Wednesday, October 21, 2015

ወያኔ የኑሮ ውድነት ለመደበቅ ቢሞክርም ሊደበቅ አልቻልም፣

October 21, 2015
በሃገራችን በኢሀዴግ ስረአት ብልሹነት ምክንያት የተነሳ የህዝባችን የኑሮ ውድነት ከግዜ ወደ ግዜ እየተባባሰና በተለይም ዝቅተኛ የኢኮኖሚ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ካለው የገበያ ውደነትና የሚፈለገው የእህል አይነት ባለ ማገኘታቸው በረሃብና በችግር ውስጥ ሆነው ኑራቸውን ይመራሉ።
ይሁን እንጂ የሃገሪቱ መሪ ተብየው የኢህአዴግ ሰረአት በተለያየ ቦታዎች የሚገኙ ህዝብ በቂ ምርት ባለ መኖሩ የፈጠረዉ ዋጋ ግሽበት እየተሰቃየ ባለበት ውቅት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በዕደገት ጎዳና ላይ እየገሰገስን ነው በማለት በሞተ ቃላት ሲናገር ይሰማል።
በተለይም በአሁን ሰአት ከዝናብ መጥፋት ጋር ተያይዞ በርካታ ዜጎች በቤታቸው ውስጥ እየሞቱ ምንም አይነት የመንግሰት ደጋፍ ያለመደረጉ እንዲሁም በተለያየ የሃገሪቱ ክፍል ከግዜ ወደ ግዜ በፍጠነት እየተባባሰ ያለዉ ኑሮ ዉድነት ትኩረት ሳይሰጠው ህዝባችን አልተቸገረም እያለ በቴሌቭዥን መስኮት መናገሩ ለህዝብ ያልቆመ መንግስት መሆኑን አሰረጂ ነገር ስለ ሆነ ህዝብ በገዡዉ የኢህኣዴግ ስርዓት ያለው እምነት ሙሉ በሙሉ ተሟጦ ተስፋ ቆርጦ ይገኛል።
በተግባር በመስራት ሳይሆን በማሰመሰል የሚታውቀው የኢህአደግ ስርአት ህዝብ በልመና በየመንገዱ ሴት ወንድ ትንሸ ትልቅ ሳይል በየሁቴል ቤቱ የተረፈ ምግብ ለመግዛት ወረፋ ይዞ መገኘቱ የሃገሪቱ የኢኮኖሚ ውድቀትን አመላካች መሆኑን ያስገነዝባል።
ሆኖም ተጎጅው ህብረተሰብ ችግሩን በተደጋጋሚ ቢናገርም ሰሚ አካል ያለማገኘቱ ብሶቱንና ሀዘኑ ከባድ እንዲሆን አድርጎት እያለ ባለሃብቶቹ ደግሞ ደስ ባላቸው ዋጋ በገበያ እየሸጡ በድሃው ህዝብ ላይ የሚፈልጉትን ያህል ዋጋ ስለሚጩንበት ህብረተሰቡ ለመግዛት ከአቅሙ በላይ ሆኖበት በችጋርና ረሃብ እየተሰቃየ ይገኛል።
የመንግሰት ሰራተኛ በተመለከተ ከሚከፈለው ገንዘብ ማነስ የተነሳ የወር ክፋያው የእህል መግዣ የወጥ (ማተሪያል) ማለትም የሽንኩርት የዘይት የመሳሰሉ ለሟሟላት አቅም ባለመኖሩ ምክንያት የሚከፈለው የቤት ኪራይ በማጣቱ ወደ ሌላ ሁለተኛ ሃገር በመሰደደ ላይ ይገኛል።
ስለ ሆነም የኢህአደግ ሰረአት ህዝባችንን በቀን ሶሰት ግዜ መመገብ ችለናል እያለ በየመድረኩ በባዶ ቃላት ለብዙ አመታት እየተናገረ ቢሆኑም ህዝብ ግን በተፈጠረው የኑሮ ወድነት የተነሳ መሬቱን ተረከቡኝ ግብር መከፈል አልቻልኩም በማለት በመንግሰት ላይ ያለውን ተቃውሞ በመግለጽ ላይ ይገኛል።
ሰሞኑን የኢህአደግ አመራሮዎች በአዲስ አበባ አንድ የእህል መጋዘን ባደረጉት የገበያ ጉብኝት ለህዝብ በሰጡት መልስ ምንም አይነት የዋጋ ውደነት የለም ሲሉ ተሰምተዋል ተጠቃሚው ህዝብ ግን ይህ የተሰጠው ምላሸ እጅግ አድረጎ እንዳሰቆጣው ለመረዳት ተችሏል።
ህብረተሰቡ ገንቢ የሆኑ ምግቦችን ማለትም እንደ ስጋ ቅቤ መጠቀም ከተው ብዙ አመት ያስቀጠረ በመሆኑና በየክልሉ እና በአዲሰ አበባ ከተማ የሚገኙ የምግብ ቤቶች የሚሰሩ ባለሃብቶች ተጠቃሚ ካለመኖሩ የተነሳ በተጨማሪም ችግሩ እየተባባሰ በመሄዱ ምግብ ቤታቸውን ለመዝጋት ተገደዋል።

No comments: