Friday, October 16, 2015

ውሸት ውሎ አድሮ መጋለጡ አይቀርም!!!

October 16, 2015
def-thumbሥልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ ተቆጣጥሮ ያለው የወያኔ አገዛዝ ካለመታከት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ተአምር ሊመስል በሚችል  መንገድ እያሳደኩ ነው እያለ ሲዋሽ አመታት ተቆጥረዋል። በተለይ ምዕራባዊያንን ሲያታልልበት የነበረው የዲሞክራሲ ጭንብል በምርጫ 97 ከተገፈፈበት ወዲህ ላለፉት አስር አመታት ባለ ሁለት አሃዝ እድገት አስመዝግቤያለሁ እያለ እጅ  እጅ እስኪለን ድረስ በባዶ ሜዳ ስለ ልማትና የዕድገት ሲነግረን ሰነበቷል።
ወያኔ በጉልበት በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ የልማትና የእድገት ፕሮፓጋንዳ ስለ ሰበአዊ መብትና ስለዲሞክራሲ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለማፈኛና አፍ ለማዘጊያነት በማገልገል ላይ ይገኛል ። አለማቀፍ የሰባአዊ መብት ተቋማት ስለሰበአዊ መብት ጥሰት ለሚያቀርቡት አቤቱታ ሁሉ የሚሰጠው መልስ “ኢኮኖሚውን እያሳደግን ነው” የሚል ነው። ኢኮኖሚ ማደግ አለማደጉን ትርጉም የሚኖረው ከህዝብ የእለተ ተእለት ኑሮ ጋር ሲያያዝ መሆኑ ሁሉ  ትርጉም አጥቷል። ራበኝ የሚለው ሰው ሁሉ ጠገብኩ ማለቱ ነው ተብሎም ይተረጎማል።
የውሸት ነገር ውሎ አድሮም ቢሆን መጋለጡ አይቀርምና ይኼው በቅርቡ የተከሰተው ድርቅ የወያኔን የውሸት ፕሮፓጋንዳ ክንብንብ ገፎታል። አለም በሙሉ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ ሲያድግ የነበረ ኢኮኖሚ ባለበት ሃገር ውስጥ አንዲት የድርቅ አመት ካለርሃብና ልመና እንዴት መሻገር አቃተው የሚል ጥያቄ በሰፊው በማንሳት ላይ ነው። ወያኔ ለዚህ ጥያቄ መልስ የለውም።  በአለም ዙሪያ ያለው ተመክሮ ሁሉ የሚያሳየው ወያኔ አድጌበታለሁ ብሎ ሲለፍፍ ከኖረው አሃዝ በታች በግማሽ ያደጉ ሃገሮች እንኳ አንድም ጊዜ አንድ የድርቅ ዘመን መሻገር አቅቶአቸው  ሲንገዳገዱና መንግሥታቸው ለልመና ሲሄድ አለመታየቱን ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ የሚያወራውን ያህል ያልሆነ ቢሆንም በአንዳንድ ከተሞች አካባቢ የሚታየው እድገት የተገኘው ከውጭ መንግስታት የገንዘብ ብድር፣ በአለም አቀፍ ተቋማት እርዳታ፣ ስደተኛው ኢትዮጵያዊ በገፍ በሚልከው ገንዘብና ወያኔ ከድሃውና ከነጋዴው ከዝርፊያ ባላነሰ ሁኔታ በሚሰበሰበው ግብርና መዋጮ የተገኘ እንጂ ወያኔ ባስፋፋው ኢንዱስትሪና ልማት እንዲሁም ሀገር ውስጥ በፈጠረው ሀብት አለመሆኑ የሚታወቅ ነው።
የወያኔ ሹማምንትና አገልጋዮች ሀብት በሀብት መሆናቸውን እንደ እድገት ካልቆጠርን በስተቀር  ህዝባችን ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮውን እንኳን መደጎም አልቻለም ።በዝርፊያ ገንዘብ ሹማምንቱና የወያኔ ባለምዋሎች የገነቡትን ፎቅ የሀገር ልማት ነው ካላልን በስተቀር እውነተኛና የህዝብ ህይወት ከመሰረቱ የሚቀይር ልማት አገር ውስጥ አለመካሄዱ ትንሽ ገለጥ ሲያደርጉት የሚታይ ሃቅ ነው። አንድ የድርቅ ወቅት መሻገር አቅቶት ብዙ ሚሊዮኖችን ከረሃብና እልቂት መታደግ ያልቻለ ኢኮኖሚ አስር አመት ሙሉ በሁለት አሃዝ አድጓል ብሎ የሚያምን ሰው ሊኖር አይችልም።
የወያኔ የኢኮኖሚ አሃዝ “መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ” ከሚለው የሀገራችን ግፈኛ አባባል  ብዙም አይለይም። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለህዝብ በሚጠቅም መንገድ የማደጉ ጉዳይ በመጀመሪያ ፍትሐዊ ኢኮኖሚያዊ ሥርአት መገንባትንና ዴሞክራሲ ማስፈንን ይጠይቃል።
በመሆኑም የዛሬው የወያኔ ኢኮኖሚ የዝርፊያ ኢኮኖሚ እንጂ ህዝባዊ ሽታ የለውም። የኢትዮጵያን ህዝብ እዚህና እዚያ በሚብለጨለጩ ያውም በአብዛኛው በብድርና እርዳታ በተገኙ ልማት ተብዬ ነገሮች ለረዥም ጊዜ ማታለል አይቻልም።
ወያኔ በሚሰጠው አሃዝ የሚያድግ ማንኛውም ሀገር የውጭ ስደተኞችን ያስተናግድ እንደሆን እንጂ ወጣቶች ሞትና ህይወትን አማራጭ አድርገው አይሰደዱበትም። ባለ ሁለት አሃዝ አዳጊ ኢኮኖሚ በየትም ሀገር የስደተኞች ምንጭ ሆኖ ታይቶ አይታወቅም በዘረኛው ወያኔ ተገዢዋ ኢትዮጵያ ካልሆነ በስተቀር።
አርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ትንሳኤ ከዘራፊው የወያኔ ሥርዐት መወገድ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን ያምናል!  ስለዚህም ህዝባችን ወያኔን ለማስወገድ የተጀመረውን ትግል በነቂስ ለመቀላቀል ዛሬውኑ እንዲነሳና ከጎናችን እንዲሰለፍ የማያቋርጥ ጥሪውን ደግሞ ደጋግሞ ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Wednesday, October 14, 2015

Journalism in Ethiopian Context

October 14, 2015
by Tewedaje Tesfu Biru
Handwritten bulletins which address the daily events of ancient Rome were the earliest journalistic effort made in the first century BC. Then, the first distributed news bulletins appeared in China around 750 AD. Germany, The Netherlands, and England produced newsletters and news books of different sizes in the 16th and 17th centuries.
By the early 18th century, politicians had begun to recognize the enormous potential of newspapers in shaping public opinion. Consequently the journalism of the period was largely political in nature; journalism was considered as an adjunct of politics and each political faction had its own newspaper. It is also during this time struggle for freedom of expression, which is immunity of the communications media including newspapers, books, magazines, radio, and television from government control or censorship, began.press freedom and the fate of journalists in Ethiopia
Ethiopia, in which freedom of expression is guaranteed as the basic right in the constitution, is among the leading countries in the world in suppression of the rights to freedom of expression and access to information. Many private media are banned, and many journalists fled their country and many others thrown to prison only because they criticized the state government. According to Human Rights Watch, Ethiopia is the second country next to Iran in the number of journalists in exile.
Journalism is a socially responsible profession, serving the needs and interest of the society by creating the necessary intelligence they need to lead better lives. However, in Ethiopia most, if not all, government journalists are the watchdogs of the government rather than the public and they are sanctioned by the government to be so. Journalists with strong position to balance their stories would be accused of having conspired with the opposition and are usually labeled as “terrorists” or “anti-government” and taken to prison. In fact, even those who work as watchdogs of the government lead their life in conflict between their professional identity and the situation.
Journalism in Ethiopia is not free of political influence. This can be indicated in the government’s dominance of the media ownership, the appointment of the media managers from the ruling party, and the imposition of restrictive media laws. The government’s clear aim is to ensure that media promote and never criticize government initiatives and policies.
As Human Rights Watch states the Ethiopian government has accused more than 38 journalists with various crimes under the Anti-Terrorism Proclamation since the 2010 election. Journalists who are known to write critical articles face regular and intense pressure from security officials. With the existing degree of censorship, it seems Ethiopia is in the 18th century as far as the development of journalism in the rest of the world is considered. Thus, it can be said that in Ethiopia where freedom of expression is highly suppressed and journalists are in trouble, journalism is fake.
Tewedaj Tesfu Biru, October, 2015, Toronto, Canada

Monday, October 12, 2015

ከመድረክ/ሰማያዊ/መኢአድ ጋር ለመነጋገር እንደሚፈልጉ አቶ ሃይለማሪያም ገለጹ - የሚሊዮኖች ድምጽ

October 12,2015
Millions of voices for freedom - UDJ's photo.
“ከስፖርት ጀምሮ እስከ ሥራ በፓርቲ አባላነት ነው “ ወ/ር ጽጌ ጥበቡ
“ እርስዎ ከምለስ ራ፤እይ ተላቀው ይራስዎት ራእይ መቼ ነው የሚኖሮት ? “ ጥያቄ ለአቶ ኃይለማሮያ
ያለፈው አርብ መስከረም 28 እና ቅዳሜ መስከረም 29 ቀን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተገኙበት፣ በአምስቱ አመቱ የእድገትና ትራስንፎርሜሽን እቅድ ዙሪያ፣ ኢሕአዴግ ስብሰባ አድርጓል። በአመስት አመቱ እቅዱ ዙሪያ ከመነጋገር በፊት በሕዝብ የሚነሱ ወቅታዊ የሰብአዊ መብት፣ የፍትህ መጓደልና የብሄራዊ መግብባባት ዙሪያ ዉይይቶች መቅደም አለባቸው በሚል፣ የአራት ደርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ፣ የሰማያዊ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ ) ስብሰባዉን አልተሳተፉም።
ከመድረክ ቀጥሎ በ2007 በርካታ ተወዳዳሪዎች በማሰለፍ ሁለተኛ የሆነው ኢዴፓን ፣ ጨመሮ ሌሎች አናሳ ድርጅቶች ስብሰባዉን ተሳትፈዋል። በዶር ጫኔ ከበደ የሚመራው ፣ ኢዴፓ፣ ጥያቄዎችን በማንሳት ጠንካራ ክርክሮች እንዳደረገ ለማረጋገጥ ችለናል። የኢዴፓ ተወካዮች፣ በድፍረትና በግልጽ ያለፈው የአምስት አመት እቅድ እንዳልተሳካ፣ መረጃዎች በማስቀመጥ ለማሳየት የሞከሩ ሲሆን፣ መሰረታዊ የፍትህ የመልካም አስተዳደር፣ የዴሞክራሲ ለዉጦች ተደርገው፣ ሕዝቡን ባቀፈና ባሳተፈ መልኩ ስራ ካልተሰራ፣ መጨው የአምሰት አመት እቅድም አይሳከም ሲሉ ለነ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ተናግረዋል።
ወ/ሮ ጽጌ ጥበቡ የሚባሉ የኢዴፓ ምክር ቤት አባል፣ “ ከስፐርት ጀመሮ እስከ ሥራ፣ የኢሕአዴግ ፓርቲ አባል ካልተኮነ በቀር ምንም ነገር ማደረግ አይቻልም” ሲሉ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ኢኮኖሚዉን፣ ፖለቲካዉን፣ ሜዲያዉና ሌሎች ሁሉንም ተቋማት ብቻውን እንደሚቆጣጠር በመገልጽ ፣ ተቋማት ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
“ እርስዎ የመለስን ፎቶ እየያዙ፣ በመለስ ራእይ እያሉ ነው። የራስዎት ራእይ የልዎትም ወይ ? ሲሉ ኤደፓዎች አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በላያቸው ላይ ያለፈው የአቶ መለስ ጥላ ገፈው ፣ ህዝብን አክብረው ፣ “ዴሞክራሲ የሕልዉና ጉዳይ ነው “ ብለው ብዙ ጊዜ የሚናገሩት ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
አቶ ኃይለማሪያም ደርጅታቸው ብዙ ስህተት ያለው፣ ብዙ ነገሮችን ማስተካከል ያለበት እንደሆነ ያመኑ ሲሆን፣ ከተቃዋሚዎች ጋር እየደጋገሙ በመነጋገገር ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንደሚሞክሩም ቃል ገብተዋል።
በስብሰባው ያልተካፈሉ ደርጅቶችም ስብሰባዉ ላለመካፈልል የወሰኑትን ዉሳኔ እንደሚያከብሩ የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም፣ በስብሰባው ካልተገኙ ደርጅቶች ጋር ለመወያየትና ለመነጋገር ፍላጎትና ፍቃደኝነቱ እንዳላቸዉም በስብሰባው ወቅት ገልጸዋል።
በኢዴፓና መድድረኩ ላይ በነበሩት በኢሕአዴግ ባለስልጣናት መካከል የጦፈ ክርክርና ምልልሶች የነበብሩ ቢሆንም በሕወሃቱ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ኢቢሲ/ኢቲቪ ግን በስብሰባው የነበረዉን ሁኔታ በግልፅ ለሕዝብ ከማቅረብ፣ እንደ አቶ ትግስቱ አወሉ ያሉትን የሕወሃት አሻንጉሊቶች በማቅረብ፣ የዉሸት ዘገባን ማቅረቡን መርጧል።

Friday, October 9, 2015

የሕወሓት ሰዎች ዶላርን በሰሜን አሜሪካ በ23 ብር እየመነዘሩ ሃብታቸውን በማሸሽ ላይ መሆናቸው ታወቀ

October 10,2015

የሕወሓት ባለስልጣናት ከሃገር ቤት ሃብታቸውን ለማሸሽ እየጠቀሙበት ያለው ዘዴ የኢትዮጵያን ባንኮች ከመጉዳቱም በላይ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ አስፈሪ ዳመና እንደጣለበት ተሰማ:: በአሁኑ ወቅት የሕወሓትና የተላላኪዎቹ ድርጅቶች ባለስልጣናት በሙስና ያከበቱትን ሃብት እያሸሹ ያሉት እዚህ ሰሜን አሜሪካ ወደ ሃገራቸው ዶላር መላክ የሚፈልጉትን በ23 ብር ሃገር ቤት ላይ እንመነዝርላችኋለን በሚል እንደሚቀበሉና በዚህም ጥቁር ገበያ የሕዝብ ሃብት እየሸሸ መሆኑ ተጋልጧል::

በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ; በሲያትል; በዴንቨር; በሚኒያፖሊስ; በአትላንታ; በዳላስ; በቺካጎ; በሂውስተን; በኦሃዮ; በፖርትላንድ; በላስቬጋስ; በካሊፎርኒያ የተለያዩ ከተሞች; በአሪዞና በተዘረጉ ኔትወርኮች ዶላር በጥቁር ገበያ 23 ብር እየተመነዘረ መሆኑ ታውቋል::

የገንዘቡ ዝውውር የሚደረገው ከላይ በተጠቀሱት ከተሞች ባሉ ኔትዎርኮች መካከል ዶላሩን እዚሁ ይሰጡና ሃገር ቤት በግለሰቦች አማካኝነት በ23 ብር ምንዛሬ ይሰጣል:: ዘ-ሐበሻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድረገጽ ባገኘችው መረጃ መሰረት በዛሬው ዕለት የዶላር ምንዛሬ ዋጋ 20.85 ሲሆን በ23 ብር በጥቁር ገበያ እየሸጠ ይገኛል::

ዶላር በሕገወጥ መንገድ እንዲህ መተላለፉ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት ዘንድ ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት የሚያባብሰው መሆኑ እየታወቀ የሕወሓት ሰዎች እንዴት እንዲህ ባለው ሕገወጥ ተግባር ላይ እንደተሰማሩ የሚያስገርም ነው የሚል አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች ከጥቂት ጊዜያት በፊት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “የኢትዮጵያን መንግስት በኢኮኖሚ ማዳከም ካስፈለገ ከውጭ የሚላኩ ዶላሮች በኢትዮጵያ ባንኮች በኩል መተላለፍ የለባቸውም:: ሕዝቡ ዶላሩ መንግስት እጅ በማይገባበት መልኩ ገንዘቡን ይላክ” ማለታቸውን ይጠቅሳሉ::
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Wednesday, October 7, 2015

በፓርላማው ውስጥ እንቅልፏን የለጠጠችው ወ/ሮ አስቴር አማረ ጋር በእንደርታ ምርጫ ተፎካካሪዋ የነበረው የአረናው አባል ስለሴትየዋ ይናገራል

October 7,2015

ፓርላማው ውስጥ ዛሬ በርካቶች እንደተለመደው እንቅልፋቸውን ሲለጥጡት ውለዋል:: ይህን ተከትሎ የተለያዩ ፎቶዎች ሲለቀቁ ውለዋል:: ከነዚህ እንቅልፋሞች መካከል ደግሞ አንዷ ወ/ሮ አስቴር አማረ ናት:: ከ እንደርታ ትግራይ የመጣችው ይህችው የፓርላማው ተቸካይ ጠርጴዛ ላይ ተቸክላ እንቅልፏን ስትለጥጥ ነበር:: ከ እርሷ ጋር በተፎካካሪነት በአንድ ምርጫ ጣቢያ ቀርቦ በሕገወጡ ምርጫ ተሸንፈሃል የተባለው የአረናው ፓርቲ ተወካይ አቶ ሰናይ የሚከተለውን መልዕክት በፌስቡክ ገጹ አስተላልፏል::

እኝህ እንቅልፋም ወ/ሮ አስቴር አማረ የተባሉት ሴት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የህወሓት የ ወረዳ እንደርታ(መቀለ ዙርያ) ተወካይ ሲሆኑ በ2002 ምርጫ በ ወረዳው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡት 7 የሚሆኑ የፓለቲካ ፓርቲዎች እኔም ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉአላውነት በመወከል ስወዳደር እኔና እሳቸቸው ከባድና እልህ አስጨራሽ ፍኩኩር ያደረግን ቢሆንም ምንም የውድድር ሜዳ፣ገለልተኛ የሆነ የምርጫ ቦርድና ፍትሓዊነት ባልነበረው ምርጫ የህወሓት ካድሬዎች 1ለ 5 በማደራጀት ያለና የሌለ አቅማቸው የሀይልም ጭምር በመጠቀም እዚ ግባ በማይባልልና በተጭበረበረ ምርጫ ፓርላማ ሊገቡ ችለዋል።

በጣም እሚገርመው ነገር ወይዘሮ አስቴር አማረ የተመረጡበት ወረዳ ያልተወለዱበት፣ያላደጉበትና የማያውቁት መሆኑ ነው።ፓርላማ ገብተው መተኛታቸውም ለመረጣቸው ህዝብ ንቀት መግለጫ ዋነኛ ምስክር ነው።በአሁኑ ግዜ እኔ በፓለቲካ ልዩነቴ ምክንያት በደረሱብኝ ችግሮች ከምወዳት አገሬና ከምወደው ወገኔን ርቄ በስደት ስንከራተት እንቅልፋምዋ ግን ደልታት ፓርላማ ውስጥ ላሽ ብላለች።

senay amare
ወይ አገሬ

Tuesday, October 6, 2015

ዘራፊው ሕወሓት ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ ውሳኔ ሰጪ ያልሆኑ ወንበሮችን ለአሽከሮቹ አድሏል::

October 6,2015
- አቶ ሬድዋን ሁሴን በሃስት ሲምሉለት የነበረውን ወንበር አጥተዋል::
- ሃይለማርያም ከኒውዮርክ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ከሰው እንዳይገናኙ ተደርገዋል::
- ጥያቄ የሚያበዙት አቶ አለማየሁ ተገኑ እና አቶ ሶፊያን አህመድ ከአሽከርነት ቦታቸው ተነስተዋል::
- ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::
Hailemariam
 ምንሊክ ሳልሳዊ:- የሕወሓት አሻንጉሊት የሆነው ሃይለማርያም ደሳለኝ በዛሬው እለት ባቀረበው የቸብ ቸብ ካቢኔ መሰረት ሕወሓት የጦር ሃይሉን የውጪ ጉዳዩን የደህንነቱን የኮሚኒኬሽን እና አስፈላጊ ቀልፍ ጉዳዮችን በመቆጣጠር ውሳኔ ሰጪ የማይባሉ ተራ ቦታዎችን ለአሽከሮቹ በማደል የተዋቀረ ሲሆን አለማየሁ ተገኑ እና ሶፍያን አህመድ ምን እንደዋጣቸው አይታወቅም::ከኒውዮርክ ስብሰባ መልስ ሁለት ቀን ከመኖሪያ ቤቱ እንዳይወጣ እና ከሰው እንዳይገናኝ የታገደው ሃይለማርያም ደሳለኝ ራሱን ፈልጎ አለማግኘቱ እና በአሽከርነት መኖሩን ቤተሰቦቹን እያበሳጨ መሆኑ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ይናገራሉ::
ቁልፍ የሆኑ ስልጣኖቹን የተቆጣጠረው እና በዘመድ አዝማድ ተሞልቶ በከፍተኛ የሃገር እና ሕዝብ ሃብት ዘረፋ ላይ የተሰማራው ሕወሓት ባለፈው የኢሕአዲግ ስብሰባ ወቅት አንዳንድ አመራሮቹ ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ ከስልጣን እንደሚባረሩ ሲነገር ነበር:: የወያኔና አሽከሮቹ ሹመት እንደሚከተለው ነው:-
አቶ ደመቀ መኮንን – ም/ጠቅላይ ሚኒስትር እና የማህበራዊ ዘርፍ ክላስተር አስተባባሪ
ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል –በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
ወይዘሮ አስቴር ማሞ – በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ሲራጅ ፈጌሳ – የመከላከያ ሚኒስትር
ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አቶ ካሳ ተክለብርሃን – የፌደራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
አቶ ጌታቸው አምባዬ – የፍትህ ሚኒስትር
አቶ አብዱላዚዝ መሀመድ – የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
አቶ ተፈራ ደርበው – የእርሻ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ ስለሺ ጌታሁን – የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
አቶ አህመድ አብተው – የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
አቶ ያዕቆብ ያላ – የንግድ ሚኒስትር
አቶ አብይ አህመድ – የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
አቶ ወርቅነህ ገበየሁ – የትራንስፖርት ሚኒስትር
አቶ ሙኩሪያ ሀይሌ – የከተማ ልማት እና ቤቶች ሚኒስትር
ዶክተር አምባቸው መኮንን – የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
አቶ ሞቱማ መቃሳ – የውሃ፣ መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
አቶ ሽፈራው ሽጉጤ – የትምህርት ሚኒስትር
አቶ ቶሎሳ ሻጊ – የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
ዶክተር ከሰተብርሀን አድማሱ – የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ – የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
ኢንጂነር አይሻ መሀመድ – የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ -የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም – የአካባቢ ደን ልማት እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
አቶ ሬድዋን ሁሴን – የወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስትር
ወይዘሮ ደሚቱ ሀምቢሳ – የመንግስት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
አቶ በከር ሻሌ – የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬከተር
አቶ ጌታቸው ረዳ – የመንግስት ኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሀላፊ ሚኒስትር
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ – የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
ዶክተር ይናገር ደሴ – የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
ትግላችን ላይ በማተኮር ሕወሓትን ከነአሽከሮቹ ልናጠፋቸው ይገባል::በአንድነት በመቆም ሃገራችንን ከጅቦች እናድናት:

Sunday, October 4, 2015

ድርጅታችንን እናጠንክር፤ በጽናት እንታገል!

October 4, 2015
def-thumb“የአርበኞች ግንቦት 7 አባል በመሆኔ እኮራለሁ” እያሉ በአገዛዙ የይስሙላ ችሎት ሳይቀር በድፍረት የሚናገሩ ወጣቶች ተፈጥረዋል። ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲ፣ ለእኩልነትና ለሀገር አንድነት መስዋዕትነት መክፈል የሚያኮራ ተግባር መሆኑ በተግባር የሚያሳዩ ወጣቶች መጥተዋል፤ አሁን በርካቶችም እየመጡ ነው። ወያኔ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በማኅበረሰባችን ውስጥ የዘራው የፍርሀትና የአድርባይነት ስሜት በራሱ በወያኔ የአገዛዝ ዘመን ተወልደው ባደጉ ወጣቶች እየተናደ፤ በምትኩ ሊጠፋ ተቃርቦ የነበረው የአገር ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እያንሰራራ ነው።
ቅንነት፣ ሀቀኝነት እና ጽናት ከተጣሉበት ጉድጓድ አቧራቸውን አራግፈው እየተነሱ ነው። በማኅበረሰባች ውስጥ ትልቅ የስነልቦና አብዮት እየተካሄደ ነው።
ከስነልቦና ለውጡ ጋርም በተግባር የአገር አድን ሠራዊትን የመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው። ወጣቶች የአገራቸው ባለቤት መሆናቸው ተገንዝበው የፓለቲካ ሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በቁርጠኝነት መነሳታቸው ተስፋ ሰጪ ነገር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 በዚህ የለውጥ ወቅት ውስጥ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ አጽንዖት ልንሰጣቸው ስለሚገቡ የድርጅትና የሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) አስፈላጊነት ላይ የጋራ ግንዛቤ መያዝና በተግባርም መተርጎም አስፈላጊ ነው ብሎ ያምናል።
ወጣቶች ትግሉን ለመቀላቀል መሻታቸው መልካም ነገር ነው። ሆኖም ግን በድንገት ብድግ ብለው መንገድ ከመጀመር ይልቅ ከሚያምኗቸው ወዳጆቻቸው ጋር የመሠረቱት፤ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋርም ትስስር የፈጠረ ስብስብ አካል ሆነው መቆየታቸው እጅግ አስፈላጊ ነው።
በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሆኖ የሚስጢር ድርጅት ማዋቀር አስቸጋሪ መሆኑ የማያጠራጥር ቢሆንም የማይቻል ነገር ግን አይደለም። ወጣቶቻችን በአምባገነን ሥርዓት ውስጥም ሆነው በዲሲፕሊን የታነፀ ድርጅት የመፍጠርን ክህሎት መላበስ ይገባቸዋል። ይህንን ማድረግ ስንችል ነው የህወሓትን ፀረ-አገርና ፀረ-ትውልድ ተግባር ማክሸፍ የምንችለው። ትግሉን በሁሉም የኢትዮጵያ ግዛቶች ማቀጣጠል የምንችለው በየአካባቢው የተደራጀ የለውጥ ኃይል ሲኖረን ነው። ስለሆነም የምስጢር የተደራጀ አካል በየመኖሪያና የሥራ አካባቢዎቻችን ሁሉ እንዲኖር ማድረግ ከአጣዳፊ ሥራዎቻችን አንዱ እናድርገው።
ሁለተኛው ነጥብ ሥነሥርዓትን የሚመለከት ነው። ሥነሥርዓት ከሌለ ድርጅት የለም። የህወሓት አገዛዝ ያሳደረብን ጎጂ የባህል ተጽዕኖ ከባድ በመሆኑ ራሳችንን በሥነሥርዓት ለማነጽ መልፋት ይጠበቅብናል። አገራችንና ራሳችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ አውጥተን የተሻለ ሥርዓት ማምጣት የምንችለው ራሳችን፣ ድርጅታችን እና ተግባሮቻችን ለሥነሥርዓት ተገዢ ስናደርግ ነው። የነፃነት ታጋዮች ራሳቸውን ለሥነ ሥርዓት ያስገዙ መሆን ይኖርባቸዋል። አስተሳሰባችን ራሱ ሥነ ሥርዓት የያዘ ሊሆን ይገባዋል። እንደዚሁም ሁሉ ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት የታነጹ ሊሆኑ ይገባል።
የንቅናቄዓችንን መዋቅር በመላው አገራችን ከዘረጋን፤ ራሳችንን፣ አስተሳሰቦቻችንና ተግባሮቻችን በሥነሥርዓት ከመራን፤ ቅንነት፣ ሀቀኝነትና ጽናት ከተላበስን ድላችን ቅርብ እና አስተማማኝ ነው። ለውጥን የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ይተግብር።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, October 1, 2015

ከመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የስንብት ጥያቄ የሚያቀርቡ መኮንኖች ቁጥር እያሻቀበ ነው

October 1,2015
መቶ በመቶ ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ ከአንድ አካባቢ በወጡ የህወሓት አባላት ድኩማን ወታደራዊ አዛዦች ብቻ ቁጥጥር ስር ሆኖ በከፋ አስተዳደራዊ በደል እየማቀቀ በዘር ሸለቆ ውስጥ የሚገኘው ብዙኃኑ የመከላከያ ሰራዊት የሰባት ዓመታት አገልግሎት የኮንትራት ጊዜውን የጨረሰው የስንብት ጥያቄ ያዘሉ ደብዳቤዎችን ያለማቋረጥ እያስገባ በየእርከኑ የሚገኙ የመከላከያ የአስተዳደር ቢሮዎች በማመልከቻ ማዕበል ክፉኛ እየተመቱ የሚገኙ ሲሆን የአገልግሎት ጊዜው አልሞላ ብሎት የስንብት ደብዳቤ ማስገባት ያልቻለው የሰራዊቱ አባል ደግሞ የሰቀቀን ኑሮውን ለማሳጠር በራሱ እርምጃ እየወሰደ ያለምንም ፋታ እየከዳ ነው ሲል የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ዘግቧል::
(Photo File)
(Photo File)















ድኩማኖቹ ህወሓታዊያን የመከላከያ ሰራዊቱ አዛዦች የአገልግሎት ጊዜ ኮንትራታቸውን ጨርሰው የስንብት ደብዳቤ ለሚያስገቡት በስርዓቱ የተንገሸገሹ እና በእጅጉ ተማረው ተስፋ የቆረጡ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የሰራዊቱ አባላት “ከመከላከያ ሰራዊቱ ፈፅሞ መልቀቅ አይቻልም…” የሚል አሉታዊና ድፍን ያለ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም ድኩማኖቹ ወታደራዊ አዛዦች የአገልግሎት ዘመኑን የጨረሰ ማንኛውም የመከላከያ ሰራዊት አባል በአሁኑ ሰዓት የስንብት ጥያቄ የማቅረብ መብት እንደሌለውና አሰናብቱኝ ብሎ በሚያመለክት ላይ እርምጃ የሚወስዱ መሆናቸውን ጠንከር ያለ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
ከየማሰልጠኛው ተመርቀው በየጊዜው ሰራዊቱን የሚቀላቀሉ አዳዲስ አባላት ብዙም ሳይቆዩ ስለሚከዱ “ነባሩ ሰራዊት” ከተሰናበተ በእነሱ ላይ ቅንጣት ታክል እምነት ስለሌላቸው በአገዛዙ ላይ የከፋ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል በማብራራት በማሳመን ለማባበል እየሞከሩ ይገኛሉ፡፡
የህወሓት አገዛዝ በየጊዜው ከመከላከያ ሰራዊቱ የሚከዱትን አባላት ከየተሸሸጉበት አድኖ የመያዝ ሰፊ እንቅስቃሴ አድርጎ ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡
በየጊዜው ያለምንም ፋታ የሚከዱ የሰራዊቱ አባላት ወደየ ትውልድ ቀያቸው አይደለም የሚመለሱት፤ ገሚሶቹ ከነትጥቃቸው በረሃ ወርደው ይሸፍታሉ፤ አብዛኞቹ የነፃነት ትግሉን ይቀላቀላሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ ድምበር ተሻግረው እግራቸው ወደመራቸው ይሰደዳሉ፡፡
በአጠቃላይ አሁን እጅግ በጣም በርካታ አባላት ላነሱት የስንብት ጥያቄ የተሰጠውን “አይቻልም” የሚል ድኩማን ህወሓታዊ ወታደራዊ አዛዦች ምላሽ ተከትሎ በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ከዳር እስከ ዳር ሰፍኖ የቆየውን ውጥረትና አለመተማመን ከጫፍ አድርሶት አገዛዙ ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ የሆነ ከባድ አደጋ እያንዣበበ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ስብሰባ ረግጠው ወጡ

October 1,2015
All members with the exception of Russia's UN Ambassador Vitaly Churkin and China's deputy U.N. Ambassador Wang Min vote in the United Nations Security Council in favor of referring the Syrian crisis to the International Criminal Court for investigation of possible war crimes at the U.N. headquarters in New York May 22, 2014. REUTERS/Lucas Jackson (UNITED STATES - Tags: POLITICS) - RTR3QEAZ
ተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በጄኔቭ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ካለው 30ኛ ጉባኤ ጋር ተያይዞ በተጠራ መድረክ ላይ የተጋበዙት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ስብሰባ ረግጠው ወጡ። ስኞ እለት የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት በተመለከተ በተጠራው ስብሰባ ላይ የተገኙትና በኋላ በቀረበው ሪፖርት ሳይደሰቱ ስብሰባውን ረግጠው የወጡት የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ወደ ስብሰባው አልተመለሱም። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተወካዮች ጨምሮ የተለያዩ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለሰቦች በጄኔቭ ስዊዘርላንድ በመገኘት በወቅታዊ የኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት አያያዞች ዙሪያ መወያየታቸውን እማኞች አስታውቀዋል። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች በመድረኩ ሊነሱ በሚችሉ የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ከጉባኤው ረግጠው መውጣታቸው ታውቋል።

ሂውማን ራይትስ ዎችን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣና አፈና ተባብሶ መቀጠሉን ገልፀዋል። ሁሉንም የፓርላማ ወንበሮች በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የሚገኘው ገዢው የኢህአዴግ መንግስት፣ የዜጎችን ሃሳብን የመግለጽ መብት ከማስፋፋቱ በተጨማሪ በነጻ የመገናኛ ብዙሃን ላይ የሚወስደው እርምጃ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ድርጅቱ አመልክቷል። ከትናንት በስቲያ ሰኞ የተካሄደውን የሰብዓዊ መብት መድረክ ያዘጋጀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን በተለያዩ ጊዜያት በኢትዮጵያ ስላለው የሰብኣዊ መብት አያያዝ ስጋቶችን ሲገልፅ መቆየቱ ይታወሳል። በጄኔብ በተካሄደው በዚሁ ልዩ መድረክ የተሳተፉ በርካታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ረፖርት ማቅረባቸውንም በመድረኩ የተሳተፉ አካላት ገልፅዋል።
የእንግሊዝ የፓርላማ አባላትን ጨምሮ በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጀቶች ኮሚሽኑ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝን ጨምሮ በተለያዩ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ክትትልን እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበው እንደሚገኙም ተችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች መድረኩን ረግጠው ስለወጡበት ምክንያት የሰጡት ምላሽ የለም።

(የሳዑዲ ጉዳይ) ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ እስከዛሬ አልታወቀችም ነበር – ኢትዮጵያ 13 በላይ ሞተውባታል ፣ 26 ቆስለውባታል ከ204 በላይ ጠፍተውባታል ፣ ፍለጋው ቀጥሏል

Oktober 1,2015
nebyu sirakየማለዳ ወግ…አድካሚው ስራ ፣የጠፉትን ሀጃጆች ፍለጋ !
ኢትዮጵያ …
* ኢትዮጵያ 13 በላይ ሞተውባታል ፣ 26 ቆስለውባታል
ከ204 በላይ ጠፍተውባታል ፣ ፍለጋው ቀጥሏል
* ጅጃ ከተላለፉት ቁስለኞች ኢትዮጵያዊ የለም
* ጅዳ ማህጀር የተላፈው ሬሳ ማንነት ገና አልተጣራም
* ከማህጀሩ ሬሳ የአፍሪካውያን አለበት ተብሏል
* ኢትዮጵያውያን መካ ላይ ለፍለጋው በግል ተደራጅተዋል
* ማፈላለጉን በሁሉም ሆስፒታሎች መከዎን ገዷቸዋል
* ቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ ተብለዋል
* በመካው ክሬን የተጎዳች ኢትዮጵያዊት ሀጃጅ ተገኘች
* ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ እስከዛሬ አልታወቀችም ነበር
* ልክ የዛሬ ሳምንት መሞቷ ተጠቁሟል
ህንድና ፖኪስታን …
* በማፈላልጉ የሳውዲ መንግስት አፋጣኝ እርዳታ ተጠየቀ
* የህንድን ፖኪስታን ቆንስሎች መግለጫ ሰጥተዋል
* ህንድ 46 ሞቶባታል 62 ቆስለዋል 82 ጠፍተውባታል
* ፖኪስታን 46 ሞተውባታል ፣ 8 ቆስለዋል 42 ጠፍተውባታል
የጠፉትን ፍለጋና ጭንቅ ድካሙ …
======================
ተቀማጭነታቸውን ሳውዲ ያደረጉ ፣ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ፣ በሀጅ ጸሎት ከአደጋው የተረፉ ሀጃጆችና ቤተሰቦቻቸው በሚና ጀማራት አደጋ የጠፉና የሞቱትን ሰዎች ለማፈላለግ ሌት ከቀን ወደ ሚና ፣ ጀማራትና መካ በመመላለስ አድካሚ የጭንቅ ሳምንት መግፋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። የጠፉ ሃጅ ቤተሰቦች በግሩኘና በተናጠል ቢያፈላልጉም በርካታዎች እንዳልተሳካላቸው ይናገራሉ ። በአደጋው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ቁጠር ገና ከአደጋ ቀን አንስቶ ከአምስት በላይ መሆኑ ግልጽ እያለ በኢትዮጵያ ኢንባሲ ፣ ቆንስልና የሀጅ ኮሚቴ የሚደረገው ፍለጋ የተቀናጀ ባለመሆኑ ዝርዝር መረጃው ቀርቶ የሞቱና የቆሰሉትን ዙሪያ ትክክለኛ መረጃ አልቀረበም ነበር ። ከብዙ ጉትጎታ በኋላም ትክክለኛውን መረጃ ለህዝብ ለማድረስ በርካታ ቀናት ወስዷል ።

አሁንም በኢትዮጵያ ተወካዮች በኩል ቀናት የወሰደው የሞቱና የቆሰሉትን የማሳወቅ መረጃ ቅበላ ከቀናት በፊት ይፋ ቢደረግም አሁንም ቁጥሩ እየጨመረ ከመጣው የሟቾቸ ብዛት አንጻር የመረጃ ክምችቱን የማሻሻል ስራ እየተሰራ አይደለም ! ጉዳዩ ያሳሰባቸው በመካ ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካ ላይ በሚገኙ በ13 ሆስፒታሎች ፍለጋ ተደራጅተዋል ጀምረዋል ። ያም ሆኖ መሊክ ፈይሰል ፣ ሄራ ፣ ጀበለር ኑርና መሊክ አብደላ በተባሉ ሆስፒታሎች ቢከለከሉም በቀሩት አንዳን ሆስፒታሎች ማፈላለግ ችለዋል። ማፈላለጉን በተወሰነ መልኩ ማሳለጥ ችለው 15 ያህል ቁስለኞችን አግኝተዋል። ነገር ግን የተጠቀሱት ሆስፒታል ሃላፊዎች የቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ በማለት የተከለከሉት ወጣቶች ከሀጅ ኮሚቴ ጋር ተቀራርበው ለመስራት የሚየሰደርጉት ሙከራ አለመሳካቱን ገልጸውልኛል! ውክልናውን ወይም መታወቂያ ይሰጣቹሃል ቢባሉም እስካሁን ከኮሚቴው መልስ ባለመሰጠቱ ጥረታቸው መሰናክል እንደገጠመው አንድ የገላጊው ቡድን አባል ገልጸውልኛል !

በአንጻሩ የመሳሳይ ችግር ያለባቸው የአንዳንድ ሀገራት የመንግስት ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ነዋሪዉን ለበጎ ስራና በማቀናጀትና በማቀዳጀት በሽዎች የሚቆጠሩ ልዩ የፈላጊ ግብረ ሃይል አቋቁመው በመካ ፣ ሚናና ጀናራት አሰማርተዋል ። የነዋሪውንና የሀጃጆችን ጭንቀት በመረዳትም የቆሰሉትንና የሞቱትን ፎቶ መረጃዎች ከሳውዲ መንግስት በመውሰድ ለዜጎቻቸው አቅርበዋል።
በሳምንት የአደጋው አድሜ በዋናነት አሳሳቢ የሆነው ቁርጡ የታወቀው የሞቱትና የቆሰሉት ዜጎች አልሆነም። ሞተው ፎቷቸውና ቆሰለውም ከሆነ ዝርዝራቸው ያልተገኙት ጉዳይ ብዙ ዜጎችን በመንፈስ እያስጨነቀና እያንገላታ ይገኛል። መዳረሻቸው ” ጠፋ” ከሚባሉት መካከል በደረሰው አደጋ ፊታቸው መለየት ያስቸገረ ይገኙበታል የሚል ጥርጣሬ ቢኖርም የሟቾችን ሬሳ ለመለየት የተለያዩ እርንጃዎች ቀርበዋል። ሀጃጆች በገቡበት አሻራ ለመለየት እየተወሰደ ያለው ማጣራት ረዠም ጊዜ መውሰዱ ተቃውሞ እየቀረበበት መሆኑ ይጠቀሳል ። የሳውዲ መንግስት የየጤና ጥበቃና የፖስፖርት ክፍል ኃላፊዎች ስለመለየቱ ስራ ሲናገሩ በሶስት መንገድ እንደሚከወን ያስረዳሉ ። እስካሁን መለየት ያልተቻለውን ሬሳ ለመለየት የቀረቡት ዘዴዎችም 1ኛ / በገቡበት አሻራ 2ኛ / በገቡበት ፎቶ መለየት እና 3 ኛው / የስጋ ዘመድ ቤተሰቦቻቸው እየቀረቡ DNA በመስጠት መለየቱ እንደሚከወን ይናገራሉ ! አሻራቸው የተነሱ ሬሳዎች ውጤት በከነገ ጀምሮ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ቢጠበቅም የተረጋገጠ መረጃ እስካሁን አላገኘሁም !

የሳውዲ መንግስት የጠፉትን በማፈላለግ ሂደቱን እብዲያፋጥንና የዜጎቻቸው እጣ ፈንታ እንዲያሳውቅ ህንድና ፖኪስታን የሳውዲ መንግስት አስቸኳይ እገዛ እንዲያደርግ በተለያዩ መንገዶች ተማጽኗቸውን በማቅረብ ላይ ናቸው !
ይቀጥላል …
ነቢዩ ሲራክ
መስከረም 20 ቀን 2008 ዓም

Wednesday, September 30, 2015

የትጥቅ ትግልና ግራ የሚያጋባ አስተያየት – ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

September 30,2015
getachew
በኢትዮጵያ ትከሻ ላይ የተቆለፈውን ቀምበር ለማላቀቅ ቍልፉ የትጥቅ ትግል መሆኑ በተነሣ ቍጥር ከአንዳንድ ሰዎች የሚሰጠው አስተያየት ግራ የሚያገባ ነው። ገዢዎቹና ደጋፊዎቻቸው ቢቃወሙ ይገባኛል። የሚሰጡት አስተያየት ግን ሕፃንን ሳይቀር የሚያሥቅ ነው። “ጦርነት በቃን” ይላሉ። “አትንኩን” ማለታቸውን የማናውቅ ይመስላቸዋል። ጦርነት ካላስፈለገ፥ ለምን ከንጉሣዊው አስተዳደር ጋር ተዋጉ? ለምን ከደርግ ጋር ተዋጉ? ጨቋኝ ገዢ የት አገር ነው በሌላ መንገድ ሥልጣን ለሕዝብ ሲለቅ የታየው? የምሥራቁ ዓለም ጨቋኞች የወደቁት በሕዝብ ዐመፅ ነው ማለት፥ የምዕራቡን ዓለም ከባድ እጅ ሚና መርሳት ይሆናል።
የኛዎቹ ጦርነት ከመረራቸው፥ ሕዝብን ወደጦርነት የሚመራ በደል አይሥሩበት። ምን ጊዜም ቢሆን የትጥቅ ትግል የመጨረሻው አማራጭ ነው። የትጥቅ ትግል የሚያደርሰው ጉዳት በአንዱ ወገን ላይ ብቻ አይደለም። መሣሪያ የሚያነሣ መሣሪያ ማንሣት የሚያመጣበትን ጉዳት ሳያውቅ አይነሣም። ሰው ሆኖ እንደከብት መገዛት ያልቻለ ሰው በቃኝ ሲል፥ ክብሩን በመጠበቁ ከተቀመጡበት ተነሥቶ “ነወር” የሚባል እንጂ፥ በባርነት ጥላ ሥር ተቀምጦ የሚተች አይደለም። “ጦርነት መርሮናል” የሚለውን ምክር መገዛት ለመረረው አይመክሩም።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ግራ አጋቢ አስተያየት “ጦርነትስ አስፈላጊ ነው፥ ግን . . .” የሚለው ነው። ይህ አስተያየት በቅን አሳብ፥ የተሰጠ ሊሆን ይችላል። ግን አዛኝ መስሎ፥ ቀምበረኛውን ለመደገፍ የተሰጠ አስተያየት አለመሆኑ በምን ይታወቃል? እውነተኛ አሳቢና ሠጊ ሰው አስተያየቱን የሚሰጠው ሲጠየቅ፥ ካልተጠየቀም በግሉ ትጥቅ ያነሡትን ፈልጎ በጨዋ ደምብ መንገር ነው። ሳይጠየቁ ተነሥቶ በይፋ ምክር መስጠት ግን ሰሚው ሕዝብ ትግሉን እንዳይደግፍ መገፋፋት ነው። የትጥቅ ትግል ከታመነበት እንዲፋፋም የማይፈለግበት ምክንያት ምንድን ነው?
ትጥቅ ትግል የራስን ሕይወት ለወገን ነፃነት መሠዋት ማድረግ ነው። ሌላ ዓለማ የሌለው ሰው መሣሪያ ሲያነሣ፥ እንዴት ይኸንን የሚሰነዘርበትንና የሚሰነዘርለትን ምክር ሳያስብበት ራሱን ለመሥዋዕትነት ያቀርባል? የሚካኼደው የትጥቅ ትግል የሚያዋጣ የመሰለው እርዳታውን ያቅርብ፤ የማያዋጣ የመሰለው ለምንድን ነው የሚቃወመው? ተቃውሞው ማንን ለመጥቀም ነው? ለታጋዮቹ አስቦ ከሆነ፥ ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው። “የኔን ያህል የማሰብ ችሎታ የላችሁም” ማለት ነው። እንዴት ነው ለታጋዮቹ ያልተገለጠ ሥጋት ለምክር ሰጪዎቹ የተገለጠው?

አንዳንዱ ደግሞ፥ “ይኸው እንታገላለን ሲሉ ዓመታት አሳለፉ፥ ግን አንዳች ውጤት አላሳዩም” ይላል፤ ውጤት እንዲያሳዩ የቀጠራቸውና ካልሆነላቸው የሚያሰናብታቸው ሹም ይመስል። አርፎ መቀመጥ ስንት ውጤት አሳየ? ሌሎችን ሙከራዎችም “አንዳች ውጤት አላሳዩም” ብለን እንንቀፋቸዋ!ውይስ ውጤት አሳይተዋል?
“በመካሄድ ላይ ያለው የትጥቅ ትግል ኢትዮጵያን የሚጎዳ ነው” ከተባለ፥ እርግጥ ሊታሰብበት ይገባል። ግን አሳሳቢው ምክንያት ሊቀበሉት በሚገባ መልኩ አልተሰጠንም። ይህ ትግል የሚያመጣው ጉዳት ከተሸከምነው ቀምበር ይበልጥ ሊከብድ እንደሚችል አሳዩን።
የወያኔ ቀምበር መሰበር አለበት የምንል ሁሉ በመሰለንና በተቻለን መንገድ እንታገል። ካልተቻለን፥ ካልመሰለን፥ አርፈን እንቀመጥ፤ ታጋዮችን አለማደናቀፍ፥ እንደ ትግል እንዲቈጠርልን።

Tuesday, September 29, 2015

አርባ‬ ምንጭ የነበረው የአሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን አካባቢውን ለቆ እየወጣ ነው

September 29,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)


‪አርባ‬ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡ ‪‎ህወሓት‬ በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡
አርባ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡

በአርባ ምንጭ እና አካባቢው ሲንቀሳቀስ እና ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ከዚያ እያስነሳ ወደ ሚፈልገው አቅጣጫ ለጥቃት ሲያሰማራ ለረጅም ጊዜ የቆየው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን ከአገሪቱ መንግስት በተሰጠው መመሪያ የቆይታ ጊዜ ኮንትራቱን አቋርጦ ሀሙስ ዕለት አካባቢውን ለቆ መውጣት መጀመሩን በቦታው የሚገኙ ምንጮቻችን ገልፅዋል፡፡ ድሮን የታጠቀው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን የአርባ ምንጭን መሬት ለቆ መንቀሳቀስ የጀመረበት ምክንያት ለጊዜው በውል ተለይቶ ባይታወቅም መንግስት ነኝ በሚለው በህወሓት አገዛዝ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል አለመግባባት ተከስቶ ቅራኔ ሳይፈጠር እንዳልቀረ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ ከአሁን በፊት ከአርባ ምንጭ በተጨማሪ በድሬ ደዋ ላይ ተቀምጦ በሰው አልባ አውሮፕላኖች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሱ የአልሸባብ ተዋጊዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት መክፈቱ ይታወቃል፡፡ ህወሓት በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ገና ከሽፍትነቱ ጀምሮ በህዝብ ላይ ሴራ በማቀነባበር የሚታወቀው ህወሓት ራሱ ግንብቶ ለግለሰቦች ያከራየውን የንግድ ማዕከል ነው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ድርጊቱን እንደፈፀሙት በማስመሰል ከህዝብ ለመነጠል ሲል ነው በተቀነባበረ ሂደት በእሳት የለቀቀው ፡፡

በህወሓት የተቀነባበረ ሴራ የተከሰተው ከባድ የእሳት አደጋ የደረሰው መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም ሲሆን ከ40 በላይ ሱቆች ተበልተው ወደ አመድነት ተቀይረዋል፤ በሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረትም ወድሟል፡፡ ህወሓት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በተከሰቱት የቦንብ ፍንዳታዎች ትግራይ ሆቴልን ጨምሮ እጁ እንዳለበት የአሜሪካ ኤምባሲ ለስቴት ዲፓርትመንት የላከውን ደብዳቤ በዋቢነት ጠቅሶ ዊክሊክስ የተባለው ድረ-ገፅ ማጋለጡ የሚታውስ ነው፡፡

Saturday, September 26, 2015

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia

September 26, 2015

logo-timeret
United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia, (pdf)

Ethiopia is one of the oldest nation-states in the world. Both written and oral history and recent archeological discoveries, despite regional rivalries, suggest the historical continuity of the nation. It was a Monarchy until 1974. From 1974 to 1991 the country was declared to be ‘Peoples Democratic Republic’ by the military junta, Derg, and went through a traumatic experience. Tigrai Peoples Liberation Front (TPLF), a guerrilla force from a minority ethnic group that led the rebellion against the military junta and captured the institutions of the State, has been in power for the past 24 years. The country is ruled as a one-party state under a façade of multi-party system since 1991.
The state is characterized by an intensifying political repression, rampant economic corruption, denial of basic human and political rights and repeated sham elections. The top brass of the army and security organs of the state, including key diplomatic positions, are effectively mono-ethnic despite the claim of the regime to stand for the equality of all ethnic groups. The people have completely lost confidence in the government after the regime shamelessly declared itself to have won 100% of the parliamentary seats in the 2015 election. Ethiopians, with no other choice available to them for democratic transition, have now risen up in arms. And this is a credible threat of force to the regime. History has time and again proven that no government that denies freedom, justice and democracy to its people will not survive their wrath.
Against this background, Ethiopian democratic forces, reflecting the broad diversity of the Ethiopian society, have recently formed the United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED) as an umbrella organization. UMSED is committed to coordinate the people’s struggle for effective resistance against TPLF’s tyranny and to ensure the transition to true democracy and stable political order in Ethiopia. No one relishes the idea of armed conflict; but, there are times when armed self-defense becomes the only choice to resist the unbearable violence by minority against majorities and to bring about an enduring peace and stability in a society.
Ethiopians have given up on elections as they have become meaningless rituals:There have been five national elections under the TPLF. The first election in 1995 resulted in 3 opposition members being elected to the parliament that has a total of 548 MPs. In the second election of 2000, the number for the opposition members rose to 27. In the 2005 general election, which was monitored by the Carter Center, European Union and other observers, Ethiopians turned out in record numbers and voted for the opposition, mainly CUD and UEDF. The results were rigged; and the election was blatantly stolen. Furthermore, many unarmed and defenseless peaceful protesters demanding the respect for the vote of the people were indiscriminately gunned down in a broad daylight. Leaders of opposition political parties, civic societies, journalists and dignified and well-meaning Ethiopian citizens were jailed for two years. Members of the fact finding commission appointed by the government itself published the evidence that the government has cold-bloodedly massacred 197 Ethiopians on this day of infamy. Today, these fact finders are themselves in exile fleeing for their lives. Only one opposition member was able to win a seat in the parliament during the 2010 fourth national election. In the most recent election of May 2015, in which the regime claimed 100% landslide victory of all parliamentary seats, no credible outside/international observers, excepting those from the corrupt African Union, were allowed to monitor the election.
The Ethiopian government owns all land in the country, including most residential and commercial real estate in towns and cities like all other communist totalitarian regimes in the world. The industrial and service sector of the economy is also heavily controlled by Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), an endowed conglomerate parastatal serving as a front for the ruling TPLF party. Until recently it was managed by the wife of the late Prime Minister. Both were members of the TPLF/EPRDF politbureau and the legislative assembly, making their work similar to the work of the late Romanian dictators, Nicolae Ceaușescu and his wife Elena Ceaușescu. The total grip on land and the economy is a source of much power to the regime and the accompanying oppression of the people in a country where eighty five percent of the population is engaged in farming and most city dwellers rely on the government for employment and housing. All land in the country was declared government property by the old communist military regime and the current regime has continued the practice. The monopolization of land by the TPLF and its surrogate administrators has been the source of wealth for some, but continued to stifle the production of food as in the communist era. Thanks to this land policy, today lives particularly that of children and cattle in the Afar, Amara, Gambella, Somali and Southern regions of the country are perishing due to a single season rainfall failure.
Ethiopians are tired of their voices being totally muffled: Independent media is not tolerated. The International Federation of Journalists has declared the regime to be one of the worst offenders of press freedom. Television, Internet, and major print media is owned and operated by the government. The state is the only Internet Service Provider and uses Chinese, Italian and British Internet hacking and intercepting technology vendors to spy, trap and intimidate its critics and opponents. The regime also spends precious resources on signal jamming technology to stop the free flow of information from the outside. Foreign based and independently operated radio and TV broadcasts by the Ethiopian Diaspora are jammed on regular basis as are broadcasts in Ethiopian languages by Voice of America and Deutsche Welle Radio.
Ethiopians can no longer tolerate an entrenched ethnic minority rule: The TPLF, the dominant party in the coalition known as Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), controls all aspects of life in the country, similar to apartheid South Africa, by installing its ethnic rulers as heads of major institutions across the entire state apparatus. Ethiopians and international observers including those who bend backwards to “apologize” for the regime know very well that ethnic Tigrayans control the army, security services, telecoms , foreign affairs, and other nerve centers of the Ethiopian state machinery. The TPLF party pits different ethnic and religious groups against one another simply to perpetuate its minority rule and monopoly on resources. The regime has no respect for religious freedom. It has created chaos in both the Ethiopia Orthodox Tewahido Church and the Muslim mosques by interfering in the administration of their purely religious institutions through its political cadres. It has similar surrogates in Pentecostal Churches. Religious leaders who resist this interference are exiled (as the Orthodox Christian leaders) and imprisoned (as the Muslim community leaders). Ethnic minority domination has become a source of stress on the harmony of the people that is essential for peaceful coexistence in a diverse mutli-ethnic and multi-religious country like Ethiopia.
Ethiopians have said enough to the regime’s oppression with impunity: In the last twenty four years, the people have been appealing to the regime to respect the fundamental political and civil liberties of the citizenry. Peaceful protests are disallowed. Countless petitions and protest demonstrations that were held in the major capitals of the world have ended in deaf ears. The response by the government has been more repression and more violence. Today there is no independent media in the country due to the wide spread practice of jailing and forcing publishers and reporters in to exile. Today there are no functioning independent political parties due to the practice of systematic disruption of their normal day-to-day activities, jailing of opposition leaders or forcing them out of their country. Currently, prisons are filled with thousands of well-known political, civic organization and religious leaders as well as journalists under trumped-up “terrorism” charges. Certain ethnic groups are targeted. These prisoners are tortured to confess and to corroborate the charges against themselves and their colleagues. In spite of this massive oppression, victims of the regime have no recourse to justice since the judiciary is made subservient to the political manipulation of the ruling party.
As presented above, Ethiopians are once again faced with a regime that is led by a group of people who oppress them in multiple ways; deny them basic human rights and are hell-bent on blocking the democratic process for self-rule. We are also aware that though the regime comes from Tigrai, a thousands of Ethiopians that come from this ethnic group are victimized and have already started armed insurrection well over one decade ago. The predicament the Ethiopian people find themselves in currently is not unique. Under similar conditions, the founding fathers of one of the earliest democracies in the world have said it best in the Declaration of Independence by the Colonies from the Great Britain: ‘We hold these truths to be self-evident, that all men are created equal, that they are endowed by their Creator with certain unalienable Rights, that among these are Life, Liberty and the pursuit of Happiness. — That to secure these rights, Governments are instituted among Men, deriving their just powers from the consent of the governed, — That whenever any Form of Government becomes destructive of these ends, it is the Right of the People to alter or to abolish it, and to institute new Government, laying its foundation on such principles and organizing its powers in such form, as to them shall seem most likely to affect their Safety and Happiness’ A similar spirited paragraph is found in the preamble of African National Congress’s Freedom Charter. These words ring true today for the people of Ethiopia.
At this critical juncture, to facilitate the Ethiopian people’s struggle with able leadership, the democratic forces in the country are coalescing under the newly formed UMSED as a “broad church”.. It is not lost on the part of these democratic forces that one of the potential obstacles on the road to the Ethiopian people’s struggle for freedom and democracy is the international community’s multifaceted collaboration with the TPLF dominated government with seeming indifference to the prevailing repressive political conditions in the country.
Following their new goal of making inroads into Africa, some countries have become major financiers of the TPLF repressive regime. This may be an expected behavior from these governments, given the nature of their systems. However, the West’s support for the rogue dictatorial regime is inconsistent with the values of freedom, justice, and democracy the West practices at home and espouses for the stable world order. The West led by the US has correctly and understandably declared terrorism as the number one menace to global peace while in a typical short-term calculus have also decided to consider dictatorial regimes like that of Ethiopia to be “allies” in its anti-terrorism effort and the disorder in the Greater Horn of Africa region. As a result, the West has made the Ethiopian regime a beneficiary of its substantial financial, political, diplomatic and even military support indirectly emboldening it to continue with impunity in its human rights abuse and repression of its own people. This policy on the part of the Western countries is not only short sighted and immoral but is more than likely to lead to greater instability especially when minority regimes collapse.
It is obvious that the repressive nature of the regime and its extensive human rights abuses are among the main causes of instability in the region. For all those who are willing to see the writing on the wall, the regime is internally in continuous conflict with its citizens; it uses scorch-earth military expeditions in the Ogaden region to the east and makes occasional incursions into Kenyan territory pursuing armed resisters. The regime is also locked in constant conflict with Eritrea in the north. This is the reason why the regime has one of the biggest standing army in Sub-Saharan Africa thus spending large portion of the poor country’s budget on the military while the danger of famine and lack of resources for basic needs of its population is always lurking around.
While this is the true reason for the TPLF regime to build an army that is beyond the country’s legitimate external security threat need, it cynically uses a fraction of this army in international peace keeping missions in order to get acquiescence from the West for its nefarious repression at home as well as use these missions as a source of hard currency income for its corrupt highest military brass. Recently, the Ethiopian government is even seen scheming to leverage its security cooperation with the West, hopefully in vain, for extending its repressive hand abroad by invoking the legitimate rebellion and resistance of Ethiopians as a terrorist act. The truth is that the Ethiopian people’s resistance is a very disciplined and well organized struggle that is focused only on a political goal of making Ethiopia a democratic country either by forcing the minority regime to come to table or removing it if it continues to persist on blocking Ethiopians’ right for self-government. The people’s resistance movement is also very much aware of its responsibilities for the Ethiopian people, the people of the region and the international community. It is a resistance movement which is informed from the rich tradition of Ethiopian history. It is not a group of bandits and terrorists. It includes several members of the opposition who contested the ill-fated 2005 election. In deed it is a democratic force and represents a cross section of Ethiopians.
In their long history of existence, Ethiopians have shown no affinity for internalizing any sort of extremist ideology let alone to terrorist practice despite the persistent attempt to impose communism during the military regime and ethno-centric politics by the current regime on them. The history of Ethiopia is replete with building good relationship with its neighbors, peaceful coexistence and social stability. Ethiopian history also shows the courage and willingness of the people to lay their lives and honor to resist and prevail over colonialism and minority rule.. Witness the Ethiopian people’s glorious victory in the battle of Adwa and their resistance against fascist Italy even when the world turned its face and gave them its cold shoulders.
To stay true to our forefathers’ tradition saying no to oppression and its own commitment for democracy, UMSED pledges to work hard and to pay the necessary sacrifice to put an end to the tyranny of TPLF dominated regime and to assure that the TPLF regime becomes the last dictatorship in Ethiopian history. The UMSED appeals to the peace loving people of the world and the international community to stand in solidarity with the Ethiopian people; for it is only by democratizing Ethiopia that a lasting stability can be achieved and the specter of terrorism can be dealt with effectively in one of the most volatile regions of the world. Anything else will further destabilize Ethiopia and turns the Horn of Africa into a hot bed of terrorism.
From the Foreign Relations Office of United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED)
September 25, 2015

Thursday, September 24, 2015

የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ እየተባባሰ መጥቶአል፣ መንግስትም ችልተኝነትን አብዝቶአል

September 24,2015
በሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣውን አረንጓዴው ድርቅ እየተባለ የሚጠራው ከፍተኛ ረሃብ በመላው ሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣ ሲሆን በአሁን ሰአት በሰሜኑ ክልል ምስራቅ እና ደቡቡን በከፊል ከማጥቃቱም በላይ ከፍተኛውን ህዝብ ወደ ስደት ሲዳርግ ብዙሃኑን ደግሞ በተለያዩ የሃገሪቱ ትልልቅ ከተሞች ለልመና እንዲሰደዱ አድርጎአል ። በተለይም የገበሪው የዚህ አመት የምርት ሁኔት ማሽቆልቆል እና መንግስት በገበሬው ህዝብ ላይ የሚያሳርፈው ጫና ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ፣ምርቱን ማምረት ያልቻለው እና ያሉትን የቀንድ ከብቶችንም ለመሸጥ ወደ ከተማ የሚያጓጉዘው ገበሬ በፖሊሶች እየተነጠቀ ለጨረታ ሲቀርብበት ገበሬውን ለረሃብ እና ለከፍተኛ ችግር እንዲሁም ቤተሰቡን በየሜዳው ትቶ እንዲሄድ እያእረገው ነው ሲሉ ከአዲስ አበባ የተሰራጨው ሪፖርት ያመለክታል ።

ባሳለፍነው ሁለት ወራት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ምንስቴር የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን ገበሬው ክብቶቹን በወቅቱ ስላላጠጣ ነው ብለው በአደባባይ ዋሽተውት የነበረውን ዘገባ እንደገና መልስ ብለው እርዳታ ያሽናል ብለው የአለም መንግስታትን መማጸን የቻሉበት አጋጣሚ እንደነበር ቢታወስም የጉዳዩ ተያያዥነት የመጣው የኢትዮጵያ መንግስት ኦባማን እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎችን ለመቀበል ያቀረበውን በጀት እንዳይቆረጥበት ያዘጋጀው እቅድ ነሲሉ ይሄውም ከ8፣ሚሊዮን ኣሜሪካን ዶላር በላይ ለዚኢያ ስብሰባ የታቀደ አላማ ላይ እንዲውል ሃገሪቱ ለስብሰባው መበጀቷን ሪፖርቱ ያመለክታል ፤ ይህ በእንዲህ እንዳለ ፕረዚዳንት ኦባማ ለሶስት ቀን ጉብኝቱ ብቻ 2.4 ሚሊዮን ዶላር ብቻ የከፈለ ሲሆን ይህም ከሁለት መቶ አባል ሰራተኞቹ እና የአየር ሃይል አባላቶቹ ጭምር እና ፣የበረራ ቁጥጥር ክፍል የሚያደርጉትንም የሚጨምር እንደሆነ ገለጸዋ አብራርቶአል ሆኖም  ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ግን በአፍሪካ የኢኮኖሚ ደረጃ ብች ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ ሲሆን ይህን ያህል ወጭ የሚሸፍኑ ኣልሆኑ ይታወቃል በዚህ ጉዳይ ላይ ሃገሪቱ ከትርፍ ይልቅ በኪሳራ ልትንቀሳቀስ ትችላለች የሚለው ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ከመሆኑም በላይ መንግስት ለሃገሩ እና ለህዝቡ እንዲሁም  ለህልውናው ቸልተኛ በመሆኑ አስጊ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

Zone9 Bloggers Are Not Alone: More Ethiopian Citizens Face Terrorism Charges

September 24, 2015
by Tedla D. Tekle | GlobalVoices
Alongside the now-famous case of the Zone9 bloggers, there are so many detained Ethiopian bloggers, online activists and politicians, whose names are not yet on the map.
Zelalem, Yonatan, Bahiru and Abraham
Zelalem, Yonatan, Bahiru and Abraham. Photo used with permission from debirhan.com
Last year on July 8, 2014, Ethiopia detained a number of local opposition leaders, bloggers, online activists and concerned citizens. Some were released after four months of interrogation. However, ten were charged on October 31, 2014 under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation with having links to diaspora-based Ethiopian opposition groups such as Ginbot 7, applying to attend an online security training, and engaging in online activism. Three of the 10 defendants are not members of any political party but ordinary citizens who were arrested for applying to attend a course. These are Zelalem Workagenegu, Yonatan Wolde and  Bahiru Degu.
The controversial Anti-Terrorism Proclamation was adopted in July 2009. Ethiopian officials tend to defend the law by arguing that its controversial provisions were copied from the existing laws of countries such as the United Kingdom. Article 6 of the Proclamation, which has been used to curtail freedom of expression, provides that:
[w]hosoever publishes or causes the publication of a statement that is likely to be understood by some or all of the members of the public to whom it is published as a direct or indirect encouragement or other inducement to them to the commission or preparation or instigation of an act of terrorism [is subject to between 10 and 20 years in prison].
Zelalem, the first defendant, is a human rights activist who blogs at DeBirhan. Yonatan and Bahiru, who are best described as concerned citizens, had applied along with Zelalem for a social media and Internet security training that was brought to their knowledge by a US-based Ethiopian journalist. After an email from the Ethiopian journalist in the US was found in their possession, these young men were also arrested and later charged with applying for “a terror training” when in fact the training was about Internet safety and security.
Ethiopian court last month acquitted Abraham Solomon, detained for having connections with the first defendant Zelalem, along with four other opposition politicians namely Abraha Desta, an official of the opposition Arena Tigray Party and social media activist, Yeshiwas Assefa, council member of the Blue (Semayawi) Party, Daniel Shibeshi, official of the now defunct Unity for Democracy and Justice (UDJ) party and Habtamu Ayalew, former Public Relations Head of the defunct UDJ. However, until today they have not been released because the Prosecutor has reportedly appealed the decision.
An article by the Electronic Frontier Foundation shows the increasing attempts of silencing online activists and netizens in Ethiopia. The organisation called Ethiopia to:
Immediately free all journalists in prison, including the remaining Zone 9 bloggers, and relieve them of all charges for the “crime” of reporting the news.
End the prosecution of individuals for pursuing security training and using encryption technologies, and free Zelalem Workagegnehu, Yonatan Wolde, Abraham Solomon, and Bahiru Degu.
Cease and desist from using invasive surveillance technologies like FinFisher and Hacking Team’s Remote Control System to spy” on Ethiopian journalists, Diaspora, and opposition groups.
While Zone9 remains among Ethiopia’s best-known case of its kind, stories like that of Zelalem demonstrate that the issues these bloggers face extend far beyond a few individuals. The next court appearance of Zelalem, Yonatan and Bahiru is between November 7-9, 2015.

በወያኔ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የሰራዊት አመራሮችና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬ ተስፋፍቶል

September 24,2014
በወያኔ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የሰራዊት አመራሮችና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬ መስፋፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች አስረድተዋል:: የሕዝብን መብት እና በልማት ስም በፕሮፓጋንዳ በመደለል በስልጣን ላይ ያለው በወያኔው አመራሮችና እና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬው እየሰፋ መምጣቱን ለምድር ጦር ክፍል ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልፀው። ባለፉት አመታት በሰራዊት ውስጥ ወታደራዊ ደህንነቶች መሰግሰጋቸው ከሰራዊቱ ጥያቄዎች ጋር ተደምሮ በተለይ በምስራቅ ደቡብ እዝ እና በሰሜን እዝ ከፍተኛ የሆነ የውስጥ ውጥረት እንዳለና እንዲሁም በሰራዊቱ ውስጥ በየስብሰባው ሶማሊያ ስለዘመቱ ወታደሮች ማብራሪያ መጠየቁን ታውቋል::
በሰራዊት ውስጥ በወታደራዊ ደህንነት ቦታ የሚያገለግሉ ምንጮች እንዳሉት ሰራዊቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና ጥርጣሬ እየጨመረ የመጣው አሁንም በየእዙ የሚጠረጠሩ መኮንኖች እስራት እንደቀጠለ ተናግረዋል::ለሆዳቸው ያደሩ የሰራዊት አባላት ቢኖሩም ይህን ያህል አይደሉም የሚሉት ምንጮቹ ሰራዊቱ ግን በመፈራራት እና እርስ በርስ ጥርጣሬ ውስጥ እየተጓዘ እንደሆነ ገልጸዋል::በተለያዩ ግምገማዎች ከ10 የሰራዊቱ አባላት ሰባቱ በማስጠንቀቂያ መታለፋቸውን በራሱ በሰራዊት ውስጥ ያለው ችግር አንደኛው ገጽታ መሆኑም አውስተዋል::

Wednesday, September 23, 2015

የተናገሩት ከሚጠፋ… (በኤፍሬም ማዴቦ – ከአርበኞች መንደር)

September 23, 2015
በኤፍሬም ማዴቦ
ባለፈዉ መጣጥፌ “ቃል የእምነት ዕዳ ነዉ” ብዬ ጀምሬ “ቃላችን አይለወጥ” ብዬ ነበር የተለየኋችሁ። አለምክንያት አልነበረም እንዲህ ያልኳችሁ፤ በአንድ በኩለ ቃል መከበርም መከፈልም ያለበት ዕዳ ስለሆነ በሌላ በኩል ደግሞ ቀትር ላይ የገባዉን ቃል ሳይመሽ እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ የሚክድ ብዙ ቃላ አባይ ሰላለ ነዉ። አገሬን ከወያኔ አጸዳለሁ ብሎ ቃል የሚገባ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዕዳ አለበት። ዕዳዉ ደግሞ ገንዘብ ወይም ንብረት አይደለም። ቃሉን መጠበቅ ወይም ቃሉን ማክበር ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ደግሞም አንድ ሰዉ የተናገርዉን ቃል ሰብሮ የእምነት ባለዕዳ ከሚሆን ዕድሜ ልኩን የገንዘብ ባለዕዳ ቢሆን ይሻለዋል። የገንዘብ ዕዳ ቆይቶም ቢሆን ይከፈላል ወይም አበዳሪዉ ሊምረን ይችላል፤ የዕምነት ዕዳ ግን የማይሽር ጠባሳዉ እየቆረቆረን አብሮን ይኖራል እንጂ አይጠፋም። ማንም ሰዉ ለአገሬ ህይወቴን እሰጣለሁ ብሎ ቃል ሲገባ መሃላዉ ከህዝብና ከአገር ጋር ብቻ አይደለም፤ እንዳዉም የሰዉ ልጅ ቃል የሚገባዉ መጀመሪያ ከራሱ ጋር ነዉ። ለራሱ የገባዉን ቃል የማያከብርና ቃሌ ቃል ነዉ ብሎ የገዛ ራሱን የእምነት ዕዳ ያልከፈለ ሰዉ ለህዝብና ለአገር ቃል መግባት አይችልም። ዛሬ ወያኔን እናጥፋ ብሎ ካራ ጨብጦ አብሮኝ የቆመ ሰዉ ነገ ከወያኔ ጋር ሆኖ ካራዉን እኔዉ ላይ አዙሮ ባየዉ እሱ ቀድሞዉንም ካራ የጨበጠዉ ወያኔን ለማጥፋት ሳይሆን ስጋ ሊቆርጥብት ነዉና ብዙ አይገርመኝም። እንዲህ አይነቱን ለቁም ነገር ሲፈልጉት አልሰማ ብሎ ሆዱ ሲሞላለት ግን ሳይጠሩት አቤት የሚል ስጋ ወዳድ ሆዳም ደግሞ ኢትዮጵያ በየዘመኑ አፍርታለችና ብዙ ሊገርመን አይገባም። ከሰሞኑ ከምድረ ኤርትራ የነፈሰዉ ነፋስ ያስተማረን አንድ ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር እንዲህ አይነቱን ሞላ ጎደለ የሚባል የካራና የስጋ ጨዋታ ነዉ። አዎ! የካራ ጨወታ – ወዲህ ማዶ ስጋ ሊቆርጡበት ወዲያ ማዶም ስጋ ሊቆርጡበት።
“የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ” . . . ገዢዎቻችን በተለይ የዛሬዎቹ ቃል አባዮች እንደቆሻሻ ዕቃ መሬት ላይ ጣሉት እንጂ ቃል የዕምነት ዕዳ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ዘመን አይሽሬ የአገራችን አባባል ነዉ። አባቶቻችን የተናገሩትን ወይም ቃል ገብተዉ የተማማሉትን ነገር ከሚያጥፉ የወለዱትን ማጣት ይቀላቸዋል። እኛ ልጆቻቸዉ ግን ከዬት የመጣን ጉዶች አንደሆንን አላዉቅም ቃል አባይነታችን እኛን፤ ልጆቻቸንና አገራችንን ሲያጠፋ በአይናችን እያየን ቅር እንኳን አይለንም። “እመጣለሁ ብሎ ሰዉ እንዴት ይዋሻል፤ ማበል እንኳን አንቺን ምድር ያበላሻል” መሬት ላይ ጠብ የማይል ትክክለኛ አባባል ነዉ። አገራችን ኢትዮጵያ ትናንት እንሞትልሻለን ብለዉ ዛሬ በሚገድሏት ቃል አባይ ልጆቿ እየተበላሸች ነዉ። እነዚህ ቃልአባዮች የኢትዮጵያን የምድር ላይና የምድር ዉስጥ ኋብቷን አንጂ የገረጣዉን ፊቷን ማየት አይፈልጉም- አዎ ወያኔ የሚያየዉ ኃብትሽን፤ የሳዑዲዉ ሰዉ ወርቅሽን፤ ባዕድ ከበርቴዉ ለምለም መሬትሽን . . . ወይኔ ኢትዮጵያ ማን ይሆን የሚያየዉ የጠቆረዉ ፊትሽን፤ ማን ይሆን የሚያብሰዉ እምባሽን፤ እኮ ማን ይሆን የሚያቆመዉ መከራሺን . . . ማን ይሆን?. . . ማን ይሆን?
የዛሬዋ ኢትዮጵያ አንድ ትዉልድ ዉሸት ብቻ እየሰማ ያደገባት የዉሸት መዲና ሆናለች። ጳጳሱ፤ ቄሱና ፓስተሩ “እኔ መንገድ፤ አዉነትና ህይወትና ነኝ” ያለዉን የሰማዩን አምላካቸዉን ረስተዉ ለምድር ዉሸታሞች አደሩ። ሂዱና ዋሹ ሲባሉ ሄደዉ ዋሹ፤ እዉነትን በዉሸት አስተባብሉ ሲባሉ አስተባበሉ፤ በሀሰት መስክሩ ሲባሉ አፋቸዉን ሞልተዉ በሀሰት መሰከሩ። “ታላቁ መሪ” እየዋሸን ኖሮ እየዋሸን ሞተ። መታወቂያዉ ዉሸት ነዉና ሞቶም አልሞተም ተብሎ ተዋሸለት። ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር ምን ለምዳ ትመጣለች እንዲሉ ሌላ ሁሉ ቢቀር ዉሸትን ይፀየፋል ተብሎ የተነገረለት የዛሬዉ ጠ/ሚኒስቴር ጭራሽ “ታላቁን መሪ” እንደዋቢ እየጠቀሰ ስራዉ ሁሉ ዉሸት፤ ዉሸት፤ ዉሸት ብቻ ሆኖ ቀረ። የኢትዮጵያ ሬድዮ ሲከፈት ዉሸት ይናገራል፤ ሲዘጋ ደግሞ ነገ ስለሚዋሸዉ ዉሸት ያስባል። ጋዜጦች በስህተት አንኳን እዉነት አይጻፍባቸዉም። የኢቲቪ ዜና አንባቢ ተመስገን በየነ ግማሽ ሰዐት የዋሸዉን ዉሸት ለማካካስ ዜናዉን አንብቦ ሲጨርስ ለ15 ደቂቃ ጎንበስ ብሎ ይሰግዳል።
ለረጂም ግዜ ተማምነን ጀርባችንን የሰጠነዉ ሰዉ ለጠላት እጁን ሰጥቶ ጦርነት ሲያዉጅብን አንዳንዴ በትግሉ ዉስጥ ማንን አምነን ጀርባችንን እንደምንሰጠዉ ግራ ሊገባን ይችላል። ከሰሞኑ የሰማነዉ ዜና እንዲህ ግራ የሚያጋባ ዜና ነዉ። ሆኖም ሳንተማመን ትግል ብሎ ነገር የለምና የትግል ጓዶቻችንን ማመን ብርታት እንጂ ደካሞች እንደሚሉት ሞኝነት ወይም የዋህነት አይደለም። በጓዶቻችን ላይ ክህደት ፈጽመን ከምናሰቃያቸዉ እኛ ብንሰቃይ ይሻላል፤ ደግሞም ጓዶቻችንን ማመን አቅቶን በጥርጣሬ ተፋጥጠን ባለንበት ከምንረግጥ አንዳንዴ አዉቀንም ቢሆን ብንታለል ብዙ መንገድ መጓዝ እንችላለን። ትግል በተለይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ከሚያስተምረን ትምህርቶች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ሌሎች በኛ ላይ እምነት እንዲኖራቸዉ ከፈለግን እኛ አስቀድመን ልናምናቸዉ አንደሚገባን ነዉ። አለዚያ ሁለታችንም አንተማመንም። አለመተማመን ደግሞ ያጠፋፋናል እንጂ አንድ ቤት ዉስጥ አብሮ አያኖረንም። እንደኔ እንደኔ የወያኔን ስርዐት ደምስሰን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር የምናደርጋት እያንዳንዳችን ለትግል ጓዶቻችን የገባነዉን ቃል ሰብረን ረጂም ህይወት ከመኖር ቃላችንን አክብረን ዛሬዉኑ መሞትን ስንመርጥ ብቻ ነዉ። ወያኔ አንደ እሳት የሚፈራዉና በፍጹም የማያሸንፈዉ አንዲህ አይነቱን ከብረት የጠነከረ ጽኑ አቋማችንን ብቻ ነዉ። ለዚህ ነዉ እንዲህ አይነት ጽናት የሌላቸዉን ደካማ ግለሰቦች ፈልጎ እያማለለ ጽናታችንን የሚፈታተነዉ። ከሰሞኑ ለህዝብ ከመታገል ህዝብን መታገል መርጦ ከለየላቸዉ የህዝብ ጠላቶች ጋር የተቀላቀለዉ ሞላ አስገዶም ለዚህ ዉሳኔ የበቃዉ ህዝባዊዉ ትግል የሚፈልገዉ የአለማ ጽናት የሌለዉ ደካማ ግለሰብ ስለሆነ ብቻ ነዉ። ዉድ ኢትዮጵያዉያን ክህደት ትናንት ነበር፤ ዛሬ አለ፤ ነገም ይኖራል። ስለዚህ ክህደት ሊያስተምረን እንጂ በፍጹም ሊያስበረግገንና አንገታችንን ሊያሰደፋን አይገባም። ክህደትና ከሀዲዎችን እያሰላሰልን የምንኖር ከሆነ የበለጠ እንዲጎዱን ተጨማሪ ዕድል እንሰጣቸዋለን እንጂ ሌላ ምንም የምንፈይደዉ ፋይዳ የለም።
ሞላ አስገዶም እሱን የመሰሉ ደካማ ጓደኞቹን ከተቀላቀለ በኋላ መቀሌ፤ አዲስ አበባና አዳማ ዉስጥ ክህደቱን አስመልክቶ እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ሦስት ጋዜጣዊ መግለጫዎችን ሰጥቷል። እርግጠኛ ነኝ ይህ ቁርስ ላይ የተናገረዉን ምሳ ላይ የማያስታዉስ ግለሰብ በተያዘለት የጉብኝት ሰሌዳ መሠረት ዘጠኙን ክልሎች የሚዞር ከሆነ ዘጠኝ የተለያዩና እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ምክንያቶችን መደርደሩ አይቀርም። የወያኔ የመረጃና የደህንነት መ/ቤት ተብዬዉም ቢሆን ምን ያህል የዉሸትና የጉራ ቤት ለመሆኑ መረጃ ብሎ የለቀቃቸዉን ዉሸቶችና ቱልቱላዎች መጥቀሱ ይበቃል። ለምሳሌ የመረጃና ስለላ ድርጅቱ ከአንድ አመት በላይ ከሞላ አስገዶም ጋር በሚስጢር ይሰራ እንደነበር ተናግሯል። ይህ እዉነት ከሆነ የደምህት ታጋዮች በዚህ አንድ አመት ግዜ ዉስጥ በወያኔ ታጣቂዎችና ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ ለወሰዷቸዉ እርምጃዎች በተለይ እግር ኳስ ጨዋታ በመከታተል ላይ እንዳሉ ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር እንዳለ ለተደመሰሱት የኢትዮጵያ ወታደሮች ተጠያቂዉ ከሞላ አስገዶም ጋር ይሰራ የነበረዉ የወያኔ የመረጃና የስለላ ድርጅት ነዉ ማለት ነዉ።
ሞላ አስገዶም ትናንት ከኛ ጋር ሆኖ እኛ ሲል ነበር፤ ዛሬ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጠለቶች ጋር ሆኖ እኛ ይላል። ይህ ሰዉ “እኛ” ሲል የሱ እኛ እነማንን እንደሚያጠቃልል አይታወቅም፤ እሱ እራሱም የሚያዉቀዉ አይመስለኝም። ሞላ አስገዶም ወያኔን እንደተቀላቀለ አፉን ሞልቶ ጥምረቱን የፈጠርነዉ “እኛ” ነን ብሎ ሲናገር በተደጋጋሚ ተደምጧል። ጥምረቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎትና ህዝባዊ ትግሉ የደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዉጤት ነዉ እንጂ ሞላ አስገዶም ስለፈለገዉ የሚፈጠር አለዚያ የሚቀር የሞላ አስገዶም የቤት ዉስጥ ዕቃ አይደለም። ደግሞም እንደ ሞላ አስገዶም ፍላጎት ቢሆን ኖሮ የደምህት ጥምረቱ ዉስጥ መግባት ለግዜዉም ቢሆን ሊዘገይ ይችል ነበር። ደምህት ጥምረቱ ዉስጥ ገብቶ አገር አድን የጋራ ንቅናቄዉ የተፈጠረዉ የደምህት ሠራዊትና ከሞላ አስገዶም ዉጭ ሁሉም የደምህት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከሌሎች ኢትዮጳያዉያን ወገኖቻቸዉ ጋር ሆነዉ በጋራ ለመታገል በመወሰናቸዉ ነዉ። የሞላ አስገዶም ፈርጥጦ ወያኔ ጉያ ዉስጥ የመሸጎጡ ዋነኛዉ ምክንያትም የዚህ ዉሳኔ ዉጤት ነዉ እንጂ የወያኔ መረጃና ስለላ ድርጀት ሚስጥራዊ ግንኙነት ዉጤት አይደለም። ሌላዉ እርስ በርሱ የሚጋጭ የወያኔ ዉሸት – በአንድ በኩል ሞላ አስገዶምና የደምህት ሠራዊት ሙሉ ትጥቃቸዉን እንደታጠቁ ጠቅልለዉ ወደ አገራቸዉ ተመለሱ የሚለዉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቁጥሩ ወደ 700 የሚጠጋ የደምህት ሠራዊት ወደ አገሩ ተመለሰ የሚለዉ የተምታታ ዘገባ ነዉ። እዚህ ላይ የደምህትን ሠራዊት ብዛት መናገሩ አስፈላጊ ባይሆንም ግንዛቤ ማግኘት የፈለገ ሰዉ ግን ተመድ ያወጣቸዉን ሪፖርቶች መመልከቱ የሚበቃ ይመስለኛል። ደግሞም ሞላ አስገዶም አታልሎ መንገድ ካስጀመረዉ ሠራዊት ዉስጥ ገሚሱ ወደ ትግሉ ሜዳ ተመልሷል፤ የተቀረዉ ደግሞ ወደ ትግሉ ሜዳ ካልተመለስኩ እያለ ከሱዳን ባልስልጣኖች ጋር እየተደራደረ ነዉ። በነገራችን ላይ የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ ሞላ አስገዶም አታልሎ ሀምዳይት ከወሰዳቸዉ በኋላ ትግል ወይም ሞት ብለዉ ተመልሰዉ ከትግል ጓዶቻቸዉ ጋር ከተቀላቀሉ ጀግኖች ኢትዮጵያዉያን ጋር አብሮ ቡና ጠጥቷል።
ጓዜን ጠቅልዬ ትግሎ ሜዳ ከመግባቴ በፊትም ሆነ ከገባሁ በኋላ የደምህት ስም በተነሳ ቁጥር አብረዉ የሚነሱ ሁለት መላምቶች አሉ። አንደኛዉ መላምት ደምህት የኤርትራ መንግስት ሆን ብሎ የፈጠረዉና ጭራሽ ኤርትራ ዉስጥ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎችን ተክቶ በመንግስታዊ ተቋሞች ጥበቃና ደህንነት ስራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነዉ የሚል መላምት ሲሆን ሁለተኛዉ መላምት ደግሞ ሞላ አስገዶም በኤርትራ መንግስት ድጋፍ ሁለተኛዉ መለስ ዜናዊ ሆኖ ህወሃትን ተክቶ አትዮጵያን ይመራል የሚለዉ መላምት ነዉ። ደግነቱ የነዚህ መላምቶች የማዕዝን ራስ የሆነዉ ሞላ አስገዶም ኮብልሎ ወያኔን መቀላቀሉና ከተቀላቀለ በኋላ የሰጣቸዉ ጋዜጣዊ መግለጫዎች ሁለቱንም መላምቶች እንዳልነበሩ አድርጓቸዋል። እኔን አልገባ ያለኝና በጣም የሚገርመኝ ግን በአንድ በኩል የኤርትራ መንግስት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች ትብብር እንዲፈጥሩ አይፈልግም ይባላል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ጥምረቱ የተፈጠረዉ በሻዕቢያ ግፊት ነዉ ይባላል። መቼም ገና በልጅነቴ ካልጃጀሁ በቀር ሻዕቢያና የኤርትራ መንግስት መሃል ልዩነት ያለ አይመስለኝም። ሌላዉ የሰሞኑ አስቂኝ ድራማ ደግሞ ሞላ አስገዶም ጥምረቱን የፈጠርነዉ እኛ ነን ሲል የሱን መኮብለል አስመልክቶ የሚሰጠዉ አስተያያት ደግሞ ሞላ አስገዶም ጨርቁን ጠቅልሎ ወያኔን የተቀላቀለዉ ብርሀኑ ነጋ በኤርትራ መንግስት ግፊት የጥምረቱ ሊ/መንበር መሆኑ አልዋጥ ብሎት ነዉ ይባላል።
ሌላዉ አሁን በቅርቡ ወይም ከሞላ አስገዶም መኮብለል በኋላ የተጠነሰሰዉ መላምት ደግሞ ደምህቶች እራሳቸዉ ኤርትራ ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ድርጅቶች በወያኔ ስርዐት ላይ ወታደራዊ እርምጃ መዉሰድ እንዳይችሉ ሆን ተብለዉ በወያኔ የተፈጠሩ እንቅፋቶች ናቸዉ የሚለዉ መላምት ነዉ። በኔ ግምት ይህኛዉ መላምት ከሁሉም መላምቶች የከፋና እጅግ በጣም አደገኛ የሆነ ጽንፈኛ መላምት ነዉ። እንደዚህ መላምት ፈጣሪዎች አባባል የትግራይ ህዝብ በህወሃት አመራር በደል አይደርስበትም ወይም የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር ሆኖ የህወሃትን ግፈኛ ስርዐት አይታገልም ማለት ነዉ። እንዲህ አይነቱ ጭፍንነትና ጠባብነት የሚመነጨዉ ደግሞ ሞላ አስገዶምንና ደምህትን ወይም ህወሃትንና የትግራይን ህዝብ ለያይቶ ማየት ካለመቻል አባዜ ነዉ። በደርግ ስርዐት ዉስጥ ጭቆናዉና በደሉ በዛብኝ ብሎ ጠመንጃ ያነሳዉ ጀግናዉ የትግራይ ህዝብ ህወሃት ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ተነጥሎ እንዲታይ ለማድርግ የሚሸርብበትን ሤራና የሚያደርስበትን ግፍና መከራ አፉን ዘግቶ የሚቀበልበት ምንም ምክንያት የለም። ስለዚህ ደምህት የትግራይ ህዝብ ብሶትና ምሬት አምጦ የወለደዉ ፀረ ህወሃት ንቅናቄ ነዉ እንጂ ወያኔ የፈጠረዉ ድርጅት አይደለም፤ሊሆንም አይችልም። ሞላ አስገዶምም ቢሆን የራሱ የተጠረቃቀመ ድክመት ከንቅናቄዉ ሊ/መንበርነቱ እንደሚያስነሳዉ ሲያዉቅ የፈረጠጠ ፈርጣጭ እንጂ እሱና ወያኔ እንደሚሉት የአንድ አመት ቀርቶ የአንድ ወርም ተከታታይ ግንኙነት አልነበራቸዉም።
ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረከ ብቅ ብለዉ የጠፉትንም ሆነ ዛሬም ድረስ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች ባህልና ድርጅታዊ አሰራር ስንመለከት የድርጅቶች ህልዉና መመዘኛና የማንነታቸዉ መለኪያ ቆምንለት የሚሉት አላማ ሳይሆን የመሪዎቻቸዉ በተለይ የዋናዉ መሪ ተክለሰዉነት ነበር። የድርጅት ወይም የፓርቲ ሊ/መንበር ከድርጅቱ ባለይ ነዉ፤ እሱ ይሁን ያለዉ ይሆናል፤አይሁን ያለዉ አይሆንም። ብዙ ግዜ የድርጅት/ፓርቲ ሊ/መንበር ድርጅቱን የማፍረስ አቅም ጭምር አለዉ። ይህንን ደግሞ በቅርብ ግዜ ታሪካችን በተደጋጋሚ አይተናል። አንድን ድርጅት ወይም ፓርቲ አባላት ሲቀላቀሉ የሚመለከቱት የፓርቲዉን ሊ/መንበር እንጂ የፓርቲዉን የፖለቲካና የኤኮኖሚ ፕሮግራም አይደለም። የፓርቲ ሊ/መንበርም ቢሆን የኔ የሚላቸዉን ሰዎች ነበር እየመረጠ የሚያሰባስበዉ። እንደዚህ አይነቱ የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር አሁን እየተቀየረ የመጣ ቢሆንም ለረጂም ግዜ የፖለቲካ ትግላችን ችግር ሆኖ ቆይቷል። ሞላ አስገዶም በቅርቡ የደምህትን ሠራዊት ከነሙሉ ትጥቁ ይዤ ኢትዮጵያ ገባሁ ብሎ በድፍረት የተናገረዉ ንግግር ይሄዉ የድርጅት ሊ/መንበር ያሰኘዉን ሁሉ ማድረግ ይችላል የሚለዉ የቆየ የፖለቲካ ባህላችን በሽታ ተጠናዉቶት ነዉ። “ዝንጀሮዉን ከጫካ ያዉጡታል እንጂ ጫካዉን ከዝንጀሮዉ ዉስጥ አያወጡትም” የሚል ብህል አለ፤ ትክክለኛ ብህል ነዉ። ሞላ አስገዶም ህወሃት/ወያኔ የኢትዮጵን ህዝብ በአጥር እየለያየ በትናናንሽ ጎጆዎች ዉስጥ ማኖሩ አልዋጥ ብሎት ሁሉንም የሚያቅፍ ሰፊ ቤት ሰርተን ኢትዮጵያን የዲሞክራሲ አገር እናደርጋለን ብሎ ለብዙ አመታት የታገለ ሰዉ ነዉ። ችግሩ ሞላ አስገዶም ነዉ ከነዚያ ትናንሽ የወያኔ ጎጆዎች የወጣዉ እንጂ ትናንሽ ጎጆዎቹ ከሞላ አስገዶም ዉስጥ ስላልወጡ እንደ ማግኔት እየሳቡት ወደነበረበት ቦታ መልሰዉታል። ለሁሉም የሞላ አስገዶም ታሪክ ሲጻፍ – መጣና ሄደ ከሚሉ አምስት ሆሄያት የዘለለ ምንም ቁም ነገር የለዉም። እየመጡ መሄድና እየሄዱ መምጣት ደግሞ ትናንሽ ቤት የሚናፍቃቸዉ ትናንሽ ሰዎች እስካሉ ድረስ ይቀጥላል።
ሁለት ሺ ሰባት ሊጠናቀቅ ሦስት ቀን ሲቀረዉ አንድ የብዙ ኢትዮጵያዉያንን ጆሮ የሳበ ዜና ቴሌቪዥኑን፤ ሬድዮኑን፤ ጋዜጣዉንና ድረገጹን ተቆጣጠረዉ። ዜናዉ የወያኔ/ህወሃትን ስርዐት በመሳሪያ ኃይል የሚታገሉ አራት ድርጅቶች አገር አድን የጋራ ንቅናቄ ፈጠሩ የሚል የአዲስ አመት የምስራች ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብ ለረጂም ዘመን የናፈቀዉ የምስራች ነበር። ግን ምን ያደርጋል – በጥባጭ እያለ ንጹህ ዉኃ አይጠጣምና ይሀንን የአዲስ አመት የምስራች ሰምተን ሳናጣጥም ነበር የሞላ አስገዶምን ዜና ክህደት የሰማነዉ። አስደንጋጭ ዜና ነበር። በእርግጥም የአራት ድርጅቶች ጥምረት ተፈጠረ የሚል ዜና በተሰማ ማግስት የጥምረቱ ምክትል ሊ/መንበር ሠራዊት እየመራ ሄዶ ወያኔን ተቀላቀለ የሚል ዜና መስማት የሚያስደነግጥና በመጀመሪያዉ ዜና ላይ ቀዝቃዛ ዉኃ የቸለሰ ልብ ሰባሪ ዜና ነዉ። ደግነቱ ሁሉም ነገር ለበጎ ነዉ። የሞላ አስገዶም መክዳት ተራ ዜና ነዉ ማለቴ አይደለም። ግን ሞላ አስገዶምና የወያኔ መረጃ ድርጅት በትብብር ሠራነዉ ያሉት አዲስ ድራማ ተዉኔቱ ሳይጻፍ አየር በአየር የተከወነ ምናቡ ያልተባ ድራማ በመሆኑ ድራማዉ ከያኒዉን ሳይሆን የኢትዮጵያን ህዝብና ለአንድነቱና ለነጻነቱ የሚታገሉ ልጆቹን በከፍተኛ ደረጃ የጠቀመ መሆኑን ማሳዉቁ አስፈላጊ ይመስለኛል።
ደምህት በዚህ የወያኔ ድራማ ዉስጥ በእሳት ተፈትኖ ወርቅነቱን አረጋግጧል። ሞላ አስገዶም የደምህትን ሠራዊት ለወያኔ አስረከብኩ ብሎ በተናገረ ማግስት የደምህት መሪዎች የሰጡት አርቆ አስተዋይነት የታየበት አመራርና ያሳዩት ቆራጥነት የፖለቲካ ድርጅቶቻችን የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ በግልጽ አሳይቷል። ደምህት እራሱም እንደ አንድ የትግል ድርጅት የተደቀነበትን አደጋና ፈተና በጣጥሶ በመዉጣት በትናንሾችና በደካሞች ሴራ በፍጹም የማይናጋ ጠንካራ ድርጅት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። የዛሬዉ ደምህት ዉስጡን ከአድርባዮች ያፀዳ ሁለትና ሦስት እርምጃዎች ወደፊት የተራመደ ጠንካራ ድርጅት ነዉ። እርግጠኛ ነኝ ይህ የደምህት መሪዎች ያሳዩት አስተዋይነት፤ ጽናትና ቆራጥነት እኔ የምፈልገዉ ነገር ካልሆነ ድርጅቱን በአፍጢሙ እደፋዋለሁ ብለዉ ለሚያስቡ ዕብሪተኛ መሪዎች ጥሩ ትምህርት ነዉ። ሌላዉ የሞላ አስገዶም ክህደት በግልጽ ያሳየን ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረክ የሀዝብ መብትና ነጻነት ይከበር በሚሉ የነጻነት ሀይሎችና ህዝብን ረግጠን እንገዛለን በሚሉ ፀረ ህዘብ ሀይሎች ለሁለት መከፈሉን ነዉ። ወደድንም ጣላን ካሁን በኋላ ያለን አማራጭ ሁለት ብቻ ነዉ፤ ወይ ወያኔ ሆኖ ከህዝብ ጋራ መዋጋት ወይም ከህዘብ ጋር ሆኖ ወያኔንና ስርዐቱን መዋጋት። ሞላ አስገዶም ጎራዉን ለይቷል፤ እኛም ጎራችንን እንለይ። መኃል ቆሞ መመልከት አብቅቷል።
ጠላቴን አግዝፌ መመልከት አልወድም፤ ትንሽ ነዉ ብዬም ጠላቴን በፍጹም አልንቅም። በቅርቡ የወያኔ የመረጃና ደህንነት መ/ቤትና ሞላ አስገዶም ከአንድ አመት በላይ አብረን ሠራን ያሉትን የጀማሪዎች ስራ ስምለከት ግን ወያኔ/ህወሃት “የምትሰሩትን ብቻ ሳይሆን የምታስቡትን ጭምር የሚያይ አይን አለኝ” እያለ የኢትዮጵያን ህዝብ ከማስፈራራት ዉጭ የረቀቀ የመረጃ ስራ መስራት ቀርቶ አረፍተነገሮችን አገጣጥሞ ለጆሮ የሚጥም ንግግር ማድረግ የሚችል አዋቂ የሌለበት የባዶዎች ድርጅት መሆኑን ነዉ የተረዳሁት። ሞላ አስገዶምም በወዶገባነት ሄዶ የተቀላቀለዉ ይህንኑ አዋቂ የሌለበትን እሱን የመሰለ ድርጅት ነዉ። ይህንን ደግሞ እስከዛሬ በሰጣቸዉ ቃለመጠይቆች በግልጽ አይተናል። ህወሃት/ወያኔን እስከዛሬ በሥልጣን ላይ ያቆዩት ሁለት ነገሮች ቢኖሩ አንዱ ጠመንጃ ሁለተኛዉ የኛ የነጻነት ኃይሎች መበታተን ብቻ ነዉ።
ነገ የምንፈልጋት ኢትዮጵያ እንደ መኪና ተገጣጥማ አትጠብቀንም – የዛሬዉ ጥረታችንና ድካማችን ዉጤት ናት። ኢትዮጵያና ህዝቧ ከወያኔ ሲፀዱ የሚነፍሰዉ የነጻነት አየር ሁላችንንም ቢያስደስትም ደስታዉ የሚገለጸዉ በግለሰብ ደረጃ ነዉ። ዛሬ ከጠላት ጋር ተፋልመን የተቀማነዉን ነፃነት ማስመለስና እንደገና እንዳንቀማ ነቅቶ መጠበቅ ግን የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት ነዉ። እንግዲህ ወገን ወገባችንን ጠበቅ የምናደርግበት ግዜ አሁን ነዉና ሁላችንም በየተሰለፍንበት መስክ እንበርታ። ጠላታችን ጠንካራ መስሎ የሚታየዉና ያለ የሌለ ጡንቻዉን የሚያሳርፍብን የማይቀረዉን ድል ማሽተት ስንጀምር ነዉ። የድል መአዛችንን የምናሸትበት ግዜ ደግሞ ሩቅ እንዳይመስለን ነገና ከነገ ወዲያ ነዉ። ከወላዋይና እዚህም እዚያም እየዘለለ ከሚያዘናጋን አጉል ጓደኛ አንዱኑ የለየለት ጠላት ይሻላልና የሞላ አስገዶም ክህደት ትግላችንን ሊያጠራዉና መንገዳችንንም ሊያሳጥረዉ ይገባል እንጂ በፍጹም ግራ ሊያጋባን አይገባም። አይዞን. . . ሞኝ ከዘመዱ ከሚያገኝዉ ጥቅም አዋቂ ከጠላቱ የሚያገኘዉ ጥቅም ይበልጣልና ጠላቶቻችን የፈጠሩልንን አጋጣሚዎች ሁሉ በሚገባ እንጠቀምባቸዉ እንጂ ለጠላት አንመቻች። ጠላታችን እየተሳሳተልን ነዉ፤ ጠላት ሲሳሳት ማቋረጥ ነዉር ነዉ። ቸር ይግጠመን!!!
አፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር ebini23@yahoo.com

በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል የሕወሃት/ብአዴን ታጣቂዎች 2 ነዋሪዎችን ገደሉ፣ ከ50 በላይ አቆሰሉ

September 23,2015

picture

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ሕወሃት) የፈጠረው የብአዴን ታጣቂዎች በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል ሁለት ነዋሪዎችን መግደላቸው፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው እንዲሁም ከሃምሳ በላይ ማቁሰላቸው ተሰማ።
የብአዴን አባላት እና መሪዎች የዐማራን ሕዝብ እያሰቃዩ እና እያስፈጁ የሚያካብቱት ማንኛውም ሃብት በክህደትና በግፍ የተሰበሰበ በመሆኑ ለህዝብ የሚያስረክቡበት ግዜ ሩቅ አይደለም።
pictureለዚህ የክህደት ተግባራችው ተገቢውን ቅጣት ያገኛሉ፣ በባህርዳር እና በጎንደር በሰፊው እየተሳሳቡ አገር እየዘረፋ መሆኑን እያንዳንዷንም ተግባራቸውንም እየተከታተልን ዝርዝር ይፋ እናደርጋለን።
እነኝህ ስግብግቦች በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት፣ የሕወሃት ብአዴን ታጣቂዎች ሁለት ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአምሳ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል። (ምንጭ፦ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት Dr.Getachew Reda ጠቅሶ መስከረም ፱ ቀን ፪ሺህ፰ ዓም የላከው መረጃ)