Tuesday, January 28, 2014

ህወሓቶች አደብ ግዙ! (አብርሃ ደስታ)

January 28, 2014
በሌሎች ላይ የምትፈፅሙት ተግባር ሁሉ በራሳቹ ላይ እንደምትፈፅሙ (እንደሚፈፀም) አስቡ። በስልጣን ላይ ያለ ሁሉ በስልጣን አይኖርም። የስልጣን ዕድምያቹ በጣም አጪር መሆኑ እናንተም ታውቁታላቹ። በሰዎች ላይ ግፍ ስትፈፅሙ ሰዎች ይጠሏችኋል። በሰዎች ስትጠሉ የስልጣን ዕድምያቹ ያጥራል። እናንተ ያላቹ የህዝብ ድጋፍ ሳይሆን ጠመንጃ ነው። ጠመንጃ ስልጣን ለመያዝ ይረዳ እንደሆነ እንጂ በስልጣን ለመቆየት አያስችልም። ስለዚህ በጠመንጃ አፈሙዝ የስልጣን ዕድምያቹ ለማራዘም የምታደርጉት ጥረት ከንቱ ልፋት ነው።
Abraha Desta the facebook
አብረሃ ደስታ
እናንተ ከስልጣን ወርዳቹ ስልጣን የህዝብ ሲሆን፣ ፍትሕ ሲነግስ፣ እኩልነት ሲሰፍን ለፈፀማችሁት ወንጀልና ላደረሳችሁት በደል በሕግ እንደምትጠየቁ አያጠራጥርም። በስልጣን የኖረ የለም። እንኳን አምባገነኖች ዴሞክራሲያዊ ስርዓቶችም በስልጣን ኮረቻ ተቀምጠው ለዘላለም አይኖሩም።
ምናልባት እናንተ ምግባራችሁ አውቃቹ በህዝብ ስትተፉ ሀገር ለቃችሁ በመውጣት ለማምለጥ ትሞክሩ ይሆናል። ገንዘቡም አላቹ። ሁሉም ካድሬዎች (በሰዎች ላይ ግፍ እንዲፈፅሙ እየታዘዙ ያሉ የህወሓት አባላት) ግን እንደናንተ (እንደ ህወሓት መሪዎች) ከሀገር ወጥተው ለማምለጥ ዓቅሙ የላቸውም። ደግሞ ዓቅሙ ቢኖራቸውስ ለምን በሰሩት ጥፋት ከሀገራቸው ለመሰደድ ይወሰንባቸባል? የህወሓት ባለስልጣንናት ከስልጣን ወርደው በሀገራቸው በሰላም የሚኖሩበት ሁኔታ ለምን አያመቻቹም? ለምን መርሃቸውን ከ “ስልጣን ወይ ሞት” ወደ “ስልጣን ለህዝብ አስረክቦ በሀገር በሰላም መኖር” አይቀይሩም? ለካድሬዎቹስ አያስቡም እንዴ? የህወሓት ዕድሜኮ ትንሽ ነው። ህወሓት ሲሞት የህወሓት አባላትም ከህወሓት ድርጅት ጋር አብረው መሞት የለባቸውም። ህወሓትም ስልጣን ለህዝብ አስረክቦ ተቃዋሚ ፓርቲ ሁኖ መቀጠል ይችል የለ?! ዕድምያችሁ ከህወሓት ድርጅት ዕድሜ በላይ እንዲሆን አድርጉ።
እኛ ሰለማዊ ታጋዮች ነን። ያላቹ ሃብትና ጠመንጃ በመጠቀም እኛን መደብደብ፣ ማሳሰር፣ ማሰቃየት፣ መግደል ትችላላቹ። አምባገነን ስርዓት የሚችለው ነገር ቢኖር ሰው ማሳሰርና መግደል ነው። የዓላም አምባገነን መሪዎች በማሳሰርና በመግደል የስልጣን ዕድምያቸው ዘለአለማዊ ማድረግ ከቶ አይቻላቸውም። ዛሬ እኛን ብትደበድቡና ብትገድሉ ዕድምያቹ እያሳጠራቹ እንጂ እያሸነፋቹ አይደላችሁም። እኛ ብንገደል ሌላ ሰው አለ። ሁሉም ሰው መግደል አይቻልም። ምክንያቱም ሁሉም ሰው ከተገደለ ማንን ትጨቁናላቹ? የሚጨቆን ሰው ያስፈልጋችኋል። ሰው ጭቆና ሲበዛት በመሪዎቹ ላይ ያምፃል። እናም ትሸነፋላቹ። አምባገነን ተሸናፊ ነው። የማይሸነፍ ህዝብ ብቻ ነው። ምክንያቱም ህዝብ ለጭቆና አይነሳም።
እኛን በማሰቃየት ሰለማዊ ትግሉ መግደል አይቻልም። ሰለማዊ ትግሉ በመግደል የሰዎች የነፃነት ጥያቄ መግደል አይቻልም። የሰዎች የነፃነት ጥያቄ በመግደል ሰዎችን ለዘላለም መጨቆን አይቻልም። ስለዚህ መሸነፋቹ አይቀርም።
የሰለማዊ ትግል በር ባትዘግቡን መልካም ነው። ምክንያቱም ደም መፋሰሱ፣ ጦርነቱ፣ መጠፋፋቱ አንፈልገውም። እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው። መንገዳችንም ሰለማዊ ነው። የሰላም በር ሲዘጋብን እጆቻችንና እግሮቻችን አጣጥፈን እንቀመጣለን ማለት ግን አይደለም። አንድ በር ሲዘጋ ሌላ በር ማንኳኳታችን ግድ ነው። ነፃነት እንፈልጋለንና። “መታፈን ይብቃን!” ብለን ተነስተናል። ስለዚህ ትግላችን በምንም ዓይነት ስትራተጂ ማስቆም አይቻልም። የሚቻለው ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ ነው። ዴሞክራሲ ማስፈን ነው።
ገዢዎች በሐሳብ መከራከር ሳይችሉ ሲቀሩ ወደ ሀይል እርምጃ እንደሚወርዱ እናውቃለን። ሐይል መጠቀም የሽንፈት ምልክት ነው። ህወሓት የፈሪዎችና የጨካኞች ስብሰብ መሆኑ አውቅ ነበረ፤ ወደ ድንጋይ ውርወራ ፖለቲካ ይወርዳል የሚል ግምት ግን ፈፅሞ አልነበረኝም። መንግስት ወንጀልን መከላከል ሲገባው ወንጀል ፈፃሚ ሆነ።
ህወሓት ዉስጧ መበስበሱ እየሸተተን ነው። ምናለ ድንጋይ ባለመወርወር ገመናችሁ ባታጋልጡ? ለማንኛውም አደብ ግዙ የምትሰሩትን እወቁ። በሃይል የሚሆን ነገር እንደሌለ ተረዱ። ካለፉ ስርዓታት ታሪክ ተማሩ። ህዝብ እያያቹ ነው።
It is so!!!

2014 Golden Pen of Freedom awarded to jailed Ethiopian journalist

January 27, 2014
World Association of Newspapers and News Publishers (WAN-IFRA)
Eskinder Nega, an Ethiopian publisher, journalist and blogger
Eskinder Nega
Eskinder Nega, an Ethiopian publisher, journalist and blogger who is serving an 18-year jail sentence under anti-terror legislation, has been awarded the 2014 Golden Pen of Freedom, the annual press freedom prize of the World Association of Newspapers and News Publishers (WAN-IFRA).
Mr Nega was arrested on September 14, 2011 after publishing an article criticising his government’s use of the 2009 Anti-Terror Proclamation to jail and silence critics, including Ethiopian actor and activist Debebe Eshetu.  He was sentenced on 23 January 2012 and denounced as belonging to a terrorist organisation.
In making the award, the WAN-IFRA Board sent a message to the Ethiopian government that misusing anti-terror legislation to jail journalists and those critical of his government is unwarranted and against international protocols, including the Vienna Declaration on Terrorism, Media and the Law.
“This award recognises the courage of Eskinder Nega to speak out despite the risks that saw him jailed under his country’s draconian and overly broad anti-terror laws,” said WAN-IFRA President Tomas Brunegård, speaking on behalf of the Board.
“We call on the Ethiopian government to release Eskinder Nega and all journalists convicted under the sedition provisions, including Solomon KebedeWubset TayeReyot Alemu,and Yusuf Getachew”, said Mr Brunegård, who recently visited Ethiopia as part of an international mission that found that the country’s publishers and journalists practice journalism in a climate of fear.
The Golden Pen of Freedom is an annual award made by WAN-IFRA since 1961 to recognise the outstanding action, in writing or deed, of an individual, a group or an institution in the cause of press freedom. More on the Golden Pen can be found athttp://www.wan-ifra.org/node/31099
The award will be presented on 9 June during the opening ceremonies of the World Newspaper Congress, World Editors Forum and World Advertising Forum, the global summit meetings of the world’s press, to be held in Torino, Italy.
In an opinion piece published in the New York Times, Mr Nega said of his imprisonment: “I’ve never conspired to overthrow the government; all I did was report on the Arab Spring and suggest that something similar might happen in Ethiopia if the authoritarian regime didn’t reform… I also dared to question the government’s ludicrous claim that jailed journalists were terrorists.”
WAN-IFRA has been vocal in their opposition to Ethiopia’s misuse of anti-terror legislation, writing to late Prime Minister H.E. Meles Zenawi in 2012 requesting the immediate release of Mr Nega and most recently demanding his release, along with four other imprisoned journalists, in a joint international press freedom mission to Ethiopia, conducted with the International Press Institute. The full report from the international press freedom mission can be found at http://www.wan-ifra.org/node/97172
Mr Nega opened his first newspaper, Ethiopis, in 1993, which was soon shut down by authorities due to its critical reporting. He then, along with his wife Serkalem Fasil, managed Serkalem Publishing House, responsible for newspapers such as Asqual, Satenaw and Menelik, all of which are currently banned in Ethiopia.  He has also had his journalist’s licence revoked since 2005, but continued to publish articles despite the ban.
Mr Nega is no stranger to being imprisoned due to his writings. He was detained at least seven times under Prime Minister Meles Zenawi.  This included a 17-month jail sentence, along with his wife, on treason charges for their critical reporting on the Meles government’s violent response to peaceful protests that followed the disputed 2005 elections.
WAN-IFRA, based in Paris, France, and Darmstadt, Germany, with subsidiaries in Singapore and India, is the global organisation of the world’s newspapers and news publishers. It represents more than 18,000 publications, 15,000 online sites and over 3,000 companies in more than 120 countries. Its core mission is to defend and promote press freedom, quality journalism and editorial integrity and the development of prosperous businesses.

አንድነት ህወሓት/ኢህአዴግ የትግራይ ህዝብ አማራጭ ሀሳብ እንዳያገኝ እያካሄደ ያለውን አፈና አጥብቆ እንደሚቃወም ገለጸ

January 28/2014
(ዘ-ሐበሻ) አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው “ህወሓት/ኢህአዴግ የትግራይ ህዝብ አማራጭ ሀሳብ እንዳያገኝ እያካሄደ ያለውን አፈና አጥብቀን እንቃወማለን” ሲል አወገዘ።

የትግራይ ህዝብ እንደ ሌላው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የዴሞክራሲ ዕጦት ሰለባ እንደሆነ ፓርቲያችን ያምናል ያለው አንድነት ስርዓቱ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል እንደሚያደርገው በትግራይም ሰብዓዊ መብት ይረግጣል፣ ፍትህ ይደፈጥጣል፣ በካድሬዎች ይደበደባል፣ ይንገላታል፣ እንዲሰደድ ይደረጋል፡፡ ስርዓቱና በስርዓቱ ውስጥ የደላቸው ሹማምንት በስሙ ከመነገድ በዘለለ ዋጋ የተከፈለበትን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ዘርግቶ ተጠቃሚ ማድረግ አልቻለም ሲል በመግለጫው ላይ አስቀምጧል።


     
        የመቀሌ ከተማ (ፋይል)

“ህወሓት/ኢህአደግ ክልሉን እንደዋና ካምፕ በማየት በአፈና ውስጥ እንዲኖር አድርጎታል፡፡ የትግራይ ህዝብ የነፃ ፕሬስ ውጤቶችን እንዳያገኝ፤ አማራጭ የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዳያዳምጥ የተፈረደበት ሕዝብ ነው ማለት ማጋነን አይደለም፡፡ ይሄ እውነትም ሕወሓት/ኢህአዴግ በተለያየ ጊዜ በህዝቡ ላይ በፈፀማቸው ኢ-ዴሞክራሲያዊና ኢ-ፍትሃዊ ድርጊቶች የታየ ነው፡፡” የሚለው የአንድነት መግለጫ ” ለዚህ ማሳያ የሚሆነው አምባገነኑ ህወሓት/ኢህአዴግ አረና ባለፈው ሳምንት በትግራይ ክልል አዲግራት ከተማ ሊያደርግ የነበረው ሕዝባዊ ስብሰባ ልክ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ታፍኖበታል፣ አባላቱ ተደብድበዋል እንዲሁም ታስረዋል፡፡ ይሄ የሆነበት ምክንያት የትግራይ ህዝብ አማራጭ እንዳያገኝና በጉልበት የህወሓት አንጡራ ሀብት ብቻ ሁኖ እንዲያገለግል ከመፈለግ ነው፡፡ ከዚህ በፊትም ፓርቲያችን በመቀሌ ከተማ ሊያደርግ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ በከፍተኛ አፈናና እስር እንዲያስተጓጉል መደረጉ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ የትግራይ ህዝብ አማራጭ ሓሳብ የማዳመጥ፣ የሚጠቅመውን የመምረጥና የመቃወም ሕገ-መንግስታዊ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን በፅኑ ያምናል፡፡” ብሏል።

አማራጭ ሓሳብ በሚያቀርቡ ፓርቲዎች ላይ ህወሓት/ኢህአዴግ እየወሰደ ያለውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ ርምጃና አፈና በጥብቅ እንደሚያወግዝ ያስታወቀው አንድነት “አንድነት የአረና ፓርቲ የሚያደርገውን ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ ህወሓት/ኢህአደግ ለማደናቀፍ የሚያደርገውን ህገወጥ ዘመቻ እንዲያቆም እየጠየቀ አሁንም ተቃዋሚዎችን ‹‹ከጠላቶቻችን ጋር የሚተባበሩ›› በማለት የትግራይን ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ለመነጠል የሚካሄደውን ዘረኝነት የተሞላበት ከፋፋይ ርምጃ ለአገራችን እጅግ አደገኛ እንደሆነ አምኖ እንደ ሌላው ህዝብ ሁሉ ለነፃነቱ መከበር የሚያደርገውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥልና ሰላማዊ ትግሉን በመደገፍ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እውን እንዲሆን የከበረ ጥሪ እናቀርባለን፡፡” ሲል መግለጫውን ቋጭቷል።

በኖርዌይ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

January 28/2014

ጥር ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “ባልመረጥነው መጅሊስ  አንተዳደርም!  ያላመንንበትን የሀይማኖት አስተምህሮ አንቀበልም! የህዝበ-ሙስሊሙ የትምህርት ተቋም የሆነው አወሊያ ትምህርት ቤት  በገለልተኝነት ይተዳደር” የሚሉ የመብት ጥያቄዎችን በማንሳታቸው የ አሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው የሙስሊም አመራሮች ወደ ወህኒ ከወረዱ ከሁለት ዓመታት በላይ ተቆጠሩ።
























ለሁለት ዓመታት ከዘለቀው የፍትህ ሂደት በሁዋላ  በቅርቡ  ለብይን  በተቀጠረው  ችሎት ላይ በብዘዎች ሰንድ ታሳሪዎቹ  በሙሉ ይፈታሉ የሚል ተስፋ የነበረ ቢሆንም፤  አብዘኞቹ እና ወሳኞቹ አመራሮች በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው እንዲከላከሉ ውሳኔ መተላለፉ፤   የሙስሊሙን ህብረተሰብ ብቻ ሳይሆን  የፍትህና የሰብዓዊ መብት ጉዳይ የሚያሣስባቸውን ሌሎች ወገኖችም ጭምር ያሳዘነ ሆኗል።

ይህ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከሲህም ባሻገር ለተወሰነ ጊዜ  ከተቃውሟቸው “ፋታ” በመውሰድ  የመሪዎቻቸውን መፈታት በተስፋ ሢጠባበቁ የነበሩትን በርካታ ሙስሊሞች  በማስቆጣት ዳግም  የተቃውሞ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ምክንያት መሆኑ ይነገራል።
ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ  በዋለው ጁምአ፤ በኢትዮጵያ  ከ40 በሚበልጡ ከተሞች  በሚገኙ መስጊዶች ውስጥ  በእስር ላይ የሚገኙ የሙስሊም አመራሮችን ለመሰከር የተዘጋጀው የሰደቃ እና የዱዓ ሥነ-ስርዓት በስኬት መጠናቀቁ ይታወሳል።
ይህቀንበተለያዩ  የውጪአገሮችጭምር የሚኖሩ ሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያኖች በአንድነት ሆነው ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰሙበት እለት  ነበር። የተቃውሞ መርሐ-ግብሩ፣ ዱአ  (ጸሎት)  በማድረግ፤ ሰደቃ  (ምጽዋት) በመስጠት፣ ስብሰባ በማካሄድ በተቃውሞ ሰልፍና   በተለያዩ የአለም ክፍሎች ተካሂዷል።

በተለያዩ የውጪ አገራት ከተካሄዱት ሰልፎች መካከል-በኖርወይ ዋና ከተማ በኦስሎ የተካሄደውየተቃውሞ ሰልፍ ይገኝበታል።
የሰልፉ አላማ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥ የሚገኙ የእስልምና ሀይማኖት መሪዎች፣ ጋዜጠኛችና ፖለቲከኞች  ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ በሀገሪቱ የእምነት ነጻነት እንዲከበርና መንግስት እጁን ከሀይማኖቶች ላይ እንዲያነሳ ለመጠየቅ፣ እንደነበር የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ ገልጿል።

የኦስሎ ሰልፈኛች፣ በ14 ሰዓት ሴንትራል ስቴሺን ፊት ለፊትካለው ከነብር ሀውልት አጠገብ  ከተሰባሰቡ በሁዋላ “ካርል ዮሀን” ተብሎ የሚጠራውን መንገድ ይዘው  ተቃውሟቸውን እያሰሙ ወደፓርላማው ተጉዘዋል።

ሰልፈኞቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ ፣  እንዲሁም የአቡበከር አህመድንና የያሲን ኑሩን ጨምሮ የሌሎች የታሰሩት  የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ፣የእነ እስክንድር ነጋን፣   የእነ ርዕዮት አለሙን፣ የነበቀለ ገርባን፣ የነ አንዷለም አራጌን፣ የነውብሸት ታዬን እና የሌሎች የህሊና እስረኞችን  ፎቶ ግራፎች በማንገብ  እና መፈክሮችን በማሰማት በ ኢትዮጵያ እየተፈፀመ ያለውን ነገር ለኦስሎ ማህበረሰብ እና ለኖርዌይ ፓርላማ አባላት አሳይተዋል።

ሰልፈኞቹ ኖርዌጂያን ፓርላማ ጋር እንደደረሱ  ከመካከላቸው የተወከሉ ሁለት ኢትዮጵያውያን ወደ ፓርላማው ጽህፈት ቤት በመግባት የተዘጋጀውን ደብዳቤ ለፓርላማው ተወካይ አስረክብዋል።

የደብዳቤው ይዘት በኢትዮጵያ እየቀጠለ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ይገታ እና የታሰሩትም የህሊና እስረኞች ይፈቱ ዘንድ  የኖርወይ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ዲፕሎማሲያዊ ጫና እንዲያደርግ  የሚጠይቅ ነው።
በሰልፉ ላይ በኖርዌይ የኢትዮጵያውያን ሙስሊም ተወካይ፣  በኖርዌይ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር እና የስደተኛች ማህበር ጸሀፊ በየተራ  ንግግር አድርገዋል።

የበረዶው  ቁልል ለአይን የሚያስፈራና የቅዝቃዜውም መጠን ከባድ የነበረ ቢሆንም፤  ሰልፎኛቹ በብርቱ ጽናትና ዲሲፕሊን   ሁሉንም ተቋቁመው ፕሮግራሙን  በታሰበው መልኩ አካሂደዋል።

በሰልፉ ላይ ሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን በአንድ ላይ  እጅ ለእጅ ተያይሰው ከመሳተፋቸውም በላይ፤ “አንድ ህዝብ ነን፣ መቼም መቼም አንለያይም”ሲሉ ተደምጠዋል።



በሽብርተኝነት ህጉ ውይይት ስም የአዲስ አበባ ህዝብ እየተሸበረ ነው ሲሉ አንዳንድ ተወያዮች ገለጹ

January 28/2014

ጥር ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በአዲስ አበባ ውስጥ ለሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞችና በተዋረድም ከህዝቡ ጋር እተደረገ ባለው የሽብርተኝነት ህግ ውይይት፣  ነዋሪዎች ጥላቸውን እንኳን ማመን እንደሌለባቸው በአሰልጣኞች እየተነገራቸው ሲሆን፣ በስልጠናው ላይ የተካፈሉ አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች፣ ስለሽብረተኝነት ልንማር ሂደን ተሸብረን መጣን ሲሉ ተናግረዋል።

በመንግስት  ከፍተኛ አመራሮች የተዘጋጀው የማሰልጠኛ ሰነድ ኢሳት እጅ የገባ ሲሆን፣ ሰነዱ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን ቆሞ ልማቱን እንዲጠብቅና እንዲያፋጥን ይጠይቃል። በመስተዳድሩ የሚገኙ  የቢሮ ሃላፊዎች፣ በአዲስ አበባ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር በሆኑት በአቶ ተወልደ ወ/ጻዲቅ መሪነት በሰነዱ ላይ ውይይት አድርገውበታል ። በሰነዱ ላይ የመስተዳድሩ የየደረጃው  አመራሮችና ሲቪል ሰራተኞች እንዲሁም የከተማው  ህዝብ እየተወያዩበት ነው።

እስካሁን ባተካሄደው ውይይት እንደታየው የመንግስት ሰራተኞች በስልጠናው ላይ የሚገኙት የስም ምዝገባ ስላለ  እንጅ በዝግጀቱ አምነውበት አይደለም ይላሉ ተሳታፊዎች።

በውይይቶች ወቅት የመንግስት ባለስልጣኖች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጡት ከህዝቡ ስለሚጠበቀው ግዴታ መሆኑን የሚናገሩት ተሳታፊዎች ፣ የአገሪቷን ደህንነት ፖሊስና የደህንነት ሃይሉ ጠብቆ ስለማይችል፣ ህዝቡ ከኮሚኒቲ ፖሊስ ጋር በመተባበር ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበት ባለስልጣኖች ማሳሰቢያ መስጠታቸውን ተሰታፊዎች ይገልጻሉ።

የፌደራል ፖሊስ ሽብርተኝነትን ለመከላከልና ወንጀለኛን ለመለየት የአፍና የጸጉር ምርመራ ሊያደርግ እንደሚችል፣ ምርምራው እንዲደረግበት የተጠረጠረ ሰው ፈቃደኛ ካልሆነ ተመጣጣኝ ሃይል በፖሊስ ሊወሰድበት እንደሚችል፣  በማንኛውም ጊዜ በድነገት በከተማ ባስና በታክሲ ላይ ፍተሻ ሊደረግ ስለሚችል ህዝቡ መተባበር እንዳለበት የመንግስት ባለስልጣናት ተናግረዋል።
የመንግስት ሰራተኞች  ቦርሳ፣ፌስታልና መሰል ቁሳቁሶችን ቢሮ ውስጥ ጥለው እንዳይሄዱ የተነገራቸው ሲሆን ፣ ቢሮ ውሰጥ የተገኙ ፌስታሎችና ቦርሳዎች ለአደጋ ከማጋለጣቸው በፊት በጥንቃቄ እንዲታዩ ምክር ተሰጥቷል።

ለማወያያነት በቀረበው ሰነድ ላይ በግልጽ እንደሚታየው “ከፍርድ ቤት ፈቃድ በመውሰድ በሽብርተኝነት የተጠረጠረን ሰው የስልክ፣ የሬዲዮ፣ የኢንተርኔት የኤሌክትሮኒክስ፣ የፋክስ፣ የፖስታ ግንኙነት እና የመሳሰሉ ግንኙነቶችን ለመጥለፍ ወይም ለመከታተል፣ ጠለፋውን ለማስፈፀም ወደ ማንኛውም ቤት በሚስጢር የመግባት ወይም ይህንኑ ለመፈጸም የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ለማስቀመጥ ወይም ለማንሳት የፌደራል ፖሊስ ስልጣን ተሰጥቶታል።

እንዲሁም “ ማስረጃ ከሚሰበሰብባቸው የተለያዩ ዘዴዎች መካከል አንዱ በሽብርተኝነት ወንጀል ከተጠረጠረው ሠው ላይ ናሙናዎችን መውሰድ እና የህክምና ምርመራ እንዲያደርግ ማድረግ በመሆኑ ፣ ተጠርጣሪውም በምርመራ ሂደት ናሙናውን ለመስጠት ወይም የህክምና ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ ካልሆነ ፖሊስ ተመጣጣኝ ኃይል ተጠቅሞ ናሙናውን የመውሰድ ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡

ሰነዱ “ የሀይማኖት አክራሪነትና አሸባሪነት ዋናው ምንጭ ድህነትና ተስፋ መቁረጥ ” መሆኑን ከገለጸ በሁዋላ ፣  ”ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ በመንግስት የወጡ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና እቅዶች ተግባራዊ በማድረግ ሂደት ሰፊ ርብርብ ማድረግ” ከህብረተሰቡ እንደሚጠበቅ ይገልጻል።

ኢሳት አስተያታቸውን የጠየቃቸው ሰልጣኞች እንዳሉት ውይይቱ ህዝቡን የበለጠ የሚያሽብር ቢሆንም መንግስትም ሽብር ውስጥ መግባቱን ያመለክታል።

በሰነዱ ላይ  ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት7፣ አልሸባብና አልቃይዳ አሸባሪ ድርጅቶች ተብለዋል

Monday, January 27, 2014

ይግባኝ ተጠይቆባቸው ከነበሩት 6ሙስሊሞች መካከል የ2ቱን ይግባኝ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አደረገው

January 27/2014

በዛሬው ዕለት አቃቤ ህጉ ይግባኝ ጠይቆባቸው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ምድብ ችሎት ቀርበው ከነበሩት 6 ሙስሊሞች መካከል የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል በሆኑት ኡስታዝ ጀማል ያሲን እና በ ኡስታዝ ሃሰን አሊ ላይ አቃቤ ህጉ አቅርቦት የነበረውን የይግባኝ ጥያቄ ማንሳቱ አስታውቋል፡፡
በተቀሩት ላይ ግን ይግባኙን ያፀና ሲሆን ፍርድ ቤቱም ጉዳዩን ለማየት ለየካቲት 20 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በታህሳስ 3 ቀን የፌደራሉ ከፍተኛው ፍረድ ቤት 4ኛው ምድብ ችሎት በኮሚቴዎቻችን እና በወንድሞቻችን ላይ የጥፋተኝነት ብያኔ ማስተላለፉ እና 10 የሚጠጉትን ደግሞ በነፃ እንዲፈቱ መወሰኑ የሚታወስ ነው፡፡
ይህንንም ውሳኔ ተከትሎ አቃቤ ህጉ በ 6ቱ ላይ ይግባኝ የጠየቀ ሲሆን በመጀመርያው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ይግባኝ የተጠቀባቸው 6ቱም ሙስሊሞቸ መጥሪያ አልደረሳቸውመ በሚል ፍርድ ቤት ሳይገኙ በመቅረታቸው ፍርድ ቤቱ ተሟልተው እንዲቀርቡ ለጥር 19 ቀነ ቀጠሮ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በዚህም ቀነ ቀጠሮ መሰረት ጉዳዩን የተመለከተው 6 ኪሎ መነን አካባቢ የሚገኘው ፍርድ ቤት ይግባኙን በመመርመር በ 2 ሙስሊሞች ላይ የቀረበውን ይግባኝ ውድቅ ያደረገ ሲሆን በተቀሩት 4 ሙስሊሞች ላይ ግን ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ለየካቲት 20 መስጠቱን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል በሆኑት በኡስታዝ ጀማል ያሲን እና በ ኡስታዝ ሃሰን አሊ ላይ አቃቤ ህጉ ያቀረበውን ይግባኝ ፍርድ ቤቱ ውድቅ ያደረገው ሲሆን በተቀሩት በሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ፣በሼህ አብዱራህማን፣በወንድም አሊ መኪ እና በወ/ሮ ሃባ መሃመድ ላይ ቀረበውን ይግባኝ ለመመርመር ተጨማሪ ቀነ ቀጠሮ ለየካቲት 20 መስጠቱን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
ይግባኙ ውድቅ የተደረገላቸው
1.የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ኡስታዝ ጀማል ያሲን
2. ኢስታዝ ሃሰን አሊ
ለየካቲት 20 ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ የተሰጣቸው
1. በሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ
2. በሼህ አብዱራህማን፣
3. በወንድም አሊ መኪ እና
4. በወ/ሮ ሃባ መሃመድ ናቸው
በተያያዘም ዜና ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያስተላለፈባቸው የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እና የተቀሩት ወንድሞች ከ 3 ቀናት ቡሃላ በጥር 22 ፍርድ ቤት በመቅረብ የመከላከያ ምስክራቸውን ለተከታታይ 5 የስራ ቀናት ለፍርድ ቤቱ ማቅረብ እንደሚጀምሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አላህ ፍትህን ያስፍንላቸው!!!

ሁለት ከፍተኛ የኦብነግ አመራሮች ከኬንያ በሕወሃት የደህንነት ሃይሎች ታፈኑ::

January 27/2014

የሕወሓት የጸጥታ እና የደህንነት ሰራተኞች አቶ ሱሉብ አህመድ እና አቶ አሊ ሁሴን የተባሉ የኦብነግ ( የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻነት ግንባር ) አመራሮችን ትላንትና ከሰአት በኋላ ከናይሮቢ ከተማ አፍኖ መውሰዱ ተሰምቷል:; እነዚህ የታፈሁ ሁለት አመራሮች ባለፈው ጊዜ ወያኔ በናይሮቢ ከኦብነግ ጋር ባደረገው ምስጢራዊ የድርድር መድረክ ላይ ድርጅታቸውን ወክለው የተሳተፉ እና ለሶስተኛው ዙር ድርድር እየተዘጋጁ ያሉ ነበሩ:: ይህ አፈና የመጀመሪያው ሳይሆን ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት የሕወሓት የደህንነት ሃይሎች ወደ ኬንያ ዘልቀው በመግባት እጅግ በሚያሰቅቅ እና በኢሰብኣዊ ሁኔታ በሰላም ድርድሮች ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የኦብነግ አባላትን አፍኖ በመውሰድ በመግደል ይታወቃል:: በ1998 የሕወሓት ሰራዊት ሶስት የኦብነግ የተደራዳሪ ቡድን አባላትን ገድሎ ሁለቱን በሃይል አፍኖ የወሰዳቸው ሲሆን ከግንባሩ ጋር በተደረገ ድርድር ወደ እብነግ የጦር ሰፈር እንዲመለሱ ተደርጓል::ከሁለት አመት በፊት እንዲሁ በናይሮቢ ከፍተኛ የኦብነግ አመራርን በአደባባይ ገድለዋል:: ምንሊክሳልሳዊ Via ኦጋዴንኔት

TPLF: The Dog That Can no longer Bark

January 27, 2014
by Amanuel Biedemariam
On January 15, 2014, ESAT reported that the Ethiopian People’s Revolutionary Front (EPRDF) conducted organizational evaluation and quoted Bereket Simon, former Ethiopia’s Information Minister and new advisor to Prime Minister Hailemariam Desalgen, on how he characterized the differences amongst the EPRDF leaders during their deliberations. He said:
Before we replaced Revolutionary Democracy with Developmental Democracy, the Front has been divided into three groups. One group of the leadership had argued that our problem was internal and that we need to first check that, while the other group held that our problem was Shabia/Eritrea and that we need to fight them first, but the third position which said that after fighting Shabia/Eritrea, we should then look at our internal problems had become the winning idea.
According to the statement, the EPRDF is no longer a Revolutionary Democracy. It is now Developmental Democracy (whatever that means). In order to come up to that determination however, the group was divided to three camps but the final outcome was a decision to fight “Shaebia/Eritrea” as a primary focus and address their issues later.
Some of TPLF ‘Mafia group’ that remained to bleed the people of Ethiopia
Some of TPLF ‘Mafia group’ that remained to bleed the people of Ethiopia
The irony, one prerequisite to development or any progress for any nation is peace. When a nation ensures relative peace then there is a foundation for progress. The decision by the EPRDF to “Fight Shaebia/Eritrea” as a prerequisite to their developmental democracy is simply absurd, laughable and dangerous at the same time.
After a 15 year period that started with a border war and morphed into the current so called No-War No- Peace strategy; the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF/EPRDF) decided to continue on the same path albeit with a dressed-up name. The question is, at what cost? Who paid for it initially? Who is responsible for the last 15 years? The TPLF evaluation did not entertain peace with Eritrea; does that mean they have no intention to make peace with Eritrea ever? Furthermore, on what grounds does Ethiopia’s current regime, the TPLF/EPRDF is trying to continue the path of hostility? What is the ultimate goal? How will Eritrea deal with the intransigent TPLF? And ultimately, what constituency of Ethiopia will support this intransigence?
Moreover, how did Ethiopia do without peace with Eritrea? Could it have done better?   How have the people of Ethiopia and Eritrea fared? Is the past 15 years a model by which two neighboring countries should conduct their affairs for the future? Who pays for all these? Who paid for the past?
The key question, why did Bereket Simon come-out now and made these absurd statements? Moreover, why now, when many particularly the US, for the first time in over 15 years is talking peace did Bereket Simon roll-out this war agenda? The questions are endless.
The answer to all these questions are found on a statement one astute Eritrean political figure made a while back. When asked to respond about outrageous repeated statements by the TPLF against Eritrea, he answered, “When a dog barks uncontrollably disturbing peace, the best option is to talk to the owners of the dog.”
There are three key reasons why Bereket Simon decided to come out and declared the continuation of the hostilities.
1) The current chatter that the US is on the verge reestablishing ties with Eritrea is a concern and they are crying for some attention. They want to make sure that the US does not abandon them. Ambassador David Shinn’s comment that we will not have relations with Eritrea at the expense of our important ally Ethiopia is designed to do just that; allay concerns. That however, is not working because the reaction to Ambassador Shinn has been very harsh.
2) Improved Eritrea US relations are a serious concern for the pocket books of the minority regime. Ethiopia has provided boots for the West that funds its military. In turn the TPLF controls its army with the billions in funding received from the West specifically the US by using it as incentive. Those who are loyal are rewarded by assignments on peacekeeping missions for lucrative pay. That means there is a security dimension to it as well because the funds pacify multi ethnic military that could turn on them.
3) Peace is the greatest threat to the very existence of the TPLF/EPRDF. Therefore, they must perpetuate these conflicts particularly with Eritrea. The TPLF is using the border issue to control the people of Ethiopia by misleading them as if the border is a negotiating ploy hence continues the declared No-Peace No-War agenda indefinitely.
Time the enemy
The TPLF/EPRDF has run out of time. There has been tremendous regional and global changes that lead to change of attitude and approach in dealing with the countries of the region. Their strategy to subdue Eritrea failed. To the contrary all economic signals indicate that Eritrea is forging ahead independently. The US waited for over a decade and half to bring regime change in Eritrea using Ethiopia and failed.
China’s influence in the region is forcing changes on US Africa policy. The changes on Western global Geo-Strategic shift away from Middle East to Asia plays a factor. Military and other budget cuts in the US will certainly affect changes. In addition, the death of Meles Zenawi and, the power transition that ensued has created a precarious power- sharing leadership arrangement that generated a great deal of uncertainty.
Moreover, countries in the region are working for their interests diligently. Recent activities by countries in the region particularly Egypt, Sudan and Eritrea are something to pay attention to for many reasons.
To Conclude
The US holds the key to Eritrea Ethiopia future relations simply because Ethiopia as a client state and dependent on US for political, diplomatic, economic, food and military support/aid is amenable to US demands. Thus, when and if the US decides it is on the best interest of the US for the TPLF to create peace with Eritrea then there will be no choice left but to acquiesce to US demands. That is the reality.
The question however remains, after paying dear lives of over 20,000 Eritrean souls, thousands more wounded; after having millions displaced; after decades of hostility that impacted families negatively in many ways; in short, after Eritrea paid the price with dear blood why on earth will the people of Eritrea throw a lifeline to the TPLF? Will they?
That simply means the neck of the TPLF is on the table. The US is at a critical point where they have to make a choice whether to save Ethiopia or the TPLF. When an organization with no constituency and according to Bereket Simon not clear about the future-direction of the nation  decide to place their fate on hostilities with a neighboring country Eritrea; the US has a lot to worry about.  When the perception remains Bereket Simon is the key figure rendering Prime Minister Hailmariam Desalegne as a figurehead, the US has a lot to worry about. Is TPLF/EPRDF Ethiopia?  These are some sticky points. Ambassador David Shinn tried to address these conundrum but no takers. He said,
“Although the United States might decide to try again to improve relations with Eritrea, it will not do so at the expense of its ties with Ethiopia.”
The statement above said Ethiopia, not TPLF/EPRDF. The US is cognizant of these complexities. The US at this stage is desperate to save Ethiopia because the current states of affairs are unsustainable.
Ambassador Hank Cohen’s approach is therefore commendable as he is trying to thread a thin line to save a nation from embedded ethnic-political-system that can spell disaster with long term consequences for the region and US long term interests.
Eritrea therefore holds the key.
Awetnnayu@hotmail.com

የአገር አቋራጭ አውቶቡስ ተገልብጦ 17 ሰዎች ሕይወታቸው አለፈ፤ የ2 ዓመት ህፃን ሕይወቱ ተረፈ

January 26/2014


(ዘ-ሐበሻ) ከሞያሌ ወደ ሻሸመኔ ተጓጓዦችን ጭኖ ይጓዝ የነበረ አንድ አገር አቋራጭ አውቶቡስ ተገልብጦ የ17 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ። የ2 ዓመቱ ህፃን ምንም ጉዳት ሳይደርስበት ሲተርፍ፤ ሌሎች 31 የሚሆኑ ሰዎች ግን ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ለዘ-ሐበሻ የደረሱት መረጃዎች አመልክተዋል።

ትናንት ማምሻውን ከሞያሌ ወደ ሻሸመኔ ሲጓዝ የነበረው ሃገር አቋራጭ አውቶቡስ የተገለበጠው በይርጋ ጨፌ ወረዳ ቆንጋ ቀበሌ እንደሆነ ሲገለጽ የአካባቢው የትራፊክ ፖሊስ በሰጠው መግለጫ ለአደጋው መንስኤ በፍጥነት ማሽከርከር ነው ተብሏል። ፖሊስ ጨምሮም መንገዱ ከፍተኛ ቁልቁለት የነበረው ሲሆን ሹፌሩ ሃላፊነት በጎደለው መልኩ በፍጥነት በማሽከርከሩ አደጋው ሊከሰት እንደቻለ ገልጿል።

በዚህ አካባቢ የተለያዩ የትራፊክ አደጋዎች በተለያየ ጊዜ እንደሚደርስ የጠቆሙት የአካባቢው ነዋሪዎች አደጋዎች በሹፌሮች አማካኝነት ይፈጠሩ እንጂ መንግስትም ተጠያቂ ነው ይላሉ። በተለይ ይህ ቦታ ብዙ የመኪና አደጋ የሚደርስበት ቢሆንም ትራፊክ ፖሊስ በሙስና በመጨማለቅ በፍጥነት በሚያሽከረክሩ ሰዎች ላይ ተገቢውን ቅጣት እንደማይጥሉባቸው የገለጹት እነዚሁ ታዛቢዎች ከአስተዳዳሪው ጀምሮ በሙስና የተጨማለቁ በመሆናቸውና ትራፊክ ፖሊስም የሚገባውን ሥራ ስለማይሰራ ለአደጋዎቹ መበራከትም ምክንያት ነው። በተለይ በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የአንድ ትራፊክ የወር ደመወዝ አንድ ሰው ለአንድ ምሽት በሬስቶራንት 2 ሰው ራት የሚጋብዝበት ሂሳብ መሆኑ ፖሊሶቹ በሙስና ላይ እንደሚሰማሩ ታዛቢዎች ለዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ገልጸዋል። በተጨማሪም በይርጋ ጨፌ ወረዳ በቂ የትራፊክ ምልክቶች አለመኖራቸው ለአደጋው መበራከት እንደምክንያት ያቀርባሉ።

በዚህ የመኪና አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የታወቀ ሲሆን አብዛኞቹ በዲላ ሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ላይ ይህን ጥናት ስለመኪና አደጋ አቅርበን ነበር። በድጋሚ እነሆ፦
በዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የ2012 ሪፖርት መሰረት በዓለማችን በዓመት 1ሚሊየን 3 መቶ ሺ ህዝብ በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው እንደሚያልፍ ሲታወቅ በኢትዮጵያ በተደረገ ጥናት ደግሞ በዓመት ክ2000 ሰዎች በላይ በመኪና አደጋ ሕይወታቸው ያልፋል።
ለመኪና አደጋ መንስኤ ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል በፍጥነት ማሽከርከር፣ ለእግረኞች ቅድሚያ አለመስጠት፣ የሌሊት ጉዞ፣ ደርቦ ማለፍ፣ ከአቅም በላይ መጫን፣ አደንዛዥ ዕፅ መጠቀምና ጠጥቶ ማሽከርከር ከመንስኤዎቹን መሀል ዋነኞቹ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተሽከርካሪ የቴክኒክ ጉድለት ወይም ብልሽት፣ የእግረኛ ግራ መንገድ ይዞ አለመሄድና የማቋረጫ ምልክቶችን (ዜብራ) በአግባቡ አለመጠቀም፣ የመንገዶች በጥራት አለመሰራትና የመንገድ ላይ ምልክቶች ተሟልተው አለመዘጋጀት ለአደጋው እንደመንስኤ የቀረቡ ናቸው፡፡

ዘ -ሐበሻ

Sunday, January 26, 2014

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ “የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው” አለ

January 26/2014

“የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው!” ሲል የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ ባወጣው መግለጫው አስታወቀ።

ንቅናቄው ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫ “የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሔራዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጥሪ ወሳኝና ህዝባዊ ጥሪ እንደሆነ ታሪካዊ ምስክርናውን በመስጠት፤ በዚህ ዘረኛ የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ከልክ ያለፈ ጭቆና ፣ ረገጣና ፣ እንግልት ደርሶብኛል የምትሉ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ዜጎችና ፣ በምንወዳት ሃገራችን ለህዝብ የሚበጅ ቀና ለውጥ ለዘለቄታው ይሰፍን ዘንድ የምትመኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፤ እንዲሁም ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ፣ የሃይማኖት ተቋማትና ፣ የሲቪክ ማህበራት ታላቅ ሃገራዊ ሃላፊነትና የህዝብ አደራ በጫንቃችሁ እንደተሸከማችሁ በመገንዘብ ፤ የሚጠበቅባችሁን ህዝባዊ ተልኮ መፈፀም ታሪካዊ ግዴታችሁ መሆኑን በመረዳት ፤ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጎን እንድትቆሙ ሲል በጥብቅ እያሳሰበ ፤ ሃገራዊ ጥሪውን በአክብሮት ያቀርባል:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጥሪ የሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ጥሪ ነው!” ብሏል።

Ethiopia: Relatives Fear for Missing Political Prisoners from Jail Ogaden, Reports

jeel-ogaadeen2
The notorious Prison locally known as “Jail Ogaden“, about 80 kilometers Eastern of the city of Harar, has been the scene of repeated atrocities carried out by the Ethiopian prison guards. 
 (Mathaba) — The Prison, which is jailed about several thousand political inmates that live in unbearable living conditions and systemically starved and beaten. This jail ,with its 20 unclean cells overcrowded with prisoners that experience lack of proper jail food services, lack of jail exercise yard, and has only two toilets that serve several thousand prisoners, moreover the Ethiopian guards constantly intimidate, severely torture including beating with strong sticks, electric shock, and suffocating with pouring buckets of ice water over the heads of the prisoners for confession during the interrogation.
Ogaden, which is home to about 8-10 million Somali ethnic population that lives on its goats, sheep and camels is a dry semi-desert region, with low bushes providing what fodder the animals need. It should be a peaceful nomadic region, but this is a region living in fear. Ethiopian Troops patrol the villages and have bases in the main towns. Over the past 5 years repeated atrocities have been inflicted on the local people, who are accused of supporting the liberation movement, the Ogaden National Liberation front. This is the testimony of former Liyu Police, Abdirahman Sharif Zekeriye, who has since fled from the country. It offers a rare glimpse into a region from which all independent journalists have been banned, and from which international aid agencies are banned.
“We had to form queues, whenever we were getting into and out of the cells due to the problems of the overcrowded cells. We had to sit forming queues along family and clan lines in the yard. We knew that a spy was among us because of during the nights, Ethiopian guards used to come and take away selected prisoners,the ones that have lucky were returned back,but those had not,never seen again”, said Mr. Zekeriye who spent 4-years in Jail Ogaden before he became a liyu police personnel.
A large number of political inmates disappeared and still remain unknown whereabouts after they have been driven away from their custody, this comes after rumors spread throughout the city indicate that Western NGOs heading to Jigjiga and they might demand to pay visit the notorious jail Ogaden .
“Whether it (the disappearance) is related to the rumors or not, we aware that the Ethiopian government has transported a large number of prisoners including my son and his uncle in an unknown location and still missing and we are very concerned about their well-being as my son having a current medical problem while my brother is said to be in a life threatening condition after several hours of sustained beatings by the Ethiopian guards”, said a father that contacted us ,and declined to be named for fear of reprisal.
A news article on the diasporas-run website,Ogaden.com reported the death of 98 inmates in the Ogaden jail in the last couple of weeks alone, citing a source from the website’s reporter and individuals with the Ethiopian Administration in Jigjiga. Most of them died violently and hunger, the report added.
The Ogaden, which is twice the size of England and Wales together with a population of about 8-10 million, has been a region ravaged by famine, droughts, tribal conflicts and successive wars between secessionists and regimes of Ethiopian highlanders.

Saturday, January 25, 2014

የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ

January 25/2014


“ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።

1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።
2. አመላካች ሁለት: ለምግብ የመክፈል አቅም (Affordability)
ይህ አመላካች “የአገሩ ሕዝብ በአገሩ ዋጋ ምግብ ገዝቶ ለመብላት ምን ያህል አቅሙ ይፈቅድለታል?” የሚለውን የሚመልስ ነው። አሁንም ከመጨረሻ እንጀምር። አንጎላ፣ ዚምባቡዌ፣ ቻድ፣ ጉያና፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ጋምቢያ እና ኢራን የየአገሩ ሕዝብ ምግብ መሸመት የሚቸገሩባቸው አገሮች ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ ከመጨረሻ አምስተኛ ናት።
3. አመላካች ሶስት: የምግብ ጥራት
ይህ የምግብ ይዘትንና የአያያዝ ንጽህናን የሚመለከት ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ሞዛምቢክ፣ ቻድ፣ ቶጎ፣ ዛምቢያ፣ ማሊ፣ ናይጄሪያ፣ ባንግላዴሽ፣ ሌሶቶ ከመጨረሻው እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ጥራት የመጨረሻዋ አገር ናት።
4. አመላካች አራት፡ የሰውነት ውፍረት እና የስኳር በሽታ
ይህ አመላካች ከልክ ያለፈ ውፍረት ዓለም ዓቀፍ የጤና ችግር እየሆነ በመምጣቱ የገባ አመልካች ነው። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥሩ ውጤት ያመጣችሁ በዚህ አመላካች ብቻ ነው። ኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝቧ ቀጫጫ ነው፤ የስኳር በሽታም እንደሌላው አገር የተስፋፋባት አገር አይደለችም።
5. አማካይ ውጤት
የእነዚህ አራት አመላካቾች ድምር ውጤት አጠቃላይ ውጤትን ይሰጣል። በአጠቃላይ ውጤት: ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ማዳካስካር፣ የመን፣ ቡሩንዲ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዚምባቡዌ፣ ሴራሊዮን ከመጨረሻ እስከ አስረኛ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛ ነች።
ይህ ምንን ያመለክታል?
ወያኔ ባለፉት አስር ዓመታት በተከታታይ ከ11% በላይ ኢኮኖሚውን አሳድጌዋለሁ ሲለን ነበር። እድገቱ ያተኮረው ገጠር፤ ምንጩም ግብርና ነው ብሎን ነበር። ሐቁ ግን ከላይ የተመለከተው ነው።
እርግጥ ነው የወያኔ ሹማምንት በከተሞች ሕንፃዎችን ይገነባሉ፤ በገጠሮች በመቶዎች ሄክታር የሚለካ ለም መሬት ይዘው ፈጣን ገንዘብ በሚያስገኙ የአበባ፣ የጫትና የቃጫ ምርት ላይ ተሰማርተዋል። ከራሳቸውም አልፈው ሀብታም የውጭ አገራት ሸሪኮቻቸውን በአገራችን ለም መሬት ይበልጥ ያበለፅጓቸዋል። የእነሱ የግላቸው፣ የቤተሰቦቻቸው፣ የዘመዶቻቸው እና የሸሪኮቻቸው ኢኮኖሚ እየተመነደገ መሆኑን እናውቃለን። ይህን በገዛ ዓይኖቻችን የምናየው ሀቅ ነው።
ሆኖም ግን የእነሱ ኢኮኖሚ ማደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ አለመሆኑ እናውቃለን። አገራችን ከጓረቤት አገሮች ጋር ስትነፃፀር ወደ ኋላ እየቀረች መሆኑ ያንገበግበናል። በቅርቡ አክስፋም በጥናት ያረጋገጠዉ የኢትዮጵያ ገበሬዎች በየቤታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር በምስጢር የሚያወሩትን እውነት ነው።
ከሳምንት በፊት ደግሞ “ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት” የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም አንድ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጎ ነበር። በዚህ የጥናት ውጤት መሠረት በዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ያሉ አስር አገሮች በቅደም ተከተል ሞንጎሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ቱርክሜንስታን፣ ቡታን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ላኦስ፣ ቲሞር-ሊስቲ፣ ኤርትራ እና ዛምቢያ ናቸው። በዝርዝሩ ውስጥ ኢትዮጵያ አገራችን የለችበትም።
በዓለም አቀፍ መድረኮችም የወያኔ መረጃዎች ውሸትነት እየተጋለጡ መሆናቸው በጎ ምልክት ነው። የሚያሳዝነው ግን ይህንን ሀቅ የሚያዉቁ ምዕራባዉያን ለጋሽ አገሮች አሁንም ወያኔን እየረዱና እየደገፉ ሥቃያችን የሚያራዝሙብን መሆኑ ነው።
ለዚህም ነው ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው በአገራችን መሠረዊ የሆነ የአስተዳደር ለውጥ ሲኖር ነው ብሎ የሚያምነው። የወያኔ አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እስካልተተካ ድረስ የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ መደህየቱ፤ ጥቂት ሀብታሞች ደግሞ በብዙሀኑ ድህነት መበልፀጋቸው አይቀርም። የወያኔ ውሸቶች ለኢትዮጵያ ድሀ ምግብና መጠለያ አይሆኑለትም። ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ማምጣት የምንችለው ወያኔን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ሁለተናዊ እድገት የሚጨነቅ መንግሥት መምረጥ ስንችል ብቻ ነው።
ስለሆነም ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በውሸት እድገት እያደናቆረን፤ በተግባር ግን እያደኸየን ያለውን ዘራፊውን ወያኔን አስወግደን በሕዝብ ነፃ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖረን ትግላችን እናጠንክር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የመቀሌ ዩኒቨርሲቲው መምህር እና የአረና ፓርቲ አባል አብረሃ ደስታ በታጣቂዎች ተደበደበ

January 25/2014

የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና የአረና ፓርቲ አባል በመሆን የትግራይ ወጣቶችን በመቀስቀስ የወያኔ አገዛዝን በመቃወም የሚታወቀው አብረሃ ደስታ በትልላንትናው እለት በትግራይ አካባቢ መደብደቡን ተገለጸ ፣ይህንን ግለሰብ እና ሌሎች የአረና አመራር አባላትን ጨምሮ እንዲሁም ሌሎች በስብሰባው ላይ የተገኙትንም የህብረተሰብ አካላት የመንግስት ባለስልጣኖች በተገኙበት በታጣቂዎች መደብደባቸው ተገልጾአል ። ከ18 ሰአታት በፊት አቶ አብረሃ ደስታ ለመላው የግል ሚዲያዎች አጭር መል እክት እንዲህ ሲል አስተላልፎ ነበር ዓረና ፓርቲ በዓዲግራት ከተማ ለእሁድ ከጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ጋር በተያያዘ ዛሬ ዓርብ ሁለት የዓረና አመራር አባላት (አቶ ዓምዶምና መምህር ገብረጨርቆስ) በዕዳጋ ሐሙስ ከተማ ፖሊስ ታስረዋል። የታሰሩበት ምክንያት ህዝብ በስብሰባ እንዲሳተፍ ቀስቅሳችኋል የሚል ነው። ህወሓቶች በተምቤን የፈሩትን ያህል በዓጋመ ፈርተዋል። በተምቤን ተመሳሳይ የእስር ሁኔታ አጋጥሞናል። ስብሰባ ፈቅደው ስለ ስብሰባው ህዝብ እንዳይሰማ ግን ከለከሉ። የዚህ የዜና ስራ ተጠናክሮ ሳይወጣ እንደገና የእርሱ መደብደብ ዜና ደርሶናል ። የኢትዮጵያ የፖለቲካ አቅጣጫ ወዴት እያዘመመ እንድሆነ ከእንስቃሴው ለመረዳት ይቻላል።

የኢሃዴግ መንግስት የኢኮኖሚ ውድቀት ገጠመው ፣ሃገሪቱ በከፍተኛ ሁኔታ ላይ በእዳ እየተሽመደመደች እንደሆነ ተጠቆመ

January 25/2014

ምንሊክ ሳልሳዊ :-ወያኔ እየመራው የሚገኘው ኢኮኖሚ ተሽመድምዶ ሃገርን ረመጥ ላይ እየከተታት ሲሆን የወያኔ ሳቦታጅ ጥቂት ሰዎች በሃገር ሀብት በህዝብ ላይ እንዲፈነጩ አድርጓቸዋል::በሃገሪቱ ማንኛውም አይነት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ከበፊቱ በተለየ እና በባሰ ሁኔታ ተንኮታኩተው አፈር መልበሳቸው በይፋ ታውቋል::ለስርኣቱ ቅርበት አላቸው ያሉ ምንጮች ወያኔ ወገቡ እንደተሰበረ እየተናገሩ ነው::በፖለቲካው ረገድ የስርኣቱ ገዢ ፓርቲዎች እርስ በርስ አለመተማመን ደረጃ ላይ ከመድረሳቸውም በላይ አመራሮቹ አድፍጠው አንዱን አንዱን እየጠበቀ በፍራቻ አለም ውስጥ እየዋተቱ ይገኛሉ::አቤት የሚባልበት እየጠፋ ነው፡፡ የውሳኔ ሰጪ ያለህ ቢባል መልስ አይገኝም፡፡ ፋይሎች የሚያያቸውና የሚያነባቸው አጥተዋል፡፡ መልካም አስተዳደር ገደል ገብቷል::በአላማ ሳይሆን በጊዜያዊ የመኖር ሂደት ላይ የተመሰረተው የካድሬዎቹ ሩጫ ድካምን በመፍጠሩ ሁሉም በያለበት ቆም ብሎ እያሰበ ሲሆን አሳቡም የገፈፍኩትን ገፍፌ ሃገርን ድባቅ መትቼ ልሽሽ ሆኗል::
ገበናን ገበና ይገፈዋል እንደሚባለው የወያኔ ጁንታ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ የገነባው ኢኮኖሚያዊ ገበና በገበና ተጋልጧል:: የማይሰማ ነገር የለም እና እኛም ሰማን አነበብን አየንም እነሆ ታዝበን ዝም አላልንም ገበናዎቹ ገበናውን ሲገልቡት አብረን አልሳቅንም ሀገር ነውና ገበናዎቹን ተመርኩዘን የምንለውን ልንል ይኸው ተከሰትን::
የስርኣቱ ቅርብ ምንጮች የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በመሽመድመዱ ወያኔ ወገቡ መቆረጡን እና መምራት አለመቻሉን በለሆሳስ በመተንፈስ ኢኮኖሚው መንኮታኮቱን ሲናገሩ የንግድ ስራዎች ከፓርቲ ድርጅቶች ውሽ በታም ተዳክመው እና ሞተው ያሉ ሲሆን የገንዘብ እንቅስቃሴዎች ጭራሽ ገደል መግባታቸውን እና ደንበኞች በባንኮች ላይ ያላቸው አመነታ በመጥፋቱ ግንኙነቶች መልፈስፈሳቸው በይበልጥ ለግል ባንኮች መዳከም ምክንያት ሆነዋል ሲሉ ይህ ደሞ አሉ የገንዝብ እንቅስቃሴውን ገድሎታል:: ምንሊክ ሳልሳዊ በጣም ድብን ያለ እውነት ነው::በውጭ ምንዛሪ ችግርና እጥረት ምክንያት በጣም የሚያስፈልጉ ዕቃዎች እንደተለመደው ከውጭ እየገቡ አይደለም፡፡ በጥቂቱ የመጡ ካሉም ዋጋቸው የማይቻል እየሆነ ነው፡፡ ብለውም አክለው አስቀምጠዋል::
ወያኔ አስፈላጊውን ገንዘብ ባለማግኘቱ ፕሮጀክቶች የቆሙ የተጓተቱ ሲሆን የሚሰበከው እድገት ለፕሮፓጋንዳዊ የሚዲያ ፍጆታ ብቻ መሆኑ ተረጋግጧል::ወያኔ የፋይናንስ ጥያቄውን ሊጨብጠው አይደለም ሊዳስሰው አልቻለም::በኢንቨስትመንት እንሰማራለን ብለው የመጡ የውጭው አለም ሰዎች በቢሮክራሲው መንተክተክ የተነሳ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ ትብብር ማግኘት አለመቻላቸውን ከመናገራቸውም በላይ የጀመሩት ኢንቨስትመት እንደሚቋረጥ የወያነ ባለስልጣናት እንደሚያስቆሟቸው እና ለምን ሲሉ መልስ የሚሰጣቸው አከል እንደሌለ እና ጨረታ ካሸነፉ በኋላ እንደሚሰረዝ ለማን እንደሚሰጥ እንደማያውቁ አማረው እየተናገሩ ነው::
ሌላው የሃገር ውስጥ ታዋቂ ነጋዴዎችን ጨምሮ የወያኔ ባላባቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያሸሹ መሆኑ ነው::የተረፈ ካለ ደሞ ወደ ባንክ ከመውሰድ ይልቅ ቤጅ መያዝ እየተመረጠ መቷል::አገር ውስጥ ደሞ ከማስቀመጥ ይልቅ ውጪ አገር መላክ እየተለመደ መቷል::ምንሊክ ሳልሳዊ አገር ውስጥ ባለው የውጭ ምንዛሪ ክምችት ላይ ተጨማሪ ጉልበት ሊፈጥር የሚገባው የውጭ ምንዛሪ ግኝትም ውጭ እንዲቀር እየተደረገ ነው፡፡ የገባ ካለም በጥቁር ገበያ እንደገና እንዲወጣ እየተደረገ በመሆኑ አገሪቱ ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም፡፡ብለዋል የስርኣቱ ታማኞች:; ይህ የሚያመለክተው ዜጎች በፖለቲካው ጉዞ ላይ እምነት እንዳሌላቸው ሲሆን እየተሽመደመደ እና እየደቀቀ ያለው የፖለቲካ ስራቲ ምንም ለውጥ ሊያመጣ አለመቻሉ ሰዎች በወንጀለኝነት ሳይሆን በአስተሳሰባቸው ወህኒ መውረዳቸው የፈጠረው ስጋት ነው:: ምንሊክ ሳልሳዊ
ዜጎች በህግ ላይ እና በንጽህናቸው ላይ ከመተማመን ይልቅ የህግ የበላይነት ከመጥፋቱ አንሳር እጅግ ፍርሃት ውስጥ በመግባታቸው የተማሩ እና በንግዱ አለም የተሰማሩ ሁሉ አፍርሃት ከመርበድበዳቸው እና ከመሰደዳቸው በላይ አሉ የተባሉትም ወያኔ በሙስና ባልደረቦቹ ላይ ፖለቲካዉ ገጀራ ሲያሳርፍ እየተመለከቱ ስራ በማቆም ከመደናበራቸውም ሌላ በራሳቸው አለመተማመን ያለባቸውን ጨምሮ በሙስናው ከባለስልጣናት ጋር የተነከሩ ሲሆን ሌሎች ደሞ እስከሚጣራ ለምን ልታሽ በሚል ባለው የፖለቲካ አመራሩ ላይ እምነት በማጣት የንግዱን ስራ ገለውት ከሃገር በመሸሽ ላይ ናቸው::
የተጭበረበረ አፋኝ ፖለቲካ ያስከተለው የኢኮኖሚ መንኮታኮት የአገሪቱን የፖለቲካ አናቶች ለውጥ እንዳያመጡ በመተብተብ ቀውስ ውስጥ የከተታቸው መሆኑን ከስብሰባዎች እና ከጭብጨባዎች ብዛት እየታዘብን ነው::በሌላ በኩል ሚዲያዎች ህዝብን መዋሸታቸው እና ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ መዋላቸው አገሪቷ እንድትንኮታኮት በር የከፈተ ሲሆን የዚህ መፍትሄ ስልጣን መልቀቅ ወይንም ሁሉን ህዝብ ያሳተፈ አዲስ ለውጥ እና ፖሊሲ ማጽደቅ ነው::ምንጭ በአደባባይ ወያኔን ይህን መርፌ የወጋቹህልንን (ያድነው/አያድነው) ባይታወቅም ውስጥ አዋቂዎች እናመሰግናለን::
ምንሊክ ሳልሳዊ

የሁለት አመት ህዝባዊ ንቅናቄ ዛሬም ተደገመ! (ድምፃችን ይሰማ)

January 24, 2014

የትግላችን ማረፊያ ድል ብቻ መሆኑን ዛሬም አውጀናል!

አርብ ጥር 16/2006
Ethiopian Muslims protest Jan 23, 2014
የዛሬዋ እለት ለህዝበ ሙስሊሙ ካለፉት ስድስት ወራት ለየት ያለ ክስተትን አስተናግዳ ያለፈች ጁሙዓ ነች፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ላለፉት ስድስት ወራት ለመንግስት በጥሞና የማሰቢያ ጊዜ ለመስጠት ከማንኛውም የአደባባይ የተቃውሞ ስነ ስርአቶች ተቆጥቦ ቆይቶ ነበር፡፡ መንግስት የእፎይታ ጊዜውን በአግባቡ ሊጠቀም ያለመፍቀዱ እንዳለ ሆኖ የሰላማዊ ትግሉን ሁለተኛ አመት ለማሰብም ‹‹730 ቀናት ለሃይማኖት ነጻነት›› በሚል ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ዘመቻ ታውጇል፡፡ የዛሬዋ ጁሙአ የዘመቻው ኦፊሴላዊ መክፈቻ ነበረች – ደማቅ መክፈቻ! ህዝበ ሙስሊሙ በበርካታ የአገሪቱ ከተሞች በሚገኙና የትግሉን መንፈስ አማክለው በቆዩ መስጊዶች በከፍተኛ ቁጥር ተሰባስቦ በመስገድ ለትግሉ ቀጣይ እርከን ሙሉ ዝግጁነቱን በከፍተኛ ወኔ አሳይቷል፡፡
በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ ከጁምአው አስቀድሞ መምጣት የጀመረው ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ አንዋርና አካባቢውን ለመሙላት ቅጽበትም አልወሰደበትም፡፡ የህዝቡ ቁጥር እንዲታይ ያልፈለጉት ፖሊሶች እንደተለመደው መኪኖችን ለህዝቡ በማስቆምና መስገጃውን እንዲያነጥፍ በመፍቀድ ፋንታ ለመከልከልና ግርግር ለመፍጠር የሞከሩ ሲሆን ለማረጋጋት የሞከሩ ወጣቶችንም ለማሰር ሙከራ አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ መዲና ህንጻ ላይ የኢቲቪ ካሜራዎች ተደግነው ህዝቡን ሲቀርጹ የነበሩ ሲሆን ህዝቡም በመሸማቀቅ ፋንታ እነሱኑ መልሶ ሲቀርጻቸው ማየት በእርግጥም አስገራሚ ነበር፡፡ ከጁምአው ስግደት በኋላ ደማቅ የዱአ ስነስርአት ተደርጎ ሰው የተበተነ ሲሆን በመምጫና መመለሻ ሰአቶችም በድልና ነስር ኒያ የአንድ ብር ሰደቃ ለችግረኞች ተሰጥቷል፡፡ በሺዎች ፊት ላይ ይታይ የነበረው ደስታና የማይሸነፍ ወኔ በእጅጉ ማራኪ እንደነበር ሁላችንም እዚያው የመሰከርነው የትግላችን ደማቅ ትእይንት ነበር፡፡
የክልል ከተሞችም እንዲሁ በከፍተኛ ድምቀት መርሀ ግብሩን አከናውነዋል፡፡ ለአዲስ አበባ አጎራባች በሆነችው አዳማ ከተማ አቡበክር መስጂድ በህዝበ ሙስሊሙ አሸብርቆ መዋሉና የዱዓና የሰደቃ ፕሮግራሙም ባማረ ሁኔታ መጠናቀቁን ማወቅ ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ በጂማ ፈትህ መስጂድ ደማቅ ሆነ የዱአና የሰደቃ ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በቀደሙ ደማቅ ተቃውሞዎቻቸው የሚታወቁት ሻሸመኔና መቱ ከተማም በደማቅ ሁኔታ ለትግሉ ያላቸውን አጋርነት ገልጸው አልፈዋል፡፡
ካሁን ቀደም የመንግስት የሀይል እርምጃ ሰለባ የነበረችው አጋሮ ከተማም በአል አዝሀር መስጂድ ላይ በከፍተኛ ቁጥር ለጁምአ በተገኘው ህዝበ ሙስሊም ዱአና ሰደቃ ደምቃ ውላለች፡፡ በዚያው በኦሮሚያ ክልል በደሌ ከተማ የሚገኘው መስጂደ ራህማ ላይም ተመሳሳይ ደማቅ ፕሮግራም ተካሂዶ የዋለ መሆኑ ተዘግቧል፡፡
ካሁን ቀደም በራሷና በሀምሳ ያክል በዙሪያዋ በሚገኙ ወረዳዎች ላይ አስገራሚ ተቃውሞ ያካሄደችው ዶዶላ ከተማም በፈትህ መስጂድ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝበ ሙስሊም አስተናግዳ ውላለች፡፡ በዶዶላ በኢማሙ አማካኝነት ከሰላት በፊት አላህ ትግሉን ለድል እንዲያበቃው ዱአ የተደረገ ሲሆን ሰደቃውም በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል፡፡ ዶዶላ በጥልቅ ዱአ ውስጥ ሆና ሳለች በርቀት በደምቢ ከተማ የሚገኙ ሙስሊም ነዋሪዎች ደግሞ በታላቁ መስጂዳቸው ተሰባስበው ተመሳሳይ የአጋርነት ፕሮግራም እያካሄዱ ነበር፡፡
በግዙፍ የቀደሙ ተቃውሞዎቿ የምትታወቀው ወልቂጤም የዛሬው የጁምአ ውሎ ተጋሪ ነበረች፡፡ በረቢእ መስጂድ የተሰባሰቡ ምእመኖቿ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል አጋር መሆናቸውን አስመስክረውባት ውለዋል፡፡
ገና በማለዳው ከ 50 ሺህ በላይ በራሪ ወረቀቶች ተበትነው ያደሩባት የደሴ ከተማም በዳውዶ መስጂድ በተሰባሰቡ ሙስሊም ነዋሪዎቿ አማካኝነት እስከ ድል ጫፍ የሚያብበውን የትግል ስሜት ያሳየች ሲሆን የዱአና የሰደቃ ፕሮግራሙም በድምቀት ተካሂዶባታል፡፡ በተመሳሳይ ሰአት በኸሚሴ ኹለፋኡ ራሺዲንም ደማቅ የዱአና የሰደቃ ፕሮግራም ተካሂዶ መዋሉ ታውቋል፡፡
በምስራቅ ኢትዮጵያ በሐረር ከተማ 4ኛ ኢማን መስጂድ፣ በአፋር ሎጊያ ከተማና በድሬዳዋ ከተማ አሸዋ ቢላል መስጂድ የተሰባሰቡ ሙስሊም ነዋሪዎችም ደማቅ የዱአና የሰደቃ ስነስርአት አድርገው ተመልሰዋል፡፡ በተመሳሳይ በሐዋሳ ከተማ ዐረብ መስጂድና ቤሎችም በርካታ ከተሞች ህዝበ ሙስሊሙ ዳግም ድምጹ አንድ መሆኑንና ወኔውም አንዳች እንዳልጎደለ ያለማወላወል አረጋግጦ አልፏል፡፡ /በተለያዩ የውጭ አገራት ከተሞች የተደረጉ ፕሮግራሞችን ለብቻ የምናወሳቸው ይሆናል!/
የዛሬው ስኬታማ መርሀ ግብር በተለያዩ ከተሞችና መስጂዶች የተደረገ ቢሆንም ያስተላለፈው መልእክት ግን አንድ እና አንድ ነው፡፡ ያም ህዝበ ሙስሊሙ ከድል ደጃፍ ሳይደርስ በምንም መልኩ ሰላማዊ ትግሉን እንደማያቆም ነው፡፡ ህዝበ ሙስሊሙ ዲኑ ላይ የሚሰነዘረውን ጥቃት እየተመለከተ እንዴትስ እጁን አጣጥፎ ሊቀመጥ ይችላል? ህዝብ የአገር ዋነኛ መሰረት መሆኑ እየታወቀ የሚፈጸምበትን በደል ተቋቁሞ የጥሞና ጊዜ መስጠቱስ እንደምን በስህተት ሊተረጎም ተገቢ ሆነ? አዎን! የዛሬው ከረጅም የጥሞና ጊዜ በኋላ የተደረገው መርሀ ግብር መልሶ ያለፈው እኒህን ጥያቄዎች ነው፡፡ ህዝብ እንደማይሸነፍና መንግስትም ለህዝብ ፍላጎት በትክክል ተገዥ እስኪሆን ድረስ ሰላማዊ ትግሉ እንደማይገታ፣ ብሎም ለድል መብቃቱ እንደማይቀር ልቦና ላለው ሁሉ ያስገነዝባል፡፡
በቀጣዮቹ ሁለት ሳምንታት የሚኖሩት መርሃ ግብሮች በሙሉ የሁለት አመት ትግላችንን በመንፈስም በተግባርም ድጋሚ እንድናልፍባቸው የታሰቡ ናቸው፡፡ ይህንን ደግሞ ዛሬ ‹‹ሀ›› ብለን ስንጀምር በህዝብ ውስጥ የተቀጣጠለ ቁጣ መብረጃው ድል ብቻ እንደሆነ ባመለካተ ህዝባዊ ወኔ ነው፡፡ ቀጣዩ የትግላችን ጉዞ እንቀደሙት ሁሉ ህዝባዊ መሰረቱን ይዞ ይቀጥላል፡፡ አሁን የምንገኝበት የእፎይታ ጊዜ በትግላችን ውስጥ እንዳለፉት እና እንደሚመጡት ምዕራፎች አንዱ ወሳኝ እርከን ነው፡፡ የእፎይታ ጊዜውን በዓላማው አምኖበት እና ለኢስላማዊ አንድነት ቅድሚያ ሰጥቶ፣ የመንግስት ግብታዊ አካሄድ እና ለከት የለሽ የጭቆና መብዛት የፈጠሩበትን ቁጣ ዋጥ አድርጎ ለመርሁ ተገዥ የሆነው መላው ሙስሊም ማህበረሰብ ‹‹የጀግኖች ጀግና›› ቢባል ያንሰው ይሆን?
በትግል ላይ መስዋእት መሆን እና በትእግስት መፅናት ሁሉም የአንድ ትግል ማዕዘናት ናቸው፡፡ ይህን መስፈርት ደግሞ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በተግባር እያሳየን እንገኛለን፡፡ ላለፉት ሁለት አመታት በጀግንነት እና በመሰዋእትነት ፀንተናል፡፡ ዛሬ ደግሞ የቀደመውን ጀግንነታችንን እንደያዝን በትግል ቃልኪዳናችን ፀንተናል፤ ወደፊትም እስከድል ደጃፎች ድረስ ጸንተን እንቀጥላለን፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!
‹‹ሁለት ጁሙአዎችን በሁለት አመት የትግል ወኔ!››
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

Friday, January 24, 2014

Ethiopia Has a Terrible Human Rights Record – Why Is the West Still Turning a Blind Eye?

january 24/2014

Eleanor Ross
Writer and journalist based in London
The Huffington Post

Some disappeared, others were given lengthy prison sentences. One thing all thirty men arrested in 2012 in Ethiopia had in common was that they had criticised the state and the policies of the former Premier, Meles Zenawi.Human Rights Charter look ever more vulnerable

And yet last week Japan’s Prime Minister Shinzo Abe and a group of Japanese business leaders met with the current Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn to discuss further support for Ethiopia at “government and private sector level.”

The former Meles Zenawi was a staunch supporter of American counter-terrorism policy while at the same time overseeing a country with a violent human rights record. In the eyes of the USA, Ethiopia is strategically situated. Located in the Horn of Africa, next to Somalia, northern Kenya and Sudan, it acts as a buffer zone between the growing Islamic extremism of Somalia and the West. As a result, the human rights violations of Zenawi were ignored.

As one of the first signatories of the UN in 1948, Ethiopia is a Western ally: 11 per cent of its entire GDP comes from Foreign Aid. The US is one of Ethiopia’s largest donors: it is estimated that it gave $3.3bn in 2008 alone. The two countries benefited from their close relation: there have been rumours that America hosted “black sites” in Ethiopia; bases where the CIA interrogated undeclared prisoners during the “War on Terror.”






















.


But Meles Zenawi died in 2012. The opportunity for a more liberal government was not seized: Zenawi was replaced by Hailemariam Desalegn, described by critics as an “identikit Zenawi” running the country on “auto-pilot”. Desalegn is following the same political manifesto as Meles – he hasn’t changed one member of parliament

The arena for debate and discussion is narrowing. Critics argue that Ethiopia is fast becoming a “one party democracy” where there are many parties but the same one wins again and again. Meles spoke to foreign press in 2005 and defended his 97 per cent electoral victory: “In democracies the party with the best track record remains in power.” The years since 2005 have seen growing unrest among the Ethiopian population and serious repression against critics of the regime. Human Rights Watch reported that Ethiopia “continues to severely restrict freedom of movement and expression”. It adds that “30 journalists and opposition members have been convicted under…vague anti-terrorism laws”.

The day before World Press Freedom Day on May 2 2013, the Ethiopian government ruled to uphold the imprisonment of one of its most well-known prisoners of conscience, Eskinder Nega. He was jailed for being a journalist who criticised the government, and yet, by standing up for his beliefs and expressing his basic human right for Freedom of Speech, he earned an 18 year jail sentence.

Prime Minister Hailemariam Desalegn has denied his release. America and Britain have done little to challenge their ally, so worried are they about creating another enemy in the Horn of Africa. Britain and America have consistently failed to challenge their ally about its abhorrent Human Rights record. Ethiopia flaunts its apathy towards the UN convention of Human Rights, denying opposition members a right to fair trial and repressing people for trying to voice their opinions peacefully.

Ethiopian political repression is worsening. There have been repeated crackdowns against the country’s Muslim minority. This has included arbitrary arrests as Muslims make peaceful demands for freedom of worship. Again, critics have voiced concern with the regime. Mehari Taddele Maru, head of the African Conflict Prevention Program at the Institute for Security Studies expressed concern that “if legitimate grievances are not met then there is a risk that extremist violent elements will exploit those grievances to further their own.”

The world is waking up to Ethiopia’s increasingly poor human rights track record and yet the United States hasn’t stopped aid flowing to Ethiopia or threatened the country with sanctions. Japan still tries to conduct business with Ethiopia when instead they should be holding Ethiopia to account.
As a founding member of the UN and an “ally” of the West, Ethiopia must be held accountable for her crimes. If the West does not challenge Ethiopia and demand that it releases its prisoners who have been locked up without fair trial, then notions of democracy and human rights accountability as embedded in the Human Rights Charter look ever more vulnerable-Human Rights globally will be laughed out of the door.

Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

የውጭ ኢንቨስተሮች የመንግሥት ተቋማት ለሙስና የተጋለጡ ናቸው አሉ

January 24/2014

በኢትዮጵያ ኢንቨስት በማድረግ ላይ የሚገኙ የውጭ ኢንቨስተሮች በሙስና ላይ ስላላቸው አመለካከት ለማወቅ በተካሄደ ረቂቅ ጥናት አብዛኛዎቹ ኢንቨስተሮች መንግሥት የሚያካሂዳቸው ግዥዎች ግልጽነት እንደሚጎላቸው አመለከቱ፡፡

በመንግሥት ተቋማት ጉዳይን ለማስፈጸም ከፍተኛ ሙስና መኖሩን ገለጹ፡፡

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ከለጋሾች ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ሰላም ዴቨሎፕመንት በተባለ ኩባንያ አማካይነት ባስጠናው ረቂቅ ጥናት፣ መንግሥት የሚያካሂዳቸው ግዥዎችና ኮንትራቶች ግልጽነት እንደሚጎድላቸው ኢንቨስተሮቹ አመልክተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለረቂቅ ጥናቱ ምላሽ የሰጡ የውጭ ኢንቨስተሮች አራት አገልግሎት ሰጪ መሥሪያ ቤቶችን ከፍተኛ ሙሰኞች ብለዋቸዋል፡፡ በረቂቅ ጥናቱ ላይ ዛሬ በሒልተን ሆቴል ውይይት ይደረጋል፡፡

በኢትዮጵያ ኢንቨስት በማድረግ ላይ የሚገኙ 350 ኩባንያዎችን ቃለ መጠይቅ በማድረግ ረቂቅ ጥናቱ ተዘጋጅቷል፡፡ ኢንቨስተሮቹ ከላቲን አሜሪካና ከአንታርቲካ በስተቀር 42 አገሮችን የሚወክሉ ናቸው፡፡

ጥናቱ በሦስት ጉዳዮች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን፣ እነሱም ሕግና ደንብ፣ የቢሮክራሲ ማነቆና ቢዝነስ ለመሥራት ያለው ቅለትና የሙስና ሁኔታ ናቸው፡፡

ከ350 ምላሽ የሰጡ ኢንቨስተሮች መካከል 20 በመቶ የሚሆኑት የመንግሥት የግዥ ኮንትራቶች ክፍያ የሚፈጸመው ግልጽ ባልሆነ መንገድ ነው ይላሉ፡፡ አገሪቱ ውስጥ ቢዝነስን ለማቀላጠፍ አስቸጋሪ መሆኑን የገለጹት ደግሞ 71 በመቶ የሚሆኑት ናቸው፡፡ ለዚህ በዋናነት ያነሱት ምክንያት ሙስና መንሰራፋቱን ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ውስብስብ የሆነውን የግዥ ሒደት በእንቅፋትነት ጠቅሰዋል፡፡

በሌላ በኩል 67.4 በመቶ የሚሆኑ ምላሽ የሰጡ ኢንቨስተሮች በበኩላቸው፣ በቢሮክራሲ ምክንያት የሚገጥሙዋቸውን ችግሮቻቸውን ለመፍታት ለመንግሥት ባለሥልጣናትና ሠራተኞች ጉቦ እንደሚሰጡ ሲገልጹ፣ የተወሰኑት ደግሞ ጉዳያቸውን በፍጥነት ለማስፈጸም ጉቦ ከመስጠት ሌላ አማራጭ ስለሌላቸው ጉቦ እንደሚሰጡ በረቂቅ ጥናቱ ተመልክቷል፡፡

እነዚህ ኢንቨስተሮች በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ያላቸው የሙስና ደረጃ በጥናቱ በመቶኛ ተገልጿል፡፡

በረቂቅ ጥናቱ ምላሽ ከሰጡት መካከል 18.9 በመቶ ያህሉ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ 8.3 በመቶ ትራንስፖርት ባለሥልጣን፣ 7.4 በመቶ የመሬት አስተዳደርና 6.5 በመቶ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ከፍተኛ ጉቦኛ መሥሪያ ቤቶች ናቸው በማለት ገልጸዋቸዋል፡፡ ይህ ረቂቅ ጥናት ዛሬ በሒልተን ሆቴል ውይይት እንደሚደረግበት ታውቋል፡፡

የፀረ ሙስና ኮሚሽን ቀደም ሲል ኪሊማንጃሮ በተባለ የውጭ አገር አማካሪ ኩባንያ አማካይነት ባካሄደው ጥናት፣ ኢትዮጵያውያን በአገሪቱ ስላለው የሙስና ሁኔታ ላይ ያላቸውን አስተያየት ማቅረቡ አይዘነጋም፡፡

በዚህ ጥናት በፍትሕ አካላትና በበርካታ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ጥያቄ የቀረበላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች በተቋማቱ ላይ እምነት እንደሌላቸው መግለጻቸው ይታወሳል፡፡  

Thursday, January 23, 2014

እነ አንዷለም አራጌ ነገ ሰበር ሰሚ ችሎት ይቀርባሉ፤ ሕዝብ ችሎቱን እንዲከታተል ጥሪ ቀረበ

Andualem Arage
በዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ዘንድ የ2005 ዓ.ም የዓመቱ ምርጥ ሰው የሚለውን ስያሜ ያገኘው የሕሊና እስረኛው አንዷዓለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንንና ክንፈ ሚካኤል ደበበ ነገ ጥር 16 ቀን 2006 (ጃንዋሪ 24 ቀን 2014) በሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርቡ ከቤተሰቦቻቸው አካባቢ የተገኘው መረጃ አመለከተ። እነዚህን የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚፈልጉ ወገኖች 6 ኪሎ የሚገኘው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት እንዲገኙ ጥሪ ቀርቧል።
በአንካሳው የኢትዮጵያ የሽብር ሕግ ከግንቦት 7 ጋር በማያያዝ ሽብር ለመፈጸም በማቀድ በሚል እድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዷአለም አራጌ በ እስር ቤት በመሆንም በጽናት በመታገል የሰላማዊ ትግል አርማ ሆኗል በሚል በብዙዎች ዘንድ ይወደሳል። ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዷዓለም አራጌ የተላለፈበትን ዕድሜ ልክ እስራት ፍርድ፤ እንዲሁም ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ የተላለፈባቸውን ቅጣት ለታሪክ ለመተው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት እንዲታይ የወሰዱት ሲሆን ነገ ሰበር ሰሚ ችሎቱ የሚሰጠው ውሳኔም በቤተሰቦቻቸው ዘንድ በትልቅ ተስፋ እንደሚጠበቅ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
ነገ በስድስት ኪሎ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ሲሰየም እነ አንዷለም አራጌም አብረው የሚቀርቡ ሲሆን የሚታገሉለትና መስዋዕትነት እየከፈሉለት የሚገኘው ሕዝብ በችሎቱ በመገኘት ይህን “ፍትህ የምትዋረድበትን ወይም ፍትህ የምትታይበትን” ታሪካዊ ቀን እንዲመለከት ከቤተሰቦቻቸው እና ከወዳጆቻቸው ጥሪ ቀርቧል። ይህን ተከትሎም በፌስቡክና በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች “እነ አንዷለም ፍትህ ያግኙ፤ ይፈቱ” የሚለው ቅስቀሳ ቀጥሏል።
ዘ-ሐበሻ 

Wednesday, January 22, 2014

በቂልንጦ ታስረው ሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ሶላት መከልከላቸውና በጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው ላይ ድብደባ እንደተፈፀመበት ታወቀ፡፡

January22/2014

በቂልንጦ ማረሚያ ቤት ዞን ሁለት ውስ ታስረው የሚገኙ እስረኞች መካከል በተነሳ ፀብ ምክኒያት በአንድ ታሳሪ ላይ ድብደባ እንደተፈፀመበት የታወቀ ሲሆን ይህን ግለሰብ ያስደበደባችሁት እናንተ ናችሁ በማለት በዞን ሁለት ውስጥ የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴዎችና ሌሎች ወንድሞች የመግሪብ የኢሻና የሱብሂ ሶላት እንዳይሰግዱ ተከልክለዋል፡፡
በዞን ሁለት ውስጥ ኡስታዝ ባህሩ ኡመር ኡስታዝ ሰኢድ አሊ ጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው አርቲስት ሙኒር ሁሴን የሚገኙ ሲሆን ጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው የእምነት ትዛዛችንን መፈፀም ህገ መንግስታዊ መብታችን ነው ብሎ በመጠየቁ ለብቻ ተወሰዶ ድብደባ እንደተፈፀመበት ለማወቅ ተችልዋል፡፡ በህግ ጥላ ስር የሚገኙ ታሳሪዎች ተገቢውን ጥበቃና ሰብአዊ ህገ መንግስታዊ መብታቸው መከበር እንዳለበት ህገ ቢደነግግም ይህን መብታቸውን በመጣስ ወከባና ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደ ሆን የቢቢኤን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም በድርድር ለየብቻችሁ ስገዱ የተባሉ ሲሆን በጋራም የመስገድ መብት አለን በማለት የሱፍ ጌታቸውም ሌሎቹም በጋራ እየጠየቁ እንደነበር ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡
የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የመከላከያ ምስክርነት ቀናት በተቃረቡበት ጊዜ መሰል እርምጃዎችን መወሰዳቸው የህዝቡን ትኩረት ለማስቀየስ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን የሚሰጡም አሉ፡፡ በነዚህ የህዝበ ወኪሎች ላይ የሚፈፀሙ የህግ ጥሰቶች በመላው ህዝበ ሙስሊም ላይ የሚፈፀሙ ናቸውና መንግስትን ለጉዳይ ትኩረት በመስጠት እርምት ማድረግ አለበት ሲሉ የቢቢኤን ምንጮች አክለው ገልፀዋል፡፡