Friday, July 25, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችን ማሰሩ እና ማዋከቡ ቀጥሏል

July 25/2014
በኢየሩሳሌም ተስፋው (አዲስ አበባ)
ዛሬ የወይኒ ፍ/ቤት ቀጠሮ ስለሆነ በጠዋት የሰማያዊ ልጆች ከያለንበት ተሰባስበን ሜክሲኮ ወደሚገኘው እንደኛ ደረጃ ፍ/ቤት ሄድን ተሰባስበን ግቢ ውስጥ ቀመን ሳለ እነወይኒን የያዘው መኪና ሲመጣ ባለፈው ያየነውን ሽብር መንዛት ጀመሩ መብታችን አይደል እንዴ መከታተል እንዴት ከግቢ ታስወጡናላችሁ? አልን ከመሃላችን አቤል ኤፍሬምን ና ብለው ወደ ውስጥ አስገቡት እንዴ ለምን ትወስዱታላችሁ ስንል ቆይ አናግሬያቸው መጣሁ ብሎን ገባ የነወይኒ መኪናም ውደውስጥ ገብቶ መውረድ ጀመሩ ወይኒዬ ጭንቅላቷ እና እጇ እንደታሸገ ነው ፊቷ ላይ እሚነበበው ጥንካሬ አሁንም እንዳለ ቢሆንም አካሏ ግን እንደተጎዳ በደንብ ያስታውቃል ከፍተኛ ድብደባ እየደረሰባት እንደሆነ ትናንት ለነ ጌች ነግራቸዋለች እጥፍጥፍ ብላ አንገቷን ደፍታ ስትቀመጥ ሳያት የእውነት ከዚች አገር መፈጠራችንን ነው የጠላሁት ወይኒ እያየችን ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ መልኩ እንባዋ ይፈስ ጀመር ጭንቅላቷን እና እጇን እየነካች የስቃይ ፊት አሳየችኝ እሱንም ፖሊሶቹ እንዳይዋት በመሳቀቅ ነው በዚህ ሁሉ ስቃይ መሃል እጇን እየሳመች እንደምትወደን ደጋግማ ታሳየናለች።Semayawi party member Abel Ephrem arrested
ችሎት ገቡ ለሐምሌ 24 እንደተቀጠረ ከዛሬ ጀምሮ ሰው እንዲጠይቀት ፍ/ቤቱ እንዳዘዘ ነገረችን የነሱ መኪና ሲወጣ ወደ ቀጣዩ እስረኛ ጓዳችን ተጠግተን ለመጠየቅ ስንሞክር ሁከት ለመፍጠር ሙከራ አድርጓል ስለዚህ ሶስተኛ ወስደንዋል እዛ ሂዱና ጠይቁ አለን አንድ ጥጋብ አናቱ ላይ የወጣ ፖሊስ እኮ ወንጀሉ ምንድነው? ሁከት መፍጠር ምንም አይነት ሁከት አልፈጠረም መብቱን ነው የጠየቀው ያ ደግሞ ወንጀል ከሆነ ሁላችንም ወንጀለኞች ነን ሁላችንንም እሰሩን አቤል ምንም አይነት ወንጀል አልሰራም ብለን ሊቀ መንበራችን ኢ/ር ይልቃልን ጨምሮ ወደ 30 እምንሆን የሰማያዊ ልጆች ተሰብስበን ገባን።
ከዛ በኋላ ምን ብዬ ልንገራችሁ ሁሉም እየተነሳ አፉን ይከፍትብን ጀምር እደፋሃለው እገልሃለው ተው አታስፈራራኝ ይለዋል ፍቅረማርያም ማስፈራራት ነው የገረመህ በድርጊት አሳይሃለው አለው ብርሃኑን ደግሞ ከዚህ በፊት እዛ ታስሮ ሳለ እሚያውቀው አንድ ፖሊስ እንተ ቤቱን ታውቀዋለህ አይደል አሁንም አስገባሃለው አለው በጣም የሚገርመው እንዲህ የሚደነፉት እኮ ተራ ፖሊሶች ናቸው።
ምንም አይነት ጥፋት የለብንም መብታችንን ነው የጠየቅነው ስንል መብታችሁን እዚህ አይደለም እምጠይቁት አለን ቆይ ፍ/ቤት መብታችንን ያልጠየቅን የት ነው እምንጠይቀው ታድያ? ሁልሽም እዛ ወስደን ስንቀጠቅጥሸ ጥጋብሽ ይወጣልሻል አለ ተሰብስበን ተቀመጥን እነሱም ይደነፋሉ ይህ ስርዓት ምን አይነት ደረጃ ላይ እንደደርሰ እና የራሱን እድሜ በራሱ አያሳጠረ መሆኑን እያሰብኩ በእልህ ስሜት ተቀምጠናል በተደጋጋሚ ያስፈራሩናል እንድንወጣ ካለበለዚያ እሚመጣው ነገር አስፈሪ መሆኑን ይነግሩናል በቃ እሚመጣውን ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነን ውሰዱን አታስፈራሩን በቃ አልን፣ ይልቃልን ጠሩት እና ያዋሩት ጀመር ይህ ፍ/ቤት መሆኑን መቀመጥ እንደማንችል ሰዓት ስለደረሰ የፍ/ቤቱ ግቢ ሊዘጋ መሆኑን እና በሰላም እንድንወጣ ይህ ህገወጥ ድርጊት መሆኑን ብቻ ብዙ ነገር ለፈለፉ ስለአቤል ጉዳይ ሔደን እዛ እንድንጠይቅ ነግረውት መጣ እኛም ወጣን አቤሎን ይዘውት ሄዱ አዎ ተራ በተራ እየለቀሙ ያስገቡናል የሁላችንም ቤት እዛው ነው የጊዜ ጉዳይ ነው።
“በሉ እናንተም ሂዱ የኛም ወደዛው ነው ወትሮም መንገደኛ ፊት እና ኋላ ነው” ቀጣይ ተረኛ ደግሞ ማን ይሆን?
ላንቺ ነው አገሬ ላንቺ ነው
ላንቺ ነው ኢትዮጵያ ላንቺ ነው
አዎ ይህ ሁሉ ስቃይ እየደረሰባቸው ያለው አንቺን በማለታቸው ብቻ ነው!

የወያኔ የግፍ ማሰቃያ የቶርቸር ዓይነቶች በማዕከላዊ እስር ቤት

July 25, 2014

የጥቁር ሽብር ሂደት እና የጋዜጠኛ አብይ አፈወርቅ መልዕክት

July24/2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ለዛሬው ወደ እስር ቤት አካባቢ እንወስዳችኋለን። መቼም በኢትዮጵያ የሚገኙ እስር ቤቶች ሰውን ለማረም ሳይሆን፤ በአመለካከት የተለየን ሰው ለማሰቃየት ተብለው የተሰሩ ነው የሚመስለው። በአሁኑ ወቅት ሰርቆ እና ሰው ገድሎ እስር ቤት ከገባ ሰው ይልቅ ኢህአዴግን ወቅሶ የጻፈ እና የተናገረ ሰው ብዙ ስቃይ እንደሚደርስበት ምንም መጠያየቅ ወይም መረጃ መቀያየር አያስፈልግም። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሚደረጉት በህግ ሽፋን ነው። የህጉም አንቀጽ “ሽብርተኝነት” መሆኑ በግልጽ ተደንግጎ በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ወጥቷል። ይህ መንግስት በህዝቡ ላይ የሚያደርሰው ጥቃት “ጥቁር ሽብር” የሚል ስያሜን አግኝቷል። እናም የሰሞኑ የጥቁር ሽብር ሰለባዎችን ጉዳይ እናስነብባችሁ እና በመጨረሻም አንድ ቅንብር እንጋብዛችኋለን።
በቅድሚያ አቤት ያደረሰንን አዲሰ መረጃ እናካፍላችሁ። በቅርቡ የታሰሩትን የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች አስመልክቶ እንዲህ ይላል።
ወያኔ በህገ ወጥ እስር በማእከላዊ እያሰቃያቸው የሚገኙት የሺዋሰ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ሃብታሙ አያሌውና ዳንኤል ሺበሺ በተለያዩ ጨለማ ክፍሎች ከየብቻ ታስረው እንደሚገኙና ሌሊት ሌሊት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ ለእስር ቤቱ ቅርብ ከሆኑ ምንጮች ያገኘኋቸው መረጃዎች አረጋግጠውልኛል፡፡ እነዚህ ሰላማዊ ታጋዮች በየቀኑ በሚደረግባቸው ድብደባ እና ስቃይ ምክንያት የሰውነታቸው ክብደት በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የሙስሊሙ ድምጽ የሆነው ቢ.ቢ.ኤን “መንግስት በኮሚቴዎቻችን ቤተ ሰቦች ላይ የተለያየ ጥቃት እና በደል እያደረሰ ነው፡ በማለት
በጥይት የተመታው የኡስታዝ ያሲን ኑሩ ወንድም ወደ ማእከላዊ የተወሰደ መሆኑን እንዲህ ሲል መረጃውን ለቋል።
ጁምዓ ሐምሌ 11 ቀን 2006 የመንግስት ሃይሎች በአንዋር መስጂድ በሰላማዊ መንገድ ድምጹን ሊያሰማ የተሰባሰበው ህዝበ ሙስሊም ላይ በወሰዱት ኢ-ሰብኣዊ የ‹‹ጥቁር ሽብር›› የሃይል እርምጃ በጥይት የተመታው የኡስታዝ ያሲን ኑሩ ወንድም ወደ ማእከላዊ ተወሰደ::
BBN ቢቢኤን የናንተው ድምፅ
በመጨረሻም የሙያ ባልደረባችን የሆነው ጋዜጠኛ አብይ አፈወርቅ ዛሬ ከአውስትራልያ የላከልን መልእክት በኢትዮጵያ ውስጥ እየደረሰ ያለውን ጥቁር ሽብር በዝርዝር ገልጿል።
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጸሙ አሰቃቂ የማሰቃያ (torture) አይነቶችን በሚመለከት የተጠናቀረውን ልዩ ዝግጅት ጋዜጠኛ አቢይ አፈወርቅ (አውስትራሊያ -ሲድኒ) እንዲህ ያቀርበዋል።

Thursday, July 24, 2014

የትግል ጓዶቼን ባሰብኩ ጊዜ! (ኣቶ ኣስራት ኣብርሃ – ኣንድነት ፓርቲ)

July24/2014
ሀብታሙ አያሌውና ዳንኤል ሺበሺ የማውቃቸው አንድነትን ከመቀላቀሌ ቀደም ብሎ ነው። የመድረክ ስራ አስፈፃሚ ሆኘ በምስራበት ወቅት የባለራዕይ ወጣቶች ሀያ ሁለት አከባቢ በሚገኝ አንድ ሆቴል አድርጎት በነበረው ስብሰባ ለመገኘት በሄድኩ ጊዜ ነበር ሀብታሙን ለመጀምሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት። የባለራዕይ ወጣቶች እንዲያ ተሰባስበው ስለሀገገር ጉዳይ ሲመክሩ ስመለከት ተስፋ ነበር የታየኝና ስሜቴን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር። አዲሱ ትውልድ በራሱ ጉዳይ ራሱን ችሎ ሲመክር በህይወቴ ለመጀመርያ ጊዜ ያየሁበት ቀን በመሆኑ ነው ደስታዬ እጥፍ ድርብ ያደረገው። ከስልሳው ትውልድ ተፅዕኖ የተላቀቀ ፍፅም አዲስ የሆነ አስተተሳስብ ያለው፤ በአከባቢያዊነት ወይም በቋንቋ ሳይሆን በሀሳብ በኢትዮጵያዊነት የተሰባሰበ፤ አንድነታችን ከልዩነታችን በላይ ነው የየሚል አዲስ ትውልድና አደረጃጀት መሪ ሆኖ ሳገኘው ለሀብታሙና ለአባላቱ አድናቆቴን የምገልፅበት ቋንቋም ሆነ አቅም አልነበረኝም። ንግግር እንንዳደርግ ስጋበዝ “ይሄ ተቋም የወደፊት የሀገራችን መሪዎች የሚፈጠሩበት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ” ነበር ያልኩት፤ በኋላ የተወሰኑ በአንድነት ሳገኛቸው ደስ ብሎኛል።
Habtamu Ayalew
Habtamu Ayalew
ሀብታሙ በተለያዩ ጊዜያት ንግግር ሲያደርግ ተመልክቸዋለሁ አንደበተ ርቱዕ የሆነ የፖለቲካ ሰው ነው፤ በተለይ በፀረ ሽብር አዋጁ ላይ በቴሌብዥን ቀርቦ ያደረገው ክርክር ብዙ ሰው የሚያስታውሰው ይመስለኛል። የፖለቲካ እስረኞችን ለመጠይቅ ወደ ዝዋይ በሄድን ጊዜ አንድ ወጣት በቴሌብዥን አይቼሀለሁ ሲለው ስምቻለሁ።
ሀብታሙ ባለትዳርና የልጅ አባትም ነው። ልጁ ማታ ማታ “ሀብታሙ ይመጣል ተይ በሩን አትዝጊው!” እያለች እናቷን እንደምታስቸግር ሰማሁ፣ የልጅ ነገር ልጅ ያለው ነውና የሚያውቀው እንደልጅ አባት ሆነህ ስታይው ያማል!
ዳንኤል ሽበሺ እጅግ የሚገርም ሰው ነው። ዓረና ወደ አንድነት እንዲመጣ ብጣም ይፈልግ ነበርና በዚህ ጉዳይ ላይ ከእኔ ጋር በተደጋጋሚ ተነጋግረናል፤ከእኔ የአቶ ገብሩ አስራት ስልክ ውስዶ ተቀጣጥረው አነጋግሮታል፤ አንድነትን የሁሉም ኢትዮጵያውያን ፓርቲ የማድረጉ ሂደት ጥንክረው ሲሰሩ ከነበሩ የአንድነት ሰዎች ዳንኤል አንዱ ነው። በደቡብ ኢትዮጵያ አንድነትን በሁለት እግሩ እንዲቆም ብዙ ፅህፈት ቤቶችና አባላት እንዲኖሩት ጊዜው፣ ገንዘቡንና ጉልበቱን ሳይሰስት የሰዋ ምርጥ የአንድነት ልጅ ነው ዳንኤል ሸሺበሺ! በዚህ ላይ የቁጫ ህዝብ እንደህዝብ እንዲታወቅቅ ያደረገ፤ የቁጫ ህዝብ ታጋይና የሰብኣዊ መብት ተማጓች ነው።
Daniel Shibeshi
Daniel Shibeshi
ዳንኤል ሺበሺ ለእኔ የትግል አጋሬ ብቻ አይደለም፤ አንድ ሰፈር ስለነበር ጓደኛዬም ነው። አንዳንድ ጊዜ አየር ጤና በሚገኘው ሳሚ ካፌ እየተናኘን ሻይ ቡና እንል ነበር። ከታሰረ በኋላ ሳሚ ካፌ ጭር ብሎብኛል፤ እናም ወደዚያ አልሄድም፤ ጥሩ ስሜትም አይሰማኝም።
የዳንኤል ቤተሰቦች እሱን ለመጠየቅ ወደ ማዕከላዊ በሄዱ ጊዜ “እንዴት ነው መገናኘት አይቻልም ወይ?” ብለው ጠባቂዎቹ ቢጠይቋቸው፤ ፌስቡክ እንዲጠቀሙ ስለተፈቀደላቸው በፌስቡክ ተከታተሉ እንዳሏቸው ሰማሁ፤ እውነት ፌስቡክ በማዕከላዊ መጠቀም የሚቻል ቢሆን ኖሮ እኔ ራሴ እሰሩኝ ብዬ እሄድ ነበር። ምክንያቱም ውጭ ገንዘብ እየከፈልኩ ነው ኢንተርኔት የምጠቀመው። እስሩ እንደሆነ አሁንስ መቼ ነፃ ሆንኩ! በሰፊው ስርቤት አይደለ ያለሁት!
እንግዲህ እስሩ እየቀጠለ ነው፤ አንንዷለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮነን፣ ርዕዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ፤ በቀለ ገርባ፣ ውብሸት ታዬ፤ የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት፤ ዞን ዘጠኝ፤ አብርሀ ደስታ፣ ሀብታሙ አያሌው፤ የሽዋስ ሌሎችም በርካታ ዜጎች በሽብርተኝነት ስም በእስር እየማቀቁ ይገኛሉ፤ እንግዲህ ሽብርተኛ ማለት እኔ እንደሚገባኝ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉዳት ያደረሰ ወይም ቦንብ ያፈነዳ እንደሆነ ነው! ኢህአዴግ ሽብርተኛ የሚለው ግን የእርሱን ስርዓት በሰላማዊም ሆነ በማነኛውም መንገድ የሚቃወሙት ነው! በዚህ ጉዳይ ላይ እርሱ እንደ መንግስት እኛ እንደ ዜጋ እኮ መግባባት አልቻልንም። በመሆኑም እስርን ራሱ እንደ አንድ የሰላማዊ ትግል ስልት እንወስደው ዘንድ ነው የምንገደደው!
አብርሃ ደስታን ባሰብኩ ጊዜ!
Abraha Desta
Abraha Desta
በ2003 ዓ.ም. አጋማሽ በአንዱ ዕለት መቀሌ በሚገኘው የዓረና ዋና ፅህፈት ፀሀፊዬ በአጋጣሚ ስላልነበረች ብቻዬ ቁጭ ብያለሁ። ከሰዓት ነበር፤ በዚህ ጊዜ አንድ ሰው መጣ፤ ስሙንና መቀሌ ዩኒቨርሲቲ እንደሚሰራ ነገረኝ። በማስከተልም አባል ለመሆን እንደመጣ አስረዳኝ፤ እኔም የፓርቲውን ህገ ደንብና ፕሮግራም በመሰጠት በመጀመርያ እነዚህን አንብብና ከዚያ የአባልነት ፎርም ትሞላለህ አልኩት። ቀድሞ አግኝቷቸው ኖሮ አይቸዋለሁ አለኝ። እንግዲያውም በጣም ጥሩ ብዬ የአባልነት ፎርም ሰጥቼው ሞላ። ያ ሰው አብርሃ ደስታ ነበር። ከዚያ በኋላ በተመደበበት መሰረታዊ ድርጅት ውስጥ በንቃት ከመሳተፉም በላይ ለአባላት ስልጠና በመስጠት በእኩል ጥሩ አስተዋፅኦ ማድረግ ጀምሮ ነበር። ከዚያ በኋላ እኔ ወደ አዲስ አበባ በመምጣቴ በየጊዜው መገናኘታችን ቢቀርም አዲስ አበባ ሲመጣ አንድ ሁለት ጊዜ አግኝቼዋለሁ፤ ሁልጊዜ ስንገናኝ ባደረግናቸው ውይይቶች ጥሩ ተግባቢና ሀሳብ ለመቀበል የማያዳግትው ሰው ሆኖ ነው ያገኘሁት። በነገራችን ላይ ብዙ ሰው የአረና አባል መሆኑ ያወቀው በአረና ሶስተኛ ጉባኤ አመራር ሆኖ በተመረጠ ጊዜ ነበር።
በነበረው ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት የትግራይ ህዝብ፤ በተለይ ደግሞ ምንም የሚዲያ እድል የሌላቸው የክልሉ ገበሬዎች ድምፅ ሆኖ አገልግለዋል፤ በስርዓቱ እስኪታሰር ድረስ። ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነን በትናንትናው ዕለት ሕድሮም የሚባል የአረና አባል ከወቅሮ አፅቢ ደውሎ እየደረሰባቸው ስላለው ሰቆቃ ነገረኝ፤ ሌሊት የአረና አባላት ሲደበደቡና ሲጨሁ በድምፅ የተቀዳውን አሰማኝና “አብርሃ ነበር ድምፃችን፤ እሱ ታሰረብን” ሲለኝ እንባ ነው የተናነቀኝ። አሁን ጥያቄው ስርዓቱ አብርሃን በማሰር የህዝቡን የፍትህና የነጻነት ጥያቄ ዝም ማሰኘት ይችላል ወይስ አይችልም የሚለው ነው። በማህበራዊው ሚዲያ ብዙ አዳዲስ ወጣቶች እያየሁ ነው፤ ስለዚህ ትግሉ ተጠናክሯል ማለት ነው ብዬ እንዳስብ አድርጎኛል!

ምርቃት ወዲህ ሥራ ወዲያ

July24/2014
(በላይ ማናዬ)
gaduation


አሁን ላይ በሐገራችን የተገነቡና እየተገነቡ ያሉ ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ደረጃዎች የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ጨምሯል፡፡ በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርትን በነባርና አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች በኩል ትምህርታቸውን ተከታትለው እየተመረቁ የሚወጡ ተማሪዎች (ምሩቃን) ቁጥር በዚያው ልክ እያደገ ይገኛል፡፡ በዚህ አመት ብቻ እንኳ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የተመራቂዎች ቁጥር ከ60 ሺህ በላይ እንደሆነ ይፋ ሆኗል፡፡ ይህ ቁጥር በግል ኮሌጆችና በተለያዩ መለስተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን የተከታተሉትን አይጨምርም፡፡
የትምህርት ተቋማትም ሆነ በእነዚህ ተቋማት ገብተው ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች ቁጥር መጨመሩ ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ዳሩ ግን እነዚህ ተማሪዎች በምን ሁኔታ ትምህርታቸውን ተከታትለው እንደሚወጡ ሲታይና ከምረቃ በኋላም ያለውን የሥራ ጊዜ ሲገናዘብ የቁጥሩ መጨመር ፋይዳ ቢስ ሆኖ ይገኛል፡፡ በመንግስት በኩል ውግዘት የገጠመው ሥራ ፍለጋ እና በቃል የሚሽሞነሞነው ስራ ፈጠራ በተመራቂዎች ላይ ያለውን ተጽዕኖ ማየቱ ብቻ ለዚህ እንደ አስረጅ የሚጠቀስ ይሆናል፡፡ ምሩቃን በአካዳሚ ከሚያስመዘግቡት ጥሩ ውጤት ይልቅ የኢህአዴግ ‹ግሬድ› ከፍተኛ ዋጋ በተሰጠበት በአሁኑ ጊዜ በትምህርት ብቁ ሆነው ለመውጣትና ሥራ ፈጣሪ ለመሆን ስንቶች እንደሚችሉ መጠየቁም እውነታውን ለመረዳት ያስችላል፡፡
ሥራ ለመፍጠር . . .
ሥራ ፈጠራ በአየር ላይ የቆመ ቅዠት ሳይሆን በምድር የወረደ እውነታ መሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው፡፡ አሁን ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሥራ ፈጠራ ሲል ኮብል ስቶን መቀጥቀጥን፣ ዶሮ ማርባትን እና የመሳሰሉትን የከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት የማይጠይቁትን ማለቱ እንደሆነ በተግባር ባለፉት አመታት የታየ መሆኑን ማስታወስ ይገባል፡፡ የዩኒቨርሲቲ ትምህርትን ተከታትሎ ወደ ድንጋይ መጥረብ የሚሰማራ ሰው እንዴት ሥራ ፈጠራ ላይ ተሰማርቷል ሊባል እንደሚችል ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ በእኔ እምነት ይህን አይነት ሥራ ለመስራት አስራ አምስትና ከዚያ በላይ ዓመታትን በትምህርት ቤት ማሳለፉ ኪሳራ ነው፡፡ ኮብል ስቶን መጥረብ የሚናቅ ሥራ አይደለም፤ የከፍተኛ ትምህርት ዝግጅትን ግን አይጠይቅም፡፡
ስለሆነም ኮብል ስቶን ጠረባ ላይ የተሰማራ አንድ የዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ሥራ ፈጠረ ሳይሆን የሚመጥነውን ሥራ በሀገሩ አጣ ነው ሊባል የሚችለው፤ አሊያ ደግሞ በትምህርት ቆይታው ወቅት አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት እንዲጨብጥ አልተደረገም ማለት ነው፡፡ በእርግጥ ምሩቃን ሥራ ፈጣሪዎች ቢሆኑ እሰየው ነው፤ የሚበረታታም ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ግን ሥራ ፈጣሪ የሰው ኃይል እንዲኖር ካስፈለገ (በእኔ እይታ) ሁለት መሰረታዊ ሁናቴዎች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
አንደኛው ምሩቃን በትምህርት ቆይታቸው ወቅት ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን የአካዳሚያዊና የተግባር እውቀትና ክህሎት በሚገባ ታጥቀው መውጣት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህም ጥራት ያለው ትምህርትን ተግባራዊ የሚያደርግ ፖሊሲ ሊኖር ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም ግን በተቃራኒው አሁን ያለው የትምህርት ጥራት የሚያወላዳ እንዳልሆነ ኢህአዴግም ራሱ የማይክደው ሀቅ ነው፡፡ ስለሆነም ሥራ ፈጣሪ የሰው ኃይልን ለማፍራት ቆንጆ የትምህርት ፖሊሲን መቅረጽና ለትምህርት ዘርፉ ተገቢውን ትኩረት መስጠትን ግድ ይላል፡፡
ቁጥር ብቻውን ግብ አይደለም፤ ተማሪዎች በካድሬነት ተመልምለው፣ ትምህርትን ችላ ብለው፣ የጥገኝነትንና የጥቅመኝነትን አስተሳሰብ ሳይሆን በሚያገኙት ትምህርት ብቁ ሆነውና እውቀትን ታጥቀው ነው ወደ ስራው ዓለም እንዲገቡ መደረግ የሚኖርባቸው፡፡ አሁን ላይ ይህ ሲሆን አይታይም፡፡ ይህን የተማሪዎችን ብቃት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ዩኒቨርሲቲዎችም ያሉ አይመስልም፡፡ ቀደም ሲል የዩኒቨርሲቲዎችን ቁጥር መጨመር አንስተናል፤ ሆኖም ዩኒቨርሲቲዎችን በየመንደሩ መገንባት ብቻ ተፈላጊውን ውጤት አያስገኝም፡፡ በቅድሚያ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች ምቹና አስፈላጊውን ሁሉ ግብዓት ያሟሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
hire meይህም ብቻ ሳይሆን ምሩቃን ሥራ ፈጣሪ ሆነው እንዲወጡ ካስፈለገ የመምህራንን ብቃት ማሳደግ ላይም በትኩረት መስራትን ይጠይቃል፡፡ መምህራን ከማናቸውም የፖለቲካ ተጽዕኖ ነጻ ሆነው ሥራቸውን እንዲያከናውኑ መፍቀድና ማስቻል፣ እንዲሁም ራሳቸውን በየጊዜው በተከታታይ የትምህርት እድል እንዲያበቁ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አስፈላጊ ይሆናል፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የተመሰረቱ መምህራንንና የትምህርት አስተዳደርን መገንባት ከተቻለ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት በማካበት ሥራ ለመፍጠር የሚያስችላቸው ደረጃ ላይ እንዲገኙ ማስቻል ይቻላል ማለት ነው፡
በሁለተኛ ደረጃ ምሩቃን ተገቢውን እውቀትና ክህሎት ይዘው መጥተውም ቢሆን ለሥራ ፈጠራ ሂደታቸው አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዩች ሊመቻቹላቸው የተገባ ይሆናል፡፡ ለአብነትም ምሩቃን በአዲስ ሥራ ላይ ይሰማሩ ዘንድ ከሚመለከተው አካል (መንግስት) የገንዘብና የቦታ አቅርቦት ሊያገኙ ያስፈልጋል፡፡ አሁን እየሆነ ያለውን ካየን ግን አንድ ምሩቅ የሆነ ሥራ መጀመር ካሰበ የገንዘብ ምንጩ ወገቡን እንደሚይዘው ይታወቃል፡፡ ምሩቃን ከትምህርት ቤት ሲወጡ ገንዘብ ይዘው እንደማይወጡ ለማንም ግልጽ ነው፤ በምትኩ ከምሩቃን የሚጠበቀው እውቀት ነው፡፡ ይህ እየታወቀ ግን ምሩቁ ሥራ ለመጀመር ብድር ቢፈልግ ማስያዝ ያለበት ገንዘብ ወይም የቤት ካርታ ይጠየቃል፡፡ እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ሥራ ፈጠራን ማንኳሰሱ የሚስተዋለው፡፡
አንድ ምሩቅ ከትምህርት ቤት እንደወጣ ብድር ለማግኘት የሚጠይቀውን 20 በመቶ ገንዘብ ከወዴት ሊያመጣ እንደሚችል መገመት ይቻላል፤ ብድር ለማግኘት ሌላ ብድር መግባት ካልሆነ በስተቀር 20 በመቶውን የትም አያገኝም! ስለሆነም ይህ አልሆን ሲል ወደ ሁለተኛው ‹አማራጭ› መሻገር ይከተላል፡፡ ይህ ግን ለምሩቁ የባሰ ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ ‹አማራጭ› የቤት ካርታ ማስያዝ ጉዳይን የሚመለከት ነው፡፡
አንድ በወላጆቹ እገዛ ትምህርቱን የተከታተለ ወጣት ምሩቅ የማንን ቤት ካርታ ነው እንዲያስይዝ የሚጠበቀው!? የወላጆቹን!? መቼም ስንትና ስንት አመታት በሥራ ላይ የሚከርሙ ኢትዮጵያውያን ቤት በማይሰሩበት በአሁኑ ጊዜ ከዩኒቨርሲቲ የተመረቀ ወጣት የቤት ካርታ ይኖረዋል፤ እሱንም ለብድር ሲባል አስይዞ ይበደራል ብሎ ማሰብ በምሩቁ ላይ መሳለቅ ነው የሚሆነው፡፡ ለዚህ ነው አሁን ላይ ምሩቃን ሥራ ፍጠሩ በሚለው እሳቤ የተተበተበው ኢህአዴግ ሥራ ፍለጋን ማውገዙ ተገቢ የማይሆነው፡፡
ሥራ ፍለጋ
ከዚህ የምረቃ ጊዜ አንስቶ በርካታ ወጣቶች ሥራ ፍለጋ ሲንከራተቱ፣ የሥራ ያለህ ሲሉ ይስተዋላሉ፡፡ በየማስታወቂያ ሰሌዳውም ዓይኖቻቸውን ያንከራትታሉ፡፡ ብዙዎች የምረቃ ደስታቸውን እንኳ ሳያጣጥሙ የሥራ ፍለጋ ጉዳይ እረፍት ይነሳቸዋል፡፡ የሥራ አጥነት ስጋት (እውነታ) ውስጣቸውን ይረብሻቸዋል፡፡ በእርግጥም አሁን ላይ በሀገር ቤት ሥራ ፈልጎ ማግኘት የሎተሪ ያህል የሆነባቸው አያሌ ተስፈኛና ባለአዲስ ጉልበት ባለቤት ወጣቶች ሞልተዋል፡፡ ዳሩ ግን ሥራ ፍለጋን የሚያወግዘው የሚመስለው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት በአስተሳሰቤ ካልተጠመቃችሁ ሥራ አታገኙም ያለ ያስመስለዋል፡፡ ስለሆነም እሱ ባስቀመጠው መስመር ብቻ ግዴታ አስገብቶ በማደራጀት የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን በድንጋይ ፈለጣ ተግባር ላይ ያሰማራቸዋል፡፡
ሐቁ፣ መደራጀት ኃይል ነው፡፡ ግን ደግሞ መደራጀት ለመጠርነፍ ሲሆን መደራጀት አቅመ ቢስነት ይሆናል፡፡ አሁን አሁን በመንግስት የሚደረገው የመደራጀት ሂደት የዚሁ አቅመ ቢስ የመሆን ማሳያ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም መንግስት ወጣቶችን ሲያደራጅ ቀዳሚ ተግባሩ በርካሽ ፖለቲካዊ ትርፍ እሳቤ ውስጥ ሆኖ እንደሆነ ማሳያዎች በመኖራቸው ነው፡፡ ለአብነትም የሚደራጁት ወጣቶች ምንጊዜም ቢሆን ለመደራጀት የበቁት መብታቸው ስለሆነ ሳይሆን መንግስት በደግነቱ ያመቻቸላቸው ዕድል እንደሆነ በአያሌው ደጋግሞ ሲገልጽ መሰማቱ የርካሽ ፖለቲካ ትርፍ ጥማቱን በግላጭ ያሳየ በመሆኑ ነው፡፡ ለዚህም ነው ምሩቃንን አደራጅቶ ከራሱ ማዕቀፍ እንዳይወጡ ለማድረግ ሲባል ሥራ ፍለጋን የሚያወግዘው፡፡
በዚህ ጠርናፊ ማደራጀት ውስጥ ገብተው ሥራ የጀመሩትም ቢሆን ሥንቶቹ ውጤት እንዳሳዩ የሚታወቅ ነው፡፡ ተደራጅተው ሥራ በጀመሩ በጥቂት ወራት ውስጥ ሥራቸውን በኪሳራና ድጋፍ በማጣት እንዲሁም በጣልቃገብነት ምክንያት አቋርጠው ለመበተንና ሀገር ጥለው ለመሰደድ የተዳረጉት በርካቶች ናቸው፡፡ ጥቂቶች እንደተሳካላቸው መካድ ባይቻልም ብዙ ጊዜ በቴሌቪዥን ተጋንኖ የሚነገርላቸው ‹ይህን ያህል፣ ያን ያህል› ንብረት አፈሩ የሚለው ጨዋታ በአብዛኛው ተራ ፕሮፖጋንዳ እንደሆነ ጋዜጠኞች በትዝብት ውስጥ ሆነው በዓይናቸው ካዩት ሐቅ ምስክርነትን የሚሰጡበት ሀቅ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ መንግስት ሥራ ፍለጋን ለማውገዝ ምን ሞራል ይኖረዋል፡፡
ከመነሻው ‹ሥራ ፍለጋ› የሚለው እሳቤ ጤነኛ አስተሳሰብ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰዎች ሥራ ለመስራት መነሳታቸው ለሥራ ያላቸውን ቀናዒነትና በሀገራቸው ማናቸውም አቅማቸው በፈቀደው ደረጃ ለመስራት ሥራ መፈለጋቸው ተገቢ ጉዳይ ነው፡፡ ሥራ ፍለጋ ማለት ለመስራት ቁርጠኛ መሆን ማለት ነው፤ ከሥራ ጋር አገናኙኝና አቅሜን ልጠቀም የማለት ቅን አስተሳሰብ ነው፡፡ በመሆኑም ሥራ ፍለጋ ፈጽሞ እንደ ውግዘት መታየት አይኖርበትም፡፡
ምሩቃን በግል ድርጅቶችም ሆነ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ሥራ ፈልገው በመቀጠራቸው ውግዘት ሊገጥማቸው አይገባም፡፡ እንዲያውም መንግስት ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ የተለያዩ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ ሚናውን መወጣት ነው ያለበት፡፡ በአደጉት ሀገሮች መንግስት የሥራ አጥነትን በየጊዜው ለማቃለል የተለያዩ እቅዶችን ይፋ በማድረግ ወደ ሥራ ይገባል፡፡ ዜጎች በተነሳሽነት ሥራ ፈጠራ ላይ እንዲገቡ ዕድሉ ይመቻችላቸዋል፡፡
ከዚህ ባለፈ ግን መንግስታት ለሥራ ፈላጊ ዜጎቻቸው ሥራ የመፍጠር ኃላፊነት እንዳለባቸው መርሳት የለባቸውም፡፡ በአሜሪካ የሥራ አጡ መጠን ወደ 9 በመቶ ደረሰ ተብሎ የኦባማ አስተዳደር ይህን ሥራ አጥነት ለመቀነስ የወሰደውን እርምጃ የምናስታውሰው ነው፡፡ በመሆኑም መንግስታት ሥራ ፈጠራ ላይ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው መዘንጋት አይኖርበትም፡፡
ሆኖም ግን ይኽ የመንግስት ሚና በእኛ ሀገር የተረሳ ይመስላል፡፡ ዜጎች በራሳቸው ምንም ምቹ ሁኔታ ሳይቀመጥላቸው ሥራ ፈጣሪ ካልሆኑ በሚል ውግዘትን ይከናነባሉ፡፡ ይህ ትክክለኛ ብያኔ አለመሆኑን ግን ማንም መረዳት ያለበት ሀቅ ነው፡፡ እናም ይህን ካለመረዳት ይመስላል ሥራ ፈልጎ ማግኘትም ሆነ ሥራ ፈጠራ ላይ ለመሰማራት ሁኔታዎች ዳገት እንደሆኑ የሚቀጥሉት፡፡ ምሩቃን ቁጥራቸው በየጊዜው ይጨምራል፣ ሥራ ግን የለም፡፡ ለዚህም ነው ምርቃት ወዲህ ሥራ ወዲያ መሆኑ፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ፤ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም ቅፅ 1 ቁጥር 21)

ለብሔራዊ አንድነትና ነፃነት – ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል!!!

July24/2014

በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙ የእብደት ተግባራትን ስናጤን ከፊት ለፊት ኢትዮጵያችንን እየጠበቀ ያለው መንታ መንገድ አመላካች ነው። ይህ ከፊት ለፊት የሚጠብቀን መንታ መንገድ አንዱ ወደ ብሔራዊ አንድነት፣ ነፃነትና ብልጽግና ሌላው ወደ እርስ በርስ ትርምስና ውድቀት የሚያመሩ ናቸው። የአንድነት፣ የነፃነትና የብልጽግና መንገድ ለመያዝ መስመራችንን ማስተካከል ያለብን ከአሁኑ ነው።
ለመሆኑ ከላይ ያልነውን ለማለት ያስቻሉን በአለፉት ጥቂት ሣምንታት በወያኔ የተፈፀሙት ተግባራት ምንድናቸው?
አንደኛ፤ ወያኔ፣ ዓለም ዓቀፍ ህግንና ሥርዓትን በጣሰ መንገድ ከየመን ባለሥልጣናት ጋር በማበር የንቅናቄዓችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ማፈኑ በአለፉት ጥቂት ሣምንታት ውስጥ ውስጥ የተደረገ አብይ ክስተት ነው። ይህ የወያኔ የውንብድና ተግባር ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። ወያኔ፣ ለሀገር ነፃነትና ለእኩልነት የሚታገልን አንድ ታላቅ ሰውን ማፈንኑና ከእይታ ከልሎ እያሰቃየው መሆኑ በሕዝቡ ውስጥ ያለው ቁጣ ወደ መገንፈል አስጠግቶታል። አቶ አንዳርጋቸው በጠላት እጅ ከወደቀም በኋላ ኢትዮጵያዊያንን አሰባሳቢ ኃይል ሆኗል።
ሁለተኛ፤ ሰላምተኞቹን ብሎገሮችንና ጋዜጠኞችን በሽብርተኝነት በመክሰስ በቋፍ ላይ የነበረውን የወጣቶች ትዕግሥት እንዲሟጠጥ አድርጓል። ስለኢንተርኔት አጠቃቀምና ጥንቃቄ ሥልጠና መውሰድ በክስ ቻርጁ ውስጥ መካከቱ ሥርዓቱ ከእውቀት ጋር የተጣላ መሆኑ በግልጽ አሳይቷል። ከዚህም በተጨማሪ በህጋዊ ፓርቲዎች ውስጥ በንቃት የሚሳተፉ ወጣት መሪዎችን መርጦ በማሠርና በሽብርተኝነት በመወንጀል የወያኔ የአፈና መዋቅር ወጣቱ ላይ ማነጣጠሩ ግልጽ ሆኗል።
ሦስተኛ፤ እጅግ ሰላማዊና ጨዋነት በተሞላበት መንገድ አቤቱታቸውን በማቅረብ ላይ የነበሩትን ሙስሊም ወገኖቻችንን ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በመደብደብ እና በጅምላ በማሠር በወያኔ መድብለ ቃላት ውስጥ “ሰላማዊ ትግል” የሚባል ነገር አለመኖሩ፤ ተቃውሞ ሁሉ “ሽብር” እንደሚባልና በሽብርተኝነት እንደሚያስከስስ በማያሻማ ሁኔታ አረጋግጧል። ይህም የሥርዓቱ አውሬዓዊ ባህሪ መገለጫ ሆኗል።
አራተኛ፤ አፈናውና እስሩ ወደ ትግራይም በመዛመቱ ወያኔ የቆመበት ምድር እየራደ መሆኑ አመላካች ሆኗል። ትግራይ ውስጥ የነበረው አፈና ድብቅ የነበረ ከመሆኑም በላይ ከወያኔ የውስጥ ሽኩቻ ጋር ሲያያዝ ቆይቷል። አሁን ግን ሁኔታዎች እየተቀየሩ ነው። አገራዊ ርዕይ ያነገቡ፤ ወያኔን በጽናት ለመታገል የቆረጡ የትግራይ ወጣቶች ወደፊት እየመጡ ነው። እነዚህ ወጣቶች የተጫነባቸውን ድርብርብ ጫና በመበጣጠስ ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ወገናቸው ጎን መቆማቸውን በተግባር እያረጋገጡ፤ ለዚህም መስዋዕትነት እየከፈሉ ናቸው።
ከላይ የተዘረዘሩት አራት ጉዳዮች በጋራ ሲታዩ የተበታተነ የሚመስለው እና በተለያዩ ስልቶች የሚደረገው ትግል የሚሰባሰብበትና የሚቀናጅበት ወቅት ላይ መደረሱ አመላካቾች ናቸው። ዛሬ የምንገኘው የተለያዩ የትግል ስልቶች እንዲናበቡና እንዲደጋገፉ ማድረግ እጅግ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ላይ ነው።
በተለይም ወያኔ፣ መሸሸጊያ ምሽጉ አድርጎ በሚቆጥረው ትግራይ ውስጥ እየዳበሩ የመጡት የአመጽም አመጽ-የለሽ ትግሎችም አስተዋጽኦ ከፍተኛነት ሌላው ኢትዮጵያዊ እንዲረዳ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ተግባር ነው። የወያኔ የአፈናና የመጨቆኛ መዋቅሮች የህወሓት አባላት በሆኑ የትግራይ ዘውጌ ማኅበረሰብ አባላት የሚዘወሩ መሆኑ እውነት ነው። ይህ ማለት ግን ህወሓት የትግራይ ሕዝብ ወኪል ወይም ጠበቃ ነው ማለት አይደለም። ትግላችን ከወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ ጋር መሆኑ እና የትግራይ ሕዝብ የዚህ ትግል አጋር፣ የውጤቱም ተጠቃሚ መሆኑ ማስረገጥ ተገቢ ነው።
ከፊት ለፊታችን ካሉት መንታ መንገዶች መካከል የአንድነትን፣ የነፃነትና የብልጽግናን መንገድ ለመምረጥ የትግራይ ሕዝብ በስፋት ትግሉን እንዲቀላቀል ማድረግ ተገቢ ነው። ትግራይ የህወሓት የግል ጓዳ መሆኗ የማብቂያ ጊዜ ማፋጠን ይቻላል። በዲሞክራሲያዊ ትግል ውስጥ ያሉ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ ግንዛቤ ከያዙ ወያኔን ማንሳፈፍ የሚቻልበት እድል በስፋት ተከፍቷል።
ስለሆነም፣ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘረኛውና ፋሽስታዊው ህወሓትን ከትግራይ ሕዝብ መነጠል አንዱ የትግላችን ስትራቴጂ ሊሆን ይገባል ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ተሰባሪ መንግሥታትና የመሰበራቸው ምክንያቶች

July24/2014
አንዱ የመሰበር ምክንያት የቡድን/የሕዝብ ሃዘን
fragilestates


በዓለማችን የመክሸፍ አደጋ የሚታይባቸውን አገራት ዝርዝር በየዓመቱ በማውጣት የሚታወቀው የውጭ ፖሊሲ መጽሔትሰሞኑን አደጋው የሚታይባቸውን አገራት በዝርዝር አውጥቷል። በዚህ የ178 አገራትን ዝርዝር በያዘው ዘገባ መሠረት ቁጥር አንድ የአደጋው ተጋላጭ ደቡብ ሱዳን ስትሆን ኢትዮጵያ ደግሞ 19ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ጠቁሟል።
ባለፈው የአውሮጳውያን ዓመት 2013 መረጃ ላይ ተመርኮዙ የወጣው ዘገባ 12 መስፈርቶችን በግብዓትነት የተጠቀመ መሆኑን አስታውቋል። እነዚህም፤
  1. የስነሕዝብ ተጽዕኖ፡ ከህዝብ ብዛት ጋር በተያያዘ የምግብ ዕጥረት፣ የሟቾች ቁጥርና ፍጥነት፤
  2. ስደተኞችና በአገር ውስጥ የሚፈናቀሉ፡ በስደት ወደ አገር የሚገቡና በአገር ውስጥ ከየቦታው የሚፈናቀሉ፤
  3. የቡድን (የሕዝብሃዘን፡ በአገር ውስጥ ባሉ ቡድኖች መካከል ያለው ውጥረትና ጠብ፤
  4. አገር ጥለው የሚሄዱና የምሁር ስደተኞች፡ ከአገር ውስጥ ወደ ውጭ የሚሰደዱ ዜጎችና ምሁራን፤
  5. ሚዛናዊ ያልሆነ የኢኮኖሚ ዕድገት፡ በአገር ውስጥ በሚገኙ ብሔሮች ወይም የሃይማኖት ቡድኖች ወይም ክልሎች መካከል የሚታይ ያልተመጣጠነ (ሚዛናዊ ያልሆነ) የኢኮኖሚ ዕድገት፤
  6. ድህነትና የኢኮኖሚ ውድቀት፡ የድህነት መጠንና የኢኮኖሚው አፈጻጸም፤
  7. የመንግሥት ህጋዊነት፡ ሙስና እና ሌሎች እንደ ምርጫ ሂደት፣ መልካም አስተዳደር፣ የመንግሥት ሥርዓት አፈጻጸም፣ ወዘተ የመሳሰሉ የዴሞክራሲ ብቃት መለኪያዎች፤
  8. የሕዝብ አገልግሎቶች፡ ትምህርት፣ የጤና አጠባበቅ፣ የንጽህና አጠባበቅ፣ እና ሌሎች ሕዝባዊ አገልግሎቶች፤
  9. ሰብዓዊ መብቶችና የሕግ የበላይነት፡ የሰብዓዊ መብቶች ከለላና እነዚህ መብቶች እንዲጠበቁ የሚደረግ ትጋት፤
  10. የደኅንነቱ አሠራር፡ የአገር ውስጥ ግጭቶችና ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ ያሉ የታጣቂዎች ቁጥር መጨመር፤
  11. የልሒቃን ወገናዊነት፡ በየአካባቢውና በብሔራዊ ደረጃ የሚገኙ ልሒቃንና መሪዎች መካከል የሚካሄድ ፉክክርና ግጭት፤
  12. የውጭ ጣልቃገብነት፡ ከውጪ የሚገባ ዕርዳታ መጠንና በውጭ ኃይላት የሚደረግ የማዕቀብና የወታደራዊ ጣልቃገብነት ተጽዕኖ ናቸው።
ዘገባው የ2013ን መረጃ በመጠቀሙ አሁን በየአገራቱ ከሚታየው ሁኔታ ጋር በመጠኑም ልዩነት የሚታይ ቢሆንም በመጪው ዓመት ግን ይኸው ከግምት ውስጥ ገብቶ ማሻሻያ እንደሚደረግ ገለጾዋል። ሆኖም በየዓመቱ የሚደረገው የደረጃ ጉዳይ እምብዛም ለውጥ የማያሳይ እንደሆነ አክሎ አስታውቋል። ከዚህም በተጨማሪ በየአመቁ የሚጠቀምበትን “failed states” (የከሸፉ መንግሥታት) ከሚለው መጠሪያ ይልቅ “fragile states” (ተሰባሪ መንግሥታት ወይም ክሽፈት ያነጣጠረባቸው መንግሥታት) በሚል መቀየሩን በዘገባው ላይ አመልክቷል።
በተለይ ከአንድ እስክ ሃያ አምስት ያሉትን አገራት ስንመለከት አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት መሆናቸው አኅጉሩ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የሚጠቁም ነው። ከዚህ ዝርዝር ውስጥ 1ኛ ደቡብ ሱዳን፣ 2ኛ ሶማሊያ፣ 3ኛ ማዕከላዊ የአፍሪካ ሪፑብሊክ፣ 4ኛ የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ 5ኛ ሱዳን፣ 6ኛ ቻድ፣ 11ኛ ዚምባብዌ፣ 12ኛ ጊኒ፣ 14ኛ ኮትዲቯር፣ 16ኛ ጊኒ ቢሳው፣ 17ኛ ናይጄሪያ፣ 18ኛ ኬኒያ፣ በእኩል የ19ኛ ደረጃ ኢትዮጵያና ኒጀር፣ 21ኛ ብሩንዲ፣ 22ኛ ዑጋንዳ፣ 23ኛ ኤርትራ፣ 24ኛ ላይቤሪያ ናቸው።
failed states 1በዚህ መረጃ መሠረት ከ25ቱ አገራት መካከል የአፍሪካውያን ቁጥር ከ70በመቶ በላይ ሲሆን የምስራቅ አፍሪካ አገራት ብቻ ደግሞ ከ30በመቶ በላይ የሚሆነውን የሚያካትቱ መሆናቸው በእርግጥ የአፍሪካ ቀንድ በከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚገኝ ቀጣና መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነው። በተለይ በቀጣናው ባሉ አገራት ላይ የበላይነትን ተጎናጽፌአለሁ የሚለው ኢህአዴግ የአፍሪካ ቀንድ ስጋት መሆኑን በዚሁ ዓመት የመጋቢት ወርጎልጉል አንድ አሜሪካዊ ዲፕሎማትን ጠቅሶ መዘገቡ ይታወቃል።
ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ባተመው በዚህ ዜና መሠረት “ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ብቸኛ ተዋናይና ፊት አውራሪ አድርጎ ራሱን የሾመው ኢህአዴግ ለቀጠናው ስጋት” መሆኑን ጠቁሟል። ዘገባው ሲቀጥልም “ህወሃት ያቋቋማቸው ጥቃቅን መንግሥታት ከህዝብ ይልቅ ለህወሃት የወደፊት እቅድ ታማኝ በመሆን መጓዛቸው ከቀን ወደቅን የፈጠረው ስሜት ኢህአዴግን እየበላው እንደሆነ የጠቆሙ የዜናው ምንጮች፣ ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪቃ የሰላም አባት ሊሆን ቀርቶ የራሱንም ችግር መፍታት ወደማይችልበት የቁርሾ ማሳ ውስጥ እንደሚገኝ” ጠቁሞ ነበር።
ሟቹ አቶ መለስ በየትኛውም አገር ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በዓለምአቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድ በመሄድ እጅግ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ኤርትራ እንድትገነጠል በይፋ ከለመኑና በትጋት ከሰሩ በኋላ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ቁጥር እየጨመረ ሄዷል። በመቀጠልም ህወሃት/ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪካ አገራትን እንደፈለገው በመዘወር በሶማሊያ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሲያማስል ቆይቶ አገሪቱን በመከፋፈል የራሱን አሻንጉሊት አስተዳደር አስቀምጧል። በሱዳንም እንዲሁ በማድረግ ደቡብ ሱዳንን የግል ቤቱ በማድረግ ከፖሊስ እስከ መከላከያና የደኅንነት ሥልጣኑን በእጅ አዙር ከተቆጣጠረ በኋላ በአሁኑ ጊዜ ደቡብ ሱዳን በዓለም ላይ መረጋጋት ከሌለባቸው (ከከሸፉ) መንግሥታት መካከል የመጀመሪያው ሥፍራ ላይ ትገኛለች።
ከአንድ እስክ ሃያ አምስት ያሉት አገራት አብዛኛዎቹ ከአፍሪካ መሆናቸው አህጉሪቱ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የሚጠቁም ነው። ለአገራቱ ተሰባሪነት ወይም መክሸፍ ምክንያት ተብለው የተዘረዘሩትን ምክንያቶች አሁን ካለው የአገራችን ሁኔታ ጋር የሚጣጣሙ ሆነው እናገኛቸዋለን። ኢህአዴግ ኢትዮጵያን መግዛት ከጀመረበት የመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ የጀመረው ስልት እየዋለ አድሮ ያመጣቸው ጣጣዎች የመክሸፍ መንስዔ ተደርገው ከቀረቡት መካካል ይገኛሉ። በየጊዜው ተጨባጭ ምክንያት በማቅረብ የሚወጡ ሪፖርቶችን በመግለጫ ከመቃወምና፣ በጭፍን ድጋፍ ከማጣጣል ውጪ ነገሮችን ረጋ ብሎ የመመርመር ችግር በመኖሩ ችግሩ ከቀን ወደ ቀን እየገዘፈ ነው።  አብዛኞች እንደሚሉት በጥናት የሚቀርቡ ሪፖርቶች በ24 ሰዓት የሚከናወኑ ሳይሆኑ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ “አዋጆች” ናቸው። በዚሁ አዋጅ መሰረት ችግር ውስጥ ያሉ አገሮች የኢህአዴግን አገዛዝ ጨምሮ ለራስም ሆነ ለአገር ሲባል የችግሮችን መልክ ለመቀየር መስራት አለባቸው። የመክሽፍ ወይም የመሰበር አደጋ ያስከትላሉ ተብለው የቀረቡትን ጭብጥ መረጃዎች ከቀነሱና ካስወገዱ በኋላ “እኔ አልከሽፍም፣ አልሰበርም” ማለት ተገቢ ሊሆን ይችላል። ይህንን ሳይፈጽሙ ግን በችግሮች የተካበ ማማ ላይ ቆሞ “ማስተባበልና ማላዘን” በከንቱ ፕሮፓጋንዳነት ለጥቂት ጊዜ ሕዝብን ለማታለል “ከመጥቀም” በላይ ላለመሰበር ዋስትና በጭራሽ አይሆንም!!
ዘገባው እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Wednesday, July 23, 2014

ከኤርትራ ጋር የታቀደው ጦርነት ሊጀመር ነው!!!

ደመቀ የኔአየህ
July 23, 2014
የዛሬ ሦስት ወር አካባቢ የ ወያኔ መንግስት ከኤርትራ ጋር ጦርነት ሊከፍት ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ ከውስጥ የተላከልኝን መረጃ ማስነበቤ ይታወሳል።

የጦርነቱም ዋና አላማ በኤርትራ ውስጥ ያሉትን የነፃነት ታጋዮችን እንቅስቃሥሤ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማምከን የሚል ነው። የዚህ ጦርነት ዋና አላማ በስልጣን ላይ ያለውን የሻብያ መንግስት በመጣል በኢትዮጵያ ውስጥ ሲያዘጋጁቸው የኖሩትን የ ኤርትራ ተቃዋሚወች ወደ ስልጣን በማምጣት በኤርትራ ውስጥ ሊከሰት የሚችለውን ማንኛውም አይነት የትጥቅ ትግል ቦታ ማሳጣት ነው። ለዚህም ይረዳሉ ተብለው በ10 ሺወች የሚሆኑ ኤርትራውያንን በኢትዮጵያ ዪኒቨርስቲወች ውሥጥ ሲያሥተምር ቆይቱል። እነዚህ ተማሪወች ከአካዳሚክ ትምህርት ባሻገር በአመት ሶሦት ጊዜ የ መንግስት አስተዳደር፣ የፓለቲካ እና የደህንነት ትምህርቶችን ሲማሩ ቆይተዋል።

ይህ ጦርነት ግቡን ይምታላቸውም አይምታላቸውም እንደተጠበቀ ሆኖ በቅርብ ጊዜ ጦርነቱ ሊጀመር መሆኑን መረጃወች ይጠቁማሉ።

ይህን የታሪክ አጋጣሚ የኢትጵያ ህዝብ እንዴት ሊጠቀምበት እንደሚችል አይታወቅም። በወያኔ ግምት የኢህዴግ ሰራዊት በድል ያጠናቅቃል የሚል እምነት እንዳለው ያመለክታል። ህዝቡ ድጋፍ አደረገም አላደረገም ሰራዊቱ አሁን ባለው አቁም ይህን አደራ በአሸናፊነት እንደሚያጠናቅቅ እምነት እንደተጣለበት ያመለክታል።

የኢህዴግ ሰራዊት ከተቁዋሚ ጎራ ይሠልፍ ይሆን የሚለውንም ሃሳብ አውጥተው አውርደው አስበውበታል። በእነሱ እምነት ይህ ሃሳብ ውሃ የሚቁጥር ሆኖ አላገኙትም።

አይቀሬው ጦርነት ሊጀመር ጫፍ ላይ መሆኑን በ ያዝነው ወር በቀን 18 የአሜሪካ የ አቬሽን ባለስልጣን ያወጣውን የ ሰላማዊ አውሮፕላን በረራ እገዳ አንድ ትልቅ ፍንጭ ነው።

በተጨማሪም በየወረዳው የተጀመረው የውትድርና ምልመላ አንድ ሌላ ተጨማሪ ፍንጭ ነው።

Hailemariam Desalegn humiliated as university withdraws honor

July 23/2014
By Abebe Gellaw
azusa1(AV) Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn faced a stinging humiliation as Azusa Pacific University (APU), whose motto is “God First”, has withdrawn an honor it had already bestowed on him.  The university administration had to reverse its decision to honor Mr. Desalegn in light of gross human rights violations in Ethiopia being perpetrated by the regime he serves.
The administration of the American evangelical university made the decision an emergency meeting last Friday after this reporter raised a number of critical questions on whether honoring a human rights violator was consistent with APU’s core values and motto. The Global Alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) also wrote a letter highlighting gross human rights violations being perpetrated by Mr. Desalegn and the TPLF-led regime he is serving.
The honoring ceremony, which was slated for July 31 at the university’s Los Angeles campus, was expected to be attended by the PM and his family, foreign diplomats, the university faculty, senior U.S. and Ethiopian government officials including Foreign Minister Tedros Adhanom and  other ministers.
Rachel White, APU’s Assistant Director of External Relations, confirmed exclusively to this reporter that the university has withdrawn the honor and cancelled the ceremony which was planned to honor him at APU’s Los Angeles campus.
“I can confirm that the event has been cancelled. The university evaluated current developments in Ethiopia including the latest U.S State Department Human Rights Report,” she said. She also indicated that the recent high court decision to file terrorism charges against Zone9 bloggers and journalists was also one of the factors considered for the cancellation of the event to honor Mr. Desalegn.
“Nothing is as important as our motto God First. Any decisions we make have to be consistent with our motto and core values,” White noted. She also pointed out that respect for human rights are very important for the university. It is now confirmed that he cancelled his trip to Los Angeles after the university communicated to him its decision to cancel the honoring ceremony.
prtAccording to a university source, who spoke on condition of anonymity as he was not authorized to give a statement on behalf of the university, APU’s administration unanimously agreed to withdraw the honor for Mr.Desalegn, whom it found to be an unsuitable honoree after evaluating not only the disturbing human rights situation in Ethiopia but also the potential negative publicity that the event was likely to generate. “It was a wise and timely  decision, as the university was likely to face backlash if it publicly honored a human rights violator,” the source said.
Exiled journalist Serkalem Fasil, who was forced to give birth in jail, commended the university for correcting its mistake in good time. “I think this university did not know who Hailemariam Desalegn was. They should have known that Ethiopian government officials like him do not deserve honor but facing justice for the crimes they are committing against humanity.”
Serkalem said Azusa Pacific corrected its mistake in an exemplary manner. “I am glad the university listened to the truth and its God First motto,” she said. Her husband, the award-winning journalist Eskinder Nega, is serving an 18-year sentence in Ethiopia after he and a number of journalists and activists were labelled “terrorists” by a Kangaroo court.
Abebe Belew, a Washington D.C.-based activist and community radio broadcaster, who was also convicted of “terrorism” offenses because of his critical views towards the repressive policies of the Ethiopian government, also praised the university for its decisive measure.
“This university is a truly Christian university. It made a bad decision but realized soon enough that honoring an ungodly human rights violator contradicted its Christian values. I appreciate the university’s administration for taking such a strong stand based on its God First motto,” he said.
“Hailemariam should also learn from the humiliating experience. He pretends to be a protestant Christian but what he is doing completely contradicts all the tenets of the bible.
“As APU has clearly demonstrated, he doesn’t deserve any honor as a human rights violator destroying the lives of so many people. I hope he and and members of this oppressive tyranny will face trial sooner rather than later. That is the kind of honor they really deserve,” Abebe added.

ኢሕአዴግ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን በሽብርተኝነት መወንጀሉን እንዲያቆም መድረክ ጠየቀ

July 23/2014
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ ሰላማዊ ታጋዮችን በሽብርተኝነት መወንጀሉን እንዲያቆም ጠየቀ፡፡
መድረክ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ ኢሕአዴግ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን እያሰረና እያሰቃየ ያለው በአምባገነናዊ አገዛዝ ለመጠቀል የነበረው ምኞት ሥጋት ውስጥ መውደቁን በመረዳቱ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
ኢሕአዴግ እያካሄደ ባለው የእስር ዕርምጃ የመድረክ አባል የሆነው የዓረና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የመድረክ ጠቅላላ ጉባዔ አባል የሆኑት አቶ አብርሃ ደስታ ከሚኖሩበትና ከሚሠሩበት መቀሌ ከተማ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ መደረጉን መግለጫው አመልክቷል፡፡ ከሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የታሰሩት አቶ አብርሃ በቤተሰቦቻቸውም ሆነ በጓደኞቻቸው እንዲጎበኙ አለመፈቀዱንም መግለጫው ያትታል፡፡
ከአቶ አብርሃ ደስታ በተጨማሪ የአንድነት አመራር አባላት የሆኑትን የአቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ እንደዚሁም የሰማያዊ አመራር አባል የሆኑት የአቶ የሺዋስ አሰፋን እስርም መድረክ ተቃውሟል፡፡
ገዥው ፓርቲ ከወሰደው የፖለቲካ ፓርቲ አመራርና አባላት እስር ጋር በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙ አባላቱ ለእስር፣ ስቃይና እንግልት መጋለጣቸውንም መድረክ አስታውቋል፡፡ በተለይም በትግራይና በኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ አባላቱ ላይ እየደረሰ ያለው እስርና ግፍ እየተስፋፋ መሄዱ፣ አገሪቱ ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ጥያቄ ውስጥ እንደሚከተው አስገንዝቧል፡፡
መድረክ የኢሕአዴግ ዕርምጃ በቀጣይ ዓመት ከሚካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ጠቁሞ፣ ዕርምጃው አስቀድሞ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና እንቅስቃሴያቸውን ለማዳከም ያለመ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ ‹‹ዕርምጃዎቹ የጠቅላይነትና ብቸኛ ገዥ ፓርቲነት ምኞት ነፀብራቆች ናቸው፤›› ያለው መግለጫው፣ የአገሪቱን ውስብስብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ችግሮችን ለመፍታት ውይይትን የገፋ ዕርምጃ እንደማይጠቅም አመልክቷል፡፡
ፓርቲው በመጨረሻም ኢሕአዴግ በሰላማዊ መንገድ የመቃወም ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን በመግፈፍ የሚፈጽማቸውን የማሰርና የማሰቃየት ዕርምጃዎች እንዲያቆምና ሰላማዊ ታጋዮችን በአስቸኳይ እንዲፈታ ጠይቋል፡፡

ተስፋለም ወልደየስ፦ “ሚዛን” በሳተበት አገር “ሚዛን” ባለ ብዕሩን የተቀማ ጋዜጠኛ

July 23/2014
አሁን በ እስር ላይ ከሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ተስፋለም ወልደየስ ነው። ዘሪሁን ተስፋዬ ስለተስፋለም ምስክርነቱን እንዲህ በማለት ይገልጸዋል።
(ከዘሪሁን ተስፋዬ)
ሌሊቱ ሊጋመስ ግማሽ ያህል ሰዓት ቀርቶታል። ወትሮም ዓርብ ምሽት ውክቢያ የማያጣው የአዲስ ነገር ቢሮ በግርግር ተሞልቷል። ጋዜጠኛ ወዲህ ወዲያ ይራወጣል። ቀሪው ኮምፒውተር ላይ አፍጥጦ ዘወትር ለሕትመት ዘግይቶ ለሚገባው ጋዜጣ ጽሑፉን ይተይባል። ጋዜጠኛ ተስፋለምም አንዲት ጥጉን ይዞ ይጫጭራል። ዜናዎች ኤዲት ያደርጋል። እኔም ለመጀመሪያ ጊዜ ይዤ የመጣሁትን ዜና ኤዲት እንዲያደረግ ሰጥቼው፤ ወደጀመርኩት የኢኮኖሚ ጽሑፍ ተመለስኩ። ነገር ግን አፍታም ሳይቆይ በንዴት እየቀዘፈ “አሁን በዚህ ሌሊት ይህ ዜና ተብሎ ይሠራል… ” ተስፋለም ይህን ይህል ግልጽ ነው። ለሞያው የሚቆረቆር። አንዳች ስህተት መስሎ የሚሰማውን ፊት ለፊት ከመናገር የማይቆጠብ።
ያን ሌሊት በብዙ ጭቅጭቅና ንትርክ ዜናው ተሰርቶ ወጣ። አጋጣሚው ግን ልዩነታችን በጋዜጠኝነት ፍልስፍና ላይ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር። እሱ “ሚዛናዊ” ብሎ የሚሟገትለት ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሥራዓት አንዳች የማያራምድ ይልቁንም ጋዜጠኝነትን አሽመድምዶ ልሳን የሚሸብብ መኾኑ ሊያግባባን አልቻለም። እኔ “balanced journalism is a zero-sum game in Ethiopia” ብዬ እሞግተዋለሁ፤ እሱ በየትኛውም የመንግሥት ሥራዓት ቢሆን የጋዜጠኝነት ሕግጋት የማይጣሱ ደንቦች ናቸው ይላል። ይህንንም በሥራው ያሳያል።
Tesfalem woldeyes
Tesfalem woldeyes
ጋዜጠኝነትን ሕይወቱ ያደረገው ተስፋለም፤ በምንም መልኩ ቢሆን ሞያው በትምህርት ቤት ያገኛቸውን የጋዜጠኝነት መርሖዎች እንዲቃረን አይፈልግም። ዜናዎች ሲያዘጋጅ “ሚዛናዊነት” የሚለው መርሕ አለመጣሱን ሲያረጋግጥ ብቻ ነው ወሬው የሕትመት ብርሃን የሚያየው። ይህ ግን በአንዳንድ ባልደረቦቻችን ላይ ጥርጣሬ አልጫረም ማለት አይቻልም። እሱ “ሚዛናዊ” ብሎ የሚጠራው ጋዜጠኝነት፣ ለዘብ የሚል በተለይም አንዳንድ ጠንካራ የሚባሉ ዜናዎችን (በአዲስ ነገር በወቅቱ ዕይታ) አግላይ ነው የሚል ክርክር ይስነሳ ነበር። የዜናዎቹ ‘ሚዛን’ ለመጠበቅ ሲባል ለዘብተኛ መኾናቸው “ተስፍሽ ለመንግሥት ተቆርቋሪነት ያሳያል” የሚል አንድምታ ያለው ጥርጣሬ ማሳደሩ አልቀረም።
ይሁንና በሚያዘጋጃቸው ዜናዎች ተዓማኒነት፣ ጥራት እና ቋንቋ አጠቃቃም ሁሉም የሚያደንቀው ነበር። በተለይ ማህበራዊ ገጾች ላይ የሚወጡ ጽሁፎችን እሱ ሳያይቸው እንዲወጡ የሚፈልግ ጋዜጠኛ አልነበረም። የመተረክ ችሎታው፤ የቋንቋ አጠቃቀሙ እና ዝርዝር ጉዳዮችን የማካተት ብቃቱ ልዩ ነው። ተግባቢነቱና ሁለ ገብነቱም የሞያ መርሕ ልዩነት ቢኖርም በሁሉም ዘንድ በፍቅር እንዲፈለግ አድርጎታል። የማይደክም ነው። የእንቅልፍ ሰዓቱ እጅግ በጣም አነስተኛ መሆኑ እንደ ሰው ቆሞ መሄዱ ሁሌም የሚገርመኝ ነው።
Tesfalem Woldeyes
Tesfalem Woldeyes
ዙረት ይወዳል። በአንድ ሥፍራ መቀመጥ የጋዜጠኛ ተግባር አይደለም ባይ ነው። በመጓዝ ጋዜጠኛ በእውቀት ይበለጽጋል የሚል ዕምነት አለው። ወደ ተለያዩ አገሮች በሚጓዝበት ወቅት ብዙ ጋዜጠኞች የማይሳካላቸውን የጉዞ ማስታዎሻዎችን ማዘጋጀት ላይ የላቀ ብልጫ እንዳለው አሳይቷል። በአንድ ጉዞ ብቻ ለወራት የሚበቃ ታሪክ ይዞ ይመለሳል።
የተስፋለም “ሚዛናዊነት” መርሕ ቢያንስ ቢያንስ ሚዛን የሳቱ አስተዳዳሪዎቻችንን ብትር እንዳይቀምስ ከለላ ይሆነዋል የሚል ዕምነት ነበረኝ። ግምቴ ግን አልሰራም። ሁሌም ጠላት ከጉያው ሥር ካልፈለቀቀ ያስተዳደረ የማይመስለው መንግሥት ተስፋለምን በጠላትነት ፈረጀው። ማዕከላዊ እስር ቤትን ለዜና ሥራ እና እሥረኛ ወዳጆቹን ለመጠየቅ ብቻ የሚሄድበት ጋዜጠኛ፤ አሁን ማደሪያው ኖኗል። እጅግ ልብ የሚሰብር ኢ-ፍትሓዊነት ነው። በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ውስጥ ይሄን ያህል ለሞያ ታማኝ መሆን የሚያስከፍለው ዋጋ እስር እና እንግልት መሆኑ አሳዛኝ ነው።
የተስፋለም እስር ኢ-ፍትሓዊነት ብቻ አይደለም ጸጸት የሚፈጥረው። ብዙዎቻችን የሥራ ባልደረቦቹ ይህንን እውነታውን ሳንረዳ መቅረታችን ነው። ስለዚህች አገር ተስፋ ነበረው። አዎንታዊ ጉዳዮችን ይበልጥ መፃፍ መንግሥትን ከአውሬነት ወደ ሰለጠነ ሰውነት ይገራዋል የሚል ዕምነት ነበረው። እምነቱ ግን ተስፍሽን ዕራሱን አስከፈለው። ሚዛን የሳተኝ አገር ሕሊና ቢሶች አስተዳዳሪዎች ተሸክማ ተስፋለምን ለአውሊያዋ መገበሪያ አደረገችው። ብዕሩን ነጥቃ ከሚወደው ሞያ ለጊዜውም ቢሆን ለየችው።
ተስፋለምን ከሞያ ባሻገርም እንደ ቅርብ ወንድም እናፍቀዋለሁ። ከነልዩነታችን የጥበብ ፍቅር ያስማማናል። ሁለታችንም ዙረት መውደዳችን በተለያየ አጋጣሚ የተለያዩ ሥራዎች እንድንሰራ አድርጎናል። ከሁሉ ግን ዑጋንዳ ለሥራ ለዓመት በቆየበት ጊዜ የመጀመሪያውን በምስራቅ አፍሪካ የሚሰራጭና በአማርኛ የሚታተም “ሐበሻዊ ቃና” የሚል በስደተኞች ላይ የሚያተኩር ጋዜጣ መጀመሩ ይበልጥ እንደወደው አድርጎኛል- ለሞያውም ጥልቅ ፍቅር እንዳለው መስክሮልኛልና።
ተስፍሽን ባልደረቦቹ በወጉ አልተረዳነውም። ፍቅርና አክብሮታችን ግን ሁሌም ነበር። አሁንም ይበልጥ እንድናከብረው ለሚዛናዊነትም የከፈለውን መስዋዕትነት እንድናስበው ሆኖል። ተስፍሽ ሁሌም የምታከብራት ሚዛናዊነት ከግፈኞች አሳሪዎችህ ነጻ በምትወጣ አገራችን ነፍስ ዘርታ እንደምትላወስ አትጠራጠር።

ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ ቡድን በሰሜን ጎንደር የዐማራ ሕዝብ ላይ የፈጸመው የዘር ማጽዳት እና የዘር ማጥፋት ወንጀል

July 22, 2014
የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት አቅዶ ሲነሳ፣ የግቡ መረማመጃ ያደረገው የኢትዮጵያዊነት መገለጫ
የሆኑ ተቋሞችን፣ ኃይማኖቶችን፣ ዕሴቶችን እና በተለይም «ዐማራ» የተሰኘውን ነገድ ተወላጆች ነጥሎ ማጥፋት የሚል ሥልት በመከተል
እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሠረት የጥፋቱ ቅድሚያ ዒላማ ያደረገው ለትግራይ ሕዝብ በችግሩ ጊዜ ደራሽ እና የተራበ
አንጀታቸውን ዳሳሽ በሆነው የወልቃይት፣ የጠገዴ፣ የጠለምትና የሠቲት ወረዳዎች ሕዝብ ላይ ነው። ወያኔ በእነዚህ የትግሬ አዋሣኝ
ወረዳዎች ሕዝብ ላይ የጥፋት ክንዱን የዘረጋው በሦስት መሠረታዊ ምክንያቶች ነው።

የትግል ጥሪ በውጭ ለመትኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ

July22/2014

የኢትዮጵያ ሕዝብ በወያኔ የአፈና ቀንበር ስር ከወደቀ አንስቶ በፖለቲካው፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በማህበራዊ ሕይወቱ እጅግ ወደከፋ አቅጣጫ እያመራ ይገኛል በተለይም የመንደር ፖለቲካው በኢትዮጵያዊያን መካከል ለመፍጠር እየተሞከረ ያለው ልዩነት ስርዓቱ እንዳሰበውና እንደሚፈልገው ገቢር አይሁን እንጂ አገዛዙ የለኮሰውን የጥፋት እሳት በአፋጣኝ ተረባርበን ካላጠፋነው ለወደፊት በኢትዮጵያዊነት ስሜት እና መንፈስ ላይ አደጋ የሚፈጥር ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር አምባገነኑንና ጎጠኛዉን የወያኔ አገዛዝ ለማስወገድ ከፍተኛ መስዋአትነት ከፍሏል። ድርጅታችን ለኢትዮጵያና ሕዝቧ ጥቅም ሲል ዳገት ቁልቁለቱን፣ ረሃብና ጥሙን፣ ውርጭ ቸነፈሩን የኔ ብሎ በመቀበል አጥንቱን በመከስከስ ደሙን በማፍሰስና መተኪያ የሌላት ውድ ህይወቱን በመክፈል ለአገሩና ለሕዝቡ ያለዉን ጥልቅ ፍቅር በተግባር አስመስክሯል ።
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለለውጥ ትግሉ በሰላማዊ ሰልፍ ፣ በሻማ ማብራት፣ የወያኔን ድብቅ አጀንዳ የተለያዩ መንግስታት እንዲያውቁት በማድረግ፣ በማማከር፣በገንዘብ ወ.ዘ.ተ ድጋፍ በማድረግ ቀላል የማይባል ሚና ተወጥተዋል ።
ይህ የተቀደሰ የአርበኝነት ትግል በተደራጀ እና ወጥነት ባለው መልኩ እንዲከናወን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በአቶ የዋርካው መንግስቱ የሚመራ የዓለም አቀፍ ኮሚቴ በጊዜያዊነት መቋቋሙን እያስታወቅን ኮሚቴው ግንኙነቱና አጠቃላይ የውጭ እንቅስቃሴዎቹ ከግንባሩ የውጭ ጉዳይ ሃላፊ አርበኛ ኑርጀባ አሰፋ እውቅናና ምክክር ይሆናል ከዚህ አሰራር ውጭ የሚደረግ ማንኛውንም አይነት የውጭ እንቅስቃሴ ግን ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን። 
በተቋቋመው የዓለም አቀፍ ኮሚቴ ስር በመደራጀት መላው ዲያስፖራ የየበኩሉን ድርሻ በመወጣት ለስደት የዳረገውን የወያኔ አገዛዝ ለመታገል ነገ ሳይሆን ዛሬ ሊነሳ ይገባል።
አንድነት ሃይል ነው !
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር
ሐምሌ 14-2006 ዓ/ም

ሰውና ልማት (ከፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም)

July 22, 2014

Pro Mesfinሰው በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ነው፤ ሕይወቱ ክቡር ነው፤ ክቡር ሕይወቱን ለመጠበቅ ብዙ ፍላጎቶቹን ማሟላት አለበት፤ አንዳንዶቹ ፍላጎቶች በየዕለቱ የሚከሰቱና የሚጎተጉቱ ናቸው፤ ስለዚህም ወዲያው ካልተስተናገዱ በጤንነት ላይ መጥፎ ውጤትን ያስከትላሉ፤ምግብና መጠጥ ግዴታዎች ናቸው፤ ልብስና መጠለያም ግዴታዎች ናቸው፤ ሰው ሁሉም ነገር ከተሟላበት ከገነት ከተባረረ በኋላ በግንባርህ ላብ ብላ ተብሎ ተረግሟል፤ በሰላም በሕግ ጥላ ስር የመተዳደር ፍላጎትም አለ፤ በአለው አቅምና ችሎታ አነዚህን ፍላጎቶች ለማሟላት ይጥራል፤ ይህ ቀላል አይደለም፤ ቀላል የማያደርጉት ብዙ ምክንያቶች አሉ።
አንደኛ፣ የሰውም፣ የእንስሳም፣ የእጸዋትም ሁሉ መኖሪያና መመገቢያ ምድር አንድ ነች፤ ስለዚህ ውድድሩ ከባድ ነው፤ በዚች ምድር ላይ እየኖሩ፣ ምድር የምታፈራውን እየተመገቡ፣ ውሀዋን እየጠጡ በሰላም መኖር አይቻልም፤ የሰው ልጅ ከቢምቢ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሰው ቢምቢ ጋርም መታገል አለበት፣ ከዱር አንበሳ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሰው አንበሳ ጋርም ነው።

ሁለተኛ፣ ፍላጎቶች የሥራ ሁሉ ምንጭ ስለሆኑ በጣም ይራባሉ፤ የመራባት አቅማቸው ከሰው ልጅ መራባትና የመፍጠር ችሎታ ጋር የተያያዘ ነው፤ በተጨማሪም ለተመቸው ሁሉ አምሮቶች ፍላጎቶች ይሆናሉ፤ ደሀዎችንና ሀብታሞችን የሚለየው አንዱ ዋና ነገር የፍላጎቶች ብዛት ነው፤ የደሀ ፍላጎቶች ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አይርቁም፤ የሀብታሙ ፍላጎቶች ከትልቅ ቤት ወጥተው በትልቅ መኪና አድርገው በአውሮጵላን ሰማይ ይወጣሉ፤ ከዚያም አልፈው ይቧጭራሉ።

ሦስተኛ፣ በፍላጎቶች መራባት ላይ አምሮት ታክሎበት፣ እነዚህን ፍላጎቶችና አምሮቶች ማስተናገድና ማርካት ከባድ ፉክክርን ይፈጥራል፤ አብዛኛውን ጊዜ በፉክክር ላይ የሚታየው የተሠራው ቤት ትልቅነትና ውበት፣ የታረደው ሙክት ትልቅነትና ስብነት፣ የሚለብሰው ልብስ ስፌትና ውበት፣ የሚነዳው መኪና ዓይነት የሰዎቹን የኑሮ ደረጃ ያሳያል፤ በግለሰብ ደረጃ ይህ ከፍተኛ የልማት ደረጃን ያመለክታል፤ የግለሰቦችን እድገት የሚጠላ የለም፤ ጥያቄው የግለሰቦች አድገት በምን ዓይነት መንገድ ተገኘ ነው፤ ግለሰቦች በሕገ-ወጥ መንገድ ደሀውን እያሠሩና እያፈናቀሉ መሬቱን በዝርፊያና በቅሚያ ሌሎቹን እያደኸዩ ራሳቸውን የሚያበለጽጉ ነገን የማያስቡ ዕለትዋን ዘለዓለም አድርገው የሚቀበሉ ግዴለሾች፣ ወይም ጅሎች ናቸው።

በግፍ የበለጸጉ በግፍ ይደኸያሉ፤ ትናንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በአንድ ቀን ስንቱን ሀብታም ባዶ እንዳደረገውና እንዳኮማተረው ይህ ትውልድ አላየም፤ ግን ሰምቷል፤ በደርግ ዘመን የመሬት አዋጁንና የትርፍ ቤቶች አዋጆች ያስከተሉትን ሐዘንና ድንጋጤ ያዩ ሰዎች እንዴት እንደገና ሊመጣ ይችላል ብለው ማሰብ ያቅታቸዋል? አንዱ የመክሸፍ ዝንባሌ እንዲህ በቅርቡ የሆነውን መርሳትና ምንም ትምህርት ሳያገኙበት ኑሮን እንደዱሮው መቀጠል ነው፤ ታሪክ የሚከሽፈው እንዲህ ትምህርት መሆን ሲያቅተው ነው፤ በየመንገዱ፣ በየቀበሌው በየስብሰባው ጥርሱን እየነከሰ የውስጥ ቁስሉን የሚያሽ ሰው ሞልቷል፤ የሚራገም ሰው ሞልቷል፤ ከተወለዱበት፣ከአደጉበትና ለስድሳ ዓመት ከኖሩበት፣ ሠርግና ተዝካር ከደገሱበት ሰፈር ተገድዶ መልቀቅ፣ በልጅነት አብረው እየተጫወቱ፣ በኋላም በትምህርት ቤት አብረው በጓደኝነት ከዘለቁ፣ በሥራ ዓለም ከገቡ በኋላ በቅርብ ወዳጅነት አብረው ከቆዩ፣ በአንድ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሃይማኖት በዓላት በደስታም በሐዘንም ከሃምሳ ዓመታት በላይ ያልተለያዩ ሰዎች ጉልበተኛ መጥቶ በግድ ሲበትናቸውና ሲለያዩ፣ መድኃኔ ዓለም ይበትናችሁ! ሳይሉ ይቀራሉ? በግፍ የበለጸጉ በዚህ እርግማን እየተበተኑ ይደኸያሉ፤ እግዚአብሔር በቀዳዳው ያያል፤ አትጠራጠሩ!

ሰውን ገድሎ በሬሣው ላይ ቤት ሠርቶ ሀብታም መሆን ልበ-ደንዳኖች ለአጭር ሕይወታቸው የሚጠቀሙበት ከንቱ ድሎት ነው፤ ሕገ-ወጥነት ነው፤ ግዴለሽነት ነው፤ በቅርቡ ኤርምያስ እንደነገረን የአዲስ አበባን የመሬት ዘረፋ የአዘዘው መለስ ዜናዊ ዛሬ ለአሻንጉሊት የተሠራች በምትመስል ቪላ ውስጥ በሥላሴ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገባው በላይ ድርሻውን ይዞአል፤ የሁሉም መጨረሻ ይኸው ነው፤ ኤርምያስ እንደሚነግረን የአዲስ አበባ የመሬት ዝርፊያ ከልማት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከዓመታት በፊት የነፍጠኞችን አከርካሪት ለመስበርና የወያኔን ትንሽ ልብ አፍኖ የያዘውን ጥላቻ ለማስተናገድ የታቀደ የሕመም መግለጫ ነው፤ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አምስት ከመቶው ዓለም-አቀፍነት ሀበታምነት ደረጃ ላይ ሲደርስ ዘጠና አምስት ከመቶ የሚሆነው ደግሞ ወደለማኝነት ደረጃ ሲወርደ ምንም አይሆንም ብሎ ማሰብ — አይ ማሰብ የት አለ — መመኘት ሳያስቡት በድንገት የሚመጣውን የሕዝብንም፣የእግዚአብሔርንም ኃይል፤ አሜሪካ ተማሪ በነበርሁበት ዘመን (በድንጋይ ዳቦ ዘመን!) አንድ ተወዳጅ ዘፈን ነበር፡– ከቀኜ ብታመልጥ ከግራዬ አታመልጥም! የሚል።

ልማት ምንድን ነው? ከመጀመሪያውኑ መጠየቅ የነበረብን ጥያቄ ነው፤ እያንዳንዱ ሰው ኑሮውን ለማሻሻል፣ ከዛሬው ኑሮ ተምሮ ነገን የተሻለ ለማድረግ ብቻውን ወይም ከሌሎች ጋር በመተባበር የሚያደርገው ጥረት ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ መክሸፍ ጎልቶ የሚታይበት የቁሞ መቅረት ጉዳይ ነው፤ እውነቱ ግን ቁሞ መቅረት አይደለም በአንጻራዊ መለኪያ ቁልቁለት መውረደረ ነው፤ እዚህ ላይ ቆም ብለን የሩቁን መክሸፍ ከቅርቡ መክሸፍ ለይተን እንመልከተው።

ዱሮ ከአክሱም ሐውልቶችና ከላሊበላ ሕንጻዎች ብንጀምር የመክሸፍ ተዳፋቱ ከባድ ነው፤ ከአክሱምና ላሊበላ የሕንጻ ሥራዎች ወደጭቃ ጎጆ ያለው ቁልቁለት ነው፤ ወደቅርብ ዘመን መጥተን በእኔ ዕድሜ የሆነውን ብናይ ወደ1950 አካባቢ ኢትዮጵያ በማናቸውም ነገር የአፍሪካ መሪ ሆና ነበር፤ ዛሬ ያለችበትን ሁሉም ያውቀዋልና አልናገርም፤ ልማት የሚባለውን ነገር ገና አልጀመርንም፤ ልማት በዝርፊያ፣ ልማት በትእዛዝ አይመጣም፤ ልማት የምንለው የማኅበረሰቡን እድገት እንጂ የጥቂት ሰዎችን መንደላቀቅ አይደለም፤ ልማት የምንለው ከእያንዳንዱ ዜጋ ነጻነትና ፈቃድ ጋር የተያያዘውን የጋራ እድገት እንጂ በጥቂት ጉልበተኞች የአገሩን ዜጎች በአገራቸው ስደተኞች የሚያደርገውን አፍርሶ መሥራት አይደለም።

Tuesday, July 22, 2014

በአብርሃ ደስታ ቤተሰብ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ከልክ አልፏል

July 22/2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ብዙዎች እንደሚያውቁት አብርሃ ደስታ በትግራይ የሚገኘው የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ነው። አረና ፓርቲ የህወሃት ተፎካካሪ ፓርቲ በመሆኑ፤ ወያኔዎች በአባላቱ ላይ ግፍ እና በደል ሲያደርሱ ቆይተዋል። አብርሃ ደስታም ትግራይ ሆኖ በዚያ የሚደረገውን ስር አት አልበኝነት በማጋለጡ፤ የትግራይን ህዝብ እንደካደ ተደርጎ ከድብደባ ጀምሮ የእስር እንግልት ደርሶበታል።  አሁንም ማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ መኖሩ ይነገራል እንጂ፤ ህዝብ እንዲያየውም ሆነ እንዲጠይቀው አልተፈቀደም። ፍርድ ቤት ያቀረቡትም ሰውነቱ በጣም ደክሞ እና ተጎሳቅሉ ከእኩለ ለሊት በኋላ ነው።
Abraha Desta
Abraha Desta

ይህ በአብርሃ ደስታ ላይ የሚደርሰው ስቃይ እና መከራ እንዳለ ሆኖ፤ እሱ ከታሰረ ጀምሮ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ ከፍ ያለ ግፍ እየተፈጸመ መሆኑን ከትግራይ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። እንዲህ ይነበባል።
• የአብርሀ ታናሽ እህትና የጤና ባለሙያ (የጤና መኮንን/ HO) የሆነችው ተኽለ ደስታ የኢህአዴግ አባልም ሁና የአብርሀ እህት ስለሆነች ብቻ ከስራ ተባራለች፣ ቢሮ እንዳትገባም በዘበኞች ተከልክላለች፣ መልቀቂያም ከልክለዋታል፤ ቀጣዩ ውሳኔም ቁጭ ብላ እንድትጠባበቅም ተነግሯታል፡፡
• ሁለቱ አዲስ ምሩቃን ወንድሞቹ ኣረጋዊ ደስታና ገ/ገርግስ ደስታ በከፍተኛ ብልጫ ሰቅለው የተመረቁ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው እነሱን ላለመቅጠርና ከነሱ ያነሰ ነጥብ ያላቸውን መቅጠሩ ተሰምቷል፤ አዋሳ ዩኒቨርሲቲም ተወዳድረው እንዳለፉ ሲነገራቸው ቆይቶ ሌሎች ከነሱ በታች የነበሩ ሲጠሩ እነሱ እስካሁን አልተጠሩም፡፡
• እናቱ ሙሉ ኣለማየሁ “አንቺ የዐረናው እናት፣ እንቺ የከሀዲው እናት ይህ የህ.ወ.ሐ.ት ምድር ነው- ወዴትም ውጪልን” ድረስ የሚደርሱ ከፍተኛ በደሎች፣ ለቃላት የከበዱ ግፎች እየተፈፀሙባት ነው፤
• ሌሎች ዘመድ አዝማዶቹም በተዋረድ በከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ ገብተዋል፣ ነገ በነሱ ላይም ምን እንደሚመጣ ስጋት ገብቷቸዋል፤
• ጀግናን መውለድ እዳው ብዙ ነው፤ በተለይም ደግሞ እዚህ በጭቆናዋ ምድር- በትግራይ! — ይላል የዘገባው መጨረሻ።

በሰሜን ሸዋ የመርሃቤቴ ወረዳ ህዝብ ከወያኔ የፀጥታ ሃይሎችና ፌደራል ጋር ከባድ ውጊያ እያካሄደ ነው፣

July22/2014

ውጥረት በሰሜን ሸዋ መርሃቤቴ በርትቷል

ደብረብርሃን አከባቢ መግቢያና መውጪያ መንገዶች ተዘግተዋል።
ለወረዳው አለም ከተማና አካባቢዋ አገልግሎት ይውላል ተብሎ ከብዙ ጊዜ በሁአላ የገባውን መብራት የወያኔ መንግስት ህዝቡ የሚገለገልበትን መብራት አቁሞ ትራንስፎርሜሽኖቹን ነቅሎ ለአስቸኩአይ ጉዳይ ይፈለጋል ብሎ ወደ ትግራይ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የወረዳው 27ቱም ቀበሌ ተጠራርቶ ትራንፈርመሩን በቁጥጥር ስር በማድረግ ከላይ ከተጠቀሱት የወያኔ የፀጥታ ሃይሎች ጋር ኣሁን ድረስ ውጊኣ እያደረገ ሲሆን እስካሁን 7 የወያኔ ወታደሮች የሞቱ ሲሆን ከህዝብ ታጣቂ በኩል 1 ሞቷል። ባሁኑ ሰዓት ወረዳውን መሉ በሙሉ የህዝቡ ታጣቂ ተቆጣጥሮት ይገኛል። ወያኔ ከአዲስ አበባና ከተለያዩ አካባቢወች ተጨማሪ ሃይል ወደ አካባቢው እያንቀሳቀሰ መሆኑ ታውቁኣል።ሁኔታው የሚመለከታችሁ ወገኖች ሁሉ እየሆነ ያለውን ሁሉ በመከታተልና አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉ ያስፈልጋል።
ቁስለኞች ሆስፒታሉን አጣብውታል ። ቁስለኞቹ የሚታከሙት በፖሊስ ታጅበው ሲሆን ህክምናውን እንደጨረሱ ውእደ እስርቤት ይወሰዳሉ ።ከቦታው የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት እስከመቼ ተታለን እንኖራለን የሚሉ የሰሜን ሸዋ ነዋሪዎች ዱር ቤቴ ብለው ሸፍተዋል። ከዚህ በታች የምትመለከቱት ከአከባቤው ከሚገኘው ሆስፒታል የተላከልንን ምስል ነው።

ዶክተሮቹን በስልክ ለማነጋገር እንደሞከርኩት የወመኔው ወታደሮች ቁስለኞች ከቁጥር በላይ ናቸው።
23
10502071054430

Monday, July 21, 2014

የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ” እጃችን ውስጥ ገባ!!

July 21, 2014
የዞን 9 ጦማሪያን አባላት “ በወያኔ የስለላ ተቋም ተደርሶበት የተከሰሱበት ማስረጃ”  እጃችን ውስጥ ገባ!!
AbbayMedia:  ለጥረታቸው እያመሰገን ኢትዮጵያውያን በሙሉ ይህንን የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ እውቀት እንዲጠቀሙበት እንመክራለን ።
ሙሉውን ዝርዝር እዚህ ላይ በመጫን ይመልከቱ፡-  https://securityinabox.org/am/howtobooklet
የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ

 ይህ የኢንተርኔት ደኅንነት መጽሐፍ ደኅንነቱ የተጠበቀ የኢንተርኔት ግንኙነት እንዲኖረን ማወቅ የሚያስፈልጉንን መሠረታዊ ነገሮች ለማብራራት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው። መመሪያው በኢንተርኔት ግንኙነት ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን በመለየትና በማብራራት፣ እነዚህን አደጋዎች ለመቀነስ የሚያስችል በተገቢ መረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ እንድንሰጥ ያስችለናል። ይህን ለማረጋገጥም ስምንት ከደኅንነት (ሴኵሪቲ)፣ ከመረጃ ጥበቃ (ዳታ ፕሮቴክሽን) እና ከጥብቅ ግንኙነት (ኮምዩኒኬሽን ፕራይቬሲ) ጋራ የተያያዙ ሰፋፊ ጥያቄዎችን ይመልሳል።

በእያንዳንዱ ምእራፍ መግቢያ የተነሳውን ርእሰ ጉዳይ ለማብራራት የተፈጠሩ ምናባዊ ክስተቶችና ገጸ ባህርያት ይገኛሉ። እነዚህ ገጸ ባህርያት የተወሰኑ ጉዳዮችን የሚያነሱበት እና የሚዘወተሩ ጥያቄዎችን የሚመልሱባቸው አጫጭር ምልልሶች በየምእራፉ ውስጥ ይገኛሉ። ከየምእራፉ የምንቀስማቸው ትምህርቶች ዝርዝርም በየምእራፉ ይቀርባል። በየምእራፎቹ የሚጋጣሙን በርካታ ቴክኒካዊ ቃላትና ስያሜዎች ትርጉም በመጽሐፉ መጨረሻ በማገናዘቢያ ዝርዝር ውስጥ ይገኛል። በማብራሪያው ውስጥ የሚጠቀሱ ሶፍትዌሮችን በተመለከተ “በአጠቃቀም መመሪያ” (Hands-on Guides) ውስጥ ተጨማሪ ማጣቀሻዎች እናገኛለን። በዚህ “የመርጃዎች ስብስብ” (ቱልኪት) ውስጥ የሚገኝ ምእራፍ ወይም መመሪያ ተነጥሎ ለብቻው ሊነበብ ይችላል፤ በወረቀት ለማተምም (ፕሪንት) ሆነ በኤሌክትሮኒክ መልኩ ለሌሎች ለማካፈልም የተመቸ ነው። ሆኖም “የኢንተርኔት ደኅንነት በእጃችን” (Security in-a-box) መመሪያው የሚጠቅሳቸውን በመጽሐፉ እና በሶፍትዌር መመሪያው ውስጥ ተበታትንው የሚገኙትን ሊንኮች (links) እና ማገናዘቢያዎች በሚገባ ብንከተላቸው ከመመሪያው የበለጠ ተጠቃሚ እንሆናለን። የዚህ “እንጎቻ መጽሐፍ” (Booklet) የታተመ ቅጂ ካለን “የአጠቃቀም መመሪያውን” (Hands-on Guides) በምንጠቀምበት ጊዜ ሁሉ ከአጠገባችን ቢኖር መልካም ነው። በእንጎቻ መጽሐፉ ውስጥ ስለአንድ ዘዴ የተጻፈውን ምእራፍ ጨርሰን ሳናነብና ዘዴውን በሚገባ ሳንረዳው የዲጂታል ደኅንነታችን አስተማማኝ መጠበቂያ አድርገን ልንቆጥረው አይገባም።

የሚቻል ሲሆን የእንጎቻ መጽሐፉን ምእራፎች በቅደም ተከተል ማንበብ የተመረጠ ነው። የኢንተርኔት ደኅንነትን (ሴኵሪቲ) ማስጠበቅ ሒደት ነው። አንድ ተጠቃሚ ኮምፒውተሩ ከቫይረሶችና ከማልዌር (Malware) ነጻ መሆኑን ሳያረጋግጥ የኢንትርነት ግንኙነቶቹ ምሥጢራዊነት ፍጹም የተጠበቀ እንዲሆን ለማድረግ ቢፈልግ ሙከራው አስተማማኝ ውጤት ሊያመጣ አይችልም። ሌባው አስቀድሞ እቤት ውስጥ ከገባ በኋላ በሩን ከውጭ እንደሚቆልፍ ባለቤት መሆን ማለት ነው። ይህ ማለት በዚህ መጽሐፍ ከሚነሱት ርእሰ ጉዳዮች መካከል አንዱ ከሌላው የበለጠ አስፈላጊ ነው ማለት አይደለም። ነገር ግን ወደ በኋላ የሚመጡት ምእራፎች ተገልጋዮች አስቀድመው ያውቋቸዋል ብለው ታሳቢ የሚያደርጓቸው መረጃዎችና እውቀቶች ይኖራሉ፤ ለምሳሌ አዳዲስ ሶፍትዌሮች (software) የምንጭንበት ኮምፒውተራችን ስላለበት ሁኔታ አስቀድመን እንደምናውቅ ታሳቢ ይደረጋል።

በእርግጥ እነዚህን ምእራፎች ያለቅደም ተከተል ለማንበብ እና ለመጠቀም የሚያስገድዱ በቂ ምክንያቶች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። በአጠቃቀም መመሪያው የተጠቀሱትን መሣሪያዎች/ሶፍትዌሮች መጫን ከመጀመራችን በፊት በኮሚፒውተራችን ውስጥ የሚገኙ እጅግ አስፈላጊ ፋይሎችን ወደ መጠባበቂያ ቋት መገልበጥን (back up) መማር ያስፈልገን ይሆናል። አለዚያም በምሥጢር መያዝ ያለባቸውን ፋይሎቻችንን በፍጥነት ለመደበቅ የሚያስገድድ ድንገተኛ ሁኔታ ሊገጥመን ይችላል፤ ይህ ደግሞ የሚገኘው በምእራፍ አራት ነው። ምናልባት ደግሞ ደኅንነቱ አስተማማኝ ባልሆነ የኢንተርኔት ካፌ ኮምፒውተር ስሱ መረጃዎችን ለመመልከት እንፈልግ ይሆናል። ለምሳሌ ያህል ከዚህ ኮምፒውተር በአገራችን የተከለከለ ድረ ገጽ ከፍተን መመልከት እንፈልጋለን እንበል፤ ይህን በቀላሉ ለመማር በቀጥታ “ማንነትን መደበቅ እና የኢንተርኔት ሳንሱርን ማለፍ” ወደሚለው ምእራፍ ስምንት እንዳንሔድ የሚከለክለን ነገር የለም።

1. ኮምፒውተርን ከማልዌር እና ከሰርጎ ገቦች (hackers) እንዴት መከላከል ይቻላል?
2. መረጃዎችን ከአካላዊ ጥፋት ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንችላለን?
3. አስተማማኝ የይለፍ (የምሥጢር) ቃል መፍጠር እና መጠቀም
4. በኮምፒውተራችን ውስጥ ያሉ ስሱ መረጃዎችን እንዴት መጠበቅ ይቻላል?
5. የጠፉ መረጃዎችን መልሶ ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው?
6. ስሱ መረጃዎችን በጥንቃቄ ማጥፋት የሚቻለው እንዴት ነው?
7. የኢንተርኔት ግንኙነታችንን በምሥጢር መያዝ ይቻላል? እንዴት
8. ማንነትን መደበቅ እና የኢንተርኔት ሳንሱርን/እገዳን ማለፍ
9. ደኅንነቱ የተጠበቀ የተንቀሳቃሽ (ሞባይል) ስልኮች አጠቃቀም
10. በማኅበራዊ ገጾች የራስን እና የመረጃዎችን ደኅንነት መጠበቅ
መፍቻ
ልብ ይበሉ የተከሰሱበትና “የወያኔ የመረጃ ስለላ ተቋም ማስረጃዪ ነው” ብሎ የያዘው ስለ ኢንተርኔት አጠቃቀም እውቀትን በማዳበራቸው ነው።ይህ ማንኛውም ተማሪ ወይም ሰው ሊያውቀውና ሊመራው የሚገባ የትምህርት አካል መሆኑንም የስለላ ተቋሙ ዘንግቶታል። ይሁን እንጂ ጦማሪዎቹ ለኢትዮጵያውያን የሚጠቅም ትምህርት በሚል ያዘጋጁቱን ትምህርት ሁሉም ሰው እንዲማርበት አጥብቀን እንመክራለን።