Saturday, August 10, 2013

ከፖለቲከኞች በላይ ገኖ የወጣው “ድምጻችን ይሰማ”

ኢህአዴግ አክራሪነትን እየጋበዘ ነው!!


የሰላማዊ ትግል ምንነት ለማይረዱ ትልቅ ትምህርት የሰጠ፣ ኢህአዴግ ፍጹም የሆነ ልምድ ባካበተበትና ኤክስፐርት በሆነባቸው
የትግል ስልቶች ብልጫ ወስዶ ለማንበርከክ እንደሚያስቸግር፣ ሰላማዊ ትግል ከራስና ከስሜት ጋር የሚደረግ ታላቅ አስተምህሮት መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። የድምጻችን ይሰማ ትግል በዚህ መልኩ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ሆኖ ይቆያል” በግል አድራሻ ከተላከ አስተያየት የተወሰደ። በአሃዝ፣ ጉዳቱ በሚገለጽበት መጠን፣ ጉዳቱ የሚገለጽበት ደረጃና የቋንቋው አቅም ልዩነት  ካልሆነ በስተቀር ሁሉም ወገኖች፣ የውጪ ታዛቢዎች፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት፣ ራሱ ኢህአዴግ፣ ህወሃትና መላው ወዳጆቹ በአንድ እውነት ይስማማሉ። እሱም ህወሃት ራሱ ባመጣው ጣጣ፣ ራሱ ትዕዛዝ ሰጪ ሆኖ ያደረሰው ሰብአዊና በቀላሉ ሊበርድ የማይችል መከራ እንደሆነ በየአቅጣጫው አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ያለ ምንም ማጋነን ኢህአዴግ ደም አፍሷል፣ ህይወት ቀጥፏል፣ አስሯል፣ ገርፏል፣ ፈንክቷል፣ ጣጣው ለሌሎች የሚተርፍ አካሄድ በመከተሉ ችግሩን አወሳስቦታል። ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ርምጃ የሚወስደው “ከብዙ ትዕግስት” በኋላ መሆኑን “በመንግሥት ወግ” ቢገልጽም “የሚያምነው ያገኘ አይመስልም” የሚል ወቀሳም ይሰነዘርበታል። እንደውም “ለየትኛዋ የሚወዳት አገር” በሚል ለፕሮፓጋንዳ አፉን በከፈተ ቁጥር ዘለፋ እየወረደበት ነው።
ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል የሚሉ ወገኖች አሉ። እነዚህ ወገኖች ገለጻቸው ለሌላው ግራ የሚያጋባ አባባል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። ግን በነሱ እምነት ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል። አቅም አልባ ያደረገው “የድምጻችን ይሰማ” የትግል ስልት ነው። ኢህአዴግ ያለውና 4የሚታወቅበት መለያው የታጠቀው መሳሪያ፣ ወታደሩ፣ የፌደራል ሃይሉ፣ የክልል ፖሊስ፣ ፈጥኖ ደራሹ፣ የሰላምና መረጋጋቱ ፣ የስለላ ሃይሉ፣ የአጋዚ ጦሩ፣ የአንድ ለአምስት አወቃቀሩ … ከሁሉም በላይ ደግሞ ጉልበተኛነቱን የሚቆጣጠሩለት የአንድ ብሔር “ታማኝ” ሃይሎች መሆናቸው እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ።
“ኢህአዴግ አለኝ የሚለውን ጉልበቱን መጠቀም ቢፈልግም መድረኩን ‘በተጠና’ የትግል ስልት በሚፈልገው ደረጃ ሊጠቀም አለመቻሉ በደጋፊዎቹና በራሱ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “የሙስሊሞች እንቅስቃሴ፣ የዕዝ ሰንሰለታቸውን ጠብቀው የሚያካሂዱት ትግል ኢህአዴግ ጉልበቱን እንዳይጠቀም ከልክሎታል። አሁን እየወሰደ ያለውና የወሰደው የሃይል ጥቃት ሊወስድ ከሚፈልገው ጋር ሲነጻጸር ሃይሉ ሽባ መደረጉን ያሳያል፤ ይህ ደግሞ የሰላማዊ ትግል ውበት ነው” ሲሉ ኢህአዴግ በገባው ጭንቅ መጠን ርምጃ ባለመውሰዱ እንደሚቆጭ ይናገራሉ። በሌላ አነጋገር የሽብር፣ የማሸበርና የመግደል “ጠቢብ” ለሆነው ኢህአዴግ አሁንም ችግሩ የሚፈታው በሃይል፣ በባሰ ሃይል እንደሆነ ከማመን አላፈገፈገም ሲሉ ያብራራሉ።
ኢህአዴግ ነገሮችን እያባባሰ የሰላማዊ ትግሉን ወደ አመጽ ለማስቀየር ሃሳብ ቢኖረውም “የድምጻችን ይሰማ ህብረት አስቀድሞ መረጃ የማግኘትና በሰላማዊ ትግል ተክኖ መገኘት ኢህአዴግ ያሰበውን እንዳይፈጽም አድርጎታል” በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። እነዚህ ክፍሎች ኢህአዴግ “አክራሪነትን የሚሰብኩና የሚያቀነቅኑ አሉ” በማለት ለሚለፍፈው “እስካሁን የአክራሪ ሙስሊም እንቅስቃሴ ስለመታየቱ መረጃ የለም። ከተፈጠረም አክራሪነት እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆነው ራሱ ኢህአዴግ ነው። ደም ማፍሰሱን አጠናክሮ በቀጠለና ዜጎችን ማሰሩ በገፋበት ቁጥር ለመሞት የሚዘጋጁ ዜጎች አገር ውስጥ የመኖራቸውን ያህል የወንድሞቻቸውን ጭፍጨፋ በመመልከት የመስዋዕትነቱ ተካፋይ ለመሆን ዓለምአቀፋዊ የሙስሊም ኅብረተሰብ ቁጣ ያስተባብርና ራሱን ችግር ላይ ይጥላል፤ ለአገርም መከራ ይሆናል፡፡”
በተቃራኒው አክራሪነት እየተስተዋለ የመጣው አሁን እንዳልሆነ የሚናገሩ ክፍሎች “በአሁኑ ሰዓት አገራችን ውስጥ ያለው የሃይማኖት ውህደት ቀደም ሲል እናቶቻችንና አባቶቻችን በየዋህነት ሲያደርጉት እንደነበር አይነት ነው ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው” በማለት ይናገራሉ። በማያያዝም እንዲህ ያለው ስጋት በሰላማዊ ትግል ጉልበት አልባ የሆነውን ኢህአዴግ ሃይል እንዲያገኝና ይህንን ሃይል እንዲተማመን አድርጎታል ሲሉ ይከራከራሉ።
ኢህአዴግ መስከሩን፣ አንጎሉ መዞሩንና የሚያደርገው እንደጠፋው የሚናገሩ ክፍሎች እንደሚሉት የኢድ ቀን ኢቲቪ ያሰራጨውን ዜና ቀላል ምሳሌ አድርገው ያቀርባሉ። የድምጻችን ይሰማ መነሻ ምክንያት የሆኑትን አዲሱን የመጅሊስ መሪ በቴሌቪዥን መስኮት አቅርቦ 2“ሙስሊሞች ላይ የወሰዳችሁትና የምትወስዱት ርምጃ የሚደገፍ ነው፣ ትክክል ነው” በማለት ያቀረበው ቃለ ምልልስ “ከስካርም በላይ አዙሪት ነው” ሲሉ የኢህአዴግን የበሽታ መጠን ይገልጻሉ። ሙስሊሙን አንኳን አሰራችሁት፣ ደበደባችሁት፣ ገደላችሁት በሚል ደረጃ “ደግ አደረጋችሁ፣ ርምጃችሁ ትክከል ነው” በማለት ዜና ማሰራጨቱ ኢህአዴግ በራሱ ሚዲያ በችግሩ ላይ እሳት ማርከፉን የሚያመላክት ስለመሆኑ በማሳያነት ያቀርባሉ።
አንድ ጤና ያለው መንግስት የህዝብ ቁጣ ሳይለሳለስ፣ የቁጣውን መንስዔ አደባባይ በማቅረብ “ተጎዳን በሚሉ የህብረተሰብ፣ በተለይም የአንድ እምነት ተከታዮች ፊት ማዘፈን ኢህአዴግን የያዘውን የስካር የዞረ ድምር (ሃንግኦቨር) የማሽተት ያህል ነው” የሚሉት ክፍሎች ኢህአዴግ ቢያንስ ለራሱ፣ ህወሃትና ቁንጮው ላይ ሆነው ሃብት ለሰበሰቡት ሲል እርቅ ሊወርድ የሚችልበትን መንገድ እንዲያስብበት ይመክራሉ። ጉዳዩንም በጥበብ እንዲይዘው ይመክራሉ።
በሙስሊም ወገኖች አወሊያ የተጀመረው የድምጻችን ይሰማ ጥያቄ፣ የኢህአዴግ የጥያቄው አያያዝ ችግር ተዳምሮበት የእምነቱ ተከታዮች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተቃውሞው እየተዳረሰ ይገኛል። የአገሪቱን ሙስሊሞች ከጫፍ እስከጫፍ በሚያስገርም የግንኙነት መረብ እያስተባበረ የሚነደው ሰላማዊ ቁጣ የሌሎች እምነት ተከታዮችን ድጋፍ አለማግኘቱን ለኢህአዴግ ሃይል እንደሆነው የሚናገሩ ወገኖች “ይህንን አስመልክቶ በሚቀርበው መረጃ ግራ ተጋብተናል” ይላሉ።
“እንኳን የሌላውን ሃይማኖት የራሳቸውን ሃይማኖትና ስርዓት ማስጠበቅ ያቃታቸው የክርስትናው ሃይማኖት ተከታዮች፣ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ደገፉ ተብሎ ሲዘገብ ዘገባው ሚዛን የሚደፋ አይሆንም” በማለት የሚከራከሩ ክፍሎች “የክርስትና እምነት ተከታዮች ለእምነታቸው ሊሰጡ የሚገባውን ክብር ከድምጻችን ይሰማ እንቅስቃሴ መማር ከቻሉ ይህ ብቻ በራሱ ይበቃል” በማለት በተቃራኒ ወቀሳ ይሰነዝራሉ። እንደውም የራሳቸውን የእምነት ቤት ማጽዳት ባለመቻላቸው ሊወቀሱ እንደሚገባ መረጃ በማጣቀስ ይከራከራሉ።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ላይ ካለው የረዥም ጊዜ የተቀነባበረ ሴራና የምንገኝበት የጂኦ ፖለቲካ ካሸከመን ጣጣ ጋር በማዳመር “ሜዳዎች ሁሉ ሸራተን ሆነው አይዋቡም” የሚል አስተያየት የሚሰጡ ክፍሎች “መተማመን ድሮ ቀረ” ሲሉ የሌሎች እምነት ተከታዮችን ዝምታ ይገልጹታል።
“ሙስሊሞች አብዛኞች በሆኑበት ቦታ ያለ ችግር ቢፈልጉ አክርረው፣ ቢፈልጉ አለዝበው እምነታቸውን ያራምዳሉ። አነስተኛ በሆኑባቸው አገራት ደግሞ ያለውን የአስተዳደር መሰረት የመጋራት ፈተና ይፈጥራሉ” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች “እነዚህ በሌሎች አገሮች የታዩ ተሞክሮዎች ከምዕራቡ መገናኛ ውስወሳ ጋር ተዳምረው በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ላይ ያስቀመጡት ጠባሳ ቀላል አይሆንም። ኢትዮጵያ ውስጥም ይህ ችግር አለ” ባይ ናቸው። በሌላም በኩል በማህበራዊ ድረገጾች አርሲ አርባ ጉጉና ጅማ የተከናወነውን በማንሳት ሰሞኑንን ለመከራከር የሞከሩትን በመጥቀስ የፍርሃቻው ማሳይ አድርገው ያስቀምጡታል።
መሰረታዊ የእምነትና አመራር ጥያቄ በማንሳት ትግላቸውን በተጠና መንገድ የሚያካሂዱት የ”ድምጻችን ይሰማ” የትግል መስመር አስገራሚ እየተባለ ነው። ህብረታቸውና በተዋረድ የሚያካሂዱት መናበብ አስደማሚ ሆኗል። አልፎ አልፎ ከሚሰራጩ ወፍ ዘራሽ5 መልዕክቶች በስተቀር መሪዎችን በመከተል የሚያሳዩት ትብብር የሚያስቀና እንደሆነ እየተነገረ ነው። ተመሳሳይ ዓላማ ይዘው እርስ በርስ የሚቧቀሱት የተቃዋሚ የፖለቲካ ሃይሎች ከድምጻችን ይሰማ “የሰላማዊ ትግል” ቀመር ሊማሩና ይሁንታ ካገኙ ስልጠናም ሊወስዱ እንደሚገባ የሚናገሩ ተበራክተዋል።
እነዚህ ወገኖች እንደሚሉት የሙስሊም ወገኖች ጥያቄና ጥያቄያቸው መልስ ካላገኘ ወደኋላ እንደማይሉ በመደጋገም ይፋ እያደረጉ ነው። ኢህአዴግ ከተካነበት ድርጅቶችን የመሰንጠቅና “የእባቡን አንገት ቁረጥ” ከሚለው የአምባገነኖች መርሁ አንጻር ድምጻችን ይሰማ ውስጥ ዘልቆ መግባት አለመቻሉ አስገራሚ የሆነባቸው ጥቂት አይደሉም። ቅንጅት እንደ ሰደድ እሳት አገር አዳርሶ ኢህአዴግን ባስጨነቀ ማግስት “ሳሎኑ ተበርግዶ ኢህአዴግ ሲንቦጫረቅበት” የተመለከቱ፤ ዓመት ከመንፈቅ ያህል የዘለቀውንና ከዕለት ወደ ዕለት በብቃትም ሆነ የኢህአዴግን መሠሪነት በመመከት እንዲሁም የተጠና የትግል ችሎታ በማሳየት ወደር ያልተገኘለትን የድምጻችን ይሰማ ትግል ከማድነቅ ወደኋላ አይሉም። ለሌሎች ሲመክሩም የመስመርና የትግል አስተላለፍ ለውጥ ለማድረግ አሁንም ጊዜው እንዳላለፈ ሊገነዘቡት ይገባል በማለት ለሌሎች የሰላማዊ ትግል ምንነት ላልገባቸውና የገባቸው መስሏቸው ተስፋ ለቆረጡ ይመክራሉ፡፡
ይህ ሪፖርታዥ የተቀናበረው የዝግጅት ክፍላችን ካነጋገራቸው ወገኖችና በኢሜል ከተላኩ መልክዕክቶችና አስተያየቶች በመመርኮዝ ነው። ለንባብ እንዲያመች የአርታኢ ስራ ከመሰራቱ ውጪ ሙሉ ሃሳቡ የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ያሰፈሯቸው ነው። አሁንም በዚህ ጽሁፍ ላይ የቀረቡትን ሃሳቦች በማስፋትም ሆነ በመቃወም የሚላኩ ጽሁፎችን ለማስተናገድ ዝግጁ ነን።
(ፎቶዎቹ የተወሰዱት ከቢላል Tube Photos ድረገጽ ነው)
 The maleda times

የእስክንድር ዳግም መታሰር ቤተሰባችን እንዲበተን አድርጓል፡፡ሰርካለም ፋሲል


ሀምሌ16/2005 ዓ.ም. በጣም መጥፎና ጥሩ ስሜት የማይፈጥር ቀን ነበር፡፡ ቤተሰብን፣ ወዳጅ ዘመድን በተለይ የሚወዷትን ሃገር ጥሎ መውጣት ምንኛ ይከብዳል? ከሀገርስ በላይ ምን አለ? አፈር ፈጭቼ ካቦካሁባት፣ ተወልጄ ካደግኩባት፣ ክፉ ደጉን ካየሁባት አገሬ የመውጣቴ የመጨረሻ ቀን መቃረቡን ሳስብ በሕይወቴ አጋጥሞኝ የማያውቅ የመደበት ስሜት ውስጥ ነው የተዘፈቅኩት፡፡

 ከቤተሰብ፣ ከጐረቤት፣ ከወዳጅ ዘመድ የመለያየት መቃረቢያው ክፉኛ ያሳምማል፡፡ ከምንም በላይ በሀገር መኖር ክብር መሆኑን እረዳለሁ፡፡ ከሚወዷት ሃገር ተገፍቶ እና ተገፍትሮ መውጣት ከመርግ የከበደ መሆኑን አሁን መጨረሻው ላይ የግዴን አወቅኩት፡፡ በቅርብ የሚያውቁኝ “ሰርካለም ከምትንሰፈሰፍላት ውድ ሀገሯ ወጥታ ለመኖር እንዴት ጨከነች?” እንደሚሉ እገምታለሁ፡፡ ሀገሬን እጅግ እወዳታለሁና “እንደወጣሁ እቀራለሁ” የሚል ድምዳሜ ላይ አልደረስኩም፡፡

ደሕንነቴ አደጋ ውስጥ ሲወድቅ፣ ውክቢያና እንግልቱ ሲከፋብኝ ግን ለራሴ ብቻ ሳይሆን በአባቱ እስራት ለሚንገላታው ልጄ ስል ይሕን መወሰኔ ግድ ሆነብኝ፡፡ ቤተሰብ ያለው ሰው የሚሰማው የተለየ ስሜት ይኖራል፡፡ ለኔ ሕይወት የራሷ የሆነች ስም ካላወጣችለት በቀር ከመደበኛው የተለየች ሆናብኛለች ማለት እደፍራለሁ፡፡ ሁሌም በውክቢያና እስር፣ በማጠስጠንቀቂያና ማስፈራሪያ ሥር ሆኖ መኖር በእጅጉ ያስመርራል፡፡ የኔ ሕይወት ይሄ ነው፡፡ ባለቤቴ እስክንድር ነጋ ለእስር ከተዳረገ ዓመቱን ሊደፍን ከአንድ ወር ያልበለጠ ጊዜ ነው የቀረው፡፡ በእስር ቤት የተወለደው ልጃችን ናፍቆት እስክንድር ነጋ የአባቱ ናፍቆት እያሰቃየው፣ እንደ እኩዮቹ ከመፈንጠዝና ከመቦረቅ ርቆ በትካዜ ውስጥ መኖሩ በእጅጉ ሲያሰቃየኝ ቆየ፡፡ ከዚህ በኋላ በዚህ እየተሰቃየና እየተጎዳ መኖር አይኖርበትም፡፡

 በእስር ያጣው ውድ አባቱን በየሳምንቱ እያየው ከሚሰቃይ ከሃገር ርቆ “አንድ ቀን እንገናኛለን” የሚል ተስፋ ውስጥ ቢገባ የተሻለ ሊሆንለት እንደሚችልም አምኛለሁ፡፡ ማንም ወላጅ ይሕን ስሜቴን ይረዳኛል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ልጃችን ናፍቆት ዕድሜው ከሚችለው በላይ መከራ በመቀበል ከማናችንም በላይ ተጐድቷል፡፡ በትምሕርት ቤት ከአቻ ጓደኞቹ ጋር መጫወት ትቶ ብቻውን አቀርቅሮ መሬት ሲጭር ይውላል፡፡ “አባቴ መቼ ነው የሚመጣው?” ከሚለው የመናፈቅ ጥያቄው ጋር እየታገለ ትምሕርቱን መከታተል የማይችልበት ደረጃ ላይ ደረሰ፡፡ ሞራሉ እየወደቀ ሲሄድ ያየሁ መሰለኝ፡፡

 የወለድኩት ቃሊቲ ወሕኒ ቤት ስለሆነ እንደ እናት ተገቢውን እንክብካቤ እንኳን አላደረግኩለትም፡፡ ከሰው ተነጥዬ የምችለውን ላደርግለት የሞከርኩ ቢሆንም አንድ ሕፃን ሊደረግለት ከሚገባው በትንሹ እንኳን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ልጄ ባህሪው በእጅጉ ተለወጠ፤ ከሰው ጋር መግባባት ተቸገረ፤ ዝምታንና ለብቻው መገለልን ምርጫው አደረገ፡፡ ሰው ይፈራል፤ ከእኔ ከእናቱና ከወንድሜ ጋር ብቻ የሚግባባው ናፍቆት ከሌላ ሰው ጋር መግባባት አልሆንለት አለ፡፡ እኛ ተጐድተን… በስነ ልቦና የተጐዳ ልጅ መፍጠር አይኖርብንም፡፡ እኔና ልጄ ከእስር ስንፈታ፣ አባቱ ተመልሶ ወሕኒ ከወረደ በኋላ ደግሞ የልጃችን የባህሪ ለውጥ እየከፋ ሄደ፡፡ እስቲ ለሰከንዶች ብቻ እንደ አንዲት እናት ሆናችሁ አስቡት፡፡ ማንም የወለደው ልጅ ሲጐዳበት ማየት አይፈልግም፡፡ ዘጠኝ ወር አርግዤው በ1998 ዓ.ም. በእስር ቤት የወለድኩት ናፍቆት እስክንድር ነጋ ላለፉት ሠባት ዓመታት የገፋው የሰቆቃ ኑሮ እንዲበቃው መፈለጌ ነው ወደማልፈልገው ስደት እንዳመራ ያስገደደኝ፡፡ የውክቢያ ዘመኑ ያኔም ዛሬም ፈፅሞ አልተቀየረም፡፡

ባለቤቴ እስክንድር ያለ ፍትሕ መታሰሩ፣ እኔና ናፍቆት የምንመራው የሰቆቃ ሕይወት የብዙሃን ግፉአን ኢትዮጵያውያን ሕይወት ግልባጭ ነው፡፡ በጠመንጃ ታጅቤ ፖሊስ ሆስፒታል የወለድኩት፣ የሕፃንነት ጊዜው የቃሊቲ እስር ቤት በር ተዘግቶበት ያሳለፈው የምወደው ልጄ አዕምሮው እንዳይጎዳ ለጊዜው ከስደት የተሻለ አማራጭ አላገኘሁም፡፡

ጉዞ ወደ አሜሪካ የጉዞዬ ዓላማ ኑሮን በአሜሪካ ማድረግ አይደለም፡፡ የአሜሪካን የተንደላቀቀ ኑሮ ብንፈልግ ኖሮ እኔም ሆንኩ ዛሬ እስር ላይ የሚገኘው ባለቤቴ እስክንድር ነጋ ልጃችንን ይዘን ቀድመን ከሀገር በወጣን ነበር፡፡ እስክንድር ለዓመታት አሜሪካ ኖሮ በሃገሩ ሃሳብን የመግለጽ መብት “ኤክሰርሳይስ” ለማድረግ ነው የመጣው፤ እኔም ብሆን አሜሪካ ደርሼ የተመለስኩት ሃገሬን ስለምወድ እንጂ ሌላ ጥቅም ስላለ ነው፡፡ ሁለታችንም ከሃገር የመውጣት ሃሳቡ አልነበረንም፤ ዛሬ የእኔው ግድ ሆነ፡፡ የልጃችን የአእምሮና ስነ ልቦና ጉዳይ በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደረሰ፡፡ ናፍቆት እስክንድር ነጋ ከሰኞ እስከ አርብ በትምሕርት ቤት ሲናውዝ ቆይቶ፣ የቅዳሜና እሁድ የዕረፍት ቀኑን እንደ እኩዮቹ መዝናኛ ቦታ ሣይሆን ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ነው የሚያሣልፈው፡፡ ናፍቆት ለአባቱ ያለው ፍቅር የተለየ ነው፡፡ እስክንድር ዳግም ሲታሰር ልጃችን ናፍቆትን ከትምህርት ቤት እያመጣ እንደነበር ይታወሳል፡፡ መሣሪያ የታጠቁ ፖሊሶች እስክንድርን ሲይዙት፣ ልጃችን ናፍቆት “አባቴን ልቀቁት” እያለ ያለቅስ ነበር፡፡ ይህንን ክስተት እስኪ ለአፍታ መለስ ብላችሁ አስቡት፡፡ እስክንድር ነጋ በሃገሩ የሚኖር ሕጋዊ ሰው፣ ቋሚ አድራሻ ያለውና ፖሊስም ሆነ የደሕንነት ባልደረቦች በፈለጉበት ጊዜ ጠርተው ሊያስሩት እንደሚችሉ ግልጽ ነው፡፡ ልጁን ከትምህርት ቤት ሲያወጣ ጠብቀው በጠመንጃ ከበው፣ እየደነፉ የያዙት እሱንም ሆነ ልጃችንን ለማሳቀቅ እንደሆነ ማንም ሰው ይረዳዋል ብዬ አምናለሁ፡፡ በወቅቱ እስክንድርን የያዙት ሰዎች የልጅ አባት ይሆኑ ይሆናል፡፡ እነርሱ በእስክንድርና በናፍቆት ላይ ያደረሱት ሽብርና ማሸማቀቅ በራሳቸውና በልጆቻቸው ቢፈፀም ምን ሊሰማቸው እንደሚችል ለመገመት ለምን እንደተቸገሩ አይገባኝም፡፡ እናም “ምነዋ! ሰርካለም ከሀገር ወጣች” ብላችሁ ለጠየቃችሁ ምላሼ ይድረሳችሁ፡፡ ወደአሜሪካ የጉብኝት እድሉን ከቅርብ ወዳጃችን ነው ያገኘነው፡፡ ልጄ የተወሰነ ቢሆን ቦታ መቀየር የራሱ የሆነ እገዛ ይኖረዋል ድምዳሜ ላይ በመድረሴ ግብዣውን ተቀበልኩት፡፡ የስማችን መጠሪያ፣ ሃገር ተረካቢው ልጃችን በኛ ዳፋ ሞራሉ ደቆ ሲጐዳ ከማየት እንዲያገግም ስል ይኸው ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጉዣለሁ፡፡ (ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሁሌም ያንብቡ)
እስክንድርን ጥሎ መሄድ ባለቤቴ እስክንድር ነጋ እስር ላይ ነው፡፡ የቃሊቲን አታካችና አሰልቺ ጉዞ ተቋቁሞ “ማን ስንቅ ያቀብለዋል?” የሚለው ጥያቄ ውሳኔዬን እንድቀለብስ ሞግቶኝ ነበር፡፡ እሱን ጥሎ መሄድ እጅግ ከባድ ነው፡፡ ለእኔ፣ ላንተ፣ ላንቺ መብት አይደል የታሰረው? እና ለእኔ ሲል ታስሮ እሱን ጥሎ መሄድ እንዴት እደፍራለሁ፡፡ እስክንድር የልጃችንን ጉዳት በመረዳቱ ከሃገር ርቀ ቢቆይ የተሻለ ነገር እንደሚየገኝ ሲያግባባኝ ዓመት አልፎታል፡፡ እስካሁን ሳልቀበለው ቆይቻለሁ፡፡ አሁን ግን እስክንድርም አመረረ፡፡ “ልጃችን ሲጎዳ እምቢኝ ከሃገር አልወጣም ያልሽኝ አንቺ ከእኔ የተሻለ አንፃራዊ ነፃነት ስላለሽ (ስላልታሰርሽ)፣ ነው” የሚለውን ግፊት አጠነከረው፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜየት በተደጋጋሚ ወዳጆቻችን የእረፍት ቪዛ ሲልኩልን አሻፈረኝ ብዬ ሳቃጥለው የነበረውን ዕድል ማክተሙን ተረዳሁት፡፡ እስክንድር “እኔ የታሰርኩበት አላማ አለኝ፤ በዚህች ሀገር ፍትህና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን አሁንም ትግሌ ይቀጥላል፤ በእስር ቤት የተወለደው ልጄ ግን አዕምሮው ከዚህ በላይ መጐዳት አይኖርበትም፡፡ እና በአፋጣኝ እረፍት እንዲያደርግ ብለሽ ውጡ” ነው ያለኝ፡፡ በሣምንት አራት ቀን የምጠይቀው ባለቤቴን መራቅ ቢከብደኝም በአንድ ነገር ግን ገዘተኝ፡፡
“እስክንድር ቢታሰርም አይሟሟም፤ እኔ ስለፍትህ፣ ነፃነትና ዴሞክራሲ የምናገር እንጂ አሸባሪ አይደለሁም፤ ልጄ ደግሞ በኔ እስር የአባቱን ፍቅር አጥቶ መጨነቅና አእምሮው መጐዳት የለበትም፤ ሲያድግ ጥሩ አእምሮ ኖሮት ሀገሩን እንዲያገለግል ውሳኔዬ ነው” የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሱ የጉዞ ውሳኔ ላይ አድርሶኛል፡፡ እናም የእሱን ቃል ማክበር ስላለብኝ ይህን አደረኩ፡፡ ውድ ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቼና እህቶቼ እኛ ማለትም ባለቤቴና እኔ ወደ አሜሪካ የምንሄድበት እድል ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ተፈጥሮልን ነበር፡፡ ግን ለምን ሀገራችንን ለቀን አንሄዳለን ብለን ነው የወሰን ነው፡፡ የኔም ሆነ ባለቤቴ አቋም ተመሳሳይ ነው፡፡ በተለይ ባለቤቴ እስክንድር ነጋ ስለዴሞክራሲ ከሀገር ወጥቶ መታገል በሚለው ነገር ላይ ፈፅሞ እምነት የለውም፡፡ ሰላማዊ ትግል በሀገር ውስጥ ማድረግ ነው የሚል እምነት አለው፡፡ ከዛ በመነሣት ነው ብዙ የቆየ ነው፡፡ አሁን ግን የልጃችን አእምሮ እየተጐዳ በመምጣቱ መቼም ወላድ ….ኢትዮጵያዊ ይመስክር የልጅን ነገር የወለደ ያውቀዋልና ለዛም ስንል የተወሰነ እረፍት ቢያገኝ ብለን ወደ አሜሪካ ይዤው ለመሄድ ተገደድኩ፡፡ ይህ ህፃን በእስር ላይ ተወልዶ የቤተሰብ ፍቅር ያልጠገበ ባይተዋር ልጅ ሆነብን፡፡ በሁሉም መጐዳት የለብንም ልጃችን በእኛ ስህተት ሣይሆን እኛ በምናደርገው ትግል ሁሌም መታሰራችን የፈጠረበት የቤተሰብ እንክብካቤ ማነስ ተጐዳ፡፡ አያት ወይም አጐት እንደ ወላጅ ሆኖ ለማሣደግ ይቸገራል፡፡ ለሀገራችን ስንታገል የልጃችን ጭንቅላት ጐዳት እስክንድርንም እኔንም ለውሣኔ አበቃን፡፡ እስክንድር ብቻውን አይደለም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በቃሊቲ “ዞን 2″ እየሄድ ይጠይቀዋል፡፡

ያለፉት ስድስት አመታት በ1998 ዓ.ም. ታስረን ከእስር ከተፈታን በኋላ ምናልባትም የስድስት አመታት ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ ለእስክንድር የከበደ ጊዜ ነበር፡፡ የጋዜጣ ፈቃድ አውጥቶ በሞያው ለመንቀሣቀስ ቢፈልግም ፈቃድ የማግኘት እድል ግን ፈፅሞ ማግኘት አልቻለም፡፡ ከዛ በኋላ በፖለቲካዊ ትንታኔዎች ዙሪያ መንቀሣቀስ ጀመረ፡፡ እስክንድር እንደሌሎች ከሀገር እንደወጡ ፖለቲከኞች ውጭ ሆኖ ድምፁን ማሰማት ይችላል፡፡ ግን የእሱ አላማ ህጋዊና ዴሞክራሲያዊ በመሆኑ በሀገር ውስጥ መንቀሣቀስ ጀመረ፡፡ ያ ነገር ግን በጠላትነት አስፈርጆት ሁሌም በክትትል ሕይወት ውስጥ እንዲኖር አደረገው፡፡ እስክንድር ሁሌም “በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ክትትል ስር የወደቀ ነበር” ቤታችን ይጠበቃል፣ እሱም ነፃ ሆኖ መንቀሣቀስ አልቻለም፡፡ እሱን ለመጠየቅ የመጣ፣ ከእሱ ጋር የቆመና የተነጋገር ችግር ይገጥመዋል፡፡ የሰቆቃ ዘመን ነበር ያሣለፈው፡፡ በመጨረሻም ታሰረ፡፡ ዳግም መታሰር ይከብዳል፡፡ እስክንድር ባለፉት 20 አመታት ወይም በኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ” የፕሬሱ ፋና ወጊ ነው” ግን በእስር እጁን እስከመሰበር ደርሷል፡፡ ከአሜሪካ ሀገር ድረስ መጥቶ በዚህች ሀገር ላይ ስለዴሞክራሲ ፣ ነፃነትና መብት የሚናገር ማነው እናም እነዚህ ያለፉት ስድስት አመታት እጅግ ውስብስብና አስቸጋሪ የሆኑ ጊዜያት ነበሩ፡፡
የወጣትነት ዘመን እኔ የወጣትነት ዘመን ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ እኔና እስክንድር ስንገናኝ የ21 አመት ወጣት ነበርኩ፡፡ ከዛ ጊዜ ጀምሮ የመዋከብና በዚህ ሕይወት ዙሪያ የመረጋጋት ሕይወት ሣይኖረን ቆይተናል፡፡ ወጣትነት ብዙ ነገር ማለት ነው፡፡ “ፈፅሞ አላውቀውም” ከእድሜ እኩዮቼ ጋር ሆኖ መዝናናት ፣ በእኔ እድሜ ላይ የምትገኝ ወጣት ልታደርግ የሚገባውን ነገር ፈፅሞ አድርጌ አላውቅም፡፡ በእኛ ስር ሦስት ጋዜጦች ነበሩ፡፡ ምኒልክ፣ አስኳልና ሳተናው፡፡ ሦስቱም በሣምንቱ ውስጥ ይወጣሉ፡፡ እነዚህን ማዘጋጀት መምራት ምን ጊዜ ይሰጣል፡፡ ለዛውም የፖለቲካ ጋዜጣ ማዘጋጀት ቀላል ነገር አይደለም፡፡ በዚህ በሦስት ጋዜጣ ስር ደግሞ ምን ያህል ሠራተኞች አሉ፡፡ እናም ወጣትነቴን አላውቀውም፡፡”ወጣትነት ምንም እንደሆነ ስለወጣትነት የተፃፈውን መፅሐፍ ከማንበብ ባለፈ ይህ ነው የሚባል የወጣትነት ትዝታ ፈፅሞ የለኝም፡፡” በበርካታ ውጣ ውረድ ውስጥ ነው ወጣትነቴን ያሣለፍኩት፡፡ ያ አልፏል ብዙም አልቆጭበትም፡፡ ከዚህ በኋላ ወጣት የሚባል ደረጃ ላይ አይደለሁም፡፡ ባለፉት ጊዜያትም የምቆጭ አይደለሁም፡፡ ስለዴሞክራሲ ስሰራ በመኖሬ ደግሞ እኮራለሁ፡፡
የእስክንድር ዳግም እስር ምን ፈጠረ; የእስክንድር ዳግም መታሰር ቤተሰባችን እንዲበተን አድርጓል፡፡ ማንም ኢትዮጵያዊ በሕይወቱ ሊያደርጋቸው ከሚገባቸው ነገሮች መካከል በትዳር ተጥምሮ ወልዶ መኖር ነው፡፡ ይህ ግን ለእኛ የተፈቀደ አይደለም፡፡ እስክንድር ከጥሩ ቤተሰብ የወጣ ጥሩ አቅም ያለው ነው፡፡ የእሱ ቤተሰብ ምንጭ ጥሩ ነጋዴ ሆነን ተንደላቀን እንድንኖር ያደርገናል፡፡ ግን አልሆነም፡፡ የእሱ ቤተሰብ ንብረት ፈፅሞ በሚገርም መልኩ ሽብርተኛ በሚል ተወረሰ፡፡ በመጨረሻም ይኸው ዳኛ ቤተሰብ በተነ፡፡ እስክንድር 18 አመት ተፈረደበት፡፡እኔም ለልጄ ጭንቅላት ስል ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ወዳጅ ዘመድ በፈጠረው እድል ተጠቅሜ ወደ አሜሪካ አመራሁ፡፡ ይገርማችኋል እኛ ሰላማዊ ነን ልጃችን አፍ ፈቶ መናገር ከቻል በኋላ አብረን ለመኖር መታገዳችን ምን ያህል ያስቆጫል፡፡ እስክንድር በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና ፍትህ የእውነት ካልሰፈነ በቀር በአደባባይ ቢሰቀልና ቢሰቃይ ቦታ የለውም፡፡ ግን ልጃችን ለምን ይሰቃይ የሚል እምነት አለው፡፡ ማንም ቢሆነ የልጁን ስቃይ ማየት አይወድምና፡፡
የሀገር ነገር ይህንን ስል እንባዬ ምን ያህል በአይኔ ላይ እየወረደ እንደጠረኩት አውቃለሁ፡፡ ያለቀስኩበት ዘመን አልፏል፡፡ …. ሀገሬን እወዳለሁ፡፡ ግን መልካም አስተዳደርን እመኛለሁ፡፡ ከሀገሬ አልርቅም ፣ ወደ ሀገሬም እመለሣለሁ፡፡ እኔና ባለቤቴ ለልጃችን ስንል እንጂ የደረሰብን በርካታ ስቃዮች የጐዳን አይደለም፡፡ እናም ሁሌም ቢሆን ኢትዮጵያን እወዳለሁ፡፡ ከሀገሬ መራቅ የምፈልግ አይደለሁም፡፡ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር፡፡ እስክንድር ነጋ ሀገሩን የሚወድ አሜሪካ መኖር እየቻለ ስለሀገሩ ሲል ቃሊቲ /ማረሚያ ቤት/ መኖሪያው የሆነ ሰው ነው፡፡

በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩ የሰው አረሞች

August 9, 2013
ዳኛቸው ቢያድግልኝ

Tigray People Liberation Front Splitአረም ማለት ያልተዘራበት የሚበቅል ገበሬ የዘራውን ሰብል የሚሻማ፣ ውሀውን የሚጠጣበት፣ ለበሽታና ተባይ መጠለያ በመሆን ለሰብል ጉዳት ምክንያት የሚሆን እጽዋት ማለት ነው። አረም በስሮቹ አማካይነት የሰብሉን ስር አንቆ የሚገድል፣ አንዳንዱም እንደ ፓራሳይት ሰብል ላይ ተጣብቆ የሚበቅል እንደ አቀንጭራ ያለ ማለት ነው። አረሞች በፈጣን አስተዳደጋቸው ሳቢያ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ከመሬት የፀሀይ ብርሃን ከሰማይ በመሻማት የሚያቀጭጩና የሚገድሉ ናቸው። የስንዴ ማሳ ውስጥ የበቀለ በቆሎም እንኳ ቢሆን አረም ነው፣ ገብስም ቢሆን አረም ነውና ተነቅሎ ይጣላል።

አረም ዘሩን በማባዛትና የመኖር እድሉን ለማራዘም በርካታ ዘዴዎችን እየተጠቀመ በብዛት የሚንሰራፋና በወቅቱ ካልታረመ ሰብል የሚያጠፋ ነው። ጎበዝ ገበሬ አርሞና ኮትኩቶ ሰብሉን ካልተንከባከበ በሰብል ምርት ምትክ አረሙን ማፈስ ይገደዳል። ልክ እንደ ምሳሌው ኢትዮጵያዊነትን የሰው አረም ውጦታል። ፀረ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት አቋምን የያዘ በሌሎች ስም ይልቁንም በትግሬ ስም ኢትዮጵያዊነት ላይ ተጣብቆ አገር እያፈረሰ ያለ የዘራፊ ቡድን አገርና ሕዝብ እያቀጨጨ ነው። ወያኔ በቆሎና ማሽላ ላይ ተጣብቆ እንደሚበቅል አቀንጭራ (ፓራሳይት፣ ጥገኛ አረም) ኢትዮጵያዊነትን ተጣብቶ ኢትዮጵያን እየገደለ ያለ ቡድን ነውና ተነቅሎ መጥፋት አለበት። በምስሉ የተቀረጹ ‘ኦፖርቹኒስት’ ገንጣዮችና ከፋፋይ ድርጅቶችም እንዲሁ።

ስንዴ ማሳ ላይ የበቀለ ገብስ አረም የመሆኑን ያህል ኢትዮጵያዊነትን አቀጭጮ የሚገድል ኢትዮጵያዊም ቢሆን የሰው አረም ነውና ተነቅሎ ሊጣል ወይም ለፍርድ ሊቀርብ ይገባዋል። ምንጫቸው ትግራይ ስለሆነና የትግራይ ተገንጣይ ግንባር ነኝ ስላሉም የትግራይ ሕዝብ ውክልና የላቸውም። በመጀመርያ እኒህ የሰው አረሞች ጭካኔና ግድያን የተለማመዱት  ኢትዮጵያዊነትን ከፍ ያደረጉ የትግራይ ተወላጆችን በማደን መሆኑን እናውቃለን። የታታሪ ገበሬን ምሳሌነት የመጠቀሚያ ጊዜው እየረፈደ ቢሆንም አረም ለማጥፋት በደቦ መጠራራት የመጨረሻው የመኖር ያለመኖር ተስፋችን ነው። እያዩ ማለቅንም እለት በእለት እየተለማመድነው ከብት ወደ መታረጃው እንደሚነዳው አቅመ ቢስነት ውስጥ ከገባን ያበቃልናል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አምርረው በሚጠሉ ሰዎች ጥፋት ምክንያት ኢትዮጵያን ልንጠላ ግን አይገባም። ሰሞኑን ሰላማዊ ሕዝብ ላይ በሚደርሰው ጭፍጨፋ ኢትዮጵያዊነታቸውን እስኪጠሉ ድረስ የሚማረሩት ወገኖች ምሬታቸው ከፍቶ ሰው መሆናቸውን እስኪጠሉና የሚፈራውና ለብዙዎች ጥፋት ምክንያት የሚሆነው የአጥፎ መጥፋት እልቂት እስኪመጣ መጠበቅ ሞኝነት ነው።

በሀገራችን ገበሬው የአረም ማጥፊያ መርዝ የሚጠቀመው ጥቂቱ ነው። የገንዘብ አቅም ስለሚያንሰው መርዛማነቱም ለሌላው ስለሚተርፍ። ልክ እንደዚያው ወያኔን ለማጥፋት የድርጅት አቅም አንሶናል ወደ መሳርያ ማንሳቱ ሁሉም እየተገፋ ከመጣ ለብዙ ህይወት መጥፋትም ምክንያት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ገበሬዎች አረምን ለማጥፋት አንድ ግሩም ባህል አላቸው። ያም ደቦ፣ ጅጊ ወዘተ የሚባልና ተጠራርቶና ተሰባስቦ በህብረት ማሳቸውን ከአረም ማጽዳት የሚችሉበት መንገድ። ተመሳሳይ ብልህነት ከጠፋንና እያማረርን ዘመን ከቆጠርን ተራ በተራ አንዴ የተበደሉ ጎሳዎች አንድ ሰሞን፣ የተፈናቀሉ ወገኖች በሌላ ሰሞን፣ ክርስቲያኖች አምና እስልምና ተከታዮች ዘንድሮ፣ ሴቶች ትናንት፣ ወጣቶች ዛሬ ልላ እያልን በወረፋ መታረድን ልንለማመደው የግድ ይሆናል። አንዱ በሌላው ሞት ዝም በመሰኘት አጥፊዎቻችንን ጉልበት እየሰጠ፣ እነርሱም እየናቁንና እያፌዙብን በመጨረሻም አገር እንዲያሳጡን መፍቀድ የለብንም። ሕዝቡና የፖለቲካ ድርጅቶች ተበታትነው እየሮጡ ሲያልቁ የሰው አረሞች እየተሰፋፉና እየተመቻቸው መኖር የሚችሉበትን ሁኔታ እያመቻቹ የመቀጠል መዘናጋት ሊያበቃ ይገባል።

ዛሬ ያስቸገረንና የከበደን ሀገር በቀል አረም ነው ነገ ግን ጉልበተኛና ጨካኝ አንዴ እግሩን ከተከለ ማጥፊያ መንገድ የሌለው መጤ አረም ይውጠናል። በዚህ ከቀጠልን የዛሬዎቹ አረሞች ነገ ስማቸውን ለኛ ሰጥተውን እኛ እንደ አረም በመርዝ እናልቃለን። በዚህ ከቀጠልን ካሁኑ በከፋ ሁኔታ እንሰደዳለን እንሳደደለንም። ተቆጥቶ ለመነሳት በጣም አርፍደናል ባለቀ ሰዐትም እንኳ ቢሆን ለመነሳቱ ዛሬ ከነገ ይሻላል። ወያኔዎች በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩና ሀገሪቱ የጦርነት ቀጠና ሆና እነሱ ወታደራዊ ስርዐትን አስፍነው ያሻቸውን እየገደሉ ለመኖር እየጣሩ ነው። አምባገነኖች ሁሌም በጦርነትና በቀውስ ሁኔታ ውስጥ መኖርን ይመርጣሉ።

ምክንያቱም ሰላም ሲሆን እነርሱ መመለስ የማይችሉአቸው የመብት ጥያቄዎች ስለሚነሱ በስልጣን መቆየት አያስችላቸውም።

በፖለቲካ ድርጅትም ይሁን በጎበዝ አለቃ ሕዝቡ መንደሩን ሊያጸዳ ገዳዮቹን ለፍርድ ሊያቀርብ የሚችል ሀይል እንደሆነ ጠላቶቹ ሊያውቁት ይገባል። ተደጋግሞ እንደተገለጸው ወያኔ እርጉም ጠላት እንጂ መጥፎ መንግስት አይደለም። የሕዝብ ክብርና የሰዎች ነጻነትም አይገባውምና ተነቃቅሎ ሊጣል የሚገባው አረም ሊወገድ የሚገባው የሀገር ጠላት ነው።

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከነፃነት ሰንደቅዓላማችን ጋር ለዘለዓለም ይኑርልን!

biyadegelgne@hotmail.com

በተለያዩ አካባቢዎች ሙስሊሞች ታፍሰው እየታሰሩ ነው

ነሃሴ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱ መረጃዎች እንዳመለከቱት በ ኢድ አል ፈጥር እለት የፌደራል ፖሊሶች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የወሰዱትን እርምጃ ተከትሎ ሌሊቱንና ዛሬም በርካታ ሙስሊሞች ከቤታቸው እየተወሰዱ ታስረዋል።

በአሁኑ ጊዜ በትክክል የታሰረውን ህዝብ ቁጥር ለማወቅ ባይቻልም   በሺዎች እንደሚቆጠር ይገልጻሉ። በዛሬው እለትም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከእስር ተፈተዋል።  ድምጻችን ይሰማ እንደገለጸው ደግሞ በትናንትናው ተቃውሞ አንዲት ነፍሰጡርን ጨምሮ 5 ሰዎች ተገድለዋል። ኢሳት የማቾቹን ቁጥር በትክክል ለማወቅ ጥረት ቢያድርግም አልተሳካለትም፤ አንዳንድ ሙስሊሞች በሚደርስባቸው ከፍተኛ ችግር እየተማረሩ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራም አልተሳካም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የሙስሊሙን  ጥያቄ በኃይል ለመፍታት መሞከሩ በአስቸኳይ እንዲቆም፣ የእምነት ነፃነት ስለጠየቁ የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱና ተጠያቂዎች ለህግ እንዲቀርቡ ጠይቋል።

ሁለት ዓመት ለመሙላት ጥቂት ወራት የቀረውን የሙስሊም  ሠላማዊ የመብት ጥያቄ እንዲያከብር፣ መንግሥት በእምነት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን እንዲያቆምና ያነሷቸውን ጥያቄዎች በአስተውሎት በማየት እንዲሁም ወደ ውይይት በመምጣት ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ እንዲሰጥ ፓርቲው ሲያሳስብ መቆየቱን አስታውሷል።

መንግሥት የህዝብ ጥያቄዎችን በኃይል ለመፍታት የሚወስደው ርምጃ ከሰብአዊ መብት ጥሰት ባሻገርም በህግ የሚያስጠይቀው ተግባር መሆኑን የገለጸው ፓርቲው፣  ከዚህ በፊት ሲጠቀምባቸው የነበሩት የመፈረጅ፣ ሽብርተኛ እያሉ የማሰር፣ የማዋከብና የመግደል ስትራቴጂዎች ህዝቡ መብቱን ለመጠየቅ ወደ ኋላ እንዲል የሚያደርጉት አይደሉም ብሎአል፡፡

አንድነት ” መንግሥት ፊት ለፊት የቀረቡ ጥያቄዎችን መመለስ አለመቻሉ ሳያንስ እንደገና ወደ ኃይል ርምጃ መመለሱ ሀገርን አደጋ ላይ የሚጥል፣ አስተውሎት የጎደለው አካሄድ እንደሆነ ገልጾ፣  አሁንም ከዜጎች እየቀረቡ ያሉ የመብትና የነፃነት ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ” ጥሪ አቅርቧል።

በተመሳሳይ ዜናም የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የወሰዱትን እርምጃ በጥብቅ አውግዟል።

Friday, August 9, 2013

SMNE Warning to the TPLF/EPRDF to Uphold Its Constitution

August 9, 2013

Stop Unlawful Acts of TPLF/EPRDF –Sponsored Terrorism Against Ethiopian Muslims or Face Future Charges

Ethiopians of Muslim faith have taken to the streets of Ethiopia to peacefully demand religious freedom in Ethiopia. According to their demonstration organizers, the numbers of protesters will increase to new levels of participation in the coming days and weeks; while at the same time, the TPLF/EPRDF government warns of new cracks down, some of which have already taken lives, injured young and old and resulted in the arrests of thousands of political prisoners.

This is no easy issue to resolve. Freedom of religion is close to the hearts of millions of Ethiopians, not only Muslims but all people who seek to pursue their faith and conscience without restriction. This has created a deadlock where the TPLF/ERPDF’s position is unsustainable without making concessions; however, based on past actions, it is highly doubtful that the TPLF/EPRDF will take the necessary steps to prevent the situation from escalating out of control, especially if the TPLF/EPRDF-sponsored violence against civilians is continued.

The Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) strongly urges the TPLF/EPRDF and all its security forces to genuinely uphold the Ethiopian Constitution, first by not interfering with the legal right of Ethiopian citizens to peacefully protest. Any violence at the hands of the TPLF/EPRDF or others, resulting in injury or murder, that is directed at unarmed, peaceful protesters may be considered acts of terrorism against the Ethiopian civilians. Those individuals involved, both those giving the orders and those executing them, may be charged with terrorism in due time. Under international laws, perpetrators may also be charged with crimes against humanity. We caution the TPLF/EPRDF to not harm any peaceful protestors during this legal protest even more so because your government is already becoming increasingly known for its serial human rights violations against innocent Ethiopians.

Secondly, as Ethiopian Muslims protest TPLF/EPRDF interference in their internal religious affairs, we urge the TPLF/EPRDF to relinquish control of religious organizations, a right given to all Ethiopians in the Constitution of our country yet also denied to Ethiopians of other religious traditions, like Ethiopian Orthodox, Evangelicals, Jews and others.

According to organizers, Ethiopian Muslims seek religious freedom within a secular society where all Ethiopians have the same freedom of worship along with other basic rights. They have called on the TPLF/EPRDF to follow the Constitution; however, this struggle for religious rights is not new. The TPLF/EPRDF has waged a decades-long assault on religious organizations and people of faith which now includes government control of Muslims leaders and educators, forcing leaders of their own choosing on Ethiopian Muslims. Those chosen to lead the Supreme Council of Islamic Affairs are leaders who will not challenge TPLF/EPRDF authority and who are also seeking to impose the teachings of a Middle Eastern sect of Islam, strongly opposed by Ethiopian Muslims.

The TPLF/EPRDF has also exerted pressure on the Ethiopian Orthodox Church to accept leaders of their choosing, ensuring cooperation with the regime. As a result, the church is split in two, one in exile and one in Ethiopia. This is against the law. Recently, Gebremedhin Araya, the former TPLF head of finance and a close colleague of former Prime Minister Meles Zenawi, revealed just how calculating, determined and brutally executed was the TPLF plan to destroy both Islam and Christianity in Ethiopia, starting in the Tigray region. Please click at the link to read Gebre Medhin Araya piece, http://ecadforum.com/2013/07/27/who-were-they-then-who-are-they-now/ He also names those allegedly involved, many of whom still maintain positions of power within the TPLF/EPRDF.

The Marxist-Leninist underpinnings of the revolutionary democracy of the TPLF/EPRDF have been hostile to our Ethiopian people of faith from its onset. The assault on religion was carried out with similar brutality from the beginning of the TPLF (TLF) rebel movement—with murder, kidnappings, disappearances, and widespread intimidation. It continues today. This attempt to diminish belief in God and the moral authority of religious organizations was also clearly laid out in the TPLF/EPRDF strategic plan from 1993. Please click at the link to read the TPLF/EPRDF strategic plan http://www.enufforethiopia.net/pdf/Revolutionary_Democracy_EthRev_96.pdf. This plan, which was distributed to TPLF/EPRDF members as a means “to establish hegemony and perpetual rule”, provides documentary evidence backing up Ato Gebremedhin Araya’s allegations.

Part of this plan included the infiltration of religious groups in order to counter their influence and use them to serve the goals of the TPLF/EPRDF.

“In the process of countering these [religious] organizations’ influence, the focus should not be on the leadership but rather on their branches at the village level; the religious leaders at the grassroots level are closer to the people. Without denying them [religious organizations] due respect, we should mold their views, curtail their propaganda against Revolutionary Democracy, and even use them to serve our end. Focus on the lower level does not mean the upper echelon should be forgotten. We should forge a close relationship with this stratum, find out and exploit to our advantage their internal contradictions, and at least disable them from coordinating their propaganda against us. If possible we should use them to disseminate the propaganda of Revolutionary Democracy.”[i]
As many shudder at the evil intent of the TPLF/ERPDF to destroy sincere religious practice, no one can deny the TPLF/ERPDF’s success in intruding into the affairs of Ethiopian religious institutions.

 Ironically, the hope of a more just, caring, equitable and reconciled Ethiopia may rest on the shoulders of those people of sincere faith who can provide the moral strength, healing and direction necessary for the restoration of Ethiopia. People of diverse faiths may work together for the common good in ways unseen before this time.

For eighteen months, Ethiopian Muslims

 have been protesting government religious interference without incident. They have shown respect towards others and there has been no violence or destruction of property. However, in the past months, the TPLF has arrested countless Muslim leaders and/or organizers of the protests and desecrated their mosque.

In the last few weeks, the TPLF/ERPDF have increased the use of violence. In the cities of Kofale and Tatolamo, the TPLF/EPRDF used excessive force against unarmed civilians that led to the killing of innocent people, including women, children and elderly persons. The death toll now stands at twenty-five. 

On August 8, the TPLF/ERPDF attacked Muslims in Addis Ababa, Dessie, Welkite and Afar as they celebrated Eid Mubarak. According to reports we received from people on the ground, many were seriously injured after being beaten with bats, the barrels of guns and other objects. Countless others were arrested. Eyewitnesses told the SMNE that the injured were denied treatment at local hospitals due to orders from the TPLF/EPRDF. A pregnant woman died of her injuries.

We are very disturbed by these testimonies; however what is encouraging is how the injured were not only helped by other Muslims, but how Christians who lived nearby came to their rescue to help the injured. This is further evidence that this is not a religious issue between people of differing faiths but about government suppression of religion and other basic rights.

These Christians who came out to help their fellow Ethiopians, even bringing the wounded into their homes, were connected by their shared humanity. When they were hurt, the Christians were there to help them. People of faith must stand together like this even while holding differing beliefs.

Ethiopian Muslim woman, attacked by government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
Ethiopian Muslim woman, attacked by government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
 
As the TPLF/EPRDF commits increasing acts of violence, propaganda is being spread that their violence is necessary in response to Muslim extremists. This has not been part of the history of Muslims in Ethiopia but instead is a deliberate attempt to slander Ethiopian Muslims when it is increasingly apparent that it is the TPFL/EPRDF that has been committing acts of violence. The trademark of this regime, even when in the bush operating as a gorilla rebel movement, was to create false flag operations where members of the TPLF committed acts of terrorism while posing as the enemy. At that time, the U.S. State Department had classified the TPLF as a terrorist group and little has changed.

We have previously spoken of other more recent false flag acts perpetrated for political and economic reasons, including one in Addis Ababa that appeared in Wiki leaks where the TPLF/EPRDF set bombs in Addis Ababa in order to blame, charge and arrest various opponents to the regime. Another example relates to a prior planned Muslim protest several months ago that was called off after its leaders learned of TPLF/EPRDF plans to hijack the peaceful demonstration by posing as Muslim protestors and burning the American flag.

No one should assume that any violence that might occur in future protests is the fault of the protestors. Instead, we believe the most likely perpetrators will be the TPLF/ERPDF, who should have the burden of proving any future allegations against Muslims in an unbiased, independent court of law. No one trusts the TPLF/ERPDF anymore.

The TPLF/EPRDF’s tactic of using false flag operations, threats and violence to silence the legitimate rights of Ethiopian Muslims is wrong. If they were people of violence, they would have shown this in the last nearly two years; however, Ethiopian Muslims, Christians, Jews, animists and non-believers have lived together in harmony for centuries. It is this ethnic-based government that has been trying, with little success, to incite division between religions.

Ethiopian Muslim and Christians make up almost our entire population of our nation. The background of both of our faiths, along with the Jews, comes from the line of Abraham; giving us a common origination of our belief in one God.  Even though we still have differences of belief, we Ethiopians have gotten along quite well for many hears until more recently when the ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF has been using our religion to divide us.

We, Ethiopian Muslim, Christians and Jews are more than neighbors; we are part of the Ethiopian family and part of the human family. We not only share the land, but the blood that runs through our veins has been passed on to us by shared ancestors. Our safety and survival depends on each other and we need to be there for members of our family. This is something demonstrated by our Ethiopian ancestors before us and we should treasure this legacy.

Our ability, as diverse religious people, to live together with respect, tolerance and peace is a cause for celebration in this world where Ethiopia is one of the few countries who have achieved this. Muhammad told his followers many years ago to find safety in this great land of ours. That tolerance is visible by going to a Christian church and finding a follower of Jesus Christ by the name of Mohammed or going to a Muslim mosque and finding someone named Peter worshiping Allah. The brothers and sisters around them worship together without suspicion or fear. This also goes back to the reality that there are many mixed families in Ethiopia where the husbands are Christians and wives are Muslims or vice versa; yet, unlike in some places in the world, there is no fear within or between families.

This Ethiopian tradition of respecting the independence of religious beliefs is unique in the world and many outsiders do not know this. Now this religious freedom is being attacked by the ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF as they are trying to make us fear, dehumanize and demonize one another. They used these same tools to reduce us to being “those others” or “tribes” or “collections of people unlike us” rather than human beings created by one God.

All of us Ethiopians must stand together as one people against the TPLF/EPRDF’s policy and reject extremism of any kind: ethnic extremism, Muslim extremism, Christian extremism, tribal extremism and feudal extremism. All of these should be discarded if we want to get our country out of the mess it is in and to pass on a healthy Ethiopia to our descendants. Some of the non-Muslim Ethiopians may be suspicious of those rallying for their religious rights, saying that what they want is different from what we want. This is exactly the reaction TPLF/EPRDF regime is looking for.

The TPLF/EPRDF’s brutal crackdown may be driven by several fear-based goals: 1) to maintain control of religious organizations because moral authority is a threat, 2) to alienate and divide Muslims from people of other faiths so there is no unity against your authoritarian rule, 3) to gain international support and financing for fighting the War on Terror by disguising the truth that these protests are based on legitimate legal rights and have been conducted in a peaceful manner from the start, and 4) out of fear the TPLF/ERPDF will collapse and violence will break out against power-holders.

The SMNE is deeply concerned that this last scenario be pro-actively avoided by trying to find a way to improve relations between Ethiopians through meaningful reforms. The TPLF/ERPDF tendency to simply up the violence or to create a new law to charge the innocent is dangerous and may likely backfire. We believe it will simply escalate the problem and could cause ethnic violence and civil chaos.

The SMNE, as a social justice movement which stands up for the rights of all Ethiopians, condemns this practice and urges the TPLF/ERPDF to instead find a peaceful and inclusive way to resolve these urgent concerns before it is too late. When these kinds of human rights abuses and the denial of justice are inflicted on any group of Ethiopians, it is inflicted upon all of us. 

We in the SMNE, together with other peace-loving people, call on donor countries and human rights groups to put pressure on the TPLF/ERPDF to respect the rights of Ethiopian citizens.

We also call on media groups to be extremely cautious so they do not report TPLF/EPRDF-provided propaganda without substantial documentation and verification from witnesses on the ground. Ethiopians on the ground should do their duty to document what is going on and who is responsible, from the top offices of government to the streets. In the future, this kind of documentation will be needed in a court of law.

We also call on all Ethiopians to stand up with their Ethiopian Muslim brothers and sisters because like we have said before, we do not only share land and a country but we also share blood, joy, pain and suffering together. When the TPLF/ERPDF government kills some of our family and puts others in jail; the TPLF/ERPDF are putting us in jail too.  In a family there is no us and them.

In the past, the TPLF/ERPDF has sought to divide and conquer Ethiopians through exploiting our differences but if the TPLF/EPRDF seeks a better future in a shared Ethiopia, the decisions you make in the coming days will be critical. If the TPLF/ERPDF continues with its characteristic brutal tactics, the people of Ethiopia will reach a limit of tolerance. If Ethiopia spins out of control, we know who is responsible. It will not be the Ethiopian Muslims but will be the TPLF/ERPDF and its security forces.

As for the SMNE, we will continue to watch this very closely in order to protect the rights, value and dignity of every human life, including those in the TPLF/ERPDF and beyond, for no one is free until all are free. Let us restore the Ethiopian legacy of religious freedom and tolerance and be an example to our conflicted world; starting by building a bridge between fellow Ethiopians. This means we cannot let these members of our Ethiopian family rally alone.

May God bring a change of heart, mind and soul to the TPLF/EPRDF, helping Ethiopians to see each other as part of His precious creation and as we do, may the rivers of love, kindness, acceptance, and justice overflow from our people, bringing life and blessings not only to Ethiopia but to the world.

Thursday, August 8, 2013

Amnesty International: Ethiopian repression of Muslim protests must stop

“We are extremely concerned at reports coming out of Ethiopia this morning of further widespread arrests of Muslim protesters. The Ethiopian government’s ongoing repressive crackdown on freedom of speech and the right to peacefully protest has to end now.”
Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Protests in Ethiopia have increased in recent months. © AFP/Getty Images
The Ethiopian government must end its use of repressive tactics against demonstrators, following initial reports of widespread arrests of Muslim protestors during this morning’s Eid al-Fitr celebrations, said Amnesty International today.
“We are extremely concerned at reports coming out of Ethiopia this morning of further widespread arrests of Muslim protesters. The Ethiopian government’s  ongoing repressive crackdown on freedom of speech and the right to peacefully protest has to end now,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Last week, another incident related to the protests reportedly ended in the deaths of an unconfirmed number of people in the town of Kofele in Oromia region.
During the 18 month-long protest movement against alleged government interference in Islamic affairs, the vast majority of demonstrations have been peaceful. However, there have been at least four incidents involving serious allegations of the excessive use of force by security forces against demonstrators in the long-running movement.  While a few isolated incidents of violence involving protestors have occurred, these have taken place during episodes where excessive police force is alleged.
“These reports of further deaths in the context of the Muslim protest movement are deeply worrying. There must be an immediate, independent and impartial investigation into the events in Kofele, as well as into the four incidents last year which resulted in the deaths and injuries of protestors,” said Claire Beston.
“With further protests planned, it is imperative that the behaviour of the security forces is scrutinised and if enough admissible evidence of crimes is found, suspected perpetrators should be prosecuted in trial proceedings that meet international standards.”
Accounts of last week’s incident in Kofele from the protestors and the government differ widely.
Protestors report that the security forces opened fire on unarmed people who were protesting against the arrests of members of the local Muslim community. One resident of Kofele told Amnesty International that 14 people were shot dead by the army, including at least three children. Another said that 11 people had been killed.
According to media reports, the authorities have said that the protestors were armed, leading to an outbreak of violence which resulted in the deaths of three protestors and injuries to a number of police officers. Government representatives refused to respond to Amnesty International’s queries about the incident.
There are also reports of large numbers of arrests in and around Kofele, Oromia, and further arrests in Addis Ababa over the last week.
Those arrested included two journalists – Darsema Sori and Khalid Mohamed – detained early last week in Addis Ababa.
The two men were working for Radio Bilal, which has regularly reported on the protest movement. Darsema Sori had also previously worked for the publication Ye’Muslimoch Guday (Muslim Affairs), from which two employees have already been arrested during the protest movement, and who are currently being prosecuted under the Anti-Terrorism Proclamation.
According to information received by Amnesty International Darema Sori and Khalid Mohamed are being held at Sostegna (third) police station in Addis Ababa and are not being permitted visitors. They have reportedly been taken to court and were remanded in custody while the police continue their investigation.
Reports of arrests and detentions of peaceful protestors and people suspected of involvement in organising the protests have continued throughout 18-months of demonstrations.
Despite many months of large-scale, peaceful protests, the government has repeatedly attempted to paint the protest movement as violent and terrorist-related in statements to the media and in parliament. Amnesty International has received a number of reports of messages aired via the state media over the last week, warning that the authorities would take firm action against anyone who attempted to take part in further demonstrations.
“This is a violation of people’s right to peacefully protest, as protected in Ethiopia’s Constitution,” said Claire Beston. “The government continues to respond to the grievances of the Muslim community with violence, arbitrary arrests and the use of the overly-broad Anti-Terrorism Proclamation to prosecute the movements’ leaders and other individuals.”
As demonstrations continue, Amnesty International is concerned that the response of the authorities will also continue to involve human rights violations, including arbitrary arrests of peaceful protestors and possible further bloodshed.
The organization urges the Ethiopian government to respect the right of its citizens to peacefully protest and urges an immediate end to heavy-handed tactics in response to the protests. Anyone arrested solely for exercising their right to peaceful protest must be released immediately.
Background
The trial continues of 29 figures related to the protest movement including nine members of a committee of representatives selected by the Muslim community to represent their grievances to the government, and one journalist, Yusuf Getachew, of the publication Ye’Muslimoch Guday. The trial has already been marred by a number of fair trial concerns, including the airing on state-run Ethiopian Television (ETV) of a programme called “Jihadawi Harakat.” It painted the Muslim protest movement and some of the individuals on trial as having connections with Islamic extremist groups, seriously jeopardising the right of the defendants to be presumed innocent until proven guilty.
The trial is now taking place in closed proceedings, increasing fears that the defendants will not receive a fair trial. Amnesty International believes that the individuals on trial are being prosecuted because of their participation in a peaceful protest movement.
Solomon Kebede, another journalist working for Ye’Muslimoch Guday was recently charged under the Anti-Terrorism Proclamation along with 27 other people, according to information received by Amnesty International.
During 2012 there were at least four incidents in which the security forces were alleged to have used excessive force during the dispersal and arrest of protestors. At least two of these incidents – in the towns of Gerba in the Amhara region, and Asasa in the Oromia region – resulted in the deaths of protestors.
Two further incidents in Addis Ababa reportedly resulted in many injuries to protestors. Amnesty International called for independent investigations to be conducted into these incidents, but according to available information, no such investigation has taken place.
Other protests have also been affected by the government’s pervasive intolerance of dissent. The opposition Unity for Democracy and Justice Party has reported arrests of its members in a number of locations around the country in recent weeks. They were engaged in organising demonstrations, handing out leaflets for demonstrations and calling on people to sign a petition calling for the revocation of the Anti-Terrorism Legislation and the release of political prisoners.
Source: www.amnesty.org

በምድረ – ኢትዮጵያ ያለው አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው!!

የወያኔ አገዛዝ ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ ያወጣው የእብሪት ማስፋራሪያና ዛቻ ቀለም ሳይደርቅ ያ የለመዱ እጁ አሁንም በንጹሃን ወገኖቻችን ደም ተጨማልቋል። የወያኔ እብሪት የሰው ልጅ ሊሸከም የሚችለውን ለከት አልፏል። አንድ አመት ከመንፈቅ ሙሉ ጠጠር ሳይወረውር መብቴን፣ ስብእናዬን፣ መሰረታዊ መብቴንና ነጻነቴን ብሎ ህገ-መንግስት እየጠቀሰ አቤት ስሙን ያለ ህዝብ በምን መለኪያ አሸባሪ ሊሆን ይችላል? ለመሆኑ ህፃን፤ሽማግሌ፤ ወንድና ሴት ሳይለይ ያገኘዉን በሙሉ በጥይት የሚቆላዉ ወያኔ ነዉ ወይስ መብቴንና ነጻነቴን አክብሩልኝ ብሎ በትእግስትና በጨዋነት የጠየቀ ህዝብ ነዉ ሽብርተኛ መባል ያለበት መልሱን ወያኔን በጭፍኑ የሚደግፉትን ጨምሮ ህሊና ላለው ዜጋ ሁሉ እንተዋለን።
ዋናው ጥያቄ መሆን ያለበት ይህንን እብሪትና እብጠት እንዴትና መቼ እናቁመው የሚለው ነው። ወያኔ የፈሪ አክራሪ ነው። ታገሱኝ፣ አፈግፍጉልኝ፣ አክብሩኝ እያለም እንኳን ከጭካኔ የሚያቆም ህሊና በሌላቸው ደነዞችና ጨካኞች የተሞላ ዘረኛ ተቋም ነው። ዛሬ የሚቀማጠሉበትን ስልጣንና ምቾት ይነካብናል፣ እንቅልፍ ይነሳናል ያሉትን የህዝብ ትንፋሽን ሁሉ ፀጥ ለማድረግ መወሰናቸውን ካየን ከሰማን ውለን አድረናል። በወያኔ መንደርና አገዛዝ በገዛ ሀገራችን ቀና ብለን መሄድ፣ በትውልድ መንደርና ቀያችን መኖር፣ በዜግነታችን የሚገባንን መሰረታዊ ጥያቄ ማንሳት ሽብርተኞች አሰኝቶ በጥይት የሚያስቆላና በወህኒ የሚያሰበስብ ወንጀልና ሀጢያት ከሆነ ዉሎ አድሯል። ህግና ህገ-መንግስቱ ተብዬዉ የተጻፈበትን ወረቀት ያህል እንኳን ዋጋ ካጣ ሰንበትበት ብሏል።
ሰሞኑን ኮልፌ ዉስጥ በንጹሃን የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ላይ ወያኔ የፈጸመው ግፍ የሚዘገንን ጭካኔ ይሁን እንጂ ከወያኔ አረመኔዎች የማንጠብቀው አይደለም። ወያኔ እያሸበረን አሸባሪ ሲለን፣ እየገደለ ገደሉ ሲለን፣ በክብር ስንለምነው እያዋረደን እንደ ህዝብ ሳይሆን እንደ መንጋ እየተቆጣጠረ ሊገዛን ቆርጧል። ወያኔ ከሰዉነት ደረጃ ወጥተን ወደ እንስሳነት ተለዉጠን ሃይማኖታችንን ጭምር እሱ መርጦልን፣ ልማትና እድገትን ከእኔ ዉጭ ከሌላ አትጠብቁ እያለበረሃብ እያለቅን ጠገብን እያልን አጎንብሰን እንድንኖር ይፈልጋል። ባለፈዉ ሳምንት ያሰራጨዉ የማስፈራሪያ መግለጫና ፀረ-ሽብርተኛ የሚለው ህግ አላማም ይሄዉ ነው። ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፤ ወጣቶችን ባጠቃላይ ሰላማዊ ታጋዮች፣ የኢትዮጵያን እስር ቤቶች የሞሉት ይህንን የወያኔን ፀረ ህዝብና ፀረ አገር ድርጊትና አላማ ስተቃወሙ ብቻ ነው።
ለወያኔ ግፍና በግፈኝነቱ እንዲቀጥል በከፊል ተጠያቂዎች የሆንን የዚች ሀገር ዜጎች ሁሉ አስተዋጽኦ አላደረግንም ማለት አይቻልም። ነግ በኔ ማለት አቅቶን ዛሬ አንዱን ሲያጠቃ፣ ሲገድልና ሲያስር ሌሎቻችን ዝም እያልን በየተራ ለመጠቃትና ለመዋረድ ተመችተነዋል። ሙስሊሙ ሲጠቃ ክርስቲያኑ ተመልካች ይሆናል። ክርስቲያኑ ሲጠቃ ሙስሊሙ ይመለከታል። ኦሮሞው ሲቀጠቀጥ አማራው ይመለከታል። አማራው ሲወገር ኦሮሞው ቆሞ ያያል። በሌላ አነጋገር ሁላችንም በቃ ብለን በአንድ ላይ መነሳት አቅቶናል። ወያኔ ትላንት ላፈሰሰው ደም ሂሳብ ስላልከፈለ ነው ደግሞና ደጋግሞ ደማችንን የሚያፈሰው። አንድ ሆነን ከመታገልና ከመነሳት ውጭ አማራጭ እንደሌለን የዘነጋነው ይመስላል። አንድ ሆነን የተነሳን እለት ወያኔ ምን ያህል ኢምንት ሃይል እንደሆነ ማየት አቅቶናል።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥቃትንና ውርደትን መሸከም፣ መስማትና ማየት፣ መሰደድና መታሰር፣ መንገላታቱ ያንገፈገፈህ ወገን ሁሉ፤ ስለ ሀገርህ፣ ስለማንነትህ ህልውና ስትል አንድ ሆነህ ለመነሳት ጊዜው አሁን ነው፤ ፈርጣማ ክንድህን የምታሳይበት፣ የአበውን እምቢና አልገዛም ባይነት ለዘረኛው ወያኔ የምታሳይበት ጊዜ ዛሬ ነዉ እንላለን፤ እኛ የወያኔን ማንነት በቅጡ የተረዳን የግንቦት 7 ንቅናቄ ልጆችህ።
በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያለው አሸባሪ ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው!! ከወያኔ ውጭ አለምአቀፍም ሆነ ሀገረኛ አሸባሪ በሀገር ውስጥ የለም። ወያኔ አሸባሪ የሚለን አለም አቀፋዊ ልመናው እንዳይቆም ብቻ ነው። ሊበላን የፈለገው አሞራ ስለሆንን ብቻ ነው ጅግራ የሚለን።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሀገራችን ህዝብ ሁሉ በአንድነት የነጻነት አሞራዎች እንድንሆን ዛሬም ጥሪውን በድጋሜ ያቀርባል። ሽብርተኛው ወያኔ፣ ህግ፣ ሰበአዊነት፣ ስልጡን ፖለቲካ ቀርቶ ተራ ይሉኝታ የሌለው፣ በልቼ ልሙት ወይም እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ብሎ የቆረጠ ዘረኛ ቡድን ነውና ልናስወግደው የግድ ይለናል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Amnesty International: Ethiopian repression of Muslim protests must stop

August 8, 2013
Amnesty International on Ethiopian Muslims
Young Ethiopian Muslim girl, attacked by Ethiopian government forces during Eid al-Fitr celebrations in Addis Ababa. August 08, 2013
The Ethiopian government must end its use of repressive tactics against demonstrators, following initial reports of widespread arrests of Muslim protestors during this morning’s Eid al-Fitr celebrations, said Amnesty International today.
“We are extremely concerned at reports coming out of Ethiopia this morning of further widespread arrests of Muslim protesters. The Ethiopian government’s  ongoing repressive crackdown on freedom of speech and the right to peacefully protest has to end now,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
Last week, another incident related to the protests reportedly ended in the deaths of an unconfirmed number of people in the town of Kofele in Oromia region.
During the 18 month-long protest movement against alleged government interference in Islamic affairs, the vast majority of demonstrations have been peaceful. However, there have been at least four incidents involving serious allegations of the excessive use of force by security forces against demonstrators in the long-running movement.  While a few isolated incidents of violence involving protestors have occurred, these have taken place during episodes where excessive police force is alleged.
“These reports of further deaths in the context of the Muslim protest movement are deeply worrying. There must be an immediate, independent and impartial investigation into the events in Kofele, as well as into the four incidents last year which resulted in the deaths and injuries of protestors,” said Claire Beston.
“With further protests planned, it is imperative that the behaviour of the security forces is scrutinised and if enough admissible evidence of crimes is found, suspected perpetrators should be prosecuted in trial proceedings that meet international standards.”
Accounts of last week’s incident in Kofele from the protestors and the government differ widely.
Protestors report that the security forces opened fire on unarmed people who were protesting against the arrests of members of the local Muslim community. One resident of Kofele told Amnesty International that 14 people were shot dead by the army, including at least three children. Another said that 11 people had been killed.
According to media reports, the authorities have said that the protestors were armed, leading to an outbreak of violence which resulted in the deaths of three protestors and injuries to a number of police officers. Government representatives refused to respond to Amnesty International’s queries about the incident.
There are also reports of large numbers of arrests in and around Kofele, Oromia, and further arrests in Addis Ababa over the last week.
Those arrested included two journalists – Darsema Sori and Khalid Mohamed – detained early last week in Addis Ababa.
The two men were working for Radio Bilal, which has regularly reported on the protest movement. Darsema Sori had also previously worked for the publication Ye’Muslimoch Guday (Muslim Affairs), from which two employees have already been arrested during the protest movement, and who are currently being prosecuted under the Anti-Terrorism Proclamation.
According to information received by Amnesty International Darema Sori and Khalid Mohamed are being held at Sostegna (third) police station in Addis Ababa and are not being permitted visitors. They have reportedly been taken to court and were remanded in custody while the police continue their investigation.
Reports of arrests and detentions of peaceful protestors and people suspected of involvement in organising the protests have continued throughout 18-months of demonstrations.
Despite many months of large-scale, peaceful protests, the government has repeatedly attempted to paint the protest movement as violent and terrorist-related in statements to the media and in parliament. Amnesty International has received a number of reports of messages aired via the state media over the last week, warning that the authorities would take firm action against anyone who attempted to take part in further demonstrations.
“This is a violation of people’s right to peacefully protest, as protected in Ethiopia’s Constitution,” said Claire Beston. “The government continues to respond to the grievances of the Muslim community with violence, arbitrary arrests and the use of the overly-broad Anti-Terrorism Proclamation to prosecute the movements’ leaders and other individuals.”
As demonstrations continue, Amnesty International is concerned that the response of the authorities will also continue to involve human rights violations, including arbitrary arrests of peaceful protestors and possible further bloodshed.
The organization urges the Ethiopian government to respect the right of its citizens to peacefully protest and urges an immediate end to heavy-handed tactics in response to the protests. Anyone arrested solely for exercising their right to peaceful protest must be released immediately.
Background
The trial continues of 29 figures related to the protest movement including nine members of a committee of representatives selected by the Muslim community to represent their grievances to the government, and one journalist, Yusuf Getachew, of the publication Ye’Muslimoch Guday. The trial has already been marred by a number of fair trial concerns, including the airing on state-run Ethiopian Television (ETV) of a programme called “Jihadawi Harakat.” It painted the Muslim protest movement and some of the individuals on trial as having connections with Islamic extremist groups, seriously jeopardising the right of the defendants to be presumed innocent until proven guilty.
The trial is now taking place in closed proceedings, increasing fears that the defendants will not receive a fair trial. Amnesty International believes that the individuals on trial are being prosecuted because of their participation in a peaceful protest movement.
Solomon Kebede, another journalist working for Ye’Muslimoch Guday was recently charged under the Anti-Terrorism Proclamation along with 27 other people, according to information received by Amnesty International.
During 2012 there were at least four incidents in which the security forces were alleged to have used excessive force during the dispersal and arrest of protestors. At least two of these incidents – in the towns of Gerba in the Amhara region, and Asasa in the Oromia region – resulted in the deaths of protestors.
Two further incidents in Addis Ababa reportedly resulted in many injuries to protestors. Amnesty International called for independent investigations to be conducted into these incidents, but according to available information, no such investigation has taken place.
Other protests have also been affected by the government’s pervasive intolerance of dissent. The opposition Unity for Democracy and Justice Party has reported arrests of its members in a number of locations around the country in recent weeks. They were engaged in organising demonstrations, handing out leaflets for demonstrations and calling on people to sign a petition calling for the revocation of the Anti-Terrorism Legislation and the release of political prisoners.

‹‹የስልጣን ጥመኝነት የወለደዉ የፀረሽብር አዋጅ›› የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ደብዳቤ ከቃሊቲ

August 8, 2013 at 1:12pm
 
የፀረሽብር አዋጁንና እየተተገበረ ያለበትን መንገድ ባሰብኩ ቁጥር  ወደአይምሮዬ የሚመላለሱ በርካታ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ከነዚህ መሀከል አዋጁ ለምን ሰብአዊ መብትን የሚጥሱ አንቀጾች ኖሩት/  ከሽብር ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌለን ንጹሀን ሰዎችስ በአዋጁ መሰረት እየተባለ ለምን ይፈረድብናል የሚሉት ይገኙበታል፡፡ እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ አዋጁ የወጣበትን ምክንያት መመርመር ግድ ይላልና ይህንኑ አደረስኩ፡፡
.
የፀረሽብር አዋጁ ለምን ወጣ
 
 
     ኢህአዴግ የፀረሽብር አዋጅ እንዲወጣ ያደረገዉ እዉተኛ የሽብር አደጋ ተደቅኖበት አለመሆኑን ለመረዳት ብዙ መጓዝ አያስፈልግም፡፡ በአሽባሪነት የተጠረጠርንና የተፈረደብንን ሰዎች ማንነት ማወቁ ብቻ ይበቃል፡፡ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዉያን ላይ እየተፈጸመ ያለዉ ግፍ ይብቃ ብለዉ ስርዓቱ በሌላ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ይለወጥ ዘንድ በሰላማዊ መንገድ ሲታገሉ የነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላት፣ በመስርያ ቤታቸዉ ወይም ደግሞ በመኖርያ ቤታቸዉ አካባቢዎች የመንግስት ሀላፊዎች በሚጠሯቸዉ ስብሰባዎች ላይ ደፋር ጥያቄዎችን በማቅረባቸዉ ብቻ ጥርስ የተነከሰባቸዉ የነፃ አስተሳሰብ  ባለቤቶች፣ መንግስት ለአገዛዙ  አመቺ በመሰለዉ መልኩ ሀይማኖታቸዉን ለመበረዝና ለመከለስ ያደርግ የነበረዉን እንቅስቃሴ በሚያስገርም ጀግንነት የመከቱ የእስልምና ሀይማኖት መሪዎችና ተከታዮች እንዲሁም የህዝብ ድምፅ መሆናችንን አምነን ሀላፊነታችንን በአግባቡ ስንወጣ የነበርን  የነፃዉ ፕሬስ አባላት የፀረሽብር አዋጁ ሰለባ ሆነናል፡፡
 
      ይህ የመንግስት ድርጊት አዋጁን ያወጣበት እዉነተኛ ምክንያት በስልጣን ወንበር ላይ ያለምንም ተቺ፣ ተቃዋሚና ተቀናቃኝ ተደላድሎ ለመቀመጥ መሆኑን የሚያሳይ ነዉ፡፡ ይህ አይነቱ አካሄድ ደግሞ ኢህአዴግ የጀመረዉ ሳይሆን እሱን ከመሰሉ አምባገነኖች የኮረጀዉ ያረጀና ያፈጀ አሰራር ነዉ፡፡ የአፍሪካዉያን የቀድሞ ቅኝ ገዢዎች አልንበረከክ ብለዉ ያስቸገሩዋቸዉን የነፃነት ታጋዮች የአሸባሪነት ታፔላ ይለጥፉባቸዉ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ዛሬ ደግሞ ኢህአዴግ ሰብአዊና የዜግነት ክብራችንን ለመጣል እምቢ ያልነዉን የገዛ ሀገሩን ልጆች እስር ቤት ለማጎርና ለማሰቃየት አመቺ ነዉ ብሎ ባመነበት በዚህ የቅኝ ገዢዎች አስቀያሚ መንገድ ላይ እየተጓዘ ነዉ፡፡
 
ምን ይሻላል?
 
   የፀረሽብር አዋጁን በመታከክ ኢህአዴግ እየፈፀማቸዉ ያሉትን የመብት ረገጣዎች ለማስቆም ከባድ ትግል ይጠይቃል፡፡ አሁን ያለዉ  የፀረሽብር አዋጅ ተገቢ በሆነ በሌላ የፀረ ሽብር አዋጅ መተካት ይኖርበታል፡፡ ይህ ባይሆን እንኳን አሁን ያለዉ አይነት ለኢህአዴግ የገበረ የፍትህ ስርዓት እስካለ ድረስ ግን ንፁሀን ዜጎች በአሸባሪነት መታሰራቸዉ አይቀርም፡፡ አሁን ባለዉ የፀረሽብር አዋጅ መሠረት በትክክል ብንዳኝ ኖሮ እንኳን ጥፋተኛ ልንባል የማይገባን ምንም አይነት ወንጀል ያልፈፀምን ግለሰቦች አሸባሪ ተብለን በእስር ላይ መገኘታችን ይህንን መራራ እዉነት የሚያሳይ ነዉ፡፡ በመሆኑም አዋጁንና በይበልጥ ደግሞ አዋጁን ለስልጣኑ ማራዘሚያነት ኢፍትሀዊ በሆነ መንገድ እየተጠቀመበት ያለዉን ኢህአዴግን በማዉገዝ እየተደረጉ ያሉትን የተቃዉሞ ሰልፎችና ሌሎች ሰላማዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎች ጠንክረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል፡፡
 
     የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎች በዋናነት ኢህአዴግ ላይ ማተኮር እንዳለባቸዉ የማምነዉ በፀረሽብር አዋጁና በአተገባበሩ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ለቁጥር የሚያዳግቱ የኢትዮጵያዉያን ችግሮች ምንጭ ራሱ ኢህአዴግ በመሆኑ ነዉ፡፡ ኢህአዴግ ስልጣኑን ለማራዘም የሚረዳዉ እስከመሰለዉ ድረስ ማንኛዉንም አይነት ተግባር ከመፈፀም ወደኃላ የማይል መሆኑን እስኪያንገሸግሸን ታዝበናል፡፡ በሌላ አነጋገር የኢህአዴግ ድርጊቶች ሁሉ ምክንያቶች ( motives ) ከዘረኝነት፣ ከስልጣን ጥመኝነት፣ ካለአግባብ ከመበልፀግና ከመሳሰሉት እኩይ ፍላጎቶች ጋር የተያያዙ ናቸዉ፡፡ “If one”s motives are wrong, nothing can be right” ከሚለዉ የአርተር ጎርደን አባባል እንደምንረዳዉ አንድ ነገር የሚደረግበት ምክንያት ስህተት ከሆነ ትክክል የሚሆን ነገር አይኖርም፡፡ በዚህም ምክንያት ከኢህአዴግ መልካም ነገር መጠበቅ አይቻልም፡፡ በመሆኑም የሚኖረን ብቸኛ አማራጭ የሰለጠነና ሰላማዊ ትግል የሚጠይቀንን መስዋዕትነት ከፍለን ስርዓቱን መለወጥ ነዉ፡፡
 
    ስርዓቱን ስለመለወጥ ስናስብ አብረን ልናስባቸዉ የሚገቡ በርካታ ተያያዥ ጉዳዮች አሉ፡፡ ስርዓቱን ለመለወጥ በምንሄድበት መንገድ ላይ ገዢዉ ፓርቲ ያስቀምጣቸዉን በዘር፣ በሀይማኖት፣በፖለቲካ ርዕዮተ ዓለምና በጥቅም የመከፋፈል እንቅፋቶች እንዴት ማለፍ እንደምንችል በጥልቀት አስቦ መንቀሳቀስ ግድ ይላል፡፡  በየአቅጣጫዉ የተበታተኑ እንቅስቃሴዎችን ከማካሄድ ይልቅ በህብረት ሆነን መታገል መቻል ይኖርብናል፡፡ ከኢህአዴግ በኋላ ስለሚመሰረተዉ ስርዓትም በደንብ ማሰብና መመካከር የሀገሬ ጉዳይ ይመለከተኛል ከሚል ማንኛዉም ሀላፊነት ከሚሰማዉ ዜጋ በተለይም ደግሞ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎችን ከሚመሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ሌሎች አካላት ይጠበቃል፡፡ የሚጠበቅብንን ሁሉ እስካደረግንና በፅናት እስከቆምን ድረስ ደግሞ ብሩህ ቀን የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡
 
ምንልክ ሳልሳ  https://www.facebook.com/minilik.salsawi
 

Wednesday, August 7, 2013

የተፈናጠረው 11ኛ ሰአት – የወያኔ የመጨረሻው የጥላቻ አጣብቂኝ

 የታሰሩትን መፍታት ለኢሕኣዴግ የፖለቲካ ኪሳራ ያስከትላል::


የታሰሩትን መፍታት ለኢሕኣዴግ የፖለቲካ ኪሳራ ያስከትላል:: ለሊቱን በስብሰባ ተወጥሮ ያደረው ወያኔ መስማማት ተስኖታል:: አደርባዮች እና የድል አጥቢያ አርበኞች ጨንቋቸዋል::ከየተኛው ወገን እንደሚለጠፉ ግራ ገብቷቸዋል::

  የደህንነት እና የህወሓት ወታደራዊው ክንፍ በተጠንቀቅ ላይ ነው:: ባለስልጣናቱ ከውጪው አለም እየተደረገባቸውን ጫና እና ግፊት በፍጹም አንቀበለም የሚል ድምዳሜ ላይ ለመድረስ እርስ በእርስ ሲላተሙ አድረዋል:: ሃገራችን የጥበበኛ ህዝቦች እና የጥበበኛ መሪዎች ሃገር የምትሆንበትን ጊዜ የምንፈልግ እኛ ለውጥ ፈላጊ ልጆቿ ዛሬ ላይን ተቀምጠን ትላንትን የምንመኝ ለነገው ትውልድ የማናስብ በፍርሃት ድባብ ተውጠን ስደትን እና ገንዝእብን የምናሳድድ መሆናችን በመታወቁ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ስልጣኑንን እንዴት አስረዝሞ ሃገር ወዳድ የሆኑ ጠላት የሚላቸውን ኢትዮጵያውያንን ነቃቅሎ የሚያጠፋበት ስልት በቡድናዊ አምባገነንነት እየዶለተ እና በስልጣን ሽኩቻ እርስ በእርሱ እየተባላ ባለበት ወቅት እኛ አንድነት አጥተል በጋራ ዘመም በቀኝ አክራሪ እና ባፈጀ ባረጀ የፖለቲካ ግራውንድ እየተሽከረከርን ህዝብዊ መቆላለፍን ልንፈጥር አለመቻላችን ለአገዛዙ አመቺ አድርጎታል:: እስኪ የወያኔን ስጋት ያነቡ ዘንድ ጋብዘናል::

ከትላንት ሃምሌ 28 ሊነጋ የተበተነው የወያነው የውጥረት ስብሰባ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ነበረ ለሊቱን የተጓዘው::እንደቀድሞው እቅዳችን ትራንስፎርሜሽናችን ልማታችን ምናምናችን ዲሞክራሲያችን ሰላማችን የጼረ ህዝቦቻችን ...ምናምን የሚል አልነበረም ..በአተካሮ የተሞላ ውጥረት የነገሰበት አድርባዮች ፍራቻ ይነበብባቸው የነበረበት የነባር ታጋዮች ጩሐት ውይይቱት ደበላልቆት ያደረበት እንደነበር በስብሰባው ላይ የነበሩ የምንሊክ ሳልሳዊ ምንጭ ተናግረዋል::
የት ከርሞ ከየት እንደመጣ ወዴትስ ሄዶ እንደነበር በማይታወቀው የአምባገነን ቡድን አስተባባሪ በደብረጽዮን የተመራው ይህ አተካራዊ ስብሰባ የወያኔ አባላቱን ለከፍተኛ ፍጥጫ ከመዳረጉም አርፎ ዘለፋ እና ዛቻ እንዲሁም የቀድሞ ጉዳዮች ወቀሳ ያካተተ የነበረ ሲሆን በብኣዴን ነባር አባላት እና በጫካው ሕወሓት እንዲሁም በሕወሃት የከተማ ህዋስ እና በጫካው ሕወሓት መካከል ከፍተኛ የሆነ ጭቅጭቅ ተስተናግዷል:: ዋናው አትኩሮት የነበረው ይላሉ የምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮች ወቅታዊው የአንድነት ፓርቲ እንቅስቃሴ;የሙስሊሙ ጥያቄ; የምእራባውያን ጫና;እና የዲያስፖራው ድጋፍ በተመለከተ ነበር::
የስብሰባው ላይ አነጋጋሪ የነበረው የአንድነት ፓርቲ ጉዳይ በስፋት መንቀሳቀስ በዚሁ ከቀጠለ ካለው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ችግር አኳያ ህዝቡ ሆ! ብሎ ሊነሳ ስለሚችል ከዚህ ቀደም እንደተለመደው ፓርቲውን በወከባ እና በጥቅም ማክሰም ወይንም ከፓርቲው ጋር መደራደር እስከሚሉ ጨከን ያሉ ሃሳቦች ተንጸባርቀዋል:: ከፓርቲዎች ጋር መደራደር የሚባል ነገር አይዋጥልኝም የሚሉት አለቃ ጸጋዬ በቁጣ እና በጩኽት ይህንን የመደራደር ሃሳብ ያቀረበችውን የሕወሓት የከተማ ህዋስ አባልን ያመጣንሽ እኮ እንድትጦሪን እንጂ ጠላት እንድትሆኚን አይደለም በማለት በቋንቋቸው አይሆኑ ዘለፋ ዘልፈዋታል::ቤቱ በዝምታ ድባብ እንዲዋጥ ያደረጉት የጫካው ሕወሓቶች የታገልነው ለድርድር አይደለም ሲሉ ተደምጠዋል:: ሰማያዊ ፓርቲ ቢነሳም ብዙም አያሰጋንም በሚል ታልፏል::
ከኦህዴድ ሙክታር ብቻ የተካፈለበት ይህ ስብሰባ 16 የህወሃት ጄኔራሎች የተመከሩ ይመስል ጂንስ በጃኬት ለብሰው ነበር በስብሰባው ላይ የተገኙት :: በአሁን ሰአት የደህንነቱ እና የወታደሩ ክፍል በተጠንቀቅ ሊሆን ይገባዋል በሚል የሚያሳዝን አንደበት መናገር የጀመሩት አቶ በረከት አትኩረውት የነበረው በሙስሊሙ እና በዲያስፖራው ጉዳይ ነበር :: ሙስሊሙች ጥያቄያቸው ሰፍቶ አለምም ጆሮ ሰቷቸዋል እንሱን ዝም ማሰኘት አሊያም ለፖለቲካ ስልት መጠቀም አስፈላጊ ነው ቢሉም የታሰሩትን መፍታት ለኢህኣዴግ የፖለቲካ ኪሳራ ስለሆነ ያለንን ሃይል መጠቀም አለብን ብለዋል:የዲያስፖራው ጥላቻ ከ60% ወደ 90% አድጓል:: 10% ደሞ ንብረት አገር ቤት ያፈሩ ወይም ከፖለቲካ ነጻ ነን የሚሉ ግለሰቦች ሲሆኑ ይህ ደሞ 10% ደጋፊ ሳይሆን የምንላቸው ለንብረቶቻቸው እና ለቤተሰቦቻቸው ደህንነት የሚለማመጡ ብንል ይቀላል :: በዲያስፖራው ዘንድ ያለው ጉዳይ ብዙም ተስፋ ሰጪ ስላልሆነ ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል:: ይህ የራሳችን የፖሊሲ ውጤት ነው ብለው ደፍረው የሚናገሩ አባላት አልተገኙም::
የህወሃት አንጋፋ ታጋዮች የተሳተፉበት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ያልተጠሩበት ጥቂት ብኣዴኖች እና አንድ ኦህዴድ የፈጠጡበት ይህ ስብሰባ የምእራቡን ጫና በተመለከተ ሰፋ ያለ የዲፕሎማቲክ ስራ እና ዝርዝር ሪፖርት ይዞ የማስረዳት ስራ እንዲሰራ የሕወሓት የውጪ ጉዳይ አትኩሮት እንዲሰጥበት ያደረገ ሲሆን ለአንድ አገር የውጪ ፖሊሲ የአንድ ፓርቲ ሰዎችን እንዲሰሩ ማዘዝ በአንዳንድ ተሰብሳቢዎች ላይ አግራሞትን ፈጥሯል::ምንም አይነት ስምምነት ያልታየበት ይህ ስብሰባ በፍጥጫ በአተካሮ እና በጩኽት የተሞላ ቢሆንም አብዛኛዎቹ አንጋፋ ታጋዮች ማስታውሻቸው ላይ ሲቸከችኩ ተስተውለዋል::
ወደማይፈታ ችግር ራሱን እየወሰደ ያለው ቡድናዊው አምባገነን ከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ እንዳለ የሚያሳየው ይህ ጨለማ የሚደረግ ስብሰባ አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ሰዎች እየተመረጡ ደጋፊዎች እየታዩ እየተጠራሩ በጎጥ እና በመንደር በመሰባሰብ ሃገርን ወደማትወጣበት አዘቅት ቁልቁል እየከተቷት ነው:: በመጪው ቀናቶች የሚጠሩ ስብሰባዎች በእነዚሁ ወቅታዊ ጉዳዮን ላይ አተኩርው እንደሚወያዩ ይጠበቃል መልካም የለሊት ስብሰባ::  ምንልክ ሳልሳዊ

120 ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያንን የያዘች መርከብ በማልታና ጣሊያን መንግሥታት ወደ ግዛቴ አላስገባም በሚል ውዝግብ በእንግልት ላይ ናቸው

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ሁኔታው ያሳሰበው የአውሮፓ ህብረት የማልታ መንግስት ያለምንም መዘግየት በእንግልት ላይ የሚገኙትን ሰዎች ወደ ድንበሩ ገብተው ሰብአዊ መብት እንዲያገኙ ጠይቋል፡፡

ማረፊያ ያጣችው መርከብ በውስጧ አራት እርጉዝ ሴቶችን፣ አንድ የተጎዳች ሴትና የ5 ወር ህጻን መያዟን የአውሮፓ ህብረት አስታወቋል፡፡

በላይቤሪያ መንግስት ንብረትነት የተመዘገበችው ጀልባ በግሪካዊ ኩባንያ አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበረች ሲሆን 120 ኢትዮጵያውያኑንና ኤርትራዊያኑን በሊቢያ ቀይ ባህር ውቅያኖስ ላይ በህገ ወጥ ዝውውር ላይ እንደነበሩ ከአደጋ መታደጓ ተገልጿል፡፡

የጣሊያን የነብስ አድን ሰራተኞች ጀልባው ስደተኞቹን እንደያዘ ወደ ሊቢያ የየብስ ግዛት እንዲያቀና ቢጠየቁትም ጀልባውን በማሽከርከር ላይ የነበረው ካፒቴን ጉዞውን ወደ ማልታ እንዳቀና አውሮ ኒውስ ዘግቧል፡፡

ነገር ግን ካፒቴኑ የማልታን የየብስ ግዛት እንዳይገባ የማልታ ባህር ሀይል ከልክሎታል፡
በተፈጠረውም ውዝግብ 120 ስደተኞች ከፍተኛ ችግር ውስጥ መውደቃቸው ታውቋል፡፡

ካፒቴኑ በጀልባው ውስጥ ያሉ ስደተኞች አፋጣኝ የህክምና እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው በመናገር ላይ ነው፡፡ የአውሮፓ ህብረት የማልታም ሆነ የጣልያን ባለስልጣናት ውዝግባቸውን ትተው ነብስ የማዳን ስራ ቅድሚያ እንዲሰጡ አሳስቧል፡፡\

በተለይም በጀልባው ውስጥ በጉዳት ላይ ያለች አንዲት ሴት በአስቸኳይ ሆስፒታል በመግባት ህክምና እንደሚያስፈልጋት ካፒቴኑ በመግለጽ ላይ ሲሆን የማልታና ጣሊያን መንግስት ጉዳዩን እንደሚያጤኑት የአውሮፓ ህብረት በመጠየቅ ላይ ይገኛል፡
ማልታ ባለፈው ወር ብቻ 1000 ስደተኞች ወደ ግዛቴ ገብተዋል በማለት ጥያቄውን አጣጥላለች፡፡ በማልታ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውን ስደተኞች በከፍተኛ ችግር እንዳሉ በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል፡፡

“ሹገር ማሚዎች” የከተማችንን ጎረምሶች እያጠመዱ ነው Sugar Mommies trap young men in Addis Ababa


Written by መታሰቢያ ካሣዬ, AddisAdmassNews.com

የተስተካከለ ቁመናውና የስፖርተኛ አቋሙ የብዙ ሴቶችን ዓይን ይስባል፡፡ ጐተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ ጂምናዚየም ውስጥ ተቀጥሮ ደንበኞቹን ስፖርት ያሰራል፡፡ በተግባቢነቱ፣ በተጨዋችነቱና በሰው አክባሪነቱ ሁሉም ይወዱታል፡፡ ከሥራው ቦታ ሳይርቅ ጎተራ ላንቻ አካባቢ ከግለሰብ በተከራየው አንድ ክፍል ቤት ውስጥ እየኖረ ሳለ ነው ህይወቱን የሚቀይር አንድ አጋጣሚ የተፈጠረው፡፡

ያቺን ዕለት አይረሳትም፡፡ ሴትየዋ ጠና ያሉ ናቸው - ከ50 ዓመት በላይ ይሆናቸዋል፡፡ የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ሁለመናቸው ይናገራል፡፡ የጂም ደንበኛ ሆነው ሲመዘገቡ ምንም የተለየ ነገር ይፈጠራል ብሎ አላሰበም፡፡ እንደ ሁልጊዜው በፈገግታና በትህትና ተቀብሎ አስተናገዳቸው፡፡

የሴትየዋ የፊት ገፅታ የዕድሜያቸውን መግፋት ቢያጋልጥም በተለያዩ ሜካፖችና ቅባቶች እንዲሁም በዘመናዊ አለባበሣቸው ወጣት ለመምሰል ጥረዋል። እንዲህ ያሉ ወይዘሮዎች በአብዛኛው አንቱ መባልን አጥብቀው እንደሚጠሉ ያውቃል። ለዚህም ነው “አንቺ” እያለ ማናገር የጀመረው። አዲሷ የጂም ተማሪ፣ ወጣቱ ላይ ዓይናቸውን ጥለዋል፡፡ ዘንካታነቱና የስፖርተኛ ቁመናው ማርኳቸዋል፡፡


የለበሰው ቲ-ሸርትና ቁምጣ በጡንቻዎቹ ተወጣጥሯል፡፡ አይናቸውን ከሱ ላይ መንቀል ተሣናቸው፡፡ በስፖርት ሰበብ መቀራረብና መነካካት መኖሩን ደግሞ ወደውታል፡፡ ከወገብሽ ጎንበስ እግርሽን ከፍ ክንድሽን ዘርጋ ከደረትሽ ገፋ እያለ ---የሚሰሩትን እንቅስቃሴ ይነግራቸዋል አንድ ሁለት አንድ ሁለት እያለ፡፡ እሳቸው ግን ብዙም አይሰሙትም፡፡ ሁለመናቸው የሚነቃቃው ቀረብ ብሎ ሲያሰራቸው ነው - ወገባቸውን ደገፍ፣ ክንዳቸውን ያዝ፣ እግራቸውን ሳብ እያደረገ ሲያንቀሳቅሳቸው አንዳች የተለየ ዓለም ውስጥ የገቡ ይመስላቸዋል፡፡ የሰራ አካላቸው ይፍታታል። ፊታቸው ይበራል፡፡ ጨዋታቸው ይደራል፡፡ ለመግባባት ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ ሲውል ሲያድር መግባባታቸው እየጠነከረ፣ግንኙነታቸው የተለየ መልክ እየያዘ መጣ፡፡ 

ወጣቱ አሰልጣኝ የሴትየዋን ስሜት ተረድቶታል፡፡ እሳቸው በቀደዱለት ቦይ መፍሰሱን አልጠላውም - የት እንደሚደርስ ባያውቀውም፡፡ ከልጅነት ጀምሮ ከሚያውቀው የድህነት ህይወት ያላቅቀው እንደሆን ማን ያውቃል? ሴትየዋ የስፖርት ሰዓታቸውን ከቀን ወደ ምሽት ሲያዛውሩትም ለምን ብሎ አልጠየቃቸውም፡፡ ልሸኝህ የሚለው ነገር የመጣውም ይሄኔ ነው፡፡ ቤቴ ቅርብ ነው ብሎ መከራከር አልፈለገም፡፡ ወይዘሮዋ ብልሃተኛ ናቸው፡፡ መንገዱን ማርዘምያ መላ አላጡም፡፡ ይሄ ኮረኮንች ነው፣ያኛው እግረኛ ይበዛዋል እያሉ ጨለማ ጨለማውን ዙሪያ ጥምጥም ይዘውት ይሄዳሉ። እንዲያም ሆኖ መድረስ አይቀርም፡፡ “ደህና እደሪ” ብሎ ከመኪና ሲወርድ፣ ጎተት አድርገው ጉንጩን መሳም አስለምደውታል፡፡ መሳሳ
ሙ ከጉንጭ ወደ ከንፈር ለመዝለል ጊዜ አልፈጀበትም፡፡ መሸኛኘት ብቻ ሳይሆን አብሮ ማምሸትም ተጀምሯል፡፡ እራት ግብዣው ቀልጧል፡፡ ውድ ውድ ስጦታዎች እየጎረፉለት ነው፡፡ ረብጣ ብሮች ሸጎጥ ይደረግለታል። 

ወጣቱ እስራው ቦታ ድረስ ሰተት ብሎ የመጣለትን ሲሣይ በደስታና በእልልታ የማይቀበልበት ምክንያት አልታየውም፡፡ መጪውን ያሳምረው እንጂ፡፡ ሴትየዋ በጥቂት ሣምንታት እጃቸው ውስጥ የገባላቸውን ግዳይ፣እያንከበከቡ ወደ መኖርያ ቤታቸው ይወስዱ ጀመር፡፡ አብሮ መዋል አብሮ ማደር መጣ፡፡ የጎመዡበትን ዘንካታ ቁመናና የተደላደለ ሰውነት፣ እንደልባቸው አገኙት፡፡ በፈርጣማ ክንዱ አቅፎ በትኩስ የወጣትነት ትንፋሹ አሞቃቸው፡፡ እርጅና ተባርሮ ወጣትነት ዳግም ተመልሶ የመጣ መሰላቸው፡፡ ዓለማቸውን አዩ፡፡ እሱም የምኞቱን አገኘ፡፡ 300ሺህ ብር አውጥተው የገዙትን አዲስ ሞዴል ያሪስ መኪና በስሙ አዛውረው ሰጡት፡፡ ከኪራይ ቤት አውጥተው በ440ሺህ ብር ኮንዶሚኒየም ገዝተው አስገቡት፡፡ ፍቅራቸው ደራ፡፡

የሴትየዋ ባለቤት ከሁለት አመት በፊት ነው በድንገተኛ ህመም የሞቱት፡፡ ሁለት ልጆቻቸው ያሉት ደግሞ ጣሊያን ነው፡፡ እናም ምንም የሚያሳስባቸውና ነፃነታቸውን የሚጋፋ ነገር አልነበረም፡፡ ወይዘሮዋና ወጣቱ ያለገደብ ደስታቸውን አጣጣሙት፣ አንድም የቀራቸው የመዝናኛ ቦታ የለም - ሁሉንም በየተራ አዳረሱት፡፡ ወጣቱ የጂም አሰልጣኝ ሥራውን ለቆ ወይዘሮዋን መንከባከብ የሙሉ ጊዜ ሥራው አደረገው፡፡ ከእጃቸው የማይለዩት ቦርሳቸው አደረጉት፡፡ በፍቅር ከነፉለት፡፡ የወዳጅ ዘመድ ምክር የሚሰሙበት ጆሮ አልነበራቸውም፡፡ “ኧረ ተይ --- አሁን ይሄ ጎረምሳ ልጅሽ አይሆንም?” የሚሏቸውን ሁሉ ጠሏቸው፡፡ ባስ ሲልም ራቋቸው፡፡ ጓደኞቻቸውንማ ልክ ልካቸውን ይነግሯቸዋል “ምቀኝነት ነው፤ እንዲህ የሚያደርጋችሁ --- ያጣ ወሬ ነው” አፋቸውን ያሲዟቸዋል፡፡

እሱም ታዲያ ከጓደኞቹ የሚያበሽቀው አላጣም “እናትህ ከምትሆን ሴት ጋር ምን ነካህ?” ይሉታል፡፡ እሱም “ምቀኞች! እናንተ ባታገኙ ነው” ይላቸዋል፡፡ የነብርን ጭራ አይዙም ከያዙም አይለቁም እንዲሉ በሴትየዋ ዘንድ ለመወደድና ለመታመን መትጋቱን ቀጥሏል። ብዙም ሳይቆይ የወ/ሮዋን ሱፐር ማርኬት የማስተዳደር ኃላፊነት ተረከበ፡፡ “እሷ የስኬቴ ሰበብ ናት፡፡ ያልኳትን የምታደርግልኝ የጠየኳትን የምትሰጠኝ የፈለኩትን የምታሟላልኝ ዓለሜ ናት፡፡” የሚለው ወጣቱ፤ ከእኔ የሚጠበቀው እሷን መንከባከብና በፍቅር ማጥገብ ብቻ ነው” ይላል፡፡ የቀድሞ ጂም አሰሪ ዛሬ ወጣት አባወራ ሆኗል፡፡ “ሃኒ” እያለ ከሚያቆላምጣቸው ወይዘሮ ጋር በትዳር ተሳስሮ ሲኖር ሁለት ዓመት አስቆጥሯል፡፡

ዛሬ ዛሬ ሹገር ማሚዎች የልጅ ልጆቻቸው የሚሆኑ ለጋ ወጣቶችን በገንዘባቸው አጥምደው፣ የወሲብ እስረኛ የሚያደርጉበት ሁኔታ በከተማችን የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡ ሹገር ማሚዎቹ የኢኮኖሚ አቅማቸው የዳበረ፣ የፈለጉትን ለማድረግ የሚያስችል በቂ ገንዘብ ያላቸው፣ ዕድሜያቸው ከ48-65 ዓመት የሚሆናቸው ሲሆኑ ልጅና ቤት ንብረት ኖሮአቸው ትዳራቸው በሆነ ምክንያት የፈረሰ ወይም ባሎቻቸውን በሞት ያጡ፣ አንዳንድ ጊዜም በትዳር ውስጥ ሆነው ከባሎቻቸው የሚፈልጉትን የወሲብ ደስታ በተለያየ ምክንያት ማግኘት የተሳናቸው ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሹገር ማሚዎች፤ የቡና ቤት ባለቤቶች፣ ልጆቻቸው በውጪ አገር የሚኖሩና የራሳቸው ድርጅት ያላቸው ዘናጭ ሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሴቶች በአብዛኛው የሚያጠምዱት ዕድሜያቸው ከ23-30 ዓመት የሚሆናቸው ጥሩ ቁመናና ደንዳና ሰውነት ያላቸው፣ ተግባቢና ተጫዋች ወጣት ወንዶችን ነው፡፡ ወጣት ወንዶች፤ ሹገር ማሚዎችን የሚቀርቧቸው ለገንዘባቸው ብለው ነው፡፡ ይሄን ደግሞ ራሳቸው ሹገር ማሚዎቹ ቢያውቁም ሌላ አማራጭ ግን የላቸውም፡፡ በርካታ ወጣት ወንዶችም ለጊዜያዊ ችግራቸው መወጫ እነዚህን ሴቶች የሙጢኝ ብለው ሹገር ቤቢነቱን ያሣምሩታል፡፡

“የተወለድኩት ከድሃ ቤተሰብ ነው፤ትምህርቴን እንኳን በአግባቡ መማር እንዳልችል ድህነቴ ትልቅ እንቅፋት ሆኖብኛል፡፡ ከ10ኛ ክፍል ላይ የተቋረጠው ትምህርቴ እዛው ላይ እንደቆመ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ሥራ የለኝም፡፡ ህይወት ለእኔ አስቸጋሪ ነበረች፡፡ ተምሮ ሥራ ይዞ ይጦረናል ለሚሉት ደካማ ወላጆቼ፣ እኔው ራሴ ተጧሪና ሸክም መሆኔ በጣም ያበሳጨኝ ነበር፡፡ በተፈጥሮ የታደልኩት ጥሩ ቁመናና ደንዳናው ሰውነቴ ችግረኛ መሆኔን እየደበቁልኝ በምቾት የምኖር ያስመስሉኛል፡፡ ሰፈር አካባቢ ቆሞ መዋሉ ሲሰለቸኝ አካባቢያችን በሚገኝ አንድ ትልቅ የሴቶች ፀጉር ቤት አጠገብ የሞባይል ማደሻ ሱቅ ከፍቶ ከሚሰራው ጓደኛዬ ጋ እየሄድኩ መዋል ጀመርኩ፡፡ ይህም ከማሚ ጋር የምትዋወቅበትን አጋጣሚ ፈጠረልኝ፡፡
እውነት ለመናገር እኔ ስተዋወቃት በመጀመሪያ ለእንደዚህ አይነት ጉዳይ አስቤአት ወይንም እሷ አስባኛለች ብዬ አልነበረም፡፡ ፀጉሯን ለመሠራት ወደ ፀጉር ቤቱ በመጣች ጊዜ ሁሉ መኪናዋን የምታቆመው በጓደኛዬ ሞባይል ማደሻ ሱቅ በራፍ ላይ ነበር፡፡ ትውውቃችን እያደገ ሲሄድ ረዘም ላለ ጊዜ አብሮ መጫወትና መነጋገሩን ቀጠልን፡፡ ከፀጉር ቤቱ ተሰርታ ስትወጣ፤ ሻይ እንጠጣ እያለች ይዛኝ መሄድ ሁሉ ጀመረች፡፡ ጓደኛዬ ሁኔታው እንዳላማረውና ሴትየዋ ልታጠምደኝ እንደሆነ ነገረኝ፡፡
 
አድርጋው ነው፡፡ አብረን ቆይተን ስንለያይ እንደዘበት ጃኬት ኪሴ ውስጥ የምትሸጉጣቸው ረብጣ ብሮች ስንቱን ችግሬን እንደሸፈኑልኝ እኔ ነኝ የማውቀው፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ቤቴን ላሳይህ ብላ ይዛኝ ሄደች፡፡ ሳር ቤት አካባቢ ያለው የሴትየዋ ቤት ዘመናዊ ቪላ ነው፡፡ ቤቱ ከባሏ ጋር ፍቺ ሲፈፅሙ የደረሳት እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ ከባሏ ጋር የተለያየችው ስሜቷን ሊጠብቅላት ባለመቻሉ እንደሆነም አጫወተችኝ፡፡ ታዛዥ ፍቅረኛዋ ሆንኩ፡፡ የእናትና የልጅ ያህል የተራራቀውን ዕድሜያችንን ዘንግተን አብረን ማበዱን ተያያዝነው፡፡ ቤተሰቦቼን ከድህነት አወጣሁ፡፡ ያማረ ለብሼ ጥሩ መኪና ይዤ ወደአደኩበት ሰፈር ስሄድ መንደርተኛው ሁሉ ያከብረኛል፡፡ ለቤተሰቦቼ ሀብታም ሚስት ማግባቴን ነገርኳቸው እንጂ “ሚስቴን” አላሳየኋቸውም፡፡ በኋላ ላይም ከሴትየዋ ጋር የማደርገው ወሲብ አልጥምህ አለኝ፡፡ በዚህ ላይ በድህነት ዘመኔ አፈቅራት የነበረች ጓደኛ ነበረችኝ፡፡

ከሴትየዋ ጋር ከተዋወቅን ጀምሮ የራቅኋት ቢሆንም አልፎ አልፎ ማስታወሴና መናፈቄ አልቀረም፡፡ ጓደኛዬን ፈልጌ አገኘኋትና ጓደኝነታችንን ቀጠልን፡፡ አሁን ኑሮዩ የተደላደለ ሆነ፡፡ ገንዘብና ድሎትን ከማሚ፣ ፍቅርን ከጓደኛዬ ማግኘት ጀመርኩ፡፡ ይህ ሁኔታዬ ግን ብዙ አልቆየም፡፡ ማሚ ከጓደኛዬ ጋር ያለኝን ግንኙነት ደረሰችበት፡፡ ፀባችን እየከረረ ሄደ፡፡ በዚህ ጊዜ እኔ በቂ ገንዘብና ንብረት ይዤ ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ሹገር ማሚዬ እንደማታስፈልገኝ እርግጠኛ ነበርኩና ሆን ብዬ ፀቡ እንዲከር አድርጌ ተለየኋት፡፡ ራቫ ፎር መኪናዋንና በርካታ መጠን ያለው ገንዘቧን ግን በእጄ ለማድረግ ችያለሁ፡፡”

በትዳር ውስጥ ያሉና በዕድሜ የገፉ ባሎች ያሏቸው ሴቶችም በአብዛኛው ሹገር ማሚነቱን ይከውኑታል፡፡ እነዚህ ሴቶች የትላልቅ ቡና ቤቶች፣ ሆቴሎች፣ ሱፐር ማርኬቶችና ድርጅቶች ባለቤቶች ናቸው፡፡ በድርጅቶቻቸው ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ጥሩ ቁመና ያላቸው፣ ተግባቢ ወጣቶች ሹገር ማሚዎቹ አይን ከገቡ አበቃላቸው፡፡ በገንዘባቸው ሃይል አንበርክከው የወሲብ እስረኞቻቸው ማድረጉን ያውቁበታል፡፡ በራሳቸው ቤት፣ ወይም ቤት ገዝተው አሊያም ተከራይተው ፍላጐታቸውን ሁሉ እያሟሉ የሚያስቀምጧቸው ጐረምሶች፤ ሹገር ማሚዎቹን እንደ ኮረዳ እያሽኮረመሙ የወጣትነት ትኩስ ፍላጐትና ስሜት እንዲሰማቸው ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በአብዛኛው በሹገር ማሚዎች የተያዙ ወንዶች፤ ከ“ሚስቶቻቸው” ጋር አብረው በአደባባይ እንደ ልብ መታየትን አይፈልጉም፡፡ ይህ ደግሞ ሹገር ማሚዎቹ እንደ ፍላጐታቸው በየአደባባዩና በየመዝናኛ ቦታው ከ “ጐረምሳቸው” ጋር በፍቅር ለማበድ እንዳይችሉ ያደርጋቸዋል፡፡ አብይ ታሪኩ (ስሙ የተቀየረ) ስለ ሹገር ማሚው ሲናገር፤ በተለየዩ መዝናኛ ቦታዎች ላይ ከእኔ ጋር አብሮ መታየት እንዲሁም በየአደባባዩ በማቀፍና በመሣም ፍቅሬን እንድገልፅላት ትፈልጋለች፡፡ ይህ ደግሞ እኔ ፈፅሞ የማልወደውና የማልፈልገው ጉዳይ ነው” ሲል ገልፆታል፡፡ አብዛኛዎቹ ሹገር ማሚዎች፤ ለፍቅረኞቻቸው ፈፅሞ ነፃነትን አይሰጡም፡፡ ከእኔ ከተለየ ሌላ ሴት (ወጣት) “ይጠብሳል” ብለው ስለሚያስቡ የ “ጐረምሶቻቸውን” ውሎ መከታተል ይፈልጋሉ፡፡ አስር ጊዜ እየደወሉ “የት ነህ?” የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውም የተለመደ ነው፡፡ ከወንድ ጓደኞቻቸዉ ጋር እንኳን ቢሆን ለረዥም ጊዜ እየተዝናኑ እንዲቆዩ አይፈቀድላቸውም፡፡ ከሹገር ማሚዎቻቸው ጋር በጊዜ ሂደት ተስማምተው በፍቅር የወደቁ፣ ተጋብተው ህጋዊ ትዳር የመሰረቱም በርካታ ወጣት ወንዶች አሉ፡፡

“ስንጀምር በዚህ መልኩ ግንኙነታችን ይቀጥላል ወይም ዘላቂነት ይኖረዋል ብዬ አልነበረም፡፡ በሂደት ግን በቃ ተመቸችኝ ፤ስንጀምር የነበሩን በርካታ ልዩነቶች እየጠፉ ፍላጐታችን እየተቀራረበ ሄደ፡፡ ታምኚኛለሽ--- ድብን ያለ ፍቅር ያዘኝ፡፡ የእንጋባ ጥያቄውን ያቀረብኩላት እኔ ነኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ የማግኘት ተስፋ እንደሌለኝ ባውቅም ብዙ ስሜት አልሰጠኝም፡፡ የምትወደድ አይነት ሴት ነች፤ ተመችታኛለች፡፡ አሁን እንኳን ከተጋባን ሶስት ዓመት አልፎናል፡፡ የእውነት ነው የምወዳት” ዘውዱ (ስሙ የተቀየረ) ስለ ሹገር ማሚው የተናገረው ነው፡፡

ሹገር ማሚዎች በአብዛኛው የሚጠሉት ነገር ከሹገር ቤቢዎቻቸው ጋር በመዝናኛ ቦታዎች ሲሄዱ “ልጅሽ ነው?” የሚሉ የጓደኞቻቸውን ጥያቄ ነው፡፡ እንዲህ እየተባሉም ቢሆን ሹገር ቤቢዎቻቸው ተለይተዋቸው እንዲቀሩ አይፈልጉም፡፡ ዛሬ ዛሬ በርካታ ወጣቶች፤ ሹገር ማሚዎችን እያሳደዱ መተዋወቅና ማጥመዳቸው የተለመደ ተግባር እየሆነ ነው፡፡ ከሹገር ማሚዎቻቸው የሚያገኙትን ገንዘብ የዕድሜ እኩያዎቻቸውን (ፍቅረኞቻቸውን) ለማዝናናት ይጠቀሙበታል፡፡ በሹገር ማሚዎቹ ለመመረጥና መስፈርቶቻቸውን ለማሟላት ወጣቶቹ ትግል ይዘዋል፡፡ ሹገር ማሚዎቹ በአብዛኛው ሰውነታቸው ደልደል ያለ ተጫዋችና ተግባቢ ወጣት ወንዶችን ለፍቅረኝነት ይፈልጋሉ፡፡ ሹገር ማሚዎቹ እነሱ የሚፈልጉትን አይነት አገልግሎት እየሰጡ አብረዋቸው የሚዘልቁ ወጣቶች የት እንደሚገኙ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ለዚህ ተግባር ተመራጩ ቦታ ጅምናዚየሞች፣ ማሳጅ ቤቶች፣ ሲኒማ ቤቶችና ናይት ክለቦች ናቸው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ሹገር ማሚዎች በአገናኝ ደላሎች አማካኝነት የፈለጉትን ወጣት ከእጃቸው ለማስገባት አይቸገሩም፡፡ እድሜ ለቴክኖሎጂ! ዛሬ ደግሞ ሹገር ማሚዎች የፈለጉትን አይነት ወጣት የሚያገኙበትና የሚቀጣጠሩበት ድረገፅ ተከፍቶ ሥራውን በስፋት እየሰራ ይገኛል፡፡ Friendfinder:sugermummy tips.com, Adult friend finder seeking arrengment.com የተባሉት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ዛሬ ዛሬ ከታዋቂ አርቲስቶቻችን መካከል በሹገር ማሚ ወጥመድ ተይዘው ተፈላጊውን አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ወጣቶች እንዳሉም ይነገራል፡፡ ከዕድሜ ጋር ግብግብ የተያያዙት ሹገር ማሚዎች፤ የዕድሜያቸው ጀንበር አዘቅዝቃ ይህቺን አለም ከመሰናበታቸው በፊት ያሻቸውን ለማድረግ፤ የፈለጉትን ለመፈፀም ትግል ይዘዋል፡፡ ወጣት ወንዶቹም (ሹገር ቤቢዎቹ) የኢኮኖሚ ችግራቸውን የሚቀርፉላቸውን ሹገር ማሚዎች ለመንከባከብና ለማስደሰት እየተጉ ይገኛሉ፡፡

ሰላማዊ የመብት ጥያቄ በሠለጠነ ውይይት እንጂ በአፈናና ግድያ መቼም ቢሆን አይፈታም!

የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ
ኅምሌ 27 ቀን 2005 ዓ/ም

22 ዓመት ሙሉ ነፍጡን ከፊት አስቀድሞ የተፈጥሮ፣ ዴሞከራሲያዊና ሕጋዊ የሆኑ መብቶቹን ለማሰከበር በግምባር ሲታገል የቆየውን ምስኪን ህዝብ በገፍ እያሠረ፤ ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ እያሠቃየውና ግፍ በተሞላበት ግድያም እየቀጣው የቆየው የህወሓት/ኢሕአዴግ ግፈኛ አገዛዝ፣ ይኸው ዛሬም በሰላማዊው ሕዝብ ላይ ባፈናና ግድያው ቀጥሎበት ይገኛል።

 ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ/ም በምዕራብ አሩሲና በሻሸመኔ አካባቢ ኢማሞቻችን/መሪዎቻችን ይፈቱ እያሉ በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ባሰሙ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የግፍ ግድያ መፈጸሙን ሽንጎው የተገነዘበው በከፍተኛ ሃዘን ነው። ልጆቻችሁ፣ አባቶቻችሁ፤ እናቶቻችሁ፣ እህቶቻችሁና ወንድሞቻችሁ ለህወሓት/ኢሕአዴግ ጥይት ሰለባ ለሆኑባችሁ ወገኖች ሁሉ ጽናቱንና ቁርጠኝነቱን ይስጣችሁ እያልን፤ ዛሬም እንደትናንቱ የታፈነ ድምጻችሁን በማስተጋባትና ጥያቄያችሁም ፍትሃዊ ምላሸ እንዲያገኝ ከጎናችሁ በመቆም ለመታገል ቃል እንገባላችሁዋለን።

የህወሓት/ኢሕአዴግን ማንቁርት ይዞና ሥልጣኑን ጠቅልሎ በመያዝ ከፋፋይ የፖለቲካ መርዙን ሲረጭ የኖረው አምባገነን መሪያቸው የዛሬ ዓመት ገደማ ሲሞት ምናልባት የፖለቲካ ምህዳሩ በመጠኑም ቢሆን ተከፍቶና ተለሳልሶ ቢያንስ አፈናና ጭፍጭፋ ይቆምና የፖለቲካ እሥረኞችም ይፈቱ ይሆናል የሚል እጅግ አናሳም ቢሆን ግምት ተንጸባርቆ ነበር። ባመቱ የመሠከርነው ዕውነታ ግን ያው የተለመደው አፈናና ግድያ በማናለብኝነት መቀጠሉን ነው። ከዚህ ካሁኑ ግድያ አንድ ቀን አስቀድሞ ባዲሱ የፖሊስ ኮሚሸነር ትዕዛዝ ባገር ውስጥ የዜና ማሠራጫ ተነገረ እንደተባለው ማስጠንቀቂያ ከሆነ፤ ደም አፍስሰው ያልጠገቡትና ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ ያሉ መሪዎች የግፍ ዱላቸውን በሌሎችም አካባቢዎች ሊቀጥሉበት የወሰኑ ይመስላል።

ከዘመን ብዛትና ከኢትዮጰያ ህዝብ ቁርጠኝነት እነዚህ የዘመናችን ገዢዎቹ የተማሩትና ሊማሩም ያሰቡት ነገር ምን ይሆን እያልንና ሥልጣኔ በጎደለው ድርጊታቸው እየተደመምን፤ ሕዝባችን ግን በገዥዎች ትንኮሳ ሳይረበሽ ባጠመዱለትም ወጥመድ ሳይጠለፍ የጀመረውንም እልህ አሰጨራሽ እና የሰለጠነ ትግል አጠናክሮ እንዲገፋ አደራ እያልን፤ እኛም ከጎኑ ቆመን ከመታገል ወደሁዋላ እንደማንል ቃል እንገባለን።

ሁሉም ኢትዮጵያውያንም ይህን የህወሓትን/ኢሕአዴግን ኋላቀር አረመኔአዊ ጭፍጨፋ አጥበቀው እንዲያወግዙና የመብት ጥያቄን ከሚያነሱ ሁሉ ጎን በመሰለፍ ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ፤ የዕምነት ነጻነት እንዲከበር፣ እንዲሁም የታሰሩት እንዲፈቱ ትግሉን እንዲያጠናሩ ጥሪአችንን እናቀርባልን።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

Tuesday, August 6, 2013

ወያኔዎች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን በሽብር ተግባር ለመወንጀል ቦምብ አያፈነዱም ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው

August 6, 2013
እንደልቡ ወርቁ

A bomb exploded near a court in the west of Ethiopia's capital Addis Ababaባለፉት ሀያ አንድ አመታት ኢትዮጵያ ውስጥ “የሽብር ተግባራት” የሚመስሉ “ሽብሮች” ተከናውነዋል። በሚኒባስ ዉስጥ፣ በሆቴሎች ዉስጥ፣ በቤተ ክርስትያን ቅጥር ግቢ ዉስጥ ወዘተ… ይሁንና ለአንዳቸውም የሽብር ጥቃቶች ባለቤት ተገኝቶላቸው አያውቅም፣ ባለቤት መገኘቱ ይቅርና የረባ ተጠርጣሪ ተይዞ ፍርድ ቤት ሲመላለስ እንኳ አልታየም።

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ህዝቡ ግን “ሽብሮቹን” የሚፈጽመው እራሱ ወያኔ ነው በማለት ያጉረመርሙ ነበር።
ህዝቡም ሆነ ተቃዋሚዎች በሽብር ተግባራቱ ወያኔን ክፉኛ ከሚጠረጥሩባቸው ምክንያቶች ውስጥ፣

1) ወያኔዎች በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ጥላቻን እንዳተረፉ ስለሚረዱ ማናቸውም አይነት የፖለቲካ ድርጅት ሀገር ውስጥ መንቀሳቀስ ከቻለ ህልውናቸው እንደሚያከትም እርግጠኛ ሆነዋል። ስለዚህም የሚያስፈራቸውን የተቃዋሚ ድርጅት በሽብር ተግባራት ፈርጆ ከጫወታ ውጭ ማድረግ የዘወትር ተግባራቸው ነው። ታድያ እንዚህን ያስፈሯቸውን ፖለቲከኞችና የፖለቲካ ድርጅቶች በሽብር ተግባር ለመወንጀልና ለመክሰስ ሽብር ቢጤ መከናወን አለበት።
 
2) ሌላው ወያኔዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር አለ ብለው እራሳቸውን የምዕራባውያን የጸረ-ሽብር አጋር አድርገው ለማቅረብ ያላቸው ፍላጎት ነው። ሶማሊያ ውስጥ ያሉትን አክራሪዎች እጃቸው ኢትዮጵያም ይደርሳል በማለት ምዕራባውያንን ማሳመንና ማግባባት ያስፈልጋቸዋል፣ ለዚህም ደግሞ እዚህና እዚያ በአካራሪዎች የተፈጸመ የሚመስል የሽብር ተግባር እንዲኖር ያስፈልጋል።
 
ይህን የህዝቡንና የተቃዋሚዎቹን ጥርጣሬ እውነት ነው የሚያስብል ሁኔታ የተከሰተው ግን ዘግይቶም ቢሆን “ዊኪሊክስ” የአሜሪካ ሚስጥራዊ ሰነዶችን ይፋ ባደረገ ማግስት ነው። የአሜሪካ ዲፕሎማቶች “በአዲስ አበባ የሚፈነዱት ቦንቦች የአሸባሪዎች ጥቃት ናቸው ብለው እንደማያምኑ” የሚያመላክቱ መልዕክቶችን በተደጋጋሚ ከአዲስ አበባ ወደ ዋሽንግቶን ዲሲ ሰደዋል።
ቦታ እየቀያየረ መጫወት የማይሆንለት የጥንቱ የጥዋቱ የደደቢቱ ወያኔ ዛሬም ድረስ ይህኑ ተጨፈኑ ላሞኛችሁ “ሽብር መጣባችሁ” ድርጊቱን ገፍቶበት ይገኛል።

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በሀይማኖታቸው ጉዳይ መንግስት ጣልቃ በመግባቱ ፍጹም ሰላማዊና ስልጡን በሆነ መንገድ ከአንድ አመት በላይ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው የፍትህ ያለህ በማለት ላይ ናቸው።

ምንም እንኳ ወያኔ በጸረ-ሽብር አጋርነቱ ታውቆ ከአሜሪካና ምዕራባውያን አሳዳሪዎቹ ዘንድ እርጥባንና የፖለቲካ ድጋፍ እየተቸረው የዘለቀ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን “አሸባሪ” ናቸው ብሎ ለማስፈረጅ ግን አልተቻለውም።
ሰሞኑን የፊታችን አርብ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የኢድን በዓል አስመልክተው በመላ ሀገሪቱ ሊያደረጉ ያሰቡት ተቃውሞ ወያኔን አስደንግጦታል። በኮፈሌ ከ25 በላይ ንጹሀን ሙስሊሞችን በአጋዚ የጎሳ ወታደሮቹ አስጨፍጭፎ ሲያበቃ በአዲስ አበባ ደግሞ ሙስሊም ወላጆችን ሰብስቦ ልጆቻችሁ ለተቃውሞ እንዳይወጡ እያለ ይማጸናል።

ወያኔ ጭንቀቱ እንደበረታበት የሚያሳየው ሌላው ትዕይንት ደግሞ፣ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ ከ30 በላይ ኤምባሲዎች የፊታችን አርብ የሽብር ጥቃት ሊፈፀም እንደሚችል በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በኩል መልዕክት ማስተላለፉ ነው።
ወያኔዎች ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን በሽብር ተግባር ለመወንጀል ቦምብ አያፈነዱም ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። በዚህ ወቅት ነቃ ብሎ አካባቢን እያጠኑ መንቀሳቀስ ደግሞ ብልህነት ነው።

ሰባር ዜና-አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ ከአገር ሸሽተው ጥገኝነት በመጠየቅ አሜሪካ ገቡ!

August 6, 2013
ድምፃችን ይሰማ
ማክሰኞ ሐምሌ 30/2005
‹‹ህሊናዬ የማያምንበትን እንድሰራ ተገድጃለሁ›› አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ
የመንግስት ክስ መጨረሻው በውል እንኳ አልታወቀም፤ ቀጠሮውም ም እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የለም!
የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችን፣ አሊሞችንና ዳኢዎችን መንግስት በሀሰት በሽብር ወንጀል ጠርጠሮ ከከሰሳቸዉ አንድ አመት ቢያልፍም እስካሁን እልባት ላይ አለመደረሱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ክስ ውስጥ ከከሳሽ መንግስት አቃቢያን ህግ መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ቴድሮስ ባህሩ ‹‹ህሊናየ የማያምንበትን እንድሰራ ተገድጃለሁ›› በማለት አገራቸውንና ስራቸዉን ጥለዉ ከአገር ሸሽተው ጥገኝነት በመጠየቅ አሜሪካ መግባታቸው ተረጋገጠ፡፡ አቃቤ ሕግ ቴዎድሮስ ባህሩ ሲሰሩ የነበረበትን የስራ ጉዳይ ሰነድ እንኳን ሳያስረክቡ ጥገኝነት ጠይቀዉ ከነቤተሰባቸዉ አሜሪካ እንደገቡ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡Ethiopian Musilms
እንደ ታማኝ ምንጫችን ገለፃ ከመጀመሪያዉ የክስ ምስረታ ጊዜ ጀምሮ በተለይ የማእከላዊ ወንጀል ምርመራ ፖሊሶች በሙያቸዉ ጣልቃ እየገቡባቸዉ ብዙ አቃቢያን ህግ ባለሙያዎች ከፍተኛ ምሬት እንዳለባቸው አስታውሶ፤ የአሁኑ የአቶ ቴዎድሮስ ሙያቸዉን ለቀዉ ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረጋቸዉ ዋናዉ ምክንያትም እንደሚታወቀዉ ለረጅም ጊዜ በተጠርጣሪ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላቶች ላይ ስልጠና የተሰጣቸው ሰዎች የሀሰት የሰዉ ምስክርነት ጋዜጠኛም ሆነ ቤተሰብ እንዲገባ ባልተፈቀደበት ሁኔታ በዝግ ችሎት ሲሰማ የቆየ ሲሆን ይህም ተጠናቆ የቪዲዮ መረጃ መቅረብ ተጀምሮ ነበር፡፡
ለጥቂት ቀናት የታየዉ ቪዲዮ መረጃ ለረጂም ጊዜ ሲሰማ የነበረዉን የሀሰት የሰዉ ምሰክርነት ሙሉ በሙሉ ከንቱ ስላስቀረባቸዉ በአቃቢያን ህግ፣ በደህንነትና በፖሊስ መካካከል ከፍተኛ ዉጥረት ተፈጥሯል፡፡ ለዚህም ይመስላል የፍርድ ቤት ቀጠሮዉ አለመከበሩ ብቻ ሳይሆን ለመቼ እንኳ እንደሚቀጥል ሳይታወቅ ሂደቱ ሁን ተንጠልጥሎ የቀረዉ፡፡ አቶ ቴድሮስ ካሉበት ሁነው ሙሉ የነበረዉን ሂደትና መረጃዉን ለህዝብና ሚዲያ ይፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Monday, August 5, 2013

የአንድነት ሰልፎች የመጀመሪያ ድሎች መንግስት ከ4 ዓመት በኋላ በፀረሽብርተኝነት ህጉ ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጀ

ስኬት አንድ!!!!!!!!!!!! የአንድነት ሰልፎች የመጀመሪያ ድሎች መንግስት ከ4 ዓመት በኋላ በፀረሽብርተኝነት ህጉ ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጀ ሪፖርት ጥንቅር በምንሊክ ሳልሳዊ ====================== አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን ለማሻር የጀመረው የፊርማ ማሰባሰብ ዘመቻ በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና የመዋያያ አጀንዳ መሆኑን ተከትሎ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት ህጉ ከፀደቀ ከ4 ዓመት በኋላ ፓርቲዎች በህጉ ላይ ያላቸውን አቋም የሚያስረዱበት መድረክ አዘጋጀ፡፡

 ኢቲቪ አንድነት ፓርቲን ጨምሮ ለተለያዩ ፓርቲዎች ደብዳቤ የላከ ሲሆን አንድነት ፓርቲ በበኩሉ በ5 የክልል ከተሞች ለሚያደርገው ህዝባዊ ንቅናቄ አመራሮቹን ስላሰማራ የውይይት መድረኩ እንዲራዘምለት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ በስኬት እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡