Monday, March 4, 2013

Fights near Awash kill 60, injure many


 Severe "ethnic and resource" fights among the Afar, Oromo and Somali ethnic groups, near the Awash River, Eastern Ethiopia, have left around sixty people dead and many injured the weekend before (Febr...uary 23-24, 2013), sources told De Birhan. The fights had also renewed over the week between the Afars and Somalis.
According to our source, so far 6 from the Somali, 18 from Afar and 36 from the Oromo ethnic groups are recorded dead due to the week long fights. Residents of the area state that they don't know who and how the clash started.
The region has been prone to clashes over resources such water and grazing land and also ethnic conflicts by pastoralists of the three ethnic groups.
Some studies, such as this one by Asknake K. Adegehe (2009), indicate that the cause of these conflicts has been the wrong federalism policy of the current regime,
The federal restructuring carried out by dismantling the old unitary structure of the country led to territorial and boundary disputes. Unlike the older federations created by the union of independent units, which among other things have stable boundaries, creating a federation through federal restructuring leads to controversies and in some cases to violent conflicts. In the Ethiopian case, violent conflicts accompany the process of intra-federal boundary making.
Similarly, De Birhan had reported that there has been an inter-ethnic clash in the Benishangul Gumz Region of Ethiopia this weekend.
By De Birhan Staffer Addis Abeba 04 March 2013
 

የሸሪያ ፍርድ ቤት” በጅጅጋ የአማራ ተወላጆችን ሰለባ አደረገ



ካለፉት አርባ ዓመታት ጀምሮ በሶማሊ ክልል በጅጅጋ ከተማ ይኖሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ቤቶቻቸውን እያስረከቡ ለጎዳና ህይወት እየተዳረጉ መሆናቸውን ኢሳት አስታወቀ።
 እስካሁን ድረስ በከተማዋ ውስጥ ዋና ዋና የንግድ ቦታዎች የነበሩዋቸው የአማራ ብሔረሰብ ተወላጆች፣ ንብረታቸውን ...ለክልሉ ተወላጆች እንዲያስረክቡ በመዳረጋቸው ብዙዎች ድርጅቶቻቸውን አስረክበው ወደ መሀል አገር ሄደዋል በማለት ኢሳት የዘገበው የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ ም ነው። ተወልደው ያደጉበትን ቦታ አንለቅም በማለት እስካሁን የቆዩትም በተለያዩ አስተዳዳራዊ ጫናዎች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ በደብዳቤ እና በቃል ተነግሯቸዋል።
በጅጅጋ ከተማ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ለኢሳት በጻፉት ደብዳቤ “የአንድ ብሄር የበላይነት በሰፈነበት መልኩ አማራ ወይም ሀበሻ የሚል መጠሪያ ተደርጎልን እነሆ ከህጻናት እስከ ትልቅ በመንገድም በቢሮም እየተሰደብንና እየተተፋብን መኖራችን ሳያንስ፣ አሁን ደግሞ ያለምንም ልዋጭ ቤታችን ተቀምቶ ጎዳና ላይ ተጥለን እንገኛለን” ብለዋል። ነዋሪዎቹ አክለውም “የእኛ ልጆች እንደልብ በመንገድ ላይ መሄድ አይችሉም፣ ሱሪ የለበሰች ሴት በፖሊስ ዱላ ትደበደባለች፣ ማን ፖሊስ ማን ሀላፊ እንደሆነ በማናውቀው ሁኔታ፣ የሸሪያ ፍርድ ቤት የሚል ተቋቁሞ ቤታችንን እንድንለቅ እያስገደደን ነው። ተወልደን ባደግንበት አገር እንደ ሁለተኛ ዜጋ እንደቆሻሻ እየታየን ነው” ብለዋል።
አንድ ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉ የከተማው ነዋሪ በክልሉ የመኖር ተስፋቸው መሟጠጡን ተናግረዋል። ኢሳት በጅጅጋ ከተማ በአማራ ተወላጆች ላይ የሚደርሰውን በደል በተደጋጋሚ መዘገቡንና መንግስትም ዝምታ መምረጡን አስታውቃል።

Sunday, March 3, 2013

Ethiopian Muslims protest: a rise of sociopolitical consciousness


by Mubarak Keder
The relationship between the Ethiopian Muslim community and the government has always been on a delicate balance reached by a compromise made by the Muslim community. For the most part, given the authoritarian rule the country is under, the Muslim community tolerated the government’s unconstitutional involvement in their religious affair and institutions. In particular, the Muslim community has, for long time, been unsettled by the government’s heavy-handed involvement in the supposedly independent Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council commonly known as Majlis. Consequently, the Majlis have been as ineffective in executing the tasks entrusted by the community. However, it was not this specific circumstance that gave way for the growing protest in the country that has been going on for more than a year.
Tension between the two start to grow when the government decided to import followers of Islamic sect from Lebanon,Ethiopian Muslims rallying all over Ethiopia known as Ahbash, on a bold and ambitious move – that disrupted the long wrestled balance between the two – to implement a Nationwide plan to introduce and impose Al Ahbash ideologies, which is completely alien to Ethiopian Muslims. Al Ahbash, is an organization based in Lebanon, formally known as Association of Islamic charitable project, which describes itself as a charitable organization promoting Islamic culture. Despite the group’s claim, some have hard time understanding the true objective of the group, one of the reasons for this being the fact that the group was in the center of the UN probe into the murder of the former Lebanese Prime Minister Rafik Hariri, following the UN inquiry naming two of its active members as key suspects.
In July 2011, the Ethiopian government has aggressively mobilized to change the country’s Muslim belief for that of ‘Ahbashism’. To this effect, it launched a nationwide training of imams and Islamic scholars in Ahbash ideologies side by side with ‘revolutionary democracy’, which is essentially an indoctrination of EPRDF’s political ideology as the only and perfect fit to govern the country. Those imams and Islamic scholars who have either refused to take part in the program or teach it in their respective mosques have been removed from their mosques otherwise arrested; mosques and Islamic institutions that turned down the government’s demand have been closed.
The Muslim community came to find out about the government’s plan before it hardly take full effect; they understood this to be a grave aggression against their constitutionally bestowed right to freedom of religion and action that farther endangered a secular form of governance, which the government have been insisting on having. So, started the protest which spread from Awolia and Anwar mosques in Addis Ababa to different part of the country, and have been growing throughout it’s more than one year period. The disorganized Muslim community started to readjust; and the first important advance they made were to form an arbitration committee of 17 Islamic leaders to negotiate with the government regarding four issues: “1) respecting the Ethiopian constitution’s guarantees of religious freedom; 2) ending government imposition of al-Ahbash on Ethiopian Muslims, while allowing al-Ahbash to operate equally with other religious communities; 3) re-opening and returning schools and mosques to their original imams and administrators; and 4) holding new elections for the EIASC, and having these elections take place in mosques, rather than in neighborhood government community centers, to ensure that the community’s selections would be honored.” as noted on the November 8, 2012 statement released by the United States commission on international religious freedom ( USCIRF).
However, the negotiation between the government and the arbitration committee failed to bring any result and the protest continued to grow in size and frequency. The same month the government arrested all 17 members of the committee along with other hundreds of protesters. Since July 13, Ethiopian police and security services have harassed, assaulted, and arbitrarily arrested hundreds of Muslims at Addis Ababa’s Awalia and Anwar mosques who were protesting government interference in religious affairs, Human Rights Watch said.
While the protest continued to gain the overwhelming support of the Muslim population, instead of dealing with the grievance of the people, the government rather got invested in campaigning to characterize the movement as a question of the few propagated by ‘extremist elements’ in the country, belittling the legitimate constitutional demand of the people. The EPRDF government attempted to justify it’s unconstitutional action as a measure that needed to be taken to eliminate terrorist cells – allegedly are trying to establish Islamic state – threatening the secular form of government. The Muslim community rejected linking the protest with terrorism as a misrepresentation of the legitimate concerns raised in a desperate attempt to scare away the support the movement is gaining. Ironically enough, the protesters demand is, for the government to uphold the laws that are entrenched in the constitution to maintain a secular state, on the contrary to that asserted by the government. This position by the protesters transcended the movement from being a theological one to that of a struggle to protect constitutional rights which the government is defying.
The statement issued by the USCIRF backed the protesters’ claim that, “Since July 2011, the Ethiopian government has sought to force a change in the sect of Islam practiced nationwide and has punished clergy and laity who have resisted.” And, when the negotiation between the committee and the government had failed in July 2011, and as the protest start to grow, “the Ethiopian government started to crack down on and intimidate the demonstrators, surrounding them with armed guards and conducting house-to-house searches.” The report further stated, “The government also has manipulated the election of the new leaders of the Ethiopia Islamic Affairs Supreme Council (EIASC). Previously viewed as an independent body, EIASC is now viewed as a government-controlled institution. The arrests, terrorism charges and takeover of EIASC signify a troubling escalation in the government’s attempts to control Ethiopia’s Muslim community and provide further evidence of a decline in religious freedom in Ethiopia.”
Regarding those people arrested during the protest the statement issued by the Amnesty international, on November 2, 2012 rebuked the government’s allegation, stating “These individuals appear to have been arrested and charged solely because they exercised their human rights to freedom of expression and to participate in a peaceful protest movement.” The report also expressed concern regarding the country’s vague anti-terrorism law and its application saying, “Since its introduction in 2009 the excessively broad Anti-Terrorism Proclamation has predominantly been used to prosecute dissenters and critics of the government, including journalists and members of political opposition parties.”
Given the level of very little, if any, freedom of expression in the country, the protest is being met with great difficulty. The people have been well aware of the risk in assembling or staging a protest. The last time the people held a demonstration, in 2005 opposing the ruling party; more than 200 people got killed. Taking this experience into account, the Muslim community was forced to come up with a way to avoid any violent incidents from happening. To this effect, instead of holding a big mass demonstration in the cities’ squares, the Muslim community have been holding the protests in separate mosques after the Friday (Jumah) prayer, where large congregation gather; and to avoid any circumstance that might give a chance for the police to turn the peaceful protest into chaos, the protesters come up with an innovative means to circumvent the challenges that are set and to get their messages across. The protesters used white and yellow placard and papers, and hold silent demonstration as a sign of peaceful intention, and as way of refuting the government’s assertion of the protest as provocative. Even though holding a mass protest in a single location might have been effective in putting the spotlight on the issues the people raised and pressuring the government for a quick measure to deal with the grievance of the community, however, with the current political environment in the country it were deemed impractical. Besides, having the protest in separate smaller group has its own perks: one of which is the fact the protest have been able to continue for more than a year, which would have been unattainable as the cost of continuing the protests would have been impossible to bear and the movement would have been long suppressed or weakened shortly. The most important thing for the community have been to keep the movement alive until their questions are being answered, fortunately enough for the community, the weekly Friday prayer offered convenient enough platform to attain this objective. The people were also able to overcome the challenge of weak communication infrastructure and managed to unify their voices. Most importantly of all, the protesters have been able to keep an impeccable record of staying peaceful, despite the provocation, depriving the government any opportunity to misconstrued the movement as a violent one and easily squash it.
Throughout the protest, the other main challenge the movement faced has been the apparent absence of free press, which left protesters to be a victim of smear campaign by the state media and no independent media outlet to have an independent investigation and coverage of events. While the EPRDF government used the state media as a propaganda tool to portray the protest as violent, terrorist-related and orchestrated by the few, it has been as much invested in cracking down the few independent newspapers for covering the protest. Journalists who published article regarding the protest were imprisoned on charges of treason and incitement to violence; police, even, raided the printing company which published the newspapers. “Ethiopia has reached a high level of harassment of the press by attempting to censor coverage of the protests,” said CPJ(committee to protect journalists) East Africa Consultant Tom Rhodes.
International human rights and other related organization have been fast to condemn the government’s action and call for a rapid judicial process. While the idea of bringing those arrested swiftly to judicial authorities and have a due process is sound and reasonable, one important fact that is being overlooked is the apparent absence of the rule of law and independent judiciary in the country. In spite of what is stated in the constitution there is no practical distinction between the executive and judicial branch of government on the ground, making it impossible for the people to see the obscure line that differentiate being charged of a crime to that of being convicted of one. One manifestation of this is the ‘documentary’ that aired on February 6, 2013 on the state controlled Ethiopian Television, which basically,’ investigated ‘ the allegation , ‘charged’ those suspected and ‘convicted’ them of a crime, all these while court hearing is far from being half way, and throwing the basic principle of ‘innocent till proven guilty’ to the side.
while the mark the movement will have on the history of the country is something to be seen, the course the protest will take and the roll it will play in the sociopolitical sphere will largely depend on the level of sociopolitical consciousness the society possess, by which the people in general, stand to defend the common principles regardless of the groups being involved. This level of consciousness by which the general public is well informed about their country’s affair and, as much importantly, are actively involved in dictating and further safeguarding the principles and values they want their country to be governed a complex development to bring given the current sociopolitical structure in the country. However, the unprecedented persistency and solidarity the people that have been exhibited by this movement for more than one year just might be an indication to the changing course.

Saturday, March 2, 2013

የስዑዲ ማስጠንቀቂያና የኢትዮጵያ ምላሽ

    
ሰሞኑን አንድ ከፍተኛ የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣን ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ የተነሳ በግብጽና በሱዳን የአባይ ወንዝ አጠቃቀም መብት ላይ አደጋ እየጣለች ነው ማለታቸውን ሱዳን ትሪብዩን የተሰኘው ድረ ገጽ ዘግቧል። ባለስልጣኑ የተናገሩት የሳውዲ አረቢያ መንግስት
አቋም መሆን አለመሆኑን አጣርቶ የኢትዮጵያ መንግስት ሰሞኑን መግለጫ እንደሚያወጣ ተዘግቧል። ሱዳን ትሪብዩን የተሰኘው ድረ ገጽ ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ምክትል የመከላከያ ምክትል ሚኒስትር ካሊድ ቢን ሱልታን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለው ፕሮጀክት፣ ግብጽና ሱዳን በወንዙ ላይ ያለቸውን መብት አደጋ ላይ እንደሚጥል መናገራቸው ተሰምቷል። ከሱዳን ድንበር 12 ኪሎሜትር ርቆ እየተሰራ ያለው የህዳሴ ግድብ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ይልቅ ለፖሊቲካ አሻጥር የሚያገለግል ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃለ አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የተባለው ዜና የሳውዲ አረቢያ መንግስት አቋም መሆኑን አጣርቶ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ መግለጫ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፣
ይህ በሰባ አራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር በመሰራት ላይ ያለው ግዙፍ የግድብ ፕሮጀክት ተፋጥኖ እየጨመረ ያለውን የኢትዮጵያን ህዝብ ለመመገብና በተደጋጋሚ የሚከሰተውን የምግብ እጥረት ለመቋቋም እንደሚረዳ የኢትዮጵያ መንግስት ይናገራል።
ኢትዮጵያና ሳውዲ አረቢያ ጥሩ የኦኮኖሚ ትስስር ያላቸው ሀገራት ናቸው። በርካታ የሳውዲ አረቢያ ባለጸጋዎች መዋለ ነዋያቸውን በኢትዮጵያ ውስጥ ያፈሳሉ። ታዋቂው የኢትዮጵያ ባለሐብት ሼ ሞሐመድ አል-አህሙዲም የሳውዲ አረቢያ ዜግነት አላቸው።

ኢትዮጵያ በአብዛኛው ለቤት ውስጥ ሥራዎች ብዙ ሰራተኞችን በየዓመቱ ወደ ሳውዲ አረቢያ ትልካለች። የምክትል መከላከያ ሚኒስትር ካሊድ ቢን ሱልጣን መግለጫ ኢትዮጵያ ከሳውዲ አረቢያ ጋር ካላት ከዚህ ትስስር ጋር የማይሄድ ነው ይላሉ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤

በግብጽ የፕሬዞዳንት ሙርሲ መንግስት ስልጣን ላይ ከወጣ ወዲህ በሳውዲ አረቢያና ግብጽ ግንኙነት እያደገ መምጣቱ ይነገራል። የብሪታኒያውያኑ የፖሊቲካ ጥናት ተቋም ቻተም ሃውስ የአፍሪቃ ቀንድ የፖሊቲካ አዋቂ ጃተም ሞስሊ እንዳሉት የሳውዲ አረቢያ መንግስት የአባይ ወንዝ ጉዳይ አይመለከተውም ማለት ይከብዳል፤


«የግብጽ የውሃ ጉዳይ ለግብጽ ብሔራዊ ጸጥታ በጣም አስፈላጊ ነው። የአሁኑ የግብጽ መንግስት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ግብጽና ሳውዲ አረቢያ ግንኙነታቸውን አሳድገዋል። ግብጽ ለሳውድ አረብያ ቅርብ ሀገር ናት። ስለዚህ በግልጽ እንዲህ ነው ባይባልም፣ በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ የሳውድ አረቢያ ፍላጎት የለበትም ማለት አይቻልም።»

ግብጽ የአረቡን አቢዮት ተከትሎ በተከሰተው የውስጥ አለመረጋጋት ምክንያት በምስራቅ አፍሪቃ ያላት የፖሊቲካ ተጽዕኖ ቀንሷል። ሱዳንም የደቡብ ሱዳንና የዳርፉር ችግሮች ፊቷን ከአከባቢው ፖሊቲካ እንድታርቅ አድርጓታል። በሌላ ኢትዮጵያም የአባይ ወንዝ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም በብርቱ እየገፋች ነው።
በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ ንትርክ ከተጀመረ ከሃምሳ ዓመታት በላይ ሆኖታል። ግብጽ የአባይ ወንዝ አጠቃቀምን በተመለከተ እአአ በ1929 የተፈረመው የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ትፈልጋለች።


ኢትዮጵያና የላይኛው አባይ ተፋሰስ ሀገራት ግን ሁሉን ተጠቃሚ የሚያደርግ ስምንነት እንዲፈረም ይሻሉ። እአአ በ2010 ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች አራት የአባይ ተፋሰስ ሀገራት በአባይን ውሃ ክፍፍል ላይ በዩጋንሳ ኢንቴቤ ከስምምነት ደርሰዋል። ከአንድ ዓመት በኋላም ጎራውን ተቀላቅላለች።

Friday, March 1, 2013

በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ሲሆን ፣ የወያኔ ካድሬዎችም ድርጊቱን ለማስቆም የተጠናከረ አሰሳ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።


በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ሲሆን ፣ የወያኔ ካድሬዎችም ድርጊቱን ለማስቆም የተጠናከረ አሰሳ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለው የሕዝብ መነሳሳት ስሜትና ተጋድሎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከለውጥ ፈላጊው ሕዝብ ጎን የቆመ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያቶች በጠላት ላይ በሚያደርሰው ጥቃት የሀገርና የወገን ደራሽነቱን ያስመሰከረ ሲሆን፣ ከወታደራዊ ትግሉ ጎን ለጎን የአካባቢውን ህብረተሰብ የማስተማር፣ የመቀስቀስ፣ የማደራጀትና የማስታጠቅ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገለፀ።
በሰሜን ጎንደር መተማና አካባቢው በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኛች ግንባር ደጋፊዎች አማካኝነት የድርጅቱ ወቅታዊ የሀገር አድን ጥሪ በራሪ ወረቀት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ በመገኘቱ ስጋት የገባው አሸባሪው የወያኔ ገዥ ቡድን የቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ ወከባና እንግልት እያደረሰ እንደሚገኝ ከስፍራው የደረሰን የመረጃ ምንጭ ያስረዳል።
በመላ ሀገሪቱ እየታየ ያለው የሕዝብ መነሳሳት ስሜት በተደራጀ መልኩ እንዲቀጥልና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀጣጠለ የመጣው ሕዝባዊ ተቃውሞ ለፍሬ ይበቃ ዘንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ተነስ! ታጠቅ! ዝመት! የሚለውን ወቅታዊ የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት በሃገሪቱ በተለያዩ ከተሞች በብዛት እንዲሰራጩ በድርጅቱ ደጋፊ አባሎች አማካኝነት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረግን ሲሆን ይህ የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀትም በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነትን ከማግኘቱም በተጨማሪ ለስርዓት ለውጥ በሚደረገው የትጥቅ ትግል መላውን ህብረተሰብም መነሳሳትን እንደፈጠ...ረለትና የተጀመረውም ሕዝባዊ አመፅ ግፊቱ እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ዘገባው ጨምሮ ገልጿል።
በመተማና አካባቢው እየተሰራጨ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት ዋና አላማ የኢትዮጵያ ሕዝብ በወያኔ ላይ ያለው ጥላቻ ግልፅ ማድረግ ቢሆንም ሕዝብ እንደ ሕዝብ እጅ ለእጅ በመያያዝና በመደጋገፍ በአምባገነኑና አሸባሪው ገዥ ቡድን አፋኝና ቀፍዳጅ ስርዓት ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር መነሳት፣ መታጠቅና መዝመት የወቅቱ አንገብጋቢ ጉዳይ በመሆኑ ህብረተሰቡ የጀመረውን ሕዝባዊ ተቃውሞ አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ የታለመ ሲሆን በዚህ የተደናገጠው ወያኔና ተላላኪዎቹ በአካባቢው ነዋሪ ህብረተሰብ ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር የቤት ለቤት አሰሳ በማድረግ ህብረተሰቡን በማስፈራራትና በማዋከብ ስራ ላይ ተጠምደው እንደሚገኙ ከስፍራው የደረሰን የመረጃ ምንጭ ያስረዳል።
አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳትና ተጨባጭ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ ህብረተሰቡን ለበለጠ የፀረ- ወያኔ የሚያነሳሱ በራሪ ወረቀቶችን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በሰፊው በማሰራጨት ትግሉ የደረሰበትን የእድገት አቅጣጫ እንዲሁም አናሳው የወያኔ ቡድን በሕዝብና በሃገር ላይ እየፈፀመ ያለውን ስውር ደባ በማጋለጥ ክፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ገልፀው፣ የጀመሩትን ፀረ- ወያኔ አመፅና ተቃዎሞ አጠናክረው እንደሚገፉበትና የድርጅቱን ወቅታዊና የሀገር አድን የትግል ጥሪ በራሪ ወረቀት በተለያዩ ቦታዎች በሰፊው የሚሰራጭበትን ስልት ቀይሰው እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም ጨምረው ገልፀዋል።
 
    ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

Thursday, February 28, 2013

BREAKING NEWS: TPLF Appointed Abune Matias of Tigre as the 6th Patiarch of EOTC

     
The Horn Times Breaking News 28 February 2013
by Getahune Bekele- South Africa

*Call for mass action reverberates across the globe

In a move expected to create more tensions and divisions, Ethiopia’s ruling minority junta has appointed yet another
Abbay Tsehaye installed 6th patriarch of the Ethiopian Orthodox Church, Aba Matias.
Abbay Tsehaye installed 6th patriarch of the Ethiopian Orthodox Church, Aba Matias. (Photo: from Facebook)
divisive figure as the 6th patriarch of the Ethiopian Orthodox Church – Abune Matias, otherwise known as the chief Rabbi of Tigraye republic.
The late Abune Pawlos’s chosen successor and the favorite of the ruling TPLF junta, Aba Matias was elected on Friday 28 Feb 2013 after Bishops of the illegal pro-TPLF synod in Addis Ababa voted for him under the watchful eyes of warlord Abbay Tsehaye.
Recently denounced and condemned for walking in public with Tigray republic’s self appointed grand Mufti sheik Elias Redman to show his support for the government’s crack down on current Muslim uprising in Ethiopia, Aba Matias is expected to be banned from entering some monasteries and Churches due to his controversial election against the divine cannon of the fathers by an illegally assembled unholy synod just like his predecessor the late Aba Pawlos.
According to the Horn Times reporters in Addis Ababa, Aba Matias received a whopping 500 votes out of 806 available while non-Tigre Bishops like Abune Yosefe got less than 100 votes in the stage managed scandalous election organized by habitual election thieves, the TPLF warlords.
Hastily recalled from the Holy city of Jerusalem by the TPLF and ordered to stand election amid controversy concerning his citizenship, Aba Matias will face enraged Ethiopians in the coming days.

የሳጅን ዘመድኩን ዛቻ እና ትርጉሙ

የሳጅን ዘመድኩን ዛቻ እና ትርጉሙ
February 28, 2013 | Filed underG7 Editorial,Slider Post | Posted by admin
ባለፉት ሳምንታት በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፈለ ከተማዎች የወያኔ መንግስት ፓሊሶችና ደህንነቶች በሙስሊሙ ወገኖቻችን መኖሪያ ቤቶች በመዘዋወር ዝርፊያ የተቀላቀለበት አሸባሪ ብርበራና ፍተሻ ሲያካሄዱ ሰንብተዋል። ይህ ብርበራ በአይነቱ ፍጹም ከሆነ የወሮባላ ተግባር የተለየ እንዳልሆነ የደረሰባቸው፣ ያዩና የሰሙ ሁሉ የሚመሰክሩት ነው።

የፍርድ ቤት ትእዛዝ ለይስሙላ እንኳን ያልያዙ ጭንብል ያጠለቁ ፓሊሶችና ደህነነቶች ጨለማን ተገን በማድረግ በር እየበረገዱ በመግባት ቅዱሳን መጸሃፍትን፣ ሞባይልን፣ ቴሌፎኖን እና ወርቅ በግፍ መዘረፋቸውን ሰለባዎቹ አረጋግጠዋል። ይህ በእነዚህ ንጹሃን ሙስሊም ወገኖች ላይ ከተፈጸመው ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ማስደንገጫ ተጨማሪ መሆኑ ነው።
...
የእነዚህን አሳዛኝ ግፈኛ ተግባር የሰማው የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዜናውን በየካቲት 14 ቀን 2005 አ.ም ምሽት ዘግቦ ነበር። በዚህ ዘገባ ላይ የቪ.ኦ.ኤው ጋዜጠኛ የሰለባዎቹን ምስክርነትና አስተያየት ብቻ ማቅረብ ተገቢ ያልመሰለው ፕሮፌሽናሉ ጋዜጠኛ፣ ሚዛናዊ ዘገባ ለማቅረብ ድርጊቱ ተፈጸመባቸው ወደተባሉት ክፍለ ከተማዎች የፓሊስ አዛዦች መደወል ነበረበት። ይኼኔ ነበር ጋዜጠኛው ሳጅን ዘመድኩንን ያገኘው። ይህን የመንግስት ወንጀል እንዲያስተባብሉ እድል የተሰጣቸው ሳጅን ዘመድኩን የሰጡት መልስ ሰዋዊ ሳይሆን አውሬያአዊ ነው ማለት ይቻላል።

የተሰራውን ግፍ መዘገቡ ያናደዳቸው የፖሊስ አዛዦች ጭራሹኑ ጋዜጠኛውን ራሱን አሁን መጥቼ አስርሃለሁ የሚል መልስ ነበር የሰጡት። እብሪተኛው ሳጅን ጋዜጠኛው እንኳን ዋሽንግተን መንግስተ ሰማያትም ገብቶ እንደማያመልጠው ካዛቱ በኋላ ቃለ ምልልሱ አለቀ።

ይህን ቃለ ምልልስና የሳጅን ዘመድኩን ዛቻ ስንሰማ ቅጽበታዊ ምላሻችን ሳቅና መገረም ሊሆን ይችላል። ከዚህ የደንቆሮ ሃሳብ ከሚመስል አስቂኝና አስገራሚ አነጋገር በስተጀርባ ግን በእጅጉ የሚያሳዝን፣ የሚያስለቅስና የሚያስቆጭ ትርጉም አለው። የሳጅን ዘመድኩን ጥያቄ አመላለስ የልዩ አጋጣሚ ጉዳይ (Isolated Event) አይደለም። እንደዚያ ከመሰለን ክፉኛ ተሳስተናል። በሳጅን አንደበት የሰማነው አውሬ ወይም የህወሃት ድምጽ ህዝባችን በእየለቱ ቁም ስቅሉን የሚያሳየውን የወያኔ የየእለቱን ዘረኛ ቋንቋ እና ተግባር ነው። ሳጅን ዘመድኩን የተናገረው የሰለጠነበትንና ወያኔ የወሰነውን ነው በእሱ ልሳን የሚናገረው።

ወያኔዎች የፈለገንን አድርገን አዋርደን እንገዛችኋለን፤ ምን አባታችሁ ትሆናላችሁ ነው የሚሉን በወያኔኛ ቋንቋ። ሳጅን ዘመድኩን እንደምንገምተው ደንቆሮ አይደለም። ወያኔ ውስጥ ያደገ ወያኔኛ የተማረና የሰለጠነ፣ ሁሉንም ጣቢያዎች ከሚያዙት ሰዎች አንዱ ነው። ትእዛዝ ፈጻሚ ወያኔ ነው። ህዝብ ደሞዝ የሚከፍለው የህዝብ ተቀጣሪ ነኝ ብሎ አያምንም። እንደሁሉም ወያኔዎች እየዘረፈ የሚኖር ሽፍታ ነው። ህግና ህገ-መንግስት ለጌጥ የተቀመጠ መሆኑን ወያኔዎች ሁሉ ያውቃሉ። ተናግረውታልም።

በሳጅን ዘመድኩን አራዊታዊ አነጋገር ስቀን ከሆነ የሳቅነው በራሳችንና በህዝባችን ሰቆቃ ነው። በራሳችን ውርደት ለመሳለቅ አይተናነስም።ሀገራችን በእንደ እነ ሳጅን ዘመድኩን ያሉ ሰዎች ነው የምትመራው። ትልቅ ውርደት ላይ ነን። ሀገራችን ከውረደት፣ ህዝባችንን ከሰቆቃ የማዳን ግዜው አሁን ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡- ምርጫችን ሁለት ነው። ወይ “ኑሮ ካሉት መቃብርም ይሞቃል እያልን የቁም ሞት ኑሮአችንን መኖር” አሊያም ወያኔን አስገድደንም ሆነ አስወግደን የሚገባንን የኩሩ ህዝብና ሀገር ስብእናችንን ማስመለስ እና ሀገርን ከማዳን ከሞራላዊ ግዴታ ተጠያቂነት ነጻ የመሆን።

እንዳንሳሳት! የሳጅን ዘመድኩን አራዊታዊና እብሪታዊ ቋንቋ ወያኔያው የእለት ተእለት ዘይቤ ነው። ስለዚህ ጀንበር ቁልቁል ሳትጠልቅብን ወያኔን አስገድዶ ለመጣል ከሚንቀሳቀሰው ህዝባዊ ሃይል ጋር በመሆን የመታገያ ጊዜው አሁን ነው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ጅሃዳዊ ሃራካት’’ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ባለስልጣናት ሊከሰሱ ነው::


Hailemariam_Desalegn_Ethiopiaጠ/ሚ ኃ/ማርያምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት
ባለስልጣናት ሊከሰሱ ነው
*ኢቴቪና ፌዴራል ፖሊስም ይከሰሳሉ
በዘሪሁን ሙሉጌታ ሰንደቅ ጋዜጣ


በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በቅርቡ ከተላለፈው ‘‘ጅሃዳዊ ሃራካት’’ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ባለስልጣናት ላይ የወንጀልና የፍትሃብሔር ክስ ሊመሰረት ነው። ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ባሻገር በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) እና በፌዴራል ፖሊስ ተመሳሳይ ክስ ይመሰረትባቸዋል።
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናቱ እና የተጠቀሱት ተቋማት ላይ ክስ የሚመሰረተው ሰሞኑን ‘‘ጃሃዳዊ ሃራካት’’ በሚል በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ደርጅት የቀረበው ዘጋቢ ፊልም በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በሕግ ጥላ ስር ያሉትን ተጠርጣሪዎች መብት ሲጣስ መከላከል ባለመቻላቸው፣ ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀማቸው፣ በሕዝብ ሐብት ያለአግባብ በመገልገላቸው፣ የተሰጣቸውን የሕዝብ አደራ ባለመወጣታቸውና በሃይማኖት ጣልቃ በመግባታቸው የወንጀልና የፍትሐብሔር ክስ ይመሰረትባቸዋል። ክሱን የሚመሰርቱት በአሁኑ ወቅት በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ ባሉት ተጠርጣሪዎች ጠበቆች አማካኝነት ሲሆን ክሱም በሁለት ደረጃ ተከፍሎ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል።
ክሱን እያዘጋጁ ከሚገኙት ጠበቆች አንዱ የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ክሱን በማስመልከት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በመንግስት ባለስልጣናት ላይ የሚመሰረተው ክስ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይቀርባል ብለዋል። በኢቲቪ ላይ የሚመሰረተው የፕሬስ ክስ ቀጥታ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን ክሱም ከሞራል ጉዳት ጋር እንደሚያያዝ ጠበቃው አስታውቀዋል።
‘‘መጀመሪያ ክርክራችን ዘጋቢ ፊልሙ እንዳይተላለፍ ነበር። ከተላለፈ በኋላ ግን ይግባኝ ማለት ሳይጠበቅብን ይሄንን ጉዳት ባደረሱ አካላት ማለትም ፊልሙን በሰሩት፣ ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች ጨማምረን ክሱ እንመሰርታለን’’ ያሉት ጠበቃ ተማም በፕሬስ ህጉ መሰረትም ዘጋቢ ፊልሙ በተላለፈ በሦስት ወራት ውስጥ ክስ መመስረት እንደሚያስችልም አያይዘው ገልፀዋል።
በኢቲቪ በተላለፈው ዘጋቢ ፊልም ላይ በሚመሰረተው ክስ እስከ 100ሺህ ብር የሞራል ካሳ እንደሚጠየቅ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ክስ ደግሞ በሌላ መዝገብ በፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በሚመሰረተው ክስ ለደንበኞቻችን የሞራል ካሳ እንዲካሱ፣ ደንበኞቻችን ይቅርታ እንዲጠየቁ፣ በተመሳሳይ የአየር ጊዜ ተሰጥቷቸው ደንበኞቻችን የራሳቸውን ኀሳብ እንዲሰጡ፣ በሃይማኖት ውስጥ በተደረገ ጣልቃ ገብነት ለደረሰው ጉዳት ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚያደርግ ክስ ነው ብለዋል።
‘‘ክሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የማያካትትበት ምክንያት የለም። የሀገሪቱ መሪ እሳቸው ናቸው። ፖሊስም እያደረገ ላለው ነገር ለምሳሌ ተጠርጣሪዎችን ቶርች በማድረግ ጭምር እንከሳለን። የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዘጋቢ ፊልሙ ያግዱ፣ አያግዱ የሚለውን አጣርተን የሚመለከታቸውን አካላት ለይተን ክሱን ለመመስረት ተዘጋጅተናል። ክሱን ለማዘጋጀት አስፈላጊ መረጃዎችን እየሰበሰብን ነው። በቅርቡም ክሱን እንመሰርታለን’’ ሲሉ ጠበቃ ተማም ጨምረው ገልፀዋል።
ደንበኞቻችን እራሳቸውን በማይከላከሉበት ሁኔታ ታስረው፣ መልስ እንዲሰጡ ባልተደረገበት ሁኔታ ስማቸው እንዲጠፋ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን የጠቀሱት ጠበቃው ዘጋቢ ፊልሙ የደንበኞቻችንን መልካም ባህሪ የገደለ (Character assination) ነው ብለዋል።
መንግስት በሽብርተኝነትና ከህገ-መንግስቱ በተቃራኒ ሃይማኖታዊ መንግስት ለማቋቋም ሲያሴሩ አግኝቻቸዋለሁ፤ በሶማሊያ ከሚንቀሳቀሰውና ከአለም አቀፍ አሸባሪ ቡድን አልቃይዳ ጋር ከሚንቀሳቀሰው አል-ሻባብ ጋር ተመሳጥረው ሲሰሩ አግኝቻቸዋለሁ ባላቸው ተጠርጣሪዎች ላይ ዘጋቢ ፊልም ማቅረቡ ይታወሳል።
ፊልሙ ከመተላለፉ በፊት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የእግድ ትእዛዝ ቢያስተላልፍም ፊልሙ ለሕዝብ አይታ መቅረቡ አይዘነጋም፤ ፊልሙ ለተመልካቾች ከቀረበ በኋላም አነጋጋሪ ሁኔታ መፈጠሩም ይታወቃል።n
ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ

Wednesday, February 27, 2013

ጀርመን ራዲዮ እና የወያኔ ሴራ በፈስ ቡክ ኢትዮጵያውያን ላይ

 



ጀርመን ራዲዮ እና የወያኔ ሴራ በፈስ ቡክ ኢትዮጵያውያን ላይ


በሃገራችን ታሪክ ታይቶ እና ተከስቶ የማያውቅ የሽፍቶች አሸባሪ መንግስት በተለያየ ስልት ኢትዮጵያውያንን መከራቸውን እያሳየ ይገኛል:: ይህ ወንበዴ መንግስት ማፊያዊ ስልቶችን በመጠቀም የተለያዩ ሽብሮችን እየፈጸመ ነው:; መውደቂያው የደረሰው እና በቋፍ ላይ ያለው ይህ መንግስት ስለ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የሚያስቡ ሰዎችን የሚዋጋበት ስልቱ የህዝብ ንብረት እና ገንዘብ በመጠቀም ስልጣኑን ላለማጣት እየተራወጠ ይገኛል::ይህንንም ለመዋጋት ድፍን ኢትዮጵያዊ ዘር ሃይማኖት ቀለም ወ.ዘ.ተ. ሳይለይ በአሁን ሰአት በጋር ድምጻችን ይሰማ እያለ ለመብቱ እና ለነጻነቱ እየታገለ ነው:: ይህንን ትግል ለማኮላሸት ሴራ ከሸረቡት አንዱ ከዚህ አሸባሪ መንግስት ጋር በማበር እየሰራ የሚገኘው የጀርመን ድምጽ አንዱ ነው ::

ይህ የራዲዮ ጣቢያ ከቀድሞው ጀምሮ ከወያኔ ጋር በመመሳጠር በኢትዮጵያ እና በዜጎችዋ ላይ የምእራባውያኑን ጥቅም ሲያራምድ ቆይቷል:: ምእራብያውያኑ በተለይ ጀርመን አጋርዋ የሆነው አሸባሪ የማፊያ ቡድን እንዳይቐየማት እና አስልፎ የሚሸጥላት የኢትዮጵያውያንን ጥቅም በማግበስበስ ለብሄራዊ ጥቅሟ ስትል የሃገሪቱ ህዝቦች ድምጽ እንዳይሰማ የህን የራዲዮ ጣቢያ እየተጠቀመች ነው::

ከዚህ በዘለለ በኢትዮጵያ አንጡረ ሃብት የተማሩ ያደጉ የት እንደደረሱ እንኩዋን ራሳቸውን የላዩ የራዲዮው ጋዜጠኞች የእናት ጡት ነካሾች ኢትዮጵያዊ የሚል ዜግነታቸውን አስረክበው ጀርመን የሚል ዜግነትን በመጎናጸፍ/ለነሱ ይመስላቸዋል/ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ እጅ አዙር ወያኔያዊ ዘመቻ ከፍተዋል::

ይህንን ዘመቻቸውን የከፈቱት በሃገራቸው መኖር መናገር መስራት በተከለከሉ ዜጎች ላይ ነው:: ይህ ደሞ እጅግ አስቀያሚ ምግባር እና ወያኔያዊ ሃራካት መሆኑን እንገነዘባለን::ወያኔ በምትሰጣቸው ጉርሻ የሚፎልሉብን እነማሙሽ ስብሃቱ ዛሬም ወሬያቸውን ይዘው እንደውሻ መጮህ ጀምረዋል::
በዚህም መሰረት አድርገው የወያኔ ተሊኮዋቸን በማማሰል ፌስቡክ በአሸባሪ እና በወንጀለኛ የተሞላ ነው እያሉን ነው ይህን እኛ ኢትዮጵያውያን በነዚህ ሰዎች ላይ ዘመቻ እንድናደርግ አስገድዶናል:: እንደዚህ አይነት ጩኸታቸውን የጀመሩት ወያኔ ከተዋረደበት የሳኡዲ አረቢያ የቦንድ ስብሰባ ጊዝይ በሁዋላ ነው ::ከዛ ቀደም ብሎ የሚሰሩትም ስራ ለማንም ኢትዮጵያዊ አይጥመውም የቦንድ ሽያጭ ስብሰባ የኢትዮጵያውያን ተቃውሞ በራዲዮናቸው ላለመናገር ሲዘባበቱ ነር ይባስ ብለው ወኪላቻው በዛ ምሽት ከወያኔ ዲፕሎማቶች ጋር ሲያሽካካ እንደነበር በሳኡዲ የሚገኘው የወጣቶች ማህበር ጠቁሟል:; ዛረ ይህንኑ የተመሸጉበት የወያኔ ምሽግ ለምን ተደፈረ ሊናድ ነውን ባማለት ፌስቡክ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ኢላማ አድርገው ተነስተዋል::

በፈስ ቡክ ያሉ እትዮጵያውያንን ለመታገል እነዚህ የወያኔ ጀሌዎች እኛ ታዋቂ ነን የእከሌ ወንድም ነን እኛ ኦዲየንስ አለን በሚሉ...አነጋገሮች በመኮፈስ የተለያዩ መላምቶችን በመሰንዘር እየተራወጡ ሲገኙ የተለያዩ የፈስቡክ አካውንቶችን ለማዘጋት ሪፖርት እያደርጉ ነው ለዚህም የሚጠቀሙበት አሸባሪ እና ወንጀለኛ የሚል የወያኔ ቋንቋ ነው::አሸባሪነትን ለመከላከል እየሰራን ነው የሚል ፕሮፖዛል ለነጭ አለቆቻቸው እስከማቅረብ ደርሰዋል::

እለት እለት እየተጠናከረ በመጣው አፈና ምክንያት ፌስቡክን እንደመተንፈሻ እና መንግስትን ለመታገል እንደዋነኛ መደራጃ እያገለገለ እንደሚገኝ ግልፅ ነው ታዲያ ሁሉንም ነገር ካላፈኑ እንቅልፍ የማይወስዳቸው ወያኔዎች የፌስቡክ ነገር ከቁጥጥራቸው እንደወጣ ስለተገነዘቡ ፌስቡክ የሚፈጠሩ ግሩፖቹን፥ገፆችንና የግለሰብ ፕሮፋየሎችን እየተከታተሉ ከመዝጋት ባሻገር ፀረ-ፌስቡክ የሆነ ዘመቻ ከጀመሩ ውለው አድረዋል እስከአሁን ፀረ-ፌስቡክ የሆኑ
የፕሮፓጋንዳ ስራዎች በኢቲቪ፥ በሪፓርተር እና በዛሚ ኤ.ኤፍ.ኤም ጀርመን ራዲዮ ቀርበዋል።ከሆድ አሳዳሪዎቹ ጋር እንዘጭ እንዘጭ ያበዛው የጀርመን ራዲዮው ማንተጋፍቶት ስለሺ (ማሙሽ ስብሃቱ) በወያኔ እየተካሄደ ያለው ፀረ-ፌስቡክ ዘመቻ እራሱን አካል ስለአደረገ ይመስለኛል ከመስመር በወጣ መልኩ ፌስቡክና ፌስቡካውያንን በአንድ ከረጢት አጭቆ የዘለፈው።

ሶስተኛው ዙር የአፈና እና የስለላ መምሪያ ንድፍ/እቅድ

 





በፈረንጆቹ አዲስ አመት ተከትሎ ወያኔ ያቋቋመው የአፈና እና የስለላ መዋቅር በደረረሰን መረጃ መሰረት ባለሃብት ናቸው የሚባሉ ሙስሊሞችን ለመጉዳት...የቤት ለቤት አሰሳ እና ፍተሻ እንደሚያካሂድ እንዲሁም ወደ ኢንተርኔት ካፌዎች ሊዘምት እቅድ እንደነደፈ የምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮች መረጃ መስጠታቸውን ተከትሎ ይኅን ጉዳይ ብሎግ ያደረግንበት ድህረገጻችን እትዮጵያ ዉስጥ ለ2ኛ ጊዜ ታግዶ ይገኛል::

የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምኒሊክ ሳልሳዊ ባደረሱት መረጃ መሰረት የስለላ እና የአፈና መምሪያው ከብሄራዊ መረጀ እና ደህንነት መምሪያ ጋር በመሆን አዲስ ሚስጥራዊ ያሉትን የአፈና ስልት ነድፈው በይፋ ለመጀመር ቅድመዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተደርሶበታል::
በዚሁ መሰረት 3ኛው ዙር የአፈና እና የስለላ እቅድ የሞባይል ጠለፋ እና ሰበብ በመፍተር ሙስሊም ወጣቶችን ከመንገድ ላይ አፍኖ የመውሰድ ሴራ ነድፈዋል:: ያሉት የምኒሊክ ሳልሳዊ ምንጮች ይህንን እቅድ ተከትሎ በሙስሊም ስሞች ተመዝግበው የሚገኙ ሲም ካርዶችን የባለቤቶቹን ስም እና አድራሻ በዝርዝር እንዲሰጠው በአቶ ደብረጺሆን በኩል ለቴሌ ምስጢራዊ ያሉት እነሱ ትእዛዝ የተላለፈ ሲሆን እያንዳንዱ የስልክ ግንኙነት እንዲመረመር ሲነገራቸው እንዲሁም የተቃዋሚ ሃይሎች እና ለቤተክርስቲያን ቅርብ ናቸው ተብለው በተቃዋሚነት የተፈረጁ ግለሰቦች የዚህ አፈና ኢላማ ናቸው::

ሌላኛው በንኡስ አንቀጽ የተቀመጠው በትምህርት በስለዋል የሚባሉ ሙስሊም ወጣቶችን እና የማህበረቅዱሳን `አማፂ` የተባሉ እንዲሁን የራእይ ወጣቶች ማህበር አባላትን ኢላማ አድርጎ ከመንገድ በሰባብ አስባቡ አፍኖ መውሰድ ሲሆን ይህም በብዛት የሚአተኩረው ፈረንሳይ ለጋሲዎንን መነሻ አድርጎ እስከ ጉለሌ እና ላፍቶ ድረስ ሊሰራ የታሰበ ሲሆን በመሃል ከተማ አከባቢ ጨለማን ተገን በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል::ሲሉ የምኒሊክ ሳልሳዊ ምንጮች ተናግረዋል::
ስለዚህ በሰፊው ማብራሪያው ደርሶን መርጃውን እስከምንሰጣቹህ ድረስ ይህንን መሰረታዊ መረጃ ተመርኩዛችሁ ቤያንዳንዱ እንቅስቃሴያችሁ ላይ ከ ፈጣሪ ጋር ተጠንቅቃችሁ እንድትታገሉ ምክር እየሰጠን ለሁላችንም ፈጣሪ ይረዳን ዘንድ በፆም እና በጸሎት እንድንተጋ መልእክታችንን እናስተላልፋለን::

ወያኔ ቅዠት እንጂ ራዕይ የለውም!


ትላንት የተናገሩትን ዛሬ፤ ዛሬ የተናገሩትን ነገ የማይደግሙ ከሀዲ አንባገነን እና ዘረኛ ቡድኖች የስልጣን ኮረቻ በሀይል ከተፈናጠቱበት እለት ጀምሮ የተለያዩ የማወናበጃ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ የበርካታ ንጹሀን ዜጎችን ህይወት ቀጥፈዋል አስቀጥፈዋል፡፡እንኳን እንደጠላት የሚቆጥሩትንና በመርሃ ግብራቸው ነድፈው መጥፋት አለበት ብለው የፈረጁትን ህዝብ ቀርቶ አርነት እናወጣሀለን እያሉ ክእናንተ በመፈጠራችን ኮራንባችሁ የሚሏቸውን የትግራይን ንጹሀን ዜጎች ሳይቀር የራሳቸውን የስልጣን ዕድሜ ለማራዘም ውድ ህይወታቸውን እንዲገብሩ አድርገዋል፡፡ የሀውዚንን ጭፍጨፋ አቀናብረዋል፣በ1991ዓ.ም በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በተደረገው ጦርነት ከ70000 በላይ የጠርነቱ ሰለባ ሁነዋል፡፡አልሻባብን ለመደምስስ በሚል በሶማሊያ በረሃ የረገፉትን ወታደሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡ስልጣን ለወያኔ ከምንም ነገር በላይ ነው፡፡ ስልጣን ከሉአላዊነት፣ከባህር በር ፣ከሀገርና ከህዝብ እንደሚበልጥባቸው ከመጀመሪያው ጀምሮ የወሰዷቸው እርምጃዎች ማሳያ ናቸው፡፡የገንዛ ሀገሩን ቆርሶ ለሱዳን የሚሰጥ፣የባህርበር አያስፈልገኝም የአሰብን ወደብ ውሰዱት፣ኤርትራ እንድትገነጠል ፈቅጃለሁና እውቅና ስጡልኝ እባካችሁ እያለ የአለም መንግትታትን የተማጸነ፣የገንዛ ዞጎቹን አፈናቅሎ ለውጭ ባለ ሀብቶች መሬታቸውን የሚሰጥ፤የሀገሪቱን ሀብት ለተደራጁ ወንበዴወች የሚያስዘርፍና የሚዘርፍ፤ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦችን አጥፍቼ ታላቋን ትግራይን እመሰርታለሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ አንባገነን እንዴት ያለ ሀገራዊ ራዕይ ነው የሚኖረው፡፡

ዘረኛው መንግስት በተለያዩ ጊዜያት እንዱን ብሄር በሌላው ብሄር ላይ በማነሳሳት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው ሀብትና ንብረታቸውን ተዘርፈው ለከፍተኛ ችግር ሲዳረጉ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለእልፈት ተዳርገዋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጋዜጠኞችን በሽብር ስም እያሰረ ንጹሀንን ሲያሸብር ቆይቷል፡፡በርካታ ፓርቲዎች በሰርጎ ገብ ሰላዮች የተነሳ ይዘውት የተነሱትን አላማ እና የህዝብ አደራ እዳር ሳያደርሱ በጅምር ቀርተዋል፡፡በወያኔ መሰሪ ተንኮል በተቀነባበረ ሴራ ጦርነት ውስጥ ያልገባ ክልልና ብሄር ባይገኝም ውጤቱ እንደሚፈልጉት ስላልሆነላቸው እና የኢትዮጵያ ህዝቦችም ባላቸው አርቆ አስተዋይነትና ረጅም ጊዜ በሰላም አብሮ የመኖር ባህሉ በመታገዝ የፕሮፖጋንዳቸው ሰለባ ባለመሆናቸው ለወያኔዎች ትልቅ ራስ ምታት ጥሮባቸዋል፡፡እስካሁን ሲጫወትበት የነበረውን ካርድም እንዲቀይርም ተገዷል፡፡ አዲሱ የመጫወቻ ካርድም ከብሄር ግጭት ወደ ሐይማኖታዊ ግጭት ለማሸጋገርም የሚያስችለውን “ጀሀዳዊ ሀረካት”የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም በመስራት ከ1500 አመት በላይ አብረው የኖሩትን ሁለቱን ታላላቅ እምነቶች ማለቂያ ወደሌለው ጦረነት በመማገድ የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ቢምክርም እናንተ ከመጣችሁት ገና 21 ዓመታችሁ ነው እኛ ደግም ለረጅም ጊዜ በፍቅር አብረን ኑረናል፤ የጋራ ጠላታችን ዘረኛው ወያኔ ነው፡፡እኛ ከእነሱ እንሻላለን አንለያይም እያሉ በየአደባባዮ አንገት ላንገት ተቃቅፈው እየተላቀሱ ቁጭታቸውን ሲገልጹ መመልከት የተለመደ ተግባር ነው፡፡ሰሞኑን ለኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕርግራም ሙኒክ ላይ የታየውም ህብረት የዚሁ አካል ነው፡፡
እንዴት እንደ ኢትዮጵያ ያለች ታላቅ ሀገር እና እንደ ኢትዮጵያውያን ያሉ ቀደምት ህዝቦች እንደ ወያኔ ባሉ ትንሽ ሰዎች ይገዛሉ?እንዴት የአለም ማህበረሰብ በሀሰት የወያኔ ፕሮፖጋንዳ ሲታለል ይኖራል?እስከመቼ ብቻቸውን በምርጫ ተወዳድረው አሸነፍን እያሉ ሲያላግጡ ይኖራሉ? ወያኔዎችስ በቀጣይ ምን የማደናገሪያ ስልት ያመጡ ይሆን? እኔ በበኩሌ በቃ ብያለሁ፡፡ ወያኔ ራዕይ የለውም ኑሮትም አያውቅም፤ ወደፊትም አይኖረውም፡፡የወያኔ ሀገር እና ህዝብ የማውደም ቅዠት እንጂ ሀገራዊ ራዕይ ብሎ ነገር አያውቅም፡፡በጋራ ጠላታችን ላይ በጋራ እንነሳ!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!



 

Tuesday, February 26, 2013

በሽብርተኝነት ተከሰው በወህኒ ቤት የሚገኙ በጣም በርካታ እስረኞች የይቅርታ ፎርም እንዲሞሉ እየተደረገ ነው

     

በሽብርተኝነት ተከሰው በወህኒ ቤት የሚገኙ በጣም በርካታ እስረኞች የይቅርታ ፎርም እንዲሞሉ እየተደረገ ነው (ምንአልባት የሀይለማርያም መንግስት ሪፎርም /ማሻሻያ/ የማድርግ ዕቅድ ካለው በዚሁ ሊጀምር አስቦ ሊሆን ይችላል፤ አሊያም እንደተለመደው እስረኛ በመልቀቅ የፖለቲካ ማሻሻያ እንደተደረገ ለማስመሰል ይሆናል)፡፡ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄርም በብዛት ከሚለቀቁት እስረኞች ጋር አብረው እንደሚፈቱ ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል፡፡
አጀንዳችን…
ዛሬ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የእነእስክንድር ነጋን ንብረት ለመውረስ ፍትህ ሚንስቴር የመሰረተው ክስ ሲታይ ውሎአል፡፡
እስክንድር ከዚህ ቀደም ‹‹የታሰርኩት በግፍ ስለሆነ ንብረቴን አትውረሱ ብዬ አልከራከርም፤ ዛሬውኑ ልትወስዱት ትችላላችሁ›› በማለት ያልተከራከረ ሲሆን፣ የአበበ በለውን ንብረት በሚመለከት በሌለበት ታይቷል፡፡ የአንዱአለም አራጌ ባለቤት ደግሞ በስሟ የተመዘገበው መኪና መወረሱ አግባብ እንዳልሆነ በጠበቃዋ አቶ ደርበው ተመስገን አማካኝነት ተከራክራለች፡፡ ፍርድ ቤቱም ለውሳኔ የፊታችን ሚያዚያ አስር ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል (በእኔ ግምት ቀጠሮው እንዲህ የራቀው መጋቢት አስራ ስምንት ቀን እነእስክንድር የጠየቁት ይግባኝ የመጨረሻ ውሳኔ ስለሚሰጥበት ከዛ በኋላ የንብረቱን ጉዳይ ለመጨረስ ይመስለኛል)
የሆነ ሆኖ ዓቃቢ ህግ የእስክንድር ንብረት ተብለው ከቀረቡት ባለሁለት ፎቅ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት፣ በባለቤቱ ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ስም የተመዘገበ የቤት መኪና፣ እንዲሁም የእስክንድር እናት ንብረት የሆነ በአንድ ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መኖሪያ ቤትን ለመውረስ ጥያቄ ያቀረበ ቢሆንም፣ በዛሬው ዕለት በእናቱ ስም የተመዘገበውን ቤት እንደተወው ገልጿል (አዲስ ታይምስ መፅሄት የእናቱ ቤት ዝርዝር ውስጥ መግባቱ ተገቢ አለመሆኑን ደጋግማ መግለጿ የሚታወስ ነው)፡፡
ይህንና ዓቃቢ ህግ በእስክንድር እናት ስም የተመዘገበውን መኖሪያ ቤት ከሚወርሳቸው ዝርዝር ውስጥ በማውጣቱ ምንም አይነት ምስጋና የለኝም፡፡ ምክንያቱም እንኳን ንብረታቸው ተከሳሾቹም ምንም ጥፋት ያላጠፉ ንፁሀን ናቸው ብዬ ስለማምን፡፡ ስለዚህም አሁንም እንዲህ እላለሁ፡- ዓቃቢ ህግ ዕዳ አለብህ! አዎ እዳ አለብህ!! ንፁሀን ወንድሞቻችንን ይቅርታ ጠይቀህ እስክትለቅልን ድረስ!!!

የመናገር ነጻነት ዘመቻው ለህወሃት መራሹ መንግስት ምኑ ነው?

የመናገር ነጻነት ዘመቻው ለህወሃት መራሹ መንግስት ምኑ ነው?

ሰሞኑን የዞን 9 አባላት የብሎጋቸውን በኢትዮጵያ መከልከል ተከትሎ ከክፈቱልን ያለፈ ፤ መሰረታዊ ሊባል የሚችል ዘመቻ በማህበራዊ ድህረ ገጾች ጀምረዋል፡፡ በዚህ ደረጃ ምላሽ መስጠቱ እና መጠቀም የሚቻለውን መድረክ ተጠቅሞ የችግሩን ጥልቀት ለማመላከት መሞከር ጥሩ ነው። ነገር ግን የመጻፍ እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እየተጠየቁ ያሉትን ቡድኖች(‘ፎርማሊ’ ካወራን መንግስት ናቸው -ያውም ፈላጭ ቆራጪ) ባህሪ ግምት ውስጥ በማስገባት፤ ዘመቻው እነዚሁ ቡድኖች አምነትውበት በማናለብኝነት የወሰዱትን ርምጃ ከማስቀየር ይልቅ በስነ ልቦናቸው ለተቀረጸው የትምክህት እና የበላይነት አስተሳሰብ ሃሴት የሚሰጥ ሆኖ ስለተሰማኝ ለነሱ ትምክህት ሃሴት ላለማዋጣት ስል በዚህ በዘመቻ አልተሳተፉኩም።
እንኳንስ የመናገር ነጻነት አይደለም ለእምነት ነጻነት ጀርባቸውን ሰጥተው የክስርቲያኑን የእምነት ተቋማት በቁጥጥር ስር አድርገው ሙስሊሙንም እንዲሁ እምነቱን ለመንጠቅ ቤት ለቤት ጭምር አሰሳ የገቡ ሰዎች ናቸው፡፡ የመናገር እና ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ጋር በእጂጉ የተቆራኘ የጋዜጣ ህትመት ማስቆም ሳያንሳቸው ዜጎችን –ያውም ኩሩ ሀገር ወዳድ ዜጎችን በሽብረተኛነት በመክሰስ ፣ብዙ እንግልት በማድረስ እና ክብራቸውን ጭምር ለማዋረድ በመሞከር ሌሌች ዜጎች የዜግነት ክብር እና ነጻነት ጥያቄ ቅብጠት እና በህይወት መቀለድ እንዲመስላቸው በማድረግ የባርነትን እስተሳሰብ በደህንነት ተቋማት ፣በህግ ተቋማት እንዲሁም የማህበራዊ ድንዝዝነት በሚያስፋፉ ሌሎች ልማዶች የሚስፋፉበትን መንገድ በስውርም በግልጽም በማበረታታት የባርነትን መስረት ለማጽናት ሌት ከቀን የሚሰሩ ለመሆናቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ ያለ ብዙ ምርምር ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
የህገ-መንግስት ጉዳይ እና የዜጎች መብት ፋይዳ ሳይገባቸው ቀርቶ ነው እንዳይባል፤ ትግል ጀመርንም ጨረስንም የሚሉባቸውን ቀናቶች በብሔራዊ ደረጃ ጭምር እንዲከበርላቸው የሚፈልጉ ናቸው። እንዲያውም ያለባቸውን የስነ-ልቦና ችግር ከሚያመላክቱ ነገሮች እንደኛው ይሄው ነው። ህወሃት ስልሳ ሺህ ሰው ሰዋበት የሚሉትን በዓላቸውን የሚያዳንቁትን እና ሰው እንዲያዳንቅላቸው የሚፈልጉትን ያህል ለኢትዮጵያ ነጻነት ከጎጠኝነት በጸዳ በንጹህ የሃገር ፍቅር ስሜት የወደቁ በሚሊየን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያኖች ጉዳይ እንዲነሳም እንዲታወስም እይፈልጉም። ታሪኩ ሲነገር ያሳንሳቸዋላ!የሃሳብ ነጻነት ወደሚያፈኑበት ጉዳይ ስመለስ -የሚያፍኑበት እና ሃሳብ እንደጦር የሚፈሩበት ጉዳይ ምንድን ነው የተባለ እንደሆነ መሳሪያ እንቆ የተኮፈሰ የፓለቲካ ስብዕናቸውን የሚያኮስስ ስለሚመስላቸው። እደፊኛ የሚነፉትን ፕሮፓጋንዳ የሚያስተነፍስ ስለሚመስላቸው። የሃሳብ ልውውጥ ላይ ያለ ስለት ስለሚያስፈራቸው። አንግበው ለተነሱት የትምክህት እና የበላይነት ግንባታ ዓላማ እንቅፋት እንደሆነ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ይመስለኛል። የእምነት ነጻነትም እስከመንጠቅ የሄዱበት ምክንያት ከፍራቻ ውጭ ሌላ ሊሆን አይችልም። የፍርሃት ገጹ ይለያያል። የህወሃት መራሹ መንግስት ፍርሃት በአንድ በኩል በጥጋብ እና በማናለብኝነት የተከናነበ ይመስላል በሌላ በኩል ደሞ በልማት ዲስኩር ተከልሎ ከዲስኩሩ በስከጀርባ በምናቡ የሚስላቸውን “ጸረ-ልማት ሃይሎች” (ኢትዮጵያውያኖች እኮ ናቸው የኢትዮጵያ ልማት ጠላቶች?) እንደምክንያት እየተጠቀመ የአፈና የሚጧጡፍበት የሞራል ፈቃድ አብረውት ክሚሰሩት “እህት ድርጂቶች” ይወስዳል፡፡ በህወሃት “የማይበገር ጀግንነት” ውስጥ ያለው እውነታ (‘ሪያሊቲ’) ሃሳብን በነጻነት የመግልጽ መብትን እስከመፍራት የሚያደርስ ፍርሃት ነው። የደህንነት ተቋማቱም እወቃቀር የሚሰማቸውን የፍርሃት ደረጃ ግምት ውስጥ ያስገባ ይመስላል።ስለ ህወሃቶች እና ስለገነቡት የማፈኛ ተቋም የራሴም የሰዎችም ተሞክሮ አለኝ። ገና በልጂነት ባደኩባት የደሴ ከተማ ፓሊስ(ህወሃት ለአፈና ተግባር ካሰለጠናቸው ውስጥ ነበር) አንዱን ያለ እግባብ እያንገላታ ለማሰር ዱብ እንቅ ሲል (እንደዛ ይደረግ የነበረው ደሞ ለሃገሩ በብሄራዊ ውትድርና ዘምቶ የመጣ ዜጋ ነው-የገባው የሚመስለው የፖለቲካ ሁኔታ እንገቱን ባያስደፋው ኖሮ የዛን ለፍዳዳ ፖሊስ ጥርሱን የሚያራግፍ ጎበዝ ነበር። አውቀዋለሁ ) ነገሩ ከንክኖኝ ከፖሊሱ ጋር “የምን እደረገህ” ያደረገውም ነገር ካለ በስነ-ስርዐት ውሰደው የሚል ሙግት ውስጥ ገባሁ። ከዚያ በኋላ ፖሊሱ ልጁን ትቶ ወደኔ ዞረ። ዱላም ጀመረ። ታሳሪው እኔ ሆንኩ፡፡ እና ሂድ እልሄድም ውዝግብ ተጀመረ። ጓደኛየ ታደሰ ባየ( ፌስ ቡክ ላይ አለ) በዛ በዝናብ ተንበርክኮ ሁሉ ለመነው ፓሊሱን፡፡ እኔ ደሞ እንኳን ልለምነው እንዴት ድንጋይ እንደሆነ በተጋጋሚ እነግረዋለሁ። የመምታት አቅሙን ተጠቅሞ ያ ሁሉ የፖሊስ ዱላ ወረደብኝ። በመጨረሻ ላለመታሰር ጨለማውን ምክንያት እድርገን ሁለታችንም አመለጥነው። የተመታሁት ብዙ እንደነበረ የገባኝ ግን በነገታው መሄድ እቅቶኝ ቀኑን አልጋ ላይ ሳሳልፍ ነው። ያኔ ተናድጄ ስለነበር ምንም አልተሰማኝም። ሶስት ቀን ያህል ሳያስነክሰኝ አልቀረም።
Eskinderኮተቤ እያለሁ ደሞ ሮብ ሮብ መብራት ይጠፋ ነበር። በዚያ ምክንያት ረቡዕ ማታ አካባቢ ጥናት የለም ። ወክ ነው የምናደርገው። ወደ ገደራ እየሄድን ስናወራ የነበረውን ከኋላ ይሰማ የነበረ አስቁሞን መታወቂያችንን ከጠየቀ በኋላ እዚያው እካባቢ ወደ ነበረ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደን ተመዝግበን የሚጠይቁትን ጠይቀው ተመልሰናል። ሌላ ጊዜ እንዲሁ አራት ኪሎ ላይ የከተማ አውቶብስ ይዞ የነበረ የትግሪኛ ተናጋሪ ሾፌር በራሱ ስህተት እና ትክምህት ምክንያት ተሳፋሪውን ከአራት ኪሎ ይዞ ሚኒሊክ እካባቢ ወደነበረው ፓሊስ ጣቢያ ወሰደን። በትግሪኛ አወራ ከሰዎቹ ጋር። እኛ “ጥፋተኞች ሆንን።” የተማሪዎች ዲን ነው ጣልቃ ገብቶ ነገሩ ያለቀው።የሌሎችን ተሞክሮ በሚመለከት እዚያው ያደኩባት ደሴ ከተማ ላይ በጠራራ ጸሃይ አፉን በደንብ ያልፈታ የህወሃት ታጣቂ እንድ ባዶ እጁን የነበረ ወጣት አሯሩጦ ከደረሰበት በኋላ ሰው እየተጯጯኽ የክላሹን አፈሙዝ ደረቱ ላይ አድርጎ ተኩሶ ከገደለው በኋላ ክላሹን እንቆ እንደያዘ ሲሄድ ያስቆመው ፓሊስ አልነበረም። ሌሎች ታጣቂዎችም ያሉት ነገር የለም። (በነገራችን ላይ ያኔ እስከማውቀው ድረስ የልጁ ገዳይ ለፍርድ እልቀረበም)እንደዛ እይነቱ የህወሃት ጭራቅነት በርሃ ባልነበሩት ዘመድ እዝማዶቻቸው ላይ ተጋብቶ “ምክንያታዊ” በሚመስል ሁኔታ ስለፍትህ በሚጮሁ ኢትዮጵያውያን የሚያሳዩትን ቅጥ ያጣ ንቀት ማየት እሁን የተጀመረው እይነት ዘመቻ በበታችነት ስሜት በሚናጥ ስብናቸው እና እስተሳሰባችው ላይ የበላይነት እና የገዠነት ካባ ከሚደርብላቸው በስተቀር ትርጉም ያለው ጩኽት ይሆናል የሚል እምነት የለኝም። የማስጮህ ስሜት እንዲሰማቸው አልፈልግም። ዛሬ ፌስ ብክ ላይ እንዲህ ያለ ዘመቻ ባለበት ሰዐት እዚሁ ፌስ ቡክ ላይ እስክንድር ነጋን በሚመለክት የነዚሁ የህወሃት ወገን የሚመስሉ ሰዎች ያደረጉትን ምልልስ ለአብነት እንዲሆን ያህል ከ’ሆም ፔጂ ላይ ስክሪን ሾት’ ወስጃለሁ፡፡
ከዚያ ውጭ የህግ ስርኦት ያለበት ሃገር ቢሆን ኖሮ እንደ ዳንኤል ብርሃነ ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች ሃገር ውስጥ ያለው የሃሳብ ሙግት በጸጥታ ሃይል እና በ”ፍትህ አካላት” እየታፈነ ባዶ ሆኖ ሙግታቸውን እና የሃሳብ ክርክራቸውን ከውጭ ሃገራት ሰዎች ጋር ሲያደርጉ ማየት የህወሃት ደጋፊዎች እና ዘመዶች ባይሆኑ ኖሮ ሊያስገርም ይችል ነበር። ከታች በሊንክ ባስቀመጥኩት የዳንኤል ጽሁፍ የሂውማን ራይቱ ቤን ራውለንስ የእንግሊዝ መንግስት የዕርዳታ እሰጣጥ የሚተች የመጽሃፍ ሪቪው አወጣ ብሎ የእንግሊዝ መንግስት ትችት ሳይሆን ምስጋና ነው የሚገባው የሚል ጽህፍ አውጥቶ ብሎጉም ላይ ጭምር ለጥፎታል። የጽሁፉ ዓላማ ምን ነበር የሚለው ሌላ ጥያቄ ሆኖ መነሳት ያለበት መሰረታዊ ጥያቄ እንደ ዳንኤል ያለው የህወሃት ፖለቲካ ደጋፊ ስለሆነ ብቻ ሃገር ቤት በሚታተሙም ራሱ በፈጠረውም ብሎግ ላይ የመጻፍ ነጻነት ሲሰጠው ሌሎች ዜጎች (ለምሳሌ የዞን ዘጠኝ ብሎገር አባላት) የሚታፈኑበት ምክንያት ከላይ የገለጽኩት ነው። እፈናውን ተቃውሞ የሚደረገውን ተቃውሞ ያልተቀላቀልኩበት ምክንያት የሚጨምርላቸውን -ተዋጋን እያሉ ለሚያወሩት ብቻ ሳይሆን ያኔ ልጆች ለነበሩት እና የደም ትስስር በሚመስል ምክንያት ብቻ እፈናን በምክንያታዊነት ለማስተባባል እና ተቀባይነት እንዲኖረው ለማድረግ ለሚሞክሩትም ጭምር- ለትምክህታቸው የሚጨምረላቸውን ሃሴት ላለመስጠት ነው። የዳኤል ፓስት
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አምባገነናዊነት ሌላ ዓለም ከሚስተዋለው በመሰረታዊነት የሚለይ እንደሆነ እምኖ ተቀብሎ የሚደረገው ተቃውሞ የህወህትን እምባገነናዊ ባህሪ ግምት ውስጥ ያስገባ እና ህወሃቶች በመንፈስም በፖለቲካም የማይጠቀሙበት እና ትምክህት የማይጨምርላቸው መሆነ አለበት ብየ ስለማምን ነው፡፡ በሌላ አንጻር ደሞ የሚደረገው ዘመቻ መሬት ላይ ያለ እና ለህዝቡ ስነ-ልቦና እና አስተሳሰብ ቅርበት ያለው ፣ በቀላሉ የሚገባ ቢሆንም ጥሩ ነው። ምን ያህል ኢትዮጵያዊ ነው በፌስ ቡክ እና ትዊተር ላይ ያለው? ፌስ ቡክ ላይ ካለውስ የህወሃት ደጋፊ ከሆነው ውጭ ስለ ህወሃት መራሹ መንግስት አፈና እና ቅጥ ያጣ እምባገነናዊነት የማያውቀም ምን ያህሉ ነው? ለ “ዓለማቀፉ” ማህበረሰብ ነው እንዳይባል ለዚሁ አፈና ለሚያደርሰው መንግስት ትብብር እና ርዳታ የሚሰጡት እነዚሁ ወገኖች ናቸው። ዳንኤል የእንግሊዝን የእርዳታ አሰጣጥ በመደገፍ የእንግሊዝን መንግስት የሚከላከል ጽሁፍ መጻፍ ደረጃ ላይ የደረሰበት ”የዲፕሎማሲ” ልምምድ ሳይሆን የፖለቲካ ትስስርንም ጭምር የሚያመላክት ይመስለኛል። ለሃወሃት የጥጸጥታ ሃይሎች ስልጠና እና ሎጂስቲክ የሚያቀርበው ማን ነው? ብዙዎቹ የህወሃት ፖሊሲዎች በርግጥ ከህወህት ብቻ የመነጩ ናቸው? “የመለስ” ራዕይን ጨምሮ?

Monday, February 25, 2013

መንግስት ሕገ መንግስቱን ንዶ እየጨረሰው ነው!
ድምፃችን ይሰማ
‹‹የያዛቸው የፖሊስ መኮንን ወይም የሕግ አስከባሪ በጊዜው ገደብ ፍርድ ቤት በማቅረብ የተያዙበትን ምክንያት ካላስረዳ፣ ፍርድ ቤቱ የአካል ነጻነታቸውን እንዲያስከብርላቸው የመጠየቅ ሊጣስ የማይችል መብት አላቸው፡፡››
ሕገ መንግስት አንቀጽ አንቀጽ 19መንግስት ሕገ መንግስቱን ንዶ እየጨረሰው ነው!
ለ200 ቀናት ያለ ክስ የታሰሩ ሙስሊሞች በኢትዮጵያ ምድር
የዜጎችን ዴሞክራሲያዊ መብት ያስከብራል ብለን ተስፋ የጣልንበት ሕገ መንግስት በመንግስት አስፈጻሚዎች እየተጣሰ መብታችንም ፈጽሞ በማይነጻጸር መልኩ እየተመዘበረ ነው፡፡ የእምነት ነጻነታችን፣ የአምልኮ መብታችን፣ ሃይማኖታችንን በነጻናት የመተግበር ተፈጥሮአዊ መብታችን፣ የእምነት ተቋማትን የማቋቋም መብታችን፣ የሃይማት መሪዎችን በነጻነት የመምረጥ መብታችንና መሰል መብቶች ሕገ መንግስታዊ እውቅና የተሰጣቸው ነገር ግን በመንግስት ባለፉት አመታት እንደዘበት እየተወረሱብን የሄዱ መብቶቻችን ናቸው፡፡ ለእነዚህ ሕገ መንግስታዊ መርሆች መከበር ሁለመናችንን አሳልፈን ሰጥተን ሰላማዊ ትግል እያደረግን ነው፡፡
ሆኖም የመንግስት የህገ መንግስት እና የመብት ጥሰት ድንበር የለሽ እየሆነ መጥቷል፡፡ መንግስት ሕገ መንግስቱን አስጠብቃለሁ በሚል የለበጣ ምክንያት ሕገ መንግስቱን እየናደው ነው፡፡ የዜግነት ሕገ መንግስታዊ መብቶቻችን ሁሉ ውሃ እየበላቸው ነው፡፡ ከቀናት በፊት ገልጸነው እንደነበረው መንግስት የህግ ጥሰቱን ለመደበቅ እንኳ የማይጨነቅበት ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡ በአገሪቱ በሁሉም አቅጣጫዎች የመብት ጥሰቱ ያለ መስፈሪያ.. ያለ ከልካይ እየተሳለጠ ነው፡፡ ሕገ መንግስቱን ማስጠበቅ የሚገባቸው አካላት ዝምታን መርጠዋል፤ እንዲያውም በሌላ አቅጣጫ የመብት ጥሰቱ አቢይ ተዋናይ እየሆኑ ነው፡፡
ፍ/ቤቶችን ተመልከቷቸው – ሕግ ከማስከበር ይልክ ከጸጥታ አስከባሪዎች ጋር በመተባበር የዜጎችን መብት እየጣሱ ነው፡፡ ሕገ መንግስቱ በአንቀጽ 19 የተያዙ ሰዎች መብት በሚል ርእስ በሁለቱ የመጀመሪያ አንቀጾች የታሰሩ ሰዎች ያላቸውን መብቶች ይጠቅሳል፡፡ ‹‹የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው፡፡ ይህም ጊዜ ሰዎቹ ከተያዙበት ቦታ ወደ ፍርድ ቤት ለመምጣት አግባብ ባለው ግምት የሚጠይቀውን ጊዜ አይጨምርም፡፡ ወዲያውኑ ፍርድ ቤት እንደቀረቡ በተጠረጠሩበት ወንጀል ለመታሰር የሚያበቃ ምክንያት ያለ መሆኑ ተለይቶ አንዲገለጽላቸው መብት አላቸው፡፡›› እንዲሁም ሌላኛው ንኡስ አንቀጽ ‹‹የያዛቸው የፖሊስ መኮንን ወይም የሕግ አስከባሪ በጊዜው ገደብ ፍርድ ቤት በማቅረብ የተያዙበትን ምክንያት ካላስረዳ፣ ፍርድ ቤቱ የአካል ነጻነታቸውን እንዲያስከብርላቸው የመጠየቅ ሊጣስ የማይችል መብት አላቸው፡፡›› ይላል ሕገ መንግስቱ፡፡ መሬት ላይ ያለው ግን ከዚህ በተቃራኒው ነው፡፡
ዛሬ ግን በኢትዮጵያ ምድር ከ190 በላይ ቀናት ያለ ክስ በእስር ላይ የሚገኙና የሚንገላቱ ዜጎች አሉ፡፡ በተለይም በአማራ ክልል ጥቂት በማይባሉ ከተሞች ኢማሞች፣ የሃይማኖት አዋቂዎች፣ አረጋውያንና ወጣቶች ያለ ክስ ከ6 ወራት በላይ በእስር ላይገኛሉ፡፡ ከሕገ መንግስቱ ይጋጫል የተባለው የጸረ ሽብር ሕጉ አንኳ በ4 ወራት ውስጥ ክስ እንዲመሰረት ያዛል – ያ ካልሆነ ታሳሪዎቹ እንዲለቀቁ ያዛል፡፡ ነሀሴ አራት በደሴ ፖሊስ ባስነሳው ግርግር የተያዙት ሸኽ ሀሰን ሀሚዲን፣ ሸኽ ጀማል እና ኡስታዝ ባህረዲን 195 ቀናት ያለምንም ክስ በወህኒ ይገኛሉ፡፡ በሰሜን ወሎ መርሳ ከተማ ያለው ደግሞ ከዚህ እጅግ የከፋ ነው፡፡ ከረመዳን ወር ጀምሮ ማለትም ከባለፈው ሐምሌ ወር 2004 ጀምሮ ያለ ክስ በእስር ላይ የሚገኙ በርካታ ሙስሊሞች አሉ፡፡ የመርሳው ታሳሪዎች ከ200 በላይ ቀናት በእስር ቤት ያለ ምንም ክስ ታጉረዋል፡፡ በወልዲያ፣ በኮምቦልቻ፣ በከሚሴ እና በሌሎችም አቅራቢያ ከተሞች በርካታ ሙስሊሞች ያለ ክስ ያለ ፍርድ በወህኒ ይገኛሉ፡፡ እነዚህን ዜጎች ዳኞች በነጻ ሊያሰናብቷቸው ቢገባም ይህ አልሆነም፡፡ እነዚህ ዜጎች የተከሰሱበት የተጠረጠሩበት ወንጀል አልተነገራቸውም – ፖሊስ ይህን እንዲያደርግ ሕጉ ቢያስገድደውም አላደረገውም፡፡ ሌላዉ ቢቀር መንግስት በራሱ ፍ/ቤቶች እንኳ አስቀርቦ ሊያቀርብባቸው የሚችለው ክስ የለውም፡፡ ንጹሀን ዜጎች ሙስሊም በመሆናቸው ብቻ፣ በሃይማኖታቸው ምክንያት ብቻ በእስር እና ስቃይ ውስጥ ይገኛሉ፡፡
ይህ ሁለ ሲደረግ የፍትህ አካላት፣ ለሕገ መንግስቱ ዘብ ነን የሚሉ ዜጎች እና ተቋማት፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ስለ ሕግ የበላይነት የሚጨነቁ ዜጎች የት ናቸው? ሕገ መንግስቱ ጠባቂ እና አስከባሪ አጣ እኮ፡፡ ዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብታቸው ተደፈጠጠ እኮ፡፡ ሕገ መንግስታዊ ዋስትናችን ተገሰሰ እኮ!
መንግስት ሕገ መንግስቱን ንዶ እየጨረሰው ነው! ክፍል ሁለት ይቀጥላል…
አላሁ አክበር!

Sunday, February 24, 2013

Ethiopia’s high profile official, Junedin Sado defects to Kenya

Ethiopia’s high profile official, Junedin Sado defects to Kenya


Awramba Times (Addis Ababa) – Junedin Sado, Ethiopia’s high profile official and former Minister of Civil Service has defected.
According to Ethiochanel, a pro-government private newspaper based in Addis Ababa, Junedin Sado is seeking asylum in neighboring Kenya.
Ethiopian authorities have charged Junedin Sado’s wife, Habiba Mohamed, with terrorism for using money from the Saudi Arabian Embassy to pay for Islamic protests against the government.
Junedin Sado

In the aftermath of Habiba’s arrest, Junedin published a letter on Ethiochannel newspaper defending his wife and criticizing the federal prosecutor’s charges. Last December, Awramba Times has reported about the Ethiopian parliament’s plan to waive the immunity of Junedin Sado.
Since 2001, Jundein Sado has served on various key positions of the government including as president of the Oromia Region , Minister of Transport and Communication and Minister of Civil Service.

Saturday, February 23, 2013

የካቲትን የምንዘክረው ከሀገር በቀል ወራሪው ህወሃት ጋር በመፋለም ነው!!

የካቲትን የምንዘክረው ከሀገር በቀል ወራሪው ህወሃት ጋር በመፋለም ነው!!

ቀደምቶቻችንን የምናስታውስበት፣ ሀገራችንን ከጠላት ወራሪ እና አንድነቷን ለማስጠበቅ ያደረጉትን ተጋድሎ ከምንዘክርበት እለት አንዱ የካቲት 12 ነው። በዚህ ግዜ ይህንን ታሪክ ገልብጦ ለማበላሸትና ለመጻፍ የሚጥረውን፣ የአሁኑን የግራዚያኒ ትንሽ ወንድም ሀገር በቀል ዘረኛ መንግስት የሆነውን ህወሃት/ኢህአዴግን ሀይማኖት፣ ዘርና ጾታ ሳይለየን የምንታገልበት ሁነኛ ወቅት ላይ እንገኛለን።
የቀድሞዋ የአፍሪካ ሀገራት የነጻነት ተምሳሌት የሆነችው እማማ ኢትዮጵያ፤ ዛሬ ሀገር በቀል በሆኑ የዘረኛ መዥገሮች ስብስብ ተጣብቃ የአበው መሰዋእትነት ከንቱ ይሆን ዘንድ ወያኔዎች እየሰሩ ነው። ጥንታዊ ታሪክን በመፋቅ፣ ባልተደረገና ባልተፈጸመ ታሪክ ለመተካት ወያኔ/ኢህአዴግ እያንዳንዱን የአበውን የታሪክ ማህደር በማጥፋት፣ እንደ አቡነ ጴጥሮስ የመሳሰሉ የጀግኖችን ሀውልት አሻራ በማፍራረስ ርካሽ የሆነ ግዚያዊ የፖለቲካ ጥቅም ማስገኛ ስራ ላይ በመሰማራት ሀገራችንን ወደኋለዮሽ እድገት እየጎተቷት ይገኛሉ።
ሁለቱን ገዳዮች የሚያገናኛቸው፤ የግራዚያኒ ወታደር አበው ለነጻነታቸው ለአንድነታቸው ሲያደርጉት የነበረውን ተጋድሎ ለማስቆም፤ የህዝቡን የትግል ሞራል ለመግደል የአዲስ አበባን ነዋሪ ቁጥሩ 30ሺ የሚሆን ንጹሃን ዜጎችን በመጨፍጨፍ ፋሽስትነቱን ለማሳየት ያደረገው ያልተሳካ ሙከራ ነው፡፡ ይሁን እንጅ ኢትዮጵያውያን ለነጻነታቸው የሚያደርጉትን ትግል ይህ አልገታቸውም። በተመሳሳይ ደግሞ ዘመን አመጣሹ የየካቲት አስራ አንዱ ወያኔም፤ እንደፋሽስቱ ሁሉ በንጹሃን ህዝባችን ላይ በጎንደር ስላሴ፣ በምርጫ 97፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ፣ በኦሮምያ፣ በአዋሳ፣ በሀረር አሁን ደግሞ በሙስሊሙ ወገናችን ያደረሰው ጭፍጨፋ፣ እስርና ግድያ ከግራዚያኒ ጋር ያመሳስለዋል። ልዩነታቸው ይሄኛው ሀገር በቀል ወራሪ መሆኑ ነው። ምን አልባትም ወያኔ ልደቴ ብሎ የሚጨፍርበት የካቲት 11 ለሱ የድል ቀን ሲሆን፤ ለእኛ ደግሞ አባቶቻችን የምናስታውስበት የመከራ ቀን ነው።
በየካቲት12 የኢትዮጵያ ህዝብ ለነጻነቱ፣ ለአንድነቱ፣ ለሀገሪቱ ከብር የፋሽስቱን ወራሪ ሃይል በመመከት፤ ልጅ አዋቂ ሳይለይ ከሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች በመጉረፍ ጠላትን በማስጨነቅ እየሞቱም አልበገርነታቸውን ያስመሰከሩበት ልዩ ቀን ነው። ኢትዮጵያ ብቸኛዋ የአፍሪካ የነጻነት ተምሳሌት ሀገር እንድትሆንም በማድረግ፤ ወርሃ የካቲት ታሪካዊ ወርና በድል አጥቢያነት በሀገራችን እንዲሁም በአሁጉራችን አፍሪካ ዘለአለም እንዲታወስና እንዲዘከር አድርገው አበው አልፈዋል። ይህን የማስጠበቅ ታሪካዊ የሞራል ግዴታ የማን ነው?
አበው የፋሽስቱን የግራዚያኒ ወራሪ ጦር ድባቅ በመምታት አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ሀገራችንን ከጠላት ወራሪ አድነው አስረክበውናል። በዚህ ታሪካዊ ገድል በሆነው በወርሃ የካቲት የተሰዉት ጀግኖች፣ የኢትዮጵያ ልጆች አጥንትና ደም መሰዋእትነት ከቶ ከታሪክ ማህደር የማይጠፋ ስማቸው ከመቃብር በላይ ሆኖ ሲዘከር ይኖራል። ይህ ትውልድ ይህን የማስጠበቅ የታሪክ ባለተራ ነው እንላለን።
ግንቦት 7፣ የአባቶቻችንን ጀግንነትና ወደር የሌለውን የሀገር ፍቅር፣ የሀገር ክብር፣ የቁርጠኝነት መንፈስና የአደረጉት መሰዋእትነት ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ይታገላል። በቁርጥ ቀን ልጆች በቁርጥ ቀን ሰዓትም ለመድረስ፤ እስከመጨረሻው በመታገል ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣትና ይህን ድል ለማስመለስ፤ አስመልሶ ለትውልድ ለማስረከብ፣ ለማስጠበቅ እያንዳንዷን ደቂቃ ሊጠቀምባት ቆርቶ ተነስቷል።እርሰዎስ?
የሀገራችን ህዝብ ሆይ፡- የኢትዮጵያ ጀግኖች እነ አጼ ሚኒሊክ፣ የበላይ ዘለቀ፣ እነ አብዲሳጋ፣ እነ ዘራይደረስ፣ እነ አቡነ ጴጥሮስ፣ እነ አፄ ዮሃንስ፣ እንደ ቋራው ካሳ እና ሌሎችም በበቀሉበት፣ በተፈጠሩበት በጥቁር አፈር ምድር፤ ፀረ-ኢትዮጵያ ሀገር በቀል ዘረኛ ሃይሎች መፈጠራቸው አሳዛኝ ታሪክ መሆኑን እኛም እንመሰክራልን። ይሁን እንጅ፣ ቅሉ ይህንን በሁለት ትውልድ መካከል የተፈጠረውን የሰማይና የምድር ልዩነት ቁጭ ብለን በማየት ከንፈራችንን እየመጠጥን የምንቀመጥበት ሰአት ላይ አይደለንም። ጥሪ ከወዲያ ማዶ እየተበራከተ ነው። የድረሱልን ጥሪ!
ስለዚህም መላው የሀገራችን ህዝብ ወያኔን ለማስገደድ አሊያም ለማስወገድ አቅሙ በፈቀደ ሁሉ በገንዘብ፣ በእውቀት በጊዜና ጉልበቱ በመርዳት ታግለን የካቲትን የመሰዋእትነት መንፈስ እያስታወስን፣ ግንቦት 7ን የህዝብ ድምጽ ለማስከበር ይህ ትውልድ ሞራላዊ ግዴታ አለበት እና እንነሳ! እንሂድ።
በአንጻሩ በወያኔ መንደር በአጋጣሚም ሆነ በጥቅም ምክንያት ያላችሁ፡- እንደ ጠዋት ጤዛ ብን ብለው ከሚጠፉ አምባገነኖች ጋር በመለጠፍ ህዝባችንና ሀገራችንን መበድልና ማሰቃየት ለታሪክ ተጠያቂነት ይደርጋል። በወንጀል ተባባሪነት ስለሚያስጠይቅ ከወዲሁ መንገድን በማስተካከል እምቢ ለህወሃት፣ በቃኝ ባርነት፤ በሚል የህዝብ አጋርነትና ድጋፍ ወደ አለው የነጻነት ትግል በመቀላቀል ከማይሻር፣ ከማይጠፋ የታሪክ ማህደር ውስጥ ራስዎትን ያስገቡ ዘንድ የካቲት ጥሩ አጋጣሚ ነው።
በተለይም ኢትዮጵያውያን አርበኞች በጠላት ላይ የወሰዱት የማያዳግም እርምጃ ለመድገም እና ኢትዮጵያን ከሀገር ውስጥ ጠላት ከሆነው ህወሃት ለመታደግ፤ ነፃነታችንን አሳልፎ ላለመስጠት፣ ብርቱ ክንዳቸውን በአኩሪ መሰዋእትነት ለማሳረፍ እና ሕያው ምስክር ለመሆን ከተነሱት ከግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ጋር ሆነን በጋራ በተባበረ ሃይል የምንታገልበት ጊዜ ዛሬ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ጊዮን ሆቴል የተጠናቀቀው የኦህዴድ ድራማ!!

ጊዮን ሆቴል የተጠናቀቀው የኦህዴድ ድራማ!!

ግለሰብ የሚጠመዝዘው “የህዝብ” ወኪል
opdo1
የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ወገኛ ድርጅት ነው። “ሲያደርጉ አይታ” እንደሚባለው እንደ ኤፈርት አይነት ታላቅ የንግድ ኢምፓየር ከፈተ። ስሙንም ቱምሳ ኢንዶውመንት አለው። ቱምሳ የድርጅት ቅርጽና መልክ ተበጅቶለት ስራ ጀመረ። በበረሃ ትግል ወቅት በነበረን ሃብት መሰረትነው ለማለት ቀዳሚዎቹ የኦህዴድ ምልምሎች ሳንቲም አዋጡና ወደ ተግባር ገቡ።
ቱምሳ በስሩ ዲንሾ ትሬዲንግ፣ ዲንሾ ትራንስፖርት፣ አግሮ ኢንዱስትሪና የንግስ ድርጅቱ የጀርባ አጥንት የሆነውን ቢፍቱ ገነማ የሚባል የጫት ንግድ አቋቋመ። የትራንስፖርት ዘርፉን ይመሩ የነበሩት የአቶ ኩማ ደመቅሳ ወንድም እንክት አድርገው በሉትና ከሰረ። ዲንሾ ንግድ ማዳበሪያ እነግዳለሁ ብሎ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ከንግድ ባንክ ተበደረና ታሪኩን በኪሳራ ደመደመው። ዲንሾ አግሮም ከእህት ኩባንያዎቹ እንደተማረው ኪሳራ ተከናንቦ መሬት ብቻ አንቆ ቀረ። መጨረሻ ላይ በገፍ የሰበሰበውን መሬት በሽርክና ስም ለሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ አስረክቦ እጁን ታጠበ።
ማዳበሪያ ንግድ ሲገባ ለመወዳደር ያሰበው ከጉና ንግድና አምባሰል ከሚባለው የህወሃት ማዳበሪያ አቅራቢ ጉልበተኛ ድርጅት ጋር ነበርና ገበያ ለመሳብ በሚል ማዳበሪያ በዱቤ አደለ። መጨረሻ ላይ “የበተነውን ብር መሰብሰብ አልቻለም” ተባለና ከማዳበሪያ ንግድ ተገለለ። ባንክ ተጨማሪ ብር እንዲሰጠው ቢጠይቅም ተከለከለ። ኤፈርት በላይ በላይ እንደሚፈቀድለት ብድር ቱምሳ ቢጠይቅም ባንክ አልሆነለትም። በክልሉ ማዳበሪያ እንኳ የመነገድ መብቱን አሳልፎ ተመልካች ለመሆን ተስማማ። ከፍተኛ የአክሲዮን ባለቤት ከሆነበት ወጋገን ባንክ እንኳ ብር ወስዶ ንግዱን ማስቀጠል ባለመቻሉ ዲንሾ ትሬዲንግ ሰመጠ። ከሙስናው ጋር ተዳምሮ ስውር ደባና ድንቁርና ገደለው። አሁን የአረም መድሃኒት ይቸረችራል።
(የምስሉ ባለቤት: ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ)
የማዳበሪያ ንግዱ እንዳከተመለት ኦህዴድ “ብልሃት አድርጎ” የወሰደውን አዲስ የንግድ ስልት ቀየሰ። ገጠር በመዝለቅ ኮንጎ /ላስቲክ/ ጫማ ለመነገድ ተስማማ። በገፍ በኮንቴነር አስገባ። አገር የሚመራው ኦህዴድ ኮንጎ ቸርችሮ ሊያተርፍ የንግድ “ፋኖ ተሰማራ” አለ። ብዙም ሳይቆይ ያስመጣውን ኮንጎ ይዞ እጁን አጣጥፎ ተቀመጠ። ድርብ ኪሳራ። አቻ ድርጅቶች መኪና መገጣጠሚያ ሲከፍቱ፣ ሲሚንቶ ማምረት ሲጀምሩ፣ ማዳበሪያ ለማምረት ሲነሱ፣ ትርፋቸውን እያሰቡ ወርቅና ማዕድን ቆፍረው ለማውጣት ሲሰማሩ፣ በትራንስፖርትና በሸቀጥ ንግድ ከብረው ትርፋቸውን በዶላር ሲያሰሉ ኦህዴድ ኮንጎ ጫማ ለመነገድ እቅድ አውጥቶ፤ እሱም ከሽፎበት ይደናበር ነበር።
እንጂ ቀደም ሲል ሽፈራው ጃርሶ፣ ከዚያም ግርማ ብሩ ሲመሩት የነበረው ቱምሳ ኢንዶውመንት እንዳይከስም ተሸክሞ የያዘው የጫት ንግዱ ስለነበር አዲስ ስልት ዘርግቶ ለመክበር ያወጣው እቅድና የበረሃ ላይ ስቃዩ ጊዮን ሆቴል እንዴት እንደተቋጨ የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚያስፈልገው ነው።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “ቱጃሯ ሱራና ኦህዴድ – ከጫት ንግድ በስተጀርባ ያለው ቁማር” በሚል ርዕስ አንድ ዘገባ ማስነበባችን ይታወሳል፡፡ በዚያው ዘገባ ላይ ኦህዴድ ሶማሌ ጫት ንግድ ውስጥ ገብቶ እንዳልተሳካለት እናስከትላለን ባልነው መሠረት በተወሰነ መልኩ ከዚህ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
ግመሉ ኦህዴድና የጊዮን ሆቴሉ ድራማ
ዋና ጽህፈት ቤቱን ድሬዳዋ ያደረገው ቢፍቱ ገነማ የጫት ንግድ አትራፊነቱ ከግለሰቦች ባይበልጥም ከፍተኛ የሚባል ነው። በዚሁ አትራፊነቱ የተነሳ “ኢገ ኬኛ” ደማችን ይሉታል። የባለስልጣኖችን ከርስ፣ የተለያዩ ሃላፊዎችንና የበታች ሰራተኞችን ቅርምት ተቋቁሞ አዲስ አበባ ኮሜርስ ፊት ለፊት ህንጻ ለመስራት ችሏል። ብቸኛው የቱምሳ ስኬት መሆኑ ነው።
በጫት ንግድ ውስጥ ያለው የገንዘብ ዝውውርና ትርፉ ያጓጓው ቱምሳ ኢንዶውመንት አዲስ ስራ አስኪያጅ ከመደበ በኋላ ወደ ሶማሌ የሚላከውን ጫት ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር እቅድ ዘረጋ። ወይዘሮ ሱሁራ እስማኤል በብቸኛነት ወይም በከፍተኛ ደረጃ የተቈጣጠሩትን የሶማሌ የጫት ንግድ ለማምከን ኦህዴድ ባሉት ከፍተኛ የፖለቲካ ሃላፊዎች አማካይነት ጡንቻውን ለማሳየት ሞከረ። ወይዘሮ ሱራ ባላቸው ከብረት የጠነከረ ሃይልና ጉንጉኑ ሊበተን የማይችል ሰንሰለት ኦህዴድ የመጀመሪያ ሃሳቡ ቅዠት ሆነ። ከሸፈ!!
የመከላከያ ድጋፍ
ሱሁራ ኢስማኤል (ፎቶ: Philipp Hedemann)
ሁለተኛው አካሄድ ወይዘሮዋ ሃርጌሳን ስለተቆጣጠሩት ሃርጌሳ ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ዋጋ በመቀነስ ጫት ማቅረብ ነበር። ሆኖም ኦህዴድ ጫት ወደ ሃርጌሳ የላከ ቀን ሃርጌሳ ጫት በነጻ ታደለ። ኦህዴድ የላከውን ጫት የሚገዛው ታጣ። ጫት በባህሪው ቶሎ ስለሚበላሽ “ተቃጠለ” አስቀድሞ መረጃ የደራሳቸው ሞኖፖሎች ኦህዴድን “አርፈህ ተቀመጥ” በማለት “አይቼሽ ነው ባይኔ ወይስ በቴሌቪዥን” የሚለውን ዘፈን ጋበዙት።
ሶስተኛው መንገድ ተቀየሰ። “ተነሳ ተራመድ፣ ክንድህን አበርታ …” ተዘመረ። በእቅዱ መሰረት ኦህዴድ የጫት አበባ ይዞ ጉዞውን ወደ ፑንት ላንድ አቀና። የፑንት ላንድ ጉዞና የንግድ አላማ በሚስጥር እንዲሆን ተወሰነ። የቱምሳ አመራሮች ስንቅና አገልግል ቋጥረው የኦጋዴንን በረሃ በመኪና ለማቋረጥና ፑንት ላንድ ለመግባት ወሰኑ። በረሃው ለህይወትም አስጊ ስለሆነ የመከላከያ ትብብር አስፈለገ።
ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ እንደሚመሰክሩት የኦህዴድ ሰዎች ፑንት ላንድ ለመግባት በበረሃ የተንከራተቱት አንዴ አይደለም። በተደጋጋሚ ፈታኝ ሁኔታዎች አጋጥሟቸዋል። የመጀመሪያውን ጉዞ አከናውነው ሲመለሱ በረሃው በልቶ ጨርሷቸው ከሰል መስለው ነበር። ከበርካታ ምልልስ በኋላ የፑንት ላንድ አስተዳደር ቀና ምላሽ ሰጠ። በውሳኔው መሰረት የፑንት ላንድ “የፓርላማ አባላት” አዲስ አበባ ተገኝተው በኦፊሴል የንግድ ውል ለመዋዋል ቀጠሮ ያዙ።
በቀጠሮው መሰረት የፑንት ላንድ ወኪሎች አዲስ አበባ ገቡ። በቱምሳ ወጪ ግዮን ሆቴል አረፉ። ምርጥ የአወዳይ ጫት ሆቴል ድረስ እየተላከላቸው “ቃሙት”። ተዝናኑ። ለቀናት ውሎ አበልና ሙሉ ወጪያቸው እየተቻለ ተምነሸነሹ። አዲስ አበባ ያሉ ጓደኞቻቸውንና ወዳጆቻቸውን በመጋበዝ ኦህዴድ የሚያቀርበውን ጫት “በሉት”። “አገር መሪ ነኝ የሚለው” ኦህዴድም የታዘዘውን እያቀረበ ጋበዘ። የቢዝነስ ማባበያ መሆኑ ነው። ይህ ሁሉ ሲደረግ የጫቱን ንግድ የተቆጣጠሩትና ከጀርባ ሆነው ከለላ የሚሰጡት ራዳራቸውን አስተካክለው ይቀርጻሉ።
ጋዜጣዊ መግለጫ
የፑንት ላንድ የፓርላማ ወኪል ናቸው የተባሉት ክፍሎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ። ታላቅ የንግድ ስራ ለመስራት ይህ የመጀመሪያ እንደሆነና ወደፊት “ዘርፈ ብዙ” ስራ በጋራ ለመስራት እቅድ እንዳለ ተናገሩ። መርቅነው መግለጫውን አደመቁት። ኦህዴድም ፈነጠዘ። በጫት ንግድ ፑንት ላንድን ሲቆጣጠር ታየው። ዶላር ለመሰብሰብ ጎመጀ። ታላቅ የንግድ ኢምፓየር ዘርግቶ ኢኮኖሚውን ሲዘውር ተመለከተ። የማዳበሪያ ቁጭቱን ሲወጣና ሲረካ ተሰማው። ሁሉም ነገር ከንቱ መሆኑ የታወቀው ግን ሰዎቹ አዲስ አበባ በገቡ በበነጋው እንደነበርና ጉዳዩ ገብቷቸው እናባራቸው ያሉም ነበሩ።
ውለታ ለመፈጸም መጥተው ከዛሬ ነገ እያሉ ከሳምንት በላይ በድሎት ጊዮን ሆቴል ተኝተው ሙሉ እንክብካቤ የተደረገላቸው እንግዶች መግለጫውን አስቀድመው ከሰጡና ውሉን ከፈጸሙ ወደ አገራቸው ስለሚመለሱ ጉዳዩን በማዘግየት ኦህዴድን ያልቡት ነበር። ከነሱ መካከል በጓሮ ከሌሎች ጋር የሚነጋገሩም ነበሩ። እንደምንም ተብሎ መግለጫ ከተሰጠ በኋላ መጽሃፉም ዝም ቄሱም ዝም ሆነ። ኦህዴድ ከፍ ዝቅ ብሎ ያስተናገዳቸው ሰዎች ደብዛቸው ጠፋ። የሞራልና የስሌት ኪሳራ ተከተለ። መንግስት ሆነው እንደ ሌባ በጓሮ ሲርመጠመጡና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ሲልከሰከሱ ተታለሉ። በግልጽ የሂሳብ ሰነድ ያልተወራረደ ከፍተኛ ገንዘብ በወቅቱ በጉርሻ ስም መሰጠቱን፣ የሽኝት ቀን የኢትዮጵያ ባህል እቃዎች ስጦታ መቅረባቸውም የአደባባይ ምስጢር ነው። የኦህዴድ “ግመሉ” የበረሃ ታሪክ ይኸው ነው። ሰዎቹ ድምጻቸውን አጠፉ። ኦህዴድም “ግመሉ” የሚለውን ስም ይዞ ቀረ።
ፉከራው
የፑንት ላንድ ጉዞ ከድግግሞሽ በኋላ መሳካቱ ሲታወቅ የቱምሳ አመራሮች “ገድላቸውን” በገሃድ ቢሮ መናገር ጀመሩ። ኦጋዴን በረሃ ውስጥ ያጋጠማቸውን መከራና ድካም እንዴት እንደተቋቋሙ በኩራት መተረክ ተያያዙ። በተለይ አዲሱ ሃላፊ የዘመቻው መሪ መሆናቸውን ለማሳየት እጅጌያቸውን ይሰበስቡ ጀመር። ወደ ቢሮ ሲገቡ አረማመዳቸውና አስተያየታቸው ተቀየረ። ሰራተኞችን ሲያዙ “የበረሃ ተሞክሮዬ” ማለት ጀመሩ። ስለቁርጠኝነትና ዓላማ መስበክ አበዙ። “ግመል” በስብሰባ ላይ ቋሚ ምሳሌያቸው ሆነ። አስተዳደሮቹን የሚከቡዋቸው በኩራት ታበዩ። ተወጣጠሩ። ቱምሳ ከክስረቱ አገግሞ በትርፍ የሚተኮስበትን አቅጣጫ ያገኙ ያህል በየቀኑ ይዘሉ ነበር። ወሬያቸውም ሁሉ “ፑንት ላንድ ተኮር” ሆነ። ፑንት ላንድ ለመመደብ ዝግጅት የጀመሩና ትርፋቸውን የሚያሰሉት ባልደረቦቻችን ድርጊታቸው ሁሉ ያሳፍር ነበር።
አገር የሚመራ ድርጅት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ “ወኪል” ነኝ የሚል ድርጅት ክብሩን ጠብቆ ስራውን መስራት እየቻለ፣ እንደ ኮንትሮባንድ ነጋዴ በረሃ ለበረሃ ሲቀበዘበዝ ማየት ያሳፍራል። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ሆነው ለጥቅም ሲሉ ግለሰብ አንግበው ሲነጉዱ ማየት ያሳዝናል። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኦሮሞ ገበሬዎች በራሳቸው መሬት ላይ የተከሉትን ጫት ለፈለጉት እንዳይሸጡ በሞኖፖል ገበያ ተወጥረው እንዲያዙ ሲደረግ ተከራካሪ ማጣታቸው አንገት ያስደፋል። የጫት ኬላ ተነስቶ ክልሉ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢውን ማጅራቱን ሲመታ አቋም የሚይዝ መጥፋቱ በባርነት የመያዝ ያህል ዘግናኝ ነው።
ከሁሉም በላይ አሳፋሪው ደግሞ የክልሉ ገቢና ጥቅም ወደ ግለሰቦች ኪስ እንዲገባ በፊርማቸው ያዘዙት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህንን ውሳኔ የወሰኑበት ምክንያት እየታወቀ የኦሮሞን ህዝብ ለቅሶ ተቀመጥ ማለታቸው ነው። በቱምሳ ቢሮ ውስጥ “ባለራዕዩ መሪያችን ተለየኸን” ተብሎ መለጠፉ በራሱ የውርደቱ ድምር ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

The former Oromia region president and Minster of Civil Service , Junedin Sado, is seeking an asylum in Kenya

The former Oromia region president and Minster of Civil Service , Junedin Sado, is seeking an asylum in Kenya. He was president of the Oromia Region from 28 October 2001 until 6 October 2005 when he was replaced by Abadula Gemeda. He subseq...uently was appointed Transport and Communication Minister, which is the office he was holding when Prime Minister Meles Zenawi moved him to the Science and Technology Ministry October 2008. Following the 2010 general election, Junedin was appointed Minister of Civil Service.

He has been at odds with the TPLF leadership at different times but his rift with the administration came in to light even more when his wife ,Habiba Mohammed, was listed among 29 Muslim activists accused of criminal conspiracy to commit unspecified acts of terrorism — charges that could attract the death penalty in October 2012

የቡድን አንቅስቃሴ ያደርጋሉ የተባሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው !!!

Thursday, February 21, 2013

የቡድን አንቅስቃሴ ያደርጋሉ የተባሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው !!!

ማስጠንቀቂያው የተሰጣቸውብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት
በምርጫው እንቅስቃሴ ዙሪያ መንግሥት ለሦስት አባቶች ማስጠንቀቂያ ሰጠ
• በስመ ደኅንነት ያጭበረበሩ 40 ግለሰቦች ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው
• እነንቡረ እድ ኤልያስ የመራጮች ዝርዝር እንዲሰጣቸው ጫና እየፈጠሩ ነው
ለስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ እየተደረገ በሚገኘው ቅድመ ዝግጅት፣ የየራሳቸውን ‹ምርጥ› ይዘው የቡድን እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ያሉ አካላትን ያስተባብራሉ ለተባሉ ሦስት ሊቃነ ጳጳሳት መንግሥት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተሰማ፡፡ ማስጠንቀቂያው የተሰጣቸው ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ እና የምሥራቅ እና ምዕራብ ሐረርጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ናቸው፡፡

ለሐራዊ ምንጮች የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ለሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ማስጠንቀቂያው የተሰጣቸው ሰኞ፣ የካቲት 11 ቀን 2005 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ተጠርተው ሲኾን፣ ያነጋገሯቸውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ኀይለ ማርያም ደሳለኝና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አማካሪ አቶ ጸጋዬ በርሄ ናቸው፡፡ ባለሥልጣናቱ÷ የፓትርያሪክ ምርጫው ቤተ ክርስቲያኒቱ ባጸደቀችው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ ደንብ መሠረት ብቻ መፈጸም እንደሚገባው መናገራቸው ተዘግቧል፡፡ ‹‹የራሳችኹን ሕገ ደንብ አክብራችኹ መሥራት ሲያቅታኹ በመንግሥት ላይ የሚቀርበውን ሰበብ ማስቆም አለባችኹ፤ በየካፌው፣ በየሬስቶራንቱ፣ በየሆቴሉና በየልኳንዳ ቤቱ እየተሰበሰቡ የሚመክሩትንና የምታስተባብሯቸውን ቡድኖችም መግታትና መቆጣጠር አለባችኹ፤›› የሚል ማሳሰቢያ መስጠታቸው ተነግሯል፡፡
ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በምርጫው ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ቡድኖች ስለመኖራቸው በማመን አስተያየት መስጠታቸው ተመልክቷል፡፡ የተለያዩ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በቢሯቸውና በማረፊያቸው ሲያነጋግሩ የተለያየ ስምና መታወቂያ ይጠቀማሉ ስለሚባሉት የቡድኖቹ መሪዎችም ሊቃነ ጳጳሳቱ ሲያብራሩ፣ ‹‹የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት መታወቂያ የሚያሳዩና ከመንግሥት እንደተላኩ የሚናገሩ፣ መንግሥት እንዲመረጥ የሚፈልገው አቡነ እገሌን ነው፤ አቡነ እገሌን መምረጥ አለባችኹ፤ አቡነ እገሌን ካልመረጣችኹ የእገሌ ተቃዋሚ አባል ናችኹ ማለት ነው፣ እናሰራችኋለን፤ ከሥራ እናባርራችኋለን፤›› የሚሉ በመኾናቸውና ይህም በየዕለቱ የሚታዘቡት ጉዳይ በመኾኑ በመንግሥት ወደማማረር መድረሳቸውን አስረድተዋል ተብሏል፡፡
በዚህ ሳምንት ሰኞ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋራ የተደረገውን ውይይት ተከትሎ የመንግሥት ስቭል፣ ፖሊስና ወታደራዊ ደኅንነት ጥምር ግብረ ኀይል በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽር ውስጥ ለሁለት ቀናት ባካሄደው ክትትልና አሠሣ፣ በስመ ደኅንነት ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉ 40 ግለሰቦችን በትናትናው ዕለት በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ተዘግቧል፡፡ አሠሣው እኒህ ስመ ደኅንነቶች በየፊናቸው ከሚመሯቸው ቡድኖች (የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳትን ለፕትርክና በማጨት የተስማሙ የመነኰሳትና ካህናት ስብስቦች ናቸው) ጋራ ያዘወትሯቸዋል በሚባሉ ካፌዎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ሆቴሎችና ልኳንዳ ቤቶች ተጠናክሮ ቡድኖቹን የመበተንና የማስጠንቀቅ ሥራ ሲሠራ መዋሉ ተነግሯል፡፡
በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽርና ዙሪያ ሲንቀሳቀሱ በጥምር የደኅንነት ኀይሉ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት 40 ግለሰቦች መካከል 35ቱ ተይዘው ማንነታቸውን ሲጠይቁ ያሳዩት መታወቂያ ሐሰተኛ ኾኖ ተገኝቷል፤ የአምስቱ መታወቂያ ደግሞ ትክክለኛ ቢኾንም ከሚመለከተው አካል ትእዛዝ ሳይሰጣቸው ራሳቸውን ለቡድናዊ ጥቅም አሰማርተው መገኘታቸው ተረጋግጧል ተብሏል፤ አብዛኞቹ ከክልሎች የመጡ፣ በአንድ ወገን የተሰጣቸውን ቡድናዊ ተልእኮ ለማስፈጸም የሚላላኩ እንጂ የመንበረ ፓትርያሪኩን መግቢያና መውጫ በሮች እንኳ በቅጡ የማያውቁ መኾናቸው በቁጥጥር ሥር ሲውሉ በታየባቸው መርበትበትና ድንጋጤ ይበልጥ ራሳቸውን ያጋለጡ መኾኑ ተገልጧል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ወገኖች መንግሥት ‹‹ተጽዕኖ አላደረግኹም፤ ጣልቃ አልገባኹም›› ለማለት ያህል የወሰደው ርምጃ ሊኾን ይችላል በሚል መረጃውን በጥርጣሬ ይመለከቱታል፤ በአንጻሩ የምርጫው እንቅስቃሴ ከመንግሥት ቀጥተኛ እይታና ቁጥጥር ውጭ ሊኾን እንደማይችል ይከራከራሉ፡፡ ሌሎች ወገኖች ደግሞ መንግሥት በጥምር የደኅንነት ኀይሉ እያካሄደው ስለ መኾኑ የተዘገበው የቁጥጥር እንቀስቃሴ የየራሳቸውን ፓትርያሪክ አጭተው በመንበረ ፓትርያሪኩ የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች÷ በአንድ በኩል የመንግሥትን የጸጥታ፣ የደኅንነትና የመከላከያ መዋቅሮች ለሚሹት ዓላማ ለመጠቀም የሄዱበትን ርቀት (በመንግሥት ቋንቋ የኪራይ ሰብሳቢዎችን ትስስር) የሚያሳይ ሲኾን በሌላ በኩል ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ ክብሯን ለማስጠበቅ ካለመቻሏ የተነሣ የምትገኝበትን አስከፊ ተቋማዊ ውርደት/ዝቅጠት እንደሚያሳይ ተመልክቷል፡፡
በዚህ ዜና ርእሰ ጉዳይ እንደሰማነው ከቀድሞውም እንደሚታወቀው ሁሉ፣ የዚህ ተቋማዊ ውርደት መነሻዎች የእኛው ሊቃነ ጳጳሳት እንደኾኑ መጠቀሱ በእጅጉ የሚያሳፍር ነው፡፡ ቡድኖቹን በማንቀሳቀስ ረገድ÷ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ለብፁዕ አቡነ ማቲያስ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ‹‹ቀጣዩ ፓትርያሪክ ከወሎ መመረጥ አለበት፤ ጊዜው የወሎ ነው›› የሚለውን ቡድን (w – group) በመደገፍ ብፁዕ አቡነ ገብርኤልን ወይም ብፁዕ አቡነ ማቲያስ ዘካናዳን፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ደግሞ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤልን በመደገፍ ስማቸው ይነሣል፡፡ የድጋፉ ስለምንነት በተለይ ለመጀመሪያዎቹ ሁለቱ በዋናነት ከጎጠኝነት ጋራ የተያያዘ ቢኾንም ሁሉም በቀጣይ ስለሚያገኘው ሹመት፣ ሥራ ወይም የኾነ ዐይነት ግላዊና ቡድናዊ ጥቅም ወይም አንዱ ሌላው ላይ ስላለው ቂምና ጥላቻ መኾኑ ደግሞ በእጅጉ ከማሳፈርም አልፎ በእጅጉ ያሳዝናል፡፡
ሹመትና ሥራ ወይም የኾነ ዐይነት ሌላ ጥቅም ፈልጎ አሉታዊ የምርጫ ድጋፍ ማድረጉ፣ በቂምና ጥላቻ መነዳቱ በውጤቱ የሚገኘውን ሹመት መንፈሳዊ ወይም ከመንፈስ ቅዱስ ነው እንደማያሰኘው ግልጽ ነው፡፡ እስኪ ይህም ይኹን ብንል እንኳ፣ የየራሳቸውን ፓትርያሪክ አጭተው በየካፌው፣ በየሬስቶራንቱ፣ በየሆቴሉና በየልኳንዳው ተሰብስበው የሚዶልቱት የ‹መነኰሳት›፣ ‹ካህናት›ና ወይዛዝርት ስብስቦች ለሹመቱም ለሥራውም የሚታመኑ፣ የሚበቁም እንዳልኾኑ ባለፉት ዓመታት በሚገባ የምናውቃቸው ናቸው፡፡
‹‹አቡነ ማቲያስን ለማስመረጥ ቤቴንም ቢኾን እሸጣለኹ›› የሚሉት ወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ
ለአብነት ያህል÷ ‹‹መንግሥት የሚፈልገው አቡነ ማቲያስን ነው፤ አቡነ ማቲያስን መምረጥ አለባችኹ፤ አቡነ ማቲያስን ካልመረጣችኹ እናስራችኋለን፤ እናባርራችኋለን›› በሚል እየተንቀሳቀሱ ያሉት እነ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ፣ መጋቤ ካህናቱ ኀይለ ሥላሴ ዘማርያም እና ወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ ምን እያደረጉ ነው? ቡድናዊና ግላዊ ጥቅም፣ ቂምና ጥላቻ የሚገፋቸው እኒህ ግለሰቦች፣ ለፕትርክና ሊመረጡ ይችላሉ ያሏቸውን ሌሎች ብፁዓን አባቶች ስም በየሚዲያው የማጥፋት ዘመቻ ይዘዋል፤ ሚዲያውም ያለአንዳች ሚዛናዊነት የእነርሱን ክሥ ያስተጋባል (የዛሬው ሰንደቅ ጋዜጣ አንዱ ነው፤ በዛሬው ዕለትም እኚህ ሴትዮ በአድልዎና በሕገ ወጥ መንገድ ከያዟቸው የቤተ ክህነት ቤቶች መካከል አንዱ የኾነውንና በአራት ኪሎ የሚገኘውን ቀራንዮ የጉዞ ወኪል የከፈቱበትን ቢሮ የሰንደቅ ጋዜጣ ማከፋፈያ አስመስለውት ውለዋል)፡፡ በስመ ደኅንነት የሚንቀሳቀሱ ነገር ግን የጸጥታና ደኅንነት ባልደረቦች የሚመስሉ በርካታ በገንዘብ የተገዙ ግለሰቦች መንበረ ፓትርያሪኩን እንዲያጥለቀልቁ ያደረጉት በቀዳሚነት እነእጅጋየሁ ናቸው፡፡
እነንቡረ እድ ኤልያስ በአዲስ አበባ አራቱ አህጉረ ስብከት፣ በባሕር ዳር፣ በደሴ፣ በሐዋሳ፣ በድሬዳዋ፣ በአሰበ
ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ
ተፈሪና በጅጅጋ አህጉረ ስብከት ስልክ እየደወሉ ከጠቅላላው መራጭ ከ600 በላይ የሚኾኑ መራጮችን ስም ዝርዝር አሳውቁን እያሉ ጸሐፊዎችንና ሥራ አስኪያጆችን እያስገደዱና እያስፈራሩ ነው፡፡ በተወሰኑ አህጉረ ስብከትም ሥራ አስኪያጆቹ የካህናት፣ ገዳማትና አድባራት አበ ምኔቶችና እመ ምኔቶች እንዲሁም የምእመናን ተወካዮችን ሰብስበው ድምፅ መስጠት ያለባቸው ለአቡነ ማቲያስ መኾን እንደሚገባው በማሳሰቡ ረገድ ተሳክቶላቸዋል፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሁለት ጸሐፊዎችና ሥራ አስኪያጆች ለየሊቃነ ጳጳሳቱ ሪፖርት ያደረጉ ሲኾን ሊቃነ ጳጳሳቱ ብፁዕ አቡነ ዳንኤልና ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለእነ ንቡረ እድ ኤልያስና ለተላላኪዎቻቸው ስመ ደኅንነቶች ጠንከር ካለ ማሳሰቢያ ጋራ ምላሽ መስጠታቸው ታውቋል፡፡
የእነእጅጋየሁ ድፍረት በዚህ ብቻ የሚያበቃ ሳይኾን አስመራጮችን በግልጽ እስከማጨናነቅም የደረሰ መኾኑም ታውቋል፡፡ ለአስመራጭ ኮሚቴው ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደሚያስረዱት የሴትዮዋ ድፍረት፣ ‹‹አቡነ እገሌ በዕጩነት መካተት ወይም መመረጥ እንደማይገባቸው የሚያስረዱ መጣጥፎችን በኮሚቴው ስብሰባዎች ላይ ለማስነበብ እስከ መሞከር የደረሰ ነው፤›› ይላሉ፡፡ የመረጃ ምንጮቹ የአንባቢውን ማንነት ባይገልጡ ም ሙከራው የአስመራጭ ኮሚቴውን ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን አስደንግጧል፤ በተለይም የታዋቂ ምእመናን ተወካዮቹን እነ ቀኝ አዝማች ኀይሉ ቃለ ወልድንና አቶ ዓለማየሁ ተስፋዬን ክፉኛ አስቆጥቷል፡፡ ‹‹በስመ ደኅንነቶቹ ላይ የተወሰደው ርምጃ አስመራጭ ኮሚቴውን ሳያነቃቃው አልቀረም፤›› ይላሉ የዜናው ምንጮች፡፡
የኾነው ኾኖ ነገ፣ የካቲት 14 ቀን 2005 ዓ.ም የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ አጣርቶ የመረጣቸውን አባቶች ለቋሚ ቅ/ሲኖዶሱ የሚያቀርብበት ዕለት ነው፡፡ እስከ ትላንት ምሽት በነበረን መረጃ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል፣ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል እና ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ከካህናትና ምእመናን በተሰበሰቡ ጥቆማዎች ብዛት ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸው ታውቋል፡፡
ቀደም ባስነበብነው ዘገባ እንዳስረገጥነው፣ በብዙ ዕጩዎች መጠቆም ለፓትርያሪክነት መታጨትን ወይም ለፓትርያሪክነት መመረጥን አያረጋግጥም፡፡ የአስመራጭ ኮሚቴው መግለጫ ደጋግሞ እንደሚያሳስበው የጥቆማው መረጃዎች ለዕጩዎች መለያ እንደ ግብአት ብቻ የሚያገለግል ነው፤ ዕጩዎቹ እነማን እንደሚኾኑ የሚታወቁት ቅ/ሲኖዶስ በነገው ዕለት ከኮሚቴው ተለይተው በሚቀርቡለት አባቶች ላይ ተወያይቶ ስማቸውን በብዙኀን መገናኛ ይፋ ሲያደርግ ብቻ ነው፤ ፓትርያሪኩም የሚታወቀው የካቲት 21 ቀን በሚሰጠው የመራጮች ድምፅ ብቻ ነው፡፡