Sunday, February 8, 2015

ለወያኔ ዉንብድና መልሱ ህዝባዊ እምቢተኝነትና ህዝባዊ አመጽ ነዉ!

February 8,2015
pg7-logoዘረኞቹ የወያኔ መሪዎ የኢትዮጵያን በትረ ስልጣን ጨብጠዉ በኖሩባቸዉ ባለፉት ሃያ አራት አመታት የአገራችን የኢትዮጵያን የፖለቲካ መድረክ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እጅግ በጣም ከዘቀጠና ከረከሰ የወያኔ ድራማ ዉጭ ሌላ ምንም ነገር የማይታይበት አለባሌ መድረክ አድረገዉት ቆይተዋል አሁንም እያደረጉት ነዉ። አንድ ቋንቋ የሚናገሩትና ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸዉ የወያኔ መሪዎች ኢህአዴግ የሚባል አጋሰስ የሽፋን ድርጅት ፈጥረዉ በኢትዮጵያ ህዝብ ሰብዓዊ መብትና ነጻነትና ላይ ተነግሮም ተጽፎም የማያልቅ ግዙፍ ግፍና በደል ፈጽመዋል። ህጻን፤አዛዉንት፤ ወንድና ሴት ሳይለዩ መብቴን አትንኩ ያለቸዉን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያለምንም ርህራሄ በጥይት ጨፍጭፈዋል። ሴቶች እሀቶቻችንን እጅና እግራቸዉን አስረዉ ጡታቸዉን በመቆንጠጫ እየቆነጠጡ በሴትነታቸዉ ላይ የዉርደት ተግባር ፈጽመዋል። ወንዶች ወንድሞቻችንን ደግሞ ዉስጥ እግራቸዉን ገልብጠዉ እየገረፉ ጥፍራቸዉን አይናቸዉ እያየ በጉጠት እየሳቡ ነቅለዋል። ባጠቃላይ የወያኔ ዘረኞች በዛሬዉ ዘመን አንኳን ወገን በወገኑ ላይ የዉጭ ጠላትም በህዝብ ላይ የማይፈጽመዉ በደል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ፍጽመዋል።
ወያኔ ስልጣን እንደያዘ “አባይ ትግራይ” ወይም “ታላቋ ትግራይ” የሚለዉን ህልሙን ለማሳካት ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ቆርሶ ከትግራይ ጋር ቀላቅሏል። ስልጣን ይዞ ከተደላደለ ከአመታት በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፈናቅሎ ለምለም መሬቱን በርካሽ ዋጋ ለባዕዳን ሽጧል፤ ከዚህ አልፎ ተርፎም የአባቶቻችን አጽም ያረፈበትን የአገራችን ዳር ድንበር ቆርሶ ለጎረቤት አገር ገጸ በረከት አቅርቧል። ይህ አገራቸዉንና የሚመሩትን ህዝብ በሚጠሉ ጠባቦች የተሞላ ድርጀት ባለፈዉ ሳምንት የኢትዮጵያን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ደጋፊዎቹንና በአንቀልባ ታዝለዉ አስከዛሬ ያቆዩትን ምዕራባዉያን ጭምር ግራ ያጋባ ፀረ አገርና ፀረ ህዝብ እርምጃ ወስዷል። ድርጅት እያፈረሰና በፓርቲ ላይ የራሱን ተለጣፊ ፓርቲ እያቋቋመ ዛሬ ላይ የደረሰዉ ወያኔ ምርጫ የሚባል ድራማ በደረሰ ቁጥር የሚይዘዉ በሽታ ዘንድሮም ይዞት አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲንና መላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅትን አፍርሶ በምትካቸዉ የራሱን መኢአድና የራሱን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ፈጥሯል። ይህ ወያኔ ከሰሞኑ የወሰደዉ የፖለቲካ እርምጃ በየትኛዉም አለም በተለይ የመድበለ ፓርቲ የፖለቲካ ስርዐትን እንከተላለን በሚሉ አገሮች ዉስጥ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ እጅግ በጣም ትልቅ የፖለቲካ ሸፍጥ ነዉ።
የወያኔን ታሪክ ተወልዶ ካደገበት ከደደቢት በረሃ እስከ ሚኒልክ ቤ/መንግስት ድረስ ያደረገዉን ጉዞ ስንመለከት ወለል ብሎ የሚታየን አንድ ሐቅ አለ፤ እሱም ወያኔ ሁሉንም ነገር በዘር መነጽር ብቻ የሚመለከትና ህዝብን በወዳጅና በጠላት ጎራ ለይቶ ወዳጅ አይደለም ያለዉን ሁሉ እንደ ሩሲያዊዉ ዮሴፍ ስታሊን እየገደለ የመጣ ድርጅት ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ጫካ ዉስጥ እያለም ሆነ ዛሬ ከተማ ገብቶ የሚቃወመዉንና በሀሳብ የማይግባባዉን ድርጅትም ሆነ ግለሰብ እያፈረሰና እገደለ ባፈረሳቸዉ ድርጅቶች ምትክ ደግሞ የራሱን ተለጣፊ ድርጅት እየፈጠረ የመጣና ከዲሞክራሲያዊ አሠራርና ከስልጣኔ ጋር የማይተዋቅ ድርጅት ነዉ።
በመርፌ የተጠቃቀመ ቁምጣና ጥብቆ ለብሶ አስራ ሰባት አመት ጫካ ለጫካ የተጓዘዉ ወያኔ ጎንደር፤ ጎጃምና አምቦ እያለ ወደ አዲስ አበባ ሲጠጋ ከተገነዘባቸዉ ነገሮች አንዱ የለበሰዉ የተጠቃቀመ ቁምጣ የትም እንደማያደርሰዉና ለከተማ ኑሮ የሚስማማ አዲስ ልብስ እንደሚያሰፈልገዉ ማዉቁ ነዉ። በጥላቻ ተረግዞ በክፋት ላደገዉ ወያኔ ቢበቃዉም ባይበቃዉም ወይም ቢያምርበትም ባያምርበትም ይህንን ለከተማ ዉስጥ ኑሮ የሚያስፈልገዉን አዲስ ልብስ ለማዘጋጀት ብዙ ግዜ እልወሰደበትም። የሚሰርቅና የሚስቅ ምን ግዜም ተባባሪ አያጣም እንዲሉ ወያኔ የአዲስ አበባን መሬት የረገጠዉ ጦር ሜዳ ላይ የማረካቸዉን ወታደሮችና አገር ዉስጥ ያገኛቸዉን ደካማ ሰዎች ሰብስቦ በፈጠረዉ ኢህአዴግ በሚባል ፈረስ ጀርባ ላይ ተፈናጥጦ ነበር። ትግራይን ነጻ አወጣለሁ ብሎ ትግል የጀመረዉ ወያኔ ኢህአዴግን የፈጠረዉ ወያኔነቱን ለመተዉ ሳይሆን እራሱን በዚህ በኢትዮጵያ ስም በፈጠረዉ ድርጅት ዉስጥ ሸሽጎ እዉነተኛ ባህሪዩን ለመደበቅ ነበር።
ከግንቦት 1983 ዓም አስከ ግንቦት 1987 ዓም ድረስ የዘለቀዉንና በወያኔ የበላይነት ተጀምሮ ወያኔን በማንገስ የተጠናቀቀዉን የሽግግር መንግስት ወደ ኋላ መለስ ብሎ የቃኘ ማንም ሰዉ የወያኔን ሁለት ዋና ዋና መሠሪ ስራዎች በቀላሉ መመልከት ይችላል።
አንደኛ- ኦነግንና የደቡብ ህዝብ ንቅናቄን ጨምሮ አያሌ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና ታዋቂ ግለሰቦችን አቅፎ ስራዉን የጀመረዉ የሽግግሩ መንግስት የስራ ዘመን የተገባደደዉ የኢትዮጵያን አንድነት ጥያቄ ያነሱ ግለሰቦችን በማሰርና ከወያኔ ቁጥጥር ዉጭ እራሳቸዉን ችለዉ ለመንቀሳቀስ የሞከሩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ከሽግግሩ መንግስት በማባረር ነበር።
ሁለተኛ- ወያኔ የኋላ ኋላ እያደር ለመስራት ላቀዳቸዉ አገር የመበተንና ህዝብን የመለያየት ስራዎች እንዲያመቸዉ ከእያንዳንዱ የፖለቲካ ድርጅት ጀርባ የኢትዮጵያ ህዝብ ተለጣፊ እያለ የሚጠራቸዉን ድርጅቶች በራሱ አምሳል እየፈጠረ ማሰማራቱ ነዉ።
ባጠቃላይ ወያኔ የፈጠረዉ የሽግግር መንግስት ኢትዮጵያዊ አጀንዳና አገራዊ ራዕይ ይዘዉ የተንቀሳቀሱ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን አጥፍቶ ወያኔን ዘለአለማዊ ንጉስ ለማደረግ ከመሞከሩ ዉጭ ሌላ ምንም ኢትዮጵያን የሚጠቅም ስራ አልሰራም።
ከሽግግሩ መንግስት በኋላ ወያኔ ተወዳዳሪዉም አሸናፊዉም እሱ ብቻ የሆነባቸዉን ሁለት ትርጉም የለሽ ምርጫዎችን አካሂዷል።እነዚህን ተወዳዳሪ የለለባቸዉን ሁለት ምርጫዎች በቀላሉ በማሸነፉ ህዝብ የወደደዉ መስሎት ልቡ ያበጠዉ ወያኔ ሦስተኛዉን አገራዊ ምርጫ ከመጀመሪያዎቹ ሁለት ምርጫዎች በተለየ መልኩ ለቀቅ አድርጎ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ፤ መራጩን ህዝብ መቅረብ እንዲችሉና ወያኔን እራሱን ምርጫዉን አስመልክቶ ክርክር እንዲገጥሙት በሩን ከፈተላቸዉ። ነገሩ “የማይነጋ መስሏት” እንዲሉ ሆነና ሜዳዉም ፈረሱም ይሄዉና ብሎ የፊልሚያዉን ሜዳ የከፈተዉ ወያኔ የምርጫዉ ቀን ደርሶ በዝረራ መሸነፉን ሲሰማ በራሱ ሜዳና በራሱ ዳኞች ፍት ያሸነፉትን የህዝብ ተመራጮች ከየመኖሪያ ቤታቸዉ እያደነ አስሮ በአገር ክህደት ወንጀል ከሰሳቸዉ ። የሚገርመዉ ወያኔ በምርጫዉ ተወዳድረዉ በምስክር ፊት በአደባባይ ያሸነፉትን የህዝብ ተመራጮች በማሰር ብቻ አልተወሰነም። በወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ አይኑ ብሌን ይመለከተዉ የነበረዉን ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲን አፍርሶ እንደለመደዉ የራሱን ቅንጅት ፓርቲ ፈጥሮ ይበጃል ብሎ ላሰባቸዉ ደካማና ሆዳም ግለሰቦች አስረክቧል።
ይህ ቆየት ያለ በሽታዉ ዘንድሮም አገርሽቶበት አንድነትንና መኢአድን ለክፏቸዋል። ይህ ወያኔ ከሰሞኑ መኢአድና አንድነት ላይ የወሰደዉ እርምጃ እነዚህ ሁለት ፓርቲዎች በመጪዉ ምርጫ ላይ ያሸንፉኛል ከሚል ፍራቻ አይደለም። ወያኔ ምርጫዉ የሚካሄድበት ሂደት ብቻ ሳይሆን ህዝብ የሰጠዉ ድምጽ የሚቆጠርበትና የምርጫዉ ዉጤት ለህዝብ የሚገለጽበት መንገድ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ስር እንደሆነና ይህንን ምርጫ ብቻ ሳይሆን የሚቀጥለዉንም ምርጫ ከሱ ዉጭ ሌላ ማንም እንደማያሸንፍ በሚገባ ያዉቃል። ወያኔ መኢአድንና አንድነትን የጥቃቱ ሰለባ ያደረጋቸዉ ህዝባዊ አላማቸዉንና አገራዊ ራዕያቸዉን በተለይ እነዚህ ሁለት ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ፤ አንድነትና እኩልነት ጥያቄ ላይ ያላቸዉን የጠራና የማያወላዉል አቋም እጅግ በጣም ስሚጠላ ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ወያኔ እንዲህ በአጭር ግዜ ዉስጥ መኢአድንና አንድነትን የጨፈለቃቸዉ እነዚህ ሁለት አንጋፋ ፓርቲዎች አዲስ አበባን ጨምሮ በየክልሉ የዘረጉት መዋቅርና ከህዘብ ጋር የፈጠሩት የቅርብ ግኑኝነት እንቅልፍ ስለነሳዉ ነዉ። ሌላዉ በፍጹም መርሳት የሌለብን ነገር ቢኖር ይዋል ይደር እንጂ ወያኔ እኛ ቀድመን ካላጠፋነዉ በቀር “ኢትዮጵያዊነት” ፤ “አንድነት” ወይም ፍትህና ነጻነት ብሎ የተነሳን ማንንም ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ወይም ድርጅት ማጥፋቱ አይቀርም። በእርግጥም ከትናንት ወዲያ ቅንጀትን፤ ዛሬ ደግሞ መኢአድንና አንድነትን አፍርሶ የራሱን ተለጣፊ አሻንጉሊቶች የፈጠረዉ ወያኔ ነገ እነዚህ ፓርቲዎች የቆሙለትን አላማ የተሸከምነዉን ኢትዮጵያዉያን አንድና ሁለት እያለ ለቃቅሞ እንደሚያጠፋን ምንም ጥርጥር የለዉም።
ወያኔ አምስት አመት አየቆየ በሚመጣዉ የምርጫ ድርማ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ እንደማይወርድ በ1997 ዓም ሰኔ ወርና በ 1998 ዓም ህዳር ወር በአዲስ አበባ አደባባዮች ላይ በወሰደዉ ፋሺስታዊ እርምጃ በግልጽ አሳይቶናል።ከላይ ከፍ ሲል ለመግለጽ አንደተሞከረዉ ወያኔ ፊታችን ላይ ባለዉ በ2007ቱ ምርጫ ወይም በተከታታይ በሚመጡት ምርጫዎች ተሸንፌ ከስልጣን እወርዳለሁ የሚል ምንም አይት ስጋት የለበትም፤ ምክንያቱም በምርጫዉ ጨዋታ ዉስጥ ተጫዋቹም ፤ ሜዳዉም ዳኛዉም ወያኔ ብቻ ነዉ። ዛሬ የወያኔን መሪዎች ያንቀጠቀጣቸዉና እንዳበደ ዉሻ ያገኙትን ሁሉ እንዲነክሱ ያደረጋቸዉ አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ በተግባራዊ ስራዎች ላይ መናበብ በመጀመሩና በህዝባዊ እምቢተኝነቱና በህዝባዊ አመጹ ዘርፍ የሚደረገዉ እንቅስቃሴ ህዝባዊ ሙቀት አግኝቶ እየተጋጋለ በመምጣቱ ነዉ። ወያኔዎች እነሱንና የገነቡትን ዘረኛ ስርዐት ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርጎ የሚያጠፋዉ የህዝባዊ አመጹና የህዝባዊ እምቢተኝነቱ ጎርፍ መሆኑን ካወቁ ቆይተዋል። ይህ ከሰሞኑ በማሰር፤ በመደብደብና ድርጅት በማፍረስ የወሰዷቸዉ እርምጃዎች የሚያሳዩን ወያኔዎች ህዝባዊ ጎርፉን ቢቻል ለማጥፋት አለዚያም ጉዳት በማያደርስ መልኩ ለመገደብ ያሚያደርጉትን ከንቱ ሙከራ ነዉ።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፤ የኢትዮጵያ ወጣት፤ ገበሬና ሰራተኛ ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ትናንት ቅንጅትን አፍርሶ የራሱን መናኛ ቅንጅት የፈጠረዉ ወያኔ ዛሬም እንደገና አሉ የሚባሉትንና አገራዊ ራዕይ ይዘዉ የሚንቀሳቀሱትን አንድነትንና መኢአድን አፍርሶ በምትካቸዉ እንደጌኛ ፈረስ የሚጋልብባቸዉን የራሱን ሁለት መናኛ ፓርቲዎች ፈጥሮ መኢአድና አንድነት ብሎ ሰይሟቸዋል። ይህ በዋና ዋናዎቹ ዘረኛ የወያኔ ባለስልጣኖች ተጠንቶ በጥንቃቄ የተወሰደዉ እርምጃ ፓርቲዎቹ ህግ ስላላከበሩ ነዉ የሚል ሽፋን ይሰጠዉ እንጂ የምርጫ ቦርዱ ሊ/መንበር ሳያስቡት ከአፋቸዉ አፈትልኮ የወጣዉ እዉነት በግልጽ እንዳስቀመጠዉ ከምርጫዉ ጨዋታ ወጥተዉ እንዲፈርሱ በተደረጉት አንድነትና መኢአድ ፓርቲና ወያኔ በተለጣፊነት ባስጠጋቸዉ ሁለቱ ተለጣፊ ፓርቲዎች መካከል ያለዉ ልዩነት አንዱ ቆሜለታለሁ ለሚለዉ ህዝብ የሚታዘዝ ህዝባዊ ሌላዉ ደግሞ ሆዱን ለሚሞላለት ወያኔ የሚታዘዝ ሆዳም መሆናቸዉ ብቻ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ወያኔ መብቴን ብለህ ስትጮህ በጥይት እየጨፈጨፈህ ነጻነት ስትለዉ በዱላ እየደበደበህና ሰላማዊ ሰልፍ ስትወጣ ደግሞ አፍሶ እያሰረህና ዉስጥ እግርህን ገልብጦ እየገረፈህ በሰላማዊ መንገድ የምታደርገዉን ትግል ምርጫ አሳጥቶሃል። ሆኖም ግልጽ በሆነ መንገድ እንነጋገር ከተባለ ወያኔ የትግል አማራጭ አያሳጣህም፤ ሊያሳጣህም አይችልም። ወያኔ እሱ እራሱ ህግ በሆነበት አገር ህጋዊ ወይም ሠላማዊ ትግል ብሎ ነገር ዋጋ ቢስ አንደሆነ ሁላችንም የተረዳን ይመስላል። ትግላችን ህዝባዊ እምቢተኝነት ነዉና ከዛሬ በኋላ ወያኔን ጥያቄ አንጠይቀዉም፤ አድርጉ የሚለንን አናደርግም፤ ሁኑ የሚለንንም አንሆንም። ትግላችን ህዝባዊ አመጽ ነዉና ከዛሬ በኋላ ወያኔ ሲገድለን እኛም እየገደልነዉ እንሞታለን እንጂ አንገታችንን ደፍተን የእሳት እራት አንሆንም። አዎ! ት ግላችን እምቢ ማለት ወይም ህዝባዊ እምቢተኝነት ነዉ፤ ትግላችን በወያኔ ላይ ማመጽ ወይም ህዝባዊ አመጽ ነዉ።

Saturday, February 7, 2015

ኢህአዴግ በጋራ ንቅናቄው መንበርከኩን አመነ!

February 7,2015
“አሜሪካ በህወሃት/ኢህአዴግ ላይ ፖሊሲዋን ልትቀይር ይገባታል”
obang metho1


* ኢንቨስተሮች “የደም ከፈን” ላለመግዛት ወሰኑ

በኦሞ ሸለቆ ድሆችን ከመሬታቸው በማባረር የሚያመርተውን ጥጥ ወደ ውጭ ለመላክ ከስምምነት ደርሶ የነበረው ኢህአዴግ ባለፈው ሰሞን ያልጠበቀው ምላሽ ደርሶታል፡፡ ምላሹን ተከትሎ የጥጥ ግብይቱ የጨነገፈው በአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) መሆኑን በገሃድ አመነ፡፡ በኢህአዴግ ስትራቴጂክ በሆኑ ቁልፍ አካሄዶች ላይ አስቀድሞ የመልስ ምት በመምታት ፈተናው ውስጥ የከተታቸው አኢጋን እና መሪው ኦባንግ ሜቶ መዋቅራቸው ሊገኝ አለመቻሉ ኢህዴግን እንዳስጨነቀው ተሰማ፡፡ ኦባንግ ሜቶ በሰማሁት ተዝናንቻለሁ ብለዋል፡፡ በዛሬው ዕለት አቶ ኦባንግ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ አሜሪካ መከተል የሚገባትን አካሄድ በመዘርዘር ለፕሬዚዳንት ኦባማ ፖሊሲ ሊያስቀይር የሚችል ደብዳቤ ልከዋል፡፡
ኢህአዴግ ነዋሪዎችን እያፈናቀለ በቦታቸው ላይ ጥጥ እያበቀለና ጨርቅ እየሰፋ ለምዕራባዊ ኩባንያዎች ለመቸርቸር የገባውን ውለታ ያጠፉበት ሁለቱ ኩባንያዎች ዓለምአቀፋዊው የስዊድን ጨርቃ ጨርቅ ሻጭ ኤች ኤንድ ኤምና የጀርመኑ ቼቦ ናቸው፡፡ ባለሃብቶቹ ከኦሞ ሸለቆ ሰብዓዊ መብታቸው እየተገፈፈ መሬታቸው በተነጠቀባቸው ዜጎች መኖሪያ ላይ ጥጥ ተመርቶ የሚፈበረከው ጨርቃጨርቅ “የደም ከፈን” አድርገው በመቁጠር ስምምነታቸውን መሰረዛቸውንና ውሉ መጨናገፉን ያመኑት የኢህአዴግ ጨርቃ ጨርቅ ተቋም የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ባንተ ይሁን ገሠሠ ለሪፖርተር ባለፈው ሰሞን በተናገሩበት ወቅት ነው፡፡
“የሰብዓዊ መብት አቀንቃኝ ነን ባዮች” በማለት የንግድ ስምምነቱ ውል ቀለሙ ሳይደርቅ፤ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ድርጅት በጉዳዩ ላይ ሃሳብ ሳይሰጥ፣ በተቋም ደረጃም ይሁን በፖለቲካ ፓርቲ መግለጫ ሳይሰጥበት፣ በአገር ውስጥም ይሁን በተለይ በውጭ የሚገኙ “አክቲቪስቶች” ድምጻቸውን ሳያሰሙበት ጉዳዩን የራሱ አድርጎ በቀጥታ ለኤች ኤንድ ኤምና ለዋና ሥራ አስፈጻሚው “የደም ከፈን” በማለት ኩባንያው ራሱን ከዚህ ዓይነት እርም የተላበሰ ስምምነት እንዲያጸዳ ማስጠንቀቂያ የላከው አቶ ኦባንግ የሚመሩት አኢጋን ነበር፡፡
ይኸው በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ጥቁሩ ሰው” ተፈርሞ የተበተነው የማስጠንቀቂ ደብዳቤ ቅድሚያ የተዘገበውም በዚሁ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ነበር፡፡ ይህ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ኤች ኤንድ ኤም ሲደርሰው በወቅቱ “በመልካም የንግድ ተግባር” ዓለምአቀፋዊ ሽልማት በዋሽንግተን ዲሲ የሚቀበልበት ወቅት ላይ ነበር፡፡ በወቅቱ የጋራ ንቅናቄው ለኤች ኤንድ ኤም ከጻፈው ደብዳቤ በተጨማሪ ከጀርመኑ ቼቦ ጋር ቀጥተኛ ባልሆኑ መንገዶች በመነጋገርና ተጽዕኖ በማድረግ የፈረመውን ውል በአንክሮ እንዲከታተል ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰው አድርጎ እንደነበር የጋራ ንቅናቄው ለጎልጉል አስታውቋል፡፡
የኢህአዴጉ ሹመኛ ለሪፖርተር ቃላቸውን ሲሰጡ ስም አይጥሩ እንጂ “ነን ባዮች” ሲሉ የገለጹት በቅድሚያ አቶ ኦባንግ የሚመሩትን አኢጋን ስለመሆኑ ጥርጥር እንደሌለ ከአዲስ አበባ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አመልክቷል፡፡ ከዚሁ አዲስ አበባ የተገኘው መረጃ እንደሚመለክተው አቶ ኦባንግ በኢህአዴግ ቁልፍ አካሄዶች ላይ አስቀድመው መረጃ በማውጣትና በማጋለጥ “ደንቃራ” እንደሆኑባቸው ታውቋል፡፡
ለኢህአዴግ ከሚያገለግሉ ቁልፍ ሰዎች መካከል የተገኘ መረጃ እንደሆነ በመጥቀስ እንደተጠቆመው ኢህአዴግ የአቶ ኦባንግን እና አኢጋንን አሠራር እንዲሁም ያለውን የግንኙነት ደረጃ በተጨባጭ ለመሰለል እንዳቃተው ታውቋል፡፡
በተለይ በዳያስፖራው የፖለቲካ ስልጠት (ሲስተም) ያለው የህወሃት/ኢህአዴግ አደረጃጀት ኦባንግ እና ድርጅታቸውን አስመልክቶ የሚሰበስበው መረጃ አቶ ኦባንግ በፌስቡክ ከሚለቁት ብዙም ያልተለየ በመሆኑ ብዥታን ፈጥሮባቸዋል፡፡ በታላላቅ ቦታዎች፣ በከፍተኛ ስብሰባዎች፣ “አንቱ” በሚጠሩ ተጽዕኖ ፈጣሪ ኃይሎች፤ ግዙፍ በሚባሉ የዓለም ተቋማት፣ በታላላቅ መንግሥታት ወዘተ ኢትዮጵያን በብቸኝነት እየወከሉ ፖሊሲ እስከማስቀየር የደረሱት አቶ ኦባንግ “ለኢህአዴግ ራስ ምታት ሆነዋል” በማለት የአገዛዙ ባለሥልጣን መናገራቸውን ከመረጃ ሰዎቻችን ለማወቅተችሏል፡፡
ይህንን አስመልክቶ አቶ ኦባንግ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ “እንዲህ ያለው የኢህአዴግ ስጋት ለእኔ እንደመዝናኛ እቆጥረዋለሁ” ነው ያሉት፡፡ በማያያዝም ድርጅታቸው አኢጋንም ሆነ እርሳቸው ምስጢር የሚባል ነገር እንደሌለው አገር ወዳዶች የሚመሩት፣ የስልኩም ሆነ ማንኛውም የመገናኛ መንገዱ በገሃድ የሚታወቅ፣ በግልጽ ቋንቋ ዘረኝነትን የሚጸየፍ፣ ለሰብዓዊነት የሚቆረቀቆር፣ አጀንዳውም ግልጽ የሆነ፣ በየትኛውም ቦታ የሚገኝ ድርጅት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “ኢህአዴግና አጋር ድርጅቶቹ አኢጋንን አወቃቀሩንና አሠራሩን ለማወቅ ስባሪ ሰከንድ ማባከን የለባቸውም፤ አስፈላጊ ነው ብለው የሚገምቱትን ነገር በሙሉ ቢጠይቁን እንነግራቸዋለን፤ ከሕዝብ ደብቀን የምንሠራው ሥራ የለንም፤ ዘረኝነትን ለመቃወም እና ለማፍረስ፤ ሰብዓዊነትን ከዘረኝነት በፊት በአዲሲቷ ኢትዮጵያ ለማስፈን ለምን ምስጢራዊ ሥራ ያስፈልገዋል? እኛ ለስለላና ለምስጢራዊ ሥራ የምናባክነው ጊዜና ገንዘብ የለንም፤ ይልቁንም የህወሃት/ኢህአዴግ ሰዎች እውነትን ለመጋፈጥ ካልፈሩ በቀጥታ በማንኛውም ጊዜ ሊያገኙን ይችላሉ” በማለት “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያውያን የጥሪ ድምጽ በተሰማመበት ቦታ ሁሉ ቀድመው በመድረስ የሚታወቁት ኦባንግ በስደት እስር ቤት ሲማቅቁ ተረስተው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ከሜክሲኮና ከጃፓን ነጻ በማስወጣት፤ በአውሮጳ አገራት የስደተኛ ጉዳያቸው በህወሃት/ኢህአዴግ ሰላዮችና በሥርዓቱ ቀጥተኛ ተሳትፎ መከራ ውስጥ እንዲገባ የተደረገባቸውን ወገኖች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር የስደተኛ ፖሊሲዎችን በማስቀየር፤ በኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ካሩቱሪና መሰል ድርጅቶች በኢንቨስትመንት ስም አለአግባብ የነዋሪዎችን መሬት በመንጠቅ የሚያደርሱትን ግፍ በተጠናቀረ ዘገባ መልክ በማውጣት የዓለም ሕዝብ እንዲያውቀው ከማድረግ አልፎ የህወሃት/ኢህአዴግን ፖሊሲ በማጋለጥ ሕንድ ድረስ በመሄድ ባደረጉት ውትወታ የካሩቱሪን አካሄድ በማስቀየር፤ የዓለም ባንክ ለኢህአዴግ የሰጠው የዕርዳታ ገንዘብ ኢህአዴግ ለወታደሮቹ ደመወዝ መክፈያ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ መከራ እያደረሰ መሆኑን ይህም የባንኩን አሠራር በግልጽ የሚጻረር መሆኑን በማጋለጥና የፖሊሲ አቅጣጫ በማስቀየር፤ ወዘተ በዳያስፖራ ከሚገኙት ድርጅቶች በተለየ መልኩ የሚንቀሳቀሱት አቶ ኦባንግ ሜቶና ድርጅታቸው ሲሰራ ብዙ ባይዘፈንለትም ውጤት በማስመዝገብ ግን “ወደር እንደማይገኝለት” ኢትዮጵያ ድረስ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦች ይመሰክሩለታል፡፡
የደም ከፈን” አልገዛም ያለውና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ የልብስ መደብሮች ያሉት የስዊድኑ ኤች ኤንድ ኤም ድርጅት ስመጥር ኩባንያ እንደሆነ መረጃዎች ይናገራሉ፡፡ የጀርመኑ ቼቦም በተመሳሳይ ሁኔታ እንደሚጠቀስ ይታወቃል፡፡ ጎልጉል ባለው መረጃ መሠረት የንግድ ስምምነቱ የጨነገፈው ከጥጥ ማምረት ጋር በተያያዘ ሳይሆን በአካባቢው ያለው የሰላም መደፍረስ፣ የሕዝብ እምቢተኝነት ማየል፣ የግፍ መባባስ ዝርፊና ቅሚያው ከልክ እያለፈ መሄድ ከአካባቢው ሙቀት ጋር ተዳምሮ “ለባለሃብቶቹ” ሰላም የሚሰጥ ኢንቨስትመንት ባለመሆኑ ነው፡፡ የተለያዩ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ከዚህ በፊትም ጎልጉል በተለያዩ ጊዜያት አስቀድሞ እንደዘገበው በኦሞ ሸለቆና በምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢ ያሉ ታላላቅ ኢንቨስትመንቶች እያደር መጨናገፋቸው የማይቀር እንደሆነ በስፋት ይታመናል፡፡ የተፈጥሮን ደን በማውደም ጣውላ ሲቸበችቡ የነበሩት “ኢንቨስተሮች” እንኳንስ ሊያለሙ የተበደሩትን መክፈል አቅቷቸው እያቃተቱ መሆናቸውን በቅርቡ ኢህአዴግ እያመነ መሆኑን በራሱ በኢህአዴግ አፍ ተመስክሯል፡፡
አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት “በጥምባሆ መግዣ ዋጋ መሬት እየቸበቸበ፣ ምስኪን ንጹሃንን እያፈናቀለ፤ ምነው ያሉትን እያሰረና እየገደለ፣ “አገር አደገች፤ ተመነደገች፤ ልማት ነው፤ ሥራ ላይ ነን” የሚለው ኢህአዴግ፤ ሸራተን በውስኪ አጅቦ ያወጀው ኢንቨስትመንት መጨረሻው ይኸው ነው፡፡ በአበባ እርሻ ላስቲክና ካርቶን የባንክ ዋስትና (ኮላተራል) አድርገው የአገሪቱን ባንክ አልበው የሄዱትን አጭበርባሪ ድርጅቶችና አጋሮቻቸውን ልማት ባንክና ህወሃት ያውቋቸዋል፡፡ ይህ ቀን ጠብቆ ሕዝብና ትውልድ ፍርድ የሚሰጡበት ነው” ብለዋል፡፡ በምዕራብ ኢትዮጵያ በተለይ በጋምቤላ አካባቢ በትንሹ ከ70 በመቶ በላይ “ባለሃብት” ተብለው መሬት የወሰዱት የትግራይ ነዋሪዎች ከኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ዳይሬክቶሬት የተገኘው ይፋዊ መረጃ ያረጋግጣል፡፡
በሌላ በኩል የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ አሜሪካ ህወሃት/ኢህአዴግን ይዛ የትም መድረስ እንደማትችልና ይልቁንም የሕግ የበላይነት እንዲከበር ፖሊሲዋን ልትመረምር እንደሚገባ በማሳሰብ ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ደብዳቤ ልከዋል፡፡ በተለይ መጪውን ምርጫ ተያይዞ ህወሃት/ኢህአዴግ የሚከተለውን የአፈና ፖሊሲ የምርጫውን ውጤት አስቀድሞ የሚተነብይ መሆኑን አቶ ኦባንግ በደብዳቤያቸው ማስረጃዎችን በመጥቀስ ዘርዝረዋል፡፡ ከዚህ ጋር በማያያዝ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ላይ ምርጫ ቦርድ የወሰደው ዕርምጃ ተጠቃሽ መሆኑን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ አስታውሰዋል፡፡
ስለሆነም ምህዳሩ እንዲሰፋ፣ አፈናው እንዲቆም፣ ምርጫ ቦርድ ያለአድልዎ መስራት እንዲችል፣ የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ያረቀቁት “ኦምኒበስ ረቂቅ 2015” ተግባራዊ እንዲሆን፣ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ እንዲሁም ቁልፍ በሆኑ የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ላይ ወደ አሜሪካ የመግባት ዕቀባ (የበረራ ማዕቀብ) እንዲጣልባቸውና በውጭ አገር ያከማቹትን ገንዘብና ሃብት እንዳይንቀሳቀስ እንዲደረግ፣ ወዘተ አሜሪካ የፖሊሲ ለውጥ እንድታደርግ ለፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል፡፡ ኦባንግ ይህንን ያቀረቡት በልመና መልክ ወይም “ያለ አሜሪካ እርዳታ አይሆንልንም” በማለት መንፈስ ሳይሆን የኢህአዴግን የበጀት ኮሮጆ በመሙላትና “አሸባሪዎችን ለመዋጋት” በሚል ድጋፍ በመስጠት ቀዳሚዋ አሜሪካ በመሆኗ ከግብር ከፋይዎቿ እየሰበሰበች በምትሰጠው ገንዘብ ሕዝብ እንዳይበደል፣ እንዳይሰቃይ፣ እንዳይገደል፣ መብቱ እንዲከበር፣ ነጻነት እንዲያገኝ፣ ወዘተ የማድረግ የሞራል ግዴታ ስላለባት ነው፡፡ የአቶ ኦባንግ ደብዳቤ ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይነበባል፡-

An Open Letter to President Barack Obama,

The alarming political conditions in Ethiopia that may threaten the future security and stability of this strategic country in the Horn of Africa
February 5, 2015
Honorable Barack Obama
The President of the United States of America
The White House
1600 Pennsylvania Avenue
Washington, DC 20501
Dear President Obama,
I am writing this to you on behalf of the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) to alert you to the alarming political conditions in Ethiopia that may threaten the future security and stability of this strategic country in the Horn of Africa. Current United States policies that strongly support the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) are being abused by this regime to undermine the democratic aspirations of the Ethiopian people. As the EPRDF intensifies the crack down on the political and human rights of the people there is fear that some event may ignite the simmering tensions, causing them to explode into violence, killing and chaos.
My name is Obang Metho. I am the Executive Director of the SMNE, a non-violent, non-political grassroots social justice movement representing the diverse people of Ethiopia.
I come to you first and foremost as a human being who believes that the future well being of our global society rests in the hands of those among us who can put humanity before ethnicity or any other distinctions that divide and dehumanize other human beings from ourselves; inspiring us to care about these others; not only because of the intrinsic God-given value of each life, but also because none of us will be free until all are free. These are the underlying principles of the SMNE. The SMNE is committed to bringing truth, justice, freedom, equality, reconciliation, accountability, respect for human and civil rights and economic prosperity to the people of Ethiopia and beyond.
Urgency of concern:
The escalation of frustrations regarding the upcoming Ethiopian national elections scheduled for May 24, 2015, may become the trigger to violence as Ethiopians face the dismal reality that all avenues to democratic political change are solidly blocked. If violence breaks out, it may spin out of control. Now is the time to take steps to avoid it; however, the TPLF/EPRDF fears the people to the degree that they may find it impossible to alter their direction, even if it is what pushes people over the edge towards a violent backlash. The SMNE seeks to help all parties avoid such an outcome.
Unfortunately, the TPLF/EPRDF will never voluntarily give up power by holding a free and fair election. They know opening up political space would lead to a reversal of power. As a result, there is little hope that the situation will improve without leverage.
We know that, the United States is the chief financial, political and security backer of the TPLF/EPRDF. If the appropriate actions are taken, it may give the US an opportunity to improve the long-term interests of the US in Ethiopia and the Horn as well as to contribute to a better future for Ethiopians and their neighbors.
Clearly, Ethiopia is the most stable country among its neighbors like Eritrea, Somalia, Sudan and South Sudan, but if it were to descend into instability, it would be devastating for the Horn of Africa and beyond. There needs to be an alternative that would offer a peaceful way out for all parties, including the TPLF/EPRDF. The TPLF/EPRDF will not and cannot do it alone. The people of Ethiopia must do the major work, but if they are facing a strongly-US, UK or EU-supported TPLF/EPRDF; the job will be all the more difficult.
The TPLF/EPRDF has become an increasingly totalitarian government over the last 24 years they have been in power; however, the real power behind them is the ethnic-based Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF) that dominates every branch of the government. Their stated goal is to gain perpetual rule and hegemony of Ethiopia. As documented by both the US Embassy in Addis Ababa and the US State Department’s human rights division, the Ethiopian government is becoming increasingly brutal in its crack down on basic freedom, democratic processes, and the rule of law. This is not new.
Since coming to power, this regime has never held a free and fair election. The closest it came to allowing a degree of political space was in 2005 when the opposition nearly won. Instead, the TPLF/EPRDF claimed a victory, killed 193 election protestors in the streets, imprisoned opposition members, and closed down all political space in the 2010 election. At that time they even misused humanitarian aid to control voting at every level; finally claiming an absurd 99.6% electoral victory. The Ethiopian Parliament has only one opposition member out of 547.
Some are willing to overlook the lack of democratic progress, believing that claims of economic progress make up for it. However, although there may be some advances made, TPLF/EPRDF statistics claiming double-digit economic growth are being challenged as Ethiopians remain at the bottom of most every poverty index. There is little to no private sector, but instead, economic opportunities are limited to regime cronies, another source of contention among Ethiopians.
A robust civil sector that could act as watchdogs of society has been eliminated due to the implementation of the Charities and Societies Proclamation. This is a law that has made it a crime for civic organizations who receive more than 10% of the funding from foreign sources to advance human and democratic rights, to promote equality among ethnicities, genders and religions, to promote rights for the disabled and children, to promote conflict resolution or reconciliation, or to promote the efficiency of justice and law enforcement services. Some 2,600 or more civic organizations closed in response. In their place, the TPLF/EPRDF has set-up pseudo-organizations they control.
Similarly, they have passed an Anti-Terrorism Law that is used to silence democratic voices, journalists, bloggers, editors, opposition leaders and religious leaders under false pretenses. Ethiopia has become one of the highest jailers of political prisoners in Africa. In present day Ethiopia, every important public and private institution is under the control of the TPLF/EPRDF, whether it is the judiciary, the police and security forces, government offices and ministries all the way to the local level, the military, the media, the telecom system, the Internet, the educational system, the economy, and most importantly right now, the National Election Board of Ethiopia (NEBE).
In the last month, they have increased their efforts to eliminate any competition. This includes beating up opposition leaders and any who speak out against them, even pregnant women and the elderly. Many are jailed in an effort to intimidate any who call for a legitimate democratic process. Obstacles are erected to block every effort of opposition parties to satisfy the impossible requirements of the NEBE.
Two prominent opposition political parties, the Unity for Justice and Democracy (UDJ) and the All Ethiopian Unity Party (AEUP), have both made valiant attempts to comply with unreasonable demands; however, they now have been denied participation in the election. Instead, the TPLF/EPRDF has hijacked the ownership of these parties, even taking on their names, UDJ and AEUP. They have appointed their own people to run as candidates against others in the TPLF/EPRDF, essentially competing with themselves in a ruse to confuse the people.
Recommendations for meaningful US action regarding Ethiopia:
US silence or only symbolic gestures regarding the evolving crisis in Ethiopia may work for the short-term, but no one knows for how long. In fact, continued US support or meaningless action may inadvertently exacerbate the crisis and undermine stability. Instead, the US should use their leverage to bring democratic change and sustainable stability to the country; both of which would enhance long-term US interests in Ethiopia and the Horn.
Meaningful actions include:
  • Calling for an independent election commission
  • Implementing the Omnibus Bill 2015 concerning Ethiopia
  • Releasing imprisoned political prisoners
  • Freezing security cooperation with the regime
  • Implementing travel bans on key regime officials and freezing their assets
It is not in the interests of anybody to wait for an explosion. Ethiopia is in crisis. Our goal is to bring peace even as some are beating the drums of violence. We strongly encourage you to put pressure on this regime. Condemn these actions. The US should not be silent when such a stance could contribute to the future wellbeing and stability of this strategic country of over 90 million people.
Respectfully yours,
Obang Metho,
Executive Director of the SMNE
910- 17th St. NW, Suite 419
Washington, DC 20006
Email:Obang@solidaritymovement.org.
Website: www.solidaritymovement.org
This letter has been Cc to
Vice President Joseph Biden
Secretary of State John Kerry
National Security Advisor Susan Rice
Senior Director for African Affairs on the National Security Council Gayle Smith
Senior Director for Democracy on the National Security Council Linda Thomas-Greenfield
Assistant Secretary of State for the Bureau of African Affairs Earl Gast

Friday, February 6, 2015

ጠቅላይ ሚነስትራችን ከእውነት ጋር ከሚጋጩ ስልጣን ቢለቁስ?

February 6,2015
ግርማ ሰ ይፉ
My Photo
የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ ቢሆኑ የሚሰሙት እና የሚያምኑት በኢቲቪ ወይም በሌላ የመንግሰት መገናኛ ብዙዓን የተላለፈ ነገር ነው፡፡ ሌላው እውነተኛ የመረጃ ምንጫቸው ደግሞ እንደ ትላንቱ (ጥር 28/2007) ጠቅለይ ሚኒሰትሩ ቀርበው እውነት ነው ብለው የሚነግሯቸውን ነው፡፡ ከዚህ ፍንክች ማለት ቢፈልጉም አይፈቀድም፡፡ ይህ እውነት ሊሆን የሚችልበት እድል የሚኖረው በሚዲያ በኩል ከፖለቲካ ነፃ የሆነ የመረጃ ምንጭ መሆን ሲችል እና ጠቅላይ ሚኒስትሩም የሚቀርብላቸውን መረጃ ከሰሩ የሚያጣሩ ቢሆን ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተነገራቸው ደረጃ እውነት ነው ያሉትን ለምክር ቤት አቅርበው፤ የራሳቸውን ፉከራ ጨምረው አስፈራርተውን ተሰናብተውናል፡፡ በዚያን ዕለት እውነት አለኝ ብዬ በምክር ቤት የነበርኩ አንድ ሰው ግን የተረዳሁት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የሚመሩን እንዲያውቁ በተፈቀደላቸው መረጃ ልክ መሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከእውነት ጋር ያጋጫል፤ እኔ እርሳቸውን ብሆን በዚህ ደረጃ ጠቅላይ ሚኒስትር ከምባል ስልጣን መልቀቅ እመርጣለሁ፡፡ ነጥቦቼን ላስቀምጥ፤

በሁለት ቦታ ሁለት መቶና ሶስት መቶ ሰው ተሰብሰቦ ጉባዔ አካሄደ የሚሉት ማብራሪያ ውሽት ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የአንድነት ጠቅላላ ጉበዔ አባላት ቁጥር 320 ከሆኑ ሁለት ቦታ ላይ ሁለት መቶና ሶሰት መቶ ሰው ሊሰበሰብ አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ የፖለቲካ እውቀት ሳይሆን መደበኛ የሂሳብ እውቀት ነው የሚጠይቀው፡፡ ለዚህ ደግሞ መሀንዲሱ ጠቅላይ ሚኒሰትር የሚቸገሩ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ ጠቅላላ ጉባዔ ያካሄደው ማን እንደሆነ መርምሮ ውሳኔ መስጠት ያልፈለገው ምርጫ ቦርድ ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀርባ ሆኖ ለሳቸው መረጃ ለምርጫ ቦርድ ደግሞ መመሪያ የሚሰጥ አንድ አካል አለ፡፡ ስለዚህ ምርጫ ቦርድ ገለልተኛ አይደለም ስንል ህንፃውን ሳይሆን በህግ ከተሰጣቸው መተዳደሪያ ይልቅ በሌላ አካል መመሪያ የሚሰሩትን ሰዎች ነው፡፡ ይህን ማለት የሚያሰከስስ ከሆነ ለመከሰስ ዝግጁ ነኝ፡፡ አሁን እንደገባኝ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ቢሆኑ መረጃ ለማጣራት ፈቃደኛ ያለመሆኑ ሚስጥር እርሶም ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብት ያሎት አይመስለኝም፡፡

ሌላው የሚያሳዝነው የተሳሳተ መረጃ ደግሞ የአንድነት አባላት ክፍፍል በውጭ እና በውስጥ የሚመራ የተባለው ነው፡፡ በውጭ የሚመራው ቡድን ውስጥ ደግሞ እኔም አለሁበት፡፡ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን አንድነትን መደገፋቸው ምንም ክፋት ባይታየንም እኔ ያለሁበት አመራር ምርጫ መግባት ስንወስን በውጭ ያሉ የፈጠሩትን ጫጫታ፤ በተለይ ደግሞ የምናቀርባቸው እጩዎች ለምርጫ ውድድር የሚያስፈልጋቸውን ወጭ ለመሸፈን የሚያስችል የግል የፋይናንስ ቁመና እና በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመሰብሰብ ያላቸው አቅም እንደ አንድ መሰፈርት ያሰቀመጥን መሆኑ ያለመረዳት አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም የሚለውን ብሂል ከማስታወስ ባለፈ ምንም ማለት አይቻልም፡፡ ይልቁንም በፓርቲው ውስጥ የምንከሰሰው እና ምርጫ ቦርድ ደጅ የሚጠኑት የአንድነት አባላት በኢኮኖሚም ሆነ በትምህርት ለዚህ መሰፈርት ስለማይመጥኑ ከዕጩነት ተገለልን የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ዘወትር የሚቀርብብኝ ክስ ፓርቲውን የተማረና የሀብትም ሊያደርገው ነው የሚለው ነው፡፡ ይኼ ደግሞ በምንም የውጭ ጥገኝነትን የሚያሳይ አልነበረም፡፡

ለማነኛውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጥር 28 መልዕክታቸው ግልፅ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድን እና ፍርድ ቤትን በተግባር በሚያሳዩት ሰማቸው ብንጠራቸው ለፍርድ እንደምንቀርብ ማስጠንቀቅ ነው፡፡ ደስ የሚለው የግል አስተያየቴ በሚል ነው የነገሩን፡፡ ይህን የግል አስተሳሰባቸውን እንደ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የምር የሚወስድላቸው ከተገኘ ሰሞኑን ፍትህ ሚኒስትር ክስ መመስረት ይኖርበታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተሰጣቸው መረጃ ትክክል የሚመስለው የፍርድ ቤት ጉዳይ በሚመለከት ላነሳሁት ጥያቄ የሰጡት መልስ ነው፡፡ ነገር ግን የፍርድ ቤቱ ም/ፕሬዝደንት ምርጫ ቦርድ አስተዳደራዊ ውሳኔ ባልሰጠበት ሁኔታ ክስ መመስረት አይቻልም ሲሉን፣ ምርጫ ቦርድ በፓርቲያችን ላይ የተለያየ ህገወጥ ውሳኔ እየወሰነ የነበረ ሲሆን ከዚህም አንዱ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት አልሰጥም፤ የጠቅላላ ጉባዔ ሪፖርት መርምሮ ውሳኔ በወቅቱ አልሰጥም እያለ የነበረ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ የፍርድ ቤት ውሳኔ የተረዳነው ቁም ነገር ፍርድ ቤት ምርጫ ቦርድ የሚሰጠውን የመጨረሻ ፖለቲካ ውሳኔ ያውቅ እንደነበረ ነው፡፡ የፖለቲካውን ውሳኔ የሚቃረን መረጃ መሰረት ያደረገ ውሳኔ እንዳይሰጥ ከለላ እየተደረገ መሆኑ ግልፅ ሆኖዋል አሁን ባለንበት ሁኔታ፡፡ የሚገርመው አሁን ፍርድ ቤት ሲኬድ በአስተዳደራዊ ውሳኔ በፖሊስ ሰራዊት የተቀማነውን አንድነት አትወክሉም ልንባል እንደምንችል ነው፡፡ ይህ ነው እንግዲ ነፃ ፍርድ ቤት ካላላችሁ ለፍርድ ትቀርባላችሁ የምንባልበት ስርዓት፡፡
ጠቅላይ ሚኒሰትር ሀይለማሪያም ከመረጃ እጥረት ይሁን አውቀው በድፍረት ሊመልሱት ያልቻሉት “የምርጫ ቦርድ ህገ ወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔ ለማሰፈፀም የፖሊስ ሀይል ማስማራትና ቢሮ የመዝረፍ መብት ማን ነው የሰጠው?” የሚለውን ጥያቄ ነው፡፡ የአንድነት አባላት የሆኑ በበሩ እንዳያልፉ በፖሊሰና ደህንነት ኃይሎች ጥበቃ የሚደረግለት አዲሱ ሹም “የአንድነት ፕሬዝደንት” አቶ ትዕግሰቱ አጉሉ በሚዲያ ቀርቦ ምርጫ ቦረድ ለእኔ ስጥቶኛል ብሎ የመሰከረውን ሀቅ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ምርጫ ቦርድ ምን ያድርግ ሊሉን አይችሉም፡፡ ምርጫ ቦረድ ኢህአዴግ እንዲያሸንፍ የታዘዘውን ሁሉ መፈፀም ነው፡፡ በምክር ቤት መቋቋም ነፃነትን የሚያረጋግጥ ቢሆን ኖሮ…… ሌላ ጊዜ በዝርዝር እንመለስበታለን፡፡
ለማነኛውም ጠቅላይ ሚኒስትራችን እውነት ነው ተብሎ በተነገራቸው መረጃ ልክ ለምክር ቤት አባላት እና ለኢትዮጵያ ህዝብ እውነት ነው ያሉትን አስተላልፈዋል፡፡ ከዚህ ውሳኔ የተረዳሁት እርሳቸው የሚመሩት ካቢኔ በዚህ ጉዳይ ውስጥ ከስረ-መሰረቱ እንዳልተሳተፈ ነው፡፡ በመጨረሻ በግንባር የተገናኘን እለት የተረዳሁት ይህን ነበር፡፡ ነገር ግን ለማስተካከል አቅም ይኖራቸዋል ብዬ እምነት ነበረኝ፡፡ መረጃ በተሳሳተ ተሰጥቷቸው እንዳይሳሳቱም መረጃ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር በገቡልኝ ቃል መሰረት እንድንገናኝ ያደረኩት ሙከራም ያልተሳካው  የተለየ መረጃ ማግኘት ስለማይፈልጉ ሳይሆን ስለአልተፈቀደላቸው ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሻለሁ፡፡ ለዚህ ነው “ከእውነት ጋር ከሚጋጩ ስልጣን ቢለቁስ?” የሚል ሃሳብ መሰንዘር የፈለኩት፡፡

ቸር ይግጠመን!!!!!! 

ETHIOPIA : DICTATORSHIP WRESTLED BEFORE DEATH,OPPOSITION PARTY HOPES TO WIN IN THE NEXT ELECTION

February 6,2015
Addis Ababa ( DIPLOMAT.SO) – According to some Ethiopian and Eritrean websites , A Week ago, the opposition party Unity for Justice and Democracy (UDJ)- widely known by its Ethiopian name ‘Andenet‘ – was brimming with confidence that it will contend for power in the national elections in May 2015. Of course, there was an uphill battle, and that was to make sure the elections would be free and fair.
The-Unity-for-Democracy-and-Justice-Party-said-the-country-is-heading-toward-“absolute-dictatorship”-under-the-ruling-party
The Unity for Democracy and Justice Party said the country is heading toward “absolute dictatorship” under the ruling party

What Andenet’s young and charismatic leaders may not have anticipated was that the ruling party and its arm, the ‘Election Board’, would cut Andenet in two, then discard the real, authentic Andenet group off the precipice, while preparing the puppet for the election.
Andenet was not only popular but also an organization that transcended the politics of ethnicity and had drawn members from all corners of the country. And this was a threat to the ruling TPLF, a pioneer of the politics of ethnicity and hate with stand-by program for the disintegration of the country in the event TPLF loses power.
Now Andenet is history. If there is any group that claims to be ‘Andenet,’ it is the puppet hatched by the ruling party.
On Tuesday, former leaders and members of Andenet Party announced at the Semayawi Party HQs that they have officially joined Semayawi because there was little or no difference in their political programs.
TPLF committed a crime but every dark cloud has a silver lining, and that is TPLF unintentionally brought two same-minded organizations into a ‘merger.’ The struggle against tyranny continues.
For more news and stories, join us on Facebook,Twitter and Subcripe ourYoutube Channel,Or contact us through our Emails : info@diplomat.so,adv@diplomat.so,diplomatnewsdesk@gmail.com
Source- diplomat.so

The Upcoming May 2015 Ethiopian General Election and Ethiopian-American Action

February 6, 2015
by Dallol Kiros
Two years ago I participated in the “Ethiopian American Convention” that was held in Washington Middle School in Alexandria, Virginia. Throughout the 2012 November election, Loudon County which is not far from where most Ethiopia American reside in northern Virginia was a battle ground. More than any time Ethiopia-American voters in swing states like Virginia has mattered and candidates should put into consideration the demand Ethiopian American constituents are making.The Upcoming May 2015 Ethiopian General Election
On 2014 mid-term election, the democratic candidate Senator Mark Warner won by small margin 49 percent versus 48 percent for the republican candidate Ed Gillespie. Historically there is a low voters turnout in mid-term election and let’s assume that most Ethiopian American did not cast their vote. But that would not be the case in upcoming 2016 presidential elections.
Therefore, Ethiopian American should follow suit on what they have started two years ago in November. The ‘Ethiopian American Convention’ that was held on Sunday October 14, 2012 “Vote Free Ethiopia’ and other civic organizations was the beginning of that process. Ethiopian community need to articulate.
When it comes to human right in Ethiopia, the Obama administration have not made a strong condemnation let alone take serious action. To our surprise in the dawn of the November mid-term election in November 2014, the US State Department has made a press releases concerned about the recent sentencing of journalist Mr. Temsegen Desalegne, which is was a little late in getting Ethiopia Americans to cast their votes for a democrat. http://www.state.gov/r/pa/prs/ps/2014/10/233556.htm
The Ethiopian government is tirelessly working with Washington lobbyist and spending millions. Hiring firms such as DLA Piper and Good Works International , chaired by Andrew Young former UN ambassador under President Jimmy Charter. According to Corporate watch dog few of the favourite African government lobbyists are Herman Cohen, former State Department official under president George Bush.http://www.corpwatch.org/article.php?id=98
On the flip side the Ethiopian-Americans have put at the bay the TPLF operatives in most major United State cities and Western Europe. One group that works tirelessly is the DC task force, is a group that consists of human right activist such First Hijarh Foundation and opposition political members from EPRP, Ginbot Seven and other human right activists.
Because of effective group such as DC task force, the TPLF regime has not been able to rally the Ethiopian Diaspora for any public meeting and fund raising events. No government official can freely mingle among the Diaspora community without being confronted by DC area task force,
All over the Western Europe, including Norway, Sweden, Canada and Australia, Ethiopian government official are confronted by protestor. Video of egg throwing on Ethiopia Ambassador in Sweden have surfaced all over the social media.
But this time around the “ the DC task force” has made a very bold move, removing Ethiopian national flag with TPLF/EPRDF rebel group emblem with the true Ethiopian flag at Ethiopia Embassy in Washington DC. This has been a big blow for Ethiopian government and regime supporters. The Prime minster of Ethiopia was so aggravated had to address the rubber stamp parliament about the group naming the participants Eritrean government agents.
A video has surfaced all over the media outlets. Showing the Ethiopian embassy security attaché Mr. Solomon Tadesse Gebre Sellasie, a former TPLF guerrilla fighter was caught on camera shooting point blank at unarmed protesters and activists Mr. Mekonnen Getachew inside the embassy grounds.
The resistance against the regime is at all time high, especially in the Washington DC metro area where large Ethiopian-Americans population reside in the North America. The Ethiopia bond purchase program is a total failure. The Ethiopian government TV channel is off the cable channels in DC metro area. Whereas more than any time in past 23 years, the Ethiopia population in Ethiopia and overseas with access to radio and TV are getting their news from the Diaspora financed TV and radio program called Ethiopian Satellite Television (ESAT).
VOA-Amharic, on time popular outlet has been accused by civic and oppositions forces for making favourable reporting for the Ethiopia regime and has lost its creditability among its listeners. In which the chief of horn African program Peter Peter Heinlein as Chief of the Horn of Africa was demoted for deliberate distortions and professional misconduct. The allegation of misinforming by his subordinate Henok Semaegzer on Ethiopia prime minster cancel award by Azusa Pacific university was first aired by ESAT radio.
The TPLF regime is also trying very hard to silence dissent among Ethiopian-American with a total failure. After the Ethiopian communication minister Rewdan Hussien was confronted and humiliated at Arlington’s Marshal store on 08/07/14 by two Ethiopian activists, the regime took the case to Arlington court where the prosecutor decided not to prosecute the case” Nolle Prosequi” against Mekonnen Getachew, the same activity from the Ethiopian Embassy flag incidence. Similarly, a German court in Munich had dropped the charge made against Tibebu Assefa for protesting against bond purchase program held by TPLF operatives for the Grand Renaissance Dam building.
Few months ago Ethiopian Americans have launched a task force to bring to justice 70 TPLF high ranking and Ethiopia government official that are accused of war crimes, crimes against humanities, genocide, extrajudicial killing, torture, illegal imprisonment, rape, corruption, extortion and embezzlement. The spoke person for the task force activist Mr. Tamagene Beyene have announced there is an effort with U.S law enforcement agencies and human right organizations.
On its official website http://www.masreja.com/ the task force have listed Ethiopian officials and security officers and army officers according to their crimes committed, at the top of the list Mr. Abay Teshaye Minster of Federal Affairs, Dr. Debrestsion Gebre-Michael Deputy prime mister and in charge of Ethiopian National Intelligence and Security Service, Mr. Tesgay Berhe National Security Affairs Adviser Minister , Mr Abay Woldu president of the TPLF and the Tigray Regional State, Mr Arkebe Oqubay the prime minster policy advisor and former Addis Ababa mayor followed by the current prime minster of Ethiopia Mr. Hailemariam Desalegn, accused of crime when he was a President of the Southern Nations, Nationalities, and People’s Region (SNNPR) from November 2001 to March 2006.
Ethiopian in Sweden has also submitted a charge against 13 Ethiopian government and Defense Force officials that are also on the list above to the Swedish International Criminal Tribunal and Courts.
More than any time the Diaspora opposition forces are organized, coordinated, committed and above all aggressive. But with all this success stories, the Ethiopia- Americans have been unable to influence the US policy toward Ethiopia.
The US together with has its strong board of directors presentence at the World Bank, has continued to write a blank check.
As recently as September 2012, the World Bank Group have mobilized US$600 million in development financing for the third phase of the Promoting Basic Services (PBS III). These are the type of programs they need to be identified. Ethiopian- American should chose a candidates for United State Senate and congress that understand their cause only vote for those candidates, preferably this time around republican candidates.
The World Bank loans are literally providing a budget support to the government of Ethiopia, which means the Ethiopian government is only accountable to donor governments, and not to the Ethiopian people.
Ethiopian-American should not be requesting that that the World Food Program’s US humanitarian assistance be stopped to Ethiopia either, but for US government to make sure food aid and humanitarian assistance are not diverted, or used to coerce the Ethiopian peasants for political gain.
Ethiopian-American that voted for Obama in good faith and had received in return a flat out insult by Ambassador Susan Rice, calling the Ethiopia American voters “Fools” in Addis Ababa on the late Prime Minister Meles Zenawi funeral in Addis Ababa. This is a strong indication that Ethiopian- American vote by Obama administration has been taken for granted.
In 2016 presidential election, the Democratic Party should not be getting the usual support it gets from Ethiopian American especially in Washington DC metro area.
Ethiopian-Americans should indentify a candidate that will serve the interest of the opposition Ethiopia American and endorse and vote for that candidate.
This time around the opposition Diaspora and the Ethiopian-American at large need to vote for a republican candidate. Ethiopian Americans should endorse and announce their choice on the local media and news outlets. The candidate should back its promise with strong actions.
Following the footsteps of African Americans that predominately votes for the Democratic Party, Ethiopian-American have been voting for the Democratic Party, this needs to change. For the upcoming 2016 presidential election, what Ethiopian-American should be demanding from both the Republican and the Democratic parties is for congress to stop writing a blank check to the government of Ethiopia. Specially, candidates in swing states like Virginia should realize Ethiopia- American vote matters.
Ethiopian-American should demand that the US government to pressures for the release of all political prisoners and journalists and give room for the Ethiopian opposition to organize freely to mobilize its supporter and raise funds, without being persecuted. They should request that the US administration make a strong statement backed by action. ESAT and Ethiopian opposition groups and civil organization coordinate their effort to mobilize and frame the agenda.
On September 25, president Obama meet prime minster Hailemariam Desalegn of Ethiopia who was also at New York to attend the 68th United Nations General Assembly. The Obama administration officials including Susan Rice and Secretary of State Kerry were present. In which, President Obama spoke in the interest of United States peacekeeping in Africa, Ethiopia being a hired gun. At least in front of the camera, good governance, democracy, corruption, the jailing and persecution of journalist and the Ethiopia oppositions were not part of his statement.
Going forward, candidate especially in swing states should not just award their votes to candidate just because they are running on the Democratic Party platform.
Ethiopian-Americans need to articulate there demand and most importantly educate voters in their community about make specific demands. Ethiopian Americans need to support only a candidate that can address their specific demand.
The 2016 elections would be the greatest one time opportunity for Ethiopian Americans to get the attention of the US legislative body.
There are groups that have no faith in the US policy maker and believe Ethiopia’s destiny should not be with the next US administration or the democratic or republic party, but Ethiopians democratic aspirations. That would flatly reject the above notion and suggestions, it does not matter who Ethiopian American should vote in the November 2016 and upcoming elections. Rehearse the famous quote from former American foreign secretary Henry Kissinger “America has no permanent friends or enemies, only interest”
By May 2015 Ethiopian general election if the Obama administration does not have a strong stance against the TPLF regime. http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2015/02/03/u-s-policy-ethiopia-a-failed-state-documentary/ The current Ethiopia- American policy must have an alternative plan toward the Ethiopia regime. The 2014, USAID and USADF foreign assistance program for Ethiopia excluding multinationals, military assistance and emergency food assistance disbursed $417 million.
The Ethiopia Diaspora have more financial leverage than the US foreign assistance program to Ethiopia. Especially for groups that believe in peaceful struggle this should be and encouraging sign. A simple action such as economic leverage by suspending remittance for 2-3 month, provided that Diaspora family members are willing to make sacrifices, is an effective method to bring the regime to its knees.
This will have one time impactful pressure on TPLF regime that is try hard to keep afloat. Ethiopian Ministry of Finance government annual Budget for 2014 is $8.92 billion of which $3 to $4 billion is financed by remittance. The Ethiopian economy is stretched beyond it means, there It is a strong indication that the National Bank Reserve is depleting with evidence that the government is cash strapped.
Group such as “DC task force” is effective but the struggle needs more commitment.

Thursday, February 5, 2015

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!

January 5,2015
ህወሓት ንፁሀንን ለመደብደብ የሚያበቃ በቂ ክፋት ያለው ልዩ ጦር ሲያሰለጥን ቆይቷል። ይህን ልዩ ጦር የፓሊስን መለያ እያለበሰ ነውረኛ ሥራዎችን እንዲሠራ በማድረግ በአንድ በኩል ንፁሀንን የመጉዳት በሌላ በኩል ደግሞ ፓሊስን በሕዝብ የማስጠላት መንታ ግቦችን ለማሳካት ተጠቅሞበታል። ይህ ልዩ ጦር በአለፉት ጥቂት ሳምንታት ባዶ እጃቸው ለተቃውሞ በወጡ ነብሰ ጡር ሴቶች ላይ ሳይቀር ባሳየው ጭካኔ፣ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ባደረሰው ድብደባ መጠን እና ባካሄደው የግለሰብ ንብረቶች ዝርፊያ የሥርዓቱ ባህርይ ፈጽሞ ከሰውኛ ተፈጥሮ እየወጣ እንደሆነ አመላካች ነው። በእነዚህ ድብደባዎች ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስባቸው ተደርጓል። በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት የተደረገው በደብዳቢዎቹ የግል ውሳኔ ሳይሆን ከበላዮቻቸው በተሰጠ ትዕዛዝ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
በአርበኞች ግንቦት 7: እምነት መሠረት የፓሊስ ከፍተኛ አዛዦች ህወሓቶች ቢሆኑም አብዛኛው የሠራዊቱ አባል በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ የተማረረ፤ የሥርዓቱ መለወጥ የሚፈልግና ሥርዓቱን ለመለወጥ የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ኃይል ነው። ስለሆነም ህወሓት የተለየ ጦር አሰልጥኖ የፓሊስ ልብስ በማልበስ ነውረኛ ወንጀል በማሠራት ፓሊስን ለማስጠላት የሚያደርገው ሴራ ሊጋለጥ ይገባል ብሎ ያምናል። የፓሊስ ሠራዊት አባላትም በስማቸውና በደንብ ልብሳቸው የሚደረገውን ደባ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንዲያጋልጡ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ህወሓት እንደሚያስበው እና የኢትዮጵያም ሕዝብ እውነት አድርጎ እንዲቀበለው እንደሚፈልገው የትግራይ ሕዝብ በጅምላ የህወሓት አፍቃሪና ደጋፊ አይደለም። እንዲያውም በተፃፃሪው ህወሓት ከትግራይ ተወላጆች ልብ እየተነቀነ ነው። የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን/ደምህት) ከትግራይ የበቀለ፤ ህወሓትን በአመጽ ለመፋለም የቆረጠ ኃይል ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በትግራይ ውስጥ ብዙ ደጋፊዎች ያሉት መሆኑ የምናውቀው ሀቅ ነው። አረና ትግራይ ህወሓትን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተነሳ ተሰሚነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ እና አቶ አብርሀ ደስታን የመሰለ ወጣት ኢትዮጵያዊ የፓለቲካ መሪ ያወጣ ድርጅት ነው። ህወሓት አንድነት ፓርቲ ላይ የመረረ አቋም ከወሰደባቸው ምክንያቶች አንዱ በትግራይ ውስጥ ያለው ተቀባይነት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ነው። ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ ለማጣላት የሚያደርገው ጥረት ማክሸፍ ይኖርብናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ተግቶ ይሠራል። አርበኞች ግንቦት 7 ከትግራይ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር ፀረ ህወሓት ትግል በትግራይ ውስጥ መቀጣጠል ይኖርበታል ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ትግራይ የህወሓት መቀበሪያ የመሆኗ ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በዘንድሮው የ2007 የሴራ ምርጫ አማካይነት ተድበስብሰው የመጡ እነዚህ ሁለት ክፋቶች ማለትም ፓሊስን በሕዝብ ማስጠላት እና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የዲሞክራሲ ወገንተኞችን ለይቶ ማጥቃት ከበስተጀርባቸው ያዘሉት እኩይ ዓላማ መጋለጡ መንገዳችን ያጠራልናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። በአንድነትና በመኢአድ የተፈፀው የድርጅትና የንብረት ዘረፋም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኝ ግልጽ ነው፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር በሰማያዊ ፓርቲም ላይ ይፈጽም ይሆናል።
በመሆኑ ከ2007 የሴራ ምርጫ ትሩፋቶች በትግራይ ሕዝብና በፓሊስ ሠራዊት ጀርባ የሚደረገው ደባ መጋለጡ ነው። ይህ ድል ጽኑ መሠረት እንዲይዝ ህወሓትንና የትግራይን ሕዝብ የመነጠል እና ፓሊስ የሕዝብ አጋር መሆኑን የማረጋገጥ ሥራዎችን አጠናክረን መሥራት እንዳለብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

Wednesday, February 4, 2015

ፍትህ እና ርትዕ ለሁሉም ( ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ)

        

  በኢትዩጵያ ውስጥ ከሁለት አስርት አምታት ወዲህ በህዝብ ላይ በጣም  እየተንሰራፋ ስለሚገኘው የዘረኝነትን ተህዋስ ሳስብ በአንድ ወቅት በእስራኤል ያሉ አይሁዳውያን ያደረጉት አድሎ እና ወገናዊነት በአዕምሮዬ ይመጣል። ሁሉም ለፈለጉት ብቻ ነበር ጥብቅና የቆሙት።የሌላውን ሀዘን እና መከራ ከመጤፍ ሳይቆጥሩት በርባን!በርባን!በርባን! እያሉ በንጉሱ በር ላይ የራሳችው ወገን ብቻ እንዲፈታ አቤቱታቸው ታልቅ ነበር። ኢየሱስን አሳልፈው  ለፍርድ ሰጥተውት የራሳቸው ወገኔ የሚሉት እንዲፈታ በታላቅ አድማ ድምፃቸውን ያሰሙ ነበር።   በዚያን ጊዜ በርባን የሚባል ታወቂ እስረኛ ነበራቸውና  መፈክራችው ሁሉ እሱን የሚያወሳ ነበር።  በወቅቱ ፈራጅ ወደሆነው ቀርበው አድሎ የተሞላበት ጥያቄያቸውን አቀረቡ ገዥውም ጥያቄውን ከሰማ በኋላ እንዲህ አላቸው፥ ከሁለቱ ማንኛቸውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ አላቸው? እነርሱም በርባንን አሉ።   

       ይህ ነው አድሎ። ይህ ነው መለያየት።  ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? አሁን የደረስንበትም   ዘመን ይህንን መስሏል ። ሁሉም ቢጤዬ ለሚለው ለራሱ ፈርጆ ማድላቱ እና ለታሰረበት ሲጮህ የሌላውን ወገን አልባ መሆን ማታሰርና መንገላታት በስራህ ያውጣህ ጆሮ ዳባ ልበስ ካለው የአንድነት እና የመቀባበል ልብ ጠፍቷል ማለት ነው።           

  እንግዲያስ ትግሉ ለማን ነው?ለግለሰብ?ለፓርቲ?ለብሔራችን? ወይስ ለኢትዮጵያ ? ሚዛኑን ሳታዳሉ ምላሽ ስጡብት ። ተለያይቶ በየሰፈራው ለራስ ወግኖ እታገላለሁ ማለቱ የወያኔን እድሜ ቢያረዝም እንጂ ለኢትዮጵያ  ምንም  አይበጃትም።ወያኔ ለራሱ ብቻ ወግኗልና 23 አመታት አስቆጥሮ ሀገሪቷን ወደሚቀጥለው ረመጥ ይዞ 24 ለማለት የብቀላ አየሩን ወደውስጥ እየሳበ ነው። ሌላ የጨለማ ጉዞ።

                   እርስ በርሷ የምትለያይ መንግስት አትጸናም እንደተባለ ኢትዮጵያን በሁሉ አቅጣጫ ሸንሽኗት ይገኛል። ጎሳው፣ ክልሉ ፣ ብሔሩ፣ ፖለቲካው፣ የእምነት ተቋማቱ፣ ሚዲያው ወ.ዘ.ተ. . .  በሌላውም የኢትዮጵያ ጉዳይ ሁሉ ይህ አስከፊ የወያኔ የመለያየት መርዝ እንደ ተስቦ በሽታ በምድሪቷ ላይ ተረጭቷል። ማምከኛው ደግሞ አንድነት ብቻ ነው። የተባበረ ክንድ!           

        ወያኔ ኢትዮጵያን በአንድነቷ ሊገዛት ስለማይችል ከሰሜን አንስቶ ደቡብ ድረስ ከምስራቅ ጀምሮ እስከ ምእራብ ገንጥለህ እና ለያይተህ ግዛ በሚለው መርሁ ትውልዱ ቤተሰብ ሆኖ ሳለ እርስ በእርስ እንዳይቀባበል የጎጠኝነት እና የባይተዋርነት መንፈስ እየዘራበት ይገኛል። ውጤቱም ደግሞ እየተስተዋለ ነው። ይህን ለሚያህሉ አመታቶች በአንባገነንነት ምድሪቷን ሲመዘብር እና ወያኔ የራሱን ሆድ ሲያጠረቃ ከተጠቀመባቸው የውንብድና እና የማጭበርበርያ ስልቶቹ መሀል አንደኛው ኢትዮጵያውያንን እንደ ቅርጫ አጥንት መከትከት እና መቆራረጥ ነው። እናም ይህ የመለያየት መተት እና አዚም ብዙዎችን ለያይቶ ለኢትዮጵያዊነት ሳይሆን ለፓርቲ፣ ለግለሰብ፣ ለክልል፣ ለጎሳ ፣ ለእምነት ቤት፣ ወ.ዘ.ተ. . . ዘብ መቆም ብዙ ቦታ እየተስተዋለ የመጣ ጉዳይ ሆኗል ። ይህም በየስፍራው ያለው ልዩነት ወያኔን በግፍ አገዛዙ እስካሁን እንዲዘልቅ  አግዞታል።       

        በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የጭቆና አገዛዝ የነዳዳቸው ታጋዮች ጥቂቶች  አይደሉም ። በገዢው ቡድን የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ አማካይነት ደብዛቸው እና ስማቸው የጠፉት በብዙ ሺህ ይቆጠራሉ። ለአመታት ያህል በአሰቃቂ ሁኔታ ከታጎሩበት እስር በነጻ እንኳን ቢለቀቁ የአዕምሮ፣ የአካል፣ ህሙም ሆነው አሊያም ከተቀበሉት ሰቆቃ አንጻር በመሀላ ወያኔን አትድረስብኝ አልደርስብህም በማለት በአይነ ቁራኛ የሚጠበቁ ይሆናሉ።  

                ወያኔ ስላሰራቸው ሲናገር ወንጀልኞችን እና አሸባሪዎችን እንጂ ማንንም ጋዜጠኛም ሆነ የፖለቲካ እስረኛ የለኝም ማለቱን ከእውነታው ጋር ሲነጻጸር አንገት የሚያስደፋ ውሸት ሆኖ እናገኘዋለን።ፀሀይ ያሞቀው የውሸት ቋንጣ።ነገር ግን ስለታሰሩት ያለው እውነታ ሌላ ነው። በፀለምት፣ ወልቃይት ፀገዴ፣በቃሊቲ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ዴዴሳ ፣ብርሸለቆ እና ዝዋይ የንፁህ ኢትዮጵያውያን ደም እምባ በምድሪቷ ላይ ድምፁን እያሰማ ይገኛል።  እስር ቤቶቹ ሁሉ በጋዜጠኞች እና ሀገር ሊቀና የሚችል እውቀት ባካበቱ ምሁራን ታጭቋል። ስለዚህ የታሰሩት ኢትዮጵያውያን ናቸው። የታሰሩት ሁሉም ናቸው! ከሁሉም ናቸው! ለሁሉም ናቸው። በሀገራችን ላይ ማንኛውንም ነገር በቀናነት ለማድረግ መብት ከሌለን ሀገር አልባ ነን ወይም ታስረናል ማለት ነው። በእስር ቤት ውስጥ አርፈህ ከተቀመጥህ ትበላለህ፣ ትተኛለህ ፣ትፀዳዳለህ ሌላ ትርፍ እርምጃ ለማድረግ ሀሳብ እንዳለህ ከተነቃብህ ፊደል ያልቆጠሩ የወያኔ ስልጡን ገራፊዎች ይገለብጡሀል። በከተማ ውስጥ ሰለተቀመጥህ ነፃ ነህ ማለት አይደለም አሊያም ነፃ መሆንህን ማረጋገጥ ካስፈለገህ እውነቱን በአደባባይ ቆመህ ተናገር ያን ጊዜ የት እንዳለህ ይገለፅልሀል። ለዚህ ነው ኢትዮጵያ ታስራለች ብለን የምንናገረው።  የእኛም  መለያየት  ወያኔ እየቆመረ እንዲቀጥል አስችሎታል።

          በወያኔ ግዞት ውስጥ በስቃይ ስላሉት ስናስብ ወደ አዕምሮአችን የሚመጡት ኢትዮጵያዊያን ናቸው ወይስ ግለሰቦች? ከታሰሩት ውስጥ የነማን ይፈቱ? የየትኞቹ የብሔር ነፃነት ታጋዮች አሊይስ የቱ ተቃዋሚ ፓርቲ? ቀደምት የነበረው ወይስ መጤው? ለማን አቤት እንበል? መልሱ ግራ የሚያጋባ አይደለም። ለኢትዮጵያውያን ነው መሆን ያለበት። በአንድነት፣ በመጣመር፣በመያያዝ ለኢትዮጵያ ሉአላዊነት ለአንድ አላማ መሰለፍ።

             ከቶውንም ኢትዮጵያዊ ባርያ ሆኖ አያውቅም። ሀገራችን በጄኔቫ የዓለም መንግሥታት ማህበር ጠቅላላ ስብሰባ ላይ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር መስከረም28 ቀን 1923 የመንግሥታቱ ማህበር ሃምሳ ሰባተኛዋ አባል ሆና መመዝገቧ በይፋ ታወጇል ።በዓለም መንግሥታት ማህበር መድረክ የክብር ቦታ ተሰጣት።ታዲያ ዛሬ ላይ ቆመን ይህንን የዚያን ዘመን ጀግንነት ስናስታውስ በፍፁም ቅንነትና የዋህነት የተሞላ ዕምነታቸውንና ተስፋቸውን ስናነብ የደማቸው ጩኽት እያስተጋባብን ማናችን የዚህ ዘመን ትውልድ ነን የዜግነት ግዴታን ቢያንስ ከእነሱ በተሻለ ለመወጣት  የሞራል ብቃት ያለን?           

    ዳር ድንበር የተጠበቀበት ከፋሺስቶች ጉልበት በላይ የተጎለበተበት ያንን  የመሰለ ለጥቁሩ ህዝብ ኩራት ሆኖ ወራሪው በተራው ያፈረበት እና ያጎነበሰበት ክንድ አሁንም በአንድነት አዲሱ ትውልድ ወያኔን ድባቅ ለመክተት ሊቀሰቀስ ይገባል።  ለፋሺስት ፀጉረ ልውጥ ወታደር ያልተበገረ ወኔ አሁንም በአንድነት በታላቅ እንቢተኝነትን እና አመፅ  የተሞላ ትግል  ያሻዋል። እንሔድብት ዘንድ ወያኔ አንጋዶ ያሰመረልን መስመር አሰናከለን፣በተነን፣ለየን እንጂ ለእድገት አላራመደንም።ስለዚህ በአንድነት በቁጣ እንነሳ ።

               ድምፃችን ይሰማ!!! ለአንዱ ብቻ አይደለም ለሁሉም ፍትህ እና ነፃነት  ይገባል። ሰሜኑ ፣ ደቡቡ፣ ምዕራቡ እና ምስራቁ በየክልሉ ያለው የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ሲደመር ነው ኢትዮጵያ የሚባለው።ስለዚህም ለሁሉም መጮህ አለበት። የታሰሩት የፖለቲካ እስረኞች ሁሉም ይፈቱ። በአንድነት ለአንድ ትግል ለአንዲት ኢትዮጵያ እንቁም።  

               ወያኔ ኢትዮጵያን ሊለቅ ይገባል።ሀገርን ቀምቶ በህዝብ ከርሰ ልብ ውስጥ ያለውን ሰላም ስርቆ ደስታን ወደ ሀዘን የለወጠውን የኢትዮጵያ ጠላት ለመፋለም  የጀግና ልጅ ሆይ ተነስ ከወያኔ ረገጣ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ያባቶችህ ወኔ እና አደራ ይጥራህ። 

ድል ለኢ ት ዮ ጵ ያ  ህዝብ !!!!                       
እናቸንፋለን!!!  Biniam Gizaw  Norway

Tuesday, February 3, 2015

ሰበር ዜና የአንድነት አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ

January 3,2015
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስታወቁ፡፡
በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር የፕሮግራምም ሆነ የስትራቴጂ ተመሳሳይነት ወዳለው ሰማያዊ ፓርቲ ተቀላቅለው ሰላማዊ ትግላቸውን ለመቀጠል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
መግለጫውን የ‹ቀድሞው አንድነት ፓርቲ› አፈ ጉባዔ የነበሩት አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔው አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እንዲሁም የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ሌሎችን በመወከል ሰጥተዋል፡፡
‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል በመግለጫው ላይ የተወከሉት አዲሶቹ የሰማያዊ አባላት፡፡ በዚህ መሰረትም በርከት ያሉ አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲ የአባልነት ፎርም ሞልተዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ወደ ሰማያዊ ቢሮ ባቀኑበት ወቅት ፖሊስ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ድረስ በመግባት ‹‹በሰማያዊ ስም መግለጫ የሚሰጡ አካላት እንዳሉ ሰለሰማን ነው›› በሚል ለፓርቲው አመራሮች ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡

Monday, February 2, 2015

ወያኔ የጋረደብንን የመበታተን አደጋ ለማክሸፍ ትግላችንን ማቀናጀትና በአንድ የአመራር ጥላ ሥር ማሰባሰብ ወቅቱ የሚጠይቀን እርምጃ ነው

February 2,2015
ትግራይን ከተቀረው የአገራችን ክፍል ለመገንጠልና የትግራይን ሪፑፕልክ ለማቋቋም ራዕይና ተልዕኮ ሰንቆ የዛሬ 40 አመት ደደቢት በረሃ ውስጥ የተፈጠረው ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ፡ በለስ ቀንቶት የመንግሥት ሥልጣን ከተቆጣጠረ ወዲህ፡ በስሙ የሚነግድበትን የትግራይን ህዝብ ጨምሮ በአገራችንና በመላው ህዝባችን ላይ የፈጸማቸው ወንጀሎችና ያደረሳቸው ሰቆቃዎች ተዘርዝረው የሚያልቁ አይደሉም::
ከነዚህ ወንጀሎች ሁሉ የከፋውና ምናልባትም የሚቀጥለውን ትውልድ ጭምር ዋጋ ያስከፍላል ተብሎ የሚፈራው ምዕራባዊያን ቅኝ ገዥዎች አህጉራችን አፍሪካን በተቀራመቱበት ወቅት የአገዛዝ ዘመናቸውን ለማራዘምና ቅኝ የገዙዋቸውን ህዝቦች ሃብትና ንብረት ለመዝረፍ እንዲመቻቸው የተጠቀሙበትን የከፋፍለህ ግዛ ፖሊስ በምድራችን ተግባራዊ በማድረግ ለዘመናት የተገነባውን የህዝብ አንድነትና የአገር ሉአላዊነት ሊያናጋ በሚችል መልኩ በዘር፤ በቋንቋና በሃይማኖት ተከፋፍለን የጎሪጥ እንድንተያይ የተፈጸመብን ደባ ነው::
በዚህ ደባ ምክንያት ዛሬ በአገራችን ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሆኔታ ኦሮሞነት፤ ሱማሌነት፤ ትግሬነት፤ አማራነት ፤ ስዳማነት፤ አፋርነት፤ ወላይታነት ፤ ከምባታነት ወዘተ ከዘግነት በላይ ገዝፎ የማንነት መለያና የፖለቲካ፤ የኢኮኖሚና ማህበራዊ መብቶች መሠረት ሆኖአል:: በዚህም የተነሳ የኦሮሞ ከብት አርቢ ለከብቶቹ ግጦሽ ፍለጋ ወደ ሱማሌ ድንበር ከተሻገረ እንደ ባዕድ ተቆጥሮ ተኩስ ይከፈትበታል፤ አፋር ወደ ኢሳ ከተሻገረ ይገደላል፤ ለቤነሻንጉል በተከለለ ክልል የሰፈረ የአማራ አርሶ አደር የደከመበትን አንጡራ ሃብት ተቀምቶ ይባረራል፤ አኝዋክ ለዘመናት ተከባብሮና ተቻችሎ ከኖረው ከኑዌር ወንድሙ ጋር እንዲጋጭ ተደርጎ በገላጋይነት ሥም የፈደራል ፖልስና የጸጥታ ሃይል በጅምላ እንዲጨፈጭፈው ይፈረድበታል :: በመልካም አስተዳደር እጦት የደረሰበትን መከራና ስቃይ አብሮ ሲጋፈጥ የኖረው የወልቃይት ጠገደ ህዝብ አንተ አማራ አንተ ትግሬ በሚል የዘር ክፍፍል ለመገዳደል ካራውን ስሎ ተቀምጦአል :: ይህ አልበቃ ብሎም የአንድ ብሄር አባላትን በጎሳ ሸንሽኖ የጉጂ ኦሮሞ ከአርስ ወንድሙ ጋር ደም እንዲቃባ ተደርጎአል:: የኦጋዴን የተለያዩ ጎሳዎችም ላይ እንዲሁ::
ወያኔ በጉልበት የጫነብን የመከፋፈልና የመለያየት አደጋ አንድ ቀን ሲያበቃ የነጻነት ብርሃን ፈንጥቆ በሠላምና በመቻቻል የምንኖርበት አገር እንኳ እንዳይኖረን በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች መጠነ ሰፊ የሆነ ድንግል መሬታችንን ለህንድ፤ ለቻይናና ለአረብ ከበርቴዎች በርካሽ ዋጋ በመቸብቸብ በገዛ አገራችን የባዕዳን አሽከሮች ሆነን እስከ ዘለአለሙ እንድንኖር መሠረት ተጥሎአል::
ይህ ሁሉ በደልና መከራ እንዲያበቃ በአገዛዙ ላይ የተቃውሞ ድምጹን ያሰማ ከሥራውና ከኑሮው ተፈናቅሎ በድህነት አረንቋ ውስጥ እንዲጣል አለያም እየታደነና የሽብርተኝነት ታፔላ እየተለጠፈበት ወደ የማጎሪያ ጥቢያዎች እንዲወረወር ተደርጎአል:: በዘርና በቋንቋ በተከለለልን ክልል በፈረቃ የሚደርስብንን አፈናና ሰቆቃ በህብረት ለመቃወም የሚደረጉ ጥረቶች በሙሉ “የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂ፤ ትምክህተኛ ፤ አክራሪ/ጽንፈኛ፤ ጸረ ልማት ወዘተ ” በሚሉ የማሸማቀቂያና የመወንጀያ ቃላቶች ጋጋታ እንዲደናቀፍ ለማድረግ ተሞክሮአል::
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጥር 2 ቀን 2007 አመተ ምህረት የፈጸሙት ውህደት ዋናው ምክንያት ከላይ የተዘረዘሩትን ግፎች ለማስቆም በተናጠል ከሚደረግ ትግል በህብረት የሚደረገው ትግል ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑ የፈጠረው ግንዛቤ ነው :: የወያኔ የጥቃት ክንዶች የፈረጠሙት በራሱ ጥንካሬ ወይም የሚተማመንበት ህዝባዊ ድጋፍ በደጀንነት ኖሮት ሳይሆን በኛ መከፋፈልና መለያየት ብቻ እንደሆነ ህዝባችን ከተረዳው ውሎ አድሮአል::
አርበኞች ግንቦት 7 በሚል መጠሪያ ሁለቱ ድርጅቶች በቅርቡ የፈጠሩት ውህደት ከድህረ ምርጫ 97 ጀምሮ ህዝባችን ከደረሰበት ስቆቃ ለመገላገል ተቃዋሚዎችን “ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” በማለት ሲያቀርብ ለኖረው የድረሱልኝ ጥሪ የተሰጠ የመጀመሪያው ተግባራዊ ምላሽ ነው:: ሁለቱም ድርጅቶች እስከ ዛሬ ምድር ላይ ያደራጁትን የሰው ሃይል ፤ እውቀትና ንብረት አዋህደው በአንድ አመራር ሥር ትግሉን ከዳር ለማድረስ መወሰናቸው በአላማና ግብ ለሚመሰሉዋቸው ሌሎች ተቃዋሚ ሃይሎች ብቻ ሳይሆን ወያኔን ከህዝብ ጫንቃ ላይ በማውረድ ፍትህና እኩልነት በአገራችን እንዲሰፍን እንታገላለን ለሚሉት ሃይሎች ሁሉ አርአያነት ያለው እርምጃ መሆኑ እየተነገረ ነው :: የአርበኞች ግንቦት 7 ውህደት በተፈጸመበት ሥነሥርዓት ላይ አገራቸውን ነጻ ለማውጣት ነፍጥ አንግበው ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ውስጥ የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ [ዴሚት] ሊቀመንበር አቶ ሞላ አስግዶም ፡ የአፋር ነጻነት ግንባር [አርዱፍ] ሊቀመንበር አቶ ኢብራሂም ሙሳ ፤የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ [ጋህነን] ሊቀመንበር አቶ ኦኬሎ አይዴድ ፡ የቤነሻንጉል ተወካይና የአድሃን ተወካዮች በየተራ የተናገሩት በአንድ የጋራ ግንባር ሥር ተሰባስቦ በገንዘብና በመሣሪያ ብዛት ተብቶ የህዝባችንን መከራና ስቃይ እድሜ እያራዘመ ያለውን የጥቂቶች አገዛዝ በሃይል የማንበርከክ አስፈላግነትና ወቅታዊነት ሁለቱ ድርጅቶች የፈጸሙት ውህደት ለትብብር ፈር ቀዳጅ መሆኑን አመላክቶአል :: አገራችንን ከመበታተን አደጋ ለመታደግ ወያኔ ባወጣቸው የአፈና ህጎች ተገዝተን ለውጥ ማምጣት አንችልም ያልን ሃይሎች እየተዋሃድንና እየተጣመርን በሄዱን ቁጥር አፈናና እንግልት ተቋቁመን እንታገላለን ያሉት ሃይሎችም በተናጠል ከሚደርስባቸው ጥቃት ለመገላገል ሲሉ ወደ ውህደትና ጥምረት ጎዳና ማቅናታቸው የማይቀር ነው::
ህዝባችን ላይ የደረሰው ግፍና መከራ ጻዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ባለበት በዚህን ሰዓት የአገሩ ጉዳይ አሳስቦት በፖለቲካ ድርጅቶች ዙሪያ የተሰባሰበ ወገን ሁሉ ለመቀራረብና ለመተባበር እያደረገ ያለው ጥረት ተስፋ ሰጪና አበረታች ሆኖአል:: በዚህ አጋጣሚ ላለፉት 24 አመታት ወያኔ በወገኖቻችን ላይ ለፈጸማቸው ሰቆቃዎች በመሣሪያነት ያገለገሉና እያገለገሉ ያሉ ወገኖች በሙሉ ከውህዱ አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አንድ የተላለፈላቸው ወገናዊ ጥሪ አለ:: ይህም ጥሪ እስከ ዛሬ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወይም ለሥራ ዋስትና ብላችሁ የዚህ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ መሳሪያ በመሆን በወገኖቻችሁ ላይ ግዲያ ፤ እስርና ግርፋት ስትፈጽሙ የኖራችሁ ሁሉ የበደላችሁትን ህዝብ ለመካስ የአገዛዙን ዕድሜ ለማሳጠር በምናደርገው የሞት ሽረት ትግል ላይ እንቅፋት ከመሆን እራሳችሁን አግልሉ ! የሚል ነው:: ትግላችን ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ገና ከመድረሱ ከህዝብ በዘረፉት ሃብትና ገንዘብ ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ወደ ባህር ማዶ ማሸሽ ለጀመሩት ስግብግብ አለቆችህ ምቾትና ድሎት ብለህ ይህ የመከራ ዘመን ሲያልፍ በሃላፊነት የሚያስጠይቅህን ወንጀል ለነጻነት በሚታገሉ ወገኖችህ ላይ እንዳትፈጽም ለአገር የመከላኪያ ሠራዊት፤ ለፖልስና የጸጥታ ሃይል አባላት ሁሉ ጥሪ ቀርቦአል::
የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ድል ማድረጋችንን ፈጽሞ የማንጠራጠር የነጻነት ታጋዮች በሙሉልብ የምንናገረው ወያኔ አገራችንን ለመበታተን የቻለውን ሁሉ ድንጋይ ቢፈነቅልም በአንድ የአመራር ጥላ ሥር ተሰባስበን አገራችንን ከተጋረጠባት የመበታተን አደጋ ለመታደግና እያንዳንዱ ዜጋ የሚኮራባት የበለጸገችና ሉአላዊነቷ የተረጋገጠ አገር ባለቤት ለመሆን የጀመርነው ትግል ግቡን እንደሚመታ ነው:: ለዚህ ደግሞ በቅርቡ የፈጸምነው ውህደትና ከሌሎች ጋር በጥምረት ጠላትን ለመፋለም የጀመርነው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ወቅታዊነት ለወገን ተስፋ ለጠላት መርዶ ነው::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Sunday, February 1, 2015

ሬድዋን ሁሴንና የወደቀው ክሱ !

February 1,2015
በኢትዮጵያችን ህግ ትርጉሟን አጥታ፤ፍትህም ተዋርዳ ከተጣለች የህወሃትን እድሜ ብታስቆጥርም እነርሱ ግን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ስለ ህግ የበላይነት ማውራታቸውን አላቆሙም። እነዚህ ቡድኖች የህግ የበላይነት ሲሉ እነርሱ ከፍ ብለው ከህግ በላይ፤ ከእነርሱ መንደር ያለሆነው ደግሞ ዝቅ ብሎ ከሥር ከጫማቸው ሥር ሁኖ እነርሱን ተሸክሞ የሚኖርበትን ሥርዓት ማስጠበቅ የሚችለውን ህግ ነው። እናንተን መሸከም ከበደኝ፤ ቀንበራችሁ ሰበረኝ የሚል ሰው ከተገኘ የሚጠብቀው ፍርድ “አሸባሪነት” ነው። ይህ የክፉዎችና የልበ ደንዳኖች ፍርድ ፍትህ ተብሎ በህወህቶች መንደር ይወደሳል። መፅሃፍ እንዲህ ይላል “ክፍዎች ሰዎች ፍርድን አያስተውሉም”። ህወሃቶች ባወጧቸው ህጎች የስንት ንፁሃን ዜጎች ቤት እንደፈረሰ፤ ስንት ህፃናት አሳዳጊ አልባ እንደሆኑ፤ ስንቶች አገራችውን ትተው ተሰደው እንደጠፉ ቆጥረን አንዘልቀውም። በህወሃት መንደር ህግ ዜጎችን ማጥቂያ እና ማስጨነቂያ መሣሪያ እንጂ የፍትህ ማስከበሪያ መሳሪያ አይደለም። በህወሃት ህግ ብዙ ዜጎች ጠፍተዋል፤ ብዙዎች ደግሞ በብዙ ጭንቀት እና መከራ ውስጥ ይገኛሉ።

በህወሃት መንደር የተሰባሰቡ ግለሰቦች እንደምን ያለ ብርቱ ጭለማ እና ድንቁርና ውስጥ እንደሚገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ማንሳት እንችላለን። ለአሁን ግን ማሰብ ካቆሙ ቅጥረኞች መካከል ሬድዋን ሁሴን የተባለው ግለሰብ የሆነውን እንመልከት። ሬድዋን ሁሴን፤ ጌቶቹ እና ሌሎች መሰሎቹ ያሉበትን ዘመን ረስተው ወይም መረዳት ተስኗቸው፤ ከስልጣኔ መንገድም ወጥተው እንዲሁ በጭለማ ዓለም እየተደናበሩ ይገኛሉ። ሬድዋን ሁሴን ያለበትን ዘመንና የያዘው የህዝብ ስልጣን የሚያስከትልበትን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤት መገንዘብ ስለተሳነው ቀና ብሎ ተናገረኝ ባላው ወጣት ላይ በአሜሪካን አገር ክስ መመሥረቱን ስንሰማ በብርቱ ተደንቀናል። አገራችንም በእንደነዚህ ዓይነት ማስተዋል በጎደላቸው ግለሰቦች የምትመራ መሆኑም በእጅጉ ያሳዝነናል።

ሬድዋን ሁሴንን በቨርጂኒያ አገረ ግዛት ያገኘው ወጣት ህወሃቶች በወገኖቹ ላይ የጫኑባቸው ሸክም ያሳመመው፤ በዚህም ህመም የተቆጣ ቁጣውንም በሰላም የመግለፅ መብቱ ያለ ገደብ የተከበረባት አገር ውስጥ ኗሪ ነው። ሬዲዋን ሁሴንን የመሰለ ራሱን ለምናምንቴ ነገር አሳልፎ የሸጠ ትንሽ ግለሰብ ይቅርና የሃያሏ አገር አሜሪካን ፕሬዝዳንትም ብዙ ወቀሳና ስድብ ይደርስበታል።ፕሬዝዳንቱም የህዝብ ተቀጣሪ መሆኑን ስለሚያውቅ ተወቀስኩ ወይም አንድ ዜጋ ተናገረኝ ብሎ የበቀል ሰይፉን አይመዝም። ፕሬዝዳንቱ ተሰደብኩ ብሎ ክፉ ቢናገር የሚከተለው መዘዝ ከስድቡ የበለጠ ጉዳት ስለሚያደርስበት ስድቡን መቻል እና መሸከም የሥራው አንዱ አካል ይሆናል።ህግ ባለበት አገር የአገሩ መሪ ህዝቡን ፈርቶ ይኖራል እንጂ፤ ህዝብ መሪውን ፈርቶ አይኖርም። ሬዲዋንና መሰሎቹ ግን እንዲህ አይደሉም። ህዝብን ረግጠውና አስፈራርተው መኖር የጎበዝ ተግባር ነው ብለው አምነው ተቀብለዋል።

ህወሃት ትንሹንም ትልቁንም ፈርቶ፤ ፍርሃቱ በወለደው ጭካኔ ዜጎችን ሁሉ አስሮ መኖር ልማዱ ሁኗል። በኢትዮጵያ ዜጎች ህወሃቶችን ፈርተው፤ ህወሃቶችም ዜጎችን አስፈራርተው የሚኖሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄ ሁኔታ ለማንም ወይም ለምንም እንደማይበጅ ለህወሃቶች ብንነግራቸውም ልቦናቸው በትዕቢት ታውሯልና አይሰሙንም። ሬድዋን ሁሴንም የዚህ መራራ ትዕቢት ትሩፋት ነው። እንደምን ሁኖ ቀና ብለው ያዩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ይናገሩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ስሜ በገበያ መሃል ይነሳል የሚል ትዕቢት ስለተፀናወተው ክስ መሠረተ፤ ክሱ ግን በህግ ፊት ሚዛን የማይደፋ በመሆኑ በአቃቤ ህጉ ውድቅ ተደረገ። ሬዲዋንም የፍትህን መራራ ፅዋ ተጎንጭቶ ሊውጣት ግድ ሆነበት። የህወሃት ቅጥረኞችና ህወሃቶች ውድቅ ከሆነው ከሬድዋን ህሴን ክስ ልትማሩ የሚገባችሁ የህግ የበላይነት በሰፈነበት አገር እናንተ ከተራው ዜጎች እኩል እንጂ የበላይ ልትሆኑ እንደማትችሉ፤ ከመጋረጃው ጀርባ ሁናችሁ ፍትህን የምትጠመዝዙበት እጃችሁ እንደሚታሰር እና ገና ወደፊት ደግሞ የእጃችሁን እንደምታገኙ ነው። እናንተን ከተራው ዜጋ እኩል የሚያደርግ ህግ ሲፈጠር የታጠቃችሁት ጠብመንጂያ የሸንበቆ ምርኩዝ፤ የመኖሪያ ድንኳን የሆናችሁ ማን አለብኝነታችሁ ደግሞ ፀሃይ እንዳየው ጤዛ እንደሚተን ልብ ልትሉ ይገባል። ሬዲዋንን የተናገረው ወጣት ኢትዮጵያ ውስጥ ሁኖ ቢሆን ኑሮ ዛሬ እነሬዳዋን ፈተው በሚለቋቸው ውሾች ሊደርስበት የሚችለውን ስቃይ ስናስበው ይዘገንነናል። ከባህር ማዶ መሆኑ ከሥጋዊ ስቃይ አድኖታል።

እንግዲህ ህወሃቶች የምትፈፅሟቸው ግፎች በየደረሳችሁበት እየተከታተሉ እረፍት ማሳጣታቸውን የሚያቆሙ አይሆንም። የምትሠሯቸው ግፎች የሚያሳድዱት እናንተን ብቻ አይደለም። ከእናንተ አብራክ የሚፈጠሩ ልጆቻችሁንም ጭምር የክፉ ሥራዎቻችሁ ሰለባዎች ከመሆን አያመልጡም። ልጆቻችሁ ተሳቀው ከህዝብ ዓይንና ጆሮ ተደብቀው መኖር ዕድል ፈንታቸው ይሆናል። እናንተ የምትፈፅሙት ወንጀል ለልጆቻችሁ ኩራት ሳይሆን እፍረት፤ ክብር ሳይሆን ውረደት ሁኖ ይቆያቸዋል። ቢያንስ ለልጆቻችሁ ሠላም ስትሉ ከእኩይ ድርጊታችሁ መታቀብ ይሻላችሁ ነበር። እናንተ ግን ለትውልዱ ሠላም የሚሻለውን ትታችሁ የጥፋቱንና የደም መፋሰሱን መንገድ መርጣችኋልና ወዮታ አለባችሁ።

እናንተን መታገል ከስጋና ከደም ጋር የሚደረግ ትግል ብቻ አይደለም። የምትፈፅሟቸው ግፎች ከሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈልቁ ብቻ አይመስልም።ከእናንተ ጋር የሚሰራ ሌላ የማይታይ የክፋት አባት ያለ እስከሚመስለን ድረስ ግፋችሁ አንገፍግፎናል። ይህን ግፍ ዝም ብለን የምናይ አይመሰላችሁ። ሊከፈል የሚገባውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተናል። ወጣቶችም ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱባቸው ኮረብቶች ላይ ተሰማርተዋል። ክፉውን ለመቃወም፤ ደም አፍሳሹን ለማስቆም፤ ሌባውን ተው ለማለት፤ ትዕቢተኛውን አደብ ለማስያዝ፤ የነፃነት ቀበኛውን ለማስተማር ሰይፋቸው ከአፎቱ ተስማምቶ ተዘጋጅቷል።

የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች ሆይ !

ህወሃቶች በዜጎችቻን ላይ የሚፈፅሙትን ግፍ ለእናንተ መንገር ለቀባሪው እንደ ማርዳት ይሆንብናል።የእነዚህ ቡድኖች ግፍ ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰሰ ነው።የአገሪቷን ታሪክ አንድ በአንድ ለማጥፋት እየሠሩ ይገኛሉ-በየቦታው በእሳት የሚቃጠሉት ታሪካዊ አምባዎቻችን የአገሪቷን ታሪክ የማጥፋት ዘመቻ አካል ነው።ዜጎች አገር አልባ እንዲሆኑ ተደርገዋል፤ አብሮ በኖረው ህዝብ መካከል የሚዘራው የጥላቻ ዘር ለአገራችን አደጋ ሁኖ ተደንቅሯል። አገራችን ታሪኳ በሚመሰክርላት ሥፍራ ላይ እንዳትሆን፤ ለአፍሪካ ቀንድም ሆነ በአጠቃላይ ለዓለም ሠላም መጫወት የሚግባትን ሚና እንዳታከናውን ተደርጋለች። በተቃራኒው የግጭት አምባ፤ የችጋር ምሳሌ፤ የስደት ምልክት ሁና ከውዳቂ መንግስታት ተርታ ገብታለች። ይሄ ሁሉ እርግማን በህወሃት ምክንያት የመጣ ነው።

እኛ በአገራችን ላይ የተተከለውን ህወሃት የተባለውን እርግማን ነቅለን ለመጣል የምንችለውን ሁሉ እያደርገን ነው። ህወሃቶች የነፃነትን ዋጋ ተረድተው፤ ለፍትህ ክብር ሰጥተው፤ ዜጎችን አክብረው፤እኛም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር እኩል ነን። ከማንም አንበልጥም፤ ሌላውም ከእኛ አያንስም ብለው በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመወያየት ፍርሃታቸው እና ድንቁርናቸው ቢፈቅድላቸው ለሁላችንም መልካም ነበር። ይህ መልካም ነገር ግን የእኛ ምኞት ብቻ ሁኖ ቀርቷል።ህወሃቶች የተፀናወታችው ትዕቢት የሰይጣን ትዕቢት ስለሆነ እንዲሁ በቀላሉ በጄ የሚሉ አይሆኑም። እኛ የቀረን አንድ መንገድ በማንኛውም መንገድ አገራችንን ከጥፋት ማዳን ብቻ ነው። ይህም ታሪካዊ ግዴታችን ሁኗል።

ይህን አገርን የማዳን ታሪካዊ ግዴታ የዚህ ቡድን ወይም ደግሞ የዚያ አካል ብቻ ተደርጎ መወሰድ ያለበት ተግባር አይደለም። እያንዳንዱ ማሰብ የሚችል እና ለራሱ ትንሽ ክብር ያለው ዜጋ ሁሉ ኢትዮጵያን ለመታደግ የሚችለውን ጠጠር መወረወር ይጠበቅበታል። ኢትዮጵያ ሬድዋን ሁሴንን በመሳሰሉ ምናምንቴዎች ስትዋረድ እጅን አጣምሮ ቁሞ መታዘብ ትክክለኛ ተግባር አይሆንም። የአገሪቷ ድሃ ዜጎች ስቃያቸው በዝቶ እና ጭንቀታቸው ልክ አጥቶ እያየን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ካሉ ዜጎች ጋር መተባበሪያ ግዜው አሁን ነው።

እኛ አርበኞች-ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ አገራችን ከገባችበት የውርደት አዘቅት ውስጥ ለማውጣት የጀመርነውን ትግል እለት እለት እያደስነው፤ እለት እለት እያሰፋነው፤ እለት እለት እያሳደግነው ቀጥለናል። እኛ ዓይናችን እያየ ህዝባችን አይዋረድም፤ አገራችንም ከሥፍራዋ በታች ስትሆን ዝም አንልም።የሚከፈለውን ማንኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፍለ አናቅማም። በአያት ቅደመ አያቶቻችን ደም ተከብራ የኖረች አገር ዳግም በእኛ ደም ተከብራ ትኖራለች። ቀጣዩ ትውልድም የተከበረች አገር ተርክቦ፤ እርሱም ተከብሮ ይኖር ዘንድ እኛ እንሰራለን እግዚአብሄርም ያከናውንልናል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!