Sunday, October 25, 2015

የህወሃት ባለስልጣናት በከፍተኛ ደረጃ ዶላር እያሸሹ ነው

October 25, 2015

በሰሜን አሜሪካ በህግ ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ለአንድ ዶላር በ23 ብር እየቀየሩ ሃብታቸውን በማካበት ላይ እንደሚገኙ ታወቀ።
የኢህአደግ ስረአት ባለ ስልጣኖች ሃብታቸውን ከውስጥ ሃገር ለማውጣት እየተጠቀሙት ያለውን ስልት የኢትዮጵያ ባንኮዎች ከመጉዳት ባለፍ በአሁኑ ወቅት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ከባድ ችግር ውስጥ አስገብተውት እንደሚገኙ የገለጸው መረጃ: በአሁን ጊዜ የኢህአዴግ ባለ ስልጣኖች በሙስና ያጠራቀሙት ሃብት ወደ ዉጭ በማጓጓዝ ላይ ተጠምደው ባሉበት ግዜ ከሰሜን አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ከመጠን በላይ በኮትሮ ባንድ ንግድ ለአንድ ዶላር በ23 ብር እንመነዝርላችሓለን በማለት በህዝብ ሃብት በመጫወት ላይ ኣንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
TPLF Ethiopian Leaders
መረጃው አክለዉ እንዳመለከተው በአሁኑ ጊዜ፡ በዋሽንግተን፤ በዱሲ፤ ስያትል፤ ዴንቭር፤ ሚኒያፖሊስ፤ አትላንታ፥ ቺካጎ፤ በሂውስተን፤ ኦሃዮ፤ ፓርትላንድ፤ ላስቬጋስ፤ ካልፎርኒያ እንዲዚሁም በተለያዩ ከተሞች በአሪዞና በተዘረጉት መረቦች መረጃ ዶላር በኮትሮ ባንድ ንግድ በ23ብር እየተመነዘር መሆኑን መረጃው አስታውቀዋል።
በመጨረሻም አንድ የአሜሪካ ዶላር በህጋዊ መንገድ ብ20.85 ብር እየተመነዘር ቢሆንም በሌቦች የኢህአድግ የገዢው ስረአት ባለ ስልጣናት ግን ዶላር ያለ ህጋዊ መንገድ የኢትዮጵያ የውጪ ምንዛሬ ያለ አግባብበ በመቀየራቸው የተነሳ የሃገር ውስጥ መንዛሪ ከፋተኛ እጥርት እያጋጠመ እንዳለ የተለያዩ ህዝቦች በመግለፀ ላይ ይገኛሉ::

Friday, October 23, 2015

እናመሰግናለን! የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

October 23, 2015
Thank You! Zone9 bloggers
በድንገት ከያለንበት ተይዘን እንደታሰርነው አፈታታችንም ግራ የሚያጋባ ነበር፡፡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበውብን እያለ ግማሾቻችን ‹ክስ ተቋርጦላችኋል› ተብለን ተፈታን፣ ግማሾቻችን ደግሞ ‹ነፃ ናችሁ› (ከሳሽ በነፃነታችን ላይ ይግባኝ መጠየቁ እንዳለ ሁኖ) ተብለን ይሄው ወጥተናል፡፡ ቀሪ ክስ ይዘን በዋስ ወጥተን እየተከራከርንም ያለን አለን፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል የሁላችንም ዕምነት ግን አንድም ቀን ሊያሳስረን የሚገባ ወንጀል አለመፈፃችን ማመናችን ነው፡፡ መፈታታችን ጥሩ ሁኖ፤ መታሰር በፍፁም የማይገባን ነበርን፡፡ መፃፋችን እና ሕግ እንዲከበር መጠየቃችን ሀገሪቱ አገራችን እንድትሻሻል እና ሁላችንም ዜጎች የተሻለ ህይወት አንዲኖራቸው ከመሻት ባለፈ ሌላ ነገር አልነበረውም/የለውም፡፡ ነገር ግን ይህን በማድረጋችን ተገርፈናል፣ ተዘልፈን-ተሰድበናል፣ ታስረናል ተሰደናልም፡፡ ይህ በፍጹም አይገባንም ነበር፡፡
የእኛ መታሰር ፖለቲካዊ ንቃት የፈጠረላቸው ሰዎች እንዳሉ ሲነግሩን ደስ ይለናል፡፡ በእኛ መታሰር ምክንያት ለመጠየቅና ለመፃፍ በጣም እንደሚፈሩ የሚነግሩን ሰዎች ስናገኝ ደግሞ እናዝናለን፡፡ የመታሰራችን ጉራማይሌ ስሜት እንደዚህ ነው፡፡ ሳይገባን በመታሰራችን የነቁ መኖራቸውን በማወቃችን የምነደሰተውን ያክል፤ ሳይገባን በመታሰራችን የተሰበሩና ከተዋስኦ መድረኩ የራቁ እንዳሉ ስናውቅ እጅግ እናዝናለን፡፡
መታሰር በደል ነው፡፡ ብዙ ነገር ያጎድላል፡፡ መታሰር መልካም ነው፡፡ ብዙ ነገር ያስተምራል፡፡ እኛ በመታሰራችን ሀገራችን የበለጠ እንድናውቃት ሁነናል፡፡ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ ነፃነት አሁንም ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፍል ተረድተናል፡፡ ሕግን መከታ አድርገው የኖሩ ‹ስም የለሽ› ዜጎች ሕጉ ሲከዳቸውና እነሱ ላይ ‹በላ› ሲያመጣባቸው ታዝበናል፡፡ ከሁሉም በላይ ፍትህ የሌለባት ሀገር ለዜጎቿ የማትመችና አገር እንደሆነች አይተናል፡፡
በእስራችን ወቅት የተለያዩ በደሎች በተቋም ደረጃ ደርሰውብናል፡፡ ግን አገር ነውና ከይቅርታ የሚያልፍ አይደለም፡፡ ለበደላችሁን አካላት እናንተ ይቅርታ ባትጠይቁንም፤ እናንተ የፈለጋችሁትን ባለማድረጋችንና ሕግን መሰረት አድርገን በመኖራችን ስላስከፋናችሁ እባካችሁ ይቅር በሉን፡፡
በዚህ ሁሉ መሃል ግን እናንተ አላችሁ፡፡ ጓደኞቻችንም ናችሁ፤ ዘመቻ አድራጊዎችም ናችሁ፤ ቤተሰቦቻችንም ናችሁ፤ ጠያቂዎቻችንም ናችሁ፤ ጠበቆቻችንም ናችሁ፣ የመንፈስ አጋሮቻችንም ናችሁ ርቀት ሳይገድባች የጮሃችሁልን አለም አቀፍ የመብት ጠያቂዎችም ናችሁ … በመታሰራችን የተረዳነው አንዱ ትልቅ ነገር የናንተን መልካምነት፣ የናንተን አጋርነት እና የናንተን የማይሰለች ድካምና ፍቅር ነው፡፡ እናንተ ባትኖሩ ‹አጭሩ› የእስር ጊዜያችን ይረዝምብን ነበር፤ ‹ቀላሏ› እስር ትከብድብን ነበር፡፡ ምስጋና ለናንተ፤ እስራችን ‹አጭር› – ፈተናችን ‹ቀላል› እንዲሆን አድርጋችሁልናልና፡፡
እናንተ ወዳጆቻችን ለሁሉም ነገር – እልፍ ምስጋና
እናመሰግናለን!
የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

Wednesday, October 21, 2015

ሶማሊያ የሚገኙ የጦር ሠራዊት አባላት ሲበደሉ ያመናል !

October 21, 2015
def-thumbየተባበሩት መንግሥታት ማኅበር የሚሰጠው ገንዘብ ህሊናቸውን በሰወራቸው፤ የህወሓት አባላት በሆኑ ጄኔራሎች አዝማችነት ሶማሊያ የገባው ኢትዮጵያዊ ድሃ ወታደር እጣ ፈንታ በጣም አሳዛኝ ደረጃ ላይ ደርሷል። በየእለቱ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች እየተገደሉ፤ አስከሬናቸው በጎዳናዎች እየተጎተተና እየተቃጠለ ነው። ሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ወገኖቻችን ናቸውና በእነርሱ ላይ የሚደርሰው ስቃይ ይሰማናል፤ ሲበደሉ ያመናል፤ ጭንቀታቸው ይጨንቀናል። ወገኖቻችን ናቸውና የደህንነታቸው ጉዳይ ያገባናል።
የህወሓት ጄኔራሎች ሙሉ ትኩረታቸው ያለው በእያንዳንዱ ወታደር ስም ከተባበሩት መንግሥታት በሚያገኙት ገንዘብ መጠን ላይ ነው። ለሶስት ሣምንታት ብለው የገቡበት ጦርነት እነሆ አስር ዓመታት አስቆጥሯል። አንዱ የገቢያቸው ምንጭ ነውና ጦርነቱ ለሌላ አስር ዓመታት ቢራዘም ለእነሱ ደስታቸው ነው። ኢትዮጵያዊው ምስኪን ወታደር ግን አዛዦቹ እንዲያልቅ በማይፈልጉት ጦርነት ውስጥ ገብቶ መስዋዕትነት ይከፍላል፤ ሲወድቅ የሚያነሳው የለም፤ መስዋዕት ሲሆን የክብር አሸናኘት የለውም፤ ቤተሰቦቹም ይኑር ይሙት አያውቁም። ይህ ሁላችንንም ሊያስቆጣ የሚገባ ግፍ ነው።
ኢትዮጵያን ለመታደግ ብሎ የዘመተን ወታደር ስለኢትዮጵያ ግድ በማይሰጣቸው፤ ጥቅማቸውን ብቻ በማሳደድ ላይ ያሉ አዛዦች ቸልተኝነት ምክንያት ለስቃይ፣ ሰቆቃና ውርደት መዳረግ የለበትም። በሶማሊያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ የሚደርሰው በደል በሁላችም ላይ የደረሰ በደል ነው፤ በእነርሱ ስብዕና ላይ እየደረሰ ያለው ውርደት በአገራችን ላይ የደረሰ ውርደት ነው።
የጦሩ አዛዦቹ በወታደሩ ስቃይና ሞት ከብረው የከተማ ድሆችን እያፈናቀሉ ሕንፃዎችን እየገነቡ፤ የባንኩን፣ የኢንሹራንሱን፣ የገቢና ወጪ ንግዱን እያጧጧፉ ነው። የወታደር ልብስ ቢለብሱም፤ “ጄኔራል እከሌ” ተብለው ቢጠሩም በተግባር መጥፎ ነጋዴዎች እንጂ ወታደሮች አይደሉም። እነዚህ የስም ጄኔራሎች በጦርነት ውስጥም የሚታያቸው ንግድና ገበያ ነው። በእንደነዚህ ዓይነቶች አዛዦች ተመርቶ ጦርነትን ማሸነፍ አይቻልም።
አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በህወሓት የጦር አዛዦች ብቃት ማነስ፣ ስግብግብነትና ቸልተኝነት ሳቢያ በሶማሊያ እየሞቱ፣ እየቆሰሉ፣ አስከሬናቸው እየተዋረደ ስላለው ኢትዮጵታዊያን የሚሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ከሶማሊያ ውጭም የኢትዮጵያ ወታደር የሚገኝበት ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ ነው። በተለይም በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደር እንደ ስሙ “የአገር መከላከያ ሠራዊት” በመሆን ፋንታ ወገንን ማጥቂያ ሠራዊት እየሆነ ነው፤ አገርን በመከላከል ፋንታ ወገንን ማጥቃት የሠራዊቱ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኗል። ለዚህ አሳፋሪ ተግባር ሠራዊቱ ራሱ መላ ሊፈልግለት ይገባል።
አርበኞች ግንቦት 7 እየታገለ ያለው ሠራዊቱን ከሚገኝበት ከዚህ አሳፋሪ ሁኔታ ለማውጣትም ጭምር ነው። ሠራዊቱ የአዛዦቹ መገልገያ መሣሪያ መሆኑ ማብቃት አለበት። ሠራዊቱ ወገንን ማጥቂያ መሆኑ ማክተም አለበት። ሠራዊቱ ወደ ውጭ አገራት ለግዳጅ ሲላክ ተገቢውን ክብር ሊሰጠው፤ ጥቅማ ጥቅሞቹም ሳይሸራረፉ ሊያገኝ ይገባል። የሠራዊቱ አባላት እየደኸዩ፣ ቤተሰቦቻቸው እየተራቡና እየታረዙ አዛዦቹ በሀብት ላይ ሀብት የሚያጋብሱበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። ይህ አዋራጅ የሠራዊት አያያዝ መቀየር አለበት፤ መቀየር ደግሞ ይቻላል።
እያንዳንዱ የሠራዊት አባል በግል የጠራ ፀረ-ህወሓት አገዛዝ አቋም ይያዝ፤ ከሚመስሉት ወዳጆቹ ጋር ውስጥ ውስጡን ይምከር፤ አርበኞች ግንቦት 7 ጋር የምስጢር ግኑኝነት ለመመስረት ይጣር፤ ጦሩ ውስጥ እያለ ሥርዓቱን የሚዳክሙ ተግባራትን ይፈጽም። ህወሓትን ለማዳከም የሚደረግ ጥረት ትንሹም ትልቅ ዋጋ አለው። ሠራዊቱ የህወሓት መገልገያ አለመሆኑ ማስመስከሪያ ወቅት አሁን ነው። የህወሓት አምባገነን አገዛዝን ከውስጥም ከውጭም ሆነን እንፋለመዋለን፤ እንደምናሸንፍ ጥርጥር የለውም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ወያኔ የኑሮ ውድነት ለመደበቅ ቢሞክርም ሊደበቅ አልቻልም፣

October 21, 2015
በሃገራችን በኢሀዴግ ስረአት ብልሹነት ምክንያት የተነሳ የህዝባችን የኑሮ ውድነት ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሰና በተለይም ዝቅተኛ የኢኮኖሚ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ካለው የገበያ ውደነትና የሚፈለገው የእህል አይነት ባለ ማገኘታቸው በረሃብና በችግር ውስጥ ሆነው ኑራቸውን ይመራሉ።
ይሁን እንጂ የሃገሪቱ መሪ ተብየው የኢህአዴግ ሰረአት በተለያየ ቦታዎች የሚገኙ ህዝብ በቂ ምርት ባለ መኖሩ የፈጠረዉ ዋጋ ግሽበት እየተሰቃየ ባለበት ውቅት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በዕደገት ጎዳና ላይ እየገሰገስን ነው በማለት በሞተ ቃላት ሲናገር ይሰማል።
በተለይም በአሁን ሰአት ከዝናብ መጥፋት ጋር ተያይዞ በርካታ ዜጎች በቤታቸው ውስጥ እየሞቱ ምንም አይነት የመንግሰት ደጋፍ ያለመደረጉ እንዲሁም በተለያየ የሃገሪቱ ክፍል ከግዜ ወደ ግዜ በፍጠነት እየተባባሰ ያለዉ ኑሮ ዉድነት ትኩረት ሳይሰጠው ህዝባችን አልተቸገረም እያለ በቴሌቭዥን መስኮት መናገሩ ለህዝብ ያልቆመ መንግስት መሆኑን አሰረጂ ነገር ስለ ሆነ ህዝብ በገዡዉ የኢህኣዴግ ስርዓት ያለው እምነት ሙሉ በሙሉ ተሟጦ ተስፋ ቆርጦ ይገኛል።
በተግባር በመስራት ሳይሆን በማሰመሰል የሚታውቀው የኢህአደግ ስርአት ህዝብ በልመና በየመንገዱ ሴት ወንድ ትንሸ ትልቅ ሳይል በየሁቴል ቤቱ የተረፈ ምግብ ለመግዛት ወረፋ ይዞ መገኘቱ የሃገሪቱ የኢኮኖሚ ውድቀትን አመላካች መሆኑን ያስገነዝባል።
ሆኖም ተጎጅው ህብረተሰብ ችግሩን በተደጋጋሚ ቢናገርም ሰሚ አካል ያለማገኘቱ ብሶቱንና ሀዘኑ ከባድ እንዲሆን አድርጎት እያለ ባለሃብቶቹ ደግሞ ደስ ባላቸው ዋጋ በገበያ እየሸጡ በድሃው ህዝብ ላይ የሚፈልጉትን ያህል ዋጋ ስለሚጩንበት ህብረተሰቡ ለመግዛት ከአቅሙ በላይ ሆኖበት በችጋርና ረሃብ እየተሰቃየ ይገኛል።
የመንግሰት ሰራተኛ በተመለከተ ከሚከፈለው ገንዘብ ማነስ የተነሳ የወር ክፋያው የእህል መግዣ የወጥ (ማተሪያል) ማለትም የሽንኩርት የዘይት የመሳሰሉ ለሟሟላት አቅም ባለመኖሩ ምክንያት የሚከፈለው የቤት ኪራይ በማጣቱ ወደ ሌላ ሁለተኛ ሃገር በመሰደደ ላይ ይገኛል።
ስለ ሆነም የኢህአደግ ሰረአት ህዝባችንን በቀን ሶሰት ግዜ መመገብ ችለናል እያለ በየመድረኩ በባዶ ቃላት ለብዙ አመታት እየተናገረ ቢሆኑም ህዝብ ግን በተፈጠረው የኑሮ ወድነት የተነሳ መሬቱን ተረከቡኝ ግብር መከፈል አልቻልኩም በማለት በመንግሰት ላይ ያለውን ተቃውሞ በመግለጽ ላይ ይገኛል።
ሰሞኑን የኢህአደግ አመራሮዎች በአዲስ አበባ አንድ የእህል መጋዘን ባደረጉት የገበያ ጉብኝት ለህዝብ በሰጡት መልስ ምንም አይነት የዋጋ ውደነት የለም ሲሉ ተሰምተዋል ተጠቃሚው ህዝብ ግን ይህ የተሰጠው ምላሸ እጅግ አድረጎ እንዳሰቆጣው ለመረዳት ተችሏል።
ህብረተሰቡ ገንቢ የሆኑ ምግቦችን ማለትም እንደ ስጋ ቅቤ መጠቀም ከተው ብዙ አመት ያስቀጠረ በመሆኑና በየክልሉ እና በአዲሰ አበባ ከተማ የሚገኙ የምግብ ቤቶች የሚሰሩ ባለሃብቶች ተጠቃሚ ካለመኖሩ የተነሳ በተጨማሪም ችግሩ እየተባባሰ በመሄዱ ምግብ ቤታቸውን ለመዝጋት ተገደዋል።

Tuesday, October 20, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አስመረቀ

October 20, 2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ
Professor Berhanu Nega with Patriotic Ginbot7 fighters
አርበኞች ግንቦት 7 በሁለት ድርጅቶች ማለትም በኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና በግንቦት 7 ንቅናቄ ውህደት ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ከተመሰረተ በኋላ ከትናትና በፊት እሁድ ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም ለሁለተኛ ጊዜ ብዛት ያላቸውን አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ወራት አሰልጥኖ አስመርቋል፡፡
እነዚህ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሁለተኛ ዙር ተመራቂ አርበኛ ታጋዮች ለሦስት ተከታታይ ወራት የተሰጣቸውን የፖለቲካ፣ የወታደራዊ እና ሌሎች ተያያዥ የሆኑ የመረጃና ደህንነት ትምህርቶችን በሚገባ ወስደው በሁሉም መስክ አመርቂ ውጤት በማስመዝገብ ነው ሊመረቁ የቻሉት፡፡
እጅግ በጣም ደማቅ በሆነ ስነ-ስርዓት በተከናወነው የምረቃ በዓል ላይ ከተለያዩ ቦታዎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች የታደሙ ሲሆን የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር አርበኛ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የድርጅቱ የትምህርትና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ታጋይ ተስፋሁን ተገኝ ንግግር በማሰማት ለተመራቂ አርበኛ ታጋዮች መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከውህደቱ ኋላ የመጀመሪያውን ዙር ሰልጣኞች ያስመረቀው ግንቦት 2 ቀን 2007 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል፡፡
Patriotic Ginbot7 fighters

Monday, October 19, 2015

የማእከላዊ ምርመራ የማሰቃየት ምርመራ መዘዝ - በጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ላይ

October 19,2015
የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መቃረብን ተከትሎ መስዋእት ከሆኑት  የዞን ዘጠኝ ጦማር አባላት ውስጥ የሽብር ክሱ ወደ ወንጀል ክስ ተቀይሮ ዛሬም በግፍ እስር በብቸኝነት የሚገኘው በፍቃዱ ዘ ኃይሉ አመጽ ለመቀስቀስ አስበህ ነው የጻፍከው የተባለውን ጽሁፍ እንዲከላከል ተወስኖበታል፡፡ ይህ የአመጽ መቀስቀስ የተባለው ጽሁፍ ራሱን ሳይሆን የበፍቃዱን የማእከላዊ ምርመራ ቃል ብቻ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ቃሉን ብቻ መሰረት በማድረግ ይከላከል በማለት የማእላዊ ምርመራን በማሰቃየት ውስጥ የተሰጠ ቃል ተቀብሎታል ማለት ነው ?

በአስገዳጅ ሁኔታ የተገኘ ማስረጃ እንደማስረጃ አይቆጠርም የሚለው የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው የሚገባለው እና በፍቃዱ ከጓዶቹ ጋር ሆኖ ይከበር! ሲል የነበረው ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 19.5 እንዲህ ይላል

‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ  በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችልየእምነት ቃል እንዲሰጡ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም፡፡ በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነትአይኖረውም፡፡››

ከወራት በፊት የጦማርያኑን እስር አንደኛ ዓመት አስመልክቶ የመብት ጥሰቶችን ዞን ዘጠኝ ጦማር ባስታወሰበት ወቅት በበፍቃዱ የደረሰበት የማሰቃየት ወንጀል እንዲህ ገልጾት ነበር ፡፡

‹‹ማዕከላዊ ምርመራ በቆየሁባቸው ቀናት ከእሁድ በስተቀር ጠዋት ከሰአትማታ እየተጠራሁ በዛቻ በአጸያፊ ስድብ ጭካኔ የተሞላበት ግርፊያ ጥፊና እርግጫ አንዲሁም ከአቅሜ በላይ የሆነ ስፓርት እየሰራሁቃሌን እንድሰጥ ተገድጃለሁ፡፡ የተያዝክበትን ድብቅ አጀንዳ ንገረን በማለት ራሴን እንድወነጅል ተገድጃለሁ፡፡
  1. መርማሪው በመጀመሪያ ቀን ምርመራ በጥፊ መማታት የጀመረ ሲሆን እያንዳንዱን ጥያቄ ከጠየቀኝ በኋላ በጥፊ ይመታኝ ነበር
  2. የዞን9 ዓላማ ጠይቆኝ ስነግረው ድብቁን አውጣ በማለት መሬት ላይ አንድቀመጥ እና ያደረኩትን ነጠላ ጫማ እንዳወልቅ አዞኝ በኮምፒውተር ገመድ እግሬን መግረፍ ጀመረ፡፡ በተጨማሪም በሆዴአንተኛ በማዘዝ እና እግሬን አጥፌ ከፍ አንዳደርገው በማድረግ ውስጥ እግሬን ገርፎኛል፣ግርፊያው ውስጥ እግሬን ሲለበልበኝ ነበር ፡፡
  3. ድብቁን አጀንዳህን ካልተናገርክ ነገ እዘለዝልሃለሁ በሚል አስፈራርቶኛል፡፡
  4. ድምጽ እንዲያፍን ሆኖ ወደተሰራው የስብሰባ አዳራሽ ተወስጄ በጥፌ እየደበደቡኝ የዞን9አላማ ተናገር ተብዬ ተደብድቤያለሁ፡፡ ስቃዬ ሲበዛብኝም የፈጠራ ታሪክ እንዳወራ ተገድጃለሁ፡፡ እኔ የምጽፈው ኢትዮጵያ ውስጥ አብዬት ለማስነሳት ነው ብዬ እንድፈርምም አስገድደውኛል››
  5. በምርመራ ወቅት እጄ በካቴና እነደታሰረ ለሰአታት ቁጭ ብድግ አንድል ተገድጃለሁ፡፡
  6. መርማሪው በአንድ ወቅት አራት የዞን9 አባላት ሆናችሁ ስለአላማው የተወያያችሁትን በቃል መስጫው ክስ ላይ ልጽፍ ነው ሲለኝ አንደዛ አይነት ውይይት ማድረጋችንን አላስታውስም ስለው እንዴት አታስታውስም ብሎ በጥፊ መማታት ጀመረ። በተደጋጋሚ ከመደብደብም በላይ እስክስታስታውስ እዚሁ ታድራታለህ በማለት ድብደባው በመቀጠሉ አስታውሳለሁ ብዬ ተገላገልኩ ፡፡ የሰጠሁት ቃል ላይም እንደፈለገው አድርጎ ጻፈው፡፡  እኔም በድብደባ ብዛት መርማሪው አለ ብሎየጻፈውን ፈርሜያለሁ ፡፡
  7. ዞን9 ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የሌለው ከሆነ ይህንን ህዝብ አንዴት ነው ነጻ የምታወጡት በሚል ሲጠይቁኝ የነጻ አውጪነት ሚና የለንም ስላቸው ከወንበሬአንድነሳ አዘዙኝ፡ ከዚያም በቆምኩበት ግራ ብብቴን እና እጄን በአንድ እጁ አንዳልወድቅ ወጥሮ ይዞ በእግሩ ጭኔን በሃይል ደበደበኝ ፡፡ ከድብደባው በማስከተል ደግሞእግሬ መሃል እግሩን በማስገባት ወደግራ እና ወደቀኝ በመምታት ተዘርጥጬ እንድቆይ በማድረግ እጄን ወደላይ አድርጌ እግሬ ግራና ቀኝ ተዘርጥጦ ( በተ<a></a>ለምዶ ስፕሊት ሚባለው) በግራ እና ከቀኝ በመደብደብ እጄን ወደላይ አድርጌ እነድመረመር ተደርጌያለሁ፡፡ከዚህ ምርመራ በኋላ ለሁለት ቀን እያነከሰኩ ነበር፡፡››
በፍቃዱ ሃሳቡን በነጻነት በመግለጹ ብቻ እንደወንጀለኛ ተቆጥሮ እስካሁንለ542 ቀናት አግባብ ባልሆነ እስር ላይ ይገኛል፣ በዚህ ሁኔታ የተሰጠ ቃል ተቀባይነት ማግኘት ስለማይገባው በፍቃዱ ሃይሉእሮብ ከቤተሰቡ ጋር ሊቀላቀል ይገባል ፡፡

A Government-in-Exile for Ethiopia?

October 19,2015
by Alemayehu G. Mariam
Foreword to a “government-in-exile for Ethiopia”A Government-in-Exile for Ethiopia?
A few weeks ago, I gave an interview to an Ethiopian civic group on the topic of “government in exile” under international law.
I was asked to comment on whether the idea and practice of “government in exile” is cognizable under international law.
The implicit question was whether Ethiopians could constitute a legitimate “government-in-exile” in opposition to the Thugtatorship of the Tigrean People’s Liberation Front (T-TPLF) lording over Ethiopia today.
A word or two on the aim of this commentary.
The aim of my analysis here is not to endorse or discredit a particular group planning or purporting to be a “government-in-exile” for Ethiopia.  Nor is it my aim to make a political point against the T-TPLF and show my opposition to their regime, their endless crimes against humanity, their bottomless corruption, their ignorant arrogance and sheer incompetence as a governance body.
I have done that with ferocious tenacity every Monday over the past nine years.
The aim of my commentary is to shed light on a question of broad interest among Ethiopians from my legal perspective.
As a defense lawyer, I have a particular perspective on legal issues. I do not pretend to be an impartial judge.
I am a highly partisan advocate for the causes I support.
But as an academic and human rights advocate, my commitment is to the unvarnished truth, impartial justice and the defense of the rights of humans against tyrants.
That’s why I proudly proclaim in the tagline of my website, “Defend human rights. Speak truth to power.”
For the last nine years, I have been speaking truth to users, abusers and misusers power in Ethiopia, in Africa and elsewhere.
To paraphrase George Bush, “I make no distinction between the abusers and misusers of power who commit crimes against humanity in Ethiopia and the hypocrites who harbor and support them.”
I have come to believe that the root of all evil and suffering in the world is ultimately the abuse of political power and the power to abuse political power. Not money.
That is why I will advocate with the same intensity for Syrian refugees suffering under the Assad/ISIL/ISIS regimes as I would for Ethiopians suffering under the T-TPLF.
My concern for human dignity is not tied necessarily to any particular nationality, but to humanity.
As I like to say, it is not about the nationality of the man or the woman but the huMANity of the man and woman.
As most of my readers have known for nearly a decade, I would not have been involved in Ethiopian politics or human rights advocacy but for the Meles Massacres of 2005.

Friday, October 16, 2015

ውሸት ውሎ አድሮ መጋለጡ አይቀርም!!!

October 16, 2015
def-thumbሥልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ ተቆጣጥሮ ያለው የወያኔ አገዛዝ ካለመታከት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ተአምር ሊመስል በሚችል  መንገድ እያሳደኩ ነው እያለ ሲዋሽ አመታት ተቆጥረዋል። በተለይ ምዕራባዊያንን ሲያታልልበት የነበረው የዲሞክራሲ ጭንብል በምርጫ 97 ከተገፈፈበት ወዲህ ላለፉት አስር አመታት ባለ ሁለት አሃዝ እድገት አስመዝግቤያለሁ እያለ እጅ  እጅ እስኪለን ድረስ በባዶ ሜዳ ስለ ልማትና የዕድገት ሲነግረን ሰነበቷል።
ወያኔ በጉልበት በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ የልማትና የእድገት ፕሮፓጋንዳ ስለ ሰበአዊ መብትና ስለዲሞክራሲ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለማፈኛና አፍ ለማዘጊያነት በማገልገል ላይ ይገኛል ። አለማቀፍ የሰባአዊ መብት ተቋማት ስለሰበአዊ መብት ጥሰት ለሚያቀርቡት አቤቱታ ሁሉ የሚሰጠው መልስ “ኢኮኖሚውን እያሳደግን ነው” የሚል ነው። ኢኮኖሚ ማደግ አለማደጉን ትርጉም የሚኖረው ከህዝብ የእለተ ተእለት ኑሮ ጋር ሲያያዝ መሆኑ ሁሉ  ትርጉም አጥቷል። ራበኝ የሚለው ሰው ሁሉ ጠገብኩ ማለቱ ነው ተብሎም ይተረጎማል።
የውሸት ነገር ውሎ አድሮም ቢሆን መጋለጡ አይቀርምና ይኼው በቅርቡ የተከሰተው ድርቅ የወያኔን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ክንብንብ ገፎታል። አለም በሙሉ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ ሲያድግ የነበረ ኢኮኖሚ ባለበት ሃገር ውስጥ አንዲት የድርቅ አመት ካለርሃብና ልመና እንዴት መሻገር አቃተው የሚል ጥያቄ በሰፊው በማንሳት ላይ ነው። ወያኔ ለዚህ ጥያቄ መልስ የለውም።  በአለም ዙሪያ ያለው ተመክሮ ሁሉ የሚያሳየው ወያኔ አድጌበታለሁ ብሎ ሲለፍፍ ከኖረው አሃዝ በታች በግማሽ ያደጉ ሃገሮች እንኳ አንድም ጊዜ አንድ የድርቅ ዘመን መሻገር አቅቶአቸው  ሲንገዳገዱና መንግሥታቸው ለልመና ሲሄድ አለመታየቱን ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ የሚያወራውን ያህል ያልሆነ ቢሆንም በአንዳንድ ከተሞች አካባቢ የሚታየው እድገት የተገኘው ከውጭ መንግስታት የገንዘብ ብድር፣ በአለም አቀፍ ተቋማት እርዳታ፣ ስደተኛው ኢትዮጵያዊ በገፍ በሚልከው ገንዘብና ወያኔ ከድሃውና ከነጋዴው ከዝርፊያ ባላነሰ ሁኔታ በሚሰበሰበው ግብርና መዋጮ የተገኘ እንጂ ወያኔ ባስፋፋው ኢንዱስትሪና ልማት እንዲሁም ሀገር ውስጥ በፈጠረው ሀብት አለመሆኑ የሚታወቅ ነው።
የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮች ሀብት በሀብት መሆናቸውን እንደ እድገት ካልቆጠርን በስተቀር  ህዝባችን ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮውን እንኳን መደጎም አልቻለም ።በዝርፊያ ገንዘብ ሹማምንቱና የወያኔ ባለምዋሎች የገነቡትን ፎቅ የሀገር ልማት ነው ካላልን በስተቀር እውነተኛና የህዝብ ህይወት ከመሰረቱ የሚቀይር ልማት አገር ውስጥ አለመካሄዱ ትንሽ ገለጥ ሲያደርጉት የሚታይ ሃቅ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት መሻገር አቅቶት ብዙ ሚሊዮኖችን ከረሃብና እልቂት መታደግ ያልቻለ ኢኮኖሚ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ አድጓል ብሎ የሚያምን ሰው ሊኖር አይችልም።
የወያኔ የኢኮኖሚ አሃዝ “መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ” ከሚለው የሀገራችን ግፈኛ አባባል  ብዙም አይለይም። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለህዝብ በሚጠቅም መንገድ የማደጉ ጉዳይ በመጀመሪያ ፍትሐዊ ኢኮኖሚያዊ ሥርአት መገንባትንና ዴሞክራሲ ማስፈንን ይጠይቃል።
በመሆኑም የዛሬው የወያኔ ኢኮኖሚ የዝርፊያ ኢኮኖሚ እንጂ ህዝባዊ ሽታ የለውም። የኢትዮጵያን ህዝብ እዚህና እዚያ በሚብለጨለጩ ያውም በአብዛኛው በብድርና እርዳታ በተገኙ ልማት ተብዬ ነገሮች ለረዥም ጊዜ ማታለል አይቻልም።
ወያኔ በሚሰጠው አሃዝ የሚያድግ ማንኛውም ሀገር የውጭ ስደተኞችን ያስተናግድ እንደሆን እንጂ ወጣቶች ሞትና ህይወትን አማራጭ አድርገው አይሰደዱበትም። ባለ ሁለት አሃዝ አዳጊ ኢኮኖሚ በየትም ሀገር የስደተኞች ምንጭ ሆኖ ታይቶ አይታወቅም በዘረኛው ወያኔ ተገዢዋ ኢትዮጵያ ካልሆነ በስተቀር።
አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ትንሳኤ ከዘራፊው የወያኔ ሥርዐት መወገድ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን ያምናል!  ስለዚህም ህዝባችን ወያኔን ለማስወገድ የተጀመረውን ትግል በነቂስ ለመቀላቀል ዛሬውኑ እንዲነሳና ከጎናችን እንዲሰለፍ የማያቋርጥ ጥሪውን ደግሞ ደጋግሞ ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Wednesday, October 14, 2015

Journalism in Ethiopian Context

October 14, 2015
by Tewedaje Tesfu Biru
Handwritten bulletins which address the daily events of ancient Rome were the earliest journalistic effort made in the first century BC. Then, the first distributed news bulletins appeared in China around 750 AD. Germany, The Netherlands, and England produced newsletters and news books of different sizes in the 16th and 17th centuries.
By the early 18th century, politicians had begun to recognize the enormous potential of newspapers in shaping public opinion. Consequently the journalism of the period was largely political in nature; journalism was considered as an adjunct of politics and each political faction had its own newspaper. It is also during this time struggle for freedom of expression, which is immunity of the communications media including newspapers, books, magazines, radio, and television from government control or censorship, began.press freedom and the fate of journalists in Ethiopia
Ethiopia, in which freedom of expression is guaranteed as the basic right in the constitution, is among the leading countries in the world in suppression of the rights to freedom of expression and access to information. Many private media are banned, and many journalists fled their country and many others thrown to prison only because they criticized the state government. According to Human Rights Watch, Ethiopia is the second country next to Iran in the number of journalists in exile.
Journalism is a socially responsible profession, serving the needs and interest of the society by creating the necessary intelligence they need to lead better lives. However, in Ethiopia most, if not all, government journalists are the watchdogs of the government rather than the public and they are sanctioned by the government to be so. Journalists with strong position to balance their stories would be accused of having conspired with the opposition and are usually labeled as “terrorists” or “anti-government” and taken to prison. In fact, even those who work as watchdogs of the government lead their life in conflict between their professional identity and the situation.
Journalism in Ethiopia is not free of political influence. This can be indicated in the government’s dominance of the media ownership, the appointment of the media managers from the ruling party, and the imposition of restrictive media laws. The government’s clear aim is to ensure that media promote and never criticize government initiatives and policies.
As Human Rights Watch states the Ethiopian government has accused more than 38 journalists with various crimes under the Anti-Terrorism Proclamation since the 2010 election. Journalists who are known to write critical articles face regular and intense pressure from security officials. With the existing degree of censorship, it seems Ethiopia is in the 18th century as far as the development of journalism in the rest of the world is considered. Thus, it can be said that in Ethiopia where freedom of expression is highly suppressed and journalists are in trouble, journalism is fake.
Tewedaj Tesfu Biru, October, 2015, Toronto, Canada

Monday, October 12, 2015

ከመድረክ/ሰማያዊ/መኢአድ ጋር ለመነጋገር እንደሚፈልጉ አቶ ሃይለማሪያም ገለጹ - የሚሊዮኖች ድምጽ

October 12,2015
Millions of voices for freedom - UDJ's photo.
“ከስፖርት ጀምሮ እስከ ሥራ በፓርቲ አባላነት ነው “ ወ/ር ጽጌ ጥበቡ
“ እርስዎ ከምለስ ራ፤እይ ተላቀው ይራስዎት ራእይ መቼ ነው የሚኖሮት ? “ ጥያቄ ለአቶ ኃይለማሮያ
ያለፈው አርብ መስከረም 28 እና ቅዳሜ መስከረም 29 ቀን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተገኙበት፣ በአምስቱ አመቱ የእድገትና ትራስንፎርሜሽን እቅድ ዙሪያ፣ ኢሕአዴግ ስብሰባ አድርጓል። በአመስት አመቱ እቅዱ ዙሪያ ከመነጋገር በፊት በሕዝብ የሚነሱ ወቅታዊ የሰብአዊ መብት፣ የፍትህ መጓደልና የብሄራዊ መግብባባት ዙሪያ ዉይይቶች መቅደም አለባቸው በሚል፣ የአራት ደርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ፣ የሰማያዊ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ ) ስብሰባዉን አልተሳተፉም።
ከመድረክ ቀጥሎ በ2007 በርካታ ተወዳዳሪዎች በማሰለፍ ሁለተኛ የሆነው ኢዴፓን ፣ ጨመሮ ሌሎች አናሳ ድርጅቶች ስብሰባዉን ተሳትፈዋል። በዶር ጫኔ ከበደ የሚመራው ፣ ኢዴፓ፣ ጥያቄዎችን በማንሳት ጠንካራ ክርክሮች እንዳደረገ ለማረጋገጥ ችለናል። የኢዴፓ ተወካዮች፣ በድፍረትና በግልጽ ያለፈው የአምስት አመት እቅድ እንዳልተሳካ፣ መረጃዎች በማስቀመጥ ለማሳየት የሞከሩ ሲሆን፣ መሰረታዊ የፍትህ የመልካም አስተዳደር፣ የዴሞክራሲ ለዉጦች ተደርገው፣ ሕዝቡን ባቀፈና ባሳተፈ መልኩ ስራ ካልተሰራ፣ መጨው የአምሰት አመት እቅድም አይሳከም ሲሉ ለነ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ተናግረዋል።
ወ/ሮ ጽጌ ጥበቡ የሚባሉ የኢዴፓ ምክር ቤት አባል፣ “ ከስፐርት ጀመሮ እስከ ሥራ፣ የኢሕአዴግ ፓርቲ አባል ካልተኮነ በቀር ምንም ነገር ማደረግ አይቻልም” ሲሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ኢኮኖሚዉን፣ ፖለቲካዉን፣ ሜዲያዉና ሌሎች ሁሉንም ተቋማት ብቻውን እንደሚቆጣጠር በመገልጽ ፣ ተቋማት ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
“ እርስዎ የመለስን ፎቶ እየያዙ፣ በመለስ ራእይ እያሉ ነው። የራስዎት ራእይ የልዎትም ወይ ? ሲሉ ኤደፓዎች አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በላያቸው ላይ ያለፈው የአቶ መለስ ጥላ ገፈው ፣ ህዝብን አክብረው ፣ “ዴሞክራሲ የሕልዉና ጉዳይ ነው “ ብለው ብዙ ጊዜ የሚናገሩት ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
አቶ ኃይለማሪያም ደርጅታቸው ብዙ ስህተት ያለው፣ ብዙ ነገሮችን ማስተካከል ያለበት እንደሆነ ያመኑ ሲሆን፣ ከተቃዋሚዎች ጋር እየደጋገሙ በመነጋገገር ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሞክሩም ቃል ገብተዋል።
በስብሰባው ያልተካፈሉ ደርጅቶችም ስብሰባዉ ላለመካፈልል የወሰኑትን ዉሳኔ እንደሚያከብሩ የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም፣ በስብሰባው ካልተገኙ ደርጅቶች ጋር ለመወያየትና ለመነጋገር ፍላጎትና ፍቃደኝነቱ እንዳላቸዉም በስብሰባው ወቅት ገልጸዋል።
በኢዴፓና መድድረኩ ላይ በነበሩት በኢሕአዴግ ባለስልጣናት መካከል የጦፈ ክርክርና ምልልሶች የነበብሩ ቢሆንም በሕወሃቱ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ኢቢሲ/ኢቲቪ ግን በስብሰባው የነበረዉን ሁኔታ በግልፅ ለሕዝብ ከማቅረብ፣ እንደ አቶ ትግስቱ አወሉ ያሉትን የሕወሃት አሻንጉሊቶች በማቅረብ፣ የዉሸት ዘገባን ማቅረቡን መርጧል።

Friday, October 9, 2015

የሕወሓት ሰዎች ዶላርን በሰሜን አሜሪካ በ23 ብር እየመነዘሩ ሃብታቸውን በማሸሽ ላይ መሆናቸው ታወቀ

October 10,2015

የሕወሓት ባለስልጣናት ከሃገር ቤት ሃብታቸውን ለማሸሽ እየጠቀሙበት ያለው ዘዴ የኢትዮጵያን ባንኮች ከመጉዳቱም በላይ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስፈሪ ዳመና እንደጣለበት ተሰማ:: በአሁኑ ወቅት የሕወሓትና የተላላኪዎቹ ድርጅቶች ባለስልጣናት በሙስና ያከበቱትን ሃብት እያሸሹ ያሉት እዚህ ሰሜን አሜሪካ ወደ ሃገራቸው ዶላር መላክ የሚፈልጉትን በ23 ብር ሃገር ቤት ላይ እንመነዝርላችኋለን በሚል እንደሚቀበሉና በዚህም ጥቁር ገበያ የሕዝብ ሃብት እየሸሸ መሆኑ ተጋልጧል::

በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ; በሲያትል; በዴንቨር; በሚኒያፖሊስ; በአትላንታ; በዳላስ; በቺካጎ; በሂውስተን; በኦሃዮ; በፖርትላንድ; በላስቬጋስ; በካሊፎርኒያ የተለያዩ ከተሞች; በአሪዞና በተዘረጉ ኔትወርኮች ዶላር በጥቁር ገበያ 23 ብር እየተመነዘረ መሆኑ ታውቋል::

የገንዘቡ ዝውውር የሚደረገው ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች ባሉ ኔትዎርኮች መካከል ዶላሩን እዚሁ ይሰጡና ሃገር ቤት በግለሰቦች አማካኝነት በ23 ብር ምንዛሬ ይሰጣል:: ዘ-ሐበሻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድረገጽ ባገኘችው መረጃ መሰረት በዛሬው ዕለት የዶላር ምንዛሬ ዋጋ 20.85 ሲሆን በ23 ብር በጥቁር ገበያ እየሸጠ ይገኛል::

ዶላር በሕገወጥ መንገድ እንዲህ መተላለፉ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሚያባብሰው መሆኑ እየታወቀ የሕወሓት ሰዎች እንዴት እንዲህ ባለው ሕገወጥ ተግባር ላይ እንደተሰማሩ የሚያስገርም ነው የሚል አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች ከጥቂት ጊዜያት በፊት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “የኢትዮጵያን መንግስት በኢኮኖሚ ማዳከም ካስፈለገ ከውጭ የሚላኩ ዶላሮች በኢትዮጵያ ባንኮች በኩል መተላለፍ የለባቸውም:: ሕዝቡ ዶላሩ መንግስት እጅ በማይገባበት መልኩ ገንዘቡን ይላክ” ማለታቸውን ይጠቅሳሉ::
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Wednesday, October 7, 2015

በፓርላማው ውስጥ እንቅልፏን የለጠጠችው ወ/ሮ አስቴር አማረ ጋር በእንደርታ ምርጫ ተፎካካሪዋ የነበረው የአረናው አባል ስለሴትየዋ ይናገራል

October 7,2015

ፓርላማው ውስጥ ዛሬ በርካቶች እንደተለመደው እንቅልፋቸውን ሲለጥጡት ውለዋል:: ይህን ተከትሎ የተለያዩ ፎቶዎች ሲለቀቁ ውለዋል:: ከነዚህ እንቅልፋሞች መካከል ደግሞ አንዷ ወ/ሮ አስቴር አማረ ናት:: ከ እንደርታ ትግራይ የመጣችው ይህችው የፓርላማው ተቸካይ ጠርጴዛ ላይ ተቸክላ እንቅልፏን ስትለጥጥ ነበር:: ከ እርሷ ጋር በተፎካካሪነት በአንድ ምርጫ ጣቢያ ቀርቦ በሕገወጡ ምርጫ ተሸንፈሃል የተባለው የአረናው ፓርቲ ተወካይ አቶ ሰናይ የሚከተለውን መልዕክት በፌስቡክ ገጹ አስተላልፏል::

እኝህ እንቅልፋም ወ/ሮ አስቴር አማረ የተባሉት ሴት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የህወሓት የ ወረዳ እንደርታ(መቀለ ዙርያ) ተወካይ ሲሆኑ በ2002 ምርጫ በ ወረዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡት 7 የሚሆኑ የፓለቲካ ፓርቲዎች እኔም ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉአላውነት በመወከል ስወዳደር እኔና እሳቸቸው ከባድና እልህ አስጨራሽ ፍኩኩር ያደረግን ቢሆንም ምንም የውድድር ሜዳ፣ገለልተኛ የሆነ የምርጫ ቦርድና ፍትሓዊነት ባልነበረው ምርጫ የህወሓት ካድሬዎች 1ለ 5 በማደራጀት ያለና የሌለ አቅማቸው የሀይልም ጭምር በመጠቀም እዚ ግባ በማይባልልና በተጭበረበረ ምርጫ ፓርላማ ሊገቡ ችለዋል።

በጣም እሚገርመው ነገር ወይዘሮ አስቴር አማረ የተመረጡበት ወረዳ ያልተወለዱበት፣ያላደጉበትና የማያውቁት መሆኑ ነው።ፓርላማ ገብተው መተኛታቸውም ለመረጣቸው ህዝብ ንቀት መግለጫ ዋነኛ ምስክር ነው።በአሁኑ ግዜ እኔ በፓለቲካ ልዩነቴ ምክንያት በደረሱብኝ ችግሮች ከምወዳት አገሬና ከምወደው ወገኔን ርቄ በስደት ስንከራተት እንቅልፋምዋ ግን ደልታት ፓርላማ ውስጥ ላሽ ብላለች።

senay amare
ወይ አገሬ

Tuesday, October 6, 2015

ዘራፊው ሕወሓት ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ ውሳኔ ሰጪ ያልሆኑ ወንበሮችን ለአሽከሮቹ አድሏል::

October 6,2015
- አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃስት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል::
- ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል::
- ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል::
- ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::
Hailemariam
 ምንሊክ ሳልሳዊ:- የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በዛሬው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር ሃይሉን የውጪ ጉዳዩን የደህንነቱን የኮሚኒኬሽን እና አስፈላጊ ቀልፍ ጉዳዮችን በመቆጣጠር ውሳኔ ሰጪ የማይባሉ ተራ ቦታዎችን ለአሽከሮቹ በማደል የተዋቀረ ሲሆን አለማየሁ ተገኑ እና ሶፍያን አህመድ ምን እንደዋጣቸው አይታወቅም::ከኒውዮርክ ስብሰባ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያ ቤቱ እንዳይወጣ እና ከሰው እንዳይገናኝ የታገደው ሃይለማርያም ደሳለኝ ራሱን ፈልጎ አለማግኘቱ እና በአሽከርነት መኖሩን ቤተሰቦቹን እያበሳጨ መሆኑ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ይናገራሉ::
ቁልፍ የሆኑ ስልጣኖቹን የተቆጣጠረው እና በዘመድ አዝማድ ተሞልቶ በከፍተኛ የሃገር እና ሕዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የተሰማራው ሕወሓት ባለፈው የኢሕአዲግ ስብሰባ ወቅት አንዳንድ አመራሮቹ ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ ከስልጣን እንደሚባረሩ ሲነገር ነበር:: የወያኔና አሽከሮቹ ሹመት እንደሚከተለው ነው:-
አቶ ደመቀ መኮንን – ም/ጠቅላይ ሚኒስትር እና የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ
ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል –በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ወይዘሮ አስቴር ማሞ – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ሲራጅ ፈጌሳ – የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አቶ ካሳ ተክለብርሃን – የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ – የፍትህ ሚኒስትር
አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ – የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
አቶ ተፈራ ደርበው – የእርሻ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ስለሺ ጌታሁን – የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ያዕቆብ ያላ – የንግድ ሚኒስትር
አቶ አብይ አህመድ – የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
አቶ ሙኩሪያ ሀይሌ – የከተማ ልማት እና ቤቶች ሚኒስትር
ዶክተር አምባቸው መኮንን – የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
አቶ ሞቱማ መቃሳ – የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ – የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ቶሎሳ ሻጊ – የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ – የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ – የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
ኢንጂነር አይሻ መሀመድ – የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ -የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም – የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን – የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ – የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
አቶ በከር ሻሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር
አቶ ጌታቸው ረዳ – የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ዶክተር ይናገር ደሴ – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::በአንድነት በመቆም ሃገራችንን ከጅቦች እናድናት:

Sunday, October 4, 2015

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!

October 4, 2015
def-thumb“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው።
ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።
ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።
ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው።
በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው።
ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል።
የንቅናቄዓችንን መዋቅር በመላው አገራችን ከዘረጋን፤ ራሳችንን፣ አስተሳሰቦቻችንና ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት ከመራን፤ ቅንነት፣ ሀቀኝነትና ጽናት ከተላበስን ድላችን ቅርብ እና አስተማማኝ ነው። ለውጥን የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ይተግብር።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, October 1, 2015

ከመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የስንብት ጥያቄ የሚያቀርቡ መኮንኖች ቁጥር እያሻቀበ ነው

October 1,2015
መቶ በመቶ ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ከአንድ አካባቢ በወጡ የህወሓት አባላት ድኩማን ወታደራዊ አዛዦች ብቻ ቁጥጥር ስር ሆኖ በከፋ አስተዳደራዊ በደል እየማቀቀ በዘር ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው ብዙኃኑ የመከላከያ ሰራዊት የሰባት ዓመታት አገልግሎት የኮንትራት ጊዜውን የጨረሰው የስንብት ጥያቄ ያዘሉ ደብዳቤዎችን ያለማቋረጥ እያስገባ በየእርከኑ የሚገኙ የመከላከያ የአስተዳደር ቢሮዎች በማመልከቻ ማዕበል ክፉኛ እየተመቱ የሚገኙ ሲሆን የአገልግሎት ጊዜው አልሞላ ብሎት የስንብት ደብዳቤ ማስገባት ያልቻለው የሰራዊቱ አባል ደግሞ የሰቀቀን ኑሮውን ለማሳጠር በራሱ እርምጃ እየወሰደ ያለምንም ፋታ እየከዳ ነው ሲል የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ዘግቧል::
(Photo File)
(Photo File)















ድኩማኖቹ ህወሓታዊያን የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዦች የአገልግሎት ጊዜ ኮንትራታቸውን ጨርሰው የስንብት ደብዳቤ ለሚያስገቡት በስርዓቱ የተንገሸገሹ እና በእጅጉ ተማረው ተስፋ የቆረጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የሰራዊቱ አባላት “ከመከላከያ ሰራዊቱ ፈፅሞ መልቀቅ አይቻልም…” የሚል አሉታዊና ድፍን ያለ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም ድኩማኖቹ ወታደራዊ አዛዦች የአገልግሎት ዘመኑን የጨረሰ ማንኛውም የመከላከያ ሰራዊት አባል በአሁኑ ሰዓት የስንብት ጥያቄ የማቅረብ መብት እንደሌለውና አሰናብቱኝ ብሎ በሚያመለክት ላይ እርምጃ የሚወስዱ መሆናቸውን ጠንከር ያለ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
ከየማሰልጠኛው ተመርቀው በየጊዜው ሰራዊቱን የሚቀላቀሉ አዳዲስ አባላት ብዙም ሳይቆዩ ስለሚከዱ “ነባሩ ሰራዊት” ከተሰናበተ በእነሱ ላይ ቅንጣት ታክል እምነት ስለሌላቸው በአገዛዙ ላይ የከፋ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል በማብራራት በማሳመን ለማባበል እየሞከሩ ይገኛሉ፡፡
የህወሓት አገዛዝ በየጊዜው ከመከላከያ ሰራዊቱ የሚከዱትን አባላት ከየተሸሸጉበት አድኖ የመያዝ ሰፊ እንቅስቃሴ አድርጎ ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡
በየጊዜው ያለምንም ፋታ የሚከዱ የሰራዊቱ አባላት ወደየ ትውልድ ቀያቸው አይደለም የሚመለሱት፤ ገሚሶቹ ከነትጥቃቸው በረሃ ወርደው ይሸፍታሉ፤ አብዛኞቹ የነፃነት ትግሉን ይቀላቀላሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ ድምበር ተሻግረው እግራቸው ወደመራቸው ይሰደዳሉ፡፡
በአጠቃላይ አሁን እጅግ በጣም በርካታ አባላት ላነሱት የስንብት ጥያቄ የተሰጠውን “አይቻልም” የሚል ድኩማን ህወሓታዊ ወታደራዊ አዛዦች ምላሽ ተከትሎ በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ከዳር እስከ ዳር ሰፍኖ የቆየውን ውጥረትና አለመተማመን ከጫፍ አድርሶት አገዛዙ ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ የሆነ ከባድ አደጋ እያንዣበበ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ስብሰባ ረግጠው ወጡ

October 1,2015
All members with the exception of Russia's UN Ambassador Vitaly Churkin and China's deputy U.N. Ambassador Wang Min vote in the United Nations Security Council in favor of referring the Syrian crisis to the International Criminal Court for investigation of possible war crimes at the U.N. headquarters in New York May 22, 2014. REUTERS/Lucas Jackson (UNITED STATES - Tags: POLITICS) - RTR3QEAZ
ተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ጋር ተያይዞ በተጠራ መድረክ ላይ የተጋበዙት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ስብሰባ ረግጠው ወጡ። ስኞ እለት የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት በተመለከተ በተጠራው ስብሰባ ላይ የተገኙትና በኋላ በቀረበው ሪፖርት ሳይደሰቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ወደ ስብሰባው አልተመለሱም። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለሰቦች በጄኔቭ ስዊዘርላንድ በመገኘት በወቅታዊ የኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት አያያዞች ዙሪያ መወያየታቸውን እማኞች አስታውቀዋል። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች በመድረኩ ሊነሱ በሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ከጉባኤው ረግጠው መውጣታቸው ታውቋል።

ሂውማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣና አፈና ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀዋል። ሁሉንም የፓርላማ ወንበሮች በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የሚገኘው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት፣ የዜጎችን ሃሳብን የመግለጽ መብት ከማስፋፋቱ በተጨማሪ በነጻ የመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚወስደው እርምጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ድርጅቱ አመልክቷል። ከትናንት በስቲያ ሰኞ የተካሄደውን የሰብዓዊ መብት መድረክ ያዘጋጀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ ስላለው የሰብኣዊ መብት አያያዝ ስጋቶችን ሲገልፅ መቆየቱ ይታወሳል። በጄኔብ በተካሄደው በዚሁ ልዩ መድረክ የተሳተፉ በርካታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ረፖርት ማቅረባቸውንም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ገልፅዋል።
የእንግሊዝ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጀቶች ኮሚሽኑ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝን ጨምሮ በተለያዩ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ክትትልን እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበው እንደሚገኙም ተችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች መድረኩን ረግጠው ስለወጡበት ምክንያት የሰጡት ምላሽ የለም።

(የሳዑዲ ጉዳይ) ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ እስከዛሬ አልታወቀችም ነበር – ኢትዮጵያ 13 በላይ ሞተውባታል ፣ 26 ቆስለውባታል ከ204 በላይ ጠፍተውባታል ፣ ፍለጋው ቀጥሏል

Oktober 1,2015
nebyu sirakየማለዳ ወግ…አድካሚው ስራ ፣የጠፉትን ሀጃጆች ፍለጋ !
ኢትዮጵያ …
* ኢትዮጵያ 13 በላይ ሞተውባታል ፣ 26 ቆስለውባታል
ከ204 በላይ ጠፍተውባታል ፣ ፍለጋው ቀጥሏል
* ጅጃ ከተላለፉት ቁስለኞች ኢትዮጵያዊ የለም
* ጅዳ ማህጀር የተላፈው ሬሳ ማንነት ገና አልተጣራም
* ከማህጀሩ ሬሳ የአፍሪካውያን አለበት ተብሏል
* ኢትዮጵያውያን መካ ላይ ለፍለጋው በግል ተደራጅተዋል
* ማፈላለጉን በሁሉም ሆስፒታሎች መከዎን ገዷቸዋል
* ቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ ተብለዋል
* በመካው ክሬን የተጎዳች ኢትዮጵያዊት ሀጃጅ ተገኘች
* ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ እስከዛሬ አልታወቀችም ነበር
* ልክ የዛሬ ሳምንት መሞቷ ተጠቁሟል
ህንድና ፖኪስታን …
* በማፈላልጉ የሳውዲ መንግስት አፋጣኝ እርዳታ ተጠየቀ
* የህንድን ፖኪስታን ቆንስሎች መግለጫ ሰጥተዋል
* ህንድ 46 ሞቶባታል 62 ቆስለዋል 82 ጠፍተውባታል
* ፖኪስታን 46 ሞተውባታል ፣ 8 ቆስለዋል 42 ጠፍተውባታል
የጠፉትን ፍለጋና ጭንቅ ድካሙ …
======================
ተቀማጭነታቸውን ሳውዲ ያደረጉ ፣ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ፣ በሀጅ ጸሎት ከአደጋው የተረፉ ሀጃጆችና ቤተሰቦቻቸው በሚና ጀማራት አደጋ የጠፉና የሞቱትን ሰዎች ለማፈላለግ ሌት ከቀን ወደ ሚና ፣ ጀማራትና መካ በመመላለስ አድካሚ የጭንቅ ሳምንት መግፋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። የጠፉ ሃጅ ቤተሰቦች በግሩኘና በተናጠል ቢያፈላልጉም በርካታዎች እንዳልተሳካላቸው ይናገራሉ ። በአደጋው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ቁጠር ገና ከአደጋ ቀን አንስቶ ከአምስት በላይ መሆኑ ግልጽ እያለ በኢትዮጵያ ኢንባሲ ፣ ቆንስልና የሀጅ ኮሚቴ የሚደረገው ፍለጋ የተቀናጀ ባለመሆኑ ዝርዝር መረጃው ቀርቶ የሞቱና የቆሰሉትን ዙሪያ ትክክለኛ መረጃ አልቀረበም ነበር ። ከብዙ ጉትጎታ በኋላም ትክክለኛውን መረጃ ለህዝብ ለማድረስ በርካታ ቀናት ወስዷል ።

አሁንም በኢትዮጵያ ተወካዮች በኩል ቀናት የወሰደው የሞቱና የቆሰሉትን የማሳወቅ መረጃ ቅበላ ከቀናት በፊት ይፋ ቢደረግም አሁንም ቁጥሩ እየጨመረ ከመጣው የሟቾቸ ብዛት አንጻር የመረጃ ክምችቱን የማሻሻል ስራ እየተሰራ አይደለም ! ጉዳዩ ያሳሰባቸው በመካ ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካ ላይ በሚገኙ በ13 ሆስፒታሎች ፍለጋ ተደራጅተዋል ጀምረዋል ። ያም ሆኖ መሊክ ፈይሰል ፣ ሄራ ፣ ጀበለር ኑርና መሊክ አብደላ በተባሉ ሆስፒታሎች ቢከለከሉም በቀሩት አንዳን ሆስፒታሎች ማፈላለግ ችለዋል። ማፈላለጉን በተወሰነ መልኩ ማሳለጥ ችለው 15 ያህል ቁስለኞችን አግኝተዋል። ነገር ግን የተጠቀሱት ሆስፒታል ሃላፊዎች የቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ በማለት የተከለከሉት ወጣቶች ከሀጅ ኮሚቴ ጋር ተቀራርበው ለመስራት የሚየሰደርጉት ሙከራ አለመሳካቱን ገልጸውልኛል! ውክልናውን ወይም መታወቂያ ይሰጣቹሃል ቢባሉም እስካሁን ከኮሚቴው መልስ ባለመሰጠቱ ጥረታቸው መሰናክል እንደገጠመው አንድ የገላጊው ቡድን አባል ገልጸውልኛል !

በአንጻሩ የመሳሳይ ችግር ያለባቸው የአንዳንድ ሀገራት የመንግስት ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ነዋሪዉን ለበጎ ስራና በማቀናጀትና በማቀዳጀት በሽዎች የሚቆጠሩ ልዩ የፈላጊ ግብረ ሃይል አቋቁመው በመካ ፣ ሚናና ጀናራት አሰማርተዋል ። የነዋሪውንና የሀጃጆችን ጭንቀት በመረዳትም የቆሰሉትንና የሞቱትን ፎቶ መረጃዎች ከሳውዲ መንግስት በመውሰድ ለዜጎቻቸው አቅርበዋል።
በሳምንት የአደጋው አድሜ በዋናነት አሳሳቢ የሆነው ቁርጡ የታወቀው የሞቱትና የቆሰሉት ዜጎች አልሆነም። ሞተው ፎቷቸውና ቆሰለውም ከሆነ ዝርዝራቸው ያልተገኙት ጉዳይ ብዙ ዜጎችን በመንፈስ እያስጨነቀና እያንገላታ ይገኛል። መዳረሻቸው ” ጠፋ” ከሚባሉት መካከል በደረሰው አደጋ ፊታቸው መለየት ያስቸገረ ይገኙበታል የሚል ጥርጣሬ ቢኖርም የሟቾችን ሬሳ ለመለየት የተለያዩ እርንጃዎች ቀርበዋል። ሀጃጆች በገቡበት አሻራ ለመለየት እየተወሰደ ያለው ማጣራት ረዠም ጊዜ መውሰዱ ተቃውሞ እየቀረበበት መሆኑ ይጠቀሳል ። የሳውዲ መንግስት የየጤና ጥበቃና የፖስፖርት ክፍል ኃላፊዎች ስለመለየቱ ስራ ሲናገሩ በሶስት መንገድ እንደሚከወን ያስረዳሉ ። እስካሁን መለየት ያልተቻለውን ሬሳ ለመለየት የቀረቡት ዘዴዎችም 1ኛ / በገቡበት አሻራ 2ኛ / በገቡበት ፎቶ መለየት እና 3 ኛው / የስጋ ዘመድ ቤተሰቦቻቸው እየቀረቡ DNA በመስጠት መለየቱ እንደሚከወን ይናገራሉ ! አሻራቸው የተነሱ ሬሳዎች ውጤት በከነገ ጀምሮ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ቢጠበቅም የተረጋገጠ መረጃ እስካሁን አላገኘሁም !

የሳውዲ መንግስት የጠፉትን በማፈላለግ ሂደቱን እብዲያፋጥንና የዜጎቻቸው እጣ ፈንታ እንዲያሳውቅ ህንድና ፖኪስታን የሳውዲ መንግስት አስቸኳይ እገዛ እንዲያደርግ በተለያዩ መንገዶች ተማጽኗቸውን በማቅረብ ላይ ናቸው !
ይቀጥላል …
ነቢዩ ሲራክ
መስከረም 20 ቀን 2008 ዓም

Wednesday, September 30, 2015

የትጥቅ ትግልና ግራ የሚያጋባ አስተያየት – ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

September 30,2015
getachew
በኢትዮጵያ ትከሻ ላይ የተቆለፈውን ቀምበር ለማላቀቅ ቍልፉ የትጥቅ ትግል መሆኑ በተነሣ ቍጥር ከአንዳንድ ሰዎች የሚሰጠው አስተያየት ግራ የሚያገባ ነው። ገዢዎቹና ደጋፊዎቻቸው ቢቃወሙ ይገባኛል። የሚሰጡት አስተያየት ግን ሕፃንን ሳይቀር የሚያሥቅ ነው። “ጦርነት በቃን” ይላሉ። “አትንኩን” ማለታቸውን የማናውቅ ይመስላቸዋል። ጦርነት ካላስፈለገ፥ ለምን ከንጉሣዊው አስተዳደር ጋር ተዋጉ? ለምን ከደርግ ጋር ተዋጉ? ጨቋኝ ገዢ የት አገር ነው በሌላ መንገድ ሥልጣን ለሕዝብ ሲለቅ የታየው? የምሥራቁ ዓለም ጨቋኞች የወደቁት በሕዝብ ዐመፅ ነው ማለት፥ የምዕራቡን ዓለም ከባድ እጅ ሚና መርሳት ይሆናል።
የኛዎቹ ጦርነት ከመረራቸው፥ ሕዝብን ወደጦርነት የሚመራ በደል አይሥሩበት። ምን ጊዜም ቢሆን የትጥቅ ትግል የመጨረሻው አማራጭ ነው። የትጥቅ ትግል የሚያደርሰው ጉዳት በአንዱ ወገን ላይ ብቻ አይደለም። መሣሪያ የሚያነሣ መሣሪያ ማንሣት የሚያመጣበትን ጉዳት ሳያውቅ አይነሣም። ሰው ሆኖ እንደከብት መገዛት ያልቻለ ሰው በቃኝ ሲል፥ ክብሩን በመጠበቁ ከተቀመጡበት ተነሥቶ “ነወር” የሚባል እንጂ፥ በባርነት ጥላ ሥር ተቀምጦ የሚተች አይደለም። “ጦርነት መርሮናል” የሚለውን ምክር መገዛት ለመረረው አይመክሩም።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ግራ አጋቢ አስተያየት “ጦርነትስ አስፈላጊ ነው፥ ግን . . .” የሚለው ነው። ይህ አስተያየት በቅን አሳብ፥ የተሰጠ ሊሆን ይችላል። ግን አዛኝ መስሎ፥ ቀምበረኛውን ለመደገፍ የተሰጠ አስተያየት አለመሆኑ በምን ይታወቃል? እውነተኛ አሳቢና ሠጊ ሰው አስተያየቱን የሚሰጠው ሲጠየቅ፥ ካልተጠየቀም በግሉ ትጥቅ ያነሡትን ፈልጎ በጨዋ ደምብ መንገር ነው። ሳይጠየቁ ተነሥቶ በይፋ ምክር መስጠት ግን ሰሚው ሕዝብ ትግሉን እንዳይደግፍ መገፋፋት ነው። የትጥቅ ትግል ከታመነበት እንዲፋፋም የማይፈለግበት ምክንያት ምንድን ነው?
ትጥቅ ትግል የራስን ሕይወት ለወገን ነፃነት መሠዋት ማድረግ ነው። ሌላ ዓለማ የሌለው ሰው መሣሪያ ሲያነሣ፥ እንዴት ይኸንን የሚሰነዘርበትንና የሚሰነዘርለትን ምክር ሳያስብበት ራሱን ለመሥዋዕትነት ያቀርባል? የሚካኼደው የትጥቅ ትግል የሚያዋጣ የመሰለው እርዳታውን ያቅርብ፤ የማያዋጣ የመሰለው ለምንድን ነው የሚቃወመው? ተቃውሞው ማንን ለመጥቀም ነው? ለታጋዮቹ አስቦ ከሆነ፥ ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው። “የኔን ያህል የማሰብ ችሎታ የላችሁም” ማለት ነው። እንዴት ነው ለታጋዮቹ ያልተገለጠ ሥጋት ለምክር ሰጪዎቹ የተገለጠው?

አንዳንዱ ደግሞ፥ “ይኸው እንታገላለን ሲሉ ዓመታት አሳለፉ፥ ግን አንዳች ውጤት አላሳዩም” ይላል፤ ውጤት እንዲያሳዩ የቀጠራቸውና ካልሆነላቸው የሚያሰናብታቸው ሹም ይመስል። አርፎ መቀመጥ ስንት ውጤት አሳየ? ሌሎችን ሙከራዎችም “አንዳች ውጤት አላሳዩም” ብለን እንንቀፋቸዋ!ውይስ ውጤት አሳይተዋል?
“በመካሄድ ላይ ያለው የትጥቅ ትግል ኢትዮጵያን የሚጎዳ ነው” ከተባለ፥ እርግጥ ሊታሰብበት ይገባል። ግን አሳሳቢው ምክንያት ሊቀበሉት በሚገባ መልኩ አልተሰጠንም። ይህ ትግል የሚያመጣው ጉዳት ከተሸከምነው ቀምበር ይበልጥ ሊከብድ እንደሚችል አሳዩን።
የወያኔ ቀምበር መሰበር አለበት የምንል ሁሉ በመሰለንና በተቻለን መንገድ እንታገል። ካልተቻለን፥ ካልመሰለን፥ አርፈን እንቀመጥ፤ ታጋዮችን አለማደናቀፍ፥ እንደ ትግል እንዲቈጠርልን።

Tuesday, September 29, 2015

አርባ‬ ምንጭ የነበረው የአሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን አካባቢውን ለቆ እየወጣ ነው

September 29,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)


‪አርባ‬ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡ ‪‎ህወሓት‬ በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡
አርባ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡

በአርባ ምንጭ እና አካባቢው ሲንቀሳቀስ እና ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ከዚያ እያስነሳ ወደ ሚፈልገው አቅጣጫ ለጥቃት ሲያሰማራ ለረጅም ጊዜ የቆየው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን ከአገሪቱ መንግስት በተሰጠው መመሪያ የቆይታ ጊዜ ኮንትራቱን አቋርጦ ሀሙስ ዕለት አካባቢውን ለቆ መውጣት መጀመሩን በቦታው የሚገኙ ምንጮቻችን ገልፅዋል፡፡ ድሮን የታጠቀው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን የአርባ ምንጭን መሬት ለቆ መንቀሳቀስ የጀመረበት ምክንያት ለጊዜው በውል ተለይቶ ባይታወቅም መንግስት ነኝ በሚለው በህወሓት አገዛዝ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል አለመግባባት ተከስቶ ቅራኔ ሳይፈጠር እንዳልቀረ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ ከአሁን በፊት ከአርባ ምንጭ በተጨማሪ በድሬ ደዋ ላይ ተቀምጦ በሰው አልባ አውሮፕላኖች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሱ የአልሸባብ ተዋጊዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት መክፈቱ ይታወቃል፡፡ ህወሓት በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ገና ከሽፍትነቱ ጀምሮ በህዝብ ላይ ሴራ በማቀነባበር የሚታወቀው ህወሓት ራሱ ግንብቶ ለግለሰቦች ያከራየውን የንግድ ማዕከል ነው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ድርጊቱን እንደፈፀሙት በማስመሰል ከህዝብ ለመነጠል ሲል ነው በተቀነባበረ ሂደት በእሳት የለቀቀው ፡፡

በህወሓት የተቀነባበረ ሴራ የተከሰተው ከባድ የእሳት አደጋ የደረሰው መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም ሲሆን ከ40 በላይ ሱቆች ተበልተው ወደ አመድነት ተቀይረዋል፤ በሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረትም ወድሟል፡፡ ህወሓት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በተከሰቱት የቦንብ ፍንዳታዎች ትግራይ ሆቴልን ጨምሮ እጁ እንዳለበት የአሜሪካ ኤምባሲ ለስቴት ዲፓርትመንት የላከውን ደብዳቤ በዋቢነት ጠቅሶ ዊክሊክስ የተባለው ድረ-ገፅ ማጋለጡ የሚታውስ ነው፡፡

Saturday, September 26, 2015

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia

September 26, 2015

logo-timeret
United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia, (pdf)

Ethiopia is one of the oldest nation-states in the world. Both written and oral history and recent archeological discoveries, despite regional rivalries, suggest the historical continuity of the nation. It was a Monarchy until 1974. From 1974 to 1991 the country was declared to be ‘Peoples Democratic Republic’ by the military junta, Derg, and went through a traumatic experience. Tigrai Peoples Liberation Front (TPLF), a guerrilla force from a minority ethnic group that led the rebellion against the military junta and captured the institutions of the State, has been in power for the past 24 years. The country is ruled as a one-party state under a façade of multi-party system since 1991.
The state is characterized by an intensifying political repression, rampant economic corruption, denial of basic human and political rights and repeated sham elections. The top brass of the army and security organs of the state, including key diplomatic positions, are effectively mono-ethnic despite the claim of the regime to stand for the equality of all ethnic groups. The people have completely lost confidence in the government after the regime shamelessly declared itself to have won 100% of the parliamentary seats in the 2015 election. Ethiopians, with no other choice available to them for democratic transition, have now risen up in arms. And this is a credible threat of force to the regime. History has time and again proven that no government that denies freedom, justice and democracy to its people will not survive their wrath.
Against this background, Ethiopian democratic forces, reflecting the broad diversity of the Ethiopian society, have recently formed the United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED) as an umbrella organization. UMSED is committed to coordinate the people’s struggle for effective resistance against TPLF’s tyranny and to ensure the transition to true democracy and stable political order in Ethiopia. No one relishes the idea of armed conflict; but, there are times when armed self-defense becomes the only choice to resist the unbearable violence by minority against majorities and to bring about an enduring peace and stability in a society.
Ethiopians have given up on elections as they have become meaningless rituals:There have been five national elections under the TPLF. The first election in 1995 resulted in 3 opposition members being elected to the parliament that has a total of 548 MPs. In the second election of 2000, the number for the opposition members rose to 27. In the 2005 general election, which was monitored by the Carter Center, European Union and other observers, Ethiopians turned out in record numbers and voted for the opposition, mainly CUD and UEDF. The results were rigged; and the election was blatantly stolen. Furthermore, many unarmed and defenseless peaceful protesters demanding the respect for the vote of the people were indiscriminately gunned down in a broad daylight. Leaders of opposition political parties, civic societies, journalists and dignified and well-meaning Ethiopian citizens were jailed for two years. Members of the fact finding commission appointed by the government itself published the evidence that the government has cold-bloodedly massacred 197 Ethiopians on this day of infamy. Today, these fact finders are themselves in exile fleeing for their lives. Only one opposition member was able to win a seat in the parliament during the 2010 fourth national election. In the most recent election of May 2015, in which the regime claimed 100% landslide victory of all parliamentary seats, no credible outside/international observers, excepting those from the corrupt African Union, were allowed to monitor the election.
The Ethiopian government owns all land in the country, including most residential and commercial real estate in towns and cities like all other communist totalitarian regimes in the world. The industrial and service sector of the economy is also heavily controlled by Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), an endowed conglomerate parastatal serving as a front for the ruling TPLF party. Until recently it was managed by the wife of the late Prime Minister. Both were members of the TPLF/EPRDF politbureau and the legislative assembly, making their work similar to the work of the late Romanian dictators, Nicolae Ceaușescu and his wife Elena Ceaușescu. The total grip on land and the economy is a source of much power to the regime and the accompanying oppression of the people in a country where eighty five percent of the population is engaged in farming and most city dwellers rely on the government for employment and housing. All land in the country was declared government property by the old communist military regime and the current regime has continued the practice. The monopolization of land by the TPLF and its surrogate administrators has been the source of wealth for some, but continued to stifle the production of food as in the communist era. Thanks to this land policy, today lives particularly that of children and cattle in the Afar, Amara, Gambella, Somali and Southern regions of the country are perishing due to a single season rainfall failure.
Ethiopians are tired of their voices being totally muffled: Independent media is not tolerated. The International Federation of Journalists has declared the regime to be one of the worst offenders of press freedom. Television, Internet, and major print media is owned and operated by the government. The state is the only Internet Service Provider and uses Chinese, Italian and British Internet hacking and intercepting technology vendors to spy, trap and intimidate its critics and opponents. The regime also spends precious resources on signal jamming technology to stop the free flow of information from the outside. Foreign based and independently operated radio and TV broadcasts by the Ethiopian Diaspora are jammed on regular basis as are broadcasts in Ethiopian languages by Voice of America and Deutsche Welle Radio.
Ethiopians can no longer tolerate an entrenched ethnic minority rule: The TPLF, the dominant party in the coalition known as Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), controls all aspects of life in the country, similar to apartheid South Africa, by installing its ethnic rulers as heads of major institutions across the entire state apparatus. Ethiopians and international observers including those who bend backwards to “apologize” for the regime know very well that ethnic Tigrayans control the army, security services, telecoms , foreign affairs, and other nerve centers of the Ethiopian state machinery. The TPLF party pits different ethnic and religious groups against one another simply to perpetuate its minority rule and monopoly on resources. The regime has no respect for religious freedom. It has created chaos in both the Ethiopia Orthodox Tewahido Church and the Muslim mosques by interfering in the administration of their purely religious institutions through its political cadres. It has similar surrogates in Pentecostal Churches. Religious leaders who resist this interference are exiled (as the Orthodox Christian leaders) and imprisoned (as the Muslim community leaders). Ethnic minority domination has become a source of stress on the harmony of the people that is essential for peaceful coexistence in a diverse mutli-ethnic and multi-religious country like Ethiopia.
Ethiopians have said enough to the regime’s oppression with impunity: In the last twenty four years, the people have been appealing to the regime to respect the fundamental political and civil liberties of the citizenry. Peaceful protests are disallowed. Countless petitions and protest demonstrations that were held in the major capitals of the world have ended in deaf ears. The response by the government has been more repression and more violence. Today there is no independent media in the country due to the wide spread practice of jailing and forcing publishers and reporters in to exile. Today there are no functioning independent political parties due to the practice of systematic disruption of their normal day-to-day activities, jailing of opposition leaders or forcing them out of their country. Currently, prisons are filled with thousands of well-known political, civic organization and religious leaders as well as journalists under trumped-up “terrorism” charges. Certain ethnic groups are targeted. These prisoners are tortured to confess and to corroborate the charges against themselves and their colleagues. In spite of this massive oppression, victims of the regime have no recourse to justice since the judiciary is made subservient to the political manipulation of the ruling party.
As presented above, Ethiopians are once again faced with a regime that is led by a group of people who oppress them in multiple ways; deny them basic human rights and are hell-bent on blocking the democratic process for self-rule. We are also aware that though the regime comes from Tigrai, a thousands of Ethiopians that come from this ethnic group are victimized and have already started armed insurrection well over one decade ago. The predicament the Ethiopian people find themselves in currently is not unique. Under similar conditions, the founding fathers of one of the earliest democracies in the world have said it best in the Declaration of Independence by the Colonies from the Great Britain: ‘We hold these truths to be self-evident, that all men are created equal, that they are endowed by their Creator with certain unalienable Rights, that among these are Life, Liberty and the pursuit of Happiness. — That to secure these rights, Governments are instituted among Men, deriving their just powers from the consent of the governed, — That whenever any Form of Government becomes destructive of these ends, it is the Right of the People to alter or to abolish it, and to institute new Government, laying its foundation on such principles and organizing its powers in such form, as to them shall seem most likely to affect their Safety and Happiness’ A similar spirited paragraph is found in the preamble of African National Congress’s Freedom Charter. These words ring true today for the people of Ethiopia.
At this critical juncture, to facilitate the Ethiopian people’s struggle with able leadership, the democratic forces in the country are coalescing under the newly formed UMSED as a “broad church”.. It is not lost on the part of these democratic forces that one of the potential obstacles on the road to the Ethiopian people’s struggle for freedom and democracy is the international community’s multifaceted collaboration with the TPLF dominated government with seeming indifference to the prevailing repressive political conditions in the country.
Following their new goal of making inroads into Africa, some countries have become major financiers of the TPLF repressive regime. This may be an expected behavior from these governments, given the nature of their systems. However, the West’s support for the rogue dictatorial regime is inconsistent with the values of freedom, justice, and democracy the West practices at home and espouses for the stable world order. The West led by the US has correctly and understandably declared terrorism as the number one menace to global peace while in a typical short-term calculus have also decided to consider dictatorial regimes like that of Ethiopia to be “allies” in its anti-terrorism effort and the disorder in the Greater Horn of Africa region. As a result, the West has made the Ethiopian regime a beneficiary of its substantial financial, political, diplomatic and even military support indirectly emboldening it to continue with impunity in its human rights abuse and repression of its own people. This policy on the part of the Western countries is not only short sighted and immoral but is more than likely to lead to greater instability especially when minority regimes collapse.
It is obvious that the repressive nature of the regime and its extensive human rights abuses are among the main causes of instability in the region. For all those who are willing to see the writing on the wall, the regime is internally in continuous conflict with its citizens; it uses scorch-earth military expeditions in the Ogaden region to the east and makes occasional incursions into Kenyan territory pursuing armed resisters. The regime is also locked in constant conflict with Eritrea in the north. This is the reason why the regime has one of the biggest standing army in Sub-Saharan Africa thus spending large portion of the poor country’s budget on the military while the danger of famine and lack of resources for basic needs of its population is always lurking around.
While this is the true reason for the TPLF regime to build an army that is beyond the country’s legitimate external security threat need, it cynically uses a fraction of this army in international peace keeping missions in order to get acquiescence from the West for its nefarious repression at home as well as use these missions as a source of hard currency income for its corrupt highest military brass. Recently, the Ethiopian government is even seen scheming to leverage its security cooperation with the West, hopefully in vain, for extending its repressive hand abroad by invoking the legitimate rebellion and resistance of Ethiopians as a terrorist act. The truth is that the Ethiopian people’s resistance is a very disciplined and well organized struggle that is focused only on a political goal of making Ethiopia a democratic country either by forcing the minority regime to come to table or removing it if it continues to persist on blocking Ethiopians’ right for self-government. The people’s resistance movement is also very much aware of its responsibilities for the Ethiopian people, the people of the region and the international community. It is a resistance movement which is informed from the rich tradition of Ethiopian history. It is not a group of bandits and terrorists. It includes several members of the opposition who contested the ill-fated 2005 election. In deed it is a democratic force and represents a cross section of Ethiopians.
In their long history of existence, Ethiopians have shown no affinity for internalizing any sort of extremist ideology let alone to terrorist practice despite the persistent attempt to impose communism during the military regime and ethno-centric politics by the current regime on them. The history of Ethiopia is replete with building good relationship with its neighbors, peaceful coexistence and social stability. Ethiopian history also shows the courage and willingness of the people to lay their lives and honor to resist and prevail over colonialism and minority rule.. Witness the Ethiopian people’s glorious victory in the battle of Adwa and their resistance against fascist Italy even when the world turned its face and gave them its cold shoulders.
To stay true to our forefathers’ tradition saying no to oppression and its own commitment for democracy, UMSED pledges to work hard and to pay the necessary sacrifice to put an end to the tyranny of TPLF dominated regime and to assure that the TPLF regime becomes the last dictatorship in Ethiopian history. The UMSED appeals to the peace loving people of the world and the international community to stand in solidarity with the Ethiopian people; for it is only by democratizing Ethiopia that a lasting stability can be achieved and the specter of terrorism can be dealt with effectively in one of the most volatile regions of the world. Anything else will further destabilize Ethiopia and turns the Horn of Africa into a hot bed of terrorism.
From the Foreign Relations Office of United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED)
September 25, 2015