Thursday, March 21, 2013

የወያኔ ዘረኝነት ፖሊሲ ትግርኛ የማይናገሩ ኢትዮጵያዉያንን የበይ ተመልካች እያደረገ መሆኑን የግንቦት 7 ጥናታዊ ሪፖረት አጋለጠ

ባለፈዉ ሳምንት ኢትዮ ተሌኮም ዉስጥ ስር እየሰደደ የመጣዉን የወያኔ ዘረኝነት በመረጃ በተደገፈ ጥናታዊ ዘገባ ለህዝብ ይፋ ያደረገዉ የግንቦት 7 የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ በዛሬዉ ዕለት ደግሞ በተመሳሳይ ደረጃ አደረጃጀቱን፤ አወቃቀሩንና የሰዉ ኃይል አመዳደቡን
ethio-metal-coorporation_jan_2013-small ለአንድ አመት ሙሉ በቅርበት የተከታተለዉን የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺንን ጥናታዊ ዘገባ ለኢትዮጵያ ህዝብ ይፋ አድርጓል። ለኢትዮጵያ ከባድ እንዱስትሪ ግንባታ መሠረት ለመጣልና በአገሪቱ ኮንስትራክሺን እንቅስቃሴ ከፍተኛ ሚና እንዲጫወት ታስቦ የተዋቀረዉ የብረታብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን የኢትዮጵያ መሆኑ ቀርቶ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪ የህወሀት መኮንኖች እጅ መግባቱን ያጋለጠዉ የኸዉ የግንቦት 7 ጥናት ኮርፖሬሺኑ ከዋና ዳይረክተር እስከ ተራ ቴክኒሺያኖች ስረስ የህወሀት አባል በሆኑ የትግራይ ተወላጆች ቁጥጥር ስር ወድቋል ብሏል። የጥናቱ ሙሉ ዘገባ እንደሚገተለው ቀርቧል።
መነቀል ያለበት ስር የሰደደ የወያኔ ዘረኝነት 
(በግንቦት 7 የአገር ዉስጥ ኢንተሊጀንስ ዘርፍ የተጠናና የተዘጋጀ)
ዘረኛዉ የወያኔ ስርአት የኢትዮጵያን ህዝብ ለጥቂት አመታት ኢትዮጵያዊያንን ባሰረና በገደለ ቁጥር ገንዘብ የሚሰጡትን አለም አቀፍ ድርጅቶችና አርዳታ ሰጪ አገሮች ደግሞ 21 አመት ሙሉ ካታለለበት መንገድ አንዱ የፌዴራል ስርአት መስርቼ ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር አደረኳት የሚለዉ ባዶ አባባሉ ነዉ። ይህንን ተጋልጦ እርቃኑን የቀረ አባባል የኢትዮጵያ ህዝብ ተገንዝቦ ወያኔን መታገል ከጀመረ ቆይቷል፤ ዋና ዋናዎቹ እርዳታ ለጋሾችም ቢሆኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ ደህንነት ግድ የሌለዉ ወያኔ ወጣቶቻችንን እየገበረ ጥቅማቸዉን ስለሚያስከብርላቸዉ ነዉ እንጂ ወያኔ እንኳን እየደገፉ እርዳታ የሚሰጡት በአንድ ተርታም አብረዉ ለመቀመጥ የማይመች የእኩዮች ስብስብ እንደሆነ ካወቁ ቆይቷል።
ህወሀት በፌዴራል ስርአቱ ዉስጥ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ በሚጠራዉ ፓርላማ ዉስጥ ያለዉ መቀመጫ 8 ብቻ ነዉ። እዚህ ፓርላማ ዉስጥ የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ የሚለዉ ህወሀት ነዉ፤ ትግራይ ደግሞ ኢትዮጵያ ዉስጥ አንድ ክልል ናት። የተቀሩት 8 ክልሎች በዚህ የእኩልነት ምልክት በሆነዉ ፓርላማ ዉስጥ ያላቸዉ የመቀመጫ ብዛት 569 ነዉ። ሆኖም በወያኔ መንደር የፖለቲካ ስልጣን ምንጭ ህዝብ ሳይሆን ጠመንጃ ነዉና ወያኔ ፓርላማዉ ዉስጥ 8 ወንበር ብቻ ይዞ 569 ወንበር ያላቸዉን የኦሮሚያን፤ የአማራን፤ የደቡብ ክልልንና የተቀሩትን አምስት ክልሎች እንደ መኪና ይነዳቸዋል። የየክልሉን መሪ ይሾማል፤ ይሽራል ወይም የማይስማማዉን የክልል ባለስልጣን ያስራል። ፓርላማዉ ዉስጥ አንድ መቶ ሰባ ስምንት፤ አንድ መቶ ሰላሳ ስምንትና አንድ መቶ ሀያ ሦስት መቀመጫ ያላቸዉ የኦሮሚያ፤ የአማራና የደቡብ ክልል ፓርቲዎች በራሳቸዉ ጉልበትም ሆነ ህልዉና ስለሌላቸዉ አንዱ ከሌላዉ የበለጠ ስልጣን ወይም ሹመት ለማግኘት አንጋጥጠዉ ወደ ላይ የሚመለከቱት ህወሀትን ነዉ።
ለመሆኑ ወያኔ የፌዴራል ስርዐት መስርቼ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት አረጋገጥኩ ሲል ምን ማለቱ ነዉ? እኩልነቱ የፖለቲካ ነዉ የኤኮኖሚ? ወይስ በየአመቱ ህዳር ወር ላይ የፌዴራልዝም ቀን ሲከበር እንደምናየዉ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት የተረጋገጠዉ በዘፈን ብቻ ነዉ? የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስርዐት ከላይና ከታች የሚቆጣጠረዉና ይህንኑ የፖለቲካ ስርአት የሚደግፍ የኤኮኖሚ መዋቅር ዘርግቶ የአገራችንን ኃብት የሚቦጠብጠዉ ህወሀት ብቻ ነዉና የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ተረጋገጠ የሚባለዉ አባባል ከተራ የቃላት ድርደራ ዉጭ ሌላ ምንም ትርጉም የለዉም።
አፄ ቴዎድሮስን እንደ ልጅነት ሞዴሉ የሚመለከተዉ ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም የመጀመሪያዉን የኢትዮጰያ ዘመናዊ ወታደራዊ እንጂኔሪንግ ተቋም ሲመሰርት ስሙን “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ ነበር የሰየመዉ። ስያሜዉ የአፄ ቴዎድሮስ ስራና ስም ህያዉ ሆኖ እንዲኖር ለማድረግ የተደረገ ሙከራ እንደነበር ግልጽ ነዉ። የኢትዮጵያን የቀድሞ መሪዎች በጅምላ የሚዘልፈዉ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት ከአንዲት የአገር ዉስጥ ጋዜጠኛ ጋር ባደረገዉ ቃለ ምልልስ አፄ ቴዎድሮስ ጋፋት ላይ ያሰሩትን መድፍና መንግስቱ ኃ/ማሪያም “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ የሰየመዉን ወታራዊ ተቋም አስመልክቶ ሁለቱንም መሪዎች ሲያንቋሽሽ ተደምጧል። የሚገርመዉ ዛሬ ወያኔ የብረታብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺን ብሎ የሚጠራዉ ግዙፍ የሲቪልና ወታደራዊ እንዱስትሪ ተቋምና በዚህ ተቋም ዉስጥ የሚገኙ ዋና ዋና ፋብሪካዎች ደርግ “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ብሎ የጀመራቸዉ የከባድ እንዱስትሪ ጅምሮች ናቸዉ። በ1970ዎቹ አጋማሽ ላይ “ጋፋት እንጂኔሪንግ” ስራዉን ሲጀምር የፋብሪካዉ ሀላፊዎች፤ እንጂኔሮች፤ የመምሪያ ሀላፊዎችና ቴክኒሺያኖች የስራ ዕድል የሚያኙት የትምህርት ደረጃቸዉ፤ ችሎታቸዉና የሰራ ልምዳቸዉ ብቻ እየታየ ነበር፤ ወይም ትግርኛ ስለተናገረ ስራ የሚከለከል አማርኛ፤ ኦሮምኛ ወይም ሌላ ቋንቋ ስለተናገረ አድሎ የሚደረግለት ዜጋ አልነበረም። ዛሬ ወያኔ ከደርግ ስርአት ተረክቦ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ብሎ በሰየመዉ እንዱስትሪ ዉስጥ አብዛኛዉን የሀላፊነት ቦታ የያዙ ሰዎች ለቦታዉ የበቁት በስራ ልምዳቸዉና ችሎታቸዉ ሳይሆን የተወለዱበት ዘርና የሚናገሩት ቋንቋ እየታየ ነዉ። ወታራዊዉ አምባገነን ደርግም ሆነ ወያኔ ይህንን እንዱስትሪ የወደፊቱ የኢትዮጵያ ከባድ እንዱስትሪ ዘርፍ መሰረት ይሆናል የሚል ራዕይ ነበራቸዉ። ልዩነታቸዉ የእንዱስትሪዉ አስፈላጊነት ላይ ሳይሆን እንዱስትሪዉን ማን ይቆጣጠረዋል የሚለዉ ጥያቄ ላይ ነዉ። ደርግ በሱ መሪነት ለማንም ችሎታ ላለዉ ኢትዮጵያዊ የእንዱስትሪዉን በር የከፈተ ሲሆን ወያኔ ግን እንዱስትሪዉ እንዳለ በአንድ ዘር ቁጥጥር ስር እንዲገባ አድርጓል። ደርግም ወያኔም አምባገነኖች ስለሆኑ አንዱስትሪዉን ከህዝብ ቁጥጥር ዉጭ አድርገዉታል፤ ወያኔ ግን ከአምባገነንም የጎሳ አምባገነን ስለሆነ ይህንን ትልቅ እንዱስትሪ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች ቁጥጥር ስር አድርጎታል።
ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ባለለፉት ሦስት አመታት ይህንን ወያኔ ገነባሁ የሚለዉን የፌዴራል ስርአትና በስርአቱ ዉስጥ የተለያዪ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የሚጫወቱትን ሚና በመረጃ አስደግፎ ለኢትዮጵያ ህዝብና ለአለም አቀፉ ህብረተሰብ አቅርቧል። የዛሬ ሁለት አመት ግንቦት ሰባት በኢትዮጵያ መላከያ ሰራዊት ዉስጥ የተዘረጋዉን የወያኔ የዘረኝነት መረብ ከሰሞኑ ደግሞ የኢትዮቴሌኮምን የዘረኝነት አደረጃጀት በመረጃ በማስደገፍ ለህዝብ ማቅረቡ ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮረፓሬሺንን የዘረኝነት አደረጃጀትና በዚህ አደረጃጀት ዉስጥ ማን ምን እንደሆነ ያጣናዉን የጥናት ዉጤት በመረጃ አስደግፎ ያቀርባል። ግንቦት ሰባት ሃያ አራት ሰአት ሙሉ የሚከታተሉትን የወያኔ የደህንነት ሰራተኞች ከበባ ጥሶ የወያኔን ዘረኝነት የሚያጋልጡ መረጃዎችን ከራሱ ከወያኔ ጓዳ እየጎተተ አዉጥቶ ለህዝብ የሚያቀርበዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔን ዘረኝነት አያውቀዉም በሚል አስተሳሰብ አይደለም። ግንቦት ሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ የፈጠረዉ ከፍተኛ የመረጃ ጉድለት አለ ብሎ ያምናል፤ስለሆነም ህዝቡ የወያኔን ዘረኝነት ቢረዳም መጠኑን፤ስፋቱንና ጥልቀቱን በሚገባ ላያዉቅ ይችላል ብለን እናምናለን። በሌላ በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በየቀኑ ደሙን እንደ መዥገር የሚመጠዉን ወያኔን የመሰለ የጀርባ ላይ አጥንት ተሸክሞ መኖር የለበትም ብለን ስለምናምን ህዝብን ለትግል ከምናዘጋጅበትና ከምናነሳሳባቸዉ መንዶች ዉስጥ አንዱ እንደዚህ ህዝብ በገዛ አገሩ “እኩል አደረግንህ” ብለዉ በሚነግሩት ከሀዲዎች ቅኝ አገዛዝ እየተገዛ መሆኑን በማሳወቅ ነዉ።
ባለፈዉ ሳምንት የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዋና ዳይረክተር ብርጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ ፓርላማ ዉስጥ ተገኝቶ የኮርፓሬሺኑን የሁለት አመት የስራ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ኮርፓሬሺኑ የግል ባለኃብቶችን አያሳትፍም እንዳዉም እያቀጨጫቸዉ ነዉ፤ ለሙስና የተጋለጠ ነዉ፤ ደግሞም አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኛ የመከላከያ ሰራዊት አባል ነዉና ይህ አሰራር ሠራተኞችን ለማስተዳደር አስቸጋሪ አይሆንም ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዉለት ነበር። የግሉን ዘርፍ መቅጨጭ በተመለከተ ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉንም ቢሆን “የወያኔ ዘርፍ” እንጂ የግል ዘርፍ የሚባል ነገር የለምና ጥያቄዉ መቅረብም አልነበረበትም። ሙስናም ቢሆን የወያኔ ስርዐት ዋናዉ መገለጫ ባህሪይ ስለሆነ ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ ሙስና “ሙስናን እናጠፋለን” ስለተባለ ብቻ የሚጠፋ ነገር አይደለም። ግንቦት ሰባትን እጅግ በጣም ያሳዘነዉና ያስገረመዉ ነገር ያንን ወያኔ የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት ነዉ ብሎ የሚናገርለትን ፓርላማ ያስጨነቀዉ (ተጨንቆ ከሆነ) የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር መዉደቁ ሳይሆን አብዛኛዉ የኮርፖሬሺኑ ሰራተኞች የመከላከያ ሰራዊት አባላት መሆናቸዉ ነዉ። በእርግጥ የአንድ ትልቅ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች በአብዛኛዉ የጦር ሠራዊት አባላት ሲሆኑ የአሰራርና የአስተዳደር ችግር መፈጠሩ አይቀርም፤ ሆኖም የሠራዊቱ ታማኝነት ለህዝብ ታዛዥነቱ ደግሞ ለህገ መንግሰስቱ ብቻ ቢሆን ኖሮ ይህ ችግር በቀላሉ የሚወገድ ችግር ይሆን ነበር።
የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን በአምሰት አመቱ የእድገትና የትራንስፎርሜሺን ፕላን ዉስጥ የሚጫወተዉን ቁልፍ ሚና ፓርላማዉ በሚገባ የሚገነዘበዉ ይመስለናል፤ ታዲያ ይህ በአገር እድገት ዉስጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወተዉ ኮርፖሬሺን ሙሉ በሙሉ በአንድ ብሔር ቁጥጥር ስር ሲወድቅ ምነዉ የብሔረሰቦች እኩልነት ምልክት የሆነዉ ፓርላማ አፉን ዘግቶ ተመለከተ? ፓርላማዉን ይበልጥ የሚገድደዉ የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ በአንድ አናሳ ብሔረሰብ ሙሉ ቁጥጥር ስር ሆኖ ሌሎቹ ብሔረሰቦች ተመልካች ሲሆኑ ነዉ ወይስ የአንድ ኮርፖሬሺን ሰራተኞች በአብዛኛዉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሲሆኑ ነዉ? ለመሆኑ የወያኔ ዘረኝነት በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን ዉስጥ ምን ያህል ዘልቆ ገብቷል? የኦሮሞ፤ የአማራ፤ የሶማሌ፤ የሲዳማና ሌሎቹም ብሔር ብሔረሰቦች በዚህ ለአገር እድገት ቁልፍ በሆነ ኮርፖሬሺን ዉስጥ የሚጫወትቱት ሚና ምን ይመስላል?
የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በአስራ አንድ መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች የተዋቀረ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎቸን ያስተዳድራል፤ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀቀበት ቀን ድረስ ቁጥራቸዉ በዉል ተለይቶ ባይታወቅም አስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎችም እያንዳንዳቸዉ በስራቸዉ ብዙ ፋብሪካዎችንና የማምረቻ ተቋሞችን ያቀፉ ናቸዉ። የኮርፖሬሺኑን አስራ አንድ ትላልቅ መምሪያዎችና አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱሰትሪዎች በዋና ሀላፊነት፤ በዳይረክተርነተና በምክትል ዳይረክትርነት የሚመሩ 29 የከፍተኛ አመራር አባላት አሉ። ከእነዚህ 29 ከፍተኛ አመራር አባላት ዉስጥ 69 በመቶዉ ወይም ሃያዉ ህወሀት ሆን ብሎ ያስቀመጣቸዉ ትግርኛ ተናጋሪ የሆኑ ወታደራዊ መኮንኖች ናቸዉ።በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የኦሮሞና የአማራ ተወላጆች ያላቸዉ ቦታ 31 በመቶ ወይም ከእያንዳንዳቸዉ በቅደም ተከተል ሦስትና ስድስት ሰዎች ብቻ ሲሆን ከተቀሩት አምስት ክልሎች በዚህ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ የተመደበ አንድም ሰዉ የለም። ኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ እንዱስትሪ ለመገንባት በሚደረገዉ ጥረት ዉስጥ ከፍተኛዉን ሚና ይጫወታል የሚባለዉ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን በሲቪልና ወታራዊ መምሪያዎች ተከፋፍሎ የተዳራጀ ሲሆን በስሩ አስራ ሦስት ግዙፍ እንዱስትሪዎች ይገኛሉ። እነዚህን እንዱስትሪዎች በማስተዳደሩ በኩል የብሔር ብሔረሰቦችን ድርሻ ወይም ኮታ ስንመለከት ከአስራ ሦስቱ እንዱስትሪዎች ዘጠኙን የሚያስተዳድሩት የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። በኮርፖሬሺኑ ዉስጥ ከፍተኛ ስልጣን ከተሰጣቸዉ የትግራይ ተወላጆች ዉስጥ እነ ብረጋዴር ጄኔራል ክንፈ ዳኘዉ የብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፖሬሺን ዋና ዳይረክተር ፤ ኮ/ል ተከስተ ኃ/ማሪያም በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮዳክሺን ግንባታ ሀላፊ ፤ ኮ/ል ፀጋሉ ኪሮስ በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ወታደራዊ ምርቶች ሀላፊ ፤ ኮ/ል ሙሉ ወ/ሰንበት በምክትል ዋና ዳይረክተር ማዕረግ የኮርፖሬት ፕሮጀክቶች አስተደዳደር ሀላፊ፤ሻምበል ካህሳይ ክሽን የምርመራና ልማት ዳይረክተርና ሻምበል ገ/ስላሴ ገ/ጊዮርጊስ የአቅም ግንባታና ስልጠና ማዕከል ዳይረክተርን የመሳሰሉ የህወሀት ታጋይ መኮንኖች ይገኙበታል።
ከትግራይ ዉጭ ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔሰቦች በብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን እንዱስትሪዎች ዉስጥ ከፍተኛ የሀላፊነት ደረጃ ባለዉ የአመራር ቦታ ላይ የመቀመጥ ዕድል ያገኙ ኢትዮጵያዉያን ቁጥር አራት ብቻ ነዉ። ይህ ጥናት የተጠናዉ ከ2004 እስከ 2005
ዓም ባለዉ የአንድ አመት ግዜ ዉስጥ ነዉ። በ2004 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ 90 ሚሊዮን አንደሚሆን የተገመተ ሲሆን ከዚህ ቁጥር ዉስጥ በትግራይ ክልል 5.4 ሚሊዮን ህዝብ በተቀሩት ስምንት ክልሎች ደጎሞ 84.6 ሚሊዮን ሀዝብ ይኖራል ተብሎ ተገምቷል። ይህ ጥናት በዋናነት የሚያመለክተዉ በዋና ዋና የሀላፊነት ቦታ የተቀመጡትን ግለሰቦችና ግለሰቦቹ የመጡበትን ብሔር ስለሆነ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺንን የሰዉ ኃይል ምደባና የደረጃ እድገትን ጠለቅ ብለን ስንመለከት አብዛኛዎቹ እንጂኔሮችና ቴክኒሻኖች የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ፤ የደረጃ እድገትን በተመለከተም ከሌሎች ሰራተኞች ጋር ሲነፃፃር በፍጥነት የደረጃ እድገት የሚያገኙት እነዚሁ የትግራይ ተወላጆች ናቸዉ። ይህ ደግሞ በአጋጣሚ የሆነ ነገር ሳይሆን ወያኔ በረሀ ዉስጥ እያለ አቅዶት ባለፉት ሃያ አመታት በስራ ላይ ያዋለዉ የረጂም ግዜ እቅድና ዝግጅት ዉጤት ነዉ። ለምሳሌ ወያኔ ትግራይ ዉስጥ ኤም አይ ቲ ወይም የመቀሌ ቴክኖሎጂ እንስቲቲዩት ብሎ የሚጠራዉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም ተቀብሎ የሚያስተምረዉ የትግራይ ተወላጆችን ሲሆን ከዚህ ተቋም የሚመረቁ እንጂኔሮችና ተክኒሺያኖች ናቸዉ በኢትዮጵያ ብረታ ብረት እንጂኔሪንግ ኮርፓሬሺን የሚሊታሪ ክንፍና በኢትዮቴሌኮም የስለላ ተቋሞች ዉስጥ ተመድበዉ ከፍተኛ የስለላ ስራ የሚሰሩት።

ethio-metal-coorporation-image-1 (1)ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝና አገር ዉስጥና በዉጭ አገር የሚገኙ ቡችሎቹ የኢትዮጵያን ተቃዋሚ ድርጅቶች በተለይ በዳያስፖራ ዉስጥ የሚገኘዉን ለእናት አገሩ ተቆርቋሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጅምላ “የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች” እያሉ ለአመታት ሲዘልፉን ኖረዋል። የፖለተካ ትግላችን አላማና ግብ ከጥላቻ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለዉ ቢሆንም – ለመሆኑ ይህንን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተና አንዱን አለቃ ሌላዉን ተላላኪ፤ አንዱን የሚሾም ሌላዉን የሚሽር፤ አንዱን አብልቶ የሚያጠግብ ሌላዉን የበይ ተመልካች የሚያደርግ፤ አንዱን የአገር መሪነት ቦታ ተረካቢ ሌላዉን ኮብልስቶን ድንጋይ ጠራቢ የሚያደርግ ስርዐት የሚወድ ማን አለ? ይህንን በንጹህ ዜጎች ደም እጁ የቆሸሰና ያደፈ ዘረኛ ስርአት ዉደዱ የሚለንስ ማነዉ? በምድርም በሰማይም የከሰሩ እነ ሚሚ ስብሀቱን የመሳሰሉ የፖለቲካ ሴሰኞች ሊነግሩን እንደሚፈልጉት ትግላችን የትግራይ ወንድሞቻችንንና እቶቻችንን በመጥላት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን የትግላችን ብቸኛ አላማ ከትግራይ ወንድሞቻችን ጋር ሊያጋጩን የሚሞክሩትን የህወሀት ወንጀለኞች አስወግደን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር ማድረግ ነዉ::ethio-metal-coorporation-image-2 (1)

የባህር ዳሩ ጊዮን ሆቴል ህወሀትንና ብአዴንን ዱላ ቀረሽ ፍጥጫ ዉስጥ መክተቱ ተሰማ

 

በደርግ ዘመነ መንግስት የአገር ሀብት የነበረዉና ባለፉት ሃያ አንድ አመታት የትግራይ ተወላጅ በሆነ ግለሰብ አላግባብ ተይዞ የነበረዉ የባህርዳሩ ጊዮን ሆቴል ባለቤትነት ለአማራ ክልል የመንግስት ቤቶች ኤጄንሲ እንዲዘዋወር መወሰኑ የህወሀትንና የብአዴንን ከፍተኛ ባለስልጣኖች ግጭት ዉስጥ እንዳስገባ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸዉ ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ለዝግጅት ክፍላችን በላኩልን ዜና ገለጹ። በ1983 ዓ.ም ወያኔ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር በመንግስት ይዞታ ስር የነበረዉን የባህርዳሩን ጊዮን ሆቴል ለመለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመደ ለሆነዉ ወልዱ ለሚባል ግለሰብ በ5000 ብር በኪራይ ስም መሸለሙ ይታወሳል። የአድዋ ተወላጅ የሆነዉ ወልዱ የሚባለዉ ግለሰብ ወያኔ የትጥቅ ትግል ያካሄድ በነበረባቸዉ 17 አመታት ባህርዳር ዉስጥ የህወሀት ሰላይ እንደነበረ የሚታወቅ ሲሆን መለስ ዜናዊ ያንን የመሰለ ዘመናዊ ሆቴል በ5000 ብር የሸለመዉ ለዚሁ የስለላ አገልግሎቱ እንደሆነ ብዙ የባህር ዳር ነዋሪዎች በግልጽ ይናገራሉ።
ባለፉት ሃያ አንድ አመታት ጊዮን ሆቴል ለወልዱና ለልጁ ለብስራት ወልዱ እጅግ በጣም ከፍተኛ ትርፍ ሲያስገኝ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን ይህ በሆነባቸዉ አመታት ሁሉ የባህርዳር ከተማ ህዝብ አንድ ኪዎስክ በ5 ሺ ብር እየተከራየ እንዴት ጊዮን ሆቴልን የሚያክል ትልቅና ዘመናዊ ሆቴል በ5 ሺ ብር ብቻ ይከራያል እያለ ተቃዉሞዉን ቢያሰማም የሚሰማዉ ጠፍቶ ሃያ አመታት አልፈዋል። ሆኖም በቅርቡ መለስ ዜናዊ ከሞተ በኋላ የፌደራል የኪራይ ቤቶች ድርጅት የአማራ ክልል መንግስት ሆቴሉን እንዲረከብ ለአማራ ክልል የመንግስት ቤቶች አስተዳደር ደብዲቤ በመጻፉ ጉዲዩ ከክልል አልፎ ገዢዉ ፓርቲ ጽ/ቤት መድረስ ችሏል። ሆቴሉን ለከልል መንግስት እንዲያስረክቡ ደብዲቤ የደረሳቸዉ ወሌደና ሌጁ ብስራት ጉዳዩን በቀጥታ ለበረከት ስምኦን፤ ለፌዳሩሽን ምክር ቤት ሰብሳቢው ካሳ ተክለብርሀንና ለአዲሱ ለገሰ የመለስ ዜናዊን ሞት ተክትል ሆቴሉን እንዱያስረክቡ መጠየቃቸውን በመናገራቸው፣ ባለስልጣኖቹ የክልሉ መንግስት የጻፈውን ደብዳቤ እንዱያነሳ ጠይቀዋል።
የክልሉ የመንግሰት ቤቶች ኤጀንሲ ጉዲዩ ከፍተኛ ዝርፊያ መሆኑን ገልጾ ዉሳኔዉን ለመለወጥ ፈቃደኛ አለመሆኑን ቢገልጽም የሆቴለ አስተዳዳሪ የሆነዉ ብስራት ወልዱ የክልሉን ባለስልጣናት በማስፈራራት እርምጃ እንደሚወስድ በመዛት ሆቴሉን ለማስረከብ ፈቃደኛ እንዳልሆነ ገልጿል። ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የዝግጅት ክፍላችን በስልክ ያናገረዉ አንድ የኪራይ ቤቶች ድርጅት ሰራተኛ የሆቴሉ አስተዳዳሪ ብስራት ወልዱ ሆቴሉን እንዲያስረክብ ደብዳቤ ሲጻፍለት “ዋጋህን ታገኛለህ” የሚል መልስ መስጠቱን ተናግሯል። የባህርዳር ከተማ ህዝብ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣኖች በአንድ ተራ የህወሀት አባል መደፈረቸዉን አስመልክቶ እያሾፈ ሲሆን እንደ ብዙ ታዛቢዎች እምነት የክልሉ መንግስት ከዚህ አይነቱ ህዝባዊ ትችት ነጻ መሆን የሚችለው ግለሰቡ ሆቴሉን እንዱያስረክቡ ሲያደርግና እንደማንኛውም ሰው ተጫርቶና ለጨረታዉ ተገቢውን ክፍያ ማስከፈል ሲችል ብቻ መሆኑ ታውቋል።

የትግራይ ህዝብ ስማ!!

(ርዕሰ አንቀጽ)

mekelle
ሰሞኑን በውዴታም ይሁን በግዴታ በመቀሌ እጅግ ከፍተኛ የሚባል ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ሲጨፍሩ፣ ሲዘሉ፣ ከበሮ እየመቱ የባህላቸውን ዘፈንና ውዝዋዜ ሲያወርዱ አይተናል። ምክንያቱ በግልጽ ባይነገርም ሲደበቅ የነበረው የህወሃት ሃብትና ንብረት ውጤት የሆኑ፣ በልዩ የመንግስት ድጋፍ የተከናወኑ ግዙፍ ተቋሞች በጎዳና ለህዝብ ሲቀርቡም ተስተውሏል። ልማቱ መልካም ነው። ደስ ይለናል። ምንም ተቃውሞ የለንም። ግን መልዕክት አለን።
ለማን?
ምሬትን፣ ጭቆናና መንገፍገፍ ሲበዛ በፍቃደኛነት በቦንብ ላይ እንደሚያስሮጥ ለሚያውቀው የትግራይ ህዝብ!! የትግራይ ህዝብ ስማ!!
ሰሞኑን ይፋ የሆነው የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም ሪፖርት የትግራይ ክልል በትምህርት፣ በኤሌክትሪክ፣ በመንገድ፣ በእርሻ፣ በደን፣ በኢንዱስትሪ፣ በጤና፣ ወዘተ ከሌሎች ክልሎች ሁሉ ርቃ መሄዷን ይፋ አድርጓል። በዚህም ደስ ይለናል። አይከፋንም። ከዚህ በላይ እንዲሆን እንመኛለን። ነገር ግን አንድ መልዕክት አለን።
ለማን?
አሁንም ለትግራይ ህዝብ!!
ሓውዜን የትግራይ ወጣቶች ለትግል ግልብጥ ብለው እንዲወጡ አደረገ። ሓውዜን የደረሰው የቦንብ ድብደባ ማንና እንዴት እንደተቀነባበር ብዙ የሚባልለት ቢሆንም የምሬት ጫፍ ሆኖ ህዝብን አሸፍቷል። ዛሬ መጨቆን ያንገፈግፋል ብለው ለትግል በተነሱና በተሰው ታጋዮች ደምና አጥንት ላይ የቆሙ ሌሎች ሓውዜኖች እንዲፈጠሩ አድርገዋል። እያደረጉም ነው።
ይህ በማን ስም እየሆነ ነው? በህወሃት አማካይነት በትግራይ ህዝብ ስም!!
ኦሮሚያ ልጆቿን በእስርና በጥይት እያጣች ነው። በጨለማ ቤት እየተሰቃዩ ያሉ የኦሮሞ ልጆች ግፍ ሰፍሮ ሞልቷል። አማራው አገር አልባ ሆኖ በየጎዳናው እየወደቀ ነው። እየተለዩ ከየክልሉ እየተባረሩ ነው። የመኖር ዋስትናቸውን ተከልክለው በሞትና በጣር መካከል ያሉ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ለቅሶ ሰማይ ደርሷል። ይህ ሁሉ አልበቃ ብሎ እስር ቤት የሚማቅቁና የሚሰቃዩ ሰውነታቸውም የሚተለተል አሉ። የተገደሉ አሉ። ይህንን የሚያደርገው ደህንነቱ የተቆጣጠረውና መሳሪያ ያነገተው ኃይል ነው። ይህ ኃይል ደግሞ ህወሃት ነው። ህወሃት ይህንን ሁሉ ግፍ የሚፈጽመው በትግራይ ህዝብ ስም ነው። እያመረተ ያለው ደግሞ ብዙ ሓውዜኖችን ነው። በደልና የበቀል ስሜት ላንድ ጎሳ ወይም ሕዝብ ብቻ የተሰጠ አይደለምና ሌሎችም ሊነሱ ይችላሉ። መቼና እንዴት? አይታወቅም። በሲዳማ፣ በሶማሌ፣ በአፋር፣ … ብዙ ችግርና ምሬት አለ።
በጋምቤላ ግፍ ነዶውን እየወዘወዘ ነው። በጋምቤላ በዘመናት ወደፊት የማናገኛው የደን ሃብት እየወደመ ነው። በጋምቤላ ሰላማዊ ህዝቦች ከቀያቸው እየተፈናቀሉ መሬታቸውን እየተነጠቁ ለውጪ “ባለሃብቶች” እንዲሁም ለትግራይ ተወላጆች እየተከፋፈለ ነው። በባሌ፣ በቦንጋ፣ በወለጋ፣ ድፍን ኦሮሚያና የደቡብ ክልል ደን እየተጨፈጨፈ ትግራይ በደን እየተሸፈነች ነው ብሎ መጨፈር ለትግራይ ህዝብ ኩራት አይሆነውም። ኢትዮጵያዊ ነው የሚባለው የትግራይ ህዝብ እሱ የሚጠላውና ልጆቹን የገበረለት ግፍ በሌሎች ወገኖቹ ላይ ሲፈጸም ዝም ማለቱ ለምንና ከምን የመነጨ እንደሆነ ለማወቅ የሚፈልጉ አሉና ጥያቄውን እናቀርባለን።
ስለመፈናቀል ስናወራ “የትግራይ ተወላጆች ተፈናቀሉ” ሲባልና “ተፈናቀልን” ብለው ቅሬታና አቤቱታ ሲያቀርቡ አንሰማም። ይልቁኑም የአማራን ለም መሬት ለትግራይ በመከለል በደል የሚፈጽመው ህወሃት የሚባለው በትግራይ ህዝብ ስም የተደራጀና በነጻ አውጪ ስም እስካሁን አገር የሚመራ ቡድን ነው። ይህ ሁሉ ሲደረግ የትግራይ ህዝብ ያውቃል። ቢያንስ ቢያንስ የሰው መሬት ወርረው የተቀመጡት አይክዱትም። ግን ይህ እስከመቼ ይቀጥላል? ፍርሃት አለን። ለምን? ይህ ሁሉ ሌላኛው የሓውዜን ክፍል ነዋ!!
ስለ ግብር ሲነሳ የትግራይ ተወላጆች በግብር ዕዳ፣ በባንክ እዳና እንደ ልብ ነጻ ሆኖ በመንቀሳቀስ ችግር ቅሬታ ሲያሰሙ አይደመጥም። በመላው አገሪቱ በኢንቨስትመንት ተሰማርተው በሰላም እየሰሩ ነው። ሌሎች ግን በብሔር ተለይተው መከራ ይደረስባቸዋል። ህወሃት በማንነታቸውና ባመለካከታቸው እየነጠለ ከጨዋታና ከኑሮ መስመር ያወጣቸዋል። የጭቃ ቤት፣ አርሰው የሚበሉበት ከብት፣ ዶሮና በግ ሃብት ተብሎ ይወረስባቸዋል። ይህ እውነት ለትግራይ ምሁራን የተሰወረ አይደለም። ይህም ሌላው ህወሃት በትግራይ ህዝብ ስም በሌሎች ዜጎች ላይ የሚፈጥረው የምሬት ሓውዜን ነው!!
ኮንትሮባንድና ህገወጥ ንግድ ሲነሳ የመጀመሪያው መስመር ላይ ሆነው አገሪቱን የሚያልቡት የቀድሞ ታጋዮችና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ነጋዴዎች ናቸው። ጤፍ ወደ ኤርትራ በማጋዝ፣ ባህር ዛፍና ቡና በማሻገር፣ የዱር እንስሳትን ቆዳና ቀንድ በመነገድ የተሰማሩት ይታወቃሉ። ብዙ እጅግ ብዙ ማለት ይቻላል። የምናነሳቸው ማሳያዎች ሁሉ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ የፖለቲካ፣ … ሓውዜኖች ናቸውና እዚህ ለጊዜው ላይ እናቁም!!
ሻዕቢያ ድንገት ወረራ አካሂዶ ድፍን ትግራይን ሲቀጠቅጥ፣ ህጻናትን በቦንብ ሲቆላ፣ አገሬ ብሎ የተነሳን ህዝብ በማያውቀው ወንጀል እየሰፈሩ ማሰቃየት ይቆም ዘንድ የትግራይ ህዝብ በቀጥታ ድምጹንና ተቃውሞውን በአግባቡ ማሳየት የሚገባው ወቅት ላይ እንደሚገኝ ይሰማናል፤ ደግሞም እናምናለን። ዛሬ “ውርሱን እንጠብቃለን” በማለት የሚጮህላቸው አቶ መለስ በወቅቱ ክህደት ሲፈጽሙ የደረሰው ዛሬ እየተነጠሉ የሚመቱትና መድረሻ ያጡ ወገኖች ናቸው። ዛሬም ቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ናቸው። በሰባና ሰማንያ ሚሊዮን ህዝብ ልብ ውስጥ የተፈጠሩት ሓውዜኖች ወደ ቁጣ ሲለወጡ አምስት አምስት ሆኖ መደራጀት፣ በስውር መታጠቅና በየሰፈሩ ያሉትን አስተባባሪዎች ስም ለቅሞ በመያዝ “ሳልቀደም ልቅደም” ብሎ መራወጥ አያዋጣም፤ ጊዜው ስለሚያልፍበት የትም አያደርስም። ሓውዜናዊ ህይወት የሚኖር ሕዝብ ከደረሰበት በላይ የሚያጣው ስለማይኖር እንኳን ስለማጣት ስለመኖርም አያስብም፡፡ በዚህ ከቀጠለ የቀን ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በየቦታው ራሱ ህወሃት የፈጠራቸው ሓውዜኖች መናደፍ መጀመራቸው አይቀርም።
“ህወሓትን እናስቀድም … ጠላቶቻችንን እናጥፋ” በሚል የማያቋርጥ ጥላቻ መቀጠል ተጨማሪ ሓውዜኖችን ከመፍጠር በስተቀር “ጠላትን” ማጥፋት የማይቻል እንደሆነ ከዚህ በፊት በሕዝብ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የወሰዱ ተሞክሮ ማስረጃ ነው፡፡ በበረሃ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ሥልጣን ይዞ “ጠላትን እናጥፋ”፤ አገር እየመሩ “ጠላትን እናጥፋ”፤ ኢኮኖሚውን ተቆጣጥሮ “ጠላትን እናጥፋ” … 40ዓመት ሙሉ በ“ጠላትን እናጥፋ” መርህ የሚጓዘው ህወሃት “ጉድጓድ የሚምስ ራሱ ይወድቅበታል” የተባለው የተቀደሰ አባባል ሲፈጸም እንዳየነው ከ70 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ለማጥፋት የሚመኘው ህወሃት የራሱ መጥፊያ የሆኑ በርካታ ሓውዜኖችን ፈጥሯል፡፡
“የ100 ዓመት የቤት ስራ ሰጥተናቸዋል” በሚል በየድረገጹ የሚለጠፉ ተራ ድንፋታና ትዕቢት የሚፈጠሩትን ሓውዜኖች ከማብዛት ውጪ ትርፍ የላቸውምና ወደ ደጉ መንገድ መመለስና ሰብዓዊነትን በማስቀደም፤ ተደጋግፎ መኖርን ማጎልበት ይሻላል ለማለት እንወዳለን። ተሳስበውና ተረዳድተው የሚገነቡት የትም ሆነ የት የአገር ነውና ሁሉም ይኮራበታል፤ ይጠብቀዋል። ተጠቃሚ ይሆንበታል። የሚያምርብንም ይህ ነው። ህወሃት አልሰማም ብሏል። የትግራይ ህዝብ ግን ስማ!! ይህ ሁሉ የሚደረገው በስምህ ነው!!

የኦህዴድ ምርጫ ውጤት ተራዘመ

ህወሃት አባረረ፣ ብአዴንና ደኢህዴን ባሉበት ቀጠሉ

tplf meeting
ድሮ “ላዩ ካኪ ውስጡ ውስኪ” እየተባለ በኢሰፓ አባላት ዩኒፎርም ይቀለድ ነበር። ዛሬ ደግሞ ኢህአዴግ ተመሳሳይ ልብስ አልብሶ በየክልሉ የሰየማቸውን ፓርቲዎችና አመራሮቻቸውን የተመለከቱ “ስቱኮ” እያሉ እንደሚቀልዱባቸው ተሰምቷል።
“ስቱኮ” ግልብጥና ግጭት የበዛበት መኪና ተቀጥቅጦ አልስተካከል ሲል፣ የተገጣጠበና አልመሳሰል ያለ ግድግዳ “በግድ” ለማመሳሰል የሚያገለግል ቶሎ የሚፈረካከስ ጭቃ መሰል የቀለም አይነት ማጣበቂያ ነው።
“ኮሚኒስቶች በችግርና በቅራኔ ውስጥ ሆነው በግድ ለመመሳሰል አንድ ዓይነት መለያ መልበስ ይወዳሉ። ኢህአዴግም በተመሳሳይ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ሳለ፣ ለተመልካችና ለካሜራ ተመሳሳይ ልብስ ለብሶ በግድ አንድ ነኝ ሲል ማየቱ ብዙም የሚገርም አይደለም” የሚለው አስተያየት በስፋት እየተሰጠ ነው። “በግድ አንድ” ሆነው በየክልሉ ስብሰባ የሚያካሂዱት እህት ፓርቲዎች የለበሱትን መለያ የሚያመርተው ደግሞ የህወሃት የንግድ ድርጅት አልሜዳ ጨርቃጨርቅ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ባህር ዳር ላይ ለሚያካሂደው ጉባኤ በዝግጅት ላይ ያሉት “እህት” ፓርቲዎች በየክልላቸው በስብሰባና በምርጫ ተጠምደው ሰንብተዋል። ውሉ ያልታወቀውና ምስጢር የተደረገው የኦህዴድ ጉባኤ የምርጫውን ውጤት ማጠናቀቅ አልቻለም። ህወሃት በመተካካት ስም ነባሮቹን አራት አመራሮች ሲያሰናብት፣ አቶ በረከትና አዲሱ ለገሰ የኢህአዴግ የመተካካቱ ስልታዊ በትር ሳይነካቸው ማለፉ ተደምጧል። ደኢህዴን በነበረበት እንደሚቀጥል ይፋ ሆኗል።
ኦህዴድን ለመምራትና ሰባት አመራር በሚሰየምበት የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ለመሆን አባ ዱላ ገመዳ፣ ግርማ ብሩ፣ ድሪባ ኩማ፣ ኩማ ደመቅሳ፣ አለማየሁ አቶምሳ፣ አስቴር ማሞና ደግፌ ቡላ ከተጠቆሙት መካከል ይገኙበታል። የህወሃት የንግድ ተቋምና አንደበት የሆነው ሬዲዮ ፋና “የተጠቆሙትን አመራሮች ለማሳወቅ የድምጽ ቆጠራው ጊዜ ስለሚወስድ ለነገ ተላልፏል” የሚል ዘገባ አሰራጭቷል።
ፋና ይህን ይበል እንጂ የጎልጉል ምንጮች ከስፍራው እንዳሉት የኦህዴድ ስብሰባ ከፍተኛ ንትርክ የተስተናገደበት ሆኗል። ምንጮቹ እንዳሉት የበታች አመራሮች፣ የቀበሌና ወረዳ የስር መዋቅሮች በድፍረት የድርጅቱን አመራሮች ነቅፈዋል። በራሳቸው ውሳኔና መንገድ የማይመሩበት ምክንያት መነሻና ይህ አካሄድ መቼ ሊያቆም እንደሚችል ሊገባቸው እንዳልቻለ የተናገሩ አሉ።
“ውርስና ቅርስ” እየተባሉ የሚወደሱት አቶ መለስ በህይወት እያሉ ህወሃት ድምጽ ነፍጎ ሲያባርራቸው “መለስ ይሁን” በማለት የተሰጣቸውን የህወሃት ሊቀመንበርነት ስልጣን ላለመቀበል ያፈገፈጉት አቶ አርከበ እቁባይ በመተካከት ስም ከህወሓት መሰናበታቸው ይፋ ሆኗል። ዊኪሊክስ ይፋ ባደረገው መረጃ ህወሃትን እንዲመሩ ተመርጠው የነበሩት አቶ አርከበ አዲስ አበባ ፎቶግራፋቸው ከተለጠፈበት ጊዜ ጀምሮ “የድስትና ማማሰያ” ምሳሌ በመሆን ጥግ ተደርገው ከተረሱ በኋላ በመጨረሻ አማካሪ ተብለው ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ተዛውረው ነበር።
አቶ በረከትን ተከትሎ አቶ ስዩም መስፍን፣ አቶ ዘርአይ አስገዶምና አቶ ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ህወሃትን በይፋ መሰናበታቸው ታውቋል። ፋና “በክብር ከማዕከላዊ ኮሚቴ ተሰናብተዋል” ሲል አሞካሽቶ መርዶ አብስሯል። ፋና በነካ እጁ የዋናውን የሚዲያ ፊት አውራሪ አቶ በረከትን ዜና ይፋ አደርጓል።
መለስ ያዘጋጁት “የማጽጃ በትር” የሚባለው መተካካት ብአዴን ውስጥ ተግባራዊ አልሆነም። ታማኞቹ የወ/ሮ አዜብ መስፍን ቡድን የሆኑት አቶ በረከት፣ ሰሞኑን በተዘጋጀ ዶክመንታሪ ፊልም በትግርኛ ተረት ሲያወርዱ የታዩት አቶ አዲሱ ለገሰ፣ አቶ ጉዱ ካሳና ፓርላማ ውስጥ የስነስርዓት ጥያቄ ሲቀርብላቸው “ታዝዤ ነው፣ ከታዘዝኩት ውጪ የማደርገው የለም” በማለታቸው የሚታወቁት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሽታዬ ምናለ በአዲሱ ምርጫ ተካተዋል።
ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደኢህዴንን በሊቀመንበርነት እንዲመሩ የተመረጡ ሲሆን አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ምክትል ሆነው እንዲቀጥሉ ተሰይመዋል። በደቡብ ክልል ሃዋሳ ከተማ ላለፉት ሶስት ቀናት የሞባይል ስልክ ማነጋገር አስቸጋሪ እንደነበር የጎልጉል መረጃ አቀባይ ከስፍራው አስታውቋል። አቶ ሃይለማርያም የአገሪቱ መሪ ከሆኑ በኋላ ሃዋሳ ሲገኙ ለደህንነት በሚል የስልክ መስመሮች ላይ ማዕቀብ መደረጉን ተገልጋዮች በቅሬታ ሲገልጹ ተሰምቷል።
ከሁሉም ጉባኤዎች ጎልቶ የወጣው የህወሃት ጉባኤ ሲሆን የትግራይ ክልል ሃብትና እድገት በታላቅ ትዕይንት ከጉባኤው በፊት ለህዝብ እንዲተላለፍ መደረጉ የተለያየ አስተያየት እየተሰነዘረበት ነው። መቀሌ በትዕይንት አቅራቢ ህዝብ ተጨናንቃ ሲጨፈርና ከበሮ ሲደበደብ ያሳየው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እንዳለው ትዕይንቱ የተዘጋጀው መለስን ለመዘከር ነው። ዜናው በተመሳሳይ ሌሎች ክልሎች የደረሱበትን የልማትና የዕድገት ደረጃ የሚያሳይ ትዕይንት እንመራዋለን ለሚሉት ህዝብ በይፋ ያላሳዩበትን ምክንያት ግን አልገለጸም።
ጋዜጠኛ ተመስገን “ሽክ” ብሎ ፊቱ ላይ ርካታ እየተነበበት ያነጋገረው ጋዜጠኛ መቀሌ ባየው ነገር መገረሙን ደጋግሞ አመልክቷል። በተሽከርካሪ ላይ በተዘጋጁ ሞዴል ማቀናበሪያና ምስሎች ትግራይ የደረሰችበትን ደረጃ የተመለከቱ “ልማት ያስደስታል። ከሰባ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚያለቅስበት ልማት መሆኑንን ስናስብ ያሳዝነናል” ሲሉ ተደምጠዋል።
አርቲስት መሐሙድ አህመድ “ትግራይ ልትሰምጥ ነው የሚባለው ውሸት ነው” በማለት የተናገረውን ያስታወሱ አስተያየት ሰጪ፣ “ብሶት ሁሉም ቦታ፣ በየትኛውም ጊዜና ወቅት የሚከፋቸውንና በቃን የሚሉ ዜጎችን ይፈጥራል። የትግራይ ህዝብም ብሶት ምን ያህል አስከፊ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ ትግራይ ብቻዋን ስትለማና ስታድግ ሌላው እየተረገጠ መሆኑንን በመገንዘብ ከመጨፈር ይልቅ በማስተዋል በስማቸው የሚፈጸመውን ግፍ እንዲቆም የመጠየቅ ሃላፊነት አለባቸው” በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Wednesday, March 20, 2013

ከህወሃት አቶ ስዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዩ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣ ከፓርቲ የአመራር ቦታቸው እንዲገለሉ ተደርገዋል፡፡


ኢህአዴግ ያወጣው የአመራር መተካካት ከመፈክር ባለፈ እየተተገበረ አለመሆኑን ለግንባሩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
የግንባሩ ከፍተኛ አመራሮች ከ17 ዓመታት በላይ በጫካ ትግል ላይ ዕድሜያቸውን ያሳለፉ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ
በአሁኑ ወቅት በተለይ ከዕድሜና ሕመም ጋር ተያይዞ ብዙዎቹ የያዙትን ከፍተኛ ኃላፊነት መወጣት የማይችሉበት ደረጃ ላይ
እየደረሱ በመሆናቸው በሌላ አመራር የመተካታቸው ጉዳይ ታምኖበት የአፈጻጸም ፕሮግራም ወጥቶለት እንደነበር
ይታወሳል፡፡
በዚሁ ፕሮግራም መሰረት እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ነባሩ አመራር በአዲስ ኃይል እንዲተካ በሟቹ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ የተነደፈ ዕቅድ ቢኖርም በአሁን ወቅት አፈጻጸሙ ከመፈክር በዘለለ እየተተገበረ አለመሆኑ ታውቋል፡፡ለዚህ ዋነኛው ምክንያት ከፍተኛ አመራሩ ስልጣን ለማስረከብ ፈቃደኛ ካለመሆኑ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ከመስከረም 5 እሰከ 7/2003 ዓ.ም በአዳማ በአባገዳ አዳራሽ የተካሄደውን የግንባሩን 8ኛ ጉባዔ ተከትሎ በዚሁ
የመተካካት መርህ መሰረት ከህወሃት አቶ ስዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዩ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣ከብአዴን አቶ
አዲሱ ለገሰ ፣አቶ ተፈራ ዋልዋ፣አቶ ታደሰ ካሳ ከፓርቲ የአመራር ቦታቸው እንዲገለሉ ተደርገዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በስራ ላይ ያሉት እነአቶ አባይ ወልዱ፣ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል፣አቶ ጸጋዩ በርሄ፣አቶ በረከት
ስምኦን፣የመሳሰሉ ነባር አባላት ስልጣናቸውን ለተተኪዎች ከማስተላለፍ ይልቅ ማጠናከር ላይ ተደምጠው መታየታቸው
ዕቅዱ መክሸፉን ማሳይ ጥሩ ምልክት ነው ብለዋል ምንጮች።
የአቶ መለስን ራዕይ አስፈጽማለሁ በሚል ጠዋት ማታ የሚምሉት በስልጣን ላይ ያሉ ወገኖች ፣ የመተካካቱን ጉዳይ
ከወሬና ከወረቀት በዘለለ መተግበር አለመቻላቸው ብዙዎችን የድርጅቱን አባላት ጭምር እያነጋገረ ነው።
ከሁለት ዓመት በፊት በአዳማ የተካሄደው 8ኛ የኢህአዴግ ጉባዔ መተካካትን በተመለከተ ሲገልጽ፡ “በጉባኤያችን ማግስት በድርጅታችን የአመራር መተካካት ስርአትን ለመቅረፅና በተግባር ላይ ለማዋል ሰፋ ያለ
እንቅስቃሴ ተካሂዷል፡፡ ድርጅታችን አላማውን ከዳር ለማድረስ ትግሉ ከሚያልፍባቸው መድረኮች ጋር ራሱን እያጣጣመና
የመምራት ብቃቱን እያዳበረ መጓዝ እንዳለበት በማመን ቀጣይ የአመራር ትውልድ የመፍጠር ስራው በስርአት እንዲመራ
ጥረት ተደርጓል፡፡ በዚህ መሰረት ነባሩ የአመራር ሃይል በስራ ብዛትና በእድሜ መግፋት መስራት የማይችልበት ደረጃ
ላይ ከመድረሱ በፊት ደረጃ በደረጃ በአዳዲስ የአመራር ሃይሎች እየተተካ እንዲሄድ ማድረግ የሚያስችል አቅጣጫ
ሊቀየስ ችሏል፡፡ በዚህ አቅጣጫ መሰረት ነባሩ አመራር ከፊት መስመር ለቆ በአዲሱ እንዲተካና በድርጅት አመራርነት
ግን አስተዋፅኦውን እያበረከተ የሚቀጥልበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተወስኖ ተግባራዊ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በዚህ
አቅጣጫ መሰረት ነባሩ አመራር በሶስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በሚቀጥሉት አምስት አመታት ከፊት መስመር የሚለቅና
ሚናውን እየተጫወተ የሚቀጥልበት ሁኔታ ተመቻችቷል፡፡ ” ብሎአል።
ይህ መግለጫ አያይዞም “በተመሳሳይ መልኩ የአብዮታዊ ዴሞከራሲያዊ አላማዎቻችንን ቀጣይ ተፈፃሚነት ለማረጋገጥ የአመራር መተካካት ስርአታችን መካከለኛ አመራሩንም የሚያካትት እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችል አቅጣጫ አስቀምጠን
ተንቀሳቅሰናል፡፡ከዚህ አኳያ ቀደም ሲል የተጀመረውን ሰፊ የመካከለኛ አመራር ሃይል የመፍጠርና በየስራው መድቦ
በማጠናከር ሰፊ የመካከለኛ አመራር ሃይል እንዲኖረን ተደርጓል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በሁሉም እርከኖች
የመተካካት ስራው አፈፃፀም በየደረጃው ያሉ የአመራር አባላት ከአንድ እርከን ወደ ቀጣዩ እርከን ወይም ወደ ትምህርት
እድል የሚሸጋገሩበት አሰራር በዝርዝር ተጠንቶ እንዲፀድቅና ይህም መተካካቱ የሚፈፀምበት ተጨማሪ አቅጣጫ እንዲሆን
ተወስኗል፡፡ በአጠቃላይ ከመተካካት አኳያ የተከተልነው አቅጣጫ በአንድ በኩል የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሃይላችንና
የስርአቱን ተጠናክሮ መቀጠል የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ህዝቡ ከመተካካት አኳያ ያነሳቸው ለነበሩ ጥያቄዎች
ትክክለኛ ምላሽ የሰጠ እንደሆነ በተግባር ከተገኘው ግብረ መልስ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ” ብሎአል።
በአሁኑ ወቅት አንዳንድ ነባር፣ ከፍተኛና መካከለኛ አመራር ላይ የሚገኙ ሰዎች ከትግል በሁዋላ ተምረን ብቃታችንን አሳድገን ሕዝባችንን ለማገልገል በተዘጋጀንበት ሰዓት መተካካት በሚል መገፍተራችን ተገቢ አይደለም በሚል በግልጽ
ተቃውሞአቸውን እየገለጹ ነው። አመራሮቹ በሙስና ያፈሩትን ሀብትና ንብረት ስልጣን ከለቀቅን እናጣዋለን ብለው ይሰጋሉ።
የፊታችን ቅዳሜ በባህርዳር ከተማ በሚጀምረው የግንባሩ 9ኛ ጉባዔ ላይ ከመተካካት አኳያ ብዙም የሚጠበቅ አዲስ
ነገር እንደማይኖር ይታመናል፡፡
ደኢህዴን ዛሬ ባካሄደው ጉባኤ እንደተጠበቀው አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ደግሞ ም/ል ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል። በሌሎችም ድርጅቶችም ተመሳሳይ ምርጫዎች ሲካሄዱ ውሎአል።

አገሪቱ የተጠመደችባቸው ውስብስብ ችግሮች!

ስለኢትዮጵያ በአጠቃላይ ምን ያልተባለ፤ያልተጻፈ አለ? ምን አዲስ ነገር ሊጻፍ ይችላል? ከሚሆሉ ነገሮች በስተቀር፤ ስለ አገራችን ያልተጻፈ ጉዳይ የለም። ሁሉም በየፊናው የተቻለውን ብሏል፤ጽፏል። አዲሱ፤ይህ መዘዘኛ ስርአት በየቀኑ እየፈለፈለ የሚያወጣቸው ፤የተደመሩና የተከማቹ፤ጊዜያቸውን ጠብቀው የሚፈነዱ የፖለቲካ ፈንጂውች እንጂ ሁሉም ተብሏል። አንድ ጉዳይ ግን እወነት ነው፤የሚጻፉ የተባሉ ሁሉ የተመሳሰሉ ቢሆኑም የቆሙበትንና የመፍትሔ ፍለጋ ላይ በአጽንኦም ተግባራዊነቱ ላይ ብዙ ፈታኝ ምእራፎች ተደቅነው ይታያሉ።
የኢትዮጵያ ችግር አንድ ሁለት ተብሎ የሚዘለቅ አይደለም። ለዘመናት በተለያዩ ስርአቶች የተፍጠሩ፤የተከማቹና ውስብስብ ለመፍትሄል አስቸጋሪ የሆኑ ናቸው።
ከዚህ በታች በጥቅሉ የተቀመጡ አሳቦች አዲስ ሳይሆኑ የነበሩ ናዘው። ለምን መጥቀስ አስፈለገ ቢባል፤ የጉዳዮቹን ፈታኝነትና የሚያመለክቱትን አደጋ አጢኖ ግንዛባ ለመውሰድ፤ ብሎም መፍትሄ ለማፈላለግ ቢረዳ ተብሎ ነው። የተዘረዘሩት ባመዛኙ ስርአቱ የፈጠራቸው፤ያገነናቸው ቢሆኑም፤ በቅድሚያ ስርአቱ፤ ያለፉት ስርአቶች፤አጎራባች አገሮች፤አለማቀፍ ሁኔታዎችና፤ ሳይጠቀስም መታለፍ የማይችሉት በጅምላ በተቃዋሚነት የተሰለፉ ባገርም፤በውጭም፤በሰላምም፤ባመጽም የሚታገሉ የተሰባሰበውና የተበታተነው ሐይሎች ጭምር ናቸው።
ብዙ የማያናቁሩም ባይሆኑ፤ በየፈርጃቸው መጠቃልለ ያለባቸውም ቢመስልም፤ ለመቃኘት ያክል አሉ የሚባሉ ፈታኝ ምስቅልቅሎቻችን ምን ይመስላሉ።

1. ዘረኝነትና መዘዙ፤

በአይነታቸው አስከፊ ከተባሉት በደቡብ አፍሪካና በሌሎች አካባቢ ከታዩት ባልተናነሰ፤እንዲያውም አገር በቀል በመሆኑ የከፋ ያንድ አናሳ ዘር የበላይነትና ጉዳዮችን በራሱ የስልጣን ጥምና ጥቅም ዙሪያ እያሽከረከረ በአሁኑ ወቅት ፈታኝ ችግሮችን ደቅኗል። ያለው እንዳለ ሆኖ የሚያመጣውና፤ እያመጣ ያለው መዘዝ በቀላሉ ለመወጣት የሚቻል አይደለም። ስር ሰዶ፤ፍሬ አፍረቶ ውጤቱ በሕዝቦች መካከል አለመተማማን፤መቃቃር፤ መጋጨት፤መፈናቀልን ፍጠሮ ጉዳዩ አሳሳቢ ሂኔታ ላይ ደርሳል። ዘለቄታውስ ምን ይሆን ብሎ መጠየቅ ተገቢ ቢሆንም፤ ማንም መገመት እንደሚችለው እትዮጵያ እንደአገር ልትቀጥል የምትችልበትን መሰርት ያናጋና አደጋ የደቀነ አብይ ችግር ሆኗል። በነጻንተ ከሚገኝ አንድንት ይልቅ የጠመንጃ ሐይል ፊት ካሰከተለው የተለየ ውጤት የለውም። ሌሎቹ ያገር ችግሮች ይህን ለበለጠ ጥፋት ይመግቡታል እንጂ አይቀርፉትም።

2. የመልካም አስተዳዳር እጦት፤

ያለው ስርአት ሁሉንም የፖለቲካ፤ የኢኮኖሚ፤የማህበረሰብና በሐይማኖት ሳይቀር አጠቃላል የአስተዳደር እርከኑንና አስከ ቤተሰብ ድረስ ዘልቆ በማፈን ህዝም እንዳይናገር፤እንዳይጽፍ፤ እዳይሰበሰብ፤ በነጻነት እናዳያመልክ ጠፍሮ ቀፍድዶ አደንዝዞ በገዛ አገሩ ባይተዋር የበዬ ተመልካች አድርጎት ለመዝለቁ የሚያጠያይቅ አይደለም። አገሪቱ በተከታታይ የሶስት ስርአቶች የንጉሥ፤ያምባገንንና የዘረኛ ስርአት ሰለባ ሆና ሕዝብ መከራውን ሲጋት፤ አገር ስትፍርስአ፤ አንድነት ሲሸረሸር፤ ጥፋት ሲመርት ለማየት በቅተናል።

3. ድህነት፤

ዛሬ አትዮጵያ ብዙዎች የሚራቡባት፤ ሉሮ ያሸቆለቆበባት፤ ድህነት አገርንና ህዝብን የአለም ጭራ ያደረገበት ደረጃ ላይ ደርሳለች። በአንዳሩም ጥቂት ባስተዳደር እርከኑ ላይ የተንጠላጠሉ አናሳውና አጋፋሪዎቹ ሀብት አካብተው ትላንት የመጡበትን ብቻ ሳይሆን ነገ የሚሄዱበትን እጣ ፍንታቸውን ለማየት የተሳናቸው አዲስ የበላታና ቡድን መፈጠሩ ነው። አብረን ሠርተን አብረን እንጠቀም ሳይሆን ሊሠራ የሚችለውን እጅ የሚያስር፤ አቅም ያለውን የሚያመክን የስግብግቡችን ጥርቅምን ፈጥራል። ድህነት የችግሮች ሁሉ መሰረት ነው። የህዝብ ድህነት ሲንር ዝም ከማለት ባሸገር አመጽን፤ ምንም ማንም ሌያግደው የማይችለውን ማእበል ይወልዳል። በመሥራት ማደግ መበልጽግ ሲቻል በዝርፊያ ድሀ፤የድሀ ድሀ
ያደረጉት ተጠያቂዎች ናቸው። ያገሪቱን ሀብት የተፈጥሮ ለም መሬተና ማእድናቱን ባልባሌ አስተዛዛቢ፤ሚዛን በጎደለው አስተሳሰብ ለባእድ አሳልፎ መስጠት ወንጀል፤ ያገር ክህደት የከፋ ወንጀል ነው።

4. ዝረፊያ - ኪራይ ሰብሳቢ ስርአት(ኮረፐሺን)፤

ምንጩ ከደፈረስ የጠራ ውሀ የለም። በአገሪቱ ዝርፊያ አይን ያወጣ ሙሰኝነት፤ ጥቅምን ማግበስብስ ፤ ያገሪቱ ሀብት በተለያየ መልኩ በሚታይና በማይታይ ስልት ወደ ውጭ እየጎረፈ ለመሆኑ፤ ከድሀ አፍ እየተነጠቀ ለመንጎዱ ብዙ ዋቢዎች በይፋ እየቀረቡ ይገኛሉ። ሕዝብ ይህን አያውቅም አይሰማም አረዳም፤ የመስሚያ የመረጃ አውታሮች ሁሉ ታፍነው ህዝብ የራሱ ጉዳይ ባይተዋር ሆኗል። በቀላሉ አደንዝዘውታል። ኪራይ ሰብሳቢነት ሌላ ትርጉም አያሻውም፤ ስርአቱን በማፈኛነት በመጠቀም መበልጸግ ብቻ ነው። በቀላሉ አይን ያወጣ እፍረት የጣ ዝርፊያ። የአገሪቱ ኢኮኖሚ የሚንቀሳቀሰው ባንጋፋ በስርአቱ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችና በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች መሆኑ የሚያሳዝንና የሚያሳፍር ተግባር ነው። በሰርአቱ ስር የተሰገሰጉ፤ጊዜ የሚገልጣቸው የማይመስላቸው ከተጠያቂነት ማምልጥ አይችሉም። በንጽህና መበልጸግ አለ፤ በዝርፊያ ግን በማንናቸውም መልኩ ያስጠይቃል። ከሁሉም የበለጠ ሓጢአት ነው። እግዚአብሔር ድሃ ሲያለቅስ አይወድም። ስላላመኑም ከቅጣት ማምለጥ የለም።

5. የሀይማኖት ነጻነት መጥፋት፤

አደጋውች በየፈርጁ ተኮልኩለዋል። የተደማመሩ ቀውሶች መዘዛቸው የከፋ ነው። ጳጳስ ፈንቅሉ የእምነት አውታሩን ከመቆጣጠር፤ የእምነትን ህገደንብ ለውጦ ሌላ እምንት ፍጥሮ፤ባማኙ ላይ መጫን፤ ለስልጣን፤ ለጥቅም ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት ነው። ገዳመት ተገለበጡ፤ ንጹህ አባቶቻችን ተዋከቡ፤አለቀሱ፤ተሰደዱ፤ለመከራ ተዳረጉ። በእምነት ጣልቃ ገብነት መዘዙ፤ ይህ ተፈጥሮ ያመጣችው ነው ተባለም አልተባለ፤ከላይ የመጣ መአት ሊፈስ ይችልል። ለተረዳውም የሆነውን አይተናል። በሌላ መልኩ፤ ተስማምቶ ተከባብሮ ባንድነት የኖረውን ሕዝም ፈተና ውስጥ ከቶታል። ከግፊትም ብዛት ሰላማዊውን ሕዝም ወደ አላስፈላጊ ጎዳና ይመራዋል፤ አመጽም ይባል ሽብር ይቀፈቅፋል። በዚህም ሆነ በዚያ እሳት ይጭራል፤ እልቂት ይጋብዛል። ጠመንጃም ሊየግደው የማይችል የሕዝብ ማእበልን ይወልዳል።

6. አካባቢ አጎራባችና ተዛማችች፤

ለችግሮቻችን መፍትሄ ሳይሆን እሳቱን ጭድ የሚመግቡ ሀይሎች ብዙ ናቸው። ኤርትራረ የሰበሰበቻቸው በአብዛኛው አገርን አንድነት የሚያናጉ ሀይሎች ከዚሁ ይመደባሉ። የተዳፈነ እሳት ይምስል እንጂ ቀውስ ሲመጣ እነዚህ ሀይሎች በአራቱም ማእዘናት እሳት የሚያነዱ የተደቀኑ አደጋዎች ናቸው። ኤርትረም ለኤትዮጵያ ሳይሆን ለረሷ ደህነት፤ በከፊልም የቂም መወጫ መንገዷ እንደሆነም መዘንጋት የለበትም። ከውጭ የሚርገበገቡ ሽብርተኝነትን የሚቀሰቅሱና የሚመግቡ ሂደቶችም ሌላዎቹ ችግሮች ናቸው።
የግድቡ ውጥንቅጥም አንድ እራሱን የቻለ ፈተና ነው:፡ አባይ መገደቡን፤አገር መልማቷን፤ ሕዝብ መበልጸጉን የሚጠላ ኢትዮጵያዊ የለም። ጥያቄው ልማት ከማን እጅ እንዲትና ለማ የሚሉት ናቸው። ያገሪቱን የአመት በጀት በሚያክል ንዋይ፤ ግዝፈቱ ለፍጻሜው አደጋ የሚጋብዝ ትልም፤ ከአካባቢውና አጎራባች አገሮች ጋር ለዘለቄታው የሚያፋርስ፤ ጦርነትን የሚጋብዝ የልማት ትልም ለሁሉም ፈታኝ ነው። ይህ አገርን የመውደድና የመጥላት ጉዳይ አይደለም ያገር የዘላቂ ደህንነት እነጂ።

7. የምእራቡ ትጽእኖ፤

ምስራቡን በእጅጉ ታዝበነዋል። ለነገሩ ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ የሆነ ነገር። የሕዝቡን ጥቅም መብትና ነጻነት፤ ያገሪቱን ደህንነት ወደጎን በመተው ከሟቹ ጋርና አሁንም አንድ በመሆን፤ከመፍትሄ ይልቅ ለሕዝብና ለአገር ስቃይ መራዘም አስተዋጽኦ መሆኑ አሌ አይባልም። ይባስ ብሎ በበለጠ ሊያስደንግጣቸው በሚችል ሁኔታ አሁን የሚታየው የሐይማኖት ማእበል፤ የበለጠ የሚያሰጋቸው፤ ስርአቱን ይበል የሚሉበትን ሁኔታነ የሚጋብዝ ለው። ምእራቡ ከፊቱ የበለጠ ምእራብ ሆነ
ማለት ይቀላል። ዲሞክራሲና ለሕዝብ መብትም መቆርቆር ካባ ልምስ እንጂ ጥቅም ቅዲሚያን ይዛ ነጉዳለች። ዘመኑም የከፋ ነው!!!!

8. የተቃዋሚው አካሄድ፤

እንግዲህ አልቀሬ! ከየትኛው ቡድን! እንበላ። ከችግሩ ወይስ ከመፍተትሔው? ስርአቱ-በአመዛኙ፤ሊሎችም ተጠያቂ ቢሆንም፤ ተቃዋሚው መፍትሔ ለመሆን በሚያደርገው ጥረት ለችግሮች እይተኛ አስተዋጽኦ መሆኑ ሳይወጠቀስ ሊታለፍ አይገባም። የተቃዋሚው ችግር አንድና አንድ ብቻ ነው። መሰባሰብ በአላማና በመርህ ባንድ ላይ አለመሆን!!!! ሌላ ላይደለም፤ጂኦግራፊም አቅምም ሌላም ሌላም ቢጠቀስ፤ ሕዝብን የሚአክል ሃይል፤ አገርን የሚያክ ጉዳይ ይዞ መዘናጋት ድክመት ብቻ ሳይሆን አተጠያቂነት ውስጥ መመደቡ አይቀሬ ነው።
ታዲያ፤ኢትየጵያ ይህን ሁሉ፤ ከዚህም በዘተረፈ ያልተጠቀሱ የዘማናት ፈተናዎችን ቀፍቅፋ ታቅፋለች። ተሸፋፍኖ መተኛት ችግሮችን አያጠፋም፤ ያባብሳል እንጂ። እስካሁን በእያንዳንዱ አእምሮ ውስጥ መፍትሔ የሚል ደወል መቃጨሉ አይቀርም።
ምፍትሄው በቅድሚያ ካለው አስተዳደር፤ ከምእራቡና ከሌሎች አይገኝም። መፍትሔው ያለው ከሕዝቡና ፋና እያበሩ፤ ፈር እየቀደዱ አቅጣጫን በሚሰጡት፤በሚጠቁሙ ልጆቹ እጅ ነው።
ገና በጥዋቱ፤ በደርግ ጊዜ ማለት ነው፤ ገበሬው ከገጠር ዱላውን የሽቅብ እየዶለ ሆ!ሆ!ሆ! እያለ አደባባዩን በሞላበት ወቅት፤ አንድ የውጪ ዜጋ "ይህ ሁሉ ዱላ ወደጠመንጃ ሳይለወጥ እግራችሁን አውጡ" ብሎ በአገር ጋዜጣ ጽፎ ነበር፤ ወገኖቹን ማለቱ ነው። ሐቁ ይኸው ነው፤ የያዘን አባዜ ቀላል አይደለምና ምሳሌው ሁሉን ይናገራል።
አገሪቱ ድህንተ የለባትም፤ሁኔታዎች አደኸይዋት እንጂ። የሰው-በያይነቱ፤የተፈጥሮ ሓብት ባለጸጋ ናት። ይህ ሆኖ ሳለ፤ ለዚህ ሁሉ ቀዳሚ መፍትሔ የሚሆነው መልከም አስተዳደር መሆኑ አይዘነጋም። መሰባሰብ ማሰባሰቡም ለዚሁ ነው። ስልታጣንም፤ የመልካም አስተዳደር ባለበት ማለት ነው፤ ከህዝም እንጂ፤ ከእንግዲህ አገሪቱም፤ሕዝብም፤ ጊዜውም ሌላ የጥፋት ስርአት አይፈልጉም። ሁኔታዎችን እንደነበሩ እንዳሉ በመርገጥ መቀጠል የጤንንት ምልክት አይደልመ። ጥቅምም፤ጊዜም፤ሰውም ያልፋሉ፤ አገርና ትውልድ ይቀጥላሉ። ይህ ሁሉ ሲያልፍ ለአድራጊዎች የሚሰጣቸው ስም ምን ይሆን? ጊዜ ምስክር ትሁን-ካለች ማለት ነው።

ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር፤በሕዝቧና በሓቀኛ ልጆችዋ ትድናለች!

ቸር ይግጠመን!!

Tuesday, March 19, 2013

የኢትዮጵያውያን ጩኸት ከመካከለኛው ምስራቅ---በሳኡዲ የመን ድንበር የታሰሩ እስረኞች ለመልቀቅ ገንዘብ እየተጠየቁ ነው::


በሳኡድ ፖሊሶችዛፍ ላይ  የታሰረው ኢትዮጵያዊ 
በሺዎች የሚቆጠሩ በሳኡዲ የመን እስር ቤት ያሉ ስደተኞች አስፈላጊውን ክፍያ እየከፈሉ እንደሚለቀቁ የየመን የደህንነት ባለስልጣን መሃመድ ነጃድ አስታወቁ::

ሁነታዎችን አደገኛ ያደረገው ባለፈው የካቲት ወር ላይ ኢትዮጵያውያን ለሃገራቸው አደገኛ እና ህገወጥ አስጊ መሆናቸውን የሳኡዲ ሚዲያዎች (  http://www.youtube.com/watch?v=DSS4bAVP-fA  )الكنبه إذا عزمك أثيوبي تروح له ؟ / Couch if your determination Ethiopian his imagination?/ የተላለፈውን ዘገባ ተከትሎ ነው:: ይህን ዘገባ የሰሙ የሳኡዲ እና የየመን ዜጎች በድንበሩ አከባቢ እና በሳኡዲ አረቢያ ውስጥ ህገወጥ ናቸው ያሉዋቸውን ሰዎች እየያዙ ያስረክባሉ ቢባልም እውነታው ግን ከኢትዮጵያውያን ገንዘብ እንዲያመጡ ያስገድዷቸዋል::

በሳ ኡዲ  አሰሪዎቹ የተቃጠለው ኢትዮጵያዊ 
በህገወጥ ደላሎች የተደፈሩ ሴቶች 
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኢኮኖሚ ድቀት እና የፖለቲካ አምባገነንነት ሸሽተው ወደየሰዉ አገር የሚሰደዱት ወገኖች
በወጣትነታቸው ሰርተው ራሳቸውን እና ቤተስቦቻቸውን ለመርዳት እንኳን አልታደሉም::ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅት( http://www.un.org/apps/news/story.asp?NewsID=43928&Cr=yemen&Cr1=refugee#.UUiOcDcj8wq ) ባወጣው ዘገባ 84.000 ኢትዮጵያውያን የኤደንን ሰርጥ አቋርጠው በአስፈሪው የውሃ ማዕበል አልፈው ወደ መካከለኛው ምስራቅ ያቋርጣሉ::

አብዛኛው አስቸጋሪውን የባህር ጉዞ የጨረሰው በቀጥታ ወደ የመን ሳኡዲ ድንበር ይሄድ እና በህገወጥ ደላሎች እና ድንበር አሻጋሪዎች ወደ ሳኡዲ ለመግባት ሲሞክር በወሮበሎች በዘራፊዎች በአጭበርባሪዎች ገንዘቡን ይበላል ተይዞ ለፖሊስ ያስረክቡታል ፖሊስም ድጋሚ ገንዘቡን ይነጥቀዋል ::
በቅርብ ጊዜ የወጣ የUNHCR ሪፖርት ( http://www.middle-east-online.com/english/?id=51172 ) እንደሚያመለክተው የየመን እና የሱዲ የድንበር ላይ ባለስልጣናት ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ኢትዮጵያውያንን አስገድደው ይደፍራሉ:ገንዘባቸውን በጉልበት ይነጥቃሉ ይላል::እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ ይጠይቃሉ ያሌለውን ገድለው አካሉን በጥቁር ገበያ ይሸጡታል:: http://www.youtube.com/watch?v=2zTA4U0W3DI&feature=player_embedded

በሳዑድ ፖሊሶች የተያዙ ኢትዮጵያውያን በመኪና ታስረው በየተራ ሲጎተቱ 
በየመን አደን ባህር ላይ የተገኘች ኢትዮጵያዊ ከነልጇ









የታሰሩት ሰልፈኞች ተፈቱ (ፎቶ እና የእስር ቤት ውሎ ዘጋባቸውን ይዘናል)

(በበፍቃዱ ኃይሉ)
EMF – መጋቢት 8/2005 የባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የኢትዮጵያውያን ጠላት የነበረው የፋሺስት ጣሊያን ጄኔራል ግራዚያኒን ኃውልት (በጣሊያን አገር፣ የትውልድ መንደሩ አካባቢ) መቆም በመቃወም የሰልፍ ጉዞ ከስድስት ኪሎ (የካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ኀውልት) እስከ ጣሊያን ኤምባሲ ድረስ ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ነበር፡፡ የሰልፉ ተሳታፊዎች ከጀርባው ላይ ‹‹ለግራዚያኒ ኀውልት ማሠራት አባቶቻችን የከፈሉትን መስዋዕትነት ማራከስ ነው›› የሚል ጽሑፍ የታተመበት ቀይ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር፡፡ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ደግሞ ‹‹ይቺ ባቄላ…›› በሚል ምክንያት ነው መሰለኝ ‹‹የተቃውሞ ሰልፍ…›› የሚባለውን ነገር ለማስቆም ራሱ ግብግብ ፈጠረ፣ ወጣቷ ዓለምን የቀን አጋጣሚ ስድስት ኪሎ አካባቢ፣ በዕለተ እሁድ (መጋቢት 8/2005) አንቀዥቅዦ አመጣት፡፡ የለበሰችው የአዘቦት ቀይ ቲ-ሸርት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለመዋል ምክንያት ይሆነኛል ብላ አልተገመተችም ነበር፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ቀይ ለባሾቹን ማፈስ ሲጀምር ዓለምንም አብሮ አፍሶ አጋዛት፡፡

ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር
ቀይ ለባሾቹ ሰልፈኞች የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር

በተመሳሳይ ሰዓት ለሥራ ጉዳይ ጓዙን ጠቅልሎ ወደአፋር ለመጓዝ እየጠበቁት ያሉ ባልደረቦቹን ለማግኘት በታክሲ ውስጥ ይጓዝ የነበረ አንድ ሰው ከስድስት ኪሎ ተነስቶ አምስት ኪሎ እስኪደርስ የተመለከተውን ሁካታ ዓይቶ ላለማለፍ ከታክሲ ይወርዳል፡፡ ፖሊሶች ከሰልፈኞቹ ውስጥ አሳደው የያዙትን እያፈሱ መኪና ውስጥ ሲያጉሩ፣ ከፖሊሶች ዕይታ እየተሰወረ በሞባይሉ ፎቶ ለማንሳት ሲሞክር፣ አንድም የረባ ፎቶ ሳያነሳ በሦስተኛው ፎቶ ላይ ከፖሊሶች ጋር ዓይን ለዓይን ተጋጠመ፡፡ እሱም ተይዞ ተከተላቸው፡፡ ይህ ድንገተኛ እስረኛ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊ ሆነ፡፡ የታፈሱት ሰልፈኞች ሁሉ የታጎሩት በአራዳ ፖሊስ መምሪያ ጊቢ ውስጥ ነበር፡፡ ጊቢው ውስጥ እንደደረስኩ ከፊት ለፊቴ ደረጃው ላይ የተኮለኮሉትን ሰልፈኞች ተመለከትኩ፡፡ ወጣቶቹ ታፍሰው የገቡ ሳይሆን ወደው የተሰበሰቡ ይመስሉ ነበር፡፡ እንዲያውም በገባሁ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ጮክ ብለው ይዘፍኑ ጀመር፡-
‹‹… ተከብረሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም፣ ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም…››
በዚህ ጊዜ ከፖሊሶቹ አንዱ አብሮ ሲዘምር ይታይ ነበር፡፡ ፖሊሶቹ የተሻለ ትሁቶች ቢሆኑም፣ ሲቪል ለባሾቹ ግን ማመናጨቅ እና ማዋከብ ዋነኛ ሥራቸው ነበር፡፡ እኔን በመኪና ይዘውኝ ከመጡት ውስጥ አንዱ ‹‹ዴሞክራሲ በዛ…›› የሚለውን ቃል እየደጋገመ በቁጭት ይናገራል፡፡ ብዙዎቹ የመምሪያው ፖሊሶች ከየት እንደመጣ የማያውቁት ኮማንደር ግን የተቆጨው በመዘግየቱ ነው፤ ‹‹ይሄን ያክል እስኪሰባሰቡ መቆየት አልነበረብንም›› አለ – እኔው ጎን ቁጭ ብለው ሲነጋገሩ፡፡ በሬዲዮናቸው ሲለዋወጡ ከነበረው ውስጥም ‹‹ሱማሌ ተራ የተጎዳውን ሰውዬ የት ወሰዳችሁት?… ተክለሃይማኖት ሆስፒታል?…›› ይባባሉ ነበር፡፡ በዚሁ ጉዳይ ይሁን አይሁን ግን ‹‹መረጃም (ማስረጃም)›› አልነበረኝም፡፡
ጊቢው ውስጥ ከሌሎቹ እንዳልቀላቀልና ብቻዬን እንድቆይ አድርገውኛል፡፡ ባንድ በኩል ስልኬ ላይ ያሉትን ፎቶዎች አጥፍተው ይፈቱኛል፣ ጉዞዬም ይቀጥላል በሚል ደስ ብሎኛል፡፡ በሌላ በኩል በዓይን የማውቃቸውን እነዚያን ልጆች ቀረብ ብዬ አለማነጋገሬ ቆጭቶኛል፡፡ በዚህ መሐል ግን ሁሉም እየሄዱ ቃል ሲሰጡ ቆዩ (ቃል ሲባል ቃል እንዳይመስላችሁ፤ ከስም አንስቶ የኔ የምትሉትን ነገር በሙሉ ይጠይቋችኋል)፤ ከዚያም የኔም ተራ ደረሰና ቃል ሰጥቼ ሳበቃ እኔም በቀላሉ እንደማልሰናበት ሲያረዱኝ የጓዝ ኮተቴን ሁሉ አስመዝግቤ እዚያው ተጠቃለልኩ፡፡
ከዚያም ቃል የመስጠቱ ሥነ ስርዓት ቀጠለ፤ የመጣው ሁሉ በራሱ መንገድ ያንኑ ጥያቄ መልሶ፣ መላልሶ እያንዳንዱን ታሳሪ (ተጠርጣሪ ልበል ይሆን?) ይጠይቃል፤ እያንዳንዱም ተጠርጣሪ ይመልሳል፡፡ ሆኖም ብዙዎቹን መርማሪዎች የብስጭት መንስኤ የሚሆን ነገር ባለራዕዮቹ ወጣቶች ሳይናገሩ አይወጡም ነበር፡፡ ብሔር ሲባሉ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ይላሉ፡፡ ይህንን የሚሉት ‹‹ብሔር›› የሚለው ቃል ከግዕዝ የተወሰደ ሲሆን፣ ትርጉሙም ‹‹አገር›› መሆኑን እያጣቀሱ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አባባል ለመርማሪዎቹ የሚያበሳጭ ድፍረት ነበር፡፡
ፖሊሶቹ የሆነችውን ሁሉ እየደወሉ፣ ለአለቆቻቸው ይናገራሉ፡፡ ከዚህ መሐል ከሰልፈኞቹ አንዱ ለብሶት የነበረው ባንዲራ ላይ በእስክርቢቶ የጻፈውን ደብዳቤ ከስልኩ ወዲያ ላለ ሰው በንባብ ሲያጽፉት ሰምቻለሁ፡፡ ጽሑፉ ባብዛኛው መንፈሳዊ ነው ቢባል ይቀላል፡፡ ‹‹ለእመቤታችን በአስራትነት የተሰጠችው አገራችን ኢትዮጵያ…›› ብሎ ነው የሚጀምረው፡፡
ምርመራው/ጥያቄው ቀጥሏል፤ ከጠያቂዎቹ መካከል የደኅንነት እና የኢንሳ ሰዎችም ነበሩበት፡፡ ከጥያቄዎቻቸውም ውስጥ የኢሜይል አድራሻ እና የይለፍ ቃል፣ የፌስቡክ አድራሻ እና የይለፍ ቃልም ይጠይቁ ነበር፡፡ እያንዳንዱ ታሳሪ (ተጠርጣሪ አልልም) ስሙን በቪድዮ ካሜራ ፊት እንዲናገር ይገደድ ነበር፡፡ እንግዲህ ይህንኛው መጀመሪያ ላይ እያንዳንዱ ሰው ከተነሳው ፎቶ በተጨማሪ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ የጅምላ እስር ውስጥ ካስተዋልኳቸው ጉዳዮች ውስጥ የሴቶቻችንን ጀግንነት ነበር፡፡ ለምሳሌ፣ እኔ ያለምንም ማንገራገር ምስሌን አስቀርጬ ወደቃለመጠይቁ ሳልፍ የሰማያዊ ፓርቲዋ አመራር አባል ሐና ዋለልኝ ‹‹አልቀረጽም፣ አሻፈረኝ›› ብላ ስትሟገት ድምፅዋ ይሰማኝ ነበር፡፡
ሲመሽ ይፈቱን ይሆን? እዚሁ ያሳድሩን ይሆን? ሌላ ቦታ ይወስዱን ይሆን? ምን ብለው ይከሱን ይሆን? እየተባባልን የተሰባሰብንባት አንዲት በረንዳ መሳይ ክፍል ውስጥ፣ ኢቴቪ በቀጥታ የሚያስተላልፋቸውን የአዳማ እና የመቐለ የኦሕዴድ እና የሕወሓት ስብሰባዎች መኮምኮም ጀመርን፡፡ አሳሪዎቻችንም በስልክ አለቆቻቸውን እያነጋገሩ ሽር ጉዳቸውን አጧጡፈውታል፡፡ ኢቴቪም ብቻውን በዓሉን ማክበር አልቻለም፡፡ መብራቱ ብልጭ ድርግም አበዛ፡፡ ብልጭ ድርግም አልኩ እንጂ ያበዛውስ ድርግም ማለት ነው፤ አልፎ፣ አልፎ ግን ላፍታ ብልጭ እያለ ነበር፡፡ በጨለማው ውስጥ ራታችንን በጨለማ ተቋደስን፡፡ ሁላችንም ምሳ ያልበላን ቢሆንም አንዳንዶች ግን ቁርሳቸውንም አልበሉም፡፡
የመታሰራችን ዜና በማኅበራዊ አውታሮች በመጠኑ ቢስተገባም የብዙዎቻችን ቤተሰቦች ግን አልሰሙም፤ ደውሎ የማሳወቅ ዕድሉም አልተሰጠንም፡፡ እዚያው ጨለማ ውስጥ ከቆየን በኋላ ወደ 3፡00 ሰዓት ገደማ ወደ ጃንሜዳ አካባቢ የሚገኝ ማረሚያ (እስር ቤት) በሁለት ዙር ተወሰድን ከ30 በላይ እስረኞች አንድ ላስቲክ ብቻ ወለሉ ላይ የተነጠፈበት ክፍል ውስጥ ብንታጎርም በእርስ በርሳችን ጫወታ ተጠምደን ነበር፡፡ (በነገራችን ላይ እኛ ወደዚህ እስር ቤት ስንዛወር ቀይ ለባሽዋ ዓለም ተለቅቃ ወደቤቷ ሄዳለች፡፡) የሄድንበት በሰልፉ ዋዜማ ሲቀሰቅሱ ከታሰሩ ሌሎች ጋር ተቀላቅለናል፡፡ የጅምላ እስሩ ጉዳይ በዋዜማው እንደተጀመረ ያወቅኩትም ያኔ ነው፡፡ ቀድመው ከታሰሩት ውስጥ ሁለቱ ክፉኛ ቡጢ እና ካልቾ ቀምሰው እንደሆነ ለማወቅ እስኪናገሩ መጠበቅ አያስፈልገንም ነበር፤ የአንደኛው ጃኬት የደረቀ ደም ከፊትለፊት ይታይበታል፡፡
ለአምስት ሰዓት ዐሥራ አምስት ደቂቃዎች ሲቀሩት ግን እንደገና እንድንንቀሳቀስ ተነገረን፡፡ ከኛ ቀደም ብለው ሴቶቹም ወደቀጨኔ (ችሎት መድኃኔዓለም ኮንዴሚኒዬም አጠገበ ያለ) ወረዳ 9 ማረሚያ ቤት እንደተወሰዱ እና ከኛም ውስጥ 12ቶቻችን መከተል እንዳለብን ተነገረን፡፡ እዚያ እንደደረስን ግን ምነው እዚያው በቀረን የሚያስብል ትዕይንት ገጠመን፡፡ እያንዳንዱ ክፍል እላይ በላይ ተደራርበው በተኙ እስረኞች ተጨናንቋል፡፡ ሌላው ቀርቶ ጫማ ማስቀመጫ ቦታ እንኳን በክፍሉ ውስጥ ስለሌለ ጫማዎቻችንን ውጪ እያስቀመጥን እንድንገባ ተገደድን፡፡ ሦስቱ (አራት ሜትር በአራት ሜትር የሚገመቱ) ክፍሎች ውስጥ አንዱ 37፣ አንዱ 34 እና ሌላኛው ውስጥ 30 እስረኞችን ይዟል፡፡
እንዳጋጣሚ 30 ሰዎች የያዘው ውስጥ ነበር እኔ የደረሰኝ፡፡ የኛ ክፍል ይሻላል ተብሎ ዶ/ር ያዕቆብንም አመጧቸው፡፡ ጉዳዩ በጣም አሳዛኝ ነበር፡፡ እኛስ ባልደከመ ጉልበታችን እንችለዋለን፤ ለርሳቸው ግን በጣም ፈታኝ እንደሚሆን መገመት ቀላል ነው፡፡ ክፍሉ በጣም ጥቅጥቅ ብሎ ከመሞላቱ የተነሳ ለኛ ቦታ ለማግኘት የቤቱ ካቦ ተነስቶ እያንዳንዱን እስረኛ እየቀሰቀሰ ማጠጋጋት ነበረበት፡፡ በቦታ ጥበት ምክንያት ደረቁ ወለል ላይ በአንድ ጎናችን እንድንተኛ ከመገደዳችን የተነሳ እኔ ይህን ጽሑፍ እስከምጽፍበት ሰዓት ድረስ ቁርቋሬው የፈጠረው ሕመም ጎኔን አያስነካኝም፡፡ ካቦው አጠጋግቶልን ሲጨርስ ሁላችንንም የገቢ ገንዘብ ተቀበለን እና ተኛን፡፡ እዚያ ክፍል ውስጥ መተኛት ማለት፣ መተኛት ማለት አይደለም፡፡ የክፍሉ መታፈን እና አስቀያሚ ጠረን፣ ሙቀት፣ በዚያ ላይ እየተቀባበሉ የሚያጨሱት ሲጃራ ጢስ፣ ከዚያ እና ከዚህ የሚተኮስ የፈስ ሽታ… ብቻ የአበሳ ናሙና ነበር፡፡ ሌሊቱን ሲዘንብ ማደሩ ግን በከፊልም ቢሆን የክፍሉን አየር አቀዝቅዞታል፤ ችግሩ ዝናቡ ውጪ ያስቀመጥነው ጫማ ውስጥ ውኃ መሙላቱ ብቻ ነበር፡፡
እንደምንም ነጋልንና ወደፍርድ ቤት እንደምንሄድ ተነግሮን ጥንድ ጥንድ እየተደረግ በካቴና ተቆላለፍን፡፡ ከመሐከላችን አንዱ የማኅበሩ አባል፣ ፀጉሩን አጎፍሮ ስለነበር (ለፍርድ ቤቱ ውበት አይመጥንም ብለው ይሆናል) ይቆረጥ አሉና መቀስ አንስተው ይከመክሙት ጀመር፡፡ ፀጉሩን ቆርጠው ሲጨርሱ አሰለፉንና ካቴናችንን ፈቱት፡፡ ‹‹ፍርድ ቤት መወሰዳችሁ ቀርቷል፣ ምናልባት ፖሊስ ጉዳዩን ይፈታዋል›› ተባልንና ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ወደጃንሜዳ ማረሚያ ቤት መልሰው ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ለፖሊስ ዋስ እያቀረብን እንድንፈታ ተፈቀደልን፡፡ ቀድሞውንም የታሰርነው ያለወንጀል በመሆኑ አስገራሚ ውለታ አልነበረም፡፡
የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስፈልገው ቅድመ ሁኔታ ለመስተዳድሩ ማሳወቅ ሲሆን፣ መስተዳድሩ ደግሞ በ24 ሰዓት ውስጥ ‹‹አይሆንም›› የሚል ደብዳቤ ካልጻፈ እንደተፈቀደ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ሰልፍ ማድረጉ ሕጋዊ ስህተት የለበትም፣ ጉዳዩ ባንድ ጀምበር የተወለደ ሳይሆን ጋዜጦች ዜና የሰሩለት፣ ቁጥቦቹ ሬድዮዎች ሳይቀሩ ያወሩለት ጉዳይ ስለሆነ ወንጀል ነው ፍርድ ቤት ሊያቀርቡት አይችሉም/አይገባቸውምም፡፡ ነገር ግን ‹‹…ካፈርኩ አይመልሰኝ…›› ይመስላል በዋስትና እንድንፈታ ፈቅደው ያገቱብንን ንብረቶቻችንን እየመለሱ መጋቢት 9/2005 እኩለ ቀን ላይ አሰናበቱን፡፡

ኢህአዴግ በዘር ማጥፋት ወንጀል ተነክሯል

ኢህአዴግ በዘር ማጥፋት ወንጀል መነከሩ በተግባር በተደጋጋሚ እየታየ ነው። በተለይም አማርኛ በሚናገሩ ዜጎች ላይ የሚፈጸመው ወንጀልና ወንጀሉን የሚፈጽሙትን ክፍሎች የሚገስጽ መጥፋቱ ጉዳዩን እያወሳሰበው ነው። ኢሳት መኢአድ ያወጣውን መግለጫ ጠቅሶ እንደዘገበው “በቋንቋ ማንነት ህዝብን መግደል፣ ማፋናቀል እና ማሰር የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው” በሚል ርዕስ ሰሞኑን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአማራ ተናገሪ ማህበረሰብ ላይ የተከፈተው ማፈናቀል፣ በጅጅጋ እና በአፋርም የቀጠለ ሲሆን በመላው አገሪቱ የአማርኛ ተናጋሪ ህዝብ ቤት እንዳይኖረው፣ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንዳይሳተፍ በተለያየ ስልት ድሃ ሆኖ በጎዳና እንዲበተን የህወሃት/ኢህአዴግ ካድሬዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ትእዛዝ የሰጡ ሲሆን በአዲስ አበባ ከፈረሱ እና እያፈረሱ ካሉ ቤቶች አብዛኞቹ የአማራ ተናጋሪዎች መኖሪያ መሆናቸውን መታዘቡን ገልጿል። የባንክ ብድርን መከልከልን ጨምሮ መሬት እንዳያገኙ ከመደረጉም በላይ ከፍተኛ ግብር እየተጫነባቸው ከንግድ ስርአቱ እንዲወጡ መደረጉን መኢአድ አመልክቷል። በአሁኑ ጊዜ ከ200 በላይ ከቤንሻንጉል ጉምዝ የተፈናቀሉ የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች በባህርዳር ያለመጠለያ በጎዳና እየኖሩ መሆኑን መኢአድ በመግለጫው አመልክቷል። በባህርዳር ለጎዳናና ተዳዳሪነት ከተዳረጉት መካከል ብዙ ነፍሰጡሮችና ህጻናት እንደሚገኙበትም ገልጿል።
አማርኛ ተናጋሪውን ህዝብ በብሄራዊ ጨቋኝነት በመፈረጁ በአርባ ጉጉ ፣ በበበደኖ፣ በአርሲ፣ በባሌ፣ በጋምቤላ እንዲጨፈጨፍ ሲያደርጉ አገዛዙ ምን ያክል የአማርኛ ተናጋሪውን ህዝብ ለማጥፋት እንደተፈለገ አመላካች መሆኑን የጠቀሰው መኢአድ፣ ከአንድ አመት በፊት በቤንች ማጂ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ በከፍተኛ ጭካኔ በአማርኛ ተናጋሪ አርሶአደር ፣ ሴቶች፣ ነፍሰ ጡር፣ ህጻናት እና ሽማግሌዎች ላይ የተጀመረው ጭካኔ የተሞላበት ስደት ተባብሶ ቀጥሎ በየጎዳናው የሚጣለው የኔቢጤ ከመሆን አልፎ ለአውሬና ለአሰቃቂ ኑሮ የተጋለጠው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ህብረተሰብ ቁጥር እየጨመረ በቤንሻንጉል ፣ በጅጅጋ፣ በአፋር እና በአንዳንድ የአሮሚያ ክልል እየቀጠለ ነው ብሏል፡፡
መኢአድ “ማንኛውም ሰው በቋንቋው ፣ በጎሳው፣ በእምነቱ፣ በቀለሙ እና በማንኛውም ልዩነት ምግብ ሲያጣ ፣መጠለያ ሲነፈገው ፣ጨቅላ ህጻናት በየጎዳናው ሲሞቱ፣ ነፍሰጡሮች በየበረንዳው ሲወድቁ፣ ህሊናን የሚያደማ መሆኑን ገልጾ” ይህንን ጨቋኝ ስርአት በአለም ህዝብ ፊት በዘር ማጥፋት ወንጀል ልንከሰው ይገባል” ማለቱን የኢሳት ዜና ያስረዳል።

Monday, March 18, 2013

የግራዚያኒን ሀውልት ግንባታ በመቃወም ታሰረው የተፈቱ ዜጎች ዘራቸው እየተጠቀሰ መሰደባቸው ታወቀ

መጋቢት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የፋሽስት ኢጣሊያ መንግስት ወኪል በመሆን በአንድ ቀን ከ30 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያንን በስድስት ኪሎ አደባባይ የጨፈጨፈውን የሮዶልፎ ግራዚያኒን ሀውልት ለማቆም እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ለመቃወም ትናንት እሁድ በስድስት ኪሎ የተሰባሰቡ የባለራእይ ወጣቶች ማህበር አባላት፣ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እንዲታሰሩ ተደርጓል።
የጸጥታ ሀይሎች ታዋቂውን የህግ ባለሙያና ፖለቲከኛ ዶ/ር ያእቆብ ሀይለማርያምን ጨምሮ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነትን ለአንድ ቀን ካሰሩዋቸው በሁዋላ በመታወቂያ ዋስ ለቀዋቸዋል። ከእስረኞች መካከል አንዳንዶቹ ብሄር ተብለው ሲጠየቁ ኢትዮጵያውዊ በማለት የመለሱ ዘራቸው ሳይቀር እንደተሰደበ ታውቋል። በርካታ ወጣቶች የኢሜል እና የፌስ ቡክ የሚስጢር ቁልፋቸውን ( ፓስወርድ) እንዲሰጡ መጠየቃቸውንም ለማወቅ ተችሎአል።
በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየታቸውን የሰጡት ለአንድ ቀን ታስረው የተፈቱት ዶ/ር ያእቆብ ፣ እርሳቸውና ሌሎች ሰዎች የታሰሩት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ፈቃድ አልተጠየቀም በሚል ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል። ።
ዶ/ር ያእቆብ የጸጥታ ሀይሎች የወሰዱት እርምጃ መንግስት ለግራዚያኒ እንደቆመ ያስቆጥርበታል ብለዋል።
የባለራእይ ወጣቶች ማህበር መሪ ወጣት ሀብታሙ አያሌው በበኩሉ ፈቃድ የጠየቁት ከ 14 ቀናት በፊት እንደነበር ገልጿል::
በታሰሩት ላይ የተደረገው ምርመራ ከጉዳዩ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳልነበረው ወጣት ሀብታሙ ተናግሯል::
ወጣት ሀብታሙ ዛሬም አንድ አባላቸው ታስሮ እንደነበር ገልጾ ወዴት እየሄድን እንደሆን አናውቅም ብሎአል:: በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስትን አቋም ለማወቅ ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

World Bank: Investigate ‘Development’ Project Abuses

(Washington, DC) – The World Bank’s board should support an internal investigation into allegations of abuse linked to a World Bank project in Ethiopia, Human Rights Watch said today.
The Inspection Panel, the World Bank’s independent accountability mechanism, has recommended aninvestigation into whether it has violated its policies in a project linked to the Ethiopian government’s resettlement program, known as “villagization.” Villagization involves the forced relocation of some 1.5 million Ethiopians, including indigenous and other marginalized peoples, and has been marred by violence. The board is scheduled to meet on March 19, 2013, to consider the Inspection Panel’s recommendation.
“The World Bank’s president and board need to let the Inspection Panel do its job and answer the critical questions that have been raised by Ethiopians affected by this project,” said Jessica Evans, senior international financial institutions advocate at Human Rights Watch. “If the World Bank doesn’t support this investigation, its Ethiopia program will continue to be shadowed by controversy.”
On September 24, 2012, several Ethiopians brought a complaint to the Inspection Panel, pressing the World Bank to apply its safeguard policies in an Ethiopia project. The safeguard policies are designed to prevent and mitigate undue harm in World Bank projects, including protecting the rights of indigenous peoples and preventing abuses related to involuntary resettlement.
The World Bank went ahead and approved the project the next day and has not applied its safeguard policies to the project.
The Inspection Panel, which reports directly to the World Bank’s board of executive directors, subsequently found that the complaint warranted a full investigation. This recommendation would have been endorsed by the board in February, but action has been delayed because the executive director representing Ethiopia has requested a discussion of the panel’s finding and recommendation.
Human Rights Watch research has found that many of the largely indigenous communities being moved in Gambella, one region where “villagization” is being carried out, have not been consulted about the resettlement process and that the government responded with violence and arbitrary detentions when people have not agreed to move.
A 20-year-old Ethiopian man who escaped to Kenya told Human Rights Watch, “Soldiers came and asked me why I refused to be relocated.… They started beating me until my hands were broken … I ran to tell [my father] what had happened, but the soldiers followed me. My father and I ran away.… I heard the sound of gunfire.” He heard his father cry out, but he kept running and hid from the soldiers in the bushes as he was “full of fear.” When he returned the next day, he learned that the soldiers had killed his father.
Once forced into new villages, families have found that the promised government services often do not exist, giving them less access to services than before the relocation. The government has also failed to provide compensation. Dozens of farmers in Ethiopia’s Gambella region told Human Rights Watch they are being moved from fertile areas where they survive on subsistence farming, to dry, arid areas. Many villagers believe that the fertile land from which they have been removed is being leased to multinational companies for large-scale farms.
The project in question is known as the Promotion of Basic Services (PBS) and is intended to improve education, health care, water and sanitation, agriculture, and rural roads. But, through this project, the World Bank is contributing to the salaries of local government staff who have been required to assist in implementing “villagization.”
Despite the human rights risks that “villagization” presents for the World Bank’s project,it has not applied its own safeguard policies. Its policy to protect indigenous people has not been applied in Ethiopia because the government does not agree that it should apply. Nor has the World Bank applied its policy on involuntary resettlement, which requires consultation and compensation when people are resettled.
The Inspection Panel recommended that it undertake a full investigation after a preliminary assessment that included interviewing Ethiopian refugees who have fled “villagization” and meeting with the Ethiopian government and donors. The Inspection Panel found the links between the World Bank’s basic services program and “villagization” to be plausible and to warrant investigation.
“Ethiopia is in great need of development aid, and its people have urgent social and economic needs that the World Bank should work to address,” Evans said. “But development by force is not development at all and Ethiopia should not be an exception to the World Bank’s commitment to upholding its own policies.”

Ethiopia ‘blocks’ Al Jazeera websites


Traffic to English and Arabic websites has plummeted since the network aired coverage of protests in August last year.Al Jazeera’s English and Arabic websites are reported to have been blocked in Ethiopia, raising fresh fears that the government is continuing its efforts to silence the media.Though the authorities in Addis Ababa have refused to comment on the reported censorship, Google Analytics data accessed by Al Jazeera shows that traffic from Ethiopia to the English website had plummeted from 50,000 hits in July 2012 to just 114 in September.Traffic data revealed a similar drop for the Arabic website, with visits to the site dropping to 2 in September from 5,371 in July.A blogger, who cannot be identified for his own safety, said Ethiopian censors had been targeting Al Jazeera since the Qatar-based network began airing coverage of ongoing protests against the way in which spiritual leaders are elected in the Horn of African nation.The steep decline in web traffic began on August 2 last year, the same day that Al Jazeera Mubasher aired a forum with guests denouncing the government’s “interference” with Muslim religious affairs, and three days after Al Jazeera English published an article detailing deadly ethnic clashes between two of the country’s southern tribes.Attempts by Al Jazeera to get an official response from authorities failed.Poor track recordEthiopia is ranked 137 out of 179 surveyed nations on the latest Press Freedom Index of Reporters Without Borders (RSF), an international advocacy group for press rights.Both RSF and the Committee to Protect Journalists (CPJ) have tied Ethiopia’s deteriorating media environment, in part, to a 2009 anti-terrorism law that has been used to jail 11 journalists since its ratification.“The usage and practice of this law is illegal. It has a clause that makes whoever writes about so-called terrorist groups, which are mostly normal opposition groups, a terrorist,” CPJ’s East Africa Consultant Thom Rhodes told Al Jazeera.“Now it’s got to the point that the law is being used to label those in the Muslim community conducting peaceful protests to defend their right to choose their spiritual leaders as terrorists. It’s a sad state of affairs.”CPJ says Ethiopia is the second-highest jailer of journalists in Africa after neighbouring Eritrea, were seven journalists are currently detained.Both the RSF and CPJ have expressed concern over reports that the country has begun using much more sophisticated online censorship systems over the last year, including ones that can identify specific internet protocols and block them.Since Ethiopia’s government owns the sole telecommunications provider in the country, Ethio Telecom, it allows authorities to tightly control internet freedom.

Image

Sunday, March 17, 2013

Ethiopia arrests 43 anti-Graziani statute protesters in Addis Ababa

 

Dr. Yacob Hailemariam, a retired professor of business law at Norfolk State University and former Senior Prosecutor for the International Criminal Tribunal for Rwanda
Awramba Times (Addis Ababa) – Ethiopian police arrested prominent opposition leaders and activists in the capital Addis Ababa today.
According to our sources, former opposition leader Dr. Yacob Hailemariam, Semayawi Party chairman, Eng. Yilkal Getnet and his deputy Sileshi Feyissa are among the detainees.
“What’s happening today is outrageous and unbelievable” said Ethiopian human rights activist, Prof. Mesfin Woldemariam. “officials could have deny the application for protest instead of detaining citizens after the incident” he added.

የሰማያዊ ፓርቲ እና የባለራዕ ወጣቶች ማህበር አመራሮች እና አባሎች ለእስር ተዳረጉ

  ሰበር ዜና
 
ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ማህበር፤ ሰማያዊ ፓርቲ እና ባለራዕ ወጣቶች ማህበር በጋራ በመሆን ለፋሽስቱ የጦር ወንጀለኛ ለማርሻል ግራዚያኒ ክብር መስጠት የአባቶቻችን መስዋዕትነት ማራከስ ነው” በሚል የተጠራውን ሰልፍ አምባገኑ የኢህአዴግ መንግስት በርካታ የፌደራል ፖሊስ፣ የደህንነት አባላትን እና የአዲስ አበባ ፖሊሶችን በማሰማራት ሲበትን፤ የተቋማቱን ከፍተኛ አመራሮች፤ ታዋቂ ግለሰቦች እና በርካታ ወጣቶችን ጨምሮ ቢያንስ 34 ሰዎች አስሯል የታሳሪዎች ቁጥር አሁንም በመጨመር ላይ ነው፡፡ እንዲሁም በትላንትናው እለት ለተቃውሞ ሰልፉ የቅስቀሳ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት ውስጥ ሁለት የሰማያዊ ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ አባላትን እንዲሁም የባለራዕይ ወጣቶች የስራ አስፈጻሚ አባላትን ጨምሮ ስምንት ሰዎችን አስረዋል፡፡
በአሁኑ ሰአት የወያኔ መንግስት ብዙዎችን ሰዎች ለእስር መዳረጉ ታውቋል::  በእስር ላይ ከሚገኙት መካከል
1. ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
2. አቶ ታዲዎስ ታንቱ 3. አቶ ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ
ሊቀመንበር)
4. ስለሺ ፈይሳ (የሰማያዊ ም/ሊቀመንበር)
5. ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ የህግ ጉዳይ
ሀላፊ)
6. ሀና ዋለልኝ (የሰማያዊ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊ)
7. ጌታነህ ባልቻ (የሰማያዊ የድርጅት ጉዳይ
ሀላፊ)
8. ብርሀኑ ተክለያሬድ (የባለራዕይ ወጣቶች
ተ/ምክትል ሊቀመንበር)
9. ያሬድ አማረ (የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ጸሀፊ)
10. ኤልሳቤጥ ወሰኔ
11. ሰለሞን ወዳጅ
12. ወይንሸት ንጉሴ
13. እየሩሳሌም ተስፋው
14. ለገሰ ማሞ 15. ትዕግስት ተገኝ
16. አማኑኤል ጊዲና
17. አለማየሁ ዘለቀ
18. አገኘሁ አሰገድ
19. ሻሚል ከድር
20. አሸብር ኪያር 21. ጌታቸው ሽፈራው
22. ግሩም አበራ
23. አቤል ሙሉ
24. ዩሀንስ ጌታቸው
25. ስማቸው ተበጀ
26. ፍቃዱ ወንዳፍራው 27. ባህረን እሸቱ
28. ሄኖክ መሀመድ
29. እንቢበል ሰርጓለም
30. አለማየሁ በቀለ
31. ዩናስ
32. የመኪናው ሹፌር 33. ዮዲት አገዘ
34. ጥላዬ ታረቀኝ
...
 
 

Saturday, March 16, 2013

መድረክ መነቃነቅ ጀመረ

የስድስት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በሀገሪቱ የፖለቲካ እንቅሰቃሴ ፈጠን ወዳለ እንቅስቃሴ ለመግባት መዋቅሮቹን ማነቃነቅ ጀመረ።
የግንባሩ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ባለፈው ሰኞ ባካሄዱት ስብሰባ የግንባሩ አራት የተግባር ኮሚቴ አባላት
የመዋቅር ለውጥ በማድረግ የራሳቸውን ዝርዝር እቅድ ይዘው እንዲቀርቡ አዟል።
ለግንባሩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት የግንባሩ አራት የተግባር ኮሚቴዎች በስራቸው ንዑስ የስራ ኮሚቴዎችን በማዋቀር፣ በዋና ጽ/ቤቱም ቋሚ ባለሙያዎችን በመቅጠር ጭምር የግንባሩን የጽ/ቤት የእለት ተዕለት ስራ ለማከናወን ወስኗል።
ግንባሩ ከአንድ ወር በፊት ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ በአባል ፓርቲዎች መካከል ያለው የመተማመን ደረጃ
እየተሻሻለ በመምጣቱ ስራዎችን በጋራ የማንቀሳቀስ ሁኔታ ተጀምሯል። በመጪው አርብ በድጋሚ በሚካሄደው ተጨማሪ ስብሰባ የግንባሩን ስራ ይበልጥ ለማቀናጀት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ እቅዶች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።
ግንባሩ በቅርቡ የራሱን ድረገጽ መክፈቱ እንዲሁም ልሳን የማዘጋጀቱንም ተግባር ልዩ ትኩረት መስጠቱ እንዲሁም
ግንባሩን ለማጠናከር የሚያስችሉ ሰፋ ያሉ የገንዘብ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎች ላይ እንደሚሰማሩም ምንጫችን ጠቁሟል።
ቀደም ሲል ‘‘መድረክ ተኝቷል’’ የሚል ወቀሳ ከአንዳንድ የፓርቲው አመራር አባላት በግልፅ ትችት ሲቀርብበት
ቆይቷል። በግንባሩ ውስጥ ሥራውን በተግባርና በአመለካከት ደረጃ የሚያጓትት አካል እንዳለም ምንጫችን ያመለከተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግንባሩ ወደ ስራ ሲገባም ስራውን የሚያጓትተው እና የሚያፋጥነው አካል እንደሚለይም ታውቋል።
መድረክ ከሁለት አመት በኋላ የሚካሄደው የ2007 ሀገር አቀፍ ምርጫ ዋናው ግቡ መሆኑን የጠቀሰው ምንጫችን በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ውስጥ በስድስቱ ፓርቲዎች መካከል በሚፈጠረው የጋራ መግባባት ከግንባር እስከ ውህደት ሊደርስ የሚችልባቸውን አማራጮች እንደሚፈትሽ የጠቆመ ሲሆን ግንባሩ አሁን እየፈጠረ ባለው አዲስ መዋቅር አዳዲስ ጠንካራ ሰዎች ይፈጠራሉ የሚል ተስፋ ይዟል።
ግንባሩ ከፍተኛ የበጀት እጥረት እንዳለበት ተደጋግሞ ቢገልፅም፤ የበጀት እጥረቱ መድረኩ ስለስራ ያጋጠመ ችግር
መሆኑም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በቀጣይ ሳምንታትም ግንባሩ ያዘጋጀው ማኒፌስቶ በመገናኛ ብዙኋን እና
በዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ይፋ እንደሚደረግም ምንጫችን ጠቁሟል።
በአሁኑ ወቅት ስድስት ፓርቲዎች በግንባር ያዋቀረው መድረክ በ2002ቱ ምርጫ ከኢህአዴግ በመቀጠል ብዙ መራጭ ማግኘቱ አይዘነጋም።

ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ኢትዮጵያ ዉስጥ በሠፊዉ ሥራ ላይ መሆኑ ተረጋገጠ


ኢትዮጵያ

ፊን ፊሸር ሰላዩ ቫይረስ

ፊን ፊሸር የተባለ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም በዓለም 25 ሀገሮች ዉስጥ መሠራጨቱንና መንግስታቱም የገዛ ዜጎቻቸዉን ለመሠለል እንደሚጠቀሙበት አንድ ጥናት አመለከተ። ኢትዮጵያ ዉስጥም በሠፊዉ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ጥናቱ ይፋ አድርጓል።
የኢንተርኔት ቫይረሱ ኮምፕዩተር ዉስጥ ከገባ ግለሰቦች በኮምፕዩተራቸዉ ላይ የሚያደርጉትን የፅሁፍ የድምፅና የምስል የመልዕክት ልዉዉጦች ወደዋና መረጃ ማሰባሰቢያዉ ማዕከል ይልካል። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች RSF ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚደረገዉን ቁጥጥር አስመልክቶ የተጠቀሰዉ የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን ጥናቱን ጠቅሶ ለዶቼ ቬለ መግለፁን ዘግበናል። ዶቼቬለ ስለጉዳዩ የጠየቃቸው የኢትዮ ቴሌኮም የኮምንኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሂም አህመድ ኢትዮ ቴሌኮም በተጠቀሰው ፕሮግራም እንደማይገለገል በስልክ ተናግረዋል። አቶ አብዱራሂም ስለጥናቱ ውጤት እንደማያውቁ ገልፀው ሆኖም ፊን ፊሸር የተባለው የስለላ የኮምፕዩተር ፕሮግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ ላይ ውሏል መባሉን ከዕውነት የራቀ ሲሉ አጣጥለውታል።
ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት RSF በያዝነዉ ሳምንትባወጣዉ የኢንተርኔት ቁጥጥርን የሚመለከት ዘገባ አምስት ሀገሮችን የኢንተርኔት ጠላት ሲል ፈርጇል። የሶርያ፤ ቻይና፤ ኢራን፤ ባህሬን እንዲሁም የቬትናም መንግስታት የኢንተርኔት መረጃዎችን ለመቆጣጠር ከሚሰነዝሩት የድረገፅ ጥቃት በተጨማሪ ዜጎችን ለመሰለል የግለሰቦችን የኢሜል መረጃ የሚያጠምዱ ፕሮግራሞችን በመጠቀም ግንባር ቀደም ተብለዋል። ከበርካታ ሀገሮች እነዚህ አምስቱ የተመረጡትም ለኢንተርኔት ቁጥጥሩ የሚጠቀሙበት ቴክኒዎሊጂ መራቀቅና በዚህ ስለላ መሠረትም ጋዜጠኞችና ዜጎቻቸዉን በማሰራቸዉ እንደሆነ የRSF የዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ተመራማሪ ግሬግዋ ፑዤ ገልፀዋል። በተለይም ቻይና የኤሌክትሮኒክ መከላከያዋ ከዓለም ምናልባትም የረቀቀ ተብሎ ሲገመት ይህንኑ ቁጥጥሯን ለማጠናከር የግል ኢንተርኔት ኩባንያዎች ዜጎቿን ለመሰለል የሚረዱ ስልቶችን እንዲያቀርቡላት ማድረጓም ተገልጿል። ኢራን በበኩሏ የራሷን «ሃላል ኢንተርኔት» በሚል አቋቁማ የኢንተርኔት መረጃ ቁጥጥሯን አጠናክራለች። RSF የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂን ሳይኖራቸዉ አምባገነን መንግስታት ዜጎቻቸዉን ለመሰለል እንደማይችሉ በማመልከት ለመጀመሪያ ጊዜ ተባባሪ የኢንተርኔት ጠላቶች ሲል የመሰለያ ፕሮግራሞችን የሚሰሩና ለሀገራቱ የሚያቀርቡ ድርጅቶችንም ስም አጋልጧል። ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት ዜጎቻቸዉን በኢንተርኔት መረጃ ልዉዉጥ ሳይቀር እንዲቆጣጠሩና እንዲሰልሉ ስልቱን እያስተካከሉ የሚያቀርቡትን አምስት የግል ኩባንያዎችም የዘመኑ «ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች» ሲል RSF ወቅሷል።
ኢትዮጵያ ዉስጥ በርከት ያሉ ድረ ገፆች መነበብ እንደማይችሉ ተደጋግሞ የተገለፀ ጉዳይ ነዉ፤ መንግስት በበኩሉ ወቀሳዉን ቢያስተባብልም። የጥናቱ ተባባሪ ፀሐፊ ግሬግዋ ፑዤ ከአምስቱ ሀገሮች ተርታ በዘገባዉ ኢትዮጵያ ያልተጠቀሰችዉ የኢንተርኔት አገልግሎቱ እንደአምስቱ ሀገሮች የተስፋፋ ባለመሆኑ እንደሆነ ለዶቼ ቬለ ገልፀዋል። ያ ማለት ግን ድርጅታቸዉ ክትትል አላደረገም ማለት አይደለም፤
«ባለፈዉ ዓመት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምን እንደተደረገ እየተካተልን ቆይተናል። ማለትም TOR የተሰኘዉ ስልት ተዘግቷል፤ የሰዎች ኢሜይል ልዉዉጥ እየሰበረ የሚበረብረዉ DPI የተሰኘዉ ፕሮግራምም ስራ ላይ መዋሉን እናዉቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ከቶሮንቶ አንድ ዘገባ አዉጥቷል፤ ያም ኢትዮጵያ ዉስጥም አንድ የግለሰቦችን የኮምፕዩተር መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም መጠቀም መጀመሩን ይገልፃል። ተቋሙ ዛሬ ይፋ ባደረገዉ ዘገባ ፕሮግራሙ ኢትዮጵያ ዉስጥ ኢንተርኔት ላይ የሚካሄደዉን ቁጥጥር የሚያረጋግጥ መረጃ አካቷል።»
ግሬግዋ ፑዤ የጠቀሱት ሲቲዝን ላብ የተሰኘዉ ተቋም ይፋ ያደረገዉ ዘገባ የግለሰቦችን መረጃ የሚያጠምደዉ የኢንተርኔት ፕሮግራም ፊን ፊሸርስ እንደሚባል ይገልፃል። እንደዘገባዉም ኢትዮጵያ በተለይም ከተቃዉሞ ፖለቲካ ቡድኖች ጋ ግንኙነት ያላቸዉ ግለሰቦችን ለመከታተል ትጠቀምበታለች።

ኩባንያዉ ይህን የግለሰቦችን የኢንተርኔት መረጃ የሚያጠምድ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ያዘጋጀዉ የግንቦት ሰባት አባላትን ፎቶዎች በመጠቀም እንደሆነም ዘገባዉ በመዘርዘር ምስሎቹን ያሳያል። ግሬግዋ ፑዤ፤
«ባለፈዉ የበጋ ወቅት ሲቲዚን ላብ ፊን ፊሸር የተሰኘዉ ፕሮግራም ኢትዮጵያ ዉስጥ ሥራ ላይ መዋሉን ደረሰበት። የግንቦት ሰባትን «ስሙን በትክክል ብየዉ እንደሁ አላዉቅም» ምስል የያዘዉ ይህ ህገወጥ ፕሮግራም በርካታ የተቃዉሞ ፓርቲ አባላት በኢሜል አድራሻቸዉ እንዲደርሳቸዉ ተደረገ። እናም ይህ ምስል ትክክለኛ መልዕክት የያዘ ሳይሆን ያ መረጃ የሚያጠምደዉ ፕሮግራም ነዉ። ይህን ፕሮግራም አንዴ ኮምፕዩተርሽ ዉስጥ ከገባ ወደማዘዣዉ ኮምፕዩተር መረጃዎችን በሙሉ እየቀዳ ይልካል። ይህ ነገር ኮፕዩተርሽ ዉስጥ ካለ እያንዳንዷ የምትፅፊያት ነገር ፕሮግራሙን ወደላከዉ አካል ይሸጋገራል።» እሳቸዉ እንደሚሉትም ሲቲዚን ላብ ባደረገዉ ክትትል የግለሰቦችን መረጃ እየቀዳ የሚልከዉ ህገወጥ ፕሮግራም ትዕዛዝ አስተላላፊ የኮምፕዩተር መረጃ ማከማቻ የሚገኘዉ እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን ደርሶበታል። ኢትዮጵያ ዉስጥ በኢንተርኔት ላይ የሚከናወነዉን ጥብቅ ቁጥጥር እና ስለላ አስመልክቶችም ሲቲዚን ላብ ይፋ ያደረገዉን አዲስ መረጃ በማካተት ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ዘገባ ይፋ እንደሚያደርግም ከወዲሁ ጠቁመዋል።

Friday, March 15, 2013

“ከምድር በታች ጨለማ ቤት ውስጥ የታሰሩትን በቀን ለ10 ደቂቃ እናያቸዋልን።ስዊድናዊ የፍሪላንሰር ጋዜጠኛ ማርቲን ካርል ሻቢዬ በኖርዌይ ኦስሎ

    
the meeting
“ከምድር በታች ጨለማ ቤት ውስጥ የታሰሩትን በቀን ለ10 ደቂቃ እናያቸዋልን። ልብ የሚነካ ነው። የብርሃን ማነስ አይናቸውን እንደጎዳቸው ያስታውቃሉ … ሴቶችን በተገኘው ሰበብ ያስሯቸዋል። ምክንያት ፈልገው እስር ቤት ይከቷቸዋል። ከዚያም ይደፍሯቸዋል። በርካታ የተደፈሩ እህቶች አሉ። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና መንግሥት ያሰማራቸው ሚሊሻዎች ይህንን አሳዛኝ ድርጊት እንደፈጸሙ ተነግሮናል” ይህ ማዕከላዊ እስር ቤት ታስሮ፣ ችግሩ ባለበት ቦታ ተገኝቶ የነበረው ስዊድናዊ የፍሪላንሰር ጋዜጠኛ ማርቲን ካርል ሻቢዬ ቃል ነው።
ስለ ማዕከላዊ እስር ቤት መስማት ይጨንቃል። ሰዎች በሲቃ የሚያሰሙት የጣር ድምጽ ለጆሮ የተለመደ ነው። ከመሬት በታች የጨለማ ክፍል አለ። በዚህ መታጎሪያ ውስጥ ሆነው ስቃይ የሚፈራረቅባቸው ወገኖች ጥቂት አይደሉም። ማዕከላዊ ብዙ ጉድ ያለበት ሲኦል ነው። የሰው ልጆች በግፍ ማቅቀውበታል። እየማቀቁበትም ነው። ለውጥ እስከሌለ ድረስ የሚቆም አይመስልም። በመሃላ የሚነገርለት ውርስና ይቀጥላል የሚባለው የመለስ ራዕይ አንዱ ክፍል ይህ ነው።
መጋቢት 3፤2005 (3/12/2013) በኖርዌይ ኦስሎ የሥነጽሁፍ ቤት (ሊትሬቸር ሀውስ) በተዘጋጀ የመወያያ መድረክ ላይ ሁለቱ ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ተገኝተው ነበር። መድረኩን ያዘጋጀው ደግሞ NOAS በሚል ስያሜ የሚታወቀው የስደተኞች ተሟጋች ድርጅት ነው። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አን-ማግሬት ኦስቴና ሁለቱን እንግዶች ካስተዋወቁ በኋላ መድረኩን እየመሩ ውይይቱ ተካሄደ። በዚህ ውይይት ላይ ሁለቱ ጋዜጠኞች እየተፈራረቁ የደረሰባቸውንና በትክክል ያዩትን አስታወቁ።
ማርቲን ካርል ሻቢዬና ባልደረባው የፎቶ ጋዜጠኛ ጆሃን ካርል አበክረው የሚናገሩት ስለ ሙያቸው ነው። “ጋዜጠኛ ለመጻፍ ማየትና ማነጋገር አለበት። በተለያዩ አገራት ጋዜጠኞች ችግር ባለባቸው ቦታዎች ገብተው ለመዘገብ ድንበር ያቋርጣሉ። አሁን በሶሪያ፣ ቀደም ሲል በሊቢያ የሆነው ይህ ነው። በኢትዮጵያ ግን ሽብርተኛ ያሰኛል” ሲሉ ግርምታቸውን ይጀምራሉ።
የ19 ዓመት ወጣት ነው። ስራዉ ሹፍርና ሲሆን “ኦነግ ነህ” ተብሎ ነው የታሰረው። መርማሪዎች ባዶ ወረቀት እየሰጡ ስለ ኦነግ ጻፍ ይሉታል። ምንም የሚያውቀው ነገር ስላልነበር መጻፍ አልቻለም። በመጨረሻ ራሳቸው ጽፈው አዘጋጅተው በራስህ እጅ ጽሁፍ ገልብጥ አሉት። እናም የተባለውን ፈጸመ። ጋዜጠኞቹ ብዙ መረጃ አላቸው። እነሱንም ያልሆኑትንና ያላደረጉትን አድርገናል እንዲሉ መደረጋቸውን አስታውቀዋል። “በሶማሊያ አምስት ዓመት ተቀምጫለሁ እንድል አስገድደው አሳመኑኝ” በማለት ጆሃን ካርል ገለጸ።

ወ/ሮ ዙፋን አማረ
የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌይ ሊቀመንበር ወ/ሮ ዙፋን አማረ እንደሚሉት ሁለቱ ጋዜጠኞች ኖርዌይ እንዲመጡ ከላይ ከተጠቀሰው ድርጅት ጋር ከመነጋገር ጀምሮ ማህበራቸው የበኩሉን ስለማድረጉ ይናገራሉ። ይህ እንዲሆን የታሰበው ደግሞ ጋዜጠኞቹ በትክክል ያዩትንና የደረሰባቸውን ለኖርዌይ ባለስልጣናት በማስረዳት በኢትዮጵያ ላይ የያዙትን አቋም እንዲያስተካክሉ የሚደረገውን የቅንጅት ትግል ለማጠናከር እንደሆነ ወ/ሮ ዙፋን ያስረዳሉ።
ሁለቱ ጋዜጠኞችም ያሰመሩበት ጉዳይ ይህንኑ ነው። ኖርዌይ የመጡበት ዋናው ምክንያት ከተለያዩ ፖለቲከኞች፣ አግባብ ካላቸው መስሪያ ቤቶችና ከዋናው ፓርላማ በመገኘት ስለ ኢትዮጵያ ማስረዳታቸውን ተናግረዋል። በርግጠኛነት ባለስልጣናቱ ያገኙትን መረጃ ለመልካም ይጠቀሙበታል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ዶ/ር ሙሉዓለም
ኢትዮጵያዊያን ባሉበትና የስደተኞች ጉዳይ በሚነሳበት ሁሉ የማይጠፉት ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም የኢትዮጵያ መንግስት ስለሚፈጽመው በደልና ግፍ ለማስረዳት ብዙ መደከሙን፣ እነሱም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ምን አይነት መንግስት እንደሆነ እንደሚያውቁ፣ መንግስትም ራሱን ሊሰውር ቢል የሚፈጽመው ተግባሩ ከግብሩ ሊሰወር እንደማያስችለው በሚያስረዳ መልኩ አስተያየት ከሰጡ በኋላ “”እነዚህን ሰዎች እኮ አቁሙ የሚላቸው የለም። የምታውቁትን ያስረዳችኋቸው ባለስልጣናትና ፖለቲከኞች ምን ምላሽ ሰጡ?” የሚል ሁሉንም የሚወክል ጥያቄ አቀረቡ።
በተደራራቢ ስብሰባና በውይይት መዳከማቸውን የገለጹት ሁለቱ ጋዜጠኞች “የኖርዌይ ባለስልጣናትና ፖለቲከኞች ያገኙትን መረጃ ለበጎ ይጠቀሙበታል የሚል እምነት አለን” በማለት መልስ ሰጥተዋል። ስለ አውሮፓና አሜሪካ ዝምታ ለተጠየቁት የመለሱት አሸባሪነትን በመዋጋት ስም ከፍተኛ ገንዝብ እንደሚገኝ በመግለጽ ነው። በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካው መልክ የተወሳሰበ በመሆኑ ኢህአዴግም ይህንኑ እንደሚጠቀምበት አመላክተዋል። አሜሪካንና እንግሊዝን ኮንነዋል።
ስለ ኢህአዴግ የስለላ መረብና በስደት ላይ በሚገኙ ወገኖች ላይ ስላሰማራቸው ጆሮ ጠቢዎች አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ አገር ቤት ያስተዋሉትንና ያላቸውን መረጃ በማጣቀስ አድማጮችን አስፈግገዋል። በካፌና ተራ መዝናኛ ቦታዎች ጆሮ ጠቢዎች እንደሚሰማሩ፣ ሰዎች ሻይ እየጠጡ የሚያወሩትን እንደሚለቅሙ፣ በመገረም ተናግረዋል። ስደተኞችን መሰለልና መቆጣጠር አደገኛ ወንጀል እንደሆነ በሃዘን ስሜት አስረድተዋል።
እስር ቤት “ግምገማ አለ” በማለት ግምገማ የምትለዋን የአማርኛ ቃል ተጠቅመው ማብራሪያ ሰጥተዋል። እስር ቤት ውስጥ ባለው ግምገማ 100 ነጥብ የሚያገኙ ይቅርታ እንደሚያገኙ፣ 10 ወይም ከዚያ በታች የሚያገኙ ደግሞ ተቃራኒው እንደሚተገበርባቸው እየሳቁ የኢህአዴግን የቆሸሸ አካሄድ ተናግረዋል።
የኖርዌይ PEN (ፔን) ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር ኤሊሳቤጥ ኤዲ “በሽርክና ላይ የተመሰረተ ፖሊሲ” ሲሉ የጠሩትን የአገራቸውንና የኢትዮጵያን ግንኙነት የገለጹት በተደጋጋሚ ኢትዮጵያ እንደሚመላለሱ መግለጽ ነው። እርሳቸውን ተከትሎ አቶ ዳዊት መሰረታዊ ጉዳዮችን አንስተው ጥያቄ የሰነዘሩ ሲሆን፣ በማዕከላዊ ምርመራ እስር ቤት ውስጥ መርማሪዎቹ እርስ በርስ የሚነጋገሩበት ቋንቋ በኢትዮጵያ ከሚነገሩት ቋንቋዎች የትኛው እንደሆነ እንዲያስረዱ ያቀረቡት ጥያቄ ፖለቲካዊ ፋይዳ ያለውና አፈናውን የሚያካሂዱትን ቡድኖች የሚያጋልጥ በመሆኑ ከስብሰባው በኋላ መነጋገሪያም ነበር። የጎልጉል ዘጋቢ ያነጋገራቸው አንድ የኖርዌይ ተወላጅ በጥያቄው መነሳት መገረማቸውን አስረድተዋል። ጥያቄው የቀረበላቸው ጋዜጠኞች ግን በተለይ ቡድን ለይተው አልመለሱም። ይሁንና በቅርቡ በሚያሳትሙት መጽሃፍ ብዙ ጉዳዮች እንደሚነሱ አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ስደተኞች ማህበር በኖርዌይ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጌዲዮን ደሳለኝ ስለ እስክንድር ነጋ አንስተው ነበር። የማህበሩ ጸሐፊ አቶ ቢኒያም በውይይቱ ላይ ከተገኙት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ፣ ሊቀመንበሯ ወ/ሮ ዙፋን በማህበራቸው ስም ከፍተኛ ምስጋና በማቅረብ ከሰብአዊ መብት መጣስ ጋር በተያያዘ ጥያቄ አንስተው ነበር።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አስቀድሞ በመታሰሩ የመገናኘት እድል እንዳላገኙ ያስረዱት ሁለቱ ጋዜጠኞች፣ ርዕዮት ዓለሙን እንዳገኙዋት፣ መነጋገር ስለማይቻል በምልክት ለመግባባት ይሞክሩ እንደነበር አስታውሰዋል። ከዚሁ ጋር አያይዘውም “እነዚህ ጋዜጠኞች የታሰሩት በመጻፋቸው ነው። የተከሰሱት ስለጻፉ ነው። ጋዜጠኞቹ ሲጽፉ ይህ እንደሚደርስባቸው ያውቁ ነበር። ሃላፊነቱን ራሳቸው ወስደው ጻፉ። አገራቸውን ስለሚወዱ፣ ሙያቸውን ስለሚያከብሩ፣ ህዝባቸውን ስለሚያፈቅሩ አደረጉት። ለነሱ ልዩ ክብር አለን” ብለዋል፡፡
“እስር ቤት እያለን አንድ ስጋት ነበረን” አሉ የስዊድን ጋዜጠኞች “ፍርሃታችን የስዊድን ጋዜጦች ስለኛ መጻፍ እንዳያቆሙ ነበር። የስዊድን ሚዲያዎች ስለኛ መጻፍ ካቆሙ እንረሳለን። መወያያ አጀንዳ የምንሆነው ካልተረሳን ብቻ ነው … ” በማለት የሚዲያን የመቀስቀስ ኃይል አጉልተው አሳይተዋል። አሁን በእስር ላይ ያሉት ጋዜጠኞች “ከመቃብር በታች ናቸው” በማለት ሁሉም ሚዲያዎች ሊረሷቸው እንደማይገባ የሚያስገነዝብ ውድ መልዕክት አስተላልፈዋል። “ነጻ ፕሬስ ከሌለ ለአገር አደጋ ነው። ነጻ ፕሬስ የሌለበት አገር አስተማማኝ መረጋጋት አይኖርም” ሲሉ የነጻ ሚዲያን አስፈላጊነት አስምረውበታል።
ጋዜጠኞቹ መጽሃፋቸውን በቅርቡ ጽፈው ለህትመት አስኪያበቁ ድረስ ዝርዝር ጉዳዮች በሚዲያ ላለመስጠት መወሰናቸው አስቀድሞ በስብሰባው አዘጋጆች በመነገሩ የሪፖርቱ አቅራቢ በዚህ ሊገደብ ችሏል። ስለሃብት ስርጭትና ሞኖፖሊ በማስረጃ ተደግፎ የቀረበውን ጥያቄ ጨምሮ ሰፊ ጉዳዮች በስብሰባው ላይ ተነስተው ነበር።
ተጋባዦቹ ጋዜጠኞች ፊትለፊት አውጥተው ባይናገሩም እስር ቤት ሆነውና፣ ኦጋዴን በአካል የታዘቡትን፣ እንዲሁም በግል ባሰባሰቡት መረጃ መሰረት በቅርቡ የሚያሳትሙት መጽሃፍ ታላቅ ዋጋ ያላቸው መረጃዎች የተካተቱበት እንደሚሆን የብዙዎች ግምት ነው። መጽሃፉ የሚታተምበት ትክክለኛ ጊዜ ባይታወቅም መጽሃፉ ከመረጃ ሰጪነቱና ኢህአዴግን ከማጋለጡ በተጨማሪ መንታ አላማ ማንገቡ የተገለጸው ሰዎቹ ከእስር እንደተፈቱ ነበር።
“በርግጥ ከእስር በመለቀቃችን እድለኞች ነን። ሆኖም ግን አዕምሯችን እረፍት አላገኘም። ምክንያቱም ብዙ ባልደረቦቻችን አሁንም እዚያው እስር ቤት ናቸው። የእስር ቤት ባልደረቦቻችን ባብዛኛው በምን ዓይነት ሁኔታ እንዳሉ ራሴን እጠይቃለሁ። እስር ቤቱ ጥሩ ስፍራ አይደለም። እንዲህ ባለ እስር ቤት ውስጥ መሞት ቀላል ነው። እኛ ከመንግስታችን ባገኘነዉ ትልቅ ድጋፍ ነጻ ወጥተናል። በርካቶች ግን አልታደሉም። ባልደረቦቻችን እዚያው ናቸው። አሁንም እዚያው ናቸው” ይህ ቃል ከእስር በተፈቱ ማግስት የተናገሩት ነው። ይህ ብቻም አይደለም በስማቸው የርዳታ ድርጅት በማቋቋም የህግ፣ የመድሃኒት፣ የእስረኞቹን ቤተሰቦች በገንዘብ ለመርዳት ቃልም ገብተው ነበር።
አትረሱ! ሚዲያ አይርሳችሁ! በሚዲያ መረሳት ሞት ነው! ነጻ ሚዲያ የሌለበት አገር አደጋ ውስጥ ነው! ነጻ ክርክርና ነጻ ሚዲያ የሌለበት አገር ሰላምና መረጋጋቱ አስተማማኝ አይደለም። ነጻ ሃሳብና ነጻ ህዝብ መፈጠር አለበት። የኢትዮጵያ ሕዝብ በታሪኩም ሆነ በማንነቱ ለነጻነት አዲስ አይደለም። በእስር ለሚማቅቁ መጮህና ደጋግሞ ያለመሰልቸት መከራከር የሚዲያዎች ሁሉ ቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል። እስረኞች ሲባሉ ደግሞ ሁሉንም ነው። በሚዲያ አትረሱ! ሚዲያ ያልደረሰላቸው ወገኖች የሚዲያ ያለህ የሚሉ ወገኖች አንደበትና ጠበቃ ከመሆን በላይ ታላቅ ስራ የለም። ብዙ የተረሱ አሉ።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened

 

federal_police08790822The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012.
The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country.
The report, which reflects extensive investigative work that Human Rights Watch undertook in collaboration with local human rights activists, was released in the beginning of February 2013. Providing heartbreaking examples, cases, and photographs, the report explains enough how dramatically the human rights crisis in Ethiopia has been worsening.
“Freedom of Expression, Association, and Assembly”
According to the report, the Anti-Terrorism Law and the Charities and Societies Proclamation (CSO Law), which criminalize independent reporting on opposition and human rights activities, have severely restricted freedom of expression, assembly, and association in Ethiopia. The report says that as a result of these two draconian laws—independent journalists, opposition politicians, human rights activists have been subjected to persistent harassment, threats, intimidation and persecution by the government authorities.
The report explains: “Ethiopia’s most important human rights groups have been compelled to dramatically scale-down operations or remove human rights activities from their man-dates, and an unknown number of organizations have closed entirely. Several of the country’s most experienced and reputable human rights activists have fled the country due to threats.”
Mentioning the Committee to Protect Journalists (CPJ), the report says that Ethiopia has now become a very dangerous country for independent journalists. This is why, the report says, “more journalists have fled Ethiopia than any other country in the world due to threats and intimidation in the last decade.”
The report, which says the Anti-Terrorism Law is misused by the government to silence opponents and repress dissent, states that only in 2012 30 journalists, political activists, and opposition party members were convicted miserably on unclear terrorism offenses under the Law. According to the report, 11 journalists in total have been convicted under the same law— since 2011.
The report explains: “On January 26, 2012, a court in Addis Ababa sentenced both deputy editor Woubshet Taye and columnist Reeyot Alemu of the now-defunct weekly Awramaba Times to 14 years in prison. On July 13, veteran journalist and blogger Eskinder Nega, who won the prestigious PEN America Freedom to Write Award in April, was sentenced to 18 years in prison along with other journalists, opposition party members, and political activists. Exiled journalists Abiye Teklemariam and Mesfin Negash were sentenced to eight years each in absentia under a provision of the Anti-Terrorism Law that has so far only been used against journalists.”
It further says: “On July 20, after the government claimed that reports by the newspaper Feteh on Muslim protests and the prime minister’s health would endanger national security, it seized the entire print run of the paper. On August 24, Feteh’s editor, Temesghen Desalegn was arrested and denied bail. He was released on August 28, and all the charges were withdrawn pending further investigation.”
The report also reveals that the government of Ethiopia is committing human rights violations in response to the ongoing Muslim protest movement in the country. It says federal police use excessive force, including beatings, to disperse peaceful protesters.
With regard to this, the report, for instance, says: “On July 13, police forcibly entered the Awalia Mosque in Addis Ababa, smashing windows and firing tear gas inside the mosque. On July 21, they forcibly broke up a sit-in at the mosque. From July 19 to 21, dozens of people were rounded up and 17 prominent leaders were held without charge for over a week. Many of the detainees complained of mistreatment in detention.”
“Extrajudicial Executions, Torture and other Abuses in Detention”
The 665 page report says that there have been so far widespread extrajudicial executions, torture and other brutal abuses in different detention centers and military barracks of the tyrannical regime in Ethiopia. It notes that Human Rights Watch has continued to document such executions and abuses.
The report explains: “An Ethiopian government-backed paramilitary force known as the “Liyu Police”, for instance, executed at least 10 men who were in their custody and killed 9 other villagers in Somali Region on March 16 and 17 in Raqda village, Gashaamo district.”
It further says: “In April, unknown gunmen attacked a commercial farm owned by the Saudi Star company in Gambella that was close to areas that had suffered a high proportion of abuses during the villagization process. In responding to the attack, Ethiopian soldiers went house to house looking for suspected perpetrators and threatening villagers to disclose the whereabouts of the ‘rebels’. The military arbitrarily arrested many young men and committed torture, rape, and other abuses against scores of villagers while attempting to extract information.”
Additionally, the report states that there is what it says “erratic access” to legal counsel and insufficient respect for other due process during custody, pre-trial detention, and even during trial phases, when the cases are politically related. “This places detainees at risk of abuse”, the report says.
“Forced Displacement”
The report notes that although the government maintain that “villagization” is a voluntary program designed to improve access to basic services by bringing scattered people all together in new villages, the reality is that the program is involuntary and mainly designed to make way for huge agriculture investments.
The report explains: “In Gambella and in the South Omo Valley, forced displacement is taking place without adequate consultation and compensation. In Gambella, Human Rights Watch found that relocations were often forced and that villagers were being moved from fertile to unfertile areas. People sent to the new villages frequently have to clear the land and build their own huts under military supervision, while the promised services (schools, clinics, water pumps) often have not been put in place.”
According to the report, indigenous peoples, amount about 200,000, are being relocated in South Omo and their land expropriated to make way for sugar plantations. It says: “Residents reported being moved by force, seeing their grazing lands flooded or ploughed up, and their access to the Omo River, essential for their survival and way of life, curtailed.”
“Key International Actors”
The report, which finally examines the response of international actors to the human rights crisis in Ethiopia, strongly criticizes donors. It says that donor countries and development agencies are failed to take into account the deteriorating human right situation and the brutality of the regime, and act responsibly.
The report explains: “The World Bank, for instance, approved a new Country Partnership Strategy in September that takes little account of the human rights or good governance principles that it and other development agencies say are essential for sustainable development. It also approved a third phase of the Protection of Basic Services program (PBS III) without triggering safeguards on involuntary resettlement and indigenous peoples.”

የስለላ ተግባርን ቀዳሚ አጀንዳ ያደረገው የወያኔ አገዛዝ የግንቦት7 ንቅናቄን መሰለሉ ተጋለጠ

 

ኢትዮጵያዊያንን አፍኖና ረግጦ አንድ ለአምስት በተሰኘ አደረጃጀት እስከቤተሰብ የወረደ የስለላ ተግባርን እየፈጸመ ያለው ዘረኛ የወያኔ አገዛዝ የግንቦት 7 ንቅናቄን መረጃ ለማግኘት ከፍተኛ የሆነ የስለላ ተግባር ሲፈጽም እንደቆየ ተቀማጭነቱ አውሮፓ የሆነ አንድ አለማቀፍ የሶፍት ዌር ኩባንያ አጋለጠ።
የወምበዴዎች ጥርቅም የሆነው የወያኔ አገዛዝ በስሩ ለዚሁ ተግባር ያቋቋመው ኢትዮ ቴሌኮም ፊን ሰፓይ በመባል የሚታወቀውን ሶፍትዌር በመጠቀም የግንቦት 7 ለፍትህ፣ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ መረጃዎችን ሲሰልል መገኘቱን ያጋለጡት ሞርጋን ማርኩዊስ ቦሪ፣ ቢል ማርዛክ ፣ ክላውዲዮ ጋርኔሪ እና ጆን ስኮት በመባል የሚታወቁ ባለሙያዎች ሬይላተን ሲትዝን ላብ በተባለ ዌብሳይት ላይ ባወጡት ጽሑፍ ነው።
እነኝሁ ባለሙያዎች ፊን ስፓይ የግንቦት 7ትን መሪዎች ፎቶግራፍ ወደ ኮምፒዩተር ተጠቃሚዎች በመላክ መረጃዎችን ለኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ለማቀበል መሞከሩን የገለጹ ሲሆን የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ኢንተለጀንስ በበኩሉ ፣ የወያኔው አፋኝ አገዛዝ ከድርጅቱ መረጃዎችን ለመውሰድ ተደጋጋሚ ሙከራ ሲያደርግ እንደነበር መረጃዎች እንዳሉት አስታውቋል።
የድርጂቱ መረጃዎች ወደ አፋኙ አገዛዝ እጅ አለመግባታቸውን ያረጋገጠው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ድርጅቱ በስልጣን ላይ ካለው ዘረኛና አፋኝ የወያኔ አገዛዝ ጋር ከፍተኛ የሳይበር ጦርነት ሲያድረግ እንደነበር ም ታውቋል።
ፊን ስፓይ ወንጀለኞችን ለመያዝ ተብሎ የፍትህና የደህንነት ሰራተኞች እንዲጠቀሙበት በሚል መነሻ የተመረተ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፣ እንደወያኔ አገዛዝ ያሉ አፋኝ መንግስታት ሶፍትዌሩን ተቃዋሚዎቻቸውን በስፋት ይጠቀሙበታል።