Saturday, August 2, 2014

በእስር ቆይታቸው 100 ቀናት ለደፈኑት ጦማርያን የተማጽኖ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ተላከ፡፡

August2/2014
‹‹ዞን ዘጠኝ››  የጦማሪያን ቡድን አባላት ዘለዓለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላና ሶልያና ሺመልስ ሲሆኑ፣ ተስፋለም ወልደየሱስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና ኤዶም ካሳዬ ደግሞ ጋዜጠኞች ናቸው፡፡ ሶልያና የተከሰሰችው በሌለችበት ነው፡፡
በቅርቡም ቀደም ሲል መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጀው የግንቦት ሰባት ዋና ጸሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከየመን ዋና ከተማ ሰነዓ በቁጥጥር ሥር ውለው ይገኛሉ፡፡ እንዲሁም ደግሞ በተመሳሳይ ጊዜ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው አራት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችን (አብርሃ ደስታ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺና ስለሺ አሰፋ) መንግሥት በቁጥጥር አውሏል፡፡
ethopia-bloggersመንግሥት የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ካፀደቀ ጊዜ ጀምሮ በርካቶች በዚህ ሕግ እየጠየቀ ይገኛል፡፡ ይህንን ሕግ፣ የሲቪል ማኅበራት አዋጅ፣ እንዲሁም የፕሬሱ አዋጅ ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ትችት ሲቀርብበት የቆየ መሆኑም አይዘነጋም፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን በርካታ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የተማፅኖ ደብዳቤ ልከዋል፡፡ ከደብዳቤው ፈራሚዎች መካከል ሂዩማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል በግንባር ቀደምትነት የሚገኙበት ሲሆን፣ እነዚህ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የሰብዓዊ መብት አያያዝና የፕሬስ ነፃነት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ተስማምተው አያውቁም፡፡
እነዚህ ድርጅቶች በየጊዜው በሚያወጡዋቸው ሪፖርቶች ከመንግሥት ጋር ሲጋጩ የቆዩ ሲሆን፣ በተለይ የኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች በሶማሊያና በኦጋዴን ተፈጸመ ባሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ምክንያት ግንኙነታቸው እጅግ እንዲሻክር ምክንያት ሆኖ ነበር፡፡
አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂዩማን ራይትስ ዎች አንዳንዴም የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት በዓመታዊ ሪፖርታቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ከፍተኛ ትችት የሚሰነዝሩ ሲሆን፣ መንግሥትም አንዳንዴ ዘጋቢ ፊልሞችን በመሥራት የአፀፋ ምላሽ ሲሰጥ ይስተዋላል፡፡
ሰሞኑን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የተላከው ደብዳቤም አርቲክል 19 እና እነዚህ ሁለት ድርጅቶች በግንባር ቀደምትነት ያሉበት ሲሆን፣ በአጠቃላይ ደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን ያሳረፉ ግን ቁጥራቸው አርባ አንድ ነው፡፡
መንግሥት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችንም ሆነ ጋዜጠኞችን ወይም  የፖለቲካ ተሟጋቾች በእስር ሲያውል እንዲህ ዓይነት ደብዳቤ መጻፍና የታቃውሞ መግለጫ ማውጣት የተለመደ ቢሆንም፣ በዚህ ደረጃ በዓለም ዙሪያ ያሉት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች (ብዙዎቹም አፍሪካ ውስጥ የሚገኙ ናቸው) በአንድ ላይ መንግሥትን ሲቃወሙ ለመጀመርያ ጊዜ ነው፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት እነዚህ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ በተለይ የምዕራባዊያን የፖለቲካ አቋም ኒዮ ሊብራሊዝምን አራማጆች በሚል ምንም ዓይነት መለሳለስ የማያሳይ ሲሆን፣ የአገሪቱ የፖለቲካ ዕድል በራሷ ሕዝቦችና በራሷ መንግሥት ብቻ እንዲወሰን የፀና አቋም አለው፡፡
ጠንካራና ነፃ የሰብዓዊ መብት ተቋም በሌለበት በየትኛውም አካባቢ በሚኖር ሕዝብ የሚፈጸም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያገባኛል የሚል አቋም ያላቸው እነዚህ ድርጅቶች ግን፣ ሰብዓዊ መብት የዓለም አቀፋዊነት (ዩኒቨርሳል) ጉዳይ መሆኑን በመከራከሪያነት ያቀርባሉ፡፡
ደብዳቤው ክብደት ይኖረው ይሆን?
አርባ አንድ ድርጅቶች ፊርማቸውን ያሳረፉበትና “Detention of Bloggers is a Violation of International Law” [ጦማርያንን ማሰር ዓለም አቀፍ ሕግን መጣስ ነው] በሚል ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የተላከው ይኸው ደብዳቤ፣ ዋና ይዘቱ ላለፉት ሦስት ወራት በእስር የቆዩትና በቅርቡ ክስ የተመሠረተባቸውን ጦማሪያን መንግሥት በነፃ እንዲለቃቸው የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሌሎች ቀደም ሲል ሲያነሱዋቸው የነበሩት ቅሬታዎችም ተካተውበታል፡፡
በመጀመሪያ ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶችንና የአፍሪካ ቻርተሮችን ፈራሚ መሆኗ ተጠቅሶ፣ የኢትዮጵያ ፀረ ሽብርተኝነት ሕግ እነዚህን ዓለም አቀፍ ስምምነቶችና የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ይጥሳል በሚል ነው፡፡ ለዚህም እንደ ማስረጃ ያቀረቡት፣ አንዳንድ የተመድ አጣሪ ቡድኖች ቀደም ሲል በሽብር የተፈረደባቸው የፖለቲካ አቀንቃኝ እስክንድር ነጋ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ መምህርትና ዓምደኛ ርዕዮት አለሙና አንዱዓለም አራጌ ላይ ያቀረቡዋቸውን ሪፖርቶች ዋቢ በማድረግ ነው፡፡ በእነዚህ ግለሰቦች ላይ ተፈጸመ ያሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ መንግሥት ተቃዋሚዎችንና ጋዜጠኞችን ለማፈን እንደ መሣሪያ ተጠቅሞበታል የሚለውን ድምዳሜ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኘ ሐሳብ እንደሆነ አቅርበዋል፡፡ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ እንዲከለስም የደብዳቤው ሌላ ዋና ይዘት ነው፡፡
በደብዳቤው ፊርማቸውን ካሳረፉት ድርጅቶች መካከል የአራቱ ተቀማጭነታቸው በናይጄሪያ፣ የሦስቱ በደቡብ ሱዳን፣ የሁለቱ በግብፅ፣ የሁለቱ ደግሞ በብሩንዲ ሲሆኑ የተቀሩት ማዕከላዊ አፍሪካ፣ ታንዛኒያ፣ ዛምቢያ፣ ዚምባቡዌ፣ ጋምቢያ፣ ምዕራብ አፍሪካና ኬንያ ውስጥ ነው፡፡ የተቀሩት ደግሞ ከዞን ዘጠኝ ጋር በተያያዘ ስሙ ተደጋግሞ ሲነሳ የነበረው አርቲክል 19ን ጨምሮ ተቀማጭነታቸው በአውሮፓና በአሜሪካ ነው፡፡
ደብዳቤው በተመድ፣ በአውሮፓ ኅብረትና በአፍሪካ ኅብረት ድርጅቶች ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ ይመስላል፡፡
‹‹መንግሥት አቋሙ መመርመር አለበት›› 
የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የቀድሞ ሊቀመንበር አቶ ሙሼ ሰሙ፣ የደብዳቤውን ተፅዕኖ ፈጣሪነት በሁለት አቅጣጫ አይተውታል፡፡ ቀደም ሲል በተመሳሳይ የተለያዩ የተቃውሞ ሪፖርቶች ቢወጡም እዚህ ግባ የሚባል ለውጥ በመንግሥት አሠራር ላይ አለማምጣታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ መንግሥትም በራሱ መንገድ ድርጅቶችን መፈረጁን እንደቀጠለ ያስረዳሉ፡፡ እነዚህ ዓይነት ሪፖርቶች ተፅዕኖ ያልነበራቸው አንድም በመንግሥት ቀድመው የተፈረጁ በመሆናቸው ለመቀበል የሚያሳየው ባህሪ አነስተኛ መሆኑን፣ እንዲሁም ድርጅቶቹ የሪፖርት እወጃቸው በመንግሥት ተቀባይነት ሲያጣ ቀጥለው የሚሠሩት ሥራ አለመኖሩ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ‹‹እስከምን ድረስ ይሄዳሉ?›› የሚል ጥያቄም ሰንዝረዋል፡፡
አቶ ሙሼ በተጨማሪ የትም ቢሄዱ ‹‹ምን ያህል ተፅዕኖ መፍጠር ይችላሉ?›› የሚል ሌላ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ‹‹ድርጅቶቹ ቀጥተኛ ተፅዕኖ መፍጠር አይችሉም፡፡ የተቀመጡባቸው አገሮች መንግሥታት ኢትዮጵያ ላይ አንዳንድ የዕርዳታና የብድር ማዕቀብ እንዲጥሉ የሚወተውቱ ቢሆንም፣ እስካሁን ተግባራዊነቱ አልታየም፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡
መንግሥታት በእነዚህ ድርጅቶች ከሚቀርብላቸው ጥያቄ የበለጠ አቋማቸውን የሚመለከቱት ከአጠቃላይ የሕዝብ ፍላጎትና የአገር ለአገር ግንኙነት አንፃር መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
አቶ ሙሼ እንደሚሉት ደብዳቤው ሌላ ፋይዳ ግን አለው፡፡ በዚህ ደረጃ ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የቅሬታ ደብዳቤ ሲጻፍ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሙሼ፣ ለድርጅቶቹ ቁጥር ትልቅ ሥፍራ ሰጥተውታል፡፡ ‹‹በያሉበት የራሳቸውን ተፅዕኖ ይፈጥራሉ፤›› ብለዋል፡፡
እሳቸው እንደሚሉት፣ መንግሥት ጥያቄው ከእነሱ ስለመጣ ሳይሆን የተጻፈውን በትዕግሥት አይቶ ክፍተቱን ለመሙላት አቋሙን በመፈተሽ ቢጠቀምበት መልካም ነው፡፡ ዋናው ተፅዕኖ አገር ውስጥ ከሚገኙት ከሕዝብና ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች መሆን እንዳለበትም መክረዋል፡፡ ‹‹ሰው በአስተሳሰቡ ምክንያት መታሰር የለበትም፤›› በማለት በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ከዚህ የዘለለ አስተያየት ከመስጠት አቶ ሙሼ ተቆጥበዋል፡፡
ቀደም ሲል እንዲህ ዓይነት ሪፖርት ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ሲወጣ መንግሥት አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ ሲሆን፣ ለዚህኛው ደብዳቤ መልስ በሚመስል ሁኔታ ስለድርጅቶቹ ሪፖርት እንከንና ስለኢትዮጵያ አቋም የሚያሳይ ዶክመንተሪ በኢቲቪ ማክሰኞ ምሽት ቀርቧል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት አጭር ምላሽ የመማር፣ የመጻፍና የማሰብ ነፃነት የመሳሰሉ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች የኢትዮጵያ መንግሥት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አካል መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ከዚህም በመነሳት፣ ‹‹ሰብዓዊ መብት የኢትዮጵያ ፖሊሲ እምብርት ነው፣ የህልውናችን ጥያቄ ነው፤›› በማለትም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ግልጽ የሆነ የሕግ ጥሰት ካልተፈጸመ በስተቀር ሰዎች የመሰላቸውን በመጻፋቸው እንደማይታሰሩ አስረድተው፣ የውጭ ድርጅቶችን የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነም ገልጸዋል፡፡ ‹‹በአንድ ሉዓላዊ አገር ፖለቲካ ውስጥ እየገቡ እገሌን ፍቱ፣ እገሌን እሰሩ የማለት መብት የላቸውም፣ በእነሱ ጥያቄ የሚመጣ ለውጥ አይኖርም፤›› ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ለተማፅኖው ደብዳቤ ግልጽ ምላሽ ያልሰጡ ቢሆንም፣ ቀደም ሲል ለእስር የተዳረጉ ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹አንድም በሙያው የታሰረ ሰው የለም፡፡ ኢትዮጵያን ለማናጋት የተዘረጋው የሽብር መረብ እስኪበጣጠስ ግን ከዚህ መረብ ጋር የተገናኘ ማናቸውም ሰው ላይ ዕርምጃ መውሰዳችን እንቀጥላለን፤›› በማለት የመንግሥታቸውን አቋም ግልጽ አድርገዋል፡፡

ስለ ዳተኛ ምሁራንቸል አንበል

August2/2014
ዳኛቸው ቢያድግልኝ
ምሁር የሚለው ስያሜ እውቀት የተካነ ጥበብን አፍላቂ የዐለምን ምስጢር መርማሪ፣ እውነት መስካሪና አስተማሪ ለሆኑ የሚሰጥ መጠርያ ነው ወይንስ በአንዱ ወይም በሌላው ተቋም ውስጥ ያለፉና ያንን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት (ከአርከበ ሱቅ ከሚገዛው በቀር) ለተቀበሉ ሁሉ የሚሰጥ ነው? የሚል ጥያቄ በየወቅቱ ይነሳል። ብዙ ባለምስክር ወረቀቶች ግራና ቀኝ ማየት የማይደፍሩ፣ እውነት የማይመሰክሩ የተሻለ ደሞዝ፣ ዝናና ክብር የሚያማልላቸው ስምና የትምህርት ደረጃቸውን ለመተዳደርያ ብቻ የሚያደርጉ ሆነዋል የሚል ወቀሳም እየበዛ ነው። እንዲያውም ‘መማር እንደዚህ ከሆነ’ የሚሉ የተሳሳተ አቅጣጫ የሚይዙ ሰዎች የመጡበትም አንደኛው ምክንያት ይኸው ነው። ይህ ማለት የተማሩ ሰዎች ሁሉ እንደ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፖለቲከኛ ለምን አልሆኑም ማለት አይደለም። ፖለቲካ ሳይንስ ነው ካልን ሰዎች ባልተካኑበት ቢቀድሱ ከመዕመናን ጆሮ ላይደርሱ ቢደርሱም እንደሳቸው ተደናግረው ሊያደናግሩ ይችላሉ። ይሁን እንጂ ነፃነት፣ መብትና ፍትህን መፈለግ የፖለቲካ ጠበብትነትን አይሻም፣ ሰው መሆንን ብቻ እንጂ። በተለያየ ሙያ ከሰለጠኑ ምሁራንም በትንሹ የሚጠበቀው ለመብትና ለነፃነት ቀናዒ እንዲሆኑ ነው።

ለመጻፍ መነሳሳቴን የፈጠረው ዛሬ ያነበብኩት በኢያሱ ለበኑ የተጻፈው Ethiopia: The Tale of Two Minister D’états የሚለው ጽሁፍ ነው። ይህ በእንግሊዝኛ የተጻፈው ጦማር ሁለት የአባትና የልጅ ያህል ልዩነት ያላቸውን ሚኒስትር ደኤታዎችን የሚያነጻጽርና አንደኛው በጣም የተማሩና አዛውንቱ ዶር ተቀዳ አለሙ ከሁሉም አገዛዞች ጋር እጅና ጓንት ሆነው የሚሄዱ ለሁሉም አገልጋይ ስለመሆናቸውና ሌላኛው ኤርምያስ (ወያኔ ሲገባ እድሜው ሃያ ያልገባ) ከመንግስት ጋር ሆኜ አገር መግደልና ሕዝብ መበደል ይብቃኝ ብለው አለቃቸውን ስለነበረን ጊዜ አመሰግናለሁ በሚል ደብዳቤ ወደ እውነት ለመጠጋት ምቾትንና ስልጣንን ጥለው ስለሄዱት ግለሰብ የሚመለከተው ነው። ወያኔ ሲገባ የነበረው ሞቅ ሞቅና በደርግ ላይ የነበረው አፍላ ጥላቻ የልጅነት መልቀቂያ ፈተና ተቀብሎ ወደ ጉርምስና የሚሸጋገር እንደ ኤርምያስ ላለ ወጣት የሚመርጠውን መንገድ መሞገት አሰቸጋሪ ነው። ወደ ጉልምስና ሲሻገር ግን እውነት ማየት ከተሳነው ችግር እንዳለ ያመለክታልና ኤርምያስም እውነትን አሻግሬ ተመለከትኩ ያለሁበትንም ጠላሁ ብለው የራሣቸውን እድል በራሳቸው ወሰኑ። ዶክተሩ ደግሞ ወደ አዲስ የመንግስት የስልጣን ግምጃ ቤት እየተቀዱና በቀላሉ እየተደባለቁ ስለመኖራቸው የሚያነጻጽረው ጦማር ጊዜያችንን ገላጭና ጥያቄ አጫሪም ነው።

የኢያሱ ለበኑ ጦማር በኦሪየንታሊዝም ጽሁፉና በሌሎችም ስራዎቹ ታዋቂ የሆነው ፕሮፌሰር ኤድዋርድ ሰይድን (1935 – 2003) ሃሳብ የሚጋራ ይመስለኛል። ፕሮፌሰሩ በአንድ ጽሁፉ …

“Nothing in my view is more reprehensible than those habits of mind in the intellectual that induce avoidance, that characteristic turning away from a difficult and principled position which you know to be the right one, but which you decide not to take. You do not want to appear too political; you are afraid of seeming controversial; you need the approval of a boss or an authority figure; you want to keep a reputation for being balanced, objective, moderate; your hope is to be asked back, to consult, to be on a board or prestigious committee, and so to remain within the responsible mainstream; someday you hope to get an honorary degree, a big prize, perhaps even an ambassadorship. For an intellectual these habits of mind are corrupting par excellence. If anything can denature, neutralize, and finally kill a passionate intellectual life it is the internalization of such habits.” (Edward Said, 1994, Representations of the Intellectual, pp.100-101)

ሃሳቡ ወደ አማርኛ ሲመለስ “… እንደ እኔ አመለካከት በመርህ ላይ የተመሰረተ አስቸጋሪ ግን ትክክለኛ አቋም ከመያዝ ሆን ብለው የሚሸሹ ምሁራንን ያህል አሳፋሪ ነገር የለም። ፖለቲከኛ ላለመምሰል ተሟጋችና አስቸጋሪ ላለመባል የአለቃን ወይም የበላይን መልካም ፈቃድ ብቻ በመጠበቅ ሚዛናዊና ተጨባጭ ሁኔታን ያገናዘቡ ናቸው በመባል በትላልቅ ስፍራ ለመጋበዝ አማካሪ ለመሆን የከፍተኛ ኮሚቴዎች አባል ለመሆንና በትላልቅ የቦርድ ስብሰባዎች ለመገኘት፣  ከሃላፊዎች ተርታ ለመቆም እናም አንድ ቀን የክብር ዲግሪ ለማግኘት፣ ትላልቅ ሽልማቶች ለመሸለም ምናልባትም አምባሰደር ለመሆን ይጥራሉ። ይህ አይነቱ ባህርይ ምሁርን ከምንም ነገር በላይ የሚያረክስና እርባናቢስ አድርጎ የሚያከሽፍ ልማድ ነው…”

በርካቶቻችን በዘልማድ ለዚህ አይነት ሰዎች ሞገስና ክብር መስጠታችን ደግሞ እጅጉን ጎድቶናል። ስለ ጨዋነትና ጥሩ ሰውነት መገለጫው ዝምተኛነትና ዳተኛነት ነው። ‘እሳቸው ዝም ነው… አይቶ እንዳላየ ናቸው… ሰው ቀና ብለው አያዩም… ከሁሉም ጋር አብረው ይሄዳሉ…. ምንም ውስጥ የሉበትም.. ኑሮአቸውን ብቻ ነው የሚኖሩት…ወዘተ። በሚሉ አባባሎች ውስጥ መልካም ነገሮች ቢኖሩም አንኳ እነዚሀ የባህርይ መገለጫዎች ለመብትና ነፃነት ተቆርቋሪ የሆኑትን ፍትህ ፈላጊዎች አሳናሽ ናቸው። ስለዚህ የመብት ታጋዮችን ‘ነገረኞች’ “አሳዳሚዎች’ ያስብላል። በነኚህ ‘ነገረኞችና አሳዳሚዎች’ ጥንካሬና ትግል ሳቢያ የሚመጣውን ጥቅም ግን ቀድመው የሚቋደሱት ምንም ውስጥ የሌሉበት ‘ጨዋዎቹ’ ናቸው። ጉዳት ቢኖረው መስቀል ተሸካሚዎቹ ‘ነገረኞቹና’ ‘አሳዳሚዎቹ’ ይሆኑና “ሳይቸግራቸው… አርፈው ቢቀመጡ ኖሮ” ተብለው ይወገዛሉ።

ለዚህም ይሆናል ዛሬ በሀገርቤትም ይሁን በውጪው አለም በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ኢትዮጵያዊ ‘ምሁራን’ በደልንና መብት ረገጣን አይቶ እንዳላየ ሲያልፉ የምንመለከተው። ከዚያ የሚብሰው ደግሞ የመፍትሄ አካል ከመሆን ይልቅ እንደ ክህሎታቸው የሚሞክሩትን ሁሉ ማብጠልጠል ማዋረድና መመፃደቅን እንደ ትልቅ ነገር በመቁጠር ሲኮፈሱ የምናያቸውም የበዙበት ምክንያትም ይህ ዳተኝነት ምንም ዋጋ ስለማያስከፍልም ነው። ከዚህ አይነት ስነምግባር በመቆጠብ እውቀታቸውን ቢፈትሹና የሚተርፋቸውን ቢያካፍሉ ከሌሎች ጋርም ቢመክሩ በስሜትና ፍላጎት ብቻ ሳይሆን በእውቀት፣ በአመክንዮና በብልህነት ወደፊት እንድንገሰግስ እገዛቸውን ቢለግሱ የተሻለ ይሆናል። መድረክ ላይ ወጥቶ መናገር ወይም ጽሁፍ መጻፍ ብቻ ሳይሆን ተቋማትን ማጠናከር፣ አዳዲስና ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎችን መፍጠር፣ የተራራቀው እንዲቀራረብ የከረረው እንዲረግብ ማድረግ፣ የእውቀት ፍላጎትን በማሳደግ የመረጃ ተፋሰስን በማስፋት ምሁራዊ አስተዋጽኦ የሚደረግባቸውን መንገዶች መፈለግና ሃሳብ ማቅረብ ድርሻቸው ነው እንዲያውም የዜግነት ግዴታቸው ጭምር ነው። ምሁራን የሃሳብ ልዩነቶቻቸውን አንደጠላትነት ሲመለከቱ ክርክራቸውን ወደ ተራ ስድብነት ሲቀይሩት ቂመኝነት የዛሬውን አይናቸውን ሲጋርደው ግን የጥፋት ጥፋት ይሆናል። ሃሳቤን በዚሁ የሃርቫርድ ፕሮፌሰር ኤድዋርድ ሰይድ ጽሁፍ ላጠቃልለው ፈቀድኩ እንዲህ ይላል…

“And finally a word about the mode of intellectual intervention. The intellectual does not climb a mountain or pulpit and declaim from the heights. Obviously you want to speak your piece where it can be heard best; and also you want it represented in such a way as to influence with an ongoing and actual process, for instance, the cause of peace and justice. Yes, the intellectual’s voice is lonely, but it has resonance only because it associates itself freely with the reality of a movement, the aspirations of a people, and the common pursuit of a shared ideal.”

ወደ አማርኛ ሲመለስ “በመጨረሻም ስለምሁራን አስተዋጽኦ እንዲህ እላለሁ። ምሁር ከተራራው ጫፍ ወጥቶ ወይም ከመድረክ ላይ ቆሞ ድል አድርጌአለሁ አይልም። ይልቁንም ሃሳብህን አድማጮችህን በሚገባ ልትደርስበት በምትችለው መንገድ ተናገር። ንግግርህም እየሆነ ባለ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ ይሁን ለምሳሌ ስለ ሰላምና ፍትህ። አዎ የምሁር ድምጽ ብቸኛ ሊሆን ቢችልም እንኳ ስለ ሕዝቡ ፍላጎት ስለ ትግሉ ስለጋራ ግብና የጋራ ስምምነት እስከሆነ ድረስ እንደ ገደልማሚቶ ያስተጋባል።” ይለናል።

ምሁራን እውቀትና ብልህነታቸውን፤ የሕዝባቸውን የነጻነትና የፍትህ ጥማት አገናዝበው ከያሉበት የሚያሰሙት ድምፅ የሚያንኳኩት በር እንደ ገደልማሚቶ እያስተጋባ የሚያስተባብረን ወደ ነጻነትና አንድነት የምናደርገውን ጎዳና የሚያሳምርልን በፍጥነትም የሚያደርሰን ይሆናልና ለዚህ ቢተጉልን በልባችን ውስጥ ሀውልት እንሰራላቸው ዘንድ እውነት ነው። ጠብታ ተጠራቅሞ ጎርፍ ጎርፍም ጎልብቶ ወንዝ እንዲሆን ሁሉ ከያላችሁበት ድምጻችሁ ይሰማ ክፋትን ጠራርጎ የሚወስድ ሕዝባዊ አመጽም ይወለዳል።

ነፃነትና ሰላም ፍትህና ብልጽግና ለኢትዮጵያችን ይሁን
biyadegelgne@hotmail.com

Friday, August 1, 2014

የህወሃት ሽብር መቆም አለበት!

August1/2014
ዛሬ በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለ አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎችን በፖለቲካ አመለካከታቸው፣ መንግስት በመተቸታቸው በግልጽ በመጻፋቸውና በአደባባይ በመናገራቸው ከዚህም አልፎ በጥርጣሬ በተለይም በብሄረሰብ ማንነታቸው እያሳደደ የሚያፍን የሚያሰቃይና የሚገል የሽብር ተቋም ካለ ወያኔ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መሬት ላይ ሰላማዊ ዜጎችን ኢላማ ያደረገ የተቃውሞ ሃይል በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ከወያኔ ውጪ አንዳች ሃይል የለም።
አፋኙ የወያኔ ስርአት በተለየም የህዝቡን ሀብትና ንብረት እየዘረፉ የሚቀማጠሉት የህወሃት መሪዎችና ሎሌዎቻቸው የተቃውሞ ድምጽ በሰሙ ቁጥር እንደሚሸበሩና እንቅልፍ አጥተው እንደሚያድሩ ይታወቃል። አፍነውና ዘርፈው ገለው የሚገዙት ህዝብ ግፍ በዛብኝ ብሎ በተናገረ ቁጥር የሚሸበሩት እነሱ ብቻ እንጂ ህዝቡ አይደለም።
በኢትዮጵያ ምድር ያለው አሸባሪ ወያኔ ብቻ መሆኑን ሺ ምሳሌዎችን ጠቅሶ ማስረዳት ይቻላል። ሶስት አመት ሙሉ የሰላም እጃቸውን እየዘረጉ ከልመና ባልተለየ ሁኔታ መብታቸውን የጠየቁና ድምጻችን ይሰማ ያሉት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማንንም ዜጋ አላሸበሩም። የተገላቢጦሽ እነሱ አሸባሪ ተብለው የግፍ ሰቆቃ ይፈጸምባቸዋል። ጋዜጠኞችና ጦማሪዎቹ መንግስት ያወጣውን ህግ እንዲያከብር ስለጠየቁ በአደባባይ ስለጻፉ ግፍ ይፈጸምባቸዋል። እነሱ ያሸበሩት ሀገርና ህዝብ የለም። ከመንገድ ላይ ጎትተው እንደ እባብ ቀጥቅጠውና ፈነካክተው በማግስቱ ፍርድ ቤት ያቀረቧት ወየንሸት ሞላ የተባለች ባለ ተስፋ ወጣት የወያኔ አረመኔዎች በሙስሊሙ ህዝብ ላይ የሚሰሩትን ጭፍጨፋ እግር ጥሏት ከማየትና ከመታዘብ ውጪ ያሸበረችው ሰው፣ ሀገር የለም። በየወህኒ ቤቱ እና አፈና ጣቢያው ታስረው የሚቀጠቀጡት የኦሮሞ ልጆች ለጥያቄያቸው መልስ ሲጠብቁ ከመጨፍጨፍ ያለፈ የፈጸሙት እብሪት የለም። በየክልሉ ቀና ብለህ ባለስልጣን ተናገርክ፣ ጥያቄ ጠየቅክ፣ ባለስልጣን ደፈርክ፣ ተሰብስበህ አየንህ ወዘተ እየተባለ የሚገረፈው እንደ እንስሳ እየተገደለ የሚጣለው ገበሬ የሰራው ወንጀል የለም። አሸባሪም አይደለም! በየቦታው ቦንብ እየቀበረ አፈንድቶ ንጹሃንን ገድሎ ሊያፈነዱ ሲሉ ፈንድቶባቸው ራሳቸውን ገደሉ ብሎ በአደባባይ የሚሳለቀው አሸባሪው ህወሃት እንጂ ንጹሃኑ አይደለም።
የኛ መሪ አንዳርጋቸው ከልጅነት እድሜው ጀምሮ ራሱን ለህዝብ ነጻነት የሰጠ አርበኛ እንጂ አሸባሪ አይደለም። በተመሳሳይ ውንብድና ከጎረቤት ሀገር ድረስ በአለም አቀፍ የወረበሎች ውንብድና መንገድ ወያኔ እያፈነ የገደላቸው አሮሞዎችና፣ ሱማሌዎች፣ አኙዋኮች፣ አማሮችና ሌሎችም ነጻነት ከመፈለግ ውጪ ያሸበሩት ህዝብና ሀገር የለም።
በኢትዮጵያ ምድር የነጻነት ድምጽና ኮሽታ በሰማ ቁጥር የሚሸበረው ህወሃትና በለሟሎች ብቻ ናቸው። ይህ የነጻነት ድምጽ ደግሞ እየጎላ መሄዱ የማይቀር ነውና ወያኔ ሰፈር ሽብር ይሆናል።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወጣት፣ ሴት፣ ሽማግሌ፣ ገበሬ እና በየቦታው ያላችሁ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ! አሸባሪህ ወያኔና ወያኔ ብቻ መሆኑን አውቀህ በገዛ ሀገርህ ላይ ነጻነት በተመኘህና በጠየቅህ ጊዜ ሁሉ ለሽብር ጥቃቱ ኢላማ ያደረጉህን ወያኔ ተባብረን ከላያችን ለማውረድ ተነስ! በያለህበት እምቢ በል! ለወያኔ የሚጠቅም የመሰለህን ነገር ሁሉ አታድርግ! አትተባበር! ሸቀጣቸውን አትግዛ! ወያኔዎችን ከማህበራዊ ሂወትህ አግል! የቻልክ ሁሉ ደግሞ የነጻነት አርበኞችን ዛሬ ነገ ሳትል አሁን ተቀላቀል!!! ነጻነታችን ያለው በእጃችን ላይ መሆኑን አትዘንጋ። ግንቦት 7 ሁልጊዜም ከመቼውም ጠንክሮ ከጎንህ ነው።
የወያኔን ሽብር በተባበረ ሃይል እናቁመው!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ ቡድን በሰሜን ጎንደር የዐማራ ሕዝብ ላይ የፈጸመው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ወንጀል

August 1/2014
end genocide now


የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት አቅዶ ሲነሳ፣ የግቡ መረማመጃ ያደረገው የኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ ተቋሞችን፣ ኃይማኖቶችን፣ ዕሴቶችን እና በተለይም «ዐማራ» የተሰኘውን ነገድ ተወላጆች ነጥሎ ማጥፋት የሚል ሥልት በመከተል እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሠረት የጥፋቱ ቅድሚያ ዒላማ ያደረገው ለትግራይ ሕዝብ በችግሩ ጊዜ ደራሽ እና የተራበ አንጀታቸውን ዳሳሽ በሆነው የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የጠለምትና የሠቲት ወረዳዎች ሕዝብ ላይ ነው። ወያኔ በእነዚህ የትግሬ አዋሣኝ ወረዳዎች ሕዝብ ላይ የጥፋት ክንዱን የዘረጋው በሦስት መሠረታዊ ምክንያቶች ነው።
የመጀመሪያውና ታላቁ ምክንያት የእነዚህ ወረዳዎች ሕዝብ ዐማራ በመሆኑ እና የትግራይ አዋሳኝ ስለሆነ የትግራይን ታሪክ ክፉውንም ሆነ ደጉን ጠንቅቆ የሚያውቅ በመሆኑ ነው። በዚህም ምክንያት የዚያ አካባቢ ሕዝብ የትግሬ-ወያኔ ለተነሳለት ፀረ-ኢትዮጵያ እና ፀረ-ዐማራ እንቅስቃሴ የማይተኛ እንደሆነ ስለሚረዳ ይህን ሕዝብ ብቻውን አቁሞ ማጥፋት ለወደፊቱ ግሥጋሴው ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው በማመን የችግር ጊዜ ደራሻቸውን ሕዝብ ያለርኅራኄ ጨፍጭፈውታል።
ሁለተኛው ምክንያት «ታላቋን ትግራይ» ለመመሥረት ባላቸው ዕቅድ ለውጭ ግንኙነታቸው መውጫ መግቢያ እንዲሆናቸው ከሱዳን ጋር የሚዋሰኑትን እነዚህን ወረዳዎች ወደ ትግራይ ማጠቃለል ስለነበረባቸው ነው። ሆኖም የአካባቢው ሕዝብ «ነገዳችን ዐማራ፣ ጠቅላይ ግዛታችን ጎንደር ነው።» እያለ እንዳያስቸግራቸው በቅድሚያ ነባር ነዋሪውን ጎንደሬ አጥፍቶ በሠፋሪ ትግሬ ማስያዝ ለዓላማቸው ሥምረት ያገለግላል ብለው በማመናቸው ነው።
ሦስተኛው ምክንያት የሠቲት፣ የወልቃይት፣ የጠገዴ፤ እና የጠለምት ወረዳዎች ለሠፋፊ የእርሻ በተለይም ለጥጥ፣ ለሰሊጥ፣ ለማሽላ፤ ለዱር ሙጫ፣ ወዘተርፈ ምርት የሚያመች የለም እና ሠፊ መሬት ባለቤት በመሆኑ ነው። ስለዚህ የእነዚህ የሚያጓጉ የተፈጥሮ ኃብቶች ተጠቃሚ ለመሆን ተቀናቃኙን የጥንት ነዋሪውን ሕዝብ የግድ ማጥፋት አለብን ብለው በማመናቸው ነው።
ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) በዐማራ ነገድ አባሎች ላይ የተቀነባበረ የዘር ማጽዳት ወንጀል መፈጸም የጀመረው  ድርጅቱ ገና «ተጋድሎ  ሓርነት ሕዝቢ ትግራይ (ተሓሕት)» ተብሎ ይጠራበት ከነበረበረበት የጨቅላነቱ ዘመን ጀምሮ እንደሆነ የድርጅቱ ታሪክ ያስረዳል። በተለይም የትግራይ አዋሣኝ በሆኑት የሰሜን ጎንደር ታሪካዊ አካሎች በነበሩት ወረዳዎች ነዋሪ የሆኑ ዐማራዎችን ለማጥፋት ተሓሕት-ሕወሓት ፕሮግራም ነድፎ መንቀሳቀስ የጀመረው ከ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነ የድርጅቱ ነባር አባሎች ያስረዳሉ። የሰሜን ጎንደር ለም እና ድንግል ወረዳዎች የሚባሉት፦ ወልቃይት፣ ሠቲት፣ ላይ እና ታች አርማጭሆ፣ ጠገዴ እና ጠለምት ናቸው። በሕወሓት ታሪክ ውስጥ «የዲማ ኮንፈረንስ» በመባል የሚታወቀው እና ከ፻፶ (አንድ መቶ ሃምሣ) ያላነሱ አባላቱ ተካፋይ በሆኑበት በየካቲት ወር ፲፱፻፷፰ ዓ.ም. «ጸደቀ» የተባለው ፕሮግራም ወልቃይትን፣ ሠቲት፣ ጠገዴን እና ጠለምትን ከዐማራ በማጽዳት ወረዳዎቹን ወደ ትግራይ መጠቃለል እንዳለባቸው ያስገነዝባል።
t1ይህ ፕሮግራም ዐማራውን ከማውገዝ አልፎ፣ በትግሬ ደመኛ ጠላትነት በመፈረጅ በግልፅ ቋንቋ «የትግላችን ዓላማ ፀረ-የዐማራ ብሔራዊ ጭቆና ነው» ይላል።ከዚህ በተጨማሪም ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ ብሔራዊ ጥቅም እና የሕዝቧን አንድነት በእጅጉ የሚጎዳ ብቻ ሳይሆን፣ አገሪቱ እንደአገር እንዳትቀጥል የሚያደርግ ዓላማ ያለው መሆኑ በፕሮግራሙ መሠረት ባለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት በመፈጸም ላይ ያሉት ተግባሮች ሁነኛ እማኖኞችና ነቃሾች ናቸው።
በ፲፱፻፷፰ ዓ.ም. የጸደቀውን የድርጅቱን ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ አርከበ ዕቁባይ «ወደ ታላቋ ትግራይ ረፐብሊክ ሊካተቱ ይገባል» የተባሉትን ከጎንደር ወልቃይትን፣ ጠገዴን፣ ጠለምትን፣ ሠቲት፤ እንዲሁም ከወሎ ክፍለሀገር ደግሞ ራያና ቆቦን፣ አላማጣን፣ ወልድያን፣ ጨምሮ እስከ አሸንጌ ኃይቅ ድረስ ያሉትን ሥፍራዎች የሚያካትት ካርታ አዘጋጀ (ተያያዥ ካርታዎችን ከ፩-፬ ይመልከቱ)። በዚህ ሁኔታ ከኢትዮጵያ ተገንጥላ የምትመሠረተው «የትግራይ ረፐብሊክ» ከሱዳን ጋር የሚያገናኛት የመሬት አካል እንድታገኝ ሆነ። በዚህም መሠረት በ፲፱፻፷፱ ዓ.ም. ተሓሕት-ሕውሓት ያለ የሌለ ኃይሉን ከጎንደር ክፍለ ሀገር ነጥቆ ወደ ትግራይ ባካለላቸው ጥንተ-ነዋሪ የዐማራ ሕዝብ ላይ የጥፋት ክንዱን አነሳ።
t2
ካርታ ፩፦ የኢትዮጵያ አስተዳደራዊ ካርታ (እስከ ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ድረስ)
ከሁሉ አስቀድሞ መታወቅ ያለበት ጉዳይ የትግሬ-ወያኔ ዐማራን ማጥፋት የጀመረው ኢትዮጵያዊነትን በሁለንተናዊ መልኩ ከትግራይ ሕዝብ አዕምሮ እንዲጠፋ ካደረገ እና የዓላማው ተቃዋሚ የሆኑ የራሱን ነገድ አባሎች ከትግራይ ምድር ካጸዳ በኋላ ነው። ይህ በዚህ እንዳለ በ፲፱፻፷፱ ዓ.ም. የተሓሕት-ሕወሓት አመራር አባላት የሆኑት ስብሐት ነጋ፣ አረጋዊ በርሄ፣ ዐባይ ፀሐዬ፣ ሥዩም መሥፍን፣ ስዬ አብርሃ እና አውአሎም ወልዱ «በትግራይ ክፍለሀገር ውስጥ የሚኖሩ ዐማሮች፣ ኦሮሞዎች እና የሌሎችም የኢትዮጵያ ነገዶች ተወላጆች ከትግራይ መሬት ለቀው ይውጡ፤ ትግራይ የትግሬዎች ብቻ ናት!» ብለው ሲወስኑ በወቅቱ ይህን ውሣኔ ተቃውመው የቆሙት ግደይ ዘርዓፅዮን እና ዶክተር አታክልቲ ቀጸላ ብቻ እንደነበሩ ስለሁኔታው የሚያውቁት አቶ ገብረመድህን አርአያ በተለያዩ አጋጣሚዎች አሣውቀዋል። ያ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኖ፣ ዛሬ ትግሬዎች ትግራይን በብቸኝነት፣ ቀሪዋን ኢትዮጵያ ደግሞ በገዥነት ተቆጣጥረው ይገኛሉ።
t3
ካርታ ፪፦ አዲሱ የትግራይ «ክልል»
ተሓሕት-ሕወሓት  የሰሜን ጎንደር አካል በሆኑ ወረዳዎች ነዋሪ በሆኑ ዐማሮች ላይ የጥፋት ተልዕኮውን ለመፈጸም  እንዲሁ ዘሎ ወደ አካባቢው አልገባም። ዓላማውን ለማስፈጸም የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ነበረበት። ለዚህም ሁኔታዎች እስኪመቻቸቹ ድረስ ጊዜ መግዛት ነበረበት። አንደኛ፥ ጠለምት፣ ወልቃይት እና ጠገዴ በኢሕአፓ ተዋጊዎች የተያዘ ስለነበር፣ አቅሙ እስኪጎለብት እና ኢሕአፓን መጓባት እስኪችል መጠበቅ ግድ በማለቱ፤ ሁለተኛ፥ በወቅቱ የአካባቢው ሕዝብ እንደማይቀበለው ያውቅ ስለነበር፣ ሕዝቡን አሸማቆ እና ረግጦ መቆጣጠር የሚችልበት አቅም መፍጠር ስለነበረበት፤ እንዲሁም ከሁሉም በላይ የአካባቢውን ሕዝብ ማንነት የሚያውቅ ባንዳ መልምሎ ማሰልጠን ጊዜ የሚጠይቁ በመሆናቸው ነበር። ይኽም ሆኖ፣ ተሓሕት-ሕወሓት በተጠቀሱት ወረዳዎች  በመሽሎክሎክ አሻራውን ከማስቀመጥ አልቦዘነም።
t4
ካርታ ፫፦ የትግራይ «ክልል» ከጎንደር የወሰዳቸው ወረዳዎች
t5
ካርታ ፬፦ የትግራይ «ክልል» ከወሎ የወሰዳቸው ወረዳዎች
በ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ላይ ለተሓሕት-ሕወሓት ዓላማ መሳካት የሚያመች አጋጣሚ ተፈጠረ። ይኸውም በሻዕቢያ እና በጀበሓ፣ እንዲሁም በኢሕአፓ እና በተሓሕት መካከል የተደረጉት የጦፉ ውጊያዎች ነበሩ። በጦርነቱም ሻዕቢያ እና ተሓሕት-ሕወሓት የድሉ ባለቤቶች ሆኑ። ጀብሓ እና ኢሕአፓ ተበታትነው የትጥቅ ወረዳቸውን ለቀው በቡድን እና በተናጠል ወዳፈተታቸው አካባቢ አመሩ። ወረዳዎቹን ሁለቱ አጥቂ ኃይሎች ተቆጣጠሯቸው። ከሁሉም በላይ የኢሕአፓ ተዋጊ የነበሩት፦ ያሬድ ጥበቡ፣ ታምራት ላይኔ፣ በረከት ስምዖን፣ አዲሱ ለገሠ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ ታደሰ ጥንቅሹ፣ ሕላዌ ዮሴፍ፣ ካሣ ተክለብርሃን እና በአጠቃላይ በቁጥር ፴፯ (ሠላሣ ሰባት) የሚሆኑት ለተሓሕት-ሕወሓት በሎሌነት አደሩ። እኒህ ቀደም ሲል ከተሓሕት-ሕወሓት ጋር ግንኙነት መሥርተው ስለነበር፣ የኢሕአፓን ተዋጊ ኃይል እንዲጠቃ የባንዳነት ሥራ ሠሩ። በዚህም የተነሳ የኢሕአፓ ተዋጊ ኃይል በተሓሕት ተገደለ፣ ተማረከ፣ ዕድለኛ የሆነውም በስደት ሱዳን ገባ። ይህ ሁኔታ ለተሓሕት-ሕወሓት ዐማራን የማጥፋት ተልዕኮው ሠፊ በር ከፈተለት።
በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ሠቲት እና ጠለምት ዐማራዎች ላይ የዘር ማጥፋት  ወንጀል እንዲፈጸም አመራር የሰጡ የተሓሕት-ሕዋሓት መሪዎች፦
(1) ስብሐት ነጋ (በወቅቱ የተሓሕት-ሕወሓት ሊቀመንበር የነበረ)፣
(2) መለስ ዜናዊ (የቀድሞው የትግሬ-ወያኔ መሪ፣ በ፪ሺህ፭ ዓ.ም. በሞት የተለየ)፣
(3) አረጋዊ በርሄ (ዶክተር፣ በስደት ሆላንድ የሚኖር)፣
(4) ዐባይ ፀሐዬ፣
(5) ሥዩም መሥፍን፣
(6) ግደይ ዘርዓጽዮን (በስደት ኖርዌይ የሚኖር) ናቸው።
መመሪያውን በማስፈጸም ጥቃቱን በአካል ያስፈጸሙት ደግሞ ሥዬ አብርሃ (በአሜሪካን አገር ይኖራል)፣ አርከበ ዕቁባይ፣ ፃድቃን ገብረተንሣይ፣ ዘርዓይ አስገዶም እና አውአሎም ወልዱ መሆናቸውን የድርጊቱን ሂደት በተጨባጭ የሚያውቁት አቶ ገብረመድኅን አርአያ ያረጋግጣሉ። ሁሉንም የሰሜን ጎንደር ዐማራዎች የጭፍጨፋ ዘመቻ በበላይነት ይመራው እና ያስተባብረው የነበረው ስብሐት ነጋ እንደነበር የዐይን እማኞች የነበሩ በተለያየ ጊዜ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
ሕወሓት በወልቃይት፣ በጠገዴ፣ በጠለምት እና በአርማጨሆ የዐማራ ተወላጆች ላይ የጥቃት ዒላማውን ሲያነጣጥር፣ መንገድ መሪ እና መረጃ አቀባይ በመሆን የጥፋቱን ከፍተኛ ድርሻ የሚወስደው በአባቱ የወልቃይት-ጠገዴ፣ በእናቱ ደግሞ የሽሬ ተወላጅ የሆነው የ«ሪጅን አንድ» የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው በዓለም ስሙ «ዮሴፍ ዘለለው» (በበረሃ ስሙ ደግሞ «መኮንን ዘለለው») በመባል የሚታወቀው ግለሰብ ነው። መኮንን ዘለለው በአሁኑ ሰዓት በስደት በአሜሪካን አገር ይኖራል። ለመኮንን ዘለለው ከሕወሓት የተሰጠው ተልዕኮ፦ በሕዝቡ መሃል እየተዘዋወረ ሠቲት፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት እና አጎራባች ወረዳዎች የትግሬ ግዛት አካል መሆናቸውን፣ ሕዝቡም ትግሬ መሆኑን በመስበክ ማሣመን፣ የሚያምኑትን መመልመል፤ «ትግሬ አይደለንም» ያሉትን እና አጥብቀው የተከራከሩትን እየመዘገበ ለፈዳያን (ገዳይ ቡድኖች) ስማቸውን በማስረከብ ማስገደል ነበር። በዚህም መሠረት መኮንን ዘለለው ከላይ በተጠቀሱት ወረዳዎች እየተዘዋወረ፦ «ይህ መሬት የትግራይ መሬት ነው። እናንተም ከእንግዲህ ወዲያ የሰሜን ጎንደር ዐማራ ተወላጆች አይደላችሁም። በመሬቱ እንኖራለን ካላችሁ ትግሬዎች መሆናችሁን አምናችሁ ተቀበሉ። እኛ ትግሬ አይደለንም፣ መሬቱም የትግራይ አይደለም የምትሉ ካላችሁ ደግሞ፣ የሕወሓትን ውሳኔ ጠብቁ።» የሚል ማስጠንቀቂያ ይሰጥ ነበር። ሆኖም ሕዝቡ ያላዳች ማመንታት የሰጠው መልስ «እኛ ዐማራዎች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም። የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የጠለምት፣ እና የሠቲት ወረዳዎችም የትግራይ አካል ሆነው አያውቁም።» የሚል ነበር። «የሁለቱ ክፍለ ሀገሮች ማለትም፦ የትግራይ እና የጎንደር (ቤጌምድርና ሰሜን) የተፈጥሮ ወሰናቸው ተከዜ ነው። የትግራይ ግዛት ተከዜን ተሻግሮ አያውቅም።» በማለት ታሪክ እያጣቀሱ ሞገቱት።
መኮንን ዘለለው ከሕዝቡ ያገኘውን ምላሽ ለአለቆቹ ሪፖርት አቀረበ። ሪፖርቱ ተልዕኮው ያልሰመረለት መሆኑን የሚያሳይ በመሆኑ፣ በወቅቱ የሕዋሓት ሊቀመንበር የነበረው ስብሐት ነጋ በብስጭት በመኮንን ላይ የስድብ ናዳውን በማውረድ ከሪጅን አንድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊነቱ እንዲነሳ አደረገው። ሕወሓቶች መኮንን ዘለለውን ባያስሩትም የተለያዩ ሥቃዮችን እንዲቀበል አደረጉት። ሕወሓትም በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ ቂም ቋጠረ። ዕውነትን ጋሻ፣ ታሪክን ማጣቀሻ አድርገው የሞገቱትን ሰዎች እየለቀሙ አድነው ጨፈጨፏቸው። በዚህም መሠረት የትግሬ-ወያኔ ከ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ጀምሮ ተከዜን ተሻግሮ በቅድሚያ ከጨፈጨፋቸው የአገር ዘብ የነበሩ የወልቃይት-ጠገዴ የዐማራ ተወላጆች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።
1) ግራዝማች ወልዴ የኔሁን፣
2) ቄስ በለጠው ተስፋይ፣
3) ቄስ ትዕዛዙ ቀለመወርቅ፣
4) ቄስ አለነ ቀለመወርቅ፣
5) አቶ ማሞ ዘውዴ፣
6) አቶ እንደሻው ታፈረ፣
7) አቶ አያሌው ሰሙ፣
8) አቶ በርሄ ጎይቶም፣
9) አቶ ሐጎስ ኃይሉ፣
10) አቶ  ልጃለም ታዬ፣
11) ወጣት ግዛቸው ዳኜው፣
12) ወጣት አዲስይ ልጃለም፣
13) ወጣት ደረጀ አንጋው፣
14) ወጣት ዋኘው መንበሩ፣
15) ወጣት ሕይዎት አብርሃ፣
16) ወጣት ታደለ አዛናው፣ እና
17) ወጣት ማሞ አጀበ ናቸው።
ከዚያን ወቅት ወዲህ የትግሬ-ወያኔ በአካባቢው ይኖሩ በነበሩ የዐማራ ተወላጆች ላይ በተከታታይ ከፈፀማቸው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ወንጀሎች መካከል ለአብነት ለመጥቀስ ያህል፦
1) በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. «ርዋሳ» የተባለውን እና ከ፭፻ (አምሥት መቶ) በላይ ቤቶች የነበሩበትን የገበሬ መንደር አቃጥለው የትግሬ ተወላጆችን አሠፈሩበት። በዚህ ቀበሌ ቤት ንብረታቸው ተቃጥሎ ለከፍተኛ ችግር ከተጋለጡት መካከል አቶ ጫቅሉ አብርሃ፣ አቶ አብርሃ ሣህሉ፣ ወይዘሮ ስንዱ ተስፋይ፣ አቶ ዋኜው ይገኙበታል።
2) ከ፲፱፻፹፰ እስከ በ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. በነበረው ጊዜ ከ፫ (ሦሥት) ሺህ በላይ ጥማድ በሬዎች ባለቤቶች የነበሩ ገበሬዎችን ገድለው እና አሰድደው የትግሬን ገበሬ አስፍረውበታል።
3) ከ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. ጀምሮ በማይ ኅርገጽ፣ በቤት ሞሎ፣ በማይ ጋባ፣ በማይ ደሌ፣ በአንድ አይቀዳሽ፣ በእምባ ጋላይ፣ በትርካን፣ በቃሌማ፣ በእጣኖ፣ በመጉዕ፣ ወዘተርፈ ይኖሩ የነበሩ ነባር የዐማራ ነገድ ተወላጆችን አባርረው የትግሬ ተወላጆችን አስፍረዋል። በአጠቃላይ የትግሬ-ወያኔዎች ሰሜን ጎንደርን ከወረሩበት ከ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ጀምሮ በነበሩት ፴፬ (ሠላሣ አራት) ዓመቶች በአካባቢው ለም መሬቶች ከ፫፻(ሦሥት መቶ) ሺህ በላይ የሚሆኑ የትግሬ ተወላጆችን አስፍረዋል።
ኃብት እና ንብረቶቻቸውን የተነጠቁ፣ እንዲሁም እንዲወድምባቸው የተደረጉ የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የሠቲት፣ እና የአካባቢው የዐማራ ተወላጆች መካከል ለመጥቀስ ያህል፦
1) የአቶ ዘነበ ሐጎስን ፬፻፶(አራት መቶ ሃምሣ) ያህል የቀንድ ከብቶች ዘርፈዋል፤
2) የአቶ አባየው ቢያድግልኝን ከ፮፻(ስድስት መቶ) የማያንሱ የቀንድ ከብቶች እና ፍየሎች ዘርፈው በመጨረሻም ሰውዬውን  ገድለዋቸዋል፤
3) የአቶ ገብረሕይዎት ኃይሌን ከ፹(ሰማንያ) በላይ የቀንድ ከብቶች እና ፍየሎች ዘርፈዋል፤
4) በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. የአቶ አለባ ሕደጎን ከ፭፻ (አምሥት መቶ) በላይ የቀንድ ከብቶች እና በርካታ ኩንታል እህል ዘርፈዋል፤
5) የቀኛዝማች ገብሩ ገብረመስቀልን ፳፬(ሃያ አራት) በሬዎቹ አርደው ከ፱፻ (ዘጠኝ መቶ) መቶ በላይ ማድጋ እህል ወርሰዋል።
ከዚህ በታች የቀረበው ሠንጠረዥ ደግሞ ከሰሜን ጎንደር የዐማራ ተወላጆች መካከል በትግሬ-ወያኔ አማካይነት ከ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ጀምሮ የተገደሉ፣ የታፈኑ እና የደረሱበት ያልታወቁ ዜጎችን ዝርዝር በጥቂቱ መለክታል።
ተራ ቁጥር
ስም ከነአባት
ተራ ቁጥር
ስም ከነአባት
ተራ ቁጥር
ስም ከነአባት
1)
አበበ ይርጋ
2)
አበራ ኃይሌ
3)
አበራ ዓለማየሁ
4)
አበራ ገብረመስቀል
5)
አበራ  አስረስ
6)
አበራ ሐጎስ
7)
አበጀ ክፍሌ
8)
አባተ እሸቴ
9)
አባው ጠጅነህ
10)
አብርሃ አዳነ
11)
አብርሃ አርጉ
12)
አብርሃ ነጋ
13)
አብርሃ በላይ
14)
አቻምየለህ ሽታዬ
15)
አቸናፊ ጽጌ
16)
አደበ ዓለም
17)
አደራጀው ገብሬ
18)
አዲሱ አበበ
19)
አዲስ አብተው
20)
አዲሰይ ልጃለም
21)
አዳነ ደረሰ
22)
አዳነው ርስቴ
23)
አለባቸው ደፈርሻ
24)
አለበል ይርጋ
25)
አለኸኝ መሥፍን
26)
አለማው ታረቀ
27)
አለማይ ካሣ
28)
ዓለሙ ጌታቸው
29)
ዓለሙ ለገሠ
30)
ዓለሙ ፈንታይ
31)
ዓለማየሁ  አበጠለው
32)
አለነ ክንዲሽ
33)
አላቸው ልጃለም
34)
አላቸው ገብረመድኅን
35)
አማረ ፈንቴ
36)
አንገረብ ተሰማ
37)
አንዶም ካሣ
38)
አረጋ ወልዴ
39)
አረጋው አየነው
40)
አረፈዓይኔ መኮንን
41)
አረፈ በለጠ
42)
አረፈ ግደይ
43)
አስገዶም ጥሩነህ
44)
አስመላሽ ይገዙ
45)
አስማረው ግደይ
46)
አስመራው ወልዴ
47)
አስማረው አስረሴ
48)
አስማረው መለሰ
49)
አስረስ ታከለ
50)
አስፋው መንግሥቴ
51)
አስፋው ወርቁ
52)
አሸናፊ ወንዱ
53)
አታላይ አበራ
54)
አታላይ አማረ
55)
አታላይ ዘነበ
56)
አጥናፈይ ዓለማየሁ
57)
ዐወቀ ዘውዱ
58)
አየነው ሙሉ
59)
አየነው ርስቴ
60)
አየነው በየነ
61)
አያሁነኝ ወንዶሻል
62)
አያሌው ሰሙ
63)
አያና ገብሬ
64)
አዘነህ ልጃለም
65)
አዛናው ቸሬ
66)
አዛናው ይደግ
67)
አዛናው ጽጌ
68)
እንዳልካቸው ጠጆ
69)
እንደሻው ታፈረ
70)
እንግተይ አየልኝ
71)
እሪበይ ገብሩ
72)
እሸቴ አያልነህ
73)
እሸቱ መስፍን
74)
በየነ ፍሬይ
75)
በየነ አየልኝ
76)
በሪሁን ደስታ
77)
በዕዱ ወንድም አገኝ
78)
በላይ ሙሉ
79)
በላይ ታደሰ
80)
በላይ መኮንን
81)
በለጠ ዓለም መብራት
82)
በለጠው ተስፋዬ
83)
በልጤ ወንድም-አገኝ
84)
በራ የማነ
85)
በራ ወልደሥላሴ
86)
በርሄ ሐጎስ
87)
በሪሁን ይግዛው
88)
ቢያድግልኝ ዘውዴ
89)
ባሕታ ፈንታይ
90)
ባሕታ መኩሪያ
91)
ባሕታ ወንድምአገኝ
92)
ባሕታ ረዳ
93)
ባሕታ እርትብ
94)
ባሕታ መንግሥቱ
95)
ባየው ባሕታ
96)
ባየው ቢያረግልኝ
97)
ባየው ልጃለም
98)
ብሪሁን ይርጋ
99)
ብላታ አብርሃ
100)
ብርሃኔ ማሞ
101)
ብርሃኑ ዳኛቸው
102)
ብርሃኑ ሽታዬ
103)
ገብረሕይዎት ኃይሌ
104)
ገብረመድኅን የኋላ
105)
ገብረመድኅን ዘርፉ
106)
ገብረመስቀል ጥርፊነህ
107)
ገብረሥላሴ ረዳ
108)
ገብረሕይዎት ባሕታ
109)
ገብረሕይዎት ገዛኸኝ
110)
ገብረማርያም አረፈዓይኔ
111)
ገብሬ ሐጎስ
112)
ገረመው ዳኜው
113)
ገሪማ ተኽላይ
114)
ጉበን ፊያሃጸን
115)
ጉዎይ መብርሃቱ
116)
ጉዎይ አዳነ
117)
ጊፍታቸው ዳኘው
118)
ጌቱ ጠለለው
119)
ጌታቸው አብርሃ
120)
ጌታቸው ብዙነህ
121)
ጌታቸው ተገኜ
122)
ጌቴው ታምሬ
123)
ግደይ ካሣ
124)
ግደይ ማሙ
125)
ግንባይ ጌታሁን
126)
ግርማ ይደግ
127)
ግርማይ ትኩስ
128)
ግርማይ ጥቄ
129)
ጎይቶም ምኅረት
130)
ጎይቶም ሐድጎ
131)
ጎርፉ ገብሩ
132)
ጎሹ አሰፋ
133)
ጎሹ ትርፍነህ
134)
ደቢል ዘነበ
135)
ደቢል ተክለሃይማኖት
136)
ደገፋ ጎይቶም
137)
ደሣለኝ ዋርካው
138)
ደስታ ሰርጸ
139)
ዳኜው ሢሣይ
140)
ድራር ገሠሠው
141)
ሀብቱ ይርጋ
142)
ሀፍቴ ዘነበ
143)
ወግሃታይ መንበሩ
144)
ወረታ ገብሩ
145)
ወልዴ ኢዮብ
146)
ወልዴ የኔሁን
147)
ወንድም ፍስሃ
148)
ወንድም ጠለለ
149)
ወንድም ጠጋ
150)
ወንድምአገኘሁ ታረቀ
151)
ወርቅዬ ገብረመድኅን
152)
ወርቅነህ አታላይ
153)
ዋኘው መንበሩ
154)
ዘውዱ ሽባባው
155)
ዘውዴ ሢሣይ
156)
ዘለቀ ግርማይ
157)
ዘራይ መርሻ
158)
ዘሩ በላይ
159)
ሐጎስ ገብራይ
160)
ሐጎስ መንግሥቱ
161)
ሐጎስ ይስፋ
162)
ጣሌ ገብሬ
163)
ጣሰው አሰፋ
164)
ጤላ ኃይሌ
165)
ጥጋቡ መኳንንት
166)
ጥላሁን ተወልደ
167)
ጥላሁን ታደሰ
168)
ጥሩነህ መብራቱ
169)
ጫኔ ይርጋ
170)
ጫቅሌ ገበየሁ
171)
ጫሉ ይዘዘው
172)
የኋላሸት ዘለቀ
173)
የሻለም በሪሁን
174)
የሽዓለም ጽጌ
175)
ይበይን ገብረእግዚአብሔር
176)
ይደግ አየነው
177)
ይደግ አያሌው
178)
ይዘዘው  ገብረመስቀል
179)
ይላቅ ተዘራ
180)
ይርጋ ደምሰው
181)
ይስፋ ፋንታይ
182)
ከሰተ ይርጋ
183)
ካሱ ንጉሤ
184)
ካሂሱ ንጉሡ
185)
ካሣሁን ሲሣይ
186)
ካሣ መብራት
187)
ካህሱ ጌታው
188)
ክንፈ ከበደ
189)
ክንፈ ናሁ
190)
ለማ ታደሰ
191)
ሉሌ መሥፍን
192)
ሊላይ ሐድጉ
193)
ልዑል ገብረመስቀል
194)
ልዕልቲ ወንድምአገኝ
195)
ልጃለም በላይ
196)
ልጃለም ታዬ
197)
መብርሃቱ ይግዛው
198)
መብርሃቱ ገብረእግዚአብሔር
199)
መሓሪ አዱኛ
200)
መኮንን ለውጤ
201)
መኮንን አበራ
202)
መኳንንት ዋርካው
203)
መኩሪያ ገብረማርያም
204)
መንገሻ ሙሉጌታ
205)
መርዕድ ገብረሚካኤል
206)
መሣፍንት ዳኜው
207)
ሙኮጠይ ታደሰ
208)
ሙሉዓለም ዋርካው
209)
ሙላው ዞፌ
210)
ሙሉ አታላይ
211)
ሙሉ አማረ
212)
ሙሉ በርሄ
213)
ሙሉ ገብረኪዳን
214)
ሙሉነህ ደሞዜ
215)
ማለፊያ ጉዎይ
216)
ማሌ ዘነበ
217)
ማሙ  ዋርካው
218)
ማሙ ቸሬ
219)
ማሙ ታደሰ
220)
ማሙነህ ይደግ
221)
ማማይ አብርሃ
222)
ማማይ አየልኝ
223)
ማማይ አለዩ
224)
ማማይ በላይ
225)
ማማይ ሙሉ
226)
ማማይ ረዳቴ
227)
ማማይ ፈረደ
228)
ማማይ በላይነህ
229)
ማሞ ደስታ
230)
ማሞ ዘውዴ
231)
ምራጭ ተሰማ
232)
ሞላ ጠለለ
233)
ነጋ አስረስ
234)
ነጋ አለበል
235)
ነጋ ጌታሁን
236)
ነጋ ሐጎስ
237)
ነጋ ምትኩ
238)
ነጋ ተበጀ
239)
ንጉሡ አብርሃ
240)
ንጉሤ ቀለመወርቅ
241)
ንግሸት ሐድጉ
242)
ሰጠኝ እንዳለው
243)
ሰጠኝ ሽታዬ
244)
ሰረበ ረዳ
245)
ሲሣይ አበራ
246)
ሲሣይ ተስፋሁነኝ
247)
ስማቸው ማሙ
248)
ስማቸው ዓለሙ
249)
ሺሙዬ ደምሰው
250)
ሺሙዬ ማሙ
251)
ሺሙዬ አለሜይ
252)
ሻንቆ በለጠ
253)
ሽፈራው ውብነህ
254)
ሽፈራው ንጉሤ
255)
ሽፈራው ተስፋይ
256)
ሽሁን ኪዳኔ
257)
ፈለቀ ግርማይ
258)
ፈረደ ዘርዓይ
259)
ፈረደ ፍሉይ
260)
ፈንቴ ገብራይ
261)
ፈንቴ ዘነበ
262)
ፋንቱ ሲሣይ
263)
ፋንታዬ አየልኝ
264)
ፍሬይ ተወልደ
265)
ፍታለው ታፈረ
266)
ጽይተይ አብርሃ
267)
ቁዊ ተዘራ
268)
ረዳኢ ለማ
269)
ርስከይ መለሰ
270)
ርስከይ ምንተስኖት
271)
ርስከይ ይልማ
272)
ርስከይ ኃይሌ
273)
ሮስኬ ማንጆስ
274)
ተበጀ መለሰ
275)
ተበጀ በቀለ
276)
ተገኘ ነጋ
277)
ተገኘ ደምሴ
278)
ተካልኝ አበበ
279)
ተካልኝ መንግሥቱ
280)
ተሰማ አብቅህለው
281)
ተሰማ ፍሬይ
282)
ተስፋ ፀጋዬ
283)
ተስፋይ አብርሃ
284)
ተስፋይ አጽብሃ
285)
ተስፋይ መኮንን
286)
ተስፋይ ኃይሉ
287)
ተሻገር ገብረመድኅን
288)
ተሾመ ፈረደ
289)
ተሾመ ጠለለ
290)
ታደለ አባተ
291)
ታደሰ ከሺ
292)
ታፈረ ሊላይ
293)
ታገል ተድላ
294)
ቶጋ ተገኘ
295)
ቻላቸው አበረ
296)
ቻላቸው ታደለ
297)
ቻላቸው ታደሰ
298)
ኃየሎም ይርጋ
299)
ኃይሉ ልዩነህ
300)
ፀጉ ዘነበ
301)
ፀጋዬ አበበ
302)
ፀጋዬ የኔሁን
303)
ፓስተር በለጠ ተስፋይ
ይህ እንግዲህ በግልጽ መረጃ የተገኘላቸው ናቸው። በአጠቃላይ ከ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ጀምሮ በሰሜን ጎንደር የትግሬ-ወያኔ በጅምላ የጨፈጨፋቸው ዐማራዎች ቁጥር ከ፳(ሃያ) ሺህ የማያንስ እንደሆነ የአካባቢው ተወላጆች ይመሠክራሉ። ከዚህ በተጨማሪም በሰሜን ጎንደር አካልነት ከሚታወቁት የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የሠቲት እና አጎራባች ወረዳዎች በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ዐማራዎች ከአፅመ-ርስታቸው ተፈናቅለው በገዛ አገራቸው ስደተኞች ሆነዋል፣ አካባቢውም በሠፋሪ ትግሬዎች ተወርሯል።
በአሁኑ ወቅት የእነዚህ በግፍ በትግሬ-ወያኔዎች ደማቸው የፈሰሰው ወገኖቻችን ደም ይጣራል፣ በገዛ አገራቸው ሥደተኛ የሆኑት ወገኖቻችንም የድረሱልን ጥሪያቸውን ያሰማሉ። ዐማራው ዘሩ እየጠፋ ነው። ይህ ሁሉ ሲፈፀም እጅን አጣምሮ በመቀመጥ የሚመጣ መፍትሔም የለም። ስለሆነም ችግሩ መኖሩን አምኖ ተቀብሎ ወገብን ጠበቅ አድርጎ ለኅልውና መታገል ይገባል።
ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!
የዐማራው ደም የውሻ ደም ሆኖ አይቀርም!
ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በጀግና እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ታፍራ እና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች!