Monday, December 30, 2013

ኢንጂነር ግዛቸው የዉህደት ጥሪ ለሰማያዊ/መኢአድ/መድረክ/አረና/ኢዴፓ አቀረቡ

December 30/2013

የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ «በመድረክ ዙሪያም ሰፊ ዉይይት ያደረገ ሲሆን፣ አዲሱ ብሄራዊ ምክር ቤት፣ በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ ፓርቲው ከመድረክና ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የጀመረውን ውህደት እልባት እንዲያበጅለት መመሪያ ሰጥቷል» ስንል መዘገባችን ይታወቃል። በዚህ ዙሪያ አስተያየት ያደረጉት አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ድርጅታቸው ከአሁን በኋላ በግንባርነት እንደማይሰራ ገልጸዋል።
ድርጅቶች ልዩነቶቻቸዉን አጣበው ወደ ዉህደት በመምጣት፣ በጋራ ትግሉን ወደፊት ማራምድ እንዳለባቸው የገለጹት ኢንጂነር ግዛቸው የዉህደትን ጥቅም አጠንክረው አስምረዉበታል። ለመኢአድ፣ ለመድረክ፣ ለሰማያዊ ፓርቲ፣ ለአረና እንዲሁም በአቶ ልደቱ አያሌዉ ይመራ ለነበረዉ ለኢዴፓም ጥሪ አቅርበዋል።
ዉህደት ማድረግ ካልተቻለ ግን፣ አንድነት ለድርጅቶች እዉቅና ሰጥቶ መተባበር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ (እንደ በጋራ ሰልፍ መጠራት የመሳሰሉ) ትብብር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይል የሚገልጽ እድምታ ያለው ንግግር ነበር ኢንጂነር ግዛቸው ያቀረቡት።
መኢአድና አረና ከአንድነት ፓርቲ ጋር የመዋሃድ ፍላጎት እንዳላቸው ከዚህ በፊት ማሳወቃቸው፣ በዚህም ረገድ አንዳንድ ንግግሮች እየተደረጉ እንደነበረ ይታወቃል።
የመድረክ አባል ድርጅቶች ከአንድነት ጋር ለበርካታ አመታት አብረው የሰሩ እንደመሆናቸው የጠነከረ መቀራረብ ሊኖራቸው እንደሚችል ቢታወቅም፣ በዉህደቱ አንጻር ግን ምን ያህል ከአንድነት ጋር ለመዋሃድ እንደሚፈልጉ፣ ምን ያህል ያላቸውን መሰረታዊ የፖለቲካ ልዩነቶች ለማጥበብ እንደሚችሉ ብዙ የሚታወቅ ነገር የለም።
ሰማያዊ ፓርቲ ለጊዜዉ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብሮ የመስራት አዝማሚያ ያለው አይመስልም። ነገር ግን በአንድነት ዉስጥ ሊከሰቱ የሚችሉ ተጨባጭ ለዉጦችን በመመልከት የአቋም ለዉጥ ሊያደርግ የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም።
የዉህደቱ ጥሪ ለኢዴፓ መቅረቡ ብዙዎችን ሊያነጋገር የሚችል አዲስ ዜና ነው። በአንድነት አካባቢ ከኢዴፓ ጋር አብሮ ለመስራት ፍላጎት መታየቱ፣ በቅርቡ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ አቶ ልደቱ አያሌው ላቀረቡት በጋራ የመስራት ጥሪ፣ ምላሽ ተደረጎ ሊወስድ የሚችልበት ሁኔታም ሳይሆን እንደማይቀር ነዉ።
ኢንጂነር ግዛቸው ለተቃዋሚ ድርጅቶች የዉህደት ጥሪ በማቅረብ ብቻ አልተወሰኑም። ገዢዊ ፓርቲ ኢሕአዴግ የከረረ አቋሙን ቀይሮ ለእርቅና ሰላም እንዲዘጋጅም አሳስበዋል።

. Jawar openly calling Jihad and genocide against Christians and other ethnic groups in Ethiopia. He was making unfounded historical fabrications when he was addressing Ethiopian Muslims in America

December 29/2013

Jawar openly calling Jihad and genocide against Christians and other ethnic groups in Ethiopia. He was making unfounded historical fabrications when he was addressing Ethiopian Muslims in America , preaching to his fellow Muslims and Oromo people (whom he claimed are all Muslims) to liberate 'fellow Muslims in central and northern Ethiopia.He is even went on saying we will cut their throat with machate . We Ethiopians need to urge Colombia university to dismiss this man. If hate speech were banned in Nazi Germany ,Holocaust could not have happened.




.

የነጻነት ታጋይነት ምስክሩ እና የነጻነት ነጣቂ ምሳሌነቱ

December 29/2013

ሰላም ጤና ይስጥልኝ ያልገባችሁና ያልተረዳችሁ ወገኖቼ ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በስጋ ለተለዩት፤ በተግባራቸው ከበሬታን፤ በእሳቤያቸው አንቱታን፤ ያተረፉት የደቡብ አፍሪካው የነጻነት አባትና፤ የዴሞክራሲና ፍትህ፤ የሰብአዊ መብትና የእድገት አርማ የሆኑትን ማዲባ ኔልሰን ማንዴላን አስመልክቶ በዓለማት ላይ ባሉ የመገናኛ ብዙሃን በብዛት ከበሬታቸውንና አድናቆታቸውን ችረዋቸዋል፡፡
ማዲባ ስልጣንን የለቀቁት ግን በምርጫ ተሸንፈው ሳይሆን በፈቃዳቸው ለሌሎች አርአያ ለመሆን ስልጣንን በፈቃድ ማሳለፍን ለማስተማር ሲሉ ነው፡፡ ማዲባ በምርጫ ባሸነፉበትም ወቅት ምርጫውን ለማሸነፍ ሲሉ ማጭበርበር አልፈጸሙም፤ ካርድ አልነጠቁም፤ በስልጣን በመመካት የድምጽ ቆጠራውን አልመዘበሩም፤ እድሜያቸው ያልደረሱትንና በሕገመንግስት ላይ ሊመርጡ አይገባም የተባሉ ወታደራዊ አባላትን አሰልፈው ድምጽ አልመዘበሩም ወዘተርፈ…..
በዚህ የሃዘን ስርአት ላይ ሃገራቸውንና ሌላም የተቀመጡበትን ወንበር ወክለው ለለቅሶ በቦታው የተገኙት በርካታ የሃገር መሪዎች፤ ታዋቂ ሰዎች፤ ነበሩ፡፡ በርካታ ጽሁፎችም የማዲባን ታላቅነት በማጉላትና ማንነታቸውን በማወደስ የመላው አፍሪካ አኩሪ መሪነታቸውን ተናግረዋል፡፡ የእኛም ሰውዬ ወንበር ላይ ተቀምጧልና በዚህ ስፍራ ‹‹ተገኝቶ›› ነበር፤ አዎን ተገኘ ይባል፡፡ ተገኝቶም ባደረገው ንግግር አንድም ቦታ ላይ ማንዴላ፤ በኢትዮጵያ እንደነበሩና ስልጠናም እንደተሰጣቸው፤ ማንዴላ ለኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር እንዳላቸውና የኢትዮጵያ ጉዳይ እንደሚቆረቁራቸው የታወቀ ቢሆንም የተገኘው የኛ ሰውዬ ግን ስለዚህ ጉደይ አንድም ቃል አልተነፈሰም፡፡
ይህ ደሞ ብዙዎችን ኢትዮጵያዊያን ሲያናድድና ሲያበሳጭ የሌሎች ሃገራትን ሰዎች ደግሞ አስገርሞ አስደምሟል፡፡ ለምን ሊባል ግን አይገባም ምክንያቱም ሰበቡ የታወቀ ነውና! የኛ ሰውዬን የፈጠራቸው ሰውዬ በሞቱ ጊዜ ባደረገላቸው የብድር መላሽ ያድርገኝ፤ እኔን ደፋ ያድርገኝ ንግግሩ ላይ በዓለም ተወዳዳሪ የማይገኝላቸው መሪ ብሎ በመናገሩ በማዲባ ስርአተ ቀብር ላይ ከተናገረው ያለፈ መናገር አይችልም፡፡ እንዴት አድርጎ ማዲባን ሊያመሰግኑና ከኢትዮጵያ ጋር ስለነበራቸው ፍቅር ሊናገር ይደፍራሉ፡፡ የሱ ጀግና እኮ ከበረሃ ጀምሮ ሲገድል ሲያስገድል በመግደል ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ነው፡፡
ማንዴላ መች ገደሉ? መች አስገደሉ? የሱ ጀግና እኮ ስልጣንን በካርድ ስርቆትና በእስር ያገኘው ነው ማንዴላ መች የምርጫ ካርድ ሰረቁ? መችስ ተቃዋሚ አሰሩ? የሱ ጀግና እኮ ሰላማዊ ሰዎችን ወንድ ሴት ሳይል፤ ልጅ አዋቂ ሳይመርጥ ያሰጨፈጨፈ ነው ማንዴላ መች ለዚህ የውርደት ክብር በቁ? የሱ ጀግና እኮ ራሱን ሽቅብ አውጥቶ ከታማኝነት ርቆ፤ ከአንድነት ተለያይቶ፤ ተወልዶ ያደገበትን ሃገር የከዳ ነው ማንዴላ ሃገራቸውን መች አፈራረሱ መቼስ ከዱ? የሱ ጀግና ከኢትዮጵያዊያን የውጭ ዜጎችን የሚያፈቅር፤ በአፍቅሮ ነዋይ ሰክሮ የረገጠውን ሁሉ ለሽያጭ፤ የተቃወመውን ሁሉ ለእስር፤ ለምን ያለውን ሁሉ ለሞት የሚዳርግ ነው ማንዴላ ከወገኖቻቸው ምንንም ሳያስበልጡ፤ ከሃገራቸው ሌላውን ሳይመርጡ፤ ለቆሙለትና መከራ ፍዳ ለተቀበሉበት ሃገርና ህዝብ ታማንነታቸውን ጠብቀው የተከበሩ ከሃገራቸው አልፈው በዓለም ዙርያ አንቱታን ያገኙ ናቸው እና ወገኖቼ እንዴት አድርጎ ማንዴላንና ኢትዮጵያን አስተሳስሮ ለመናገር ይብቃ፡፡
ከኋላው አለንጋ ይዘው አፍ አፉን የሚጠብቁት መች ያናግሩትና፤ እሱስ መች ከተሰጠው ውጪ ይተነፍስና! ለነገሩ በገዳዮች፤ በሌቦች፤ በአጭበርባሪዎች፤ በንጹሃን አሳሪዎች አፍ የኢትዮጵያና የማንዴላ ፍቅርና ግንኙነት ከሚነገር አለመነሳቱ ይሻላል፡፡ ተዋርደው ከሚያዋርዱ መጠበቃቸው ያልተጠበቀ ምርቃን ነው፡፡

Sunday, December 29, 2013

በስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ላይ የጸረ ግብረ ሃይል ባይ ነኝ በኩል የደረሰውን አሳዛኝ ግፍና በደል የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አባላትን እንባ ያስራጨውን ክስተት ይመልከቱ

Genocide or Terrorism? Transnational Advocacy and the Ogaden Conflict

December 29/2013

by Terrence Lyons, Associate Professor of Conflict Resolution at George Mason University

Political processes and outcomes within particular nation-states today are significantly impacted by the migrant communities and diasporas of those polities. Understanding contemporary politics therefore requires a perspective that recognizes how political processes and actors increasingly operate both within and across specific territorially defined spaces. The polity often remains defined by a specific identity with attachments to a particular “homeland,” but these communities are now often transnational and characterized by patterns of ongoing migration and movement. 

Diverse political entrepreneurs — including, in some cases, the governments of migrant sending nations — increasingly see diaspora networks as effective instruments to mobilize resources and key constituencies in order to shape political outcomes on a particular issue in a specific state. (For more on transnational politics see the volume I edited with Peter Mandaville, Politics from Afar: Transnational Diasporas and Networks).

One channel of transnational political activism attempts to frame local conflicts for international audiences in order to shape global policy toward parochial issues. In Ethiopia, for example, there has been a protracted conflict in the Somali-inhabited eastern region where the Ogaden National Liberation Front (ONLF) has fought with the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF). The ONLF mobilized its supporters in the diaspora and attempted to link its cause with transnational advocacy groups focused on genocide prevention. At the same time the EPRDF reached out to its supporters in an effort to frame the conflict within the broader narratives of the global war on terrorism. Both of these competing transnational campaigns sought to shape the policies of governments and international organizations, and the ONLF further sought to influence prominent international advocacy groups and human rights organizations. The outcome of a very local conflict over control of the Ogaden was linked to larger regional, international, and transnational political processes.


These dynamics were illustrated by a particular episode in August 2009 when a government-led delegation from Ethiopia’s Somali region visited diaspora leaders in Sweden and North America to brief them on current developments. While the ruling EPRDF sought to characterize the ONLF as an “instrument of other anti-peace elements in Somalia and Eritrea who have been playing a game with the blood of the innocent civilians in Somalia for the last 18 years and who want to import the same game into the people of the Somali region of Ethiopia,” the Ogadeni diaspora leaders mobilized to counteract the tour’s narrative. The diaspora recognized the delegation’s visit as an opportunity to educate and influence the international community. Community leaders issued a press release noting their “shock” that visas would be issued to these “perpetrators of crimes against humanity in the Ogaden Region.”

In contrast with the security language used by the officials from Ethiopia, those in the diaspora emphasized the language of human rights and international law: “We are also extremely concerned with the ongoing and widespread violations of human rights in the Ogaden, specifically the right to life, the right not to be subjected to torture or to cruel, inhuman or degrading treatment or punishment, the right to liberty and security, the right to a fair trial and the rights to freedom of assembly, association and expression.” An editorial on the diaspora-run website, Ogaden.com, named specific individuals within the visiting delegation and insisted that all were “directly responsible for the genocide that has, and continues to date, taken place in Ogaden.” The statement went on to urge those whose relatives are victims of the “Ogaden genocide” to lodge criminal complaints in Sweden and elsewhere against members of the delegation. “We beg these victims to use the European, American, or African legal systems to bring these perpetrators to justice.”

In return, the Ethiopian regime attempted to frame the issue as a response to “terrorism” and illegitimate interference in domestic affairs by Asmara. Addis Ababa asked Washington to add the ONLF and other opposition groups to the list of terrorist groups and therefore political activities and most importantly fundraising remained legal in the United States. The US declined. The Ethiopian Ministry of Foreign Affairs saw this as a double-standard on terrorism, where terrorists who targeted Africans were not treated as seriously as terrorists who targeted Americans. A pro-EPRDF diaspora website even asked why “Ethiopia’s most wanted terrorist roam America freely!”

The struggle to determine how the violence in the Ogaden was understood internationally was deeply contested, involving the ONLF, the Ethiopian government and key figures in multiple diasporas. Each of these actors sought to influence important governments, international organizations, and transnational advocacy groups. All recognized that the outcome of the armed struggle would be determined in part by the reaction of the United States and other international actors. The transnational dimensions of the civil war in the Ogaden are fundamental to conflict dynamics and key to understanding the main parties and their strategies. As is true throughout the networked world today, actors and processes that are based in communities that are geographically dispersed and linked through transnational networks shape local conflicts and politics.

Ze-Habesha

የአኖሌ ሐውልት ጉዳይ … «አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል» እንዳይሆን – (ሞረሽ ወገኔ)

December 29/2013

በቅርቡ የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ በሚቆጣጠረው የቴሌቪዥን ጣቢያ አንድ ዝግጅት ቀርቦ ነበር
የዝግጅቱ ትኩረትም «የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሠራዊት በአርሲ እናቶች ላይ በፈፀመው የጡት መቁረጥ ግፍ» መታሠቢያ የሆነ ሐውልት ስለመቆሙ ነበር። «ነገርን ከሥሩ ፣ ውኃን ከጥሩ» ይባላልና ለመሆኑ የዚህ አዲስ ሐውልት ባለቤቶች እነማን ናቸው? በሐውልቱስ መቆም ማን ምን ፋይዳ ያገኝበታል? ብሎ መጠየቁ ተገቢ ይሆናል።
ከታሪክ እንደምንገነዘበው ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ነገሥታት ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ታሪካዊ ተግባሮችን ያከናውኑ ከሚባሉት ጥቂቶች መካከል የሚመደቡ ናቸው። የኢትዮጵያን አንድነት በማጠናከር ረገድ ከአፄ አምደጽዮን ወዲህ የተነሡት ትልቁ አገር ገንቢ ናቸው። በዚህ አኳያ የላቀ ድርሻ ያላቸው ምናልባትም ከዚያ በፊት እነ አፄ ካሌብ እና አፄ ኢዛና (አብርሃ) ናቸው። ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት ደረጃ ኮትኩተው ካሣደጓቸው ከዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የላቀ ስኬት ለማስመዝገብ ብልህነቱም ሆነ መልካም አጋጣሚው ነበራቸው። ከሁሉም በላይ በጥቁር አፍሪቃ ብቻ ሣይሆን በዓለም ደረጃ «ደካማ» የሚባሉ የዓለማችን ዜጎች «ጠንካራ» በሚባሉት ቅኝ ገዢዎች ላይ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገብ እንደሚችሉ እርሣቸው የመሩት የዐድዋው ድል ሕያው ምሥክር ነው። ስለዚህ እኒህን ሁሉ ታላላቅ ተግባሮች ባከናወኑ ንጉሠ ነገሥት ላይ ይህ ሁሉ ውርጅብኝ እና ስም ማጉደፍ በእነማን ፣ ለምን ተብሎ እንደሚካሄድ አብጠርጥሮ ማሣወቅ ያስፈልጋል።
ለመሆኑ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ማን ነበሩ? ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የሸዋው ንጉሥ የኃይለመለኮት ሣህለሥላሤ እና የወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያቦ ልጅ ናቸው። በአባታቸው ወገን ኢትዮጵያን ከቀዳማዊ ምኒልክ ጀምሮ ያስተዳደረው የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት ደም ያላቸው ሲሆን እናታቸው ደግሞ ከጉራጌ ነገድ የሚወለዱ ናቸው። በእናታቸውም ሆነ በአባታቸው ወገን ያለው ዝርዝር የትውልድ ሐረጋቸው በደንብ ቢጠና ከሁለት በላይ ከሆኑ ነገዶች ቅይጥ ዘር እንደሚኖራቸው እሙን ነው። በዚህ ጽሑፍ ደረጃ ለማስተላለፍ የሚፈለገው ሃቅ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ቢያንስ ከሁለት የኢትዮጵያ ነገዶች የተገኙ እንጂ የዘመኑ ዘባራቂዎች በሐሰት እንደሚደልዙት «የዐማራ ንጉሠ ነገሥት» አልነበሩም። እርሣቸውም በየትኛውም አጋጣሚ ራሣቸውን በእንደዚህ ዓይነት መጠሪያ ገልፀው አያውቁም።
መቼም ሥልጣኔ ማለት ለሰው ልጅ መልካም ሕይዎት መደላደል የሚያስችሉ ቁሣዊ እና ኅሊናዊ ጉዳዮችን ማሟላት እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ማለት በቁሣዊ መልኩ ሲታይ የራቀውን ማቅረብ፣ የከበደውን ማቅለል፣ የተራራቁትን ማቀራረብ፣ ጨለማውን ብርሃን ማድረግ፣ ሙቀቱን ማቀዝቀዝ፣ ቀዝቃዛውን ማሞቅ፣ አድካሚውን ማቃለል፣ የጠበበውን ማስፋት፣ ባንድ ቃል ተፈጥሮን መግራት እና ለሰው ልጅ ሁለንተናዊ ጥቅም ማዋል መገለጫዎቹ ናቸው። በኅሊናዊ መልኩ ደግሞ ክፋትን በደግነት፣ ጠላትነትን በወንድማማችነት፣ ቂምን በይቅርታ፣ ካለፈው መጪውን፣ የኋሊት ከማየት ወደፊት ማትኮርን፣ የሕይዎት መመሪያ ማድረግ ነው። ሠሞኑን ይህችን ዓለም በሞት የተሰናበቱት የቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ መሪ ፕሬዘዳንት ኔልሰን ማንዴላ፣ የዓለምን የዜና አውታሮችን ትኩረት የሣቡት እና የዓለማችን ኃያላን መሪዎች በቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ላይ በብዛት ታድመው አድናቆታቸውን ለመግለጽ የተገደዱት፣ በአፓርታይድ አገዛዝ ለ፳፯ ዓመታት በመታሠራቸው አይደለም። ይልቁንስ ለአሣሪዎቻቸው ይቅርታ በማድረግ ራሣቸውን እና አሣሪዎቻቸውንም ጭምር ከኅሊና ተወቃሽነት ነፃ በማውጣታቸው፣ አልፎ ተርፎም ያለፈውን ክፉ ድርጊት ለታሪክ ትተው፣ ለወደፊቷ ደቡብ አፍሪቃ አንድነት ምቹ መሠረት በመጣላቸው ነው። እኒህ ተግባሮቻቸው ኔልሰን ማንዴላን የዘመናችን ታላቅ ሰው አድርገዋቸዋል። በተቃራኒው ግን በኢትዮጵያ ላይ የተጫኑ እና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጉዳይ አስፈጻሚዎች የሆኑት ዘረኛ የትግሬ-ወያኔዎች የዘመናዊቲቱን ኢትዮጵያ መሥራች ዳግማዊ አፄ ምኒልክን ነጋ ጠባ ያወግዛሉ፣ ሥራዎቻቸውንም ያራክሣሉ። ሻቢያ ፣ የትግሬ-ወያኔ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ኢትዮጵያውን ለዘመናት ይዘውት እና አስጠብቀውት የኖሩትን አንድነት በመናድ ሕዝቡን አገር-አልባ አድርገውታል። ከዚህም አልፈው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወደፊት ሣይሆን ወደ ኋላ እንዲያይ፣ እንዲሁም እርስ በርሱ ተናክሶ «ኢትዮጵያዊነት» የተሰኘ የዜግነት መታወቂያው እና «ኢትዮጵያ» የተባለችው አገሩ እንዳትኖር የሚያደርግ የልብ ወለድ ታሪክ በሐውልት መልክ አቁመው ትውልዱ እሳት እና ጭድ እንዲሆን እያደረጉት ይገኛሉ።
ሻዕቢያ እና ወያኔ በትጥቅ ትግል ዘመናቸው ኢትዮጵያን ለመበታተን ላቀዱት ዓላማ እውን መሆን፣ በአገሪቱ ካሉት ነገዶች መካከል በቁጥር ከፍተኛ መጠን ያላቸውን ዐማራን እና ኦሮሞን እስከ ወዲያኛው እንዳይገናኙ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራቸው ነበር፣ ዛሬም ነው። ለዚህም ተግባር አስፈፃሚነት «ተስፋዬ ገብረአብ» በመባል የሚታወቀውን በኢትዮጵያ ተወልዶ ያደገውን ግለሰብ፣ የሁለቱ ነገዶች ልጆች ወደፊት ዐይን ለዐይን ሊተያዩ የማይችሉበትን ሥራ እንዲሠራ ወያኔና ሻዕቢያ መመሪያ ሰጡት። ተስፋዬ ገብረአብም በተሰጠው መመሪያ መሠረት «የቡርቃ ዝምታ» የተሰኘ ዳግማዊ አፄ ምኒልክን እና የዐማራን ነገድ በጅምላ የሚያጥላላ ልብ ወለድ መጽሐፍ ጽፎ ከኦሮሞዎቹ በላይ ኦሮሞ ሆኖ ወጣ። «ላለቅስ ሲሻኝ ጢስ ወጋኝ» የሆነላቸው አንዳንድ የኦሮሞ ልሂቃንም «ለካ ይኸን ያህል ተበድለን ኖሯል» በሚል ስሜት ውስጥ በመግባት ዐማራውን የአባታቸው ገዳይ ደመኛ ጠላታቸው አድርገው ያዙት። ይህን ተከትሎም «የኦሮሚያ ክልል» በተሰኘው እና ጥንተ-መሠረቱ የዐማራው፣ የሐዲያው፣ የጉራጌው፣ የከምባታው፣ የሲዳማው ፣ የጋፋቱ ፣ የዳሞቱ፣ የዝዩ፣ ወዘተርፈ አጽመ-ርስት ከነበረው ቦታ ሁሉ ዐማራው በገፍ እና በግፍ እንዲባረር ተደረገ። ልብ ወለዱን መጽሐፍ የኦነግ ነባር ሰዎች ሣይቀሩ ዕውነታኛ ታሪክ ነው ብለው አመኑ። በመሆኑም የኦነግ ወታደራዊ መሪ የነበረው አብረሃም ለታ ስለቡርቃ ዝምታ አስተያየት ሲሰጥ፦ ይህ መጽሐፍ በኦሮሞ ልጅ ቢጻፍ ኖሮ የቱን ያህል ዋጋ ሊኖረው ይችል አንደነበር መቆጨቱን ይፋ አድርጓል። ከሁሉም የሚያሣዝነው ግን፣ የልብ ወለዱ መጽሐፍ የተዘጋጀው ሆን ተብሎ ኢትዮጵያን ለመበታተን በሻዕቢያ እና በወያኔ የተቀነባበረ ሤራ አካል መሆኑ በግልጽ እየታወቀ፣ ኢትዮጵያ ብትከፋፈል በመጀመሪያ ተጎጂ ከሚሆነው ከወላይታ ነገድ በሚወለደው በኃይለማርያም ደሣለኝ አመራር፣ በተስፋዬ ገብረአብ ልብ ወለድ መጽሐፍ መሪ ገጸ ባሕሪይ በ«አኖሌ» ስም በአርሲ ውስጥ ሐውልት እንዲሠራለት መደረጉ ነው።
ሐውልቱ «የኦሮሚያን ባህል እና ታሪክ ለትውልድ ለማስተዋወቅ» በሚል ሽፋን በሥፋት በተንጣለለ የባህል ማዕከል እና ሙዚየም መካከል የቆመ ነው። በስተቀኝ ባለው ፎቶግራፍ እንደሚታየው፣ በተዘረጋ ቀኝ እጅ መዳፍ ማህል የተቆረጠ ጡት ጉች አለበት። ይህ ሐውልት የሚወክለውም በዐፄ ምኒልክ የአገር ግንባታ ወቅት ሠራዊታቸው «በኦሮሞ ሴቶች ላይ ፈጸሞታል» የሚባለውን የ«ጡት መቁረጥ ድርጊት» እንዲወክል ታስቦ መሆኑ ተገልጿል። በእርግጥ ይህ ሐውልት ዕውነትን የሚወክል ቢሆን ኖሮ ምንኛ ጥሩ በሆነ። ነገር ግን አንዳችም የታሪክ ዕውነትነት የሌለው መሆኑን ማሣያው፦ በመጀመሪያ ደረጃ «የቡርቃ ዝምታ» የተጻፈው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ታስቦ ነው። ሁለተኛ ተስፋዬ ገብረአብ ዕውቀቱን ከቤተሰቦቹ አገኝቷል እንዳይባል ትውልዱ ከኤርትራ ወደ ደብረዘይት በአፄ ኃይለሥላሤ የአገዛዝ ዘመን በሥራ ምክንያት ከመጡ የኤርትራ ተወላጆች እንደሆነ ይታወቃል። ሦስተኛ በትምህርት አገኘው እንዳይባል ፲፪ኛ ክፍልን እንኳን በወጉ ያጠናቀቀ አይደለም። አራተኛ በሥራ ዓለም ያካበተው ዕውቀት ነው እንዳይባል ዕድሜውም ሆነ ሌሎች ሁኔታዎች ለዚህ አያበቁትም። ስለዚህ የቡርቃ ዝምታን እንዲጽፍ ልብ ወለድ ኃሣቦችን የሰጡት የሻዕቢያ እና የወያኔ ሰዎች ስለመሆናቸው ከተስፋዬ ማንነት የምንረዳው ሃቅ ነው። የቡርቃ ዝምታ እንዲጻፍ ያደረጉ ሰዎች አብይ ግባቸው፣ ዐማራ እና ኦሮሞ ለዘለዓለም እንዳይገናኙ አድርጎ ኢትዮጵያን የማጥፋት ዓላማቸውን ማሳካት መሆኑ ግልጽ ነው። የሐውልቱ መገንባትም፣ በሐሰት የተገነባውን ኅሊናዊ ቅዠት ቁሳዊ መሠረት በመስጠት
የሁለቱን ነገድ አባሎች እንዳይይገናኙ አድርጎ ማፋታት ብቻ ሳይሆን ማጠፋፋት መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው። ምክንያቱም ይህን ሐውልት የሚያይ ወጣቱ የኦሮሞ ልጅ ከማንም የዐማራ ልጅ ጎን ፈጽሞ አይቆምም። አለመቆም ብቻ ሳይሆን፣ ዐማራን አድኖ እንዲያጠፋ፣ የማይፈታ የቂም ቋጥሮ እንዲይዝ እና በቀልን እንዲወልድ የሚያደርግ እንደሆነ ለማንም የተሰወረ አይደለም። ይህም ቢሆን ሐውልቱ የሚወክለው የተስፋዬ ገብረአብን የምናብ ዓለም እንጂ፣ ዕውነቱን ባለመሆኑ ባህላቸውን እና ታሪካቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁ የኦሮሞ ልጆች በዚህ እኩይ የትግሬ-ወያኔ ማባበያ ይደለላሉ ተብሎ አይገመትም። እንደዕውነቱ ከሆነ ጥንትም ቢሆን የወንድ ብልት መስለብ እና የሴት ጡት መቁረጥ የኦሮሞ እና የአንዳንድ የኢትዮጵያ ነገዶች ባህል እንጂ፣ የዐማራው ባህል አለመሆኑ የታወቀ ነው። ለዚህ ማስረጃ ካስፈለገ አሁንም በዘመናችን በጉጂ፣ በከረዩ፣ በአርሲ አካባቢዎች ይህ ባህል አለመተዉ ይታወቃል።
ዐማራው፣ ለአገር ዕድገት እና ለብልጽግና የሚበጀው፣ ያለፈውን ትቶ ወደፊት ማዬት፣ ክፉውን በበጎ አለመመለስ መሆኑን በመገንዘብ፣ በሌሎች የተፈጸሙበትን ግፎች ለልጆቹ ግቶ ባለማሳደጉ እንጂ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንደ ዐማራው በሌሎች ነገዶች እና ጎሣዎች ልሂቃን በደል የተፈጸመበት የለም። ሆኖም በዕምነቱ፣ በባህሉ እና በአመለካከቱ «ጠላትህን ውደድ፣ ክፉን በክፉ አትቃወም፣ ክፉ ለሠራብህ ደግ መልስለት» በሚለው ኃይማኖታዊ ትምህርት የተገራ በመሆኑ፣ በማናቸው ነገድ እና ጎሣ ላይ ቂም ቋጥሮ በቀል አለመፈጸሙ እንደአላዋቂ አስቆጥሮት፣ ለተደጋጋሚ ጥቃት ዳርጎት እያየን ነው። የተስፋዬ ገብረአብ ልብወለድ እንደ ዕውነት ተቆጥሮ ዐማራን ለማጥፋት እንደመሣሪያ እንዲያገለግል ከተደረገ፣ ኦሮሞውም ለወደፊት ልዕልናው የሚበጀውን ሣይሆን፣ ሁልጊዜ ባልተፈጸመበት የልብ ወለድ ታሪክ ላይ ተመሥርቶ አገሩን ኢትዮጵያን እና ወገኑን በጠላትነት እንዲያይ ይገፋፋል። ይህ ደግሞ ለራሣቸው ለኦሮሞው ነገድ ተወላጆችም ሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም አይጠቅምም። እንዲያውም በትክክለኛው አቅጣጫ ከተሄደ ዐማራውም በታሪኩ በተደጋጋሚ በደረሱበት ጭፍጨፋዎች እና ግፎች ላይ በመመርኮዝ በርካታ ሐውልቶችን ማሠራት ይችላል፣ አገሪቱም ሐውልት በሐውልት ትሆናለች። ለአብነት ያህል በዐማራው ላይ የተሠሩ ግፎችን እንይ፦

አንደኛ፦ ትውልዱን ከሶማሌ ነገድ የሚስበው አህመድ ኢብራሒም አል-ቃዚ (ግራኝ አህመድ) ከ፲፭፻፲፱ ጀምሮ በዘንተራ የጦር ግንባር እስከሞተበት ረቡዕ የካቲት ፳፯ ቀን ፲፭፻፴፭ ዓም ድረስ፣ ለ፲፯ ዓመታት ኢትዮጵያን በወረራ እሳት በለበለባት ወቅት፣ የጥቃቱ ዋነኛ ሰለባ የነበሩት ዐማራ እና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ነበሩ። ግራኝ አህመድ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን በአሠቃቂ ሁኔታ አስጨፍጭፏል። በአምባ ግሼን ላይ ታሥረው የነበሩትን የዘመኑን የነጋሢ ዘሮች በሙሉ አርዶ ገድሏቸዋል። በሺህዎች የሚቆጠሩ አብያተ ክርቲያናትን የነበራቸውን ልዩ ልዩ ቅርስ እና ንብረት አስዘርፎ ሙሉ በሙሉ አቃጥሏቸዋልል። ይባስ ብሎም በርካታ ክርስቲያን ዐማሮችን በባርነት እየፈነገለ ወደ አረብ አገሮች፣ ቱርክ፣ ፋርስ (ኢራን)፣ ሕንድ፣ ፓኪስታን እና ኢንዶኔዥያ ሣይቀር ሸጧል። ከዚህም በተጨማሪ የፍራፍሬ ዛፎችን ሣይቀር ከሥራቸው እያስመነገለ አጥፍቷል።
ሁለተኛ፦ በጦርነት የማረኩትን የዐፄ ገላውዲዎስን አንገት የቆረጡት እና ሐረር ግንብ ላይ የሰቀሉት አደሬዎች ናቸው።
ሦስተኛ፦ ኦሮሞዎች ከ፲፭፻፶ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ ከሕንድ ውቅያኖስ ጠረፍ ተነስተው አሁን እስካሉበት የአገሪቱ ክፍሎች ድረስ የተስፋፉት ባለፉበት አገር ሁሉ ወተት እና ማር እያዘነቡ ሣይሆን፣ አልገዛም ብሎ የተዋጋቸውን ነባሩን ሕዝብ በጅምላ በመጨፍጨፍ፣ ሚስት ለማግባት የደረሰውንም በመስለብ፣ የሴቶችን ጡት እየቆረጡ፣ በአጠቃላይ የተወራሪውን ሕዝብ ማንነት በከፍተኛ ወታደራዊ ዘመቻዎች በመጨፍለቅ እንደሆነ ይታወቃል።
አራተኛ፦ በ፲፯፻፸ዎቹ በአገሪቱ ከነበሩት መሥፍኖች አንዱ የትግሬው ራስ ሥሁል ሚካኤል ነበር። ይህ መሥፍን በጎንደር ተቀምጦ ነገሥታቱን በአሻንጉሊትነት በማስቀመጥ እና በታሪካችን «ዘመነ-መሣፍንት» የሚባለውን አሣፋሪ የታሪክ ምዕራፍ በመክፈት ይታወቃል። በእርሱ የምሥፍንና ዘመን በአስተዳደሩ ያልተደሰተው ፋሲል የተባለ የጎጃም የጎበዝ አለቃ በአገዛዙ ላይ አመጸ። ሥሁል ያመጸውን ፋሲልን ለማስገበር በርካታ ሠራዊት አሰልፎ ወደ ጎጃም ዘመተ። በዘመቻውም ሥሁል ሚካኤል ቀንቶት ፋሲልን ድል ነሣ። ከድል በኋላ የሥሁል ሚካኤል ሠራዊት ጨዋቃ የተባለውን የፋሲል ተከታይ አርደው፣ ቆዳውን ስልቻ በማውጣት ጭድ ሞልተው፣ ለሥሁል ሚካኤል ግዳይ ጥለውለታል። ይህ በዚያን ዘመን በትግሬዎች አማካይነት በዐማሮች ላይ የተሠራ ግፍ ነው። ወደ ኋላ ማየት ካስፈለገ ይህም ሐውልት ያሻዋል።
አምሥተኛ፦ ዐፄ ዮሐንስ ፬ኛ የወሎን እስላም «ክርስትና ካልተነሳህ» ብለው ምላስ ቆርጠዋል፣ አፍንጫ ፎንነዋል፣ ከርስቱም ነቅለዋል።
ስድስተኛ፦ ዐፄ ዮሐንስ «ደርቡሽን እዋጋለሁ» ብለው ከትግራይ ከተነሱ በኋላ አስቀድመው የዘመቱት ወደ በደርቡሽ ላይ ሣይሆን በሚያሣዝን ሁኔታ በደርቡሽ በተቃጠለው በጎንደር፣ ከደርቡሽ ጋር በተዋጋው በጎጃም እና «የእስልምና ኃይማኖትህን ቀይር» ብለው ባስገደዱት በወሎ ሕዝብ ላይ ነበር። በተለይም በጎጃም ሕዝብ ላይ ልጅ አዋቂ ሣይለዩ ከሕፃን እስከ ሽማግሌ ሁሉንም በግፍ አስጨፍጭፈዋል። ይህንንም ተግባራቸውን አብረዋቸው በጦርነቱ ዘምተው የነበሩት ግብፃዊው ጳጳስ አቡነ ሉቃስ «ድርቡሽን እዋጋለሁ ብለህ መጥተህ፣ አንተ ራስህ በጎጃም ሕዝብ ላይ ድርቡሽ ሆንክበት» በማለት የግፍ ግድያውን ማውገዛቸው ይታወቃል። የጎጃም አስለቃሽም የግፉን አሰቃቂነት በመመልከት እንዲህ ብላ ማስለቀሷ ይታወሳል።
ጎጃም ተቃጠለ ዐባይ እስከ ዐባይ፤
ትግሬ ቅጠል ይዞ ሊያጠፋው ነዎይ፤
ሰባተኛ፦ በ፲፱፻፳፰ ዓም የጅማው ባላባት የአባ ጅፋር የልጅ ልጅ አባ ጆቢር (የኦነግ አመራር አባል የአባ ቢያ አባት)፣ ከፋሽስቱ ወራሪ ጣሊያን ጋር በማበር፣ የዐማራ አንገት እየቆረጠ ለሚያመጣለት ኦሮሞ ሁሉ ፴ ጠገራ ብር እንደሚከፍል አዋጅ አስነግሮ፣ አያሌ ዐማሮችን ማስጨፍጨፉ ይታወቃል። ከአባ ጆቢር ይልቅ ፋሽስቱ ግራዚያኒ ሰብአዊነት ተሰምቶት ግድያውን ማስቆሙ ታሪካችን ያረጋግጣል።
ስምንተኛ፦ በ፲፱፻፹፪ ዓም በአሶሳ ይኖሩ በነበሩት ዐማሮች ላይ የሻዕቢያ እና የኦነግ ታጣቂዎች በጣምራ በመዝመት ከ500 በላይ የሚሆኑትን ሰብስበው ቤት ውስጥ በመዝጋት በእሳት አቃጥለው እንደጨረሱዋቸው ይታወቃል።
ዘጠነኛ፦ ከ፲፱፻፹፬ እስከ ፲፱፻፹፮ ዓም በነበሩት ፫ ዓመታት ውስጥ ብቻ በበደኖ፣ በወተር፣ በአርባ ጉጉ፣ በአሰቦት ገዳም በሌሎችም የምሥራቅ ኢትዮጵያ ክፍሎች ዐማሮች ዐማራ በመሆናቸው ብቻ በዘራቸው እየተለቀሙ ከነሕይዎታቸው ወደ ገደል ተወርውረዋል፤ ታርደዋል፣ ነፍሰጡር እናቶች ሆዳቸው በሳንጃ ተሰንጥቆ ሽል ተሰልቧል፤ ሰዎች ቆዳቸው እንደ ፍየል ሙክት ተገፍፎ ስልቻ ወጥቷል።
አሥረኛ፦ በ፲፱፻፺፫ ዓም ምሥራቅ ወለጋ ውስጥ ለዘመናት ይኖሩ የነበሩ ከ፳ ሺ በላይ ዐማሮች «አገራችሁ አይደለም፣ ውጡ» ተብለው፣ ቤት ንብረታቸውን ተነጥቀው ተባርረዋል። በዚህ ዐማራን የማፈናቀል ሂደት ውስጥ ይታየው መሥፍን የተባለውን ኅዳር ፳፰ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓም ከነከብቶቹ በእሳት አቃጥለው ገድለውታል። መልካሙ ውባለም የተባለውን ገድለው ምላሱን ቆርጠው ወስደዋል። አስረግደው ውቡ የተባለውን በጥይት ገድለው በሬሣው ላይ በአንገቱ፣ በወገቡና እና በእግሩ ላይ አንካሤ ቸክለውበታል። አባ በላይ የተባሉትን ማዬት የተሳናቸው አዛውንት ከገደሉ በኋላ «ዐማራ ዐማራ ነው» በማለት ሰልበዋቸዋል። የሁለት ዓመቱን ሕፃን ልጅ እናቱን ስለገደሉበት አባቱ አቶ አዲሱ እናት አልባ የሆነውን ልጁን ያለእናት ማደጉን ለመግለጽ ስሙን «ቀረብህ» ብሎታል። ። (ዝርዝር ታሪኩን ጦቢያ መጽሔት ቅጽ ፰ ቁጥር ፰ ፲፱፻፺፫ ዓም ዕትም ይመልከቱ)።
አሥራ አንደኛ፦ የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የጠለምት፣ የሰቲት እና የአርማጨሆ ዐማራ በጅምላ ተገድሎ ታስሮ እና ተፈናቅሎ፣ በአጽመ ርስቱ ላይ ትግሬ እንዲሠፍርበት ተደርጓል።
አሥራ ሁለተኛ፦ በምሥራቅ ኢትዮጵያ በጅጅጋ ከተማ ለዘመናት ይኖሩ የነበሩትን ዐማሮች «አገራችሁ አይደለም» ተብለው ኃብት ንብረታቸውን ተነጥቀው ተባርረዋል።
አሥራ ሦስተኛ፦ ከ፪ሺህ፬ ዓም ጀምሮ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጉራ ፈርዳ ወረዳ ይኖሩ የነበሩትን ከ፸፰ ሺህ በላይ ዐማሮች «አገራችሁ አይደለም» ተብለው በግፍ ኃብት ንብረታቸውን ተነጥቀው ተባርረዋል፤ በአሰቃቂ ሁኔታም ብዙዎች ተገድለዋል።
አሥራ አራተኛ፦ ባለፈው ዓመት በ፪ሺህ፭ ዓም በአሶሳ እና በመተከል (ጎጃም) ይኖሩ የነበሩትን ከ፶ ሺህ በላይ ዐማሮችን «አገራችሁ አይደለም፣ ውጡ» ተብለው ቤት ንብረታቸውን ተነጥቀው ተባርረዋል። በማባረሩ ሂደት ውስጥም አቶ አሥራደ መቅጫ የተባለውን ዐማራ አርደው፣ ሰልበው እና የፊቱን ቆዳ ገፍፈው አስከሬኑን ጫካ ውስጥ ጥለውታል። አቶ ተሰማ ስዩምን በጥይት ደብድበው ገድለዋል። ሌሎች ፲፪ ሰዎችን ሠርተው እንዳይኖሩ አድርገው፣ ከሞት መልስ ቀጥቅጠው ደብድበዋቸዋል። ወላድ ሴቶች በመንገድ ላይ እንዲወልዱ በመገደዳቸው የእንግዴ ልጃቸውን ውሻ እንዲበላው ተደርጓል። እትብት መቁረጫ አጥተው በባልጩት እንዲቆርጡ ተገድደዋል።
አሥራ አምሥተኛ፦ ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ዐማራውን ከምድረ ኢትዮጵያ ለማጥፋት በኤች አይ ቪ ቫይረስ የተበከለ ደም በመርፌ እየወጋ በሽታውን እያሰራጨ እንደሆነ የአደባባይ ሚስጢር ነው። በዚህም አጥፊ ጉዞው ከ፲፱፻፹፱ እስከ ፲፱፻፺፱ ዓም ድረስ በነበሩት በ፲ ዓመታት ጊዜ ውስጥ ብቻ የዐማራው ቁጥር ከሌሎች ነገዶች በተለየ ሁኔታ በሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ እንዲቀንስ አድርጓል።
አሥራ ስድስተኛ፦ በተላላፊ በሽታ እና በወሊድ ቁጥጥር ሰበብ የዐማራውን ተወላጅ፣ ወንዱን የሚያኮላሽ፣ ሴቱን የሚያመክን መድኃኒት በመስጠት ከፍተኛ የሆነ የዘር ማጥፋት ወንጀል ይፈጸምበታል።
ከላይ ከተዘረዘሩት መካከል እኛ ባለንበት በ፳፩ኛው ክፍለ-ዘመን የተፈፀሙት እና የሚፈፀሙት በፍርድ ሂደት ዕምነት-ክህደት የሚጠየቅባቸው እንኳን አይደሉም። በጥቅሉ ሲታይ በዐማራው ነገድ ላይ በተከታታይ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ተፈጽሞበታል። እነዚህ ሁሉ፣ «ወደ ኋላ እንይ፣ ትውልዱን በቂም በቀል ስሜት ውስጥ ከትተን እስከ ዝንተ-ዓለሙ እንዳይገናኝ አድርገን ኢትዮጵያን እናፍርሳት» ብለን ካሰብንና ካመንን፣ ታላላቅ ሐውልቶች ማቆም ብቻ ሣይሆን ብዙ የደም መፋሰስ የሚያስከትሉ እንደሆነ ማንም ኅሊና ያለው ሰው ይገነዘበዋል። ከዚህ አንፃር የጥፋት መልዕክተኛውን የተስፋዬ ገብረአብን የልብ ወለድ መጽሐፍ የቅዠት ተረት ተረት፣ በገሃዱ ዓለም የተፈጸመ አስመስሎ «የአኖሌ እጅ» ላይ የተቆረጠ ጡት አስቀምጦ ሐውልት ማቆም፣ አተራማሾቹ የፈለጉትን ኢትዮጵያን የመናድ ተልዕኮአቸውን እንዲወጡ ከማድረግ ያለፈ ለኦሮሞ ሕዝብ የሚሰጠው አንዳችም ቁሳዊም ሆነ ኅሊናዊ ፋይዳ የለም። በትርምሱ ተጠቃሚ የሚሆኑትም የአናሳዎቹ የሻዕቢያ እና የትግሬ-ወያኔ ቡድኖች እና ተከታዮቻቸው ብቻ ናቸው። ለ፳፫ ዓመታት በሥልጣን ኮርቻ ተፈናጥጠው ለመቆየት የቻሉትም፣ በእነዚህ ሁለት ታላላቅ ነገዶች መካከል ባሠራጩት የጠላትነት ፕሮፓጋንዳ፣ ሆድና ጀርባ ሆነው እንዲተያዩ በማድረጋቸው እንደሆነ ግልፅ ነው።
ኢትዮጵያዊነትን፣ ብሔራዊ አንድነትን እና የአገራችንን ኅልውና ማስጠበቅ የሚቻለው ለሥልጣን እና ማዕከላዊ አስተዳድርን ለመመሥረት ሲባል የተደረጉትን ግብግቦች እና ግጭቶች፣ አልፎ አልፎም ጦርነቶች ያስከተሉትን ጥፋት፣ የተወሰኑ ነገድ አባሎች ብቻ እንዳደረጉት በመቁጠር፣ አልፎ ተርፎም የዚያን ነገድ አባሎች በጅምላ ለመበቀል በመነሣት አይደለም። ውሾች በአጥንት ይጣላሉ፤ ጅብ ሲመጣባቸው ግን ጠባቸውን ትተው በጅቡ ላይ ያብራሉ። የእስከዛሬዎቹ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን እና እናቶቻችንም ሲያደርጉ የኖሩት ይህንኑ ነበር። ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ የአፍሪቃ መመኪያ እስከመሆን የዘለቀችውም አባቶቻችን «የዘመድ ጥል፣ የሥጋ ትል» ብለው በየግል የደረሰባቸውን በደል በሠፊዋ ኢትዮጵያ ኅልውና ለድርድር የማያቀርቡ በመሆናቸው ነበር።
በአገራችን ብሔራዊ አንድነት ግንባታ ወቅት «ተከሰተው ነበር» የሚባሉ ችግሮች ሁሉ፣ በአድራጊ ግለሰቦች እና በአደራረግ ሁኔታ እንዲሁም በቦታ እና በጊዜ ከመለያየት ውጪ፣ በየትኛውም አገር የተከሰቱና ሁሉም አገሮች ያለፉባቸው የኅብረተሰብ ዕድገት ውጤቶች ናቸው። በዚያን ጊዜ ሠፊ መሬትና የፈላጭ ቆራጭነት ሥልጣን ከመፈለግ አኳያ አንዱ ነገድ ሌላውን ፈጽሞ ለማጥፋት የቃጣበት ወቅት የለም። እንዲያውም የጦርነቶቹ ባህርይ፣ «የተገዛ፣ አልገዛም» ግብግብ መገለጫ ስለነበር፣ በተመሣሣይ የነገድ አባሎች መካከል የነበረው የእርስ በእርስ ግጭት የበዛ ነበር። በዚህ ረገድ በእኛ አገር ዋነኞቹ ተፋላሚዎች «ከዘውድ እንወለዳለን» በሚሉት የመሣፍንት ወገኖች መካከል ስለነበር፣ ጦርነቱ ከነገድ ወርዶ በወንድማማቾች መካከል የተካሄደ ነበር። ይህም በመሆኑ በአገራችን የግራው አመለካከት በትውልዱ መሐል እስከተዘራበት እስከ ፲፱፻፷ዎቹ ድረስ አንድም ነገድ ሌላውን ነገድ በጠላትነት ፈርጆት አያውቅም ነበር። የ«አኖሌ የጡት ቆረጣ» ታሪክም የዚሁ የግራ-ዘመሙ ትውልድ የፈጠራ ታሪክ ውጤት ነው። የግራው አመለካከት ለእኛ አገር ቀርቶ ለበቀለበትም አገር የማይጠቅም ሆኖ፣ ተወግዞ ከተወገደ ከ፳ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። ስለሆነም፣ ኢትዮጵያን የሚያጠፋ፣ ሕዝቡን ለመተሣሠብ እና ለአንድነት ሳይሆን ለቂምና ለቁርሾ የሚያነሣሣ ልብ ወለድ ድርሰትን በታሪክ ስም ማስቀመጥ፣ አልፎ ተርፎም ሐውልት መገንባት፣ ከጥቅሙ ይልቅ ዘለቄታዊ ጉዳቱ እንደሚያመዝን በስማቸው ለሚነገድባቸው የኦሮሞ ተወላጆች ግልፅ ሊሆንላቸው ይገባል። የኦሮሞ አባቶችም በስማቸው የሌላቸውን ጠላት የሚገዛላቸውን ይህን ሐውልት እንዲያወግዙ ይለመናሉ።
ይህ ካልሆነ ግን የዐማራ ተወላጅ ሁሉ እንዳለፉት ዘመናት «ለጋራ ጥቅም» እያለ «ሆድ ይፍጀው» ብሎ በዝምታ አይቀመጥም። እስከዛሬ ድረስ የዐማራው ወላጆች በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር አብሮ ለመኖር ሲባል ለልጆቻቸው ሲያስጠኑ የኖሩት፣ የታሪካችንን ደግ ደጉን ክፍል እንጂ፣ ክፉ ክፉውን አይደለም። ሆኖም ዐማራውን የሚያጥላሉ «የቡርቃ ዝምታ» ዓይነት ጽሑፎች እና የአኖሌ ሐውልትን ዓይነት ቋሚ ሥራዎችን ማስፋፋት፣ ለዘመናት ሣይገለፅ የኖረውን ዕውነተኛ የኦሮሞዎችን ማንነት ግልጥልጥ አድርጎ እንዲያስተምር ይገፋፋሉ። ስለዚህ የአኖሌ ሐውልት መቆም እንደ ሶባስቶፖል መድፍ ወደ ኋላ ተተኩሶ ተኳሹን የሚያጠፋ ከመሆን ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም፦ «ደባ ራሱን፣ ስለት ድጉሡን» ወይም በሌላ አገላለፅ «አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል፣ የሰው ፈላጊ የራሱን ያጣል» ነውና!
ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደግ!
ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

በቁም እስር ላይ ያሉት ብጹእ ኣቡነ ማቲያስ ከአሜሪካን መልስ በደህንነት ቢሮ ለ72 ሰአታት ታስረው ነበር::

December 29/2013

ኢትዮጵያ ውስጥ ኢትዮጵያዊ አሸባሪ የለም::" ብጹእ አቡነ ማትያስ


"ከኦሮሞ እና አማራ ጳጳሳት ጋር ትፈተፍታላችሁ::" አቶ ጸጋዬ በርሄ ..የአፋኝ ደህንነቶች ሹም

በጳጳሳቶች እና በፌዴራሉ ሚኒስትሮች መካከል በስብሰባ ላይ በተነሳው አለመግባባት እና የጳጳሶቹ ድምጽ በደል እና ግፍን በማስተጋባቱ እንዲሁም ለመጣው ችግር ሁሉ ተጠያቂው የኢሕኣዴግ መንግስት ነው:ማለታቸውን ተከትሎ እንዲሁም ጳጳሱ አሜሪካን ተጉዘው ከመጡ በኋላ የሚያሳዩትን የቁጥብነት ባሕሪ ተከትሎ እንዲሁም በቤተክህነት ውስጥ የሚወስዱትን አስተዳደራዊ እርምጃ ያልጣመው ኢሕኣዴግ በአቶ ጸጋዬ በርሄ የሚመራው የአፈና እና የቶርች ቡድን ብጹእ አቡነ ማትያስን ለ72 ሰአታት በደህንነት ቢሮ በቁጣ እና በስድብ በማስጠንቀቂያ አሰቃይተው እና አንገላተው ወደ መኖሪያቸው እንደመለሱዋቸው ከደህንነት ቢሮ ምንጮቻችን ገልጸዋል::ጻጻሱ ለ72 ሰአታት ከመኖሪያቸው ሲታጡ በጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ ካድሬ ቄሶች አቡኑ ለህክምና ውጪ አገር ሂደዋል የሚል ወሬ ሲያስወሩ ነበር::

ብጹ አቡነ ማትያስ በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ መሰረት ከአገሪቱ የመንግስት አካልት ጋር እንዲሁም ከጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ ካሉ የትግራይ ተወላጆች ጋር በቅርበት እንዲሰሩ የተነገራቸው ሲሆን በዙሪያቸው ያሉ የሲኖዶስ አባላትን ፊት እንዳይሰቷቸው እና አማራ እና ኦሮሞ ጳጳሳቶች እንቅስቃሴያቸው ሁሉ ከአቡነ መልከጻዲቅ እና ከተቃዋሚ ሃይላት መሆኑ አውቀው ጥንቃቄ እንዲወስዱ እንዲሁም አስተዳደራዊ ስራዎችን ለንብረዑድ ኤልያስ አብርሃ እንዲያስረክቡ ተነግሯቸዋል:: ከሳቸው ጋር በረዳትነት አቡነ ሳሙኤል እንዲሰሩ መመሪያ የተሰጣቸው መሆኑ ታውቋል::

ብጹእ አቡነ ማቲያስ በደህንነት ቢሮ የአቶ ጸጋዬ በርሄ ቡድን ማስፈራሪያ ሲሰጣቸው ፊታቸውን ቅጭም አድርገው በሃዘን እና በቁጭት ስሜት ያዳምጡ እንደነበር ታይተዋል:: መልስ ሲሰጡ የነበሩት እጅግ ዘግይተው በትካዜ እንደነበር ታውቋል::አሸባሪዎችን መዋጋት አለብዎ ሲባሉ በኢትዮጵያ ምድር ኢትዮጵያዊ አሸባሪ የለም ብለው የመለሱት አቡኑ አብዛኛው መልሶቻቸው "...እስኪ ካላችሁ ይሁን እግዛብሄር እንደፈቀደው...' የሚል እንደነበር የደህንነት ቢሮ ምንጮች ጠቁመውናል::

በዚህም መሰረት አቡነ ማትያስ የፖለቲካ ፍጆታ በሚያስፈልጋቸው መንፈሳዊ ስብሰባ ላይ አይገኙም:: በተገኙበትም ቦታ ደሞ ስለ ልማት ካልሆነ በቀር ስለ አስተዳደራዊ ጉዳይ እና ስለ ብሶት ቀስቃሽ ንግግር እንዳያደርጉ ተነግሯቸዋል:: በአሁኑ ወቅት ማንኛውም የአገር ውስጥ እንቅስቃሴያቸው በደህንነት አይን ስር ያለ ሲሆን የቁም እስር ላይ ናቸው::

  ሚኒሊክ ሳልሳዊ

Ethiopian woman found hanging in Lebanon (warning: graphic image)

December 29/203
EthiopianReview.com

(Al-Akhbar) – An Ethiopian woman was found hanging from an electrical cord outside her employer’s South Lebanon home in an apparent suicide, state news reported Saturday.

Ethiopian woman found hanging in Lebanon
The National News Agency identified the victim as Dimi Kash-Kalashou Kata. It published a disturbing image of the woman hanging by her neck in the southern town of Rmeich.

Police have launched an investigation into the incident, the report said, adding that they believed the woman hung herself as is common among maids in Lebanon, which hosts about 200,000 domestic workers.
Domestic workers in Lebanon and other Arab countries are employed under the heavily criticized sponsorship, or kafala system which denies the maid the right to terminate her contract or leave her employer.

Maids employed under this system are not covered by Lebanese labor laws, meaning they have no minimum wage, social security or other basic rights.

It is almost always the case that an employer holds the maid’s passport over fears she might run away. It is also common for an employer to lock the maid inside their home when they leave the house or travel.
In July a Bangladeshi worker was found hanging in her employer’s home in East Lebanon, and a month before that a pregnant Ethiopian maid committed suicide in Mount Lebanon.

Human Rights Watch documented an average death rate of one per week among domestic workers due to unnatural causes in 2008. Those cases included suicides and death by falling from buildings.

ጃዋርና ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ – ዓለማየሁ መሀመድ (3)

December 28/2013

አቧራው ጬሷል። ግለቱ ጨምሯል። ሙቀቱ አይሏል። የሳይበሩ ጦርነት ተጋግሏል። በሁሉም ወገኖች ትርፍና ኪሳራው ገና አልተሰላም። ከመነሻው ትርፋማ መሆኑ የተረጋገጠለት ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ዘና ፡ ከወንበሩ ለጠጥ ብሎ በትዝብት ፈገግታ ሁለቱን ወገኖች ይመለከታል። ቢቻለው ካራ አቀብሎ የፌስ ቡኩ ጦርነት ደም ወደ ሚያፋስስ ዕልቂት ቢቀየርለት ምንኛ በመረጠ?!

በእርግጥ እያሰበበት ነው። የመረጃ ምንጮቼ ሹክ እንዳሉኝ ከሆነ የህወሀት ስሌት እስከ እልቂቱ የሚሻገር ነው። ሰሞንኛዋ ግርግርም አራት ኪሎ ቤተመንግስ ተቀምራ፡ ዋሽንግተን ዲሲ በህወሀት ኤምባሲ ተከሽና በእነ ጃዋር መሀመድ ታውጃ፡ ሺዎች በደመነፍስና በስሜታዊነት የተቀላቀሉት ስለመሆኑ ከበቂም በላይ መረጃው አለኝ።




ለዛሬ መረጃዎቹን ላካፍላችሁ። ማስረጃዎቹን እየጠበኩኝ ነው። የድምጽና የፎቶግራፍ ማስረጃዎቹ ከእጄ እንደገቡ ጀባ እንደምላችሁ ከወዲሁ ቃል እገባለሁ። በእርግጥ አንድ ላይ ላወጣቸው ነበር እቅዴ። ሆኖም የጬሰው አቧራን እየቃሙ ላሉት ወገኖች በተወሰነ ደረጃ ሰከን እንዲሉ፡ ሰማይ ምድሩን የበጠበጠው ንትርክ የኦሮሞ ህዝብን ብሶት ለመግለጽ ታስቦ ሳይሆን በህወሀት መንደር ተዘጋጅቶ የቀረበ መርዛማ አጀንዳ መሆኑን በቶሎ እንዲያውቁት በሚል መረጃዎቹን ብቻ ላፈነዳቸው ፈለኩ። ሁለት ናቸው

መረጃ አንድ

ፋይሳል አልዬ ዓመታት የዘለቀ የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ አባል ነው። እሳት የላሰ ካድሬ ይሉታል። ለህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ሰዎች ምቾት የሚሰጣቸው፡ በኦሮሚያ ክልል ወጣቱ ለህወሀትቀጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ የቤት ስራቸውን በሚገባ የሚሰራላቸው በመሆኑ ፋይሳል በህወሀት መንደር ስሙ ወፍራም ነው። ወጣት ነው። ምላሱ ጤፍ ይቆላል የሚባልለት ዓይነት ነገር።

ጃዋርን ለመመልመል ጊዜ አልወሰደበትም። ጎረምሳው ጃዋር ከአከባቢው የነቃ፡ ነገር በቶሎ የሚገባው ስለነበረ የፋይሳል ቀልብ ውስጥ የገባው በጠዋቱ ነው። በእድሜም እኩያሞች የሚባሉ ናቸው። እናም ጎረምሳው ጃዋር፡ ሰተት ብሎ ኦህዴድን ተቀላቀለ። ኦህዴድ የበኩር ልጆቿን መልምላ ከጨረሰች በኋላ ለተለያዩ ተልዕኮዎች ማሰማራት ጀመረች። ጃዋር በአዲስ አበባ ቆይታው ውሎው ዶሮ ማነቂያ አከባቢ ካሉ ጫት ቤቶች ነበር። ጃዋርና ምልምል የኦህዴድ ካድሬዎች ብዙውን ጊዜ የስለላ ስራዎችን የሚያከናውኑት በዶሮ ማነቂያ አከባቢ በተሰገሰጉ ጫት ቤቶች ነበር። ጫቱን እያመነዥጉ ወሬ ሲለቃቅሙ መዋል የእነ ጃዋር መደበኛ ስራቸው ነበር።

በዚህን ጊዜ ወጣቱ ፋይሰል ወደ ዋሽንግተን ዲሲ የህወሀት ኤምባሲ ይዛወራል። ምሳዩን፡ እኩያውን፡ በግብርም በምግባርም የሚመስለውን ወዳጁን ጃዋርን ተስፋ ሰጥቶት ወደ ዲሲ ይበራል። ጃዋር እዚያው ጨፌ ኦሮሚያ ውስጥ ድርጅታዊ ተልዕኮዎችን እየተወጣ እያለ በመሃል ከወዳጁ ፋይሳል ጥሪ ይደርሰዋል። በትምህርት እድል ሰበብ ጃዋር ወደ አሜሪካ የሚመጣበት አጋጣሚ ይፈጠርለታል።

ለጃዋር የምስራች የነበረው ዜና እንደመጣች በኦህዴድ አማካኝነት ህወሀት ተልዕኮ ማዘጋጀት ጀመረ። የዲያስፖራውን ፖለቲካ ለመበጥበጥ፡ ጊዜ እየጠበቀ እንዲያተራምሰው የሚያስችል የቤት ስራ ተዘጋጀና በዋሽንግተኑ ፋይሳል መሪነት እንዲከናወን ህወሀት አዘዘ። ጃዋርን ይሄን ተልእኮ ሰንቆ ዋሽንግተን ዲስ ከተፍ አለ።

የህወሀት ኤምባሲ የጃዋር መሸሸጊያ ሆነ። ጠዋት ነግቶ ኤምባሲ ይገባል። ከፋይሳል ጋር ሲሰራ ይውልና ማታ ጸሀይ ስትጠልቅ ኤምባሲው አከባቢ ወደተከራዩለት መኖሪያው ይሄዳል። ለአንድ ዓመት ያህል በዚህ ሁኔታ ዘለቀ። አሁን ከወያኔ መንደር የተሰናበተው ብርሃኑ ዳምጤ አባመላ የቅርብ ግንኙነት ነበረው። ሻይ ቡና የሚባባሉት እነዚሁ የኤምባሲው ሰራተኞችና ባለልዩ ተልእኮ አስፈጻሚዎች ነበሩ።

ሁኔታዎች በዚሁ እየቀጠሉ እያለ ጃዋር ከሚኒሶታ የኦሮሞ አንድ ማህበር ጥሪ ይደረግለታል። ወንበር እያሞቁ መዋልና ማደር የሰለቸው ጃዋር ለሚኒሶታው ጥሪ ምላሽ ለመስጠት አልዘገየም። ጓዙን ጠቅልሎ ሚኒሶታ ገባ። ጽንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ተቀባበሉት። ህወሀት ያዘጋጀው፡ ኦህዴድ ያስጠናው ተልኦኮ ለጊዜው አደጋ ገጠመው። የኦነግን የ40 ዓመት ሙዚቃ በቅርበት ለመኮምኮም ዕድል ያገኘው ጃዋር በሚኒሶታ ውርስ ነበር የጠበቀው። ያረጀውን፡ የሻገተውን የኦነግን ፍልስፍና አፈሩን አራግፎ ለማንሳት ቃል የገባው ጃዋር በዋና ጊዜው ትምህርት እየተከታተለ፡ በትርፉ ደግሞ የኦነግን ዜማ እያቀነቀነ የሚኒሶታውን ህይወት ጀመረው።

እነፋይሳል የጃዋር መክዳት ብዙም ያሳሰባቸው አይመስሉም። የተሸከመውን አደራ ሳይወጣ፡ ኮትኩታ ያሳደገችውን፡ ለወግ ማዕረግ ያበቃችውን ኦህዴድን(ህወሀት) ለጊዜው ተለይቷታል።

ፋይሳል በመሃሉ ወደ አዲስ አበባ ይመለሳል። በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ትልቅ የሃላፊነት ቦታ ተሰጥቶት መስራት ይጀምራል። ጃዋር ደግሞ በዲያስፖራው ውስጥ እንዴት መሰስ ብሎ መግባት እንዳለበት ሂሳብ ማስላት ጀመረ። በልቡ ውስጥ የኦነግን ነፍስ ተሸክሞ ወደ ተቀሩት ኢትዮጵያውያን መጠጋት ያዘ። እንደቪኦኤ፡ ዶቸቬሌ፡ ኢሳት የመሳሰሉ ሚዲያዎች ላይ ቀርቦ ሲናገር በእርግጥ እኔን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጃዋር አልጎረበጣቸውም ነበር።

ጃዋር እዚህም እዚያም ይናገራል። ይጽፋል። ህወሀትን ያወግዛል። ኦህዴድን ይረግማል። በቃ! እውነተኛ ተቃዋሚ የሚል ታርጋ ተለጠፈለት። ወጣቱ የፖለቲካ ምሁር እየተባለ ይጠራም ጀመር።

ነገሮች ጃዋር ባሰባቸው መልኩ እየሄዱ ናቸው። እናት ድርጅቱን ኦህዴድን ለጊዜው ከድቷል። በልቡ የቀበረው የኦነግ ፍልስፍናም እዚያው ተዳፍኖ ይቀመጣል። ቀን ሲመጣ ሁለቱ ተስማምተው ይወጣሉ። የጃዋር ህልም እናት ድርጅቱን ኦህዴድንና የነፍሱ ማረፊያ የሆነውን ኦነግን ማጋባት ነው። ለዚህ ደግሞ ስሙን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ መተከል አለበት። እያደረገው ዘለቀ።

እነፋይሳል ጸጥ ብለዋል። ጃዋር መጨረሻው ከየት እንደሆነ ያውቁታል። አስረዝመው አሰሩት እንጂ ፈተው አለቀቁትም። ጃዋርም ይህቺን ልቅም አድርጎ ያውቃታል። አንድ ቀን ወደ እናት ድርጅቱ እንደሚመለስ ያም ቀን እየቀረበ እንደመጣ ተረድቷል።

ፋይሳል በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ ሌላ ከፍተኛ ሃላፊነት ተሰጠው። የዲያስፖራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር። ጃዋር አልጀዚራ ላይ ቀርቦ ኦሮሞ ፈርስት ብሎ አውጇል። ከዚያም በፊት በሚኒሶታ አንድ መድረክ ላይ የሜንጫ አብዮት ቀስቅሷል። ከኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ተለይቶ ወደ ጽንፈኛው የኦሮሞ ጎራ ጠቅልሎ ገብቷል። አቧራው መጬስ ጀምሯል።

ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ፈተና ውስጥ ገብቷል። ከሀገር ቤትና ከባህር ማዶ የለውጥ ነፋስ እየነፈሰ ነው። ዲያስፖራው ወያኔን በየመድረኩ ማሳፈር፡ ማባረር ጀምሯል። የህወሀት ወንበር እየተነቃነቀ ነው። ዲያስፖራው የማይገፋ ተራራ ሆኗል። እነፋይሳል አሁን መነቃነቅ አለባቸው። ጃዋር የሚባል በዲያስፖራው ላይ የዘመተ ሃይል ተነስቷል። ፋይሳል ስልኩ አነሳ። ኢሜይሉን ከፈተ:: ….ጃዋር::

መረጃ ሁለት

በኒውዮርክ የሚገኘው በመንግስታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ ተልእኮ ጽህፈት ቤት ብዙ ሰራተኛ የለውም። አምባሳደሩ ዶክተር ተቀዳ ዓለሙ ለይስሙላ ይቀመጡ እንጂ እውነተኛ ስልጣኑ ያለው በሁለት ሰዎች እጅ ነው። ኮነሬል ገብሬ ገብረጻዲቅ የወታደራዊ አታሼውና የጽህፈት ቤቱ አንደኛ ጸሀፊ አቶ ኪዳነማርያም ግደይ የህወሀት ልዩ ተልእኮ አስፈጻሚ ናቸው። ዶክተር ተቀዳ ፕሮቶኮል ጠብቀው በየስብሰባው ይገኛሉ። እነኮነሬል ገብሬና ኪዳነማርያም ዋሽንግተን ዲሲ ካለው ኤምባሲ ጋር በመሆን የስለላና ሌሎች ድርጅታዊ ስራዎችን ያከናውናሉ።
ተቃዋሚዎችን በመሰለል፡ በገንዘብ እየሸነገሉ በማስከዳት፡ የተለያዩ ተለጣፊ ድርጅቶችን በማቋቋም የዲያስፖራውን እንቅስቃሴ የማዳከም ሃላፊነቱ እነዚህ ሁለቱ የህወሀት ሰዎች ላይ ወድቋል።

ጊዜው ለህወሀት ከባድ ሆኗል። ተቃውሞው በየቦታ ጠንከር ብሎ ተነስቷል። ህወሀት አደጋ ውስጥ ነው። እነኮነሬል ገብሬ የቤት ስራ ተሰጥቷቸዋል። ዲያስፖራው መበጠበጥ አለበት። ዘረኝነት ክፉ ነው። የኦሮሞ ዲያስፖራ ማህበረሰብ ራሱን ተጠቂ አድርጎ የሚኖር በተለይ በአማራው ላይ ቂም ቋጥሮ የተቀመጠ ነው የሚል ድምዳሜ ህወሀት ዘንድ አለ። እናም ይሄን መቀስቀስ አንዱ ህወሀት እፎይታ የሚያገኝበት መንገድ ነው። ለዚህ ደግሞ ትክክለኛው ሰው ጃዋር ነው። ኮነሬል ገብሬ ስልካቸውን አነሱ። ጃዋር የሚኖረው እዚያው እሳቸው ካሉበት ከተማ ነው ኒውዮርክ።
ፋይሰል ከአዲስ አበባ ይደውላል። ኮነሬል ገብሬ ከኒውዮርክ ስልኩን እየመቱ ናቸው። ሁለቱም ከአንድ ቦታ ነው የሚደውሉት። ጃዋር ዘንድ።
ጃዋር አሁን ስራውን ጀመረ። የእናት ድርጅቱን ውለታ ለመመለስ ተዘጋጀ። አቧራውን አጬሰው። እንደተፈለገው እንደታቀደው የኦሮሞ ማህበረሰብ ብድግ አለ። ጽንፈኛው ሆ ብሎ ተነሳ። ህወሀት ለጊዜው እፎይ ያለ መስሏል።

በመረጃ ደረጃ ያገኘሁት እንደሚያመለክተው ጃዋርን ጨምሮ የተወሰኑ የኦነግ መሪዎች አዲስ አበባ ይገባሉ። ለዚህም አባዱላ ገመዳ እና ግርማ ብሩ ስራውን እየሰሩት ነው። ምናልባትም በቅርቡ ጃዋርና የኦነግ መሪዎቹ ኦህዴድን ይዘው ብቅ ሊሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል።
እንግዲህ ይህ መረጃ በማስረጃ ተደግፎ ይመጣል። እነጃዋር ከህወሀት ጋር የፈጸሙት ጋብቻ ኢትዮጵያን በመበጥበጥ ላይ ያተኮረ ነው። ጊዜውን ልብ በሉ። ህወሀት ተዳክሟል። እያጣጣረ ያለውን ስርዓት ወደ መቃብሩ ሸኝቶ በእኩልነት ላይ የተመሰረተች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነው እነጃዋር የዘረኝነት ካርድ አንስተው ህወሀትን ለማዳን ወገባቸውን ታጥቀው በማህበራዊ መድረኮች ላይ የዘመቱት።

ዘረኝነት ልብንም አይንንም ያውራል። የሰከነ ውይይት ለማድረግ የሚፈቅድ ትዕግስት አይሰጥም። በእርግጥ የተነሳው አቧራ ይጠፋል። ሰማዩም ይጠራል። እነጃዋር ለህወሀት ከቆሙለት ዓላማ ጋር በታሪክ ጥቁር ስም ታቅፈው ይኖሩዋታል። መልካም ንትርክ!!

በእርግጥ እያሰበበት ነው። የመረጃ ምንጮቼ ሹክ እንዳሉኝ ከሆነ የህወሀት ስሌት እስከ እልቂቱ የሚሻገር ነው። ሰሞንኛዋ ግርግርም አራት ኪሎ ቤተመንግስ ተቀምራ፡ ዋሽንግተን ዲሲ በህወሀት ኤምባሲ ተከሽና በእነ ጃዋር መሀመድ ታውጃ፡ ሺዎች በደመነፍስና በስሜታዊነት የተቀላቀሉት ስለመሆኑ ከበቂም በላይ መረጃው አለኝ።
ዘ -ሐበሻ

ይድረስለኢትዮጵያመለዮለባሾች (ለፖሊስሠራዊት፤ለፌድራልፖሊስና ለጦርኃይልሠራዊትዓባላት)

December 28/2013


በገብረክርስቶስ ዓባይ ታህሣሥ 2006 ዓ/ም

ከታሪክ እንድምንገነዘበው የአንድ ሀገር ደኅንነት ወይም ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው፤ ዳር ድንበሯ ተከብሮ ፤በውስጧ የሚኖሩ ሕዝቦች በሰላም ላይ የተመሠረተ፤  ቀልጣፋ ዕድገትና ብልጽግና ያለምንም ሥጋትና መሸማቀቅ ማከናወን ሲችሉ፤ የዜጎች ኅልውና ተጠብቆ፤ የሕግ የበላይነት ነግሦ፤ ያለማንም ጣልቃገብነትና ያልተንዛዛ የፍትሕ ሥርዓት ማስፈን ሲቻል ነው።

ለዚህ ዓይነተኛና ቁልፍ የሆነ ተግባር የመለዮ ለባሹ ተሳትፎ ጉልህ አስተዋጽዖ ይኖረዋል። ይሁን እንጅ መለዮ ለባሹ የተማረም ይሁን ያልተማረ የንቃተ ኅሊናው ደረጃ ግን ለጥሩም ሆነ ለመጥፎ ውጤት ወሳኝ ሚና መጫወት እንዲችል ያደርገዋል።

በመሠረቱ መለዮ ለባሹ የማን ወገን ነው? ብለን ብንጠይቅ መልሱ እጅግ በማያሻማ ሁኔታ የሕዝብ የሚል መልስ እናገኛለን። ምክንያቱም በቅድሚያ መታወቅ ያለበት ሁሉም መለዮ ለባሽ  የገባው ቃል ኪዳን ለአገሩና ለወገኑ  ደኅንነት በሙሉ ኃይሉና ዕውቀቱ መሥራት ሲሆን አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ  ደግሞ እስከ ሞት የሚደርስ የሕይወት መስዋዕትነት እከፍላለሁ በማለት ነው።

በሁለተኛ ደረጃ ቅጥሩ በውክልና ማለትም በወቅቱ በሥልጣን ላይ ባሉ ኃላፊዎች ቢፈጸምም ወርኃዊ ደመወዝና ተጓዳኝ ጥቅማጥቅሞችን የሚከፍለው ወገኑ (ሕዝቡ) መሆኑን መለዮ ለባሹ ጠንቅቆ መረዳት ይገባዋል።

በሦስተኛ ደረጃ መጠቀስ ያለበት ሹመኛ ጥፋት ሠርቶ ይሻራል፤ ዕድገት አግኝቶ ይዛወራል፤ በሞትም ሊለይ ይችላል ወይም ደግሞ በመንግስት ለውጥ የተነሣ የኃላፊነት ቦታውን ሊያጣ ይችላል። ሕዝብ ግን ትውልዱን እያደሰ እንደሚቀጥል እንገነዘባለን።

ስለሆነም መለዮ ለባሹ ምንጊዜም ከሕዝብ አብራክ የተገኘ እንደመሆኑ መጠን የሕዝብ አካል ነውና ለሕዝብ ጥቅምና ደኅንነት ጥብቅና የመቆም ግዴታ አለበት። ሕዝብ በተለያዬ ምክንያት ጉዳት ሊደርስበት ይችላል። ያንንም ተከትሎ ሕገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት ትኩረት ለማግኘት ሲል ሰብሰብ ብሎ ጥያቄዎቹንና አቤቱታዎቹን በሰላማዊ ሰልፍ በኅብረት ሆኖ ለመንግሥት እንዲያቀርብ የሚያስገድድ ሁኔታ ይገጥመው ይሆናል። ነገር ግን ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው ግለሰቦች(ኃላፊዎች) የሕዝቡን ጥያቄ አዳምጠው መፍትሔ መፈለግ ሲገባቸው  በተለያዬ ስንካላ ምክንያት የሕዝቡን ጥያቄና ድምፅ ለማፈን፤ አልፎ ተርፎም በድንገት ተነስተው መለዮ ለባሹን በወገኑ ላይ አስከፊና አጸያፊ እርምጃ እንዲወስድ መመሪያ ሊያስተላልፉ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ መለዮ ለባሹ የቃል ብቻ ሳይሆን የጽሑፍ ማስረጃ መያዝ ይጠበቅበታል።

ያንንም ካደረገ በኋላ የደረሰውን ትዕዛዝና የሕዝቡን ጥያቄ አግባብነት ከሕገመንግሥቱ ጋር ማገናዘብ ይኖርበታል። ሕገ መንግሥቱ የሕዝቡን ጥያቄ አግባብነት የሚፈቅድ ከሆነ ጉዳዩ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ መንገድ ራሱን መለዮ ለባሹንም ጭምር የሚጠቅምና የሚያቅፍ ስለሚሆን ሰላማዊ ሰልፉ በሥርዓት እንዲመራና እንዲጠናቀቅ ድጋፍ መስጠት ይኖርበታል እንጅ ያንን የሚያደናቀፍ እርምጃ መውሰድ የለበትም።
ለምሳሌም ያህል በቅርቡ የተፈጸመውን እንጥቀስ፡ አገራችን ኢትዮጵያ በሦስት ሺህ ዘመን ታሪኳ እንዳሁኑ መንግሥት ጊዜ እጅግ ተዋርዳና ተደፍራ አታውቅም።

የሳዑዲ አረብያ ሕዝቦች ቀደም ሲል ከ604-607 ዓ/ም የመጀመሪያዎቹ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ከነብዩ መሐመድ በተነገራቸው መመሪያ መሠረት ወደ አገራችን ኢትዮጵያ ተሰደው በመምጣት በሰላም የመኖራቸውን ሁኔታ ታሪክ መዝግቦት ይገኛል። የሳዑዲ ሕዝቦች እጅግ በጣም ድሀዎች ነበሩ። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ተሰደው በአገራችን ይኖሩ ነበር። በተለይ በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እስከ 1967 ዓ/ም ድረስ አዲስ አበባን ጨምሮ  በተለያዩ የኢትዮጵያ ጥቃቅን ከተሞች ሳይቀር የንግድ ሡቅና ሻይ ቤት ከፍተው፤እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ እየሠሩ በሰላም ሲኖሩ ቆይተው እንደ ዕድል ሆኖ በአገራቸው በሳዑዲ አረብያ የነዳጅ ዘይት በገፍ መውጣት ሲጀምርና፤ በአንድ ተራራ የወርቅ ማዕድን ክምችት መገኘትን ተከትሎ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል። በዚህ የኢትዮጵያ ቆይታቸው ጊዜ የደረሰባቸው ወከባም ሆነ እንግልት አልነበረም።

መቼም ዓለም ተለዋዋጭና ተገለባባጭ ናትና ሁኔታው ተቀይሮ፤ አሁን ባለው ዘረኛ የወያኔ መንግሥት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፤ ወንዱ ለአሽከርነት፤ ሴቷ ለግርድና ወደ ሳዑዲ አረብያ ተሰደዱ። የኢትዮጵያ መንግሥትም በእነዚህ ወገኖቻችን አማካኝነት ወደ አገራችን የሚገባው የውጭ ምንዛሬ ስለጣመው በረጅሙ ታሪካችን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ፤ እኛን ብቻ ሳይሆን ዓለምን ባነጋገረ መልኩ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፤ ለዘመናዊ ባርነት ከሳዑዲ መንግሥት ጋር ስምምነት ተፈራርሞ በቀን 1500 በወር 45000 ወገኖቹን በይፋ ሲልክ መቆየቱ ይታወቃል።

ሆኖም መንግሥት ለውጭ ምንዛሬ ማግኛ ብሎ የሸጣቸውን ወገኖች የሰብአዊ መብታቸውንና ደኅንነታቸውን ተከታትሎ ለማስከበር ጥረት ለማድረግ ባለመሞከሩ በዘመናችን ሊታሰብ የማይችል እጅግ በጣም የሚዘገንንና ስሜትን የሚሰቀጥጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል። ሌላው ቀርቶ ዓለም አቀፍ የሆነው የሰብአዊ መብታቸው አልተከበረላቸውም።

ከዚህም የተነሳ በሳዑዲ አረብያ ያሉ ኢትዮጵያውያን የድረሱልን ድምፅ ሲያሰሙ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የወያኔው መንግሥት ዓይኔን ግምባር ያድርገው፤ የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ ብሎ ጸጥ አለ። በዚህ ጊዜ ለወገን ደራሽ ወገን ነውና የወቅቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዓይንና ጆሮ በሆነው የኢሳት ሳተላይት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ዜናው ተላለፈ።

ወዲያውኑ፤ በዚሁ ለመንግሥትነት ብቃት በሌለው ዘረኛ የወያኔ አስተዳደር፤ በተለያየ ምክንያት እየተገፉ በዓለም ዙሪያ ተበትነው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፤ የወገኖቻቸውን እሮሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረስብ ማለትም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፤ ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ማኅበር፤ የስደተኞች ድርጅትና የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች እንዲያውቁት በሰላማዊ ሠልፍ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ በቅብብሎሽ ተስታጋባ።

በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፤ የሳዑዲ ዓረብያ መንግሥት በስደትኞች ወገኖቻችን እያደረሰባቸው ያለውን መከራና ሥቃይ በዩ ቲዩብ፤ በምስል በታገዘ የድረ ገጽ ዘገባዎችና በተዕይንተ ሕዝብ በመላው ዓለም አካሂደዋል። ጥቂቶችን ለመጥቀስ በአሜሪካ በብዙ እስቴቶች፤ በካናዳም እንዲሁ፤ በእንግሊዝ ለንድን፤ ከአውሮፓ በስዊድን ስቶክሆልም፤ በኖርዌይ ኦስሎ፤ በፊንላንድ፤ በአምስተርዳም፤ በኮፐንሀገን፤ በፓሪስ፤በጀርመን፤ በስዊዘርላንድ፤ በብራሰልስ፤ በሮም፤በእሥራኤል፤በደቡብ አፍሪካ፤ በአውስትራሊያ፤በደቡብ ኮሪያ፤በቶክዮ ጃፓን ባጭሩ ኢትዮጵያውያን በተሰደዱበት የዓለማችን ክፍል በሙሉ ሰላማዊ ሠልፍ ተካሄዷል።

በአገር ውስጥም በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራው ሰላማዊ ሠልፍ ቢሞከርም በመንግሥት ታጣቂዎች ድብደባና ወከባ እንዲበተን ተደርጓል። እዚህ ላይ የመንግሥት ታጣቂዎች የተበሉት እነማን ናቸው?
ከልዩ ዓለም የመጡ? ወይስ ከብረትና ከመሳሰሉት የተገጣጠሙ፤ በራሳቸው አእምሮ የሌላቸውና ሰው ሠራሽ አእምሮ (artificial intelligence)የተገጠመላቸው ሮቦቶች? ይህንን መመለስ ያለባቸው፤ በወቅቱ ግዳጅ ተሰጥቶአቸው ትዕዛዛቸውን ተቀብለው እንደወረደ የተገበሩት መሆን ይገባቸዋል።

በመሠረቱ አንድ የመንግሥት ባለሥልጣን ይህንን መሰል ትዕዛዝ ሲያስተላልፍ ትዕዛዝ ተቀባዩን ክፍል እንዴት ቢንቀው እንደሆን በትክክል መግለጽ ይከብዳል። ምክንያቱም ጉዳዩ የሕዝባችንን ክብርና የአገራችንን ሉዓላዊነት የሚመለከት እንደመሆኑ መጠን ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተውንና የሁኔታው ተካፋይ በመሆን ጥብቅና መቆም የሚገባውን አካል ተቃዋሚ እንዲሆን ለማድረግ መሞከር እጅግ በጣም ከባድ ነውና።

አንደኛ በስደት ላይ ሆነው ሥቃይና መከራ እየተቀበሉ ያሉት ወገኖቹ፤ በሁለተኛ ደረጃ በወገኖቻቸው ላይ እየደረሰ ያለው ይህ አስከፊ መከራና ሰቆቃ እንዲቆምላቸው በሠላማዊ ሠልፍ የሚገኙትም እህቶቹና ወንድሞቹ ሆነው እያለ፤ እርሱም እብሮ መሳተፍ ሲገባው፤ ሂዱና ሠላማዊ ሰልፉን አስቁሙ ተብሎ ሲታዘዝ አሜን ብሎ ሄዶ ለራሱ ክብር ጭምር የተሰለፉ ወገኖቹን በዱላ የሚቀጠቅጥ፤ ይሄ ከሰባዊነት በእጅጉ የወረደ ሮቦት አልያም ደግሞ ውሻ ነው።

በመጀመሪያ ደረጃ ለዚህ ተግባር ለመታዘዝ መታሰቡ ከፍተኛ ንቀት ሲሆን ከዚህ የበለጠ ውርደት የለም። በሁለተኛ ደረጃ በራስህ ላይ ዝመት ሲባል እሺ ብሎ የሚቀበል ይሄ በቁሙ የሞተ ጎፍላ፤ አልያም ሰሎግ ውሻ ነው። ወያኔዎች ከናዚ ዓለም አቀፍ ወንጀለኛ መንግሥት የቀዱትን ወንድምህን ግደል ብትባል እንኳ  ትዕዛዝክን ከፈጸምክ በኋላለምን ብለህ ጠይቅ በማለት መለዮ ለባሹን እንደሚያሠለጥኑ ይታወቃል፡፡ ሙያ በልብ ነው እንዲሉ በሥልጠናው ወቅት ዝም ቢባልም በተግባር ጊዜ ግን ማን በቅድሚያ እርምጃ እንደሚወሰድበት ግልጽ ነው። እንደኔ ያን መሰል ትዕዛዝ በንቀት ያዘዘኝን ባለሥልጣን በፍጹም አልምረውም፤ ደረቱን እሰነጥቀዋለሁ እንጂ ወንድሜን ግን በክፉ ዓይን እንኳ አላየውም። መከጀሉ ራሡ ትልቅ ውርደት ነው። ከዚህ የበለጠ ሞት ከየት ይመጣል? ተዋርዶና ተንቆ ከመሞት  ግን በክብር መሞት ሺህ ጊዜ እንደሚበልጥ ማስተዋል ያስፈልጋል።

ይኼ ምን ይላል የጎበዝ ገራም፤
ሲያኩት ይቆማል እንደ ጎፍላ ላም።
የሚሉት አበው እንዲህ ያለውን ነፈዝ ነው።   እንዲህ ያለው መለዮ ለባሽ ሚስትህን ለዛሬ አውሰኝ ቢለው አለቃው እሺ ብሎ ሌላ ሰው ሳይቀድመው ባለቤቱን ወስዶ የሚያስረክብ ነው። ወያኔ የሕዝብን አእምሮ እንዴት እንደሚጫወትበት ከዚህ መረዳት ይቻላል። ራሱ ያወጣውን ሕግ እንኳ የማያከብር አምባ ገነን ሥርዓት ነው።

እንደሠይጣን ከፋፍሎ ካልሆነ አስማምቶና አፋቅሮ ማስተዳደር አይሆንለትም። የአገርን ሉዓላዊነት ማዋረድና ሰባዊ ክብርን ማርከስ ያስደስተዋል።
ለመሆኑ እንዲህ ያለው መለዮ ለባሽ የአገርን  ዳር ድንበር ያስከብራል ወይ? ብለን ብንጠይቅ መልሱ በፍጹም አይታሰብም ነው። ለነገሩ ይህ አባባል እውነት ለመሆኑ እሩቅ አያስኬድም፤ መልሱ አጭርና ግልጽ ነው። በጀግኖች አባቶቻችን ደም ለዘመናት ታፍራና ተከብራ የቆየችው ሀገራችን በዘረኛው የወያኔ  የአስተዳደር ዘመን ጊዜ በአሁኑ ሰዓት  በምዕራብ ጎንደር፤ ጎጃም፤ ወለጋና ኢሉባቦር ድንበር ከአንድ ሺህ ኪሎሜትር በላይ ለም መሬት፤ ኃላፊነትን ባላስጠበቀ መልኩና ሠፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ  በተለይም ድንበሩን በግልጽ የሚያውቁት የአካባቢው ነዋሪዎች ሳይመክሩበት፤ በጓዳ በኩል ለሱዳን ለመስጠት ላይ ታች ሲባል እያየና እየሰማ ዝም ብሎ የሚመለከተውን መለዮ ለባሽ፤ ለማን እንደቆመ እንኳ የማያውቅ፤ ከእንስሳ በታች አድርገው ቆጥረውታል። ይሄም ሌላው ሞት ነው።

በግልጽና በስውር በሕዝብ ላይ ሲፈጽሙት በቆዩት ሠይጣናዊ ተንኮል የተነሳ በደም የተበከለ እጃቸውን ሳያጸዱ፤ ለንስሐ ሞት እንኳ ሳይበቁ እስከ ሐጢያታቸው በሰማያዊ ፍርድ በድንገት የተቀሠፉት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (ለመሆኑ የተቀበሩት የት ነው?ቅድስት ሥላሴ እንዳልሆነ ሹክሹክታዎች በሠፊው ይወራሉ ቀብርማ ዓየን እኮ! በደቡብ አፍሪካ የተከናወነውን የሰላም አባት የሆነውን የኔልሰን ማንዴላን በግልጽና በይፋ የተተገበረውን፤ እንዲያው ነገርን ነገር ያነሳዋል ነው እንጂ የመለስ ቀብር የኢትዮጵያ ሕዝብ አጀንዳ ሳይሆን የወያኔ አጀንዳ ነው ለዚህም ነው ከእውነት የራቀ ድራማ የተሠራብን) የሚጠሉትን ሕዝብ ቁጥር ለመቀነስ በክትባት ስም  እንዳይራቡ የሚያደረግ ማምከኛ መርፌ  እስከ ማስወጋት እርምጃ መውሰዳቸው በገሐድ እየወጣ ነው፤ በተባባሪነትና በአስፈጻሚነት የተገበሩት ደግሞ አሁን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ቦታ መሆናቸው ይታወቃል።

እኒሁ እኩይ ሰው በሥልጣን ወዳድነታቸውና፤ ኢትዮጵያን ከመጥላታቸው የተነሣ ገና በትረ መንግሥቱን እንደጨበጡ የወሰዱትን እርምጃ ማጤን አስፈላጊ ይሆናል። ከሌላው ታጋይ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በመደራደርና በመመካከር ሕዝቡ ሳይለያይ ማስተዳደር ሲገባ፤ ለብዙ ሺህ ዓመታት በመልክአ ምድር አቀማመጥ ብቻ ሳይሆን በደምና በአጥንት ተዋህዶ በአንድ ዘውዳዊ አስተዳደር ጥላ ሥር የኖረውን የኤርትራና የኢትዮጵያ ወንድማማች ሕዝብን ጉዳይ ወደጎን ትተው ለሥልጣናቸው ብቻ በማድላት በቅድሚያ ያደረጉት ለአፍሪካ አንድነት ድርጅትና ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤርትራ ነፃ ሀገር ሆናለች፤ ለዚህም ኢትዮጵያ ዕውቅና ትሰጣለችና እንደ መንግሥትእንድትመዘገብ ድጋፋችንን እናረጋግጣለን” የሚል ደብዳቤ በመጻፍ ነበር ቀልባቸውን ለመሰብሰብና ሥልጣናቸውን ለማደላደል የሞከሩት።

እንዳጋጣሚ ሆኖ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ የነበሩት የኢትዮጵያ ዋነኛዋ ጠላት የሆነችው ሀገር ሰው ግብጻዊው ቡጥሮስ ቡጥሮስ ጋሊ ነበሩና ሐሳባቻው እውን ሆነላቸው። ለዚህም ተግባራዊነትና ፈጣን የሆነ ምላሽ እንዲገኝ ቡጥሮስ ቡጥሮስ ጋሊ ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ በተደረገበት ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተቃውሞ በማቅረባቸው ድብደባና ከእስር እስከ ግድያ እርምጃ ተወስዶባቸዋል። ይህንንም አሠቃቂ ድርጊት የፈጸሙት መለዮ ለበሾች ናቸው። በዚህም ወቅት ያገለገሉት ሕዝብን ሳይሆን፤ የገዛ ወንድሞቻቸውንና እህቶቻቸውን በመግደል የፈጸሙት ተግባር ከውሻነት ደረጃ ከፍ ሊያደርጋቸው አይችልም። መለዮ ለባሹ እንደዚህ ያልውን ደረቅ የጭፍጨፋ ተግባር የሚፈጽመው የሀገራችንን  ሉዓላዊነት ረግጦ፤ ድንብር ጥሶ በሚመጣ የውጭ ጠላት ላይ ያውም እስኪማረክ ድረስ ከተማረከ ግን ዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብቱ የተከበረ ነው፤ እንጂ በወገን ላይማ ከቶ የሚታሰብ እንኳ መሆን አልነበረበትም።

በሥልጣን ወንበር ያለው ዘራፊ መንግሥት በሕዝቡ ላይ የሚፈጽመውን ወንጀል ስለሚያውቅ፤ ምናልባት ከእስክሪቢቶና ከወረቀት በስተቀር ሌላ ነገር በእጁ ምንም ያልያዘውን ሰላማዊ ሠልፈኛ፤ መንግሥት ለመገልበጥ በማሴር ላይ ናቸውና ሄዳችሁ አስፈላጊውን  እርምጃ በመውሰድ ሠልፉን በትኑ በማለት ቀጭን ትዕዛዝ የሚሰጥ ባለሥልጣን አንደኛ ወንጀለኛ ነው፤ ሁለተኛ ሕገመንግሥቱን አያከብርም፤ በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ መለዮ ለባሹን በመናቅ እንደግቢው ውሻ ያዘዋል ማለት ነው።

መለዮ ለባሹ ለማንኛውም ግዳጅ ዝግጁ መሆኑን ካመነ ከሕዝቡ ጎን በመቆም ለሠፊው ሕዝብ ጥቅም መስዋዕት ቢሆን ስሙ ለዘለዓለም በክብር ሲነሳ ይኖራል። ነገር ግን ራሡን አዋርዶ ለጊዜያዊ ጥቅም የሚኖር ከሆነ ግን በግዳጅ ላይ እያለ ድንገት እንኳ ቀኑ ደርሳ ሕይወቱ ብታልፍ የውሻ ሞት እንደሞተ ይቆጠራል እንጂ ምንም ከብር አይሰጠውም።

በተለይ ፌድራል ፖሊስ የሆናችሁ መለዮ ለባሾች የአገሪቱን ሕገ መንግሥትና ታሪካችሁን ጠንቅቃችሁ ማወቅ ይገባችኋል። የአብርሃ ደቦጭና የሞገስ አስገዶምን ለወገን ክብርና ለአገር ሉዓላዊነት ሲሉ በጠላት ላይ የወሰዱት ቆራጥ የሆነ የጀግንነት ወኔ ከልባችሁ ሠሌዳ ላይ ለአፍታም ቢሆን መጥፋት ቀርቶ መደብዘዝ የለበትም። ጣሊያን የባዕድ አገር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አዋራጅ ገዥ ሲሆን ወያኔ ደግሞ ከወገን የወጣ ቢሆንም ታሪክን እያጠፋ ቅስም የሚሰብር ከሃዲ ቡድን ነው።  ስለሆነም የወያኔው ዘረኛ መንግሥት ከሰብዓዊ ክብራችሁ አዋርዶ እንደ ሮቦት ወይም እንደውሻ ሊገለገልባችሁ ስለሚፈልግ ኃላፊነታችሁን በብቃትና በጥራት ለመወጣት እንድትችሉና ከኅሊና ወቀሳም ነፃ እንድትሆኑ ሕገመንግሥቱን በማወቅ፤ በዚያ መሠረት የወገናችሁን ሰብዓዊ ክብር በማይጋፋ መልኩ ግዳጃችሁን እንድታከናውኑ ይረዳችኋል።

እዚህ ላይ ማጤን ያለባችሁ እናንት ወዶ ዘማቾች(mercenaries) አይደላችሁም:: የተከበራችሁ የወገን አለኝታና መከታ ናችሁ። ወዶ ዘማች ማለት በሌላ ሰው አገር በገንዘብ ተገዝቶ የሚዘምት ሆድ አደር ማለት ነው እናንተ ግን ለአገራችሁና ለወገናችሁ ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር ቃለመሃላ የፈጸማችሁ እንደመሆኑ መጠን ወገናዊ ሆናችሁ መቆም ያለባችሁ ከሠፊው ሕዝብ ጎን እንጂ፤ የወገናችሁን ሰብዓዊ መብትና ክብር በመደፍጠጥ ከድሀው ሕዝብ አላግባብ እየዘረፉ እራሳቸውን ለሚያደልቡ አምባገነን አሳማዎች መሆን የለበትም። የፈለገው ነገር ጥንቅር ብሎ ይቅር እንጂ በወገን ላይ ያላግባብ እየተዘመተ በሚገኝ እንጀራ እንደ ውሻ ተዋርዶ ከመኖር ይልቅ የክብር ሞት ይሻላችኋል። ለነገሩ በየዋሃን ወገን ላይ ከመዝመት የበለጠ ሞት አለን?

አገራችን ኢትዮጵያ እንደቀድሞ አባቶቻችን ሁሉ ዛሬም  በሐቀኛና ጀግኖች ልጆቿ  ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር !

ይህን ጽሑፍ ያነበባችሁ ላላነበቡ ወገኖች በማስተላለፍ ተባበሩ!


መንግስት ይግባኝ ጠየቀ ፣ይግባኙ የተጠየቀባቸው ሰዎችን ስም ዝርዝር ይዘናል

December 28/2013

የደህንነት ሃይሎች በአንዳዶቹ ቤት ሲመላለሱ ነበር :: የጁነዲን ሳዶ ባለቤት ወይዘሮ ሀቢባ መሐመድ በአቃቤ ህግ ይግባኝ ተጠየቀባቸው:: 

መከላከያ ምስክር ሳያስፈልጋቸው በነፃ ከተለቀቁት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ አባላት እና ወንድሞች መካከል አቃቤ ህጉ ይግባኝ የጠየቀባቸው ሙስሊሞች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ፡፡የፌደራሉ አቃቤ ህግ ፍርድ ቤቱ በነፃ እንዲሰናበቱ ከወሰነላቸው 10 ሙስሊሞች መካከል በ 6ቱ ላይ ይግባኝ እንደጠየቀባቸው ዘግበን ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራቸው የደረሰን ሲሆን ከህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች መካከል አንዱ የሆኑት ኡስታዝ ጀማል ያሲን ይግባኝ የተጠየቀባቸው ሲሆን የተቀሩት ደግሞ ሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ሼህ አብዱራህማን፣ኡስታዝ ሀሰን አሊ፣ወንድም አሊ መኪ እና በ ወ/ሮ ሃቢባ መሃመድ ላይ አቃቤ ህጉ ይግባኝ እንደጠየቀባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
የፊታችን ሰኞም ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡
1. ኡስታዝ ጀማል ያሲን
2. ሼህ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ፣
3. ሼህ አብዱራህማን፣
4. ኡስታዝ ሀሰን አሊ፣
5. ወንድም አሊ መኪ እና
6. በ ወ/ሮ ሃቢባ መሃመድ ( የጁነዲን ሳዶ ባለቤት) ላይ የፉደራሉ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቋባቸዋል፡፡
የዚህ መሰሉ የይግባኝ ድራማ ፍርድ ቤቱ ገለልተኛ እና ነፃ ነው ለማስባለል ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ውድቅ በማድረግ ፍትሃዊ ውሳኔ እንደወሰነ ለማስመስሰል እንደሚጥር ይጠበቃል፡፡
የደህንነት ሃይሎችም በአንዳዶቹ ቤት ሲመላለሱ እንደነበር ምንጮች አክለው ገልፀዋል፡፡

Saturday, December 28, 2013

የኦሮሞ ሙስሊሞችን የበላይነትን በኦሮሞ ክርስቲያን ና ኦሮሞ ባልሆኑ ሙስሊሞች ላይ ለመጫን የታለመ ድብቅ አጀንዳ ይፋ ሆነ

December 28/2013


aa
ጃዋር ማህመድ የተባለው ግለሰብ ባገኘው መድረክ ላይ ሁሉ በጣም የተሳሳቱ አዘናጊና አግላይ ንግግሮችን በማድረግ ይታወቃል :ባለፈው ወር በሙስሊም ኦሮሞች ስብሰባ ላይ በመገኘት የሰጠውም በጣም አደገኛ አስተያየት ብዙ ሰዎችን አስደንግጥዋል:: ጃዋር በንግግሩ ሙስሊሞች ያለኦሮሞ ነጻነት ሊሳካላቸው እንዳማይችልና የኦሮሞ ድል የ ሙስሊም ድል እንደሆነ ገልጽዋል::ክርስቲያን ኦሮሞዎችን እንዲሁም አማራና እንዲሁም ሌሎች ብሄሮችን ባገለለ መልኩ ጃዋር ጅቡቲ ና ሶማሊ ስላሉ ሙስሊሞች ሲናገር ተደምጥዋል:: የዘር ጉዳይና ሀይማኖት ሲደባለቁ ምን አይነት ችግር እንደሚፈጥሩ ያልተገነዘው ጃዋር በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የተወሳሰብ የህዝብ ግንኙንት ባላገናዘብ መልኩ በየመድረኩ ላይ የሚሰጣቸው ይተጣመሙና በውሸት ላይ ይተመሰረቱ አስተያየቶች ብዙ ኢትዮጵያውያን እያስቆጣ ይገኛል::

‪ ጃዋር ሞሀመድ የፖለቲካ እብደት “እኔ ባለሁበት 99% ሙስሊም ነው ማንም ሰው ደፍሮ ቀና አይልም ‪#‎በሜንጫ‬ ነው አንገቱን የምንለው ” በአሜሪካ በተደረገ ስብሰባ ላይ ከተናገረው(ሜንጫ የማጭድ ቅርፅ ያለው ረዘም ያለ ባለስለት የቁጥቋጦ መቁረጫ መሳሪያ ነው)

ከሁሉ በባሰ ብዙ ኢትዮፕያውያንን ያስደነገጠው የሀጂ ነጅብ በጃዋር አስተያየት መስማማት ነው:: እንደ ሀጂ ነጅብ አስተያየት ከሆነ 50 ሚሊዮን ሙስሊም እንዳለና 80% ሚሊዮኑ ኦሮሞ እንደሆነ ተናግረዋል:: ይህም ማለት 40 ሚሊዮኑ ኦሮሞ ሙስሊም እንደሆነና ይህም ማለት መቶ በመቶ የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው ማለት ነው:: የኦሮሞ ህዝብ ብዛት 34.4 ሚሊዮን መሆኑ መዘንጋት የለበትም::
ሀጂ ነጅብ በማስከተልም ኦሮሞች ሙስሊሙን ነጻ ማውጣት እንዳለባቸው አስምረውበታል::ይህ በውነቱ በጣም አሳዛኝና ከሙስሊም ትግል ጀርባ ያለውን ኢትዮጵያን እስላማዊ ለማድረግ የታለመውን እቅድ ያሳያል::
የሙስሊምን እንቅስቃሴ በመደገፍ ክርስቲያኖች ያረጉት አስትዋጾኦ ቀላል አይደለም ከ ጳጳስት ጀመሮ የፖለቲካ መሪዎች አክቲቭኢስቶች ጭምር ይህንን ትግል በመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ይህንን ያረጉት በኢትዮጵያዊንት መንፈስ እንጂ መስሊም ወይም ኦሮሞ ስለሆኑ አይደለም ::አቶ ነጂብ እንደ ኢትዮጵያ ሙስሊም ተወካይነታቸው ሁሉንም ሙስሊም መወከል ሲኖርባቸው ወደ ዘር በተደራጀና ሀይልን መሰረት ባደረገው የጃዋርና የአክራሪዎች ስብሰባ ላይ ተገኝቶ እናንተ ናቹ ነጻ ምታወጡን ማለት በጣም ሚያሳዝን ነገር ነው::
ጃዋር መሀመድ ሌሎች የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ባገለለ መልኩና የራሱን ዘር ባስቀደመ መልኩ ባድረገው ንግግርን መደገፍ የሙስሊም እንቅስቃሴ ከጀርባው የያዘው ድብቅ አጀንዳ እንዳለ ሚያመላከት ነው::

ጃዋር መሀመድ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ድምጻችን ይሰማ ከሚባለው የሙስሊም የዲያስፖራ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ ሲያድረግ እንደነበር ይታወቃል:: የጃዋር አጀንዳ የሆነውን የኦሮሞ ሙስሊሞች ስልጣን መያዝ ከመድረክ ጅርባ ይነጋግሩበት እንደነበር ሀጂ ነጅብ አምነዋል:: ኢትዮፕያውንን አብሮ ሚያኖረው የህግ የበላይነት, ዲሞክራሲ, ፍትህና እኩልነት መሆኑ እየታወቀና ኢትዮጵያ የብዙ ሀይማኖቶች ብሄሮች አገር እንደሆነች እየታወቀ በየመድረኩ ላይ እንደዚህ አይነት ሀላፊነት የጎደለውና ዘረኛ አስተያየት መስጠትና ያንንም መደገፍ በጣም ሚያሳዝን ነው::
የነጃዋር አላማ ይፍትህ የበላይነትን በኢትዮጵያ ምድር ለማምጣት አይደለም::አላማቸው ግልጽና ግልጽ ነው:: የኦሮሞ ሙስሊሞችን የበላይነትን በክርስቲያን ና ኦሮሞ ባልሆኑ ሙስሊሞች ላይ ለመጫን ነው::ይህንን ደግሞ በፍጹም ምንቀበለው አይሆንም::ክርስቲያኑ አንድ ነን በሚል መማማል አንድ መሆን እንደማይቻል ሊገነዘበው ይገባል::

ይድረስ ለብአዴን አባላት

December 28/2013
በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ ወደ ባህር ዳር አቅንተው ነበር። መቸስ በረከት ስምዖን አማራ ካልሆንኩ ሞቼ እገኛለሁ ብሎ አለመንደሩ የአማራ ህዝብ መሪ እኔ ነኝ ብሎ ከአማራ ህዝብ ፊት ሲቆም አለማፈሩ ያስገርማል። አዲሱ ለገሰም እንደ በረከት ራሱን የአማራ ህዝብ ወኪል እኔ ነኝ ይላል።እነዚህ ሁሉት ህወሃት የሠራቸው ፍጡራን ባህር ዳር እንዲወርዱ ያደረጋቸው ብአዴን ተዳክሟል ተብሎ መታሠቡ ነበር።
እንግዲህ በእንበረከት የአስተሳሰብ ደረጃ ብአዴን ተዳከመ ሲባል ምን ማለት ይሆን?
ከጥቂት ደካማ ካድሬዎች በቀር ሌሎች እንደ ሰው ማሰብ የሚችሉ የብአዴን አባላት አገሪቷ እየሄደች ያለችበት መንገድ ያሳስባቸዋል። ህወሃት በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ የሚያንገበግባቸው በርካታ ናቸው። ጉርፋርዳ እና ቤንሻንጉል አገራችሁ አይደለም ተብለው አማሮች ከኖሩበት ቀየ ተፈናቀለው ሜዳ ላይ የመውደቃቸው ድርጊት የእግር እሳት ሁኖ የሚለበልባቸው ብዙዎች አሉ። በዚህ ሁኔታ ያዘኑና የተቆጡ የብአዴን ካድሬዎች ድርጅቱ ቆሜለታለው የሚለው ፍትህ የት አለ፤ እኩልነትስ ከወዴት አለ፤ ኢትዮጵያስ የሁላችን አገር ነች የምትባለው መገለጫው ምንድ ነው እያሉ ይጠይቃሉ። እነዚህ ጥያቄዎች በካድሬዎች መካከል መመላለስ ሲጀምሩ ድርጅቱ ተዳክሟል ተብሎ ግምገማ ይካሄዳል።
በረከት እና አዲሱ ነፃነትን ሳያውቁ ራሳቸውን ነፃ አውጪ አድርገው የሚቆጥሩ የህወሃትን ዙፋን ከመጠበቅ የዘለለ ምንም ሚና የሌላቸው ያልሆኑትን ለመሆን የሚውተረተሩ ደካሞች መሆናቸውን እናውቃለን። እነዚህ ግለሰቦች ስለ አማራ ህዝብ ነፃነትና ክብር ይሠራሉ ብሎ ማሰብ የሚቻልበት ሁኔታ የለም። በረከትና አዲሱ በህዝብ መካከል እየኖሩ የህዝብ ፍቅር የሌላቸው፤ ከህዝቡ ጋር መኖርንም የማያውቁ፤ እለት ዕለት በሚፈጥሩት የፍርሃት አረንቋ ውስጥ የሚኖሩ እና ሠላም የራቃቸው ግለሰቦች ናቸው። ከእነዚህ ግለሰቦች እውነትን ፈልጎ ማግኘት፤ ነፃነትን ጠይቆ መቀዳጀት፤ ለፍትህ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት የሚቻል አይደለም። የአማራ ህዝብ ከጉራፋርዳ እንዲወጣ የተደረገበት ምክንያት ምንድ ነው ተብለው ሲጠየቁ የጠባቦች ጥያቄ ብለው ይሳደባሉ። አያቶቻችን በደምና አጥንታቸው ያቆዩልንን ድንበር አፍርሳችሁ ለባእዳን ለምን ትሰጣላችሁ ሲባሉ የጦርነት ናፋቂ ጥያቄ እያሉ ይዘባበታሉ። እንደምን ሁኖ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አማራ ከቁጥሩ ጎድሎ ተገኘ ሲባሉ የትምክህተኞች ወሬ እያሉ ይሳለቃሉ። አዎን እነበረከት ስምዖን የሚፈልጉት ዜጎች ስድባቸውን ተሸከመው እንዲኖሩላቸው እንጂ እውነትን፤ ፍትህን እና እኩልነትን እንዲጠይቁ አይደለም።
የሰሞኑ የባህር ዳር አስቸኳይ ስብሰባ ምክንያትም በብአዴን ካድሬዎች መካከል የፍትህ፤ የነፃነት እና የእኩልነት ጥያቄዎች ሥር እየሰደዱ መምጣታችው ነው። በካድሬዎቹ መካከል እንደ እሳት ሰደደ እየተሰራጩ ላሉ የፍትህ፤ የነፃነት እና የእኩልነት እጦት ጥያቄዎች ከህወሃት መራሹ “መንግስት መሰል” አካል በቀላሉ መልስ ማግኘት የሚቻል አይደለም። ይሄ ቡድን ነፃነትን ሳያውቅ ነፃ አወጣኋችሁ ማለትን ብቻ የሚያውቅ፤ራሱ ለሠራው ህግ መገዛትን ሳይወድ ስለ ህገ-መንግስት የበላይነት የሚሰብክ፤ ራሱ ከሁሉ በላይ እኔ ነኝ ብሎ ሲያበቃ ስለ እኩልነት ለመስበክ የማያቅማማ የነውረኞች ስብሰብ ነው። በረከትና አዲሱም የዚህ ነውረኛ ቡድን አካል እንጂ የአማራ ህዝብ አካል ናቸው ለማለት ለአማራ ህዝብ የሠሩት በጎ ነገርን ፈልጎ ማግኘት አይቻልም።
የብአዴን ካድሬዎች ሆይ !
ብአዴን ከተመሠረተ በኋላ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አማራ መጥፋቱን በፓርላማ ሪፖርት መደረጉን ሰምተችኋል።ለመሆኑ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አማራ የት ጠፋ? በአገሪቷ ካሉ ብሄረ ብሄረሰቦች መካከል እንደምን ሁኖ የአማራ ቁጥር ብቻ ሊቀንስ ቻለ? ከአማራ ክልል ወጥተው በሌላ ክልል የሚኖሩ አማሮች ይሄ አገራችሁ አይደለም፤ ወደ አገራችሁ ሂዱ ተብለው የሚባረሩት ለምንድ ነው? ኢትዮጵያ አገራቸው ካልሆነች የእነዚህ አማሮች አገር ወደየት አለች? ከጉራፈርዳ እና ከቤንሻንጉል ተነቅለው ሜዳ ላይ እንዲወድቁ የተደረጉ አማሮች በደላቸው ምንድ ነው? ለነዚህ ጥያቄዎች አማራ ካልሆንን ሞተን እንገኛለን የሚሉት በረከት ስምዖንና አዲሱ ለገሰ መልስ አይሰጡም። እነርሱ የቆሙት በህወሃት “የትግራይ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት አማራ ነው” ተብሎ የተያዘውን እምነት በተግባር ለማስፈፀም እንጂ ለአማራ ህዝብ ደህንነት እንዳለሆነ ምግባራቸው ህያው ምስክር ነው።
ብአዴን ከተመሠረተ ዘመን ጀምሮ በአማራ ህዝብ ላይ የደረሰውን ግፍ እናውቃለን። የአማራን ቅስም መሰበር፤ ትምክህቱን ማስተንፈስ፤ ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ማዋረድ የሚሉት የእነበረከት ስምዖን ዋነኛው መፈክሮቻቸው ናቸው።በዚህ መፈክር መሪነት ከሁለት ሚሊዮን በላይ አማሮች ጠፍተዋል፤ኢትዮጵያ አገራችሁ አይደለችም ተብለው ከጉራፈርዳ እና ከቤንሻንጉል ውጡ ተብለው ሜዳ ላይ ተጥለዋል። ከንግዱ አምባም ሳይቀር ቀስ በቀስ አማሮች እንዲጠፉ ተደርገው ሥፍራቸውን ለሌላ እንዲለቁ ሁነዋል። ከፕሮፌሰር አሥራት ጀምሮ ለአማራ ህዝብ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ለኢትዮጵያ ህዝብ ምልክት እና ጥሩ ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ አማሮች ቀስ በቀስ እንዲጠፉ መደረጋቸውን በአይናችን አይተናል በጆሮአችንም ሰምተናል። ብአዴን የተባለው ድርጅት በአማራ ስም ቢቋቋምም አማሮችን ከውርደትና ከሚደርስባቸው በደል ሊታደጋቸው አልቻለም።እንዲያውም ግፉንና በደሉን ለማስፈፀም የተወከለ ድርጅት ሁኗል።
እንግዲህ የብአዴን ካድሬዎች ሆይ እናንተም ከበረክተ ስምዖንና ከአዲሱ ለገሰ ጋር ተሰልፋችሁ ህዝባችሁን ትወጉ ዘንድ አይገባም። ዙሮ መግቢያችሁ ዛሬ እንወክለዋለን ያላችሁት ግን ደግሞ በአሣር በመከራ ውስጥ ያለው ህዝብ እንጂ ሌላ ዙሮ መግቢያ እንደሌላችሁ እወቁ። የወከላችሁት ህዝብ ሲረገጥ የለም ህዝቤን አትበድሉ ማለት ይጠበቅባችኋል። አማራ ከቁጥሩ ጎደለ ሲባል ምን ሆኖ እንደጎደለ በመጠየቅ የችግሩን ምንጭ ማወቅ ሥራችሁ ነው። አማራ ወደ “አገርህ” ሂድ ተብሎ ከኖረበት ሲነቀል ኢትዮጵያ አገሩ ካልሆነች የአማራ አገሩ የት ነው ብላችሁ መጠይቅ አለባችሁ።
ዛሬ እናንተን ትምክህተኞች እያለ የሚገመግማችሁ በረከት ስምዖን አያሌው ጎበዜን አስነስቶ ገዱ አንዳርጋቸው እንዲተካ አድርጓል። የአያሌው መሄድና የገዱ መምጣት ለአማራ ህዝብ ነፃነት እና ክብር የሚፈይደው አንዳችም ቁም ነገር የለም። አያሌውም ሆነ ገዱ ለቆሙለት ህዝብ ይቅርና ለራሳቸውም ክብር የሌላቸው ደካሞች መሆናቸው የታወቀ ነው። ለራሱ ክብር ያለው የህዝብ ወኪል እወክለዋለው የሚለው ህዝብ ከኖረበት ቀየ እየተነቀለ ሜዳ ላይ ሲጣል አይቶ ዝምታን አይመርጥም። አያሌውና ገዱ ከአማራ ህዝብ አብራክ ወጥተው ደሃውን አማራ በሙሉ ነፍጠኛ፤ ትምክህተኛ፤ ሌላም ሌላም እያሉ እየሰደቡ ለሳዳቢ አሳላፈው የሰጡ ደካሞች ናቸው። ካድሬ ሆይ ስማን! የገዱ በአያሌው መተካት የተዋረደውን ክብርህን አይመልሰውም። ያጣኸውን ነፃነት መልሶ አያቀዳጅህም። ለሱዳን ተቆርሶ የተሰጠውን በአያቶችህ ደምና አጥንት የቆየውን መሬትም አይመልስልህም። የብአዴን ካድሬዎች ሆይ ስሙ ለክብራችሁ፤ ለማንነታችሁ፤ ለነፃነታችሁ ቀናዒ እንድትሆኑ ሁኑ እንጂ የህወሃትን ትርፍራፊ የምትለቃቅሙ አትሁኑ።
በብአዴን ውስጥ ያላችሁ የንቅናቄያችን አባሎች ሆይ !!
የህወሃት ስንቅና ትጥቁ ጥላቻ መሆኑን ታውቃላችሁ። ህወሃት “አማራ የትግራይ ህዝብ ቀንደኛ ጠላት ነው” ብሎ የሚያምን ቡድን ነው። ከዚህ ቡድን ፍትህ፣ እኩልነትና ነፃነት ያለመስዋእትነት እንደማይገኝ መዘንጋት አያስፈልግም። እስከ አሁን የንቅናቄያችንን መሠረት ለማሲያዝ ያደረጋችሁት አስተዋፅኦ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። በህወሃት የተነጠቀው ነፃነታችን፤ የተዋረደው ክብራችንና ማንነታችን በቀላሉ እንደማይመለስ መገንዘብ ይኖርብናል። ትግሉ መራራ የሚሆንበት ግዜ መጥቷል። ለነፃነትና ለማንነት የሚከፈል መሥዋእትነት ደግሞ አስፈላጊ መሥዋዕትነት ነው።ጥቂት ዘረኞች አንገታችንን አስደፍተው በማንነታችን ላይ ተሳልቀው፤ ህዝባችንን አጎሳቁለውና ረግጠው ሲገዙ በአይናችን እያየንና በጆሮአችን እየሰማን ተንጋለን ለመተኛት አልተፈጠርንም። እንዲህ ዓይነቱን ሥንፍና ከቀደሙት ከኩሮዎቹ አያቶቻችንና አባቶቻችን አልተማርንም።
በአውሬው መረብ ውስጥ ሁናችሁ የለውጥ ኃዋሪያ ለመሆን መነሳታችሁ የሚደነቅ ነው።የለውጥ ኃዋሪያነት ትልቅ ሸከም ያለው ነው።ጥላቻን ወደ ፍቅር የሚቀይር፤ ለይቅርታ ራስን ማዘጋጀት፤ ከግዜያዊ ጥቅም ይልቅ ትውልድን አሻግሮ የማየት ራዕይን የሚጠይቅ ነው። ህወሃት አገሪቷን እያፈረሰ ያለው ከፍቅር ይልቅ በጥላቻ ስለተሞላ፤ ከይቅርታ ይልቅ በበቀል ልቦና የሚመላለስ በመሆኑን፤ ትውልድን አሻግሮ ከማየት ይልቅ የስግብግብነት ስሜቱ ያየለበት ሆኖ በመገኘቱ ነው። ንቅናቄያችን ይህን ከመሰለ አገር አጥፊ አስተሳሰብ በላይ ነው። ንቅናቄያችን ሁል ግዜ ለይቅርታ የተዘጋጀ ልቦና አለው። ይሄ ሲባል ግን የበቀለኞችን ሠይፍ ለመመከት ራሱን አያዘጋጅም ማለት አይደለም። እንዲያውም ሰይፋችን ከእነርሱ ሠይፍ በላይ የሳለ መሆኑን ያውቁት ዘንድ እንወዳለን። ንቅናቄያችን ትውልድን አሻግሮ የሚያይ ባለ ረዥም ራዕይ ነው። እንደ ህወሃት ለዘረፋ የተሠለፈ፤ እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል የሚል አይደለም። ዘራፊውንና እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይበቀል የሚለውን ሁሉ ነቅሎ ሥፍራውን ለማስለቀቅ ሳያቅማማ በፅናት የሚሠራ ነው።
በብአዴን ውስጥ ያላችሁ የንቅናቄው አባላት ሆይ!!
የገዱ በአያሌው መተካት የሚያመጣው ለውጥ የለም።አያሌው ሄደ ገዱ መጣ ሁለቱም ከአንድ ምንጭ የተቀዱ ደካሞች ናቸው። ገዱ የነፃነትን፤የፍትህንና የእኩልነትን ዋጋ የሚያውቅ አይደለም። ገዱ ሲሊኩት ወደየት፤ ሲጠሩት አቤት ከማለት የዘለለ ለዚያች አገር ለውጥ የሚፈይደው አንዳችም ነገር እንደማይኖር እወቁ። ስለሆነም የተጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ ሳታቅማሙ በፅናት ቁሙ። ፍርሃትን ግደሉት። ከፍርሃት አርነት የሚያወጣን ነፃነት፤ ፍትህና እኩልነት ብቻ ነው። እነዚህ ለሰው ልጆች መሠረታዊ ቁም ነገሮች በአገሪቷ ሰፍነው ዜጎች ሁሉ እፎይ እሰከሚሉ ድረስ የሚከፈለውን መሥዋ ዕትነት ለመክፈል ወደ ኋላ እንዳትሉ። በእኛም በኩል አስፈላጊውን መሥዋዕትነት ለመክፈል የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። የጀመርነውንም ትግል ሳናቅማማ እና ሳናፈገፍግ እንቀጥላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

“ካልተሳፈርኩ” ብሎ የታክሲ ሹፌሩን በሽጉጥ ገደለ

December 28/2013

መገናኛ አካባቢ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መስመር፣ አንድ መንገደኛ ትናንት ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ካልተሳፈርኩ ብሎ ሾፌሩን ወንደሰን ደምሴን በሽጉጥ ገደለ፡፡ “ታክሲው ውስጥ ካልተሳፈርኩ፣ አትሳፈርም” በሚል በተነሳው ጭቅጭቅ፣ ሾፌሩን ገድሏል የተባለውን ደጀኔ ገመቹ በቁጥጥር ስር እንደዋለ የገለፀው ፖሊስ፤ የአይን ምስክሮችን ቃል በመቀበል ምርመራ እያካሄደ ነው፡፡ ታክሲ እየጠበቁ የነበሩ የአይን ምስክሮች በወቅቱ አቶ ደጀኔ እጁን በማወዛወዝ ሚኒባስ ታክሲውን እንዳስቆመ ተናግረው፣ ከሾፌሩ ጋር ጭቅጭቅ እንደተፈጠረ ገልፀዋል፡፡ 

አቶ ደጀኔ በታክሲው ለመሳፈር ሲጠይቅ፣ ሾፌሩ “ቤተሰቤን ነው የጫንኩት፣ ሌላ ሰው አላስገባም” በማለት ምላሽ እንደሰጠው በአካባቢው የነበሩ መንገደኞች ተናግረዋል፡፡ ታክሲ የሚጠባበቁ ብዙ ሰዎች በአካባቢው ስለነበሩ፣ ጭቅጭቁን ከመነሻው እስከ መጨረሻው የተመለከቱ እማኞች በርካታ ናቸው፡፡ የፖሊስ መረጃ እንደሚጠቁመው፤ የሾፌሩ አባት ታክሲው ውስጥ ነበሩ፡፡ “አትሳፈርም የምትለኝ ንቀት ነው” በሚል ክርክርና “የጫንኩት ቤተሰቦቼን ስለሆነ ሌላ ሰው አልጭንም” በሚል ምላሽ በተባባሰው ጭቅጭቅ፣ አቶ ደጀኔ ሽጉጥ እንዳወጣ እማኞች ተናግረዋል፡፡

 ሽጉጡን ሾፌሩ አንገት ስር በመደገን ነው የተኮሰው ብለዋል-ምስክሮች፡፡ በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሰው መግደል ዲቪዥን ክፍል ተወካይ፣ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል።

የጋዜጠኞች እስር መንግስትን፣ ማህበራትንና ፓርቲዎችን እያወዛገበ ነው

December 28/2013

የጋዜጠኞች እስር መንግስትን፣ ማህበራትንና ፓርቲዎችን እያወዛገበ ነው
           መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገው ሲፒጄ የተሠኘው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ጋዜጠኞችን በማሠርና በማንገላታት ኢትዮጵያ ከአለም ሁለተኛ ናት ማለቱን መንግስት እና በሃገሪቱ የሚገኙ የጋዜጠኞች ማህበራት አምርረው ሲያወግዙ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በበኩላቸው፤ በእርግጥም ሃገሪቱ ጋዜጠኞችን እያሠረች ነው፤ ደረጃው ይገባታል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ አብርሃም፤ “ሲፒጄ የሃገራችንን ስም ለማጥፋት ስለሚፈልግ ነው እንጂ፣ በፃፈው ፅሁፍ የታሠረ አንድም ጋዜጠኛ የለም፡፡ 3 ጋዜጠኞች የታሠሩት አሸባሪ ተብለው ነው” ብለዋል፡፡ በማህበራችን ጥረት በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች እስር ቆሟል ሲሉም ተናግረዋል አቶ አንተነህ። የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞች ማህበር (ኢነጋማ) ሊቀመንበር አቶ ወንደሰን መኮንን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሙያው ጋር በተያያዘ የታሠረ ጋዜጠኛ እንደሌለ ገልፀው፣ የታሠሩ ጋዜጠኞች ጉዳያቸው ሌላ ቢሆንም መፈታት አለባቸው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡
የሲፒጄን መግለጫ እንደማይቀበሉትና ድርጅቱ የራሱ ተልዕኮ እንዳለው አቶ ወንደሰን ጠቁመው፤ “ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሠር በአለም ሁለተኛ መሆን አትችልም፤ ሆናም አታውቅም” ብለዋል። የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው፤ “ሲፒጄ የፖለቲካ አጀንዳ ያለውና መንግስትን በሃይል ለመለወጥ ከሚንቀሣቀሡ ድርጅቶች ጋር የተሰለፈ ድርጅት ስለሆነ፤ በተግባር ከጋዜጠኝነት ጋር ምንም ግንኙነት የለውም” ብለዋል፡፡ አቶ ሽመልስ፤ “እናንተ መቼ ታሠራችሁ? የማታውቁት ከማርስ የመጣና ‘የታሠረ ጋዜጠኛ አለ እንዴ?’ ሲሉም ጠይቀዋል። የሲፔጂ የአፍሪካ ወኪል፣ በ97 ምርጫ የቅንጅት አመራር የነበረና የኢትዮጵያን መንግስት በሃይል ለመገልበጥ የሞከረ ግለሠብ ያሉት አቶ ሽመልስ፤ እንዲህ ያሉግለሠቦች እየፈተፈቱ የሚያቀርቡለትን ነገር ሲፒጄ እየተቀበለ ያስተጋባል ብለዋል፡፡ ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና በሠጡት አስተያየት፤ መንግስት ጋዜጠኞችን እንደሚያስርና እንደሚያንገላታ ለማረጋገጥ እስር ቤት ሄዶ ማየት ይቻላል ብለዋል፡፡
የታሠረ ጋዜጠኛ የለም እየተባለ መነገሩ የተለመደ ቀልድ ነው ያሉት ዶ/ር መረራ፤ እነ እስክንድር፣ ውብሸት እና ርዕዮት በጋዜጠኝነታው እንጂ ሽጉጥ ሲሠርቁ አይደለም የታሠሩት ብለዋል፡፡ “ለመሆኑ እዚህ አገር ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገት ማህበር አለ እንዴ?” በማለት የጠየቁት ዶ/ር መረራ፤ “የነፃ ጋዜጦች እና የጋዜጠኞች ህልውና ከፖለቲካ ምህዳሩ ጋር አብሮ የተዳፈነ ነው” ብለዋል። የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ በበኩላቸው፤ ሲፔጂ መግለጫውን ሲያወጣ የራሱ መስፈርት እንዳለውና ዝም ብሎ እንደማይዘላብድ በመግለፅ፣ ሪፖርቱ ትክክለኛ መሆኑን ተናግረዋል። “ኢትዮጵያ ሃሣባቸውን በነፃነት የሚገልፁ ሠዎች በአደባባይ የሚሠቃዩባት፣ ጋዜጠኞች እስር ቤት የሚታጎሩባት ማተሚያ ቤቶች መንግስትን የሚተች ጋዜጣ አናትምም የሚሉባት፣ ጋዜጦች ተዘግተው ጋዜጠኞች የተሰደዱባት አገር መሆኗን በተጨባጭ እናውቃለን” ብለዋል አቶ ዳንኤል፡፡ የታሠሩት ጋዜጠኞች ከሙያው ጋር በተያያዘ አይደለም መባሉን እንደማይቀበሉት አቶ ዳንኤል ገልጸው፤ ከነፃው ፕሬስ ጀማሪዎች መካከል አንዱ የሆነው እስክንድር ነጋ፤ ለሃሣብ ነፃነት የቆመ የመብት ተከራካሪ መሆኑ መታሠብ አለበት ብለዋል፡፡