚጠራ)፣ የካቶሊክ እርዳታ አገልግሎት/Catholic Relief Services (CRS) (በዩናይትድ ስቴትስ ለካቶሊክ ማህበረሰብ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታ ድርጅት) እና ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት የሚባል አንድ የሀገር ውስጥ መንግስታዊ ያልሆነ እርዳታ ሰጭ ድርጅት ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 – 86 የረሀብ ሰለባ ለነበሩ ወገኖቻችን ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ቀርቦ የነበረውን የምግብ እርዳታ ያለምንም ይሉኝታ በረሀብተኞች ጉሮሮ ላይ በመቆም የተለያዩ ሸፍጦችን እና የማታለያ ዘዴዎችን እየፈበረከ ሙልጭ አድርጎ የበላ እና ለእራሱ የውንብድና ሀራራው የመሳሪያ ግዥ ያዋለ ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት የተባለው ያው ድርጅት አሁንም በ2014 በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሀብ ዓይን ባወጣ መልኩ እርዳታ አከፋፋይ ሆኖ ቀርቧል፡፡ የሌባ ዓይነደረቅ መልሶ ልብ ያወልቅ እንዲሉ!
እ.ኤ.አ በ2010 እና በ2014 (እንዲሁም ከ2010 በፊት) ማረት ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚሆን የምግብ እርዳታ ተቀብሎ በማከፋፈል ስራው ላይ ተሳታፊ የነበረ ብቸኛው የሀገር ውስጥ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው፡፡ እ.ኤ.አ ኦገስት 15/2014 ዩኤስኤአይዲ/USAID እንዳወጣው ዘገባ ከሆነ ዩኤኤአይዲ በእራሱ ምግብ ለሰላም ጽ/ቤት/Office of Food for Peace እያለ በሚጠራው ጽ/ቤቱ በኩል እ.ኤ.አ በ2014 ለማረት እና ለሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶች 237 ሚሊዮን ዶላር፣ እ.ኤ.አ በ2013 ደግሞ 236 ሚሊዮን ዶላር፣ እ.ኤ.አ በ2012 ደግሞ 307 ሚሊዮን ዶላር፣ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ2011 ሌላ 313 ሚሊዮን ዶላር እና እ.ኤ.አ በ2010 ደግሞ 452 ሚሊዮን ዶላር አድሏል፡፡
ማረት እስከ አሁንም ድረስ እራሱን “የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ/ህወሀት የሰብአዊ እርዳታ ክንፍ” አድርጎ ይቆጥራል፡፡ በእርግጥ ማረት እ.ኤ.አ በ2014 በሞኖፖል የያዘ መንግስታዊ ያልሆነ የሀገር ውስጥ ድርጅት እና ልክ እ.ኤ.አ በ1984 ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ በኢትዮጵያ ይህንን ግዙፍ የሆነ ዓለም አቀፍ እርዳታን በማጭበርበር በእራሱ የማስተላለፊያ ቱቦ ለህወሀት የሚያስተላልፍ በእርዳታ ሰጭ ድርጅት ስም የሀሰት ጭምብላ ያጠለቀ መንታፊ ድርጅት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ዓለም አቀፋዊ እርዳታን ለማከፋፈል የሚወዳደሩ ሌሎች ሀገር በቀል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሉም፡፡ በእርግጥ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ እየተባለ የሚጠራው መንግስታዊ ተቋም በኢትዮጵያ ያሉትን ሁሉንም መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሲያከስም (እ.ኤ.አ በ2010 አዋጁ ከወጣ በኋላ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ብዛት በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከ4,600 ወደ 1,400 ወርደዋል) ለማረት ጥሩ እድል በመፍጠር ምንም ዓይነት ተቀናቃኝ የሌለው ብቸኛው የሀገር ውስጥ ጠቅላይ ለመሆን በቅቷል፡፡
እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ምሁር ዘገባ ከሆነ ማረት የህወሀት የገንዘብ እና ቁሳቁስ ማስተላለፊያ ቱቦ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የህወሀት የንግድ ግዛት የመነሻ ካፒታል ከተለያዩ ምንጮች ይመጣል፡፡ አንዱ እና ዋናው የማስተላለፊያ ምንጩ የረኃብ እርዳታ የህወሀት ክንፍ የሆነው ማህበረ ረድኤት ትግራይ (ማረት) ነው፡፡ ማረት የእርዳታ ገንዘብን እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ካልተጠበቁ እና በፈቃዳቸው ከሚሰጡ የውጭ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በመቀበል ገንዘብ እና ቁሳቁሶችን ወደ ህወሀት የገንዘብ ሳጥን ውስጥ የሚያስተላልፍ ድርጅት መሆኑ በስፋት ይታወቃል፡፡
የበጎ አድራጎት ድርጅት አዋጅ እየተባለ የሚጠራው መንግስታዊ ተቋም የሚያሳየው እውነታ አገር በቀል የሆኑ እና በሀገር ውስጥ መንቀሳቀስ የሚችሉት በህወሀት ስር ተጠቃለው የተያዙ ወይም ደግሞ ሌሎች ከህወሀት ጋር ወይም እርሱ ከሚፈልግላቸው ድርጅቶች ጋር በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚችሉ ድርጅቶች ብቻ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 ህወሀት በማረት በኩል ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ እርዳታን ለመሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅሙ አውሏል፡፡ እ.ኤ.አ በ2014 ህወሀት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታን በማረት በኩል በመጠቀም አሁንም ለግል ጥቅሙ በማዋል ላይ ይገኛል፡፡ ምን ያህል! ነገሮች የበለጠ በተለዋወጡ ቁጥር የበለጠ አንድ ዓይነት እየሆኑ ይሄዳሉ!
ከመላ አፍሪካ ዩኤስኤአይዲ ትልቅ የእርዳታ ፕሮግራም ያለው በኢትዮጵያ ነው፡፡ ባለፉት 23 ዓመታት ብቻ በአስር ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ከዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ለህወሀት በእርዳታ ስም የተሰጠው ገንዘብ ከምን ላይ ዋለ? ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ እዕምሮን የሚበጠብጥ አስቸጋሪ ይሆናል! ማንም ሊያውቅ አይችልም፡፡ ዩኤስኤአይዲ/USAID እራሱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወደ ህወሀት የገንዘብ ካዝና ውስጥ የሚረጨው እንኳ አያውቀውም! ለዚያም ነበር የዩናይትድ ስቴትስ የመንግስት መምሪያ ጽ/ቤት ኢንስፔክተር በዘገባቸው ላይ እንዲህ የሚል መደምደሚያ የሰጡት፣ “የዩኤስኤአይዲ ኦዲት የምርመራ አገልግሎት የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ተግባራት (የኦዲት ዘገባ ቁጥር 4-6663-10-003-P (እ.ኤ.አ ማርች 30, 2010)“ በሚከተለው መልክ አስቀምጦታል፡
….የኦዲት ኢንስፔክተር [የግብርና ዘርፍ ምርታማነት] ፕሮግራም  የገበያ መር የኢኮኖሚ ዕድገት ማምጣቱን እና ገበሬዎች፣ አርብቶ አደሮች፣ እና ሌሎች በኢትዮጵያ የሚገኙት ተጠቃሚዎች ሁሉ መሻሻል እያሳዩ መሆናቸውን በጥናቱ አግኝቷል፡፡ ሆኖም ግን ያ የተገኘው ውጤት ምን ያህል እንደሆነ በአፈጻጸም አያያዝ እና የስራ አፈጻጸም ዘገባ ማቅረብ ደካማነት ምክንያት መወሰን አይቻልም፡፡ በተለይም ድርጅቱ በተለያዩ አካባቢዎች የስራውን ሂደት እና አፈጻጸሙን ለመከታተል እንዲቻል በሚል የስራ አፈጻጸም መለኪያ አመልካቾች እና ግቦችን በማስቀመጥ የሚጠቀም ቢሆንም… ለአብዛኞቹ መለኪያ አመልካቾች በዘገባ የቀረበው ውጤት ግን በግብነት ከተያዙት ጋር አልተነጻጸረም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቀረበው የኦዲት ዘገባ በዩኤስኤአይዲ/ኢትዮጵያ የቀረቡት  የአፈጻጸም ውጤቶች ተይዞ ከነበረው ዕቅድ ጋር መነጻጸር መቻል አለመቻላቸውን ለመወሰን አይቻልም ምክንያቱም የድርጅቱ ሰራተኞች እነዚህ ውጤቶች እንዴት እንደተገኙ መግለጽ አይችሉም ወይም ደግሞ ለእነዚያ ተገኙ ለተባሉት የስራ ውጤቶች ድጋፍ አይሰጡም፡፡ በእርግጥ የኦዲት ቡድኑ በዘገባው የቀረቡ የአፈጻጸም ውጤቶችን ተገቢነት ያላቸው እንዲሆኑ ለማድረግ ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም ይህንን ለመስራት በድርጅቱ ወይም ደግሞ የድርጅቱ ተባባሪ አስፈጻሚዎች ሳይቻል ቀርቷል (ከገጽ 6 – 12)…
እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2010 ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በኢትዮጵያ እርዳታ ከዓላማው ውጭ ለሌላ ጉዳይ መዋሉን አስመልከቶ መግለጫ አውጥቶ ለህዝብ ከመልቀቁ ከጥቂት ቀናት በፊት ዩኤስኤአይዲ/USAID እና የልማት እርዳታ ቡድን/Development Assistance Group (ለኢትዮጵያ እርዳታ የሚሰጡ 27ቱ የሁለትዮሽ እና በይነ መንግስታት የልማት ድርጅቶች (አንዳንድ ጊዜም በጥቅሉ ዓለም አቀፍ የድህነት ወትዋቾች/አቃጣሪዎች እየተባሉ የሚጠሩት) በኢትዮጵያ የልማት እርዳታ ላይ መጠነ ሰፊ እና ስልታዊ የሆነ ገንዘቡን ከታለመለት ዓላማ ውጭ የዋለ የለም ብለዋል፡፡ የእኛ ጥናት ስልታዊ የሆነ የእርዳታ ገንዘብ የጠፋ ወይም ደግሞ ለሌላ ዓላማ የዋለ ለመሆኑ ያገኘው ማስረጃ የለም ብለዋል፡፡ የወፍ ምስክሯ ድንቢጥ እንደሚባለው! ዳምቢሳ ሞዮ አሳማኝ በሆነ መልኩ እንደምትሞግተው ሁሉ ዓለም አቀፍ እርዳታ ለኢትዮጵያ እና ለሌሎች የአፍሪካ አገሮች ወጥመድ ሆኖ ቆይቷል፡፡ አሁንም ወጥመድ ነው፡፡ የዓለም አቀፉ የእርዳታ ምጽዋት ለኢትዮጵያ የጥገኝነት አዙሪትን፣ የተንሰራፋ ሙስናን፣ የገበያ መመሰቃቀልን፣ ስር የሰደደ ድህነት ማስፋፋትን እና ዘላለማዊ የእርዳታ ሱስ ውስጥ የሚያስገባ አደገኛ መርዝ ነው፡፡
ድህረ ጽሑፍ፣
በኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲከሰት በቆየው ረኃብ ላይ ጥናት በማካሄድ ዘገባ በማቅረብ ጠቃሚ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ የቆዩ ሁለት ያልተዘመረላቸው ጀግኖች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 ተከስቶ ለነበረው በኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ 30ኛ ዓመት በሚታወስበት ዕለት እኔ በግሌ እንግሊዛዊውን ጋዜጠኛው ሚካኤል ቡርክን ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡ ይህ ጀግና ጋዜጠኛ የኢትዮጵያን የ1984 ረኃብ በመዘገብ ሙዚቀኛ ቦብ ጌልዶፍን በማነሳሳት በቀጥታ በሚተላለፍ የእርዳታ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት በመጠቀም ግዙፍ የሆነ ገንዘብ እንዲሰበሰብ በማድረጉ ብቻ አይደለም ሆኖም ግን በአስከፊው ረኃብ ምክንያት በመርገፍ እና በመሰቃየት ላይ የሚገኙትን የኢትዮጵያን ህዝቦች ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስተዋወቅ በፈጠረው ከፍተኛ የሆነ ግንዛቤ ጭምር እንጅ፡፡ እንደዚሁም ደግሞ የቢቢሲ ዘጋቢ እና በኋላም የአፍሪካ አርታኢ ሆኖ ሲሰራ የነበረውን እና እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በተከሰተው ረኃብ ሰበብ ከምዕራቡ ዓለም ለተራቡት ወገኖቻችን የመጣውን በብዙ ሚሊዮን ዶላር የሚቆጠረውን እርዳታ በአቋራጭ ለመሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅም ውሎ የነበረበትን እኩይ ምግባር ያጋለጠውን ጀግና ጋዜጠኛ ማርቲን ፕላውትን ከልብ ለማመስገን እወዳለሁ፡፡
የጋዜጠኝነትን ክቡር ሙያ በማስመልከት ታዋቂው የአሜሪካ ጸሐፊ፣ ዘጋቢ እና የፖለቲካ ተንታኝ የሚከተለውን አስፍሮ ነበር፣ “በጋዜጠኝነት ሙያ እውነታውን ከመናገር እና ሰይጣናዊ ድርጊትን ከማሳፈር እና ከማጋለጥ የበለጠ ትልቅ ህግ የለም፡፡“ እውነታን አፍርጦ በመናገር እና ሰይጣናዊ ድርጊትን በማሳፈር እና በማጋለጥ የ1984-85ን የኢትዮጵያን ታላቅ ረኃብ የዘገበ ከቡርክ እና ፕላውት ውጭ ማንም ጋዜጠኛ ይኖራል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ኢትዮጵያዊ/ት የሆን ሁሉ እነዚህን ጀግኖች የማመስገን ዕዳ አለብን፡፡
ዓለም አቀፋዊ እርዳታ ለኢትዮጵያውያን/ት የድህነት አዙሪት ቀለበት ወጥመድ ሲሆን ለህወሀት ግን የመስረቅ እና የመዝረፍ ፈቃድ ነው!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ጥቅምት 25 ቀን 2007 .

Monday, November 10, 2014

ሌ/ጄነራል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ሊወጡ ሲሉ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በደህንነቶች ተመለሱ

November11,2014
(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ጄ/ል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ለመውጣት ሲሉ ከቦሌ አየር ማረፊያ በደህንነቶች እንዳይወጡ መደረጋቸውን ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል።
ከመከላከያ የጦር አዛዥነታቸው በጄ/ል ሳሞራ የኑስ እንዲነሱ የተደረጉት ጄ/ል አበባው ከአገር እንዳይወጡ የተደረገበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የተለያዩ ጥያቄዎች እንዳሉ በመግለፅ ለኢታማጆር ሹሙ ጄ/ል ሳሞራ ከረር ያለ ሪፖርት ያቀረቡት ጄ/ል ሰዓረ፣ ጄ/ል ሞላና ጄ/ል አበባው መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ በሳሞራ የተሰጠው መልስ « የትምህክተኞች ጥያቄ ነው፤ ችግር የለም..» የሚሉና ጥያቄዎቹን የሚያጣጥሉ እንደነበሩ አስታውሰዋል።
abebaw tadese'
ሶስቱ ጄኔራሎች በሳሞራ ምላሽ በመበሳጨት ከስልጣናቸው ለማስነሳት በምስጢር ቢመክሩም መረጃው ባልታወቀ መንገድ አፈትልኰ ጄ/ል ሳሞራ ዘንድ በመድረሱ ጄ/ል ሰዓረ ከሰሜን ዕዝ አዛዥነታቸው፣ ጄ/ል ሞላ ከአየር ሃይል እንዲሁም ጄ/ል አበባው ከያዙት ስልጣን በሳሞራ በአስቸኳይ እንዲነሱ ሲደረግ በተለይ ጄ/ል አበባው ከ2 ወር በፊት ከመከላከያ እንዲባረሩ መደረጉን ምንጮቹ አስረድተዋል። በጄ/ል ሰዓረ ቦታ ጄ/ል ገብራት አየለ ሲተኩ በጄ/ል ሞላ ደግሞ የአግአዚ ክ/ሰራዊት አዛዥ ጄ/ል አደም መሐመድ መተከታቸውን አስታውቀዋል።
ሁለቱ ጄኔራሎች ዝቅ ባለ ደረጃ ተራ የመምሪያ ሃላፊ ተደርገው መሾማቸውን ምንጮቹ ገልፀዋል። ጄኔራል የመሾምና የመሻር ስልጣኑ የጠ/ሚ/ሩ እንደሆነ ህገመንግስቱ ቢደነግግም ነገር ግን የተጠቀሱት ጄኔራሎች የተነሱት በጄ/ል ሳሞራ ትእዛዝ፣ የተተኩትም በሳቸው ውሳኔ እንደሆነና ጠ/ሚ/ር ሃ/ማርያም ከወራቶች በኋላ እንዲያውቁ ተደርጐ ለተሾሙት ጄኔራሎች የማእረግ እድገት እንዲሰጡ መደረጉን ምንጮቹ አስረድተዋል። ጄ/ል አበባውና ጄ/ል ሰዓረ በሙስና ከተዘፈቁ የጦር አዛዦች እንደሚጠቀሱ አክለው ገልፀዋል። ..ይህ በእንዲህ እንዳለ በመከላከያ ከፍተኛ ግመገማ ከሰሞኑ እየተካሄደ ሲሆን ስር የሰደዱ ቀውሶች እየፈነዱ መሆኑ ታውቋል።

ለአንድ ወር የጠፋችው የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አስከሬን ከነመኪናዋ ጭቃማ ኩሬ ውስጥ ተገኘ

November11,2014
(ዘ-ሐበሻ) የቴክሳስ ፖሊስ ከኦክቶበር 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የጠፋችውን ኢትዮጵያዊት እናት አስከሬን ከሃይቅ ያነሰ ውሃ (ኩሬ) ውስጥ ከነመኪናዋ ገብታ ማግኘቱን አስታወቀ::

በመዲ ክሬክ የገበሬዎች ከሃይቅ አነስ ያለ ውሃ ውስጥ አንድ ቫን መኪና የተገኘ ሲሆን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ ገብረመድህንን ሰውነት እንዳገኘ ጠቁሟል:: የወ/ሮ አልማዝ ሰውነት የተገኝበት ጭቃማ ኩሬ የሚገኘው ከምትሰራበት ቦታ በ3 ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው:: ፖሊስ የአልማዝ ሰውነትን ከነ ሼቭሮሌት መኪናዋ እንዳገኘ ለቤተሰብ ያስታወቀ ሲሆን አሁን እንዴት መኪናው እዚያ ውሃ ውስጥ እንደገባ በምርመራ ላይ ይገኛል::ተጨማሪ መረጃ ተመልሰን ይዘን እንመጣለን…
almaz


Sunday, November 9, 2014

የፈርዖኖች ድንኳን እየፈረሰ ነው

November 9,2014
“ዓረብ ስፕሪንግ” እየተባለ ስለሚነገረው ህዝባዊ አብዮት ብዙ ተብሏል። ያ ህዝባዊ አመፅ ለውጥ አምጥቷል።ማን ይነካኛል ብሎ ዜጎቹን መከራ ሲያበላ የነበረው የቱኒዚያው ቤኒ ዓሊ ዛሬ የተረሳ ግለሰብ ሁኗል። እኔ ከሌለው ይህች አገር ትጠፋለች ሲል የነበረው ጋዳፊ ከተደበቀበት የአይጥ ጉድጓድ ውስጥ ተጎትቶ ወጥቶ እንደ ውሻ ተቀጥቅጦ ሙቷል። ሆስኒ ሙባረክም እንዲሁ ተርስቶ ቀርቷል። የየመንም አምባገነን አገር ጥሎ ሂዷል።በሶሪያም አምባገነኖች ከእንግዲህ ተረጋግተው ህዝባቸው ላይ የሚያላግጡበት ዘመን አብቅቷል።
በቱኒዚያዊው ሙሃመድ ቦዛዚ መስዋዕትነት የተጀመረው ህዝባዊ ዓመፅ ብዙ የዓረብ አገራትን አዳርሷል። ይህ ህዝባዊ አመፅ ከዓረቡ ዓለም ባሻገር ወደ ጥቁር ህዝቦች ተሽጋግሯል። ቡርኪና ፋሶዎች ለ27 ዓመት ስልጣኑን ሙጥኝ ብሎ የኖረውን ብሌስ ኮምፓዖሬን ከተቆናጠጠው የስልጣን ወንበር ላይ አባረውታል።
ብሌስ ኮምፓዖሬ የገዛ ወገኑን ሠላም እያሳጣ በጎሬቤት አገሮች ዋና አስታራቂ፤ የሠላም ሰው መስሎ ለመታየት ይኳትን ነበር። አሜርካኖች ቁልፍ ወዳጃችን ይሉትም ነበር። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በጎረቤት አገሮች መረጋጋት ዋና ተዋኒያኒ እያለ ያሞጋግሰው ነበር። ብሌስ ኮምፓዖሬ የራሱ እያረረበት፤ የጎሬበቱን እያማሰለ የአሜሪካኖችንና የአውሮፓዊያንን ቀልብ ይዞ ድፍን ሃያ ሰባት ዓመት በስልጣን ተንጠላጥሎ ኑሯል።
የቡርኪናው ብሌስ ኮምፓዖሬ 27 ዓመት ስልጣን ላይ ሲቆይ እንደ ህወሃት ከገዛ ህዝቡ ድምፅ ይልቅ የሌሎችን ድምፅ መስማት ይመርጥ ነበር። ህዝቡ ነፃ ምርጫ ይደረግ፤ ዜጎች በመረጡት መሪ ይመሩ፤ አገር አይታመስ ቢሉት ሊሠማ አልወደደም። ከዚህ ከወገኑ ድምፅ ይልቅ ከባህር ማዶ “ቁልፍ ወዳጃችን” ለሚለው ድምፅ ይገዛ ነበር። በጎረቤት አገሮች ውስጥ አስታራቂ እና ሽማግሌ እኔ ነኝ ብሎ ራሱን በመሾም ላይ ታች እያለ ሌሎችን ለማስደሰት ይንከላወስ ነበር።ይህ ግን ክብር አልሆነለትም።
አልቃይዳና ቦኩ ሃራምን የመሰሉ አሸባሪ ኃይሎች በተነሱ ግዜ ለብሌስ ኮምፓዖሬ ሰርግና ምላሽ ሆነለት። አሸባሪነትን ለመዋጋት የአሜሪካኖች ምርጥ ወዳጅ ለመሆን በቃ። የአየር ክልሉንም ለአሜሪካን የስለላ አውሮፕላኖች እንደልብ ፈቀደ።አሜሪካኖችም በወቅቱ ወዳጅ ብለው የጠሩትን ግለሰብ የሚፈፀመውን ኢ-ዲሞክራሲያዊ ሁኔታ እና የሚፈፀመውን ሰብዓዊ መብት ጥሰት አይተው እንዳላዩ ሆነው ልክ ለህወሃት እንደሚያደርጉት የገንዘብና ሌሎች እርዳታዎችን መለገሳቸውን ቀጥለው ነበር። አሸባሪ ተብለው የተፈረጁ ኃይሎች በየቦታው የመፈጠራቸው ሁኔታ ለህወሃቶችም የተመቻቸ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው የሚካድ አይደለም።
ኮምፓዖሬ በመፈንቀለ መንግስት ስልጣን ከጨበጠ በኋላ ምርጫ በተካሄደ ቁጥር እርሱና ፓርቲው ምርጫ አካሂደን አሸንፈናል እያሉ ለ27 ዓመት በስልጣን ቆይተዋል። በሌላ መልኩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫው የተጭበረበረ እንደሆነ ቢናገሩም ሰሚ ሳያገኙ ኑረው ነበር። ግዜው ደርሶ የህዝብ ቁጣ ገንፍሎ ከፍርሃት በላይ ሆነና ኮምፓዖሬ ሃያ ሰባት ዓመት ሙሉ ከተዘባነነበት ቤተ-መንግስት ሾልኮ ለሰደት ተዳረገ።
ህወሃቶች ይሄንና ከዚህ ቀደም የታየውን የህዝብ ቁጣ አይተዋል። ከዚህ ዓይነቱ የህዝብ ቁጣ የሚቀስሙት ትምህርት ይኖራል ብለን አንጠብቅም። በፈርዖን ትዕቢት ድንኳን ተጠልለው የሚኖሩ ኃይሎች የህዝብ ቁጣ ገንፍሎ መቃብር እስከ ሚጨምራቸው ድረስ ይማራሉ ብሎ መጠበቅ ከንቱ ምኞት ነው።ዛሬ ሁሉ በእጃቸው፤ ሁሉ በደጃቸው ፤ሚድያው የእነርሱ፤ የመረጃ መረቡ ከአገር ደህንነት ይልቅ የእነርሱን እድሜ ለማራዘም የሚሰራ ሆኖ እንደሚቀጥል አምነዋል። የአገሪቷ አጠቃላይ ሃብትም በእጃቸን ነው። መከላከያ ኃይሉም እኛን ከመጠበቅ ውጪ ሌላ ተልዕኮ የለውም ብለዋል።ይሄን ሁሉ በእጃችን ይዘን ማነው የሚነካን? የትኛውስ ህዝብ ነው የሚነሳብን ብለው ልባቸውን እንደ አለት ማደንደንን መርጠዋል። የህዝብ አመፅ ተነስቶ አገር ከመታመሱ በፊት ለሁሉም በእኩል ደረጃ ሊጠቅም የሚችል ምን በጎ ነገር እንሥራ ብለው ለማሰብ ምንም ፍላጎት የላቸውም። እንዲያውም የህዝብ አመፅ ቢነሳ ውጤቱን ስለማታውቁት “ከማታውቁት መላክ፤የምታውቁት ሴይጣን ይሻላችኋል” ለማለት እየዳዳቸው እንደሆነ እያየን ነው።
ህወሃቶች ትውልድ፤ ወገን፤ አገር የሚባል ቋንቋ እንደማያውቁ በተግባር አሳይተውናል።የህወሃቶች አገራቸው ድርጅታቸው እንጂ ኢትዮጵያ አይደለችም።እነርሱ አገር ሲሉ እነርሱን እንጂ ሌላውን እንደማይጨመር መልሰው መላልሰው ነግረውናል። ”እኛ ከሌለን ኢትዮጵያ ትበተናለች” የሚለው መፈክር ምንጩ ህወሃቶች አገርና ትውልድ የሚል ቋንቋ በውስጣቸው የሌለ መሆኑን ይገልጥልናል። ይሄ መፈክራችሁ ቅዥት ነው፤ ተው ከዚህ ቅዥታችሁ ወጥታችሁ ወደ ገሃዱ ዓለም ተመለሱ፤ በገሃዱ ዓለም አገር እና የተቆጣ ትልቅ ህዝብ አለ። ይህ አገርና ህዝብ ከእናንተ በላይ ነው ብሎ ሊመክራቸው የሚሞክር ከተገኘ አሸባሪነት ተለጥፎበት ጠላት ይባላል።
ለብሌስ ኮምፓዖሬ የአልቃይድና የቦኩ ሃራም መፈጠር ሰርግና ምላሽ የሆነውን ያህል አሸባሪነት ለህወሃቶች የመኖሪያቸው ድንኳን ሁኗቸዋል። አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል ኮምፓዖሬ ለአሜሪካኖች ብርቱ ወዳጅ እንደ ነበረው ሁሉ ህወሃቶችም አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል ሽፋን ለአሜሪካኖች ወዳጅ ለመሆን በቅተዋል። አሜሪካኖችም የህወሃትን ሥም ከአሸባሪነት መዝገብ ሳይፍቁ፤ ህወሃቶች የሚፈፅሙትን ወንጀል እያወቁ እንዳላወቁ፤ አይተው እንዳላዩ ሁነው እርዳታቸውን ሳያቋርጡ እሰከ ዛሬ አሉ። ይህ ለህወሃቶች ባዶ ድፍረት እና የትዕቢታቸውም ምንጭ ሁኗቸው የተሻለ ሃሳብ አለኝ የሚለውን ሁሉ አሸባሪ እያሉ ነው። ህወሃቶችን የሚያሸብራቸው ብዙ ነው። የነፃነት ጥያቄ ያነሳ ያሸብራቸዋል። እኛ ከህወሃት አናንስም፤ህወሃትም ከእኛ አይበልጥም የሚል ከተነሳም ያሸብራቸዋል። እኔ ህወሃትን አልመርጥም የሚል ድምፅ ከተሰማም አሸባሪ ነው። ይሄ የሚያሳየን ህወሃት ኃጢአቱ የሚያሳድደው እና ጥላው የሚያስበረግገው ድርጅት ወደ መሆን መሸጋገሩን ነው። ህወሃቶች በሰሙት ድምፅ ሁሉ እየበረገጉ አገሪቷን እያመሱ እንደማይዘልቋት እኛ ልናስታውሳቸው እንወዳለን።
ህወሃቶች ከህዝቡ ድምፅ ይልቅ የሌሎችን ድምፅ መስማት ከነ ልጅ ልጆቻችን አገሪቷን ለመበዝበዝ ይረዳናል የሚል የደንቆሮ ዕምነት አላቸው። በየጎረቤት አገር ውስጥ ዘው ብለው እየገቡ ራሳቸውን የሠላም መለእክተኛ አድርገው ለዓለም ህዝብ ለማሳየት ይኳትናሉ። እኛ ከሌለን ምስራቅ አፍሪካ በአክራሪ ኃይማኖተኞች ትጠለቀለቃለች፤የአሸባሪዎችም መናኽሪያ ትሆናለች ኢትዮጵያም ትበተናለች እያሉም የሌሎችን ቀልብ ለመያዝ ደጅ ይጠናሉ።ከአሜሪካንና ከአውሮፓዊያን እጅ ለሚወረወርላቸው ምናምን ሲሉ ሳይላኩ ይሄዳሉ፤ ሳይጠሩ ከተፍ ይላሉ። ህወሃቶች ይህን ተላላኪነትንና አደር ባይነት እንደ ሥራ ይቆጥሩታል።ሥራ በመሆኑም ሶማሊያ ዘው ብለው ገብተው የእኛን ልጆች አስከሬን በመቋዲሾ ጎዳና ላይ አስጎትተው መሳለቂያ እንዲሆን አድርገዋል። ህወሃቶች ሶማሊያ ዘው ብለው በመግባታቸው ኢትዮጵያ እንደ አገር ስትጎዳ በግል ደረጃ ግን የህወሃት ጄኔራሎችና ባለሟሎቻቸው በተገኘው የደም ገንዘብ ስም አጠራሩን እንኳ የማያውቁትን አልኮሆል እየተጎነጩ ተዘባነውበታል። ባለ ሃብትም ለመሆን በቅተዋል።
እነዚህ ቡድኖች በህዝቡ እና በአጠቃላይ አገሪቷ ላይ የሚፈፅሙት ክህደት በየትም አገር ታይቶ የሚታወቅ አይደለም።ብሌስ ኮምፓዖሬና ፓርቲው ከህወሃቶች ጋር ሲነፃፀሩ እንደ መልዓክና ሴይጣን ናቸው። ህወሃቶች ከሰው አብራክ የተፈጠሩ አይመስሉም። የስግብግብነታቸው ወሰን ማጣት፤ ምንም አገራዊ ራዕይ የሌላቸው መሆን፤ ርህራሄ የሌላቸው ፍፁም ጨካኞች መሆናቸው፤ ከእውነት ጋር የማይተዋወቁ ውሸትን የኑሯቸው ድንኳን ማደረጋቸው ሲታይ ህወሃትን የሚመስል ክፉ በየትም ዓለም አለ ለማለት ይቸግራል። የኢትዮጵያ ህዝብ በህወሃቶች የደረሰበትን ብዙ መከራ ተሸክሞ ለብዙ ዘመን ኑሯል። ብዙ ዜጎች አገር አልባ ሁነው ተንክራታች ሁነው ቀርተዋል። ብዙ እናቶች እንባቸውን በመዳፋቸው የሚያፍሱ ሁነው ቀርተዋል። ይህ ግን የሚያበቃበት ግዜ እሩቅ አይደለም።
ህወሃቶች ሆይ ስሙ !
ነገ እንደ ዛሬ አይሆንላችሁም። አንድ የዋህ አምባ ገነን ገዢ ሊፈፀመው የሚችለውን ድርጊት ለፈፀመው ለብሌስ ኮምፓዖሬ ዛሬ እንደ ትላንትና እንዳልሆነለት ተመልከቱ። እናንተ እያደረሳችሁ ያላችሁት በደል እና እየፈፀማችሁ ያላችሁት የአገር ክህደት ምሳሌ የማይገኝለት ነው። የእናንተ ምርጫ ከሰላም ይልቅ ደም መፋሰስ፤ አብሮ ከመኖር ይልቅ መለየት፤ ለወገንና ለአገር ከማሰብ ይልቅ ለግል ጥቅም ብቻ መሯሯጥ ሁኗል። በዚህ ምርጫችሁ የተቆጣ ህዝብ እንደ ተደፋነ እሳት ውስጥ ውስጡን እየጨሰ መሆኑን ለማስተዋል ትዕቢታችሁ ሂሊናችሁን ጋርዶታል። ትዕቢታችሁ ወሰን ከማጣቱ የተነሳ እዚህም እዚያም እየተነሱ ያሉትን ብዙ የብሶት ድምፆችን ለማፈን ብዙ ንፁሃን ዜጎችን ትገድላላችሁ፤ታስራላችሁ፤ ታንገላታላችሁ፤ ታዋርዳላችሁ። እናንተን ሸሽቶ ወደ ጎሬቤት አገር የሚሰደደውን ሳይቀር በቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች ታስገድላላችሁ፤ እያሳፈናችሁ ትወስዳላችሁ።የምትፈፅሙት ግፉ ፅዋውን ሞልቷል።
እኩይ ዲርጊታችሁ እያሳደዳችሁ የገዛ ጥላችሁ እንኳ እያሸበራችሁ ለአገራቸው በጎ ራዕይ ያላቸውን ጥሩ ዜጎች በሙሉ አሸባሪ እያላችሁ እንደምትከሱ ዓለም ሁሉ ዓይኑን ከፍቶ እየታዘበ ነው። በእኩይ ዲሪጊቶቻችሁ ምክንያት ከመሸበራችሁ የተነሳ ሁሉንም ድምፅ ለማፈን የምታጠፉት የአገር ሃብት ነፃነትን፤ እኩልነትን፤ ፍትህንና በእውነት ሊሠራ የሚችል ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ቢውል ኑሮ በእውነት ሠላም አግኝታችሁ መኖር በቻላችሁ ነበር። እናንተ ግን የጨለማውን መንገድ መርጣችኋልና እርሱን እንደምታገኙ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ አይግባችሁ።
አዎን በምርጫችሁ መሠረት በሚገባችሁ ቋንቋ የሚያናግራችሁ ትውልድ የአያቶቹን የነፃነት ጋሻና ጦር አንስቶ ተሠማርቷል። አይናችሁ እያየ፤ጆሯችሁም እየሰማ ወጣቶች ከመላዋ ኢትዮጵያ ተሰባስበው አያቶቻቸው በኩራት በቆሙበት ተራራ ላይ አንገታቸውን ቀና አድርገው እየተመላለሱበት ነው። ህወሃትን የመሠለ ዘረኛ፤ ሌባ እና አደረ ባይ ቡድን ኢትዮጵያን የመሰለች ትልቅ አገር ሲያዋርድ አይተን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ያሉ የኢትዮጵያ ልጆች ዝናራቸውን ታጥቀው ተነስተዋል። እናቶችም ወገባቸውን በገመድ ታጥቀው ወጣቶቹን እየመረቁ ወደ ጀግኖቹ መንደር እየሸኙ ነው። የተቀሩትም ሳያቅማሙ የኃላ ደጀን ሁነው ቁመዋል። እንግዲህ ኢትዮጵያን የሚያዋርዱ፤ አገሪቷን የሚዘርፉ፤ ንፁሃን ዜጎችን የሚያሰቃዩ ወየውላቸው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Friday, November 7, 2014

አንድነት በአባላቱ ላይ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ

November7,2014
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ አባላቱ ላይ መጠነ ሰፊ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ጥቅምት 28/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስረዳው ገዥው አካል አንድነትን በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የፓርቲው አባላትን በማሰር ላይ እንደሚገኝ ገልጹዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ በወላይታ ያሉ አባላቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባና ማዋከብ እንደሚፈጸምባቸው ያስታወቀ ሲሆን፣ ከቀናት በፊት በጎንደር፣ በጎጃምና በመቀሌ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ላይም እስር እየተፈጸመባቸው መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል፡፡ መግለጫው አክሎም በእስር ላይ የሚገኙት አባላቱ የት እንዳሉ እስካሁን ማወቅ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡

‹‹በሀገሪቱ ላሉት ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እስርና ወከባ መፍትሔ አይሆንም›› ያለው የአንድነት መግለጫ አሁን ያሉት ችግሮች በዚሁ ከቀጠሉ የህዝቡ ብሶት ወደሌላ አቅጣጫ ሊሄድ እንደሚችልና ያልታሰበ ጥፋት ሊመጣ እንደሚችል ስጋቱን ገልጹዋል፡፡ አንድነት በቀጣይ ለሚያደርገው ትግልም ህዝቡ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል፡፡
Photo: አንድነት በአባላቱ ላይ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ አባላቱ ላይ መጠነ ሰፊ እስርና ወከባ እየተፈጸመበት መሆኑን አሳወቀ፡፡

ፓርቲው ዛሬ ጥቅምት 28/2007 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስረዳው ገዥው አካል አንድነትን በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ የፓርቲው አባላትን በማሰር ላይ እንደሚገኝ ገልጹዋል፡፡ 

አንድነት ፓርቲ በወላይታ ያሉ አባላቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባና ማዋከብ እንደሚፈጸምባቸው ያስታወቀ ሲሆን፣ ከቀናት በፊት በጎንደር፣ በጎጃምና በመቀሌ በሚገኙ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ላይም እስር እየተፈጸመባቸው መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል፡፡ መግለጫው አክሎም በእስር ላይ የሚገኙት አባላቱ የት እንዳሉ እስካሁን ማወቅ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡ 

‹‹በሀገሪቱ ላሉት ዘርፈ ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እስርና ወከባ መፍትሔ አይሆንም›› ያለው የአንድነት መግለጫ አሁን ያሉት ችግሮች በዚሁ ከቀጠሉ የህዝቡ ብሶት ወደሌላ አቅጣጫ ሊሄድ እንደሚችልና ያልታሰበ ጥፋት ሊመጣ እንደሚችል ስጋቱን ገልጹዋል፡፡ አንድነት በቀጣይ ለሚያደርገው ትግልም ህዝቡ ከጎኑ እንዲቆም ጥሪውን አቅርቧል፡፡

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

November 7,2014
ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

fantahun berhanu

Thursday, November 6, 2014

መልዕክት ከቃሊቲና ከቂሊንጦ

Novenber 6,2014
ነገረ ኢትዮጵያ
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ የዝግጅት ክፍል አባላት ወደ ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤቶች በማቅናት እስረኞችን ጠይቀዋል፡፡ እስረኞቹ ያስተላለፉትን መልዕክት ነገረ ኢትዮጵያ እንደሚከተለው ጠቅለል አድርጋ አቅርባዋለች፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም›› እስክንድር ነጋ
በማህበራዊ ድረ-ገጽም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች መልካም ልደት ለተመኛችሁልኝ ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የቡርኪናፋሶው አምባገነን መውደቁን በመስማቴ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ይህ ለእኔ ውድ የልደት ቀን ስጦታየ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፡፡ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥም ለውጥ የሚቀር አይደለም፡፡ የእኛ ችግር ከማንም የባሰ ነው፡፡ ቱኒዚያ ላይ የተጀመረው አብዮት ሰሜን አፍሪካ አንቀጥቅጧል፡፡ ኢትዮጵያ ከሰሜን አፍሪካ አገራት ይልቅ ለእነ ቦትስዋና ትቀርባለች፡፡ የቦትስዋና ጉዳይ ሌሎቹንም ማነቃነቁ የማይቀር ነው፡፡ ይህ ለውጡ ቅርብ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም፡፡
‹‹ቂሊንጦም ገደብ አለብኝ›› አብርሃ ደስታ
አሁን ደህና ነኝ፡፡ ማዕከላዊ ምርመራ ማዕከል ሳለሁ ጨጓራ በጣም ያመኝ ነበር፡፡ እዛ ያለው ምግብ ነበር ያሳመመኝ፡፡ ከሰማያዊ ወጣቶች ምግብ ከውጭ መምጣት ከጀመረ ወዲህ ተሽሎኛል፡፡ አሁንም ቂሊንጦ እየመጡ እየጠየቁን ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ የሰማያዊ ወጣቶችን እጅግ በጣም አመሰግናለሁ በሉልኝ፡፡
እዚህ እስር ላይ ያለን ሰዎች ከውጭ ምን መረጃ አለ የሚለውን ነው የምንፈልገው፡፡ አሁን ወደእናንተ ስመጣ ጎብኝ ይፈልገኛል ብዬ የእስር ቤቱን ተወካይ አስፈቅጄ ነው የመጣሁት፡፡ ገደብ አለብኝ፡፡ እኔ እና በእኛ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ የሆነው ዘላለም ወርቃገኘሁ ጠያቂ ሲመጣ ለኃላፊዎች በጎብኝዎቻችን እንደተፈለግን ሳንናገር መውጣት እንደማንችል ተነግሮናል፡፡
‹‹ስለእኔ የእስር ጉዳይ ማሰብ አልፈልግም›› አንዱዓለም አራጌ
እኔ ለሀገሬና ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሆን የምፈልገው መልካም ነገር መቼ ይፈጸማል የሚለው እንጂ እኔ መቼ ከእስር እወጣለሁ የሚለው አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ ሰላማዊ ትግል በባህሪው ውጤቱ በጎ ነው፡፡ እኔና መሰሎቼ በሰላማዊ ትግል ነው የምናምነው፡፡ በዚህ የትግል ስልት ደግሞ ለውጥ ሲመጣ ማየት እሻለሁ፡፡ ስለእኔ የእስር ጉዳይ ማሰብ አልፈልግም፡፡ በጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ መልካም ነገሮች እንዲሆኑ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ነው የእኔ ምኞት!
‹‹እኛ ነጻ የምንወጣው የተባበርን ዕለት ነው›› የሺዋስ አሰፋ
በማዕከላዊ ያሳለፍነው ጊዜ ዘግናኝ ነው፡፡ በተለይ 3 ወር ተኩል የቆየንበት ሳይበሪያ የሚባል ቦታ በረዶ ቤት ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ድብደባው አለ፡፡ ማዕከላዊ ውስጥ ምርመራ፣ ህክምና፣ እስረኛ አስተዳደር፣ ጥበቃና የቢሮ አስተዳደር የሚባሉ አምስት ክፍሎች አሉ፡፡ ማዕከላዊ ውስጥ ድብደባ ይፈጽማሉ፣ ሰብአዊ መብት ይጥሳሉ፡፡ ነገር ግን ሁሉም ሰው ተመሳሳይ አይደለም፡፡ ለምሳሌ በምርመራ ወቅት የምንደበደበው በሚስጥር ነው፡፡ ከአምስቱ ክፍል ውስጥ በአንዱ የሚሰራ መደብደባችን አሊያም የሆነ ችግር እንደተፈጠረብን ሲሰማ መረጃው ወደውጭ ይወጣል፡፡ ማዕከላዊም ቢሆን ጨካኝ ሰዎች እንዳሉት ሁሉ ጥቂትም ቢሆኑ መልካም ሰዎች አሉበት፡፡
የመርማሪዎቹ ሁኔታ ግን የሚገርም ነው፡፡ እነሱ የያዙኝ ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለህ ብለው ነው፡፡ ምርመራው ግን የሰማያዊ ፓርቲ የገንዘብ ምንጭ ከየት ነው? ጠንካራ ቢሮ ያላችሁ የት ነው? ጠንካራ አባልና አመራራችሁ የትኛው ነው? የሚል ነው፡፡ በምርመራ ወቅት ሳልታሰር የግንቦት ሰባትን ተቃውመው እንደሚጽፉ የማውቃቸው ሰዎች ሳይቀር ‹‹የግንቦት ሰባትን ጽሁፍ ልከውልሃል!›› ተብያለሁ፡፡
ሰው ገለዋል፣ ሰርቀዋል ....እየተባሉ ማዕከላዊ የታሰሩ ሰዎች አሉ፡፡ እነሱና ሌሎች ታሳሪዎች ቃላቸው ከክስ መዝገባቸው ጋር ይያያዛል፡፡ የእኛ ግን የሚረባ ነገር ስላላገኙበት ሊያያይዙልን አልቻሉም፡፡ በጣም የሚገርመው እኛ ተዘግቶብን ስንውል ሌሎቹ (በስርቆትና በመሳሰሉት የታሰሩት) መውጣት መግባት ይችላሉ፡፡ እንደኛ በረዶ ቤትም አይታጎሩም፡፡
እኛ የታሰርነው ለሌላ ሰውም ብለን አይደለም፡፡ እኛ የታሰርነው ለራሳችን ነጻነት ነው፡፡ ስለሆነም ምንም የሚያስፈራን ነገር የለም፡፡
ውጭ የምንሰማው እንቅስቃሴ ደስ ይላል፡፡ ዳያስፖራው እንያደረገ ያለውን አንዳንድ እንቅስቃሴ እንሰማለን፡፡ በተለይ 9 ፓርቲዎች በትብብር ለመስራት መስማማታቸው ስለሰማሁ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ለመስራት ያቀዱትም ደስ ያሰኛል፡፡ እኛ ነጻ የምንወጣው የተባበርን ዕለት ነው፡፡ ከታሰርን ጀምሮ ከጎናችን ለቆመው የኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ ምስጋና ማቅረብ እፈልጋለሁ፡፡
‹‹መሰባሰብ አለብን›› ሀብታሙ አያሌው
ማዕከላዊ የነበረን ቆይታ ዘግናኝ ነበር፡፡ የታሰርነው በጣም ቅዝቃዜ ካለው ቤት ነው፡፡ ጠዋት 11 ሰዓት ለጥቂት ጊዜ ወጥተን ማታ እንደገና ይከፈትልንና እንደገና እንገባለን፡፡ በተለይ እኔ ህመም ነበረብኝ፡፡ ብነግራቸው ሊሰሙኝ አልቻሉም፡፡ እየቆየ በጣም በረታብኝ፡፡ በጣም ታምሜ ነበር፡፡ በምርመራ ወቅት የሚደረገው በጣም ያሳዝናል፡፡ እነሱ የከሰሱኝና የሚመረምሩት የተለያየ ነው፡፡
አብዛኛው ክስ የተነሳብኝ ከኢሳት ጋር ግንኙነት በማድረግ ስርዓቱን ለመገልበጥ የሚል ነው፡፡ ኢሳት ሚዲያ ነው፡፡ እኔ የተለያዩ አስተያየቶችን ሰጥቼ አውቃለሁ፡፡ ከዘመኑ ካሴ ጋር አለህ የተባልኩት ግንኙነት የሚገርም ነው፡፡ ከፓልቶክ የወሰዱት ንግግር ነው፡፡ በሌላ ጊዜ የተጻፈ ብቻ ሳይሆን ድምጽም ያሰሙ ነበር፡፡ የእኔን አላሰሙም፡፡ የሚገርመው ከዘመነ ጋር ተገናኘህ የተባልኩት በግንቦት 2004 ነው፡፡ በነገራችን ላይ በዚህም ወቅት ቢሆን እሱን አልከሰሱትም፡፡ እኔን የከሰሱኝ በአንድነት የህዝብ ግንኙነት ሆኖ የግንቦት ሰባትን አላማ ለማሳካት የሚል ነው፡፡ የሚያሳዝነው በዚህ ወቅት እኔ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ነው የነበርኩት፡፡
በጣም የሚያሳዝነው በእኛ ላይ ያቀረቡት ክስ አይደለም፡፡ በክሱ ላይ አንድነት፣ ሰማያዊና አረና የጸረ ሽብር፣ የሚዲያ፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችና የመሳሰሉትን አዋጆችና ህጎች ስለማይቀበሉ ህገ ወጦች ተደርገው ተወስደዋል፡፡ እኛ ከእነዚህ አመራሮቻቸው መካከል እየተባልን ነው ድምዳሜው የተሰጠብን፡፡ ሌላም ሊያጠቁት የሚፈልጉት ሰው አለ ማለት ነው፡፡
ተቃዋሚዎች ተባብረው ለመስራት እየጣሩ እንደሆነ ሰምቻለሁ ደስ ብሎኛል፡፡ መንገዳችን አንድ ነው፡፡ መሰባሰብ አለብን፡፡ አንድነትም ወደ ስብስቡ እንደሚመጣ ተስፋ አለኝ፡፡ ተሰባስበን ስንሰራ ነው በደሉን ልናስቆመው የምንችለው፡፡
በስተመጨረሻም ከታሰርንበት ጊዜ ጀምሮ ከጎናችን ለቆመው አገር ውጥም ሆነ በውጭ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ላቀርብ እፈልጋለሁ፡፡