Sunday, May 25, 2014

ፖሊስ አቶ አስራት አብርሃን አስሮ “ያሉበትን አላውቅም” አለ

May 25/2014

የራት ፓርቲዎች መድረክ የሆነው መድረክ ትናንት በአዲስ አበባ ላደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቀደም ብለው የቅስቀሳ ስራ ሲሰሩ የነበሩ አስራ ሁለት ሰዎች በቡራዩ ከተማ በፖሊስ መታሰራቸውን የሰሙት የአረና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ሐብታይ ገብረ ሩፋኤልናበቅርቡ አንድነት ፓርቲን የተቀላቀለው ደራሲና ፖለቲከኛ አስራት አብርሃ እስረኞቹን ሊጠይቁ በሄዱበት በወረዳው ከታሰሩ በኋላፖሊስ አቶ ሐብታይን ሲለቅ አቶ አስራትን በወረዳው አሳድሯቸው ነበር፡፡

ዛሬ ማለዳ አቶ አስራትንና የመድረክ አባላትን ለመጠየቅ ወደ ቡራዩ ያመሩት የአቶ አስራት ባለቤትና የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች አቶ አስራት በፖሊስ ጣብያው አለመታሰራቸው ተነግሯቸዋል፡፡አቶ ሐብታይ በስፍራው በመገኘት
‹‹አስራት ከእኔ ጋር ታስሮ ነበር››ቢሉም የኦሮሚያ ፖሊስ ‹‹የምትሉትን ሰው እኔ አላሰርኩትም››የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡

በቡራዩ ከተማ ሶስት ፖሊስ ጣብያዎች በመኖራቸው አስራትን ፍለጋ ወደ ፖሊስ ጣብያዎቹ ያመሩት የአንድነት አመራሮች ተመሳሳይ ምላሽተሰጥቷቸዋል፡፡አብርሃ ደስታ በበኩሉ የአቶ አስራትን መታሰር በማስመልከት የሚከተለውን በፌስቡክ ገጹ አስፍሯል::

ፖለቲከኛ አስራት አብርሃም በደህንነት ሰዎች ከቡራዩ ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ ተወሰደ። ምንም ወንጀል ሳይሰራ በቡራዩ ከተማ ለሰለማዊ ሰልፍ ሲቀሰቅሱ የታሰሩ የመድረክ አባላትን ለመጠየቅ በመሄዱ ምክንያት ታፍኖ ከተወሰደ የሕገወጥ ዓማፂ ቡድን አባል ቢሆን ኑሮስ ምን ያደርጉት ነበር? ደሞ ሰለማዊ ሰዎችን እያፈኑ ከደርግ እንሻላለን ይሉናል! ደርግ ኮ እያፈነ የገደለን ሕገወጥ ዓማፂ ቡድን (ህወሓት) ስለነበረ ነው። በደርግ ግዜ ህወሓት ዓማፂ ሕገወጥ ቡድን ነበር። የህወሓት አባል የሆነ ወይ ህወሓትን የተባበረ ሁሉ እርምጃ ሲወሰድበት ደርግን እንቃወመው ነበር። አሁን ደግሞ ሰለማዊ ሕጋዊ ታጋዮችን እየታፈኑ የሚወሰዱበት ግዜ ላይ ደረስን! አሁን እንደ ህወሓት ያለ ሕገወጥ ድርጅት (ዓማፂ ቡድን) ቢኖር ኑሮስ ምን ያደርጉን ነበር? ወይ ግንቦት 20!



በአውሮፕላን ጎማ ስር ተደብቆ 5 ሰአት በአየር ላይ የተጓዘው ተአምረኛ ወጣት እናት ያለችው ኢትዮጵያ ነው

May 25/2014
ባለፈው ሰሞን ከካሊፎርኒያ ተነስቶ ሃዋይ ድረስ በአውሮፕላን ጎማ በመንጠላጠል የተጓዘው ወጣት ህይወት መትረፍ ተአምርመሰኘቱን መዘገባችን ይታወሳል። ይህ የ 16 ዓመት ወጣት ሶማልያዊ መሆኑ ሰሞኑን ሲዘገብ፣ እናቱ ደግሞ ያለችው ኢትዮጵያመሆኑ አብሮ ተነስቷል።

ሶማሌያዊዋ እናት ምርጊቱ ከጭቃ በተሰራ ደሳሳ ጎጆ ውስጥ ተቀምጣለች። ግድግዳው ከመሳሳቱ የተነሳ ነፋስ እንዳያስገባ በአሮጌአንሶላ ተሸፍኗል። ያለችው ሸደር በተሰኘ የስደተኞች መጠለያ ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው። እንግዲህ የካሊፎርኒያው የ 16 ዓመትወጣት ሶማሌያዊ አውሮፕላን ላይ የተንጠለጠለው እዚህች ስደተኛ እናቱ ጋር ኢትዮጵያ ለመምጣት በመፈለጉ ነበር።ዩባ መሃመድ የተባለችው ይህችው እናት፣ እሷን ናፍቆ አውሮፕላን ላይ ተንጠለጠለ የተባለው ይህን ልጇን ላለፉት 8 ዓመታት አላየችውም። ጸጉሯን የሸፈነችበትን ነጭና ጥቁር ሂጃብ እያሻሸች፣ያህያ አብዲ ስለተባለው ይኸው ወጣት ልጇ ስትናገር በእምባ ጭምር ነው። ለ 5 ሰአት ተኩል በአውሮፕላን ጎማ ተንጠልጥሎ ከአገር አገር ሄደ መባልን ስትሰማ እንደተንቀጠቀጠች ትናገራለች።ወጣቱ ያህያ አብዲ ካሊፎርኒያ ሊያሳድጉት በወሰዱት ቤተሰቦች ዘንድ ደስተኛ አልነበረም። ደስተኛ ያልሆነው በነሱ አያያዝ ሳይሆን፣እናቱን እጅግ በመናፈቁ ነበር። እናም ናፍቆቱ ሲብስበት ባለፈው ኤፕሪል 20 ቀን ፣ ከቤቱ በመውጣት ሳንሆዜ ከተማ ባለው አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አጥር ጥሶ ገባ። እናም በልጅነት ሃሳቡ፣ ወደ እናቱ ሊወስደው የሚችለው አውሮፕላን ነውና ፣ ያገኘው አውሮፕላን ጎማ ላይ ተንጠላጠለ። አውሮፕላኑ ደግሞ እንዳጋጣሚ ወደ ሃዋይ የሚሄድ ነበረ።

እሱ እንደተንጠለጠለ ፣ አውሮፕላኑ ተነሳ፣ ጎማውን አጠፈና ወደውስጥ ከተተ፣ ያህያ አብዲም አብሮ ውስጥ ገባ። ከዚያ በኋላ ነው አምስት ሰአት ተኩል ፣ በነጌቲቭ 50 ዲግሪና በ32ሺ ጫማ ከፍታ የተጓዘው። በዚያ ቅዝቃዜና ኦክስጅን አየር በማይገኝበት ሁኔታበህይወት መድረሱ እጅግ ተአምር ተሰኝቷል።“በጣም ጎበዝ ልጅ ነው ..” ትላለች ዩባ ስለልጇ ስትናገር .. “ጎበዝ ልጅ ነው፣ በጣም ይወደኛል፣ እኔን ለማየት እንደሚፈልግና እንደሚናፍቅም በልቤ አውቃለሁ። ግን አባቱ በፍጹም ከኔ ጋር እንዲገናኝ አይፈልግም፣ ለዚህ ነው “እናትህ ሞታለች” ብሎ የነገረው”አሁን በቅርብ ግን ወጣቱ ያህያ እናቱ በህይወት መኖሯን በወሬ ወሬ ሰማ። ከዚያ ወዲህ ናፍቆቱ ባሰበት። አባቱና ሶስት ወንድሞቹ አብረውት ካሊፎርኒያ ቢኖሩም ፣ እሱ ግን ድሮም ለ እናቱ ልዩ ፍቅር ነበረው።

በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኘው ሸደር የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ከ10ሺ በላይ ሶማሌያውያን ስደተኞች አሉ። ከነዚያ አንዷየሆነችው የያህያ እናት የ 33 ዓመት ወጣት ስትሆን፣ ላለፉት 4 ዓመታት እዚያ ቆይታለች። በስደተኞቹ ካምፕ ውስጥም አትክልትበመሽጥ ትንሽ ገንዘብ ለማግኘት ትሞክራለች።

ባለፈው ዓመት ታዲያ ከካምፑ ወጥተው ካሊፎርኒያ መምጣት የቻሉ ኡዌይ እና ጃማ የተባሉ ስደተኞች፣ ካሊፎርኒያ ክደረሱ በኋላለያህያና ለሌሎቹም ወንድሞችና እህቶቹ “እናታቸው በኢትዮጵያው ሸደር ጣቢያ እንደምትገኝ” ይነግሯቸዋል። በዚያ ጊዜ የተፈጠረውን ሁኔታ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ሃላፊ ፋቲ ሊዩኒ ሲናገሩ … “ልጆቹ በአባታቸው እንዴት ሞታለች ትለናለህ ብለው በጣም ተበሳጩ፣ አሁኑኑ ያለችበት ቦታ ካልሄድንም ብለው ተነሱ፣ አባታቸው ግን “ውሸት ነው ሞታለች” እያለ ይከራከራቸው ነበር” ነበር ያሉት።

ከዚያች ቅጽበት በኋላ ነው የ 16 ዓመቱ ወጣት ያህያ እናቱን ለማግኘት ቆርጦ የተነሳው። እናት ዩባ አብዱል ፣ ልጇ በአውሮፕላን ተንጠላጥሎ እሷን ፍለጋ መሄዱን የሰማቸው አሜሪካ ከሚኖርና ከምታውቀው ክበበው አበራ ከተባለ ሰው መሆኑን ትናገራለች።ከዚያ ወዲህ ከልጇ ጋር ለመገናኘት እሷም ውላ ማደር አትፈልግም። ሁሉም ተባብሮ እንዲያገናኛት ልመና ይዛለች።

ምኞቷም እውን ሊሆን የሚችልበት መንገድ መኖሩን የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ይናገራል። አሁን ወደ አሜሪካ ሊወሰዱ ከሚችሉ ስደተኞች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያውን ቃለመጠይቅ አልፋለች:፡ ሁለተኛውን ማጣሪያ ደግሞ ካለፈች በአንድ ዓመት ውስጥ አሜሪካ ልትሄድ ትችላለች። ተሳክቶላት ከመጣችም እሷን ለማግኘት ህይወቱን አደጋ ውስጥ ጥሎ በአውሮፕላን የተንጠለጠለውን ልጇን ታገኘው ይሆናል።

ከአድማስ ራድዮ የተገኘ

Saturday, May 24, 2014

የአኖሌ ሃውልት ፖለቲከኞችንና ምሁራንን እያወዛገበ ነው

May 24/2014

ታሪኩ አፈ ታሪክ ነው፤ በደንብ ሊጠና ይገባዋል ተብሏል

በአፄ ምኒሊክ ዘመን ተፈጽሟል የሚባለውን ኢ-ሠብአዊ ድርጊት ለማሳየት በኦሮሚያ አርሲ ዞን አኖሌ በተባለ ስፍራ የተገነባው ሃውልት፤ የታሪክ ምሁራንን እና ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ሲሆን፤ የታሪኩ እውነተኛነትና የሃውልቱ አስፈላጊነት አከራካሪ ሆኗል፡፡

ተቃራኒ አስተያየቶችን ለአዲስ አድማስ የሰጡ ፖለቲከኞች፤ ታሪኩ እውነተኛ ነው ወይስ አይደለም በሚለው ጥያቄ አልተስማሙም፡፡ በአኖሌ ተፈጽሟል የተባለው ጡት እና እጅ የመቁረጥ ድርጊት በታሪክ ሰነዶች ያልተመዘገበና ያልተረጋገጠ አፈታሪክ ነው የሚሉ ፖለቲከኞች፤ ሃውልቱ ጥላቻና ቂም በቀልን የሚሰብክ ስለሆነ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ በአኖሌ ኢሰብአዊ ድርጊት መፈፀሙ እውነተኛ ታሪክ መሆኑን የሚያምኑ ፖለቲከኞች በበኩላቸው፤ ሃውልቱ  መገንባቱ ተገቢ የሚሆነው  ድርጊቱ እንዳይደገም መማሪያ ስለሚሆን ነው ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የታሪክ መምህር አቶ አበባው አያሌው፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሴት ልጅ በጦርነት ጊዜ የተለየ ጥበቃ እንደሚደረግላት ጠቅሰው፤ በአኖሌ ጡት ተቆርጧል ለሚለው ማረጋገጫ የሚሆን የታሪክ ሰነድ የለም ብለዋል፡፡ አፈታሪኩ ከብሔርተኝነት ጋር ተያይዞ የተፈጠረ ነው ያሉት አቶ አበባው፤ አፈታሪክን መነሻ አድርጐ ሃውልት መገንባት አይገባም፤ ከዚህ በተጨማሪ ሃውልቱ ጥላቻና ቂም በቀልን ከማንፀባረቅ የዘለለ ፋይዳ የለውም ብለዋል፡፡

የታሪክ ምሁሩና ፖለቲከኛው ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በበኩላቸው፤ የሃውልቱን መገንባት እንደማይቃወሙ ገልፀው፤ ከአፈ ታሪክ የዘለለ ማረጋገጫ ሰነድ አልተገኘለትም፤ ነገር ግን ከታሪክ የመረጃ ምንጮች መካከል አንዱ አፈ ታሪክ በመሆኑ  በጉዳዩ ላይ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሃውልቱ መገንባት ጥላቻና ቂም በቀልን ለቀጣይ ትውልድ ያስተላልፋል የሚለውን አመለካከት እንደማይቀበሉት የገለፁት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፤ የታሪኩን እርግጠኛነት ከዩኒቨርስቲ መምህራን መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡ ሃውልቱም በትክክል ድርጊቱን ከማንፀባረቅና ለመማሪያ ከመሆን ባለፈ ጥላቻና ቂም በቀልን አያስተላልፍም ባይ ናቸው፤ አቶ ቡልቻ፡፡ የመድረክ አመራር የሆኑት አቶ ገብሩ ገ/ማርያም በበኩላቸው፤ የሃውልቱን መገንባት የሚቃወሙ ሰዎችን አጥብቀው ኮንነዋል፡፡ ጡት እና እጅ የመቁረጥ ድርጊት ተፈጽሟል የሚሉት አቶ ገብሩ፤ ፖለቲከኞች እና ምሁራን ይሄን ታሪክ ለማድበስበስ መሞከራቸው ተቀባይነት የለውም ሲሉ ተችተዋል፡፡ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ሞጋ ፈሪሣ በበኩላቸው፤ ጥንት የተደረገ ታሪክ እየተመዘዘ ለፖለቲካ ፍጆታ መዋሉን ይቃወማሉ፡፡ የአሁኖቹ ባለስልጣናት ሃውልቱን የማስገንባትም ሆነ ታሪኩን የመንገር የሞራል ብቃት የላቸውም የሚሉት ዶ/ር ሞጋ፤ ዛሬም ቢሆን የኦሮሞ ህዝብ በወገኖቹ እየተበደለ ነው ብለዋል፡፡ የፍልስፍና ምሁሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሠፋ፣ የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሃሪ እና የአንድነት ፓርቲ የቀድሞ አመራር ዶ/ር ሃይሉ አርአያ ሃውልቱን አጥብቀው እንደሚቃወሙ አመልክተው፤ የሃውልቱ መገንባት የፖለቲካ ሴራ ነው ሲሉ ኮንነዋል፡፡ ከሣምንታት በፊት የኦሮሚያ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙክታር ከድርን ጨምሮ የኦህዴድ ከፍተኛ ባለስልጣናት የመረቁት ይሄ አወዛጋቢ ሃውልት፤ ለግንባታው 20 ሚሊዮን ብር የወጣበት ሲሆን በውስጡ የአካባቢውን ባህል የሚያንፀባርቅ ሙዚየምን ጨምሮ የባህል ማዕከልን እንደማያካትት ታውቋል፡፡ 

ወያኔ በባሕርይው ጅብና ውሻ ነው::

May 24/2014


አውሬ አውሬነቱን አይረሳም” አለ ልበል ተወልደ (ተቦርነ) ስለአንበሣው ቀላቢውን መግደል ሲያወራ አሁን? አዎ፣ ብሏል፡፡ እውነት ነው ፤ አውሬ አውሬነቱን አይረሳም፡፡ ወያኔም ወያኔነቱን አይረሳም – እባብ የትምና መቼም ቢሆን እባብነቱንና የወጣበትን ጉድጓድ እንደማይረሣ ሁሉ፡፡ ወያኔ ፀረ-ኢትዮጵያ ነው፤ ወያኔ ፀረ-አማራ ነው፤ ወያኔ ፀረ-ሃይማኖት ነው፤ ወያኔ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ዴምክራሲ ነው፡፡ ወያኔ ኢትዮጵያንና ትውፊቶቿን ለማጥፋት የተነሱ የውጭ ኃይላት ብቸኛ ወኪል ነው - ‹የአድኅሮት ኃይላት ተላላኪ፣ የኢምፔሪያሊዝምና የቢሮክራሲያዊ ካፒታሊዝም አራማጅ ቅጥረኛ› ልበልና የደርግን ዘመን አብዮታዊ ትዝታ ልቀስቅስባችሁ ይሆን? ወያኔ እነኚህን መሰሎቹን የተፈጥሮ ሣይሆን የተጋቦት ባሕርያቱን መቼም አይረሳም - ቢጠግብም - ቢወፍርም -አገርና አካባቢ ቢለውጥም - እርስ በርሱ ቢጣላም - በሎሚ ተራ ተራ አንዱ አንዱን ቢያስርና ቢገርፍም - በማንኛውም ረገድ ወያኔ የተነሣበትን የወያኔነት ጠባይና ምግባሩን አይረሳም፡፡

 በዚያ ላይ ደግሞ ሰውን ጨምሮ በብዙ እንስሳት የማይታይ አንድ እጅግ አስገራሚ ጠባይ አለው፤ ያም “አህያ ለአህያ ቢራገጥ ጥርስ አይሳበርም” እንዲሉ በወያኔዎች መካከል ደም እስከመቃባት የደረሰ ጠብና ቅራኔ በነሣም እንደቃል ኪዳን ሆኖ ወያኔ ወያኔን ለሌላ አካል አጋልጦ የማይሠጥ መሆኑ ነው፤ ለዚህም ነው አቶ ስዬ አብርሃ ለአሳሪው ለአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ፍራሽ አንጥፎ ከነቤተሰቡ ልቅሶ ተቀምጦ እንደነበር መስማት የቻልነው - መቼም ስዬ እንደክርስቶስ መሓሪ ወይም እንደእግዚአብሔር ሁሉን ታጋሽና ቻይ ሆኖ ነው ብንል ራሱ ስዬ ይታዘበናል - ይህ አስገራሚ ክስተት ከዘረኝነትና ከጎጠኝነትጋር የተያያዘ መሆን አለበት፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ያን ሁሉ ግፍና በደል በኔና በቤተሰቤ ያደረሰብኝ ደብረታቦሬ የ‹ሀገር መሪ› ቢሞት ከሞራልና ከሃይማኖት እንዲሁም ከባህል አንጻር በደስታ ጮቤ መርገጡ ቢቀርብኝ ማቅ መልበሱና ሀዘን መቀመጡ ግን በሟቹ የመቀለድ ያህል እንደሚያስመስልብኝ እገምታለሁና የምሞክረው አይመስለኝም፡፡ የነእንትና ነገር ግን ‹አታሃዛዚቡና› እንደተባለው ነው፡፡ እያልኩ ያለሁት በመለስም ሆነ በሌሎች ወያኔዎች የተበደሉ ወያኔዎች አይዘኑ አይደለም፡፡ ከፈለጉ ቅጥ ባለው መንገድ ማዘን ይችላሉ፤ በይሉኝታቢስነታቸው ቀጥለውበት ትዝብት ውስጥ መግባትን ከቁብ ካልጣፉት ደግሞ ፊታቸውን መንጨትና ሰባትም ዐሥራ አራትም ዓመት ከል መልበስ ይችላሉ፡፡ መጠቆም የፈለግሁት የነሱን ጠብ በውኃ እንደሚፀዳ ተራ ነገር የሚቆጥሩ ሲሆኑ፣ በሌሎች ላይ ቂምና የነገር ቁርሾ ከቋጠሩ ግን ባላጋራዎቻችን ናቸው ብለው የፈረጇቸውን ዕድለቢስ  ወገኖች መቀመቅ ካላስገቡ በቀላሉ የማይለቁ እጅግ ሲበዛ መርዘኛ መሆናቸውን ነው፡፡  


አለመለከፍ ማለት ቀድሞውን ወያኔን አለመሆን ወይም ወያኔን ሆኖ አለመፈጠር ነው እንጂ አንዴውኑ በወያኔነት ልምሻ ከተኮደኮዱ በኋላ የፈውሱ ነገር አዳጋች ነው - በተለይ እንዳሁኑ ዘመን ጊዜ እየነጎደ በሄደ መጠን የተፈጠሩበትን ዕለት እስከመራገም ለሚያደርስ አሰቃቂ የመጨረሻ ዕጣ ይዳርጋል፡፡ ከዚህ ከወያኔው ዓይነት የዘረኝነት ልክፍት የሚፈወሱና ጤነኛ ሰው የሚሆኑ - ጤነኛ ሆነውም አውቀው አምነውበትም ይሁን ሳያውቁ ተታልለው የበደሉትን ሀገርና ሕዝብ ለመካስ የሚተጉ እጅግ ጥቂቶች ናቸው - ያም እንደገና የመወለድ ያህል መታደል ነው - ለነሱም ለሀገርም፡፡ እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች ደግሞ የዕንቁ ያህል ውድ ናቸው፤ በቀላሉና የትም አናገኛቸውም፡፡ እናም እንግባባ - ወያኔ ወያኔነትን የትም ሆኖና በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆኖ  ለአፍታም አይዘነጋትም፡፡ መዘንጋት ለኅልውናው አደጋ እንደሆነ ያህል ስለሚቆጥረው ይመስለኛል፡፡ አንዲት ማረሚያ ቤት የምትገኝ  የወያኔ ወታደር ከዚህ በፊት በጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ላይ ፈጸመችው የተባለው አስነዋሪ የዘረኝነት ድርጊትም ከዚህ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ነው - ለዚህች ደንቆሮ ‹እሥረኛ› ወያኔነት ማለት የገነትም የመንግሥተ ሰማይም ገዢ ነው - ‹እሥር ቤቱና አሣሪዎቹ እኛው እስከሆን ድረስ፣ ገዢዎቹ እኛው እስከሆን ድረስ ይበልጥ እሥረኛ ሌሎች እንጂ እኛ አይደለንም› ብላ ሳታምን አልቀረችም(ይህ ዓይነቱ ከፍተኛ ሞኝነት የሚነበብበት የወያኔዎች አካሄድ የጆርጅ ኦርዌልን “All animals are equal, but some animals are more equal than the others.” የሚለውን ያስታውሰኛል፡፡) የብዙዎቹ ወያኔዎች መርሆ  እነዚህ ብሂሎች ልብ እንድንል ያደርጉናል፡- “የዘሬን ብተው ያንዘርዝረኝ”፣ “ትንሽ ሥጋ እንደመርፌ ትወጋ” ፤ “የሥጋ ትል የዘመድ ጥል” ፣ በእንግሊዝኛው ደግሞ  “Blood is thicker than water.”  ይህ የወያዎች ‹የዋህነት› የሚያሳየን ግን የእግዚአብሔርን መንገድና ትክክለኛውን ማኅበረሰብኣዊ የዕድገት ደረጃን ሣይሆን በዝቅተኛ የንቃትና የዕውቀት ደረጃ የሚገኙ የሌሎች እንስሳትን ነሲባዊ የመሳሳብ ጠባይ ነው፡፡ ሰው ከሰውነት ደረጃ ወርዶ እንዲህ ያለ የደምና የአጥንት ማነፍነፍ ቅሌት ውስጥ ሲገባ ማየት ደግሞ በማኅበረሰብም ይሁን በሀገር ደረጃ ከፍተኛ አለመታደልና የሀፍረት ምንጭም ነው፡፡
የተወልደ በየነ ንግግር እንደዐረብ ጣቢያ ድንገት ጣልቃ ገብቶብኝ በርሱ አባባል ጀመርኩ እንጂ አነሳሴ ቲቪ እያየሁ ሳለ በተጓዳኝ እያነበብኩት በነበረውና አሁን በጨረስኩት አንድ ድንቅ መጣጥፍ ላይ ተመርኩዤ የበኩሌን ጥቂት ለማት ነበረ፡፡ ይህን መጣጥፍ ያገኘሁት በዘሀበሻ ድረ ገጽ ላይ ነው - በፒዲኤፍ የቀረበና ከሰሞነኛ መጣጥፎች ቀልቤን ክፉኛ የሳበ ቆንጆ ጽሑፍ ነው፡፡ ይህ ግሩም ጽሑፍ የቀረበው ከአንድ በስደት ላይ እንደሚገኝ የገለጸ የቀድሞ የመንግሥት ሚዲያ ዘጋቢና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ ነው፡፡ ጽሑፉ የሚያትተው ወደፊት መጽሐፍ ሆኖ ይወጣል ከተባለና አንድ የወያኔ ከፍተኛ ባለሥልጣን ይሄው የመንግሥት ሚዲያ ዘጋቢ ከሀገር ሊወጣ ሲል  ለሰባት ሰዓታት ያህል በመቅረፀ ድምጽ አጋዥነት ሰጠው ከተባለው የኑዛዜ ቃል ተቀንጭቦ የቀረበ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ርዕሱ “በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ ከሚገኝ የልብ ወዳጄ ጋር በአገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያደረግሁት ምሥጢራዊ ውይይት” ይላል፡፡ ትንሽ ረዘም ቢልም መነበብ ያለበት ማለፊያ ጽሑፍ ነውና እባካችሁ አንብቡት - ሀገር በጣር ላይ እያለች ለማንበብ መድከም የለብንም፡፡ በተፋፋመ ጦርነት ውስጥ ገብቶ ለሀገር መዋደቅስ አለ አይደል? እየቀነጨብኩ ለፈርጥ ያህል በዚች መጣጥፍ ውስጥ በመጠኑ እንዳልጠቅስላችሁ ጽሑፉን ከፒዲኤፍ ወደወርድ ስለውጠው አንዳንድ ሆሄያት ቅርጻቸው እየተንሻፈፈብኝ ተቸገርኩ፡፡ ወያኔ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚተገብራቸውን ሥልቶች ብዙዎቹን ታገኙበታላችሁ፡፡ ወያኔ የቱን ተመርኩዞ የቱን እንደሚያጠፋና ቀጥሎም አንዱን ለማጥፋት የተጠቀመበትን ምርኩዝ ሰባብሮ የትም እንደሚጥል - ባጭሩ ሕወሓት አስብቶ አራጅ መሆኑን ትረዱበታላችሁ›፡፡ በምታምኑት ይሁንባችሁና ግዴላችሁም አንብቡት!
ወያኔ በባሕርይው እንደጅብም፣ እንደውሻም፣ እንደዓሣማም፣ እንደእስስትም፣ እንደእባብም … ነው፡፡ ለወያኔ የባሕርይ መግለጫነት የማይሆኑ ርግብን የመሳሰሉ የዋሃን ፍጡራን ብቻ ናቸው፡፡ በተረፈ ወያኔ ማለት የክፋት ተምሳሌት የሆኑ የተፈጥሮም ይሁኑ ሰው ሠራሽ ነገሮች ውሁድ ሥሪት ነው፡፡ የክፋት አድማሱ ደግሞ ወሰን የለውም፡፡ ድንበር የለሽ ክፋት ደግሞ ድንበርን ተሻግሮ ብዙ ዘመናትን የማጣቀስ ጠባይ አለው፡፡ ለዚህ ነው የክፋት አምባሳደሩ ወያኔም ሞተ ሲሉት እየተነሳ በአፈ ታሪክ ዘጠኝ ነፍስ ያላት መሆኗ እንደሚወራላት ድመት እስካሁኒቷ ቅጽበት ድረስ በአፀደ ሕይወት ሊገኝ የቻለው፡፡
የወያኔ ውሻዊ ባሕርይ፡፡ ውሾች እርስ በርስ ሊዋደዱም ላይዋደዱም ይችላሉ፡፡ ግን ግን እነሱም ልክ እንደብዙዎቹ እንስሳት ዘር መንጣሪና ከ”species”ኣቸው ውጪ ከሌሎች ጋር እምብዝም አይቀላቀሉምና በአደንም ሆነ በሥሮት ወቅት  አይለያዩም፡፡ ወያኔዎች ከውሻ የወሰዱት ጠባይ ታዲያ ውሾች በግላቸው የፈለጉትን ያህል ይጣላሉ፣ ይነካከሳሉም እንጂ የውጪ ጠላትና የአደጋ ሥጋት ከተደቀነባቸው ቂጣቸውን ይገጥሙና ያን ጠላት በጋራ ይከላከላሉ፤ በክፉ ቀን በመካከላቸው ንፋስ አይገባም፡፡ አጥንት ላይ የተፋጠጡና የሰገሌን ጦርነት በውሻኛ “version” ሊደግሙት የተዘጋጁ ውሾች ሳይቀሩ ያን ሆድ-ተኮር ጠብ በጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት አቁመው የመጣባቸውን የጋራ ጠላት በጋራ ይጋፈጣሉ፤ በውነቱ ይህ መልካም ጠባይ ነው፡፡ በወያኔዎች ላይ ብቻ ተወስኖ መቅረቱና በሰባና ሰማንያ ሚሊዮን በሚገመተው አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁም በሌሎች የፖለቲካና ማኅበረሰብኣዊ ስብስቦች ዘንድ አለመሥራቱ ግን ያሳዝናል፤ ይቆጭማል፡፡ እነሱ ብልጥ ሲሆኑ ሌላው ጅላንፎ ሆኖ እስከወዲያናው በሚመስል ሁኔታ ሲጃጃል መታዘብ ትልቅ ቁጭት ነው፡፡ ከውሻ እንኳን መማር ያቃታቸው ኢትዮጵያውያን ተቃዋሚዎች ወያኔ በቀደዳለቸው የልዩነት መስመር እየተመሙ ለወያኔው ዕድሜ መራዘም ጠንክረው በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡ መቼ ነፍስ እንደሚያውቁና ለከርታታው ‹ሕዝባቸው› መሢሕነታቸውን እንደሚያሳዩ አናውቅም፡፡ ውሻ በበጎም ሆነ በክፉ ብዙ ተጠቃሽ ባሕርያት ቢኖሩትም ለጊዜው ይህ በቂየ ነው፡፡
የወያኔ ጅባዊ ጠባይ፡፡ ጅብ ፈሪ ነው፡- ወያኔም በጣም ፈሪ ነው፡፡ ገደልኩት ብሎ የሚያምነውን ‹ጠላቱን› እንኳን የሚፈራና መቃብር ውስጥም ገብቶ ዐፅምን በምናባዊ የስድብና የምፀት ጅራፍ የሚገርፍ፣ በሙታንም ላይ የሚሣለቅና የሚቀልድ ነው - ወያኔ፡፡ ለምሳሌ አማራንና ኦርቶዶክስን ገድሎ እንደቀበራቸው በወያኔዊ መድረኮች ካላንዳች ሀፍረትና ይሉኝታ እየተደሰኮረ ነው፡፡ ግዴለም ሞቱ እንበል፡፡ በሕይወት ያሉ እየመሰለው ታዲያን በባነነ ቁጥር በሚናገራቸው የዕብሪት ቃላቱና በሚያከናውናቸው ፀረ-ሕዝብ ተግባራቱ  ለትዝብት እንደተዳረገ አለ ፡፡ ፍርሀት በራስ የመተማመን ችሎታን ያሳጣል፤ ፍርሀት ቤቱን የሠራበት ሰው እንደመለስ ተሳዳቢና አሽሟጣጭ ይሆናል፡፡ ፍርሀት ያሸነፉትን ጠላት እንዳላሸነፉት በማስቆጠር ቀን በእውን ሌት በውን እያስባተተና እያስቃዠ ወንጀለኛና ኃጢኣተኛ ያደርጋል፡፡ የወያኔ ወንጀል እየተቆለለ ሄዶ ለፍርድ አስቸጋሪ እስኪሆንበት ድረስ ፈጣሪን እያስጨነቀ ያለው እንግዲህ ከዚህ መሠረታዊ ምክንያት በመነጨ መሆን አለበት፡፡ እንዲያ ባይሆንስ ቁናው ከሞላ ሰንብቷል፡፡
ጅብ ሆዳም ነው፡፡ የጅብ ሆድ ደግሞ የሚመርጠው የለም፡፡ ያገኘውን እየሰለቀጠ ወደጎሬው ይገባል፡፡ የነጋበት ጅብ በተለይ አይጣል ነው፡፡ ወያኔ እንደዛሬው ሳይነጋበትም ሆነ እንደዱሮው በጊዜ ያገኘውን ሁሉ ማግበስበስ መነሻና መድረሻ ዋና ጠባዩ ነው፡፡ ወያኔ አይጠግብም - እምብርት የለውምና፡፡ ከመሰል ሰብኣዊ ጅቦች ጋር ሆኖ ኢትዮጵያን ራቁቷን እያስቀራት ያለ ወያኔ ነው፡፡ ጅብ ሆዳም ብቻ አይደለም፡፡ የብዙ ብልሹ ምግባራት ተምሳሌት ነው፡፡ ለአብነት እርስ በርሱ አይተማመንም፡፡ ከዚያም የተነሣ ሲሄድ እንኳን ፊትና ኋላ ሆኖ ሳይሆን ጎን ለጎን ሆኖ ነው ይባላል፤ በተለይ የቆሰለ ጅብ በመንጋው ውስጥ ካለ በጣም ካልተጠነቀቀ በስተቀር ከአህያ ያልተናነሰ ዕድል እንደሚገጥመው ይነገራል - በቁሙ ነው አሉ እሚዘረጥጡት፡፡ ወያኔም እንደዚሁ ነው፡፡ አይተማመኑም፤ እርስ በርስ ይበላላሉ፡፡ ተባልተው ተባልተው መጨረሻቸው ደርሷል እየተባለ ነው አሁን፡፡ ለሰው ማን እንዲህ ሹክ እንደሚለው አላውቅም፤ ግን ‹መዥገሩ ወያኔ በደም አብጦና በደም ሰክሮ ሊፈርጥና ሊበታተን ነው› እየተባለ በየቦታው ሲወራ እሰማለሁ - ወፍ ትሆናለች እንዲህ እያለች ምሥጢር እያወጣች ያለች - እንዳፏ ያድርግልን፡፡ ለመሆኑ ግና - መለስ ብለን መለስን ስናስታውስ የወዲ ዜናዊ ሠይፍ ያልቀላው ትላልቅና ትናንሽ ወያኔ አለ ወይ? እንዴ፣ ያልተቆረጠመ ሰው እኮ የለም፤ የመለስ ነዲድና ፍላጻ ሞኛሞኙንና ቅን ታዛዡን ብቻ መርጦ ትቷል፡፡ በልዩ ወርቃማ ዕድል ከዐይኑ የተሠወሩበት ጥቂት ብልጣብልጦችና አድርባዮች ለዘር እንዲተርፉ የመለስ ውቃቢ አምላክ ምሯቸው እንደሆነ እንጂ መለስ የፈጀው ሕዝብ እኮ በውነቱ ከግምት በላይ ነው፤ መለስ ዜናዊ? ኧሯ! በጊዜ መሰብሰቡ በጄ(ን/-ኣቸው(?)) እንጂ ከርሱ ሾተል ማን ሊተርፍ ይቻለው ነበር? በተለይ እሱ የወያኔ ባለሥልጣን ከሆነበት የብረት ትግሉ የመጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ በዚህ ሰውዬ ሥውርና ግልጽ ትዕዛዝ እንዲሁም የሽርና የተንኮል ሤራ በመርዝና በጥይት ብዙ የወያኔ ታጋይ እንዳለቀ ለጉዳዩ ቅርበት ባላቸው ሃቀኛ ወገኖች የተጻፉ ድርሳናት ይመሰክራሉ - የገብረ መድኅን አርአያ ጽሑፎችን ያነቧል፡፡ ይሄ ሁሉ እየታወቀ ግን መለስን እስከማምለክ ተደርሷል - ምክንያቱም መለስን መቃወምና መንቀፍ ማለት ከጥቅምና ከጋርዮሽ ዘውጋዊ ቁርኝት ጋር ይጣረሳላ! ምክንያቱም መለስን መቃወም ማለት አሁን የተደረሰበትን የአንድ ብሔር ሸፋፋና ቅጥየለሽ “የበላይነት” ሊያሳጣ እንደሚችል ይታመናላ! ድንቄም የበላይነት! የበላይ የሆኑትስ እየተበደሉና እየተረገጡ የሚገኙት በርካታ ሚሊዮን ወገኖች ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ እየተራቡና እየተጠሙ፣ እየታረዙና እየታመሙ፣ እየተጋዙና እየተገደሉ፣ በእሥርና በስደት አሰቃቂ ሕይወትም መከራቸውን እየበሉ ያሉት ምሥኪኖች ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ በገዛ ሀገራቸው እንደሦስተኛና አራተኛ ዜጋ ተቆጥረው የማንኛውም የኢኮኖሚና የፖለቲካ መብታቸው ሳይከበርላቸው እንደከብት እንዲኖሩ የተገደዱ ትግሬውን ጨምሮ የየትኛውም ዘውግ አባላት ናቸው፡፡ የበላይ የሆኑትስ ለኅሊናቸው ያደሩና ሀገራቸውን ከወያኔ ጋር ተባብረው ያልሸጡ የሁሉም ዘውግ አባላት ወገኖቻችን ናቸው፡፡ ማን የበላይ ማን ደግሞ የበታች እንደሆነ በጊዜ ሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ በጮማ ግሣትና በውስኪ ብስናት ሕዝብ ላይ እያቀረሹ መኖር የበላይነት መገለጫ ሳይሆን የአውሬነትና የእንስሳነት ጠባይ ማሳያ ነው፡፡ ኤዲያ … በቃኝ እባክሽ፤ አናጋሪዎች!

በራችንን ከፍተን የወያኔን ሌብነት ማቆም አንችልም!

May 24/2014
ግንቦት 7
የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ስልጣናቸውን በህዝብ ፈቃድ ላይ እንዳልቆመ አሳምረው ያውቃሉ። ነጻ የህዝብ ምርጫ ቢኖር ምን እንደሚሆኑ የዛሬ ዘጠኝ አመት በአይናቸው አይተዋል፣ በጀሮቸው ሰምተዋል። ከዚያ ተመክሮ ተነስተው ዳግም የህዝብ ፈቃድ ላለመጠየቅ ምለዋል። ቅዱሱን የዴሞክራሲና የፍቅር መንገድ ሳይሆን ሳይጣናዊውን የከፋፍሎና አናክሶ የመግዛትን መንገድ ዋና ምርጫቸው አደርገው ከወሰዱ ሰንብተዋል። የፍትህና የዴሞክራሲ ሂደት በኢትዮጵያ እነሱ እስካሉ ድረስ እንዳይነሳ አድረገው ቀብረውታል። በራሳቸውና ጥቅማቸው ላይ ኮሽታ በመጣባቸው ቁጥር ችግሩ በምስኪኑና የነሱ ሰለባ በሆነው ህዝብ ውስጥ መካከል እንደተፈጠረ ግጭት ለማስመሰል እና ለማድረግ የማያደርጉት ነገር የለም።
ወያኔ ሰሞኑን በመላው የኦሮሞ ተወላጆች የመጣበትን ተቃውሞ የአማራና የኦሮሞ ህዝቦች ጠብ ለማድረግ ያላደረገው ነገር የለም። መሰረታዊ የሆነውን የኦሮሞ ተማሪዎች ጥያቄ የባህርዳር እና በሌሎች የሀገሪቱ የሚገኙ ተማሪዎች ደግፈው ሂወታቸውን ያጡለትን የጋራ የወገንን ጥያቄ ለመቀልበስና፣ የኦሮሞና የአማራ ህዝብ ጠብ ለማድረግ ያላደረገው ጥረት የለም።
መሰረታዊ የሆነውን የኦሮሞ ተማሪዎች ጥያቄ በጥይት ብቻ ሊመልሰው እንደማይችል የተረዳው ወያኔ፤ በግርግሩ ውስጥ አማሮችና ኦሮሞዎች ደም እንዲቃቡና እንዲጋጩ አድርጎ ገላጋይ ለመምሰል የሚያደርገው ሙከራ ባይሳካለትም ይህን ተንኮል በህዝቡ ውስጥ የመትከል አባዜ ስራውን በስፋት ተያይዞታል። ሰሞኑን በመላው ኦሮምያ ካድሬ በማሰማራትና ገላጋይ በመምሰል ዋናውን የወያኔ መሬት ዝርፊያ ይቁም የሚለውን ጥያቄ በማለባበስና በማፈን ዘዴ ላይ ይገኛል።
ወያኔ ይህን ስልት የመረጠው ወያኔን የምንቃወም የነጻነትና የዴሞክራሲ አንድነት ሃይሎች የትብብር ደረጃ ያለበትን ሁኔታ ከግንዛቤ በማስገባት ነው። በርግጥ ይህን ሳይጣናዊ በር የከፈትንለት እኛው የነፃነትና የዴሞክራሲ ሃይሎች ነን። በመካከላችን የተቀናጀና የተባበረ እንቅስቃሴ ማድረግ አለመቻላችን በብዙ መልኩም ህዝባችን የሚያስተባብር የጋራ አመራር በመጥፋቱ ነው።
የወቅቱም ሆነ የዘላቂው ችግር መፍቻ ይህ የዴሞክራሲና የነጻነት ሃይሎች የተግባር ህብረትና ቅንጅት መሆኑን ለመማሪያ ከሰሞኑ ተሞክሯችን የበለጠ መማሪያ ያለ አይመስለንም። የወያኔ ጉልበት የተቃዋሚዎች ክፍፍል ብቻ ነው። እኛ ተጠቂዎቹ የችግሩን ማስወገጃና የዘላቂ የሀገራችንን ህይዎት የሚመራ የጋራ ራእይ አለማበጀታችን ነው። ሌባው ህዝባችንን የሚከፋፍልብን በራችንን በርግደን ስለከፈትን እና ለመከፋፈል ስለተመቸናቸው ነው። ይህን በር ከፍተን እስካቆየነው ድረስ የህዝባችን ደም በግፍ መፍሰሱ፣ ህዝባችን መዘረፉና በውርደት መኖሩ ይቀጥላል።
ከወያኔ ፍትህም ሆነ የህዝባችን መሰረታዊ ችግር መፍትሄ አይጠበቅም። ከእባብ እንቁላል ርግብ መጠበቅ አይቻልምና።
ግንቦት 7 የየፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ በኢትዮጵያ የአንዱ ብሄረሰብ ችግርየሚፈታው የሁላችንም ችግር ሲፈታ መሆኑን ያምናል። የተናጠል ትግላችን ከሚያስጠቃን በቀር ውጤት የለውም ብሎ ያምናል።
በእኛ የግንቦት 7 አስተያየት የሰሞኑ የወያኔ ጭካኔና ደባ ከቁጭት ዘሎ የዘላቂ መፍትሄ መፈለጊያ እድል አድረገን ልንጠቀምበት ይገባል። ይህንና ተመሳሳይ ጥቃቶችን ተባብረን መመከት ባቃተን ቁጥር የህዝባችን መከራ እያራዘምን ነው። በዚህ ወቅት ህዝባችን ከአገራችን አጽናፍ እስከ አጽናፍ አንድ ድምጽ መሰማት መቻል ይኖርበታል። የሁላችንም አይን ያን ጊዜ ወያኔና ጉጅሌዎች ላይ ብቻ ይሆናል። ወያኔ የሚደግስልን የጎን ለጎን ግጭት ድግስ የሚከሽፈው ይህን ጊዜ ብቻ ነው።
በሚደርሱን መረጃዎች መሰረት ወያኔ በተለይ በኦሮሞ ህዝብና በሌላው ብሄረሰቦች መካከል ስር የሰደደ ጠብ ለመፍጠር በመራወጥ ላይ ይገኛል።
ለዚህ ተግባር የሚሆን የሰው፣ የገንዘብና የሚዲያ ሃይል አደራጅቷል። የተደገሰው የብሄር ለብሄር ግጭት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ብሄረሰብ ውስጥ ክፍፍል በመፍጠር ህዝብ የማባላት ድግስ ነው። ወያኔ ለውጪ አሳዳሪዎች የህዝቡን ደም የማፈሰው የእርስ በእርስ ግጭት ለማስወገድ ነው የሚል መልስ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል። ራሱ የሚያደርሰውን ጥፋት ሁሉ በተቃዋሚዎቹ እና በራሱ ህዝብ ውስጥ ባሉ ሰለባዎቹ ላይ ለማመካኘትና በዚሁ እብሪቱ ለመቀጠል መወሰኑን አረጋግጠናል።
ግንቦት 7 ዘወትር እንደሚለው ሁሉ ህዝቡ የወያኔ የተንኮል መሳሪያ እንዳይሆን የልዩነት በሩን እንዲዘጋ የቻለውን ሁሉ ያደርጋል። ለሁሉም የነጻነትና ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች የእንተባበር ጩኸቱንም ደግሞ ያሰማል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Friday, May 23, 2014

በሕገ ወጥ መንገድ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ

May 23/2014
ያለ በቂ ማስረጃ በሕገ ወጥ መንገድ ከአራት ሳምንት በፌት ከተያዙት ስድስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን በተጨማሪ በአንድ ጦማሪ አባል መኖሪያ ቤት ላይ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ፡፡

በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ በዞን ዘጠኝ ጦማሪና መስራች ሶልያና ሽመልስ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ፖሊስ ብርበራ ያካሄደ ሲሆን የጸረ-ሽብር ሕጉ ይፈቅድልናል የሚል ምክንያት ሰጥተው ያለ ፍርድ ቤት የብረበራ ማዘዣ ከካሜራ ቀራጭ ጋር የተገኙት ሰባት ፖሊሶች በጦማሪዋ ክፍል እና ሌሎች አስፈላጊ ነው ባሉዋቸው ክፍሎች ሲያካሂዱ ነበረውን ብርበራ ጨርሰው ይጠቅመናል ያሉትን የዶ/ር መረራ ጉዲና የመጨረሻ መጽሀፍ እና ሌሎች ወረቀቶች ወስደው ቤት ውስጥ የነበሩትን የጦማሪዋን ወላጅ እናት አስፈርመው ከጠዋቱ 4 ሰአት አካባቢ ቤቱን ለቀው ወጥተው ነበር፡፡ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ተመልሰው በመምጣት ተጨማሪ ፍተሻ በዋናው መኖሪያ ቤት መካሄድ እንፈልጋለን ብለው ሁለተኛ ዙር ብርበራ በምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ እናካሂዳከን በሚል ሰበብ ትንሹ ክፍል ውስጥ የጦማሪዋን እናት እነዲወጡ በማግለል ከማቀዝቀዛውን አንቀሳቅሰው አፍታም ሳይቆዩ 19 ገጽ የግንቦት ሰባት ፕሮግራም አግኝቻለሁ ሲል አንዱ ፈታሽ ተናግሯል፡።


የጦማሪዋን ወላጅ እናት እነዲፈርሙ ያግባቡ ቢሆንም ወላጅ እናትዋ ከክፍሏ እና ሌላም ቦታ በመፈተሽ ስታገኙ ያየሁት ወረቀት ላይ ፈርሜያለሁ ይህ ግን ምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ ያልነበረ እና እዚህ ያልተገኘ ሌላ ወረቀት ነው ሲገኝም አላየሁም በማለት አልፈርምም ብለዋቸዋል፡፡ በመሆኑም ፈታሾች ተጨማሪ የሰው ሃይል ደውለው በማስጠራት ለማግባባት ቢሞክሩም ስላልተሳካላቸው ይዘዋቸው የመጡትን የራሳቸውን ሁለት ምስክሮች ብቻ አስፈርመው ባለቤትዋ ለመፈረም ፍቃደኛ አይደሉም ብለው ቤቱን ለቀው ሄደዋል፡፡ ከፓሊስ ጋር የመጡት ምስክሮች አንደኛው አድራሻቸው በብርበራ ምስክርነት ዶክመንቱ ላይ ያልተጻፈ መሆኑንም ለመረዳት ችለናል ፡፡


በብርበራው ወቅት በነበራቸው የ7 ሰአት ቆይታ የጦማሪዋን መጸሃፍት የጉዞ ትኬቶች የስልጠና ማንዋል እና የመሳሰሉትን ጥቃቅን ወረቀቶች የወሰዱ ሲሆን ማብሰያ ክፍል ከፍሪጅ ጀርባ አገኘነው ካሉት ወረቀት ግን ቤት ውስጥ ያልነበረና ፓሊሶች ራሳቸው ያመጡት በመሆኑ እናትዋ ተናግረዋል፡፡
የዞን ዘጠኝ ጦማሪ አባላት ከየትኛውም በፓርላማ በአሸባሪነት ከተፈረጀ የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑና ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው እነዲሁም አነዚህ ድርጅቶች ላይ በተለያየ አጋጣሚ ትችቶቻቸውን ሲያቀርቡና ሲቃወሙ የሚታወቁ ቢሆንም ሲሆን በተያዙት አባሎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስገድዶ ለሃሰተኛ መረጃ እንዲፈርሙ የማድረግ ተግባር ሳያንስ ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ለማያያዝ ማስረጃን እንደተገኘ አድርጎ የማቅረቡ ተግባር መንግሰት ይታማበት የነበረውን የፓለቲካ ውንጀላን በሽብር የመቀየር ክስ በተግባር እንድናይ ያስቻለን ነው ፡።
በመሆኑም አሁንም ቢሆነ ጦማሪ ጓደኞቻችን ሃሳባቸውን በነጻነት ከመግለጻቸው ውጪ ምንም አይነት የወንጀልም ሆነ ሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው እያስታወስን መንግስት ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አንዲፈታ አሁንም አንጠይቃለን፡፡
#‎FreeZone9bloggers‬‪#‎FreeEdom‬ ‪#‎FreeTesfalem‬ ‪#‎FreeAsemamaw‬ ‪#‎Ethiopia‬
Photo: በሕገ ወጥ መንገድ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ፡፡ #FreeZone9bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsemamaw #Ethiopia
Minilik Salsawi Via Zone 9
ያለ በቂ ማስረጃ በሕገ ወጥ መንገድ ከአራት ሳምንት በፌት ከተያዙት ስድስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን በተጨማሪ በአንድ ጦማሪ አባል መኖሪያ ቤት ላይ ፖሊስ ለ7 ሰአት የቆየ ብርበራ አካሄደ፡፡
በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ በዞን ዘጠኝ ጦማሪና መስራች ሶልያና ሽመልስ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ፖሊስ ብርበራ ያካሄደ ሲሆን የጸረ-ሽብር ሕጉ ይፈቅድልናል የሚል ምክንያት ሰጥተው ያለ ፍርድ ቤት የብረበራ ማዘዣ ከካሜራ ቀራጭ ጋር የተገኙት ሰባት ፖሊሶች በጦማሪዋ ክፍል እና ሌሎች አስፈላጊ ነው ባሉዋቸው ክፍሎች ሲያካሂዱ ነበረውን ብርበራ ጨርሰው ይጠቅመናል ያሉትን የዶ/ር መረራ ጉዲና የመጨረሻ መጽሀፍ እና ሌሎች ወረቀቶች ወስደው ቤት ውስጥ የነበሩትን የጦማሪዋን ወላጅ እናት አስፈርመው ከጠዋቱ 4 ሰአት አካባቢ ቤቱን ለቀው ወጥተው ነበር፡፡ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ተመልሰው በመምጣት ተጨማሪ ፍተሻ በዋናው መኖሪያ ቤት መካሄድ እንፈልጋለን ብለው ሁለተኛ ዙር ብርበራ በምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ እናካሂዳከን በሚል ሰበብ ትንሹ ክፍል ውስጥ የጦማሪዋን እናት እነዲወጡ በማግለል ከማቀዝቀዛውን አንቀሳቅሰው አፍታም ሳይቆዩ 19 ገጽ የግንቦት ሰባት ፕሮግራም አግኝቻለሁ ሲል አንዱ ፈታሽ ተናግሯል፡።
የጦማሪዋን ወላጅ እናት እነዲፈርሙ ያግባቡ ቢሆንም ወላጅ እናትዋ ከክፍሏ እና ሌላም ቦታ በመፈተሽ ስታገኙ ያየሁት ወረቀት ላይ ፈርሜያለሁ ይህ ግን ምግብ ማብሰያ ክፍል ውስጥ ያልነበረ እና እዚህ ያልተገኘ ሌላ ወረቀት ነው ሲገኝም አላየሁም በማለት አልፈርምም ብለዋቸዋል፡፡ በመሆኑም ፈታሾች ተጨማሪ የሰው ሃይል ደውለው በማስጠራት ለማግባባት ቢሞክሩም ስላልተሳካላቸው ይዘዋቸው የመጡትን የራሳቸውን ሁለት ምስክሮች ብቻ አስፈርመው ባለቤትዋ ለመፈረም ፍቃደኛ አይደሉም ብለው ቤቱን ለቀው ሄደዋል፡፡ ከፓሊስ ጋር የመጡት ምስክሮች አንደኛው አድራሻቸው በብርበራ ምስክርነት ዶክመንቱ ላይ ያልተጻፈ መሆኑንም ለመረዳት ችለናል ፡፡
በብርበራው ወቅት በነበራቸው የ7 ሰአት ቆይታ የጦማሪዋን መጸሃፍት የጉዞ ትኬቶች የስልጠና ማንዋል እና የመሳሰሉትን ጥቃቅን ወረቀቶች የወሰዱ ሲሆን ማብሰያ ክፍል ከፍሪጅ ጀርባ አገኘነው ካሉት ወረቀት ግን ቤት ውስጥ ያልነበረና ፓሊሶች ራሳቸው ያመጡት በመሆኑ እናትዋ ተናግረዋል፡፡
የዞን ዘጠኝ ጦማሪ አባላት ከየትኛውም በፓርላማ በአሸባሪነት ከተፈረጀ የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆኑና ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው እነዲሁም አነዚህ ድርጅቶች ላይ በተለያየ አጋጣሚ ትችቶቻቸውን ሲያቀርቡና ሲቃወሙ የሚታወቁ ቢሆንም ሲሆን በተያዙት አባሎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስገድዶ ለሃሰተኛ መረጃ እንዲፈርሙ የማድረግ ተግባር ሳያንስ ከሽብርተኛ ድርጅቶች ጋር ለማያያዝ ማስረጃን እንደተገኘ አድርጎ የማቅረቡ ተግባር መንግሰት ይታማበት የነበረውን የፓለቲካ ውንጀላን በሽብር የመቀየር ክስ በተግባር እንድናይ ያስቻለን ነው ፡።
በመሆኑም አሁንም ቢሆነ ጦማሪ ጓደኞቻችን ሃሳባቸውን በነጻነት ከመግለጻቸው ውጪ ምንም አይነት የወንጀልም ሆነ ሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት እንደሌላቸው እያስታወስን መንግስት ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አንዲፈታ አሁንም አንጠይቃለን፡፡

በአዲስ አበባ ከሚፈርሱ ቤቶች ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ እየተከሰተ ነው

May23/2014
ግንቦት ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተጠናክሮ በቀጠለው የቤት ፈረሳ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በድንገት ቤቶቻቸው እየፈረሱባቸው ንብረቶቻቸውን እየተዘረፉ ሜዳ ላይ እየወደቁ ሲሆን፣ ትናንት ሌሊት በድንኳን ተጠልለው ከነበሩት ነዋሪዎች መካከል የ4 ልጆች አባት የሆኑ ግለሰብ በጅብ ተበልተው ዛሬ ከፊል አካላቸው በፖሊሶች መነሳቱን የአካባቢው ሰዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

ፖሊሶች መረጃው እንዳይወጣ አካባቢውን ተቆጣጥረው ሰዎች እንዳይንቀሳቀሱ ሲያደርጉ የዋሉ ሲሆን፣ ቀሪው አስከሬን ከተነሳ በሁዋላ ደግሞ በማይክራፎን እየዞሩ በላስቲክ ድንኳን የተጠጉትን ሰዎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ እያዘዙዋቸው ነው። ብዙዎቹ ልጆቻቸውን የት እንደሚያስጠጉዋቸው ጨንቋቸው ለኢሳት በመደውል የድረሱልን ጥሪ አቅርበዋል የሟቹን ግልሰብ ስም ለማግኘት ጥረት ብናደርግም እስካሁን አልተሰካላንም።ፖሊስ አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰጠን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናድርግም አልተሰካላንም።

ቤታቸው የፈረሰባቸው ሰዎች ለኢሳት በጻፉት የጋራ ደብዳቤ ደግሞ ፣ እንደ አዲስ ሰሞኑን የሚፈርሱ ቤቶች በዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ተስፋ በተደረገ ፈንድ ለሚገነባው የኦሎምፒክ መንደር ፕሮጀክት ቦታ ለማዘጋጀት ሲባል በመሆኑ ኦሎምፒክ ኮሚቴው የህዝቡን ስቃይ አይቶ፣ ድጋፉን እንዲያዘገይ ጠይቀዋል።

ነዋሪዎቹ በደብዳቤያቸው “የኢትዮጵያ መንግስትና የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ 2 ሚሊዩን የኢትዮጵያ ብር እንደሚሰጣቸው” ገልጸዋል።

“በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በሦስት ቀናት ውስጥ መኖሪያቸውን ነቅለው ከአካባቢው እንዲወጡ ጥብቅ ትዕዛዝ የተላለፈው ከዚህ ፕሮጅክት ጋር በተያያዘ መሆኑን ነዋሪዎች በደብዳቤያቸው ጠቁመዋል።

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ” የተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ ከዚህ በፊት ቤታቸውን ነቅለው አካባቢውን እንዲለቁ በተደጋጋሚ እንደ ተገለጸላቸው የሚጠቁም  ቢሆንም ፣  ከዚህ በፊት ቤት ግን አንድም ቀን ነዋሪዎቹ ነቅለው እንዲነሡ እንዳልተነገራቸውና ደብዳቤም ተጽፎላቸው እንደማያውቅ” ጠቅሰዋል፡፡

በሦስት ቀናት ውስጥ ቤቶች እንዲፈርሱ የታዘዘበት ምክንያት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተቋማት ሁሌም እንደ ሚያደርጉት የኗሪዎችን ቤት ነቅለው በመወሰድ እንጨቶችን፣ ቆርቆሮዎችን፣ በሮችንና መስኮቶችን በወረዳ አሰተዳደር ቅጥር ግቢ እያጫረቱ በመሸጥ ቤት አፍራሾቹና አመራሩ እንዲካፈሉት ለማድረግ መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

“የወረዳው ዋና ሥራ አስፈጻሚ  ከክፈለከተማው አስተዳደር የመጣ ትእዛዝ ነው ምንም ማድረግ አልችልም የሚል መልስ ለአቤቱታ አቅራቢዎች ሲሰጡ፣ የክፍለ ከተማው አስተዳዳሪ አቶ ደስታ ደግሞ አቤቱታ አቅራቢዎች ከቢሯቸው እንዲባረሩ ማስደረጋቸውን ነዋሪዎች በጽፋቸው አስፍረዋል።

ኗሪዎች በንብረታቸው ላይ ሊካሄድ የታቀደውን ዝርፍያ በመፍራት የቤቶቻቸውን ጣራና በር አንስተው ዘመድ ያለው ከዘመድ የሌላቸው ደግሞ ላስትክ ዘርግተው በተጠለሉበት ቅዳሜና እሁድ ባለማቋረጥ የዘነበውን ዝናብ በላያቸው ማሳለፋቸውን፣ አራስ እናቶች እና አዲስ የተወለዱ ሕጻናት፣  ነፍሰጡር ሴቶች  በበሽታ ላይ መውደቃቸውንም አመልከተዋል።

የኢህአደግ መንግስት በሕይወት እያለን ገድሎን በድኖቻችንን በሜዳ ላይ በትኗል የሚሉት ነዋሪዎቹ፣  በካሬ እስከ ሠላሳ ሺ ብር ድረስ የሚያጫርቱትን የአዲስ አበባ መሬት 18 ብር ብቻ ተቀብለው እንዲለቁ የታዘዙ በዙሪያችን ያሉ የኦሮሚያ አርሶ አደሮች እያለቀሱ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ በደብዳቤያቸው መጨረሻ ” የኦለምፒክ ፌዴሬሽን በዓላማውና ባለው እሴት ሰብዓዊ መብትን ከሚጋፋ ተግባር ጋር የማይተባበር ተቋም ቢሆንም በጭካኔ ከሚታወቀው የኢትዮጵያ መንግስት መተባባሩን ኮንነዋል።

” በኢትዮጵያውያን ላይ በኦሎምፒክ ኮሚቴ ስም እያረፈ ያለውን ሊረሳ የማይችል ጠባሳ በተመለከተ  በማስገንዘብ በእኛ ላይ ለሚፈጸመው ግፍ ከዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴ የሚያገኘውን ፈንድ እንዲቆምላቸው” ጠይቀዋል።

ከአለማቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴው ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎችም ጉዳዩን እንዲያደርሱላቸው ተማጽነዋል።
ደብዳቤውን የጻፉትን ሰዎች በስልክ አነጋግረን እንደተረዳነው፣ ደብዳቤያቸውን ከጻፉ 2 ሳምንታት ያለፈው ሲሆን፣ መንግስት የሚወሰድውን እርምጃ በመፍራት እስካሁን ይፋ ለማድረግ ሳይፈልጉ ቀርተዋል።

በኮልፌ ቤቱ የፈረሰበት አባወራ በጅብ ሲበላ አንዲት ወላድ በድንጋጤ ህይወቷ አለፈ

May23/2014
‹ቪዛ ይሰጠንና ወደ ሱማሌያ ቢሆንም እንሂድ›› ቤታቸው የፈረሰባቸው>>
ዳዊት ሰለሞን 
በኮልፌ ቀራኒዮ አለም ባንክ አካባቢ ህገ ወጥ የመሬት ወረራ በማድረግ ቤቶችን ሰርታችኋል የተባሉ ዜጎች ቤቶቻቸው በላያቸው ላይ በሀይል ፈርሶ ንብረታቸው መወረሱን አመለከቱ፡፡ ከ15.000 የሚልቁ ነዋሪዎች በሚገኙበት አለም ባንክ አካባቢ ሰዎቹ አነስተኛ መጠለያ ያረፉባቸውን ቤቶች ከገበሬዎች ላይ በመግዛት መኖር ከጀመሩ አመታት መቆጠሩን ያስረዳሉ፡፡ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ልከውና ወደ ስራ በተሰማሩበት ቅጽበት ከጸጥታ ሰራተኞች ጋር አካባቢውን የወረሩት አፍራሽ ግብረ ሃይሎች መኖሪያ ቤቶቹን ማፍረሳቸውን በሀዘን ተውጠው ገልጸዋል፡፡ ቤቶቹ በድንገት መፍረሳቸውን በመቃወም ድምጻቸውን ያሰሙ የአካባቢው ነዋሪዎች በፖሊሶች ክፉኛ መደብደባቸውንና መወሰዳቸውን የአይን እማኞች አስረድተዋል፡፡ቤቷ ሲፈርስ የደነገጠች እመጫት ወዲያኑ ህይወቷ ሲያልፍ ቤቱ በመፍረሱ መሄጃ ያጣ አባወራ ላስቲክ ዘርግቶ በተኛበት ጅብ ጎትቶት ወስዶት በልቶታል፡፡በጅብ የተበላው አባወራ ስርዓተ ቀብርም ዛሬ መፈጸሙ ታውቋል፡፡ ቤታቸው ፈርሶ ለጎዳና እንደተዳረጉ የሚናገሩ ሰዎች‹‹ኢትዮጵያዊነታችን ተሰርዟል፣ቪዛ ይሰጠንና ሌላው ቢቀር ወደ ሶማሊያ እንድንሄድ ይደረግ ›› ብለዋል፡፡

አረና አመራሮች በሐውዜን ከተማ አዳራሽ ውስጥ ታግተዋል

May23/2014

ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ በሰበር ዜናው እንደገለጸው አረና ትግራይ ለሉአላዊነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ በዛሬው ዕለት በሀውዜን ከተማ ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ሕዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እንዳለ ከመቀሌ የመጡ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ደርሰው እኛ ሰላማዊ ሰልፍ ስለምናደርግ ስብሰባ የሚባል ነገር የለም በማለት ወደ አዳራሹ የሚመጣውን ሰው ድንጋይ በመወርወር ስብሰባው እንዳይካሄድ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ስብሰባውን እንዲታደም ሲቀሰቅሱ የነበሩ አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና ሁለት አባላት ታርጋ በሌላቸው ሞተር ሳይክሎች በመግጨት አደጋ አድርሰውባቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት አዳራሹ ውስጥ ተዘግቶብን ዙሪያውን ተከበናል ፖሊስ መቆጣጠር ስላልቻለ ተጨማሪ ኃይል ጠይቋል ሲሉ የአረና አመራር ለፍኖተ ነፃነት ገልጸዋል፡፡

ከአሁን ቀደም በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የትውልድ ስፍራ ወላይታ ከተማ በተደራጁ ሰዎች ዝርፊያና ታርጋ በሌላቸው ሞተር ሳይክሎች አደጋ ለማድረስ መሞከራቸውን ፍኖተ ነፃነት መዘገቧ የሚታወስ ነው፡፡

ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ዙሪያ መረጃ እንዳያቀርብ ታገደ

May23/2014


በሳውዲ አረቢያ እና በመካከለኘው ምስራቅ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በደል እና ስቃይ በማለዳ ወጎቹ ዘገባው የሚታወቀው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በመረጃ ቅበላው ባልተደስቱ ወገኖች ለእስር መዳረጉ ይታወሳል። ነብዩ ሲራክ ላለፉት ሁለት አስርት አመታት ከኖረባት ሳውዲ አረቢያ «ጅዳ» ከተማ በስሙ በከፈተው ሶሻል ሚዲያ እና ከቅርብ ግዜ ወዲህ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ወኪል በመሆን በአረቡ አለም የሚገኙ ወገኖች የሚያሰሙትን እሮሮ በማስተጋባት በህዝብ ዘንድ ክብር እና አድናቆትን ያተረፈ ጋዜጠኛ ነው።

ይህ ጋዜጠኛ እንደማንኛውም ሰው የስደት አለም ህይወቱን ለመግፋት በግል ተቀጥሮ ከሚሰራበት መ/ቤት የስራ ሰዓት ውጭ የእረፍት ግዜውን መስዋት በማድረግ ሰለቸኝ፡ ደከመኝ ሳይል «ሳይማር ያስተማረውን ወገኑን» በሙያው ሲያገለግል የኖረ ጋዜጠኛ መሆኑ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ዘንድ ይነገራል። ነብዩ ሲራክ በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈፀሙ ቅጥ ያጡ ግፍ እና በደሎች መቋጫ ይበጅላቸው ዘንድ በሚያቀርባቸው ተከታታይ ዘገባዎቹ በስልክ እና በጽሑፍ ይሰነዘሩበት ለነበሩ ስድብ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ቅንጣት ያህል ሳይሸበር ወህኒ እስከገባበት ዕለት የወገኑን ህይወት ለመታደግ ከማለዳ ወግ የመረጃ ቅበላው ባሻገር በስው ሃገር በወረበሎች የታገቱ እህቶቻችንን ነጻ ለማውጣት ከህግ አስከባሪዎች ጎን ቆሞ የአጋች እና ታጋች ድራማ በሠላም እንዲጠናቀቅ ያደረገ ከህዝብ የወጣ ለህዝብ የኖረ ኢትዮጵያዊ ነው።
ከዚህ ባሻገር ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ለውጭ ሃገር ዜጎች ያወጣውን የ 6 ወር እና የ 3 ወር የግዜ ገደብ መጠናቀቅ ተከትሎ ሰነዶቻቸውን ለማስተካከል ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት አይን ያልገልጹ ህጻናት ልጆቻቸውን ታቀፈው በጠራራ ጸሃይ ሲነፍሩ ለነበሩ እናቶች እና በስደት አለም ግራ ተጋብተው በተስፋ ቆንስላ ጽ/ቤት በር ላይ ድንጋይ ተንተርሰው ጸሃይ እና ነፋስ ሲፈራረቅባቸው ለነበሩ ዜጎች ቀዝቃዛ ውሃ በማደል ከሰው ምስጋናንን ከፈጣሪ ጽድቅን ያገኘ ሩሩሁ እና ለወገን አዛኝ መሆኑ ይታወቃል።
በሰው ሃገር ተስፋ ሰንቀው ግፍ በደሉ የስደት አለም ኖሮቸውን መቅኔ ላሳጣው ወገኖች ድምጽ በመሆን የሚታወቀው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በቆንስላው ጽ/ቤት በአግባቡ መስተናገድ እና ፈጣን የሆኑ አገልግሎቶችን ማግኘት እንደሚገባው ባቀረበው የመፍትሄ ሃስብ በተበሳጩ አንዳንድ የጽ/ቤት ሹማምንቶች ቂም ተይዞበት ጉድጓድ ሲማስለት መሰንበቱ ይታወሳል። ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንደ ዜጋ በጅዳ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ስር የሚገኙ ንብረቶችን ለማስተዳደር በት/ቤት የወላጆች ኮሚቴ እና በተለያዩ የኮሚኒቲው መዋቅሮች የሃላፊነት ቦታዎች እንዲያገለግል በማህበረሰቡ ተመርጦ የመረጠውን ህዝብ በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል በነበረው ሂደት ውስጥ ህሊናው የማይቀበላቸውን አያሌ ሚስጥራዊ አሰራሮች በመቃወሙ ብቻ ከነበረበት የሃላፊነት ቦታ እንዲነሳ ከማድረጉም በላይ ላልተወሰነ ግዜ ቆንስላ ጽ/ቤት አካባቢ እንዳይደርስ ህገወጥ ውስኔ ተላልፎበት እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ከወህኒ ነጻ ከወጣም በኃላም ስለወገኑ ስቃይ እና በደል እንዳይጽፍ እና እንዳይናገር የተጣለበት የህሊና ነጻነት ገደብ ከዚህ በላይ በተገለጹ መስረታዊ ጉዳዩች ህዝብ መረጃ የማግኘት መብቱን ለመቀልበስ በእጅ አዙር የተውሰደ እርምጃ ሊሆን እንደሚችል ይነገራል።
ከሁለት ወራት ወህኒ ቆይታ በሃላ በቀርብ ቀን ነጻ የወጣው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በአሁኑ ሰአት በመልካም ጤንነት ላይ መሆኑን ቢታወቀም ጋዜጠኛው ከእንግዲህ በስደተኞች ዙሪያ ምንም አይነት መረጃዎችን በሶሻል ሚዲያ ሆነ በጀርመንድ ድምጽ እንዳይዘግብ ከባድ ማስጠንቀቂያ የተላለፈበት መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል ። የጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ የህሊና እስረኛ መሆንን ተከትሎ አንዳንድ ወገኖች በመካከለኛው ምስራቅ ግፍ እና በደል የሚፈጸምባቸውን በሚልዮን የሚቆጠሩ ድምጽ አልባ ኢትዮጵያውያን ህይወት የከፋ ሊያደርገው እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

የኢትዮጵያ መንግስት በጎረቤት ኤርትራ በኩል እየጠነከረ የመጣውን የነጻነት ሃይሎች እንቅስቃሴ ለመግታት ሲል ኤርትራውያን ስደተኞችን መስታጠቅ ሊጀምር ነው።

May 23/2014
(አባይ ሚዲያ)፡ የኢትዮጵያ መንግስት በጎረቤት ኤርትራ በኩል እየጠነከረ የመጣውን የነጻነት ሃይሎች እንቅስቃሴ ለመግታት ሲል ኤርትራውያን ስደተኞችን መስታጠቅ ሊጀምር ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት በጎረቤት ኤርትራ በኩል እየጠነከረ የመጣውን የነጻነት ሃይሎች እንቅስቃሴ ለመግታት ሲል ኤርትራውያን ስደተኞችን መስታጠቅ ሊጀምር ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት በጎረቤት ኤርትራ በኩል እየጠነከረ የመጣውን የኢትዮጵያውያን የነጻነት ሃይሎች እንቅስቃሴ ለመግታት ያስችለው ዘንድ በኢትዮጵያ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞችን በማሰባሰብ የአስመራን መንግስት በሃይል በመገልበጥ ዴሞክራሲ በኤርትራ መፈንጠቅ አለበት የሚል አዲስ ዘዴ መጀመሩን ከአካባቢው ለመረዳት ችለናል።
አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ወጣት ኤርትራዊ ሲገልጽ፡- አካባቢው የእርስ በርስ የጦርነት ቀጠና መሆኑ ለወያኔ የትኩረት አቅጣጫን በኤርትራኖች የእርስ በርስ ጦርነት በመለወጥ በአካባቢው እየጠነከረ የመጣበትን ሃይል ወደ ህዝቡ እንዳይዳረስ ለማድረግ ለራሱ ጥቅም የጀመረው ሴራ እንጂ ለእኛ የኤርትራውያን ተቃዋሚዎች አስቦ በኤርትራ ዴሞክራሲ ይፈጠር በሚል ትላንት በድንገት ወደ ትግሉ ግቡ ሊለን አይችልም ሲል መረጃውን ሰጥቶናል።
በትላንታናው እለት የኤርትራውያን ስደተኞች 23ኛ የነጻነት አመታቸውን በሚያከብሩበት የስደተኞች መጠለያ የወያኔ ባለስልጣኖች ተገኝተው ስደተኞችን ወደ ተቃዋሚው ጎራ ገብተው እንዲታገሉና የኢሳያስን መንግስት እንዲገለብጡ በጥብቅ ያሳሰቡ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ይህን ተከትሎም ለተለያዩ የመገናኛ ብዙሃኖች “ በኢትዮጵያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ትጥቅ አንስተው ለመታገል ተቃዋሚ ሃይሎችን ሊቀላቀሉ ነው” የሚል ዜና መላኩን ሱዳን ትሪቢውት የተባለው ድህረ ገጽ አስፍሮታል።
በአለፈው ሳምንት የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል 4ኛ ዙር በርካታ የነጻነት ታጋይ ወታደሮችን ማስመረቁን መዘገባችን ይታወሳል።
አባይ ሚዲያ

ወጣቱና ለነጻነት የሚያደርገው የትግል መስዕዋትነት (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ ሌና)

  May24/2014
By Gezahegn Abebe (Norway Lena )

የአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ህልውና የሚወሰነው ወጣቶች ባላቸው ሚና ላይ ሲሆን በብዙ ሀገራት እንዳየነው እና እንደተመለከትነው ወጣቶች ስለ ነፃነታቸው ፊት ለፊት መንግስታትን በመጋፈጥ ለመብታቸው ታግለዋል መስዋህትነትምበመክፈል የፈለጉትን አለማና ግብ አሳክተዋል::ለዚህም የሰሜን አፍሪካ አገሮችንና የመካከለኛው ምሥራቅን የለውጥ አብዮት ያቀጣጠሉትን ወጣቶች ዞር ብሎ መመልከት ያሻል:: የአንባ ገነኖች የስልጣን አገዛዝ አልዋጥላቸው ያላቸው እነዚህ የሰሜን አፍሪካ አገሮች እንደነ ግብጽ ፣ ቱኒዚያ እና ሊቢያ ያሉ ሀገሮች የሚኖሩ ወጣቶች በጊዜው ለናፈቁት እናለተመኙለት ነጻነት ብዙ መስዋትነትን በመክፈል ዓላማቸውን አሳክተዋል:: በወቅቱ የነበረው የዓረብ የፖለቲካ ትኩሳትመነቃቃት ለብዙ ሀገራት ወጣቶች ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ታሪክ ነው::

ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ ስንመለስ የኢትዮጵያን የፖለቲካ አካሄድ ወደ ኋላ ዞር ብለን በምናይበት ጊዜ በኢትዮጵያ ሲደረግ በነበረው የፓለቲካ እንቅስቃሴ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ትልቁን ሚና ይጫወት እንደነበር ከታሪክ መረዳት እንችላለን::እነሆ በኢትዮጵያ ረዥም ታሪክ ውስጥ እያንዳንዱ ትውልድ በተለያየ ጊዜና ወቅት የራሱን አሻራ ጥሎ አልፏል፡:

በተለይ በንጉሡ ጊዜ የመሬት ላራሹንና ሌሎችንም የፖለቲካዊ ጥያቄዎች አንግቦ ሲንቀሳቀስ የነበረው የተማሪ ንቅናቄ ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ የታሪክ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሲሆን በዚያን ጊዜው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩትና ግንባር ቀደሞቹ ዋለልኝ መኮንንና ጥላሁን ግዛው በድንገት በወታደራዊው ኃይል ቁጥጥር ሥር ለወደቀው የተማሪው አብዮት ተጠቃሾች ሲሆኑ፣ በዘመኑ ለነበረው ሃይለኛ እና ወኔን የታጠቀ ትውልድም መታወቂያ ሆነው ማለፋቸውን የታሪክና የፖለቲካ ተንታኞች ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የሚያወሱት የታሪክ ትውስታ ነው፡፡

ከቅርብ አመታት በፊትም ማለትም በ97 ምርጫ ሁሉም ሰው እንደሚያስታውሰው ይህ ወቅት ወያኔ ወጣቶችን ሙሉ በሙሉ የገፋበት ወቅት ጊዜ እንደነበር እና መንግስት ስራ አጥተው የሚንከራተቱ ወጣቶችን “አደገኛ ቦዘኔ” የሚል ታፔላ በመስጠት የተለያዩ እስሮችና የማንገላታት እርምጃዎችን የወሰደበት እና የፈፀመበት ወቅት እንደነበር በብዙዎች ዘንድ ይታመናል፡፡ ይህ አይነቱ የመንግስት ግብታዊ እርምጃ ወጣቱን ወደ ተቃውሞ ጐራ እንዲያዘነብል አድርጐታል፡፡ ለዚህም ይመስላል በወቅቱ በምርጫ 97 ዋዜማ ወያኔ ትግሬ ያቀረባቸውን የተለያዩ ማባበያዎች “አደገኛ ቦዘኔ ራሱ ወያኔ” የሚል ዜማ በማቀንቀን ለተቃዋሚዎች ድጋፍ የሰጠው፡፡ ወያኔ በምርጫ 97 የደረሰበትን አስደንጋጭ ሽንፈት ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ቀዳሚ ተጠቂ የሆነውም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል እንደነበር እናስታውሳለን፡:ለዚህም ነው ምርጫ 97 ተከትሎ በጊዜው የወያኔው መለስ መንግስት ከሃያ ሺ በላይ ወጣቶች በእስር ቤቶችና በወታደራዊ ካምፖች ታሰረው የተሰቃዩት እና ከ200 በላይ የሆኑ ባብዛኛው ወጣት የሆኑ ንፁሀን ዜጐች በግፍ በአደባባይ የተገደሉት::ይህንን ለነጻነት ትግል የተደረገን የወጣቶች የህይወት መስዋትነት ሁል ጊዜ ስናስታውሰው የምንኖረው ነው::

እንደሚታወቀው በአሁን ወቅት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚኖረው ህዝብ ከፍተኛውን ቁጥር ይዞ የሚገኘው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል መሆኑ ይታወቃል:: ይህንንም ተከትሎ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከወጣቶች ብዙ የምትጠብቀው ነገር መኖሩ የማያጠያይቅ እውነታ ነው;; ምክንያቱም የኢትዮጵያ ሀገራችን የወደፊት ሁለንተናዊ ህልውናዋ ያለው እና የሚወሰነውም በእነዚሁ በዛሬዎቹ የኢትዮጵያ ወጣቶች ስለሆነ :: ከላይ እንደገለጽኩት በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚኖረው ሕዝብ አብዛኛውን ቁጥር የያዘው ወጣቱ እንደመሆኑ ይሄ ወጣት የህብረተሰብ ክፍል በስልጣን ላይ ባለው ስርዓት ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ፍላጐቱ ሊሞላለት አልቻለም:: ከዚያም ባለፈ ወጣቶች የነጻነትም ሆነ የመብት ጥያቄያቸውን ወይም ፍላጐታቸውን መግለጥ እና መናገር የሚችሉበት አግባብ የተዳፈነ በመሆኑ፣ በአለም ላይ ኢትዮጵያን የተገፉ ወጣቶች የበረከቱባት ሀገር እና ሀገራቸውን እየጣሉ ከሚሰደዱ ወጣቶች መካከል ቅድሚያውን እንድትይዝ አድርጓታል፡፡

የወያኔ መንግስት በስልጣን በቆየባቸው ባለፉት 23 አመታቶች እየበደለ እና እያሰቃየ ያለው በመላ ሀገሪቱ ላይ የሚኖረውን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ቢሆንም ይበልጥኑ በወያኔ ራዳር ውስጥ በመግባት በአገዛዙ ጭቆናና ግፍእየደረሰበት ያለው በሀገራችን የሚኖረው ወጣቱ ዜጋ መሆኑ የታወቀ ነው:: ዛሬ የአማራው፣ የጋምቤላው፣ የኦሮሞው ፣የደቡቡ፣ የአፋሩ መላው የኢትዮጵያ ወጣት ዜጋ ለነጻነቱ በሚያደርገው ትግል በወያኔ ጨካኝ መንግስት እያተደበደበ፣እየታሰረና እየተገደለ ለነጻነቱ መስዕዋትነትን በመክፈል ላይ ይገኛል :: ለዚህ ማሳያ የሚሆነን በሀገራቸው ፖለቲካበመሳተፍ የተቃዋሚዎችን ጐራ የተቀላቀሉ እንደነ አንዱ አለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን እና ኦልባና ሌሊሳ የመሳሰሉወጣት ፖለቲከኞች እንዲሁም እንደነ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርዮት አለሙን የመሳሰሉ የወደፊቷ ኢትዮጵያተስፈኞች ብዙ የምትጠብቅባቸው ወጣት ጋዜጠኞች እንዲሁም በቅርቡ ህገ መንግስቱ ይከበር በማለት ሀሳባቸውን በብህራቸው የገለጡ የዞን9 ጦማሪዎች የወያኔ መንግስት እያራመደ ካለው የዘረኝነት ፖለቲካ የተለየ አቋም በመያዛቸው እና በተለያዩ ጋዜጦች ላይ ሀሳባቸውን በመግለፃቸው ብቻ በአሸባሪነት ተከሰው ወደ እስር ቤት በግፍ መወርወራቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች በገዥው  ስርዓት ምን ያህል መብታቸው እየተረገጠ እና ነጻነታቸው እየታፈነ በወያኔ የግፍ አለንጋ እየተገረፉ እንደሚኖሩ አመላካች ነው፡፡

የወያኔ መንግስት በወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል እየወሰዳቸው ያnለው እነዚህ በግፍ የተሞሉ እርምጃዎች ወጣቶች እጃቸውን አጣጥፈው እንዲቀመጡ አላደረገም፡፡ ይባሱኑ ወጣቱ ሀይሉን እያጠናከረ እና ወደ ተቃዋሚ ጎራ በመግባት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ለወያኔ መንግስት የእግር እሳት እየሆነበት ይገኛል::ከተለያዩ አካባቢዎች በአሁን ሰአት እንደማገኛው  መረጃዎ በኢትዮጵያ የሚገኙ ወጣቶች የወያኔን መንግስት ለመጣል በሚደረጉ ማንኛውም አይነት ትግል መስዋህት ለመሆን ከመቼውም ጊዜ ቆርጠው መነሳታቸውን በብዙ መንገድ እያስመሰከሩ ይገኛሉ ::በመሆኑም ይህ በወያኔዎች የግፍ አለንጋ እየተገረፈ ለነፃነቱ መስዕዋት እየከፈለ ያለ ወጣት የወያኔን ዘረኛ መንግስት ወደ መቃብር እንደሚያስገባው ምንም ጥርጥር የለኝም::

   ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, May 22, 2014

በባሌ ዩንቨርስቲ አንዲት የአማራ ብሄር ተወላጅ ተማሪ በአክራሪ ሙስሊም ኦሮሞዎች ከፎቅ ላይ ተገፍታ ኮንክሪት ላይ በመውድቅዋ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወትዋአልፍዋል::

MaY22/2014
ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መስፋፋት ጋር በተያያዘ በተስፋፋው አመጽ ምክንያትነቱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ይሁን እንጂ አላማው በክልሉ ለረጅም ጊዜ በኖሩት አማራዎች ላይ መሆኑ ከቀን ወደ ቀንእየታየ ያለ ሀቅ ነው:: የአማራ ቢዝነሶች ይቃጠላሉ የዓማራ ተወላጆች ከፍተኛ የሆነ የአካልና የስነ ልቦና ጥቃት እንዲሁም የግድያ እርምጃ እየተወሰደባቸው ነው:: በባሌ ዩንቨርስቲ የ 3 ኛ አመትተማሪ የነበረችና ከአማራ ክልል የሄደች ተማሪ ከ ፎቅ ላይ ተገፍታ ኮንክሪት ላይ በመ...ውደቛ ሰውነትዋ ና ጭንቅላትዋ ተፈጥፍቶ ህይወትዋ ወዲያው ሊያልፍ ችልዋል:: ኢሳትን ጨምሮ ሌሎችሚዲያዎች ይህንን በዘር ላይ ያተኮረ ጥቃት ከማጋለጥ ይልቅ ዝምታን መርጠዋል::

 በኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ , አብዲ ፈቲና ጃዋር የሚመራው በአክራሪ የኦሮሞ እስላማዊ ቡድን በየ ዩንቨርስቲውስር የሰደደ መረብ ያለው ሲሆን በአሁኑ ሰአት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን መሰረት አድርጎ የተነሳውን ተቃዎሞ ወደ ጸረ አማራ ና ክርስቲያን ለመለወጥ ተግቶ እየሰራ ነው :: በዚህም የተሳካ መረብአማካኝነት በክልሉ በሚኖሩና ለትምህርት ወደዚያው ባመሩት የአማራ ክልል ተወላጆችና ተማሪዎች ላይ ጥቃቱ ቀጥልዋል :: አዲስ አበባ ማስተር ፕላን ይሁን ሌላ ነገር ጋር ምንም ግንኙነትየሌላቸውን ደሀ ዜጎች ላይ ጥቃት እንዲዘር በጃዋር መሀመድ, አብዲ ፈቲ, መሀመድ አዴሞ ,ትግስት ገሜ ና ሌሎችም በከፍተኛ ሁኔታ ኦሮሞ ፈርስት በሚባለው እንቅስቃሴ ሲሰራበት የቆየ በመሆኑዛሬ ውጤት አምጥቶ ምስኪን ዜጎች ዋጋ እየከፈሉበት ይገኛሉ:: የኢትዮጵያ የሚባሉ ሚዲያዎች ለምን ዝምታን እንደመረጡ ለብዙዎች አነጋጋሪ ሆንዋል::

የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ በድንጋይ ተፈነከተ

May222/2014
ዳዊት ሰለሞን
የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ሰብሳቢ አቶ ስንታየሁ ቸኮል ትናንት ለምሳ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲያቀና ማንነታቸውን ባልለያቸው ሰዎች በድንጋይ መፈንከቱ ታውቋል፡፡ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ኳስ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 8፡00 እንደደረሰ ሁለት ሰዎች ወደ እርሱ በመቅረብ ምንም ሳያነጋግሩት በድንጋይ ፈንክተውት መሰወራቸውን አቶ ስንታየሁ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡በድንጋይ ከተፈነከተ በኋላ ለደቂቃዎች ራሱን ስቶ የወደቀው አቶ ስንታየሁ በሰዎች እገዛ ህክምና አግኝቶ በአሁኑ ሰዓት በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል፡፡ አንድነት ፓርቲ ‹‹የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት››የሚለውን ህዝባዊ ንቅናቄ መጀመሩን ተከትሎ አቶ ስንታየሁ ታላቅ አስተዋጽኦ ሲያበረክት ቆይቷል፡፡ፓርቲው በመስከረም 19 እና ሚያዚያ 26/2006 አዲስ አበባ ላይ ባደረጋቸው ሰላማዊ ሰልፎች ስንታየሁ እጆቹን በካቴና አስሮ በእስር ቤት የሚገኙትን የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ትኩረት እንዲያገኙ ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ በቅርቡ አንድነት ላደረገው ሰላማዊ ሰልፍ የቅስቀሳ ስራ ለመስራት ስንታየሁ ከሌሎች የፓርቲው አባላት ጋር ሲንቀሳቀስ በፖሊስ ተይዞ በህገ ወጥ መንገድ ታስሮ መለቀቁም አይዘነጋም፡፡
ፍኖተ ነፃነት

ፍትህ በምዕራብ ወለጋ እንጨት ለቀማ ወጥቶ በወታደሮች ጥይት ሕይወቱ ላለፈው ገመቺስ

May 22/2014
ከዳዊት ሰለሞን
ፍትህ ለገመቺስና ለመሰሎቹ
በምዕራብ ወለጋ የጊምቢ አጎራባች በሆነችው ዋሎ የሱስ መንደር ነዋሪ የነበረው ገመቺስ ደበላ ከእንጨት ከሰል እያመረተ
ቤተሰቦቹን በመደጎም ህይወትን ሲጋፈጥ ቆይቷል፡፡የ16ዓመቱ ገመቺስ በ02/09/2006 እንደተለመደው ማለዳ ተነስቶ
ለከሰል የሚሆነውን እንጨት ፍለጋ ወደ ጊምቢ እያቀና ነበር በወታደሮች በተተኮሰበት ጥይት እግሩ ላይ የተመታው፡፡የዘጠነኝክፍል ተማሪ የነበረውን ገመቺስን በጊምቢ የሚገኘው የአድቪንቲስት ሆስፒታል ህክምና ሲሰጠው ቢቆይም በ12/09/2006ይህችን አለም በግፍ ተሰናብቷል፡፡

Ethiopia crackdown on student protests taints higher education success

May22/2014
Western backers of the Ethiopian education system should not ignore reports of violent clashes on university campuses
MDG : Ethiopi : Student protest in Ambo
Oromia, Ethiopia, where at least three dozen people were reportedly shot dead by security forces during student protests
Over the past 15 years, Ethiopia has become home to one of the world’s fastest-growing higher education systems. Increasing the number of graduates in the country is a key component of the government’s industrialisation strategy and part of its ambitious plan to become a middle-income country by 2025. Since the 1990s, when there were just two public universities, almost 30 new institutions have sprung up.
On the face of it, this is good news for ordinary Ethiopians. But dig a little deeper and tales abound of students required to join one of the three government parties, with reports of restricted curricula, classroom spies and crackdowns on student protests commonplace at universities.
Nowhere has this been more evident than in Ambo in Oromia state. On 25 April, protests against government plans to bring parts the town under the administrative jurisdiction of the capital, Addis Ababa, began at Ambo University. By the following Tuesday, as protests spread to the town and other areas of Oromia, dozens of demonstrators had been killed in clashes with government forces, according to witnesses.
As Ethiopia experiences rapid economic expansion, its government plans to grow the capital out rather than up, and this involves annexing parts of the surrounding Oromia state. An official communique from the government absolved it of all responsibility for the clashes, claiming that just eight people had been killed and alleging that the violence had been coordinated by a few rogue anti-peace forces. The government maintains that it is attempting to extend Addis Ababa’s services to Oromia through its expansion of the city limits.
However, Oromia opposition figures tell a different story. On 2 May, the nationalist organisation the Oromo Liberation Front (OLF) issued a press release that condemned the “barbaric and egregious killing of innocent Oromo university students who have peacefully demanded the regime to halt the displacement of Oromo farmers from their ancestral land, and the inclusion of Oromo cities and surrounding localities under Finfinnee [Addis Ababa] administration under the pretext of development”. The Addis Ababa regime dismisses the OLA as a terrorist organisation.
While news of the killing of unarmed protesters has caused great concern among many Ethiopians, there has been little coverage overseas. The government maintains strict control over the domestic media; indeed, it frequently ranks as one of the world’s chief jailers of journalists, and it is not easy to come by independent reporting of events in the country.
Nevertheless, the government’s communique does run contrary to reports by the few international media that did cover the attacks in Ambo, which placed the blame firmly on government forces.
The BBC reported that a witness in Ambo saw more than 20 bodies on the street, while Voice of America (VOA) reported that at least 17 protesters were killed by “elite security forces” on three campuses in Oromia. Local residents maintain that the figure [of those killed] was much higher.
These reports, while difficult to corroborate, have been backed up by Human Rights Watch, which issued a statement saying that “security forces have responded [to the protests] by shooting at and beating peaceful protesters in Ambo, Nekemte, Jimma, and other towns with unconfirmed reports from witnesses of dozens of casualties”. One university lecturer said he had been “rescued from the live ammunition”, and that it was the “vampires – the so-called federal police” who fired on the crowds.
The Ethiopian government likes to trumpet its higher education system to its western aid backers as a crowning success of its development policy. As billions in foreign aid are spent annually on Ethiopia, the west must be more cognisant of the fact that this money helps reinforce a government which cuts down those who dare to speak out against it.
Inevitably, continued support for such an oppressive regime justifies its brutal silencing of dissent. Yes, the higher education system has grown exponentially over the past 15 years but the oppression and killing of innocent students cannot be considered an achievement. Any system which crushes its brightest should not be considered a success.
Paul O’Keeffe is a doctoral fellow at La Sapienza University of Rome, where he focuses on the higher education system in Ethiopia.

መድረክ የጠራው ሰልፍ ተከለከለ

May 22/2014

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ህዳር 29 ቀን 2006 ዓ.ም ለማድረግ ያሳወቀው ሰልፍ ተከለከለ፡፡ መድረክ
ሰልፉን ለመጥራት በሀገራችን መሰረታዊና ወቅታዊ የሆኑ ችግሮችን እንዲሁም በሳውዲና በአለም ዙሪያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰያለው ሰቆቃ መሰረቱ የስደት መንስኤው ላይ በመሆኑ፣ መንግስትን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንደነበር ለማወቅ ችለናል፡፡
ሰልፉን ለማድረግ የታቀደው ስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ አምስተኛ በር ፊት ለፊት ከሚገኘው የመድረክ ቢሮ በመነሳት በአምስት
ኪሎና ስድስት ኪሎ አድርጎ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ድረስ ለመጓዝ ነበር፡፡ ነገር ግን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከንቲባፅ/ቤት “ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እውቅና የጠየቃችሁበት ስፍራ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ አሰራር ስነ-ስርዓት አንቀፅ አምስት ሀ እና መ የሰላማዊ ሰልፍ የማይካሄድባቸው ቦታዎች ተብለው የተጠቀሱ በመሆናቸው የተጠየቀው የሰላማዊ ሰልፍእውቅና መስጠት የማንችል መሆናችንን እንገልፃለን” ሲል መልስ ሰጥቷል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያት እንዲሰጡ የጠየቅናቸው የመድረክ ስራ አስፈፃሚና የአንድነት ፓርቲ ዋና ፀሀፊ አቶ አስራት ጣሴ “መልሱ
የመድብለ ፓርቲ ቅልበሳ ከመሆን አይዘልም” ይላሉ፡፡ አስተዳደሩ እውቅና ለመንፈግ የተጠቀመበት ደንብ ማንም የማያውቀው መሆኑንየተናገሩት አቶ አስራት በማያውቁት ህግ እንደማይዳኙ ገልፀውልናል፡፡
በ1983 ዓ.ም የወጣው የሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 3/1983) የተከለከሉ ብሎ የሚጠቅሳቸው ቦታዎች
እንደሌሉና ከኤምባሲዎች፣ ት/ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የሀይማኖት አምልኮ ስፍራዎች፣ በገበያ ቀን (ከገበያ ስፍራ) መቶ ሜትር መራቅእንዳለበት ማዘዙን አቶ አስራት ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ከጦር ካምፕና የደህንነት ተቋማት 500 ሜትር መራቅ እንዳለበት አዋጁማስገደዱን ያስረዱት አቶ አስራት ከዚህ ቀደም አንድነት መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በጠራው ሰልፍ ይህንን አዋጅ በመሻር በጦርካምፕና በደህንነት መስሪያቤቶች በተከበበው ጀንሜዳ እንድንወጣ ነግረውናል ብለዋል፡፡
በተሰጠው መልስ ላይ አቋም ለመያዝ የመድረክ አመራር እንደሚሰበሰብ ከአቶ አስራት ጣሴ ለማወቅ ችለናል፡፡
መድረክ ህዳር 5 ቀን 2006 ዓ.ም መድረክ ለጠራው ሰልፍ አስተዳደሩ ከተደራራበ የስብሰባ ጫና የተነሳ የፖሊስ ሀይል ስለሌለኝ
ጥበቃ ላደደርግለት አልችልም በሚል እውቅና መንፈጉ ይታወቃል፡፡

Ethiopia: Bloggers of the World, Unite!

May 22, 2014
Zone 9 Bloggers in Ethiopia Jail
Today is the 25th day in jail for Zone 9 Bloggers in Ethiopia. They have not been charged; in fact, the government could not come up with reasonable cause for detaining the 6 bloggers and 3 journalists. It has now come to our attention that two have been tortured. All they did was blog about conditions in their own country. Corruption has gone out of control; in a decade beginning in 2001 $16.5 billions have been illicitly transferred to foreign banks [according to Washington, DC-based Global Financial Integrity]. There are chronic water, power and food shortages. The state security literally eavesdrops on telephone conversations and controls Internet connectivity making Ethiopia the least served in Africa. The ruling party took office through the barrel of the gun and divided the country arbitrarily along ethnic lines [and later orchestrated a sham elections that it won]. This is 22 years ago. It has made it clear that it will not hand over or share power through the ballot box. It refused to abide by results of the 2005 elections when it was dealt a humiliating defeat. A year later, it abolished all opposition on the pretext of terrorism which the US and UK governments wholly endorsed and financed. All grassroots organizations that the ruling party did not like were de-registered. Ethiopia now leads the world in the number of journalists jailed or exiled and in human rights abuses.
If you are a blogger you can be part of a global effort to give voice to those denied and to help free those in jail for demanding their constitutional and unalienable rights. Please send a note to Obama and Cameron Administrations, to European Parliament, etc or simply to friends. We can change conditions both locally and globally if we come together. We refuse to bend to those who seek to divide our humanity in order to remain in power! Freedom! Freedom! Freedom!

Wednesday, May 21, 2014

በቀጣይ ዓመት የሚጠናቀቀው የኢትዮጵያ መንግሥት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በአብዛኛዎቹ ዘርፎች እንደማይሳካ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ጠቆመ፡፡

May 21/2014
ግንቦት ፲፫ (አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ2003 እስከ 2007 ዓ.ም ሊከናወን የታቀደው የእድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከፋይናንስ አቅም ፣ከሰለጠነ የሰው ኃይል እና ከመሠረተ ልማት አለመሟላትና ከመሳሰሉ ጉዳዮች  ጋር በተያያዘ ፈተናዎች ገጥመውታል፡፡

በዕቅዱ ዓመታት  11 በመቶና ከዚያ በላይ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ የታሰበ ቢሆንም ባለፉት ሶስት የዕቅዱ ዓመታት የተመዘገበው እድገት 10 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ከኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ አንጻር በሚጠበቀው አቅጣጫ እና በጎላ መልኩ ለውጥ ማምጣት አለመቻሉን መረጃው ይጠቅሳል፡፡

በተለይ ባለፉት ሶስት ኣመታት ካጋጠሙ ፈተናዎች መካከል በመጀመሪያዎቹ ሁለት ዓመታት የተከሰተው የዋጋ ንረት፣ የግብርና ዘርፍ ምርታማነት ዕድገት አርኪ አለመሆን፣ ኤክስፖርት የገቢ ድርሻ ማሽቆልቆል ፣ የኢምፖርት ድርሻ በከፍተኛ ደረጃ ማደግ፣ የግብርና ዘርፍ የምርታማነት ዕድገት የተፈለገውን ያህል አለመሆን፣ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከመነሻው መሠረተ ጠባብ መሆን፣ የግል ባለሃብቱ ተሳትፎ ማሽቆልቆል ፣ ከምንም በላይ የማስፈጸም አቅም ማነስ እና በየደረጃው የሙስናና ብልሹ አሰራር ፣የመልካም አስተዳደር ችግሮች መንሰራፋት ይጠቀሳሉ፡፡

የመካከለኛና ትልልቅ ኢንዱስትሪዎች ልማት በውጪ ንግድ የሚመራ፣ የውጪ ምንዛሪ እጥረትን የመቅረፍና ለግብርና ልማት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከተቀመጡ ኣላማዎች አኳያ ባለፉት ሶስት የዕድገትና የትራንስፎርሜሸን ዕቅድ የትግበራ ዓመታት ክንውን ወደኃላ የቀረ መሆኑን የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር መረጃ ይጠቅሳል፡፡

በፕሮጀክቶችም ደረጃ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በአሁኑ ወቅት በመንግሥት መረጃ መጠናቀቅ የቻለው 30 በመቶ ያህል ብቻ ሲሆን በባቡር ፤ በስኳር፣ በማዳበሪያ ፋብሪካዎች ግንባታ የተያዙ ዕቅዶች ቀጣዩ የእቅዱ መጨረሻ ኣመት ድረስ የሚሳኩ አይደሉም፡፡

በዚህም ምክንያት ለመጪው ዓመት ምርጫ ድረስ የአዲስአበባ ቀላል ባቡርን ስራ ለማስጀመር ኢህአዴግ መራሹ መንግሥት የቻይና ኩባንያዎችን ጥብቅ መመሪያ የሰጠ ሲሆን ይህ ዓይነቱ የጥድፊያ አካሄድ በግንባታው ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው ባለሙያዎች ከወዲሁ አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው፡፡

የአዲስአበባ ቀላል ባቡር ግንባታ በዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅዱ ውስጥ የሌለና በእነአቶ መለስ ዜናዊ ደንገተኛ ውሳኔ የተጸነሰ ዕቅድ ሲሆን ግንባታው ከፍተኛ ወጪ የወጣባቸውን የመንገድ መሰረተ ልማቶች፣ ሕንጻዎች እያፈራረስ ከመምጣቱም ባሻገር የባቡሩ መስመር ዝርጋታ ለእግረኞችና ለተሸከርካሪዎች ማቋረጫ ግምት ውስጥ ባላስገባ መልኩ እየተከናወነ መሆኑ በባለሙያዎች ጭምር ጠንካራ ትችትን አስከትሎአል፡፡

የመንግሥት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ እጅግ የተለጠጠ እና በፋይናንስና በሰውኃይል አቅም ሊተገበር እንደማይችል በተለይ በአገር ውስጥ በሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቶዎችና በውጪ አገር በሚገኙ ኢትጽያዊያን ባለሙያዎች በሰፊው ሲተች የቆየ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግሥት ይህ የኒዮሊበራሊስቶች አፍራሽ አስተሳሰብ ነው በሚል ሲያጣጥለው ከመቆየቱም በላይ የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር በፓርላማ ተቃዋሚዎችን በኃላ ዕቅዱ ሲሳካ እንዳታፍሩ እስከማለት መድረሳቸው የሚዘነጋ አይደለም፡፡