Friday, March 28, 2014

በአዲስ አበባና አካባቢዋ የጅብ መንጋ ሰዎችን መብላቱ በምልኪነት እያነጋገረ ነው

March 27, 2014
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
ሙከራውን ማድረጉ ቢያንስ ኪሣራ የለውም፡፡ ውጤታማነቱን ግን እጠራጠራለሁ ብቻ ሣይሆን እንዲያውም መሣቂያ እንዳያደርጉን እሰጋለሁ፤ ክፉዎችና በሰው ስቃይ የሚደሰቱ ስለሆኑ በእሪታችን ቢሣለቁብን ማን ይከሳቸዋል? ከስም ባለፈ የሰላምን ምንነት ከማያውቅ ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ችግርንHyena's in Addis Ababa causing problems ማስረዳትና መፍትሔ ለማግኘት መመኘት ከምኞትና ከህልም አያልፍም፡፡ እናም ወያኔን በእሪታ ለማስበርገግ የሚቻል አይመስለኝም፤ ተስፋ ለማስቆረጥ አይደለም – ተስፋ ብሎ ነገር ቀድሞውንም ከሀገራችን ከጠፋች ሰንብታለችና ማንም ማንንም ተስፋ ሊያስቆርጥ አይቻለውም፡፡ መቼም የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ነውና ወደአእምሯችን የመጣልንን ዘዴ ሁሉ አሟጠን መጠቀሙን የመደገፍ የሞራል ግዴታ ስላለብን እንጂ በአራት ከተሞች አይደለም በአራት መቶ ከተሞች እሪታችንን ብናቀልጠው ወያኔ ንቅንቅ አይልም፤ በጩኸታችን ከማላገጥም በዘለለ አንጀቱ በሀዘኔታ አይላወስም፡፡ የጅቦች ስብስብ በጩኸት እሩምታ ሣይሆን በአልሞ ተኳሽ አናብስት ነው የማያዳግም እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ፡፡ ዓሣማው ወያኔ በሰላማዊ መንገድ ይወገዳል ወይም በምርጫ ሥልጣኑን ያስረክባል ብላችሁ ተጃጅላችሁ የምታጃጅሉ ወገኖች ካላችሁ – እንዳላችሁም ይታወቃል – ሕዝብን ከምታነሆልሉ ሌላ አማራጭ ብትፈልጉ ይሻላልና ጊዜና ምኞትን አታባክኑ፡፡ ሕዝቡ በዚህ ከዳሎል እሳተ ገሞራ ይበልጥ በሚያቃጥል የኑሮ ውድነት እየተቀቀለና እየተገነፈለ በግፍ አገዛዝ እየተሰቃዬ ባለበት ወቅት ወደ ተቃዋሚ ጽ/ቤቶች በብዛት የማይጎርፈው ለምን እንደሆነ መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ የደነዘዘ የመሰለው የሚተማመንበት አታጋይ ድርጅት ያገኘ መስሎ ስላልታየው ሆን ብሎ አድፍጦ እንጂ አንድ ሁነኛ ድርጅት ቢያገኝ በደቂቃዎች ውስጥ ምን ሊሠራ እንደሚችል በበኩሌ ይገባኛል – ሚያዚያ 30/97ን እዚህ ላይ ማስታወስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን ሕዝቡ እንደዚያች  “ሙሽራው እየመጣ ነው፤ በተሎ ተዘጋጂ!” እየተባለ በተደጋጋሚ እንደተነገራትና የሚባለው ውሸት መሆኑን ስትረዳ “ካልታዘልኩ አላምንም” እንዳለችው ዕድለቢስ ሙሽሪት ሆኗልና እንዳንዳንድ የዋህ ታዛቢዎች ለነፃነት የመታገል ፍላጎቱ እንደተቀዛቀዘ የሚነገርለት ሕዝብ የሚያዋጣ መስሎ የሚታየው ታግሎ የሚያታግል ድርጅት ቢያገኝ ምን ተዓምር ሊሠራ እንደሚችል በቅርብ የምናየው ይመስለኛል፡፡ መነሻየ ወዳልሆነ ነገር ለምን ገባሁ?
አሣዛኝ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አዲስ አበባና አካባቢዋ በጅብ መንጋ እየተወረረች ብዙ ዜጎች እየተበሉ ነው፡፡ በፉሪ ቆሼ ተራ በሚባለው አካባቢ፣ በአራት ኪሎ ግንፍሌ አካባቢ፣ ኮተቤ አዲሱ መንገድ አካባቢ ወዘተ. ሰዎች በጅብ መንጋ እየተጠቁ ሕይወታቸውን እያጡ ነው፡፡ ፍየልና በጎችማ በቀንም ሣይቀር እየተበሉ ነው፡፡ ጅብ ተፈጥሯዊ የሌሊት ይትበሃሉን ለውጦ ቀን ከሰው ጋር እየተጋፋ ያሻውን እያደረገ ነው፡፡ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ነን፡፡ “አንበሣን ፈርቼ ዛፍ ላይ ብወጣ ነብር ጠበቀኝ” እንደሚባለው የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማጥቃት ከወያኔ እስከ ዐረብ ጀማላ፣ ከ“ፌዴራል” ሠራዊት እስከ ጅብ አራዊት፣ ከተፈጥሮ ድርቅ እስከ ሰው ሠራሽ የቤተ ሙከራ ቫይረስ ሁሉም ይህን ዘመን ዳግም የማያገኘው ያህል በመቁጠር ይመስላል አናት በአናት ይረባረብበት ይዟል፡፡ የመጨረሻ ያድርግልን፡፡ ይሄ ሰሞነኛ የተፈጥሮ የጅብ መንጋ ደግሞ በሚገርም ሁኔታ ከወያኔ ጅቦች ላይ ተደምሮ ሕዝቡን መቆሚያ መቀመጫ እያሳጣ ይገኛል – ሕጻናትን ከጉያ እየነጠቀ መውሰድም ይዟል፡፡ ምን ዓይነት ፍርጃ ነው ጎበዝ!
እስኪ ይህችን ሴት እንዘንላት፡፡ በጀግንነቷና በአስተዋይነቷም እናክብራት፡፡ ነፍሷንም በነያዕቆብና በነአብርሃም ነፍሳት ጎን ለጎን እንዲያስቀምጥ ፈጣሪን እንለምንላት፡፡ የጀግንነት መገለጫ በግድ የመሣሪያ ተኩስና ግዳይ ማስቆጠር ብቻም አይደለም፡፡ እንዲህ ነው ታሪኩ፡፡
ድርጊቱ ከተፈጸመ አንድ ወር አልሞላውም፡፡ ሴትዮዋ ሥራ ለመግባት እንደወትሮዋ ማለዳ ላይ ትነሣና ትራንስፖርት ወደምታገኝበት ቦታ ጉዞዋን ትጀምራለች፡፡ ከቤቷ ወጥታ ጥቂት እንደተጓዘች ግን በጅቦች ትከበባለች፡፡ ይህች ቆራጥ ሴት የምታደርገውን ብታጣ ሞባይሏን ታወጣና ለባለቤቷ እንዲህ ትላለች፤ “ … አደራህን ከማንም ሰው ጋር እንዳትጣላ፡፡ ሰው ገደላት ብለህ ማንንም እንዳትጠረጥር፡፡ በጅቦች ተከብቤያለሁ፤ ሊበሉኝ ስለሆነ በጭራሽ አልተርፍምና እስከወዲያኛው ደህና ሁኑልኝ፤ ልጆቼንም ሣምልኝ፡፡…” ብላ ንግግሯን ከመጨረሷ የከበቧት ጅቦች ዘረጠጧት፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ቤተሰብና ጎረቤት ሲደርስ ከፀጉሯና ከጥፍሯ በስተቀር ሌላ የረባ የሰውነት ክፍል አላገኙም፡፡ በዚህ መልክ በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባና አካባቢዋ በጅብ መንጋ እየደረሰ ያለውን ያልተለመደ ወረራና ጥቃት ብናይ ምን መቅሰፍት ታዘዘብን የሚያስብል ትንግርት እንታዘባለን፡፡
ይህ ሁሉ ከወያኔ ጅቦች ያለፈ የእውነተኛ ጅቦች አስቀያሚ ድርጊት ምን ያመለክታል? ምልኪው ምንድን ነው?
ትናንት ማታ የሆነ ቦታ ከትላልቅ ሰዎች (elders)  ጋር እጫወት ነበር፡፡ ከልምድና ከአያት ከቅድመ አያት ከሰሙት ተነስተው የተገነዘቡትን ሲነግሩኝ ፈራሁ፡፡ የፈራሁት እኔም ከአንዱ ቦታ ስመጣ ወይም ወደ አንዱ ቦታ ስሄድ ጅብ እንዳያነክተኝ በመስጋት አይደለም፡፡ እንዲያ ብቻ ቢሆን ዕዳው ገብስ በሆነ – ያንድ ሰው ጉዳይ ነውና፡፡ ምልኪው ጥሩ ስላልሆነ ነው ክፉኛ የደነገጥሁት፡፡ ባህላችን በምልኪ ያምናል፤ እኔም፡፡
የጅቦች ባልተለመደ ሁኔታ እንደዚህ በጠራራ ፀሐይ ሣይቀር ሰዎችን መተናኮልና መቆርጠም ምልኪው በግምባር ክፉ ዘመን የሚመጣ መሆኑን በግልጽ የሚያመለክት ነው ይላሉ አብረውኝ ያመሹ “የምልኪ ኤክስፐርቶች”፡፡ ድርቅ ሊሆን ይችላል፤ ጦርነት ሊሆን ይችላል፤ የተፈጥሮ መቅሰፍት ሊሆን ይችላል፡፡ ብቻ አደጋ አለ አሉኝ፡፡ ለነገሩ የወያኔን የመጨረሻ ሰዓታት እየጠበቀ ላለ እንደኔ ያለ ሞኝ ዜጋ የወደፊቱ ጊዜ ከእስካሁኑ አሳሳቢ እንደሚሆን ቢገምት አይፈረድበትም፡፡ ባህላዊ ሥነ ቃሉም እኮ “እንዲህ ጨሶ ጨሶ የነደደ እንደሆን፤ ያመዱ ማፍሰሻ ሥፍራው ወዴት ይሆን” ይላል፡፡ ስለሆነም የምልኪውን መፃኢ ውጤት ማለትም አደጋውን ፈጣሪ ቀለል እንዲያደርግልን መጸለይ እንጂ ወደፊት – በጣም በቅርቡ – መሬትን ከሰማይ የሚደባልቅ ከፍተኛ ሀገራዊ ቀውስና ሚሌኒየማዊ የሪከርድ ደረጃ ሊሰጠው የሚችል አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ከግምት ባለፈ እርግጠኛነት መተንበይ ይቻላል፡፡ አሁን እኮ ፊሽካው በኦፊሴል ባለመነፋቱ እንጂ ወያኔንና ጥምብ ሥርዓቱን የሚያስወግደው ሕዝባዊ ጦርነት ተጀምሯል፡፡ “እኔም በአንድ ቀን አልተቆመጥኩም” ብላለች አንዷ አክስቴ – ለልጇ፡፡ ጓዶች! ደርግ የወደቀው ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ.ም ነው እንዴ? ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ መሆኑ ቀረ እንዴ? የነበረ አለ፤ ያልነበረ እንደ አዲስ አይመጣም፡፡ ወያኔዎች ሲወድቁ የተፈጠሩባትን ዕለት እንደ ኢዮብ አምርረው እንደሚራገሙና – ሊያውም ለመራገምም ዕድል ካገኙ ነው – ከዚያም ባለፈ እንደጪስ በንነው እንደሚጠፉ ቅንጣት ልንጠራጠር አይገባም፡፡ እናያለን!! ምን ቀረው?
ልብ አድርጉ፡፡ በቦቅቧቃነቱ የሚታወቀው ጅብ ልብ አግኝቶ እንኳንስ የቆመ ሰው ሊጥል ሞቶ አሳቻ ቦታ ላይ የወደቀን የሰው ሬሣ ለመብላት ራሱ ስንትና ስንት የመጠጋትና የመፈርጠጥ maneuvering ካደረገ በኋላ ነው እንደምንም ደፍሮ የሚጠጋና የሚበላ የነበረ፡፡ ጥላውን እየፈራ እንትኑን የትም እየዘራ አይግባኙን የሚሸመጥጥ ጅብ በርግጥም አንዳች ምልኪያዊ ነገር የልብ ልብ ካልሰጠው በስተቀር እንዲህ ያለ ድፍረት ሊያገኝ አይችልም፡፡ ለማንኛውም እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንንና ሕዝቧን ይባርክ፤ ከጠላቶቿ ወጥመድም ይጠብቃት፡፡ ግን ግን አሁንም ፈራሁ …

“ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

March 27, 2014
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሁለት ወር በፊት ወደ አሜሪካና የአውሮፓ አገራት ለስራ ጉብኝት ሄደው ነበር፡፡ አሁንም ወደ አሜሪካ ጉዞ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ የአሁኑ ጉዞ አላማ ምንድን ነው?
Eng. Yilkal Getnet Semayawi party chairman with Negere Ethiopia newspaper
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
ኢንጅነር ይልቃል፡- መጀመሪያ ያደረኩት ጉዞ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የፓርቲውን አላማና ፕሮግራም፣ የሰራናቸውን እንዲሁም ወደፊት ልንሰራቸው ያሰብናቸውን ስራዎች፤ ሰማያዊ እንደ አዲስ ኃይል ሲመጣ የቆመላቸው ሀሳቦችና እምነቶች ምን እንደሆኑ ለማስተዋወቅ ታስቦ የተደረገ ነበር፡፡ የአሁኑ ግን ከበፊቱ የተለየና ለሰማያዊ ሊቀመንበር በሚል በቀጥታ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የተደረገ ግብዣ ነው፡ ፡ የአሁኑ ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሊሆኑ የሚችሉ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ፣ በውድድር ከተመረጡ በኋላ በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በሚደረግ ምርጫ መመዘኛዎቹን ለሚያሟሉ ሰዎች የሚሰጥ እድል ነው፡፡ በመመዘኛዎቹ መሰረት በማሸነፌ የአሜሪካ መንግስት ሙሉውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና፣ የአሜሪካ መንግስት ባለስልጣናትም ባሉበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል ይኖረኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የፖለቲካ መሪዎች ጋር ተወዳድረው ነው ያሸነፉት ማለት ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አዎ! ግን ሌሎች ያሸነፉ ተጨማሪ ሰዎች ይኑሩ አይኑሩ አላውቅም፡፡ ይህ የፕሬዝዳንቱም ‹ኢኒሸቲቭ› ይመስለኛል፡፡ ለእኔ ግን የተሰጠኝ አዲስ ትውልድ አመራሮች፣ ወደፊትም በአገራቸው መሪ መሆን የሚችሉ፣ ስትራቴጅካሊ የሚያስቡ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይም ሆነው መልካም ስራ ለሰሩ ሰዎች የሚሰጥ ልዩ የጉብኝት እድል ነው፡፡ በአጠቃላይ ውድድርም ተደርጎ የሚወሰድ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ይህንን እድል ሲሰጥ እርስዎ እንደ መሪም ሆነ ሰማያዊ እንደ ፓርቲ ያሸነፋችሁበትን ዋና ዋና መመዘኛዎች ነግረዋችኋል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሲመርጡኝ ዝርዝር መረጃዎችን ወስደዋል፡ ፡ መሰረታዊ የሚባሉትን ለምሳሌ ያህል የፖለቲካ ቆይታዬ፣ የትምህርት ዝግጅቴን፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበረኝን ተሳትፎ የመሳሰሉትን መረጃዎች ለእጩነት በቀረብኩበት ወቅት ከእኔ ወስደዋል፡፡ ከዛ በኋላ ያስመረጠኝን ዝርዝር መስፈርት አላውቅም፡፡ ነገር ግን ወጣት (እስከ 45 አመት ባለው ውስጥ)፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ መልካም ስራ የሰራ፣ ወደፊትም የአገሩ መሪ ሊሆን የሚችል የሚሉት ዋና ዋና መመዘኛዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡ ፡ ይህም በተለይ ከሰማያዊ አንጻር ከሁለት ነገሮች አኳያ እንድናየው ያደርጋል፡፡ አንደኛው በምስራቅ አፍሪካ ያለውን ፖለቲካና እስካሁን ጠቅልሎ የያዘው ኢህአዴግ ነበር፡፡ ሌላ አማራጭ እንደሌለ አድርጎ ነበር የሚያየው፡፡ ሆኖም እንደዚህ አይነት እድል እንደ አሜሪካ ባለ ትልቅ መንግስት የተቃዋሚ መሪ የተለየ ስራ ሰርቷል ተብሎ ሲጋበዝ ሰማያዊ ፓርቲ አዲሱንና ወደ ፖለቲካ ያልመጣውን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ ማበረታቻ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ በሌሎች መስኮች ከምናደርጋቸው የዲፕሎማሲ ስራዎች በተጨማሪ ለሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች ፓርቲዎች በተለየ ይህኛው ግብዣ ሲደረግለት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
ከአሁን በፊት ለሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የ35 አገራት ኤምባሲዎች የ‹ኢትዮጵያ ፓርትነርስ ግሩፕ› የሚባለው ሲደረግ በአመታዊ ስብሰባቸው ላይ ዋና ተናጋሪ ሆኜ ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካና ስለ ሰማያዊ ፓርቲ ዋና የትግል እንቅስቃሴና የወደፊት አላማችን እንዳስረዳ የተለየ እድል ተሰጥቶኛል፡፡ ይህም ለፓርቲው ሌት ተቀን ለሚሰሩ ወጣቶች፣ እንዲሁም ሁል ጊዜም ቢሆን ወጣቱ ተከታይና ጀሌ እግረኛ ከመሆን አልፎ ራሱ ኃላፊነት የሚወስድ፣ መምራትና የራሱን መሪዎች ማውጣት የሚችል ትውልድ መምጣቱን የሚያሳይ መልካም ጅምር ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የአሜሪካ መንግስት ከ9/11 እንዲሁም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ሶማሊያ ውስጥ ባለው ጥቅም ኢህአዴግ ላይ እስከመጨረሻ ግፊት ማድረግ አልቻለም ነበር፡፡ አሁን ለእርስዎና ለፓርቲዎ ይህን እድል ሲሰጥ ለኢህአዴግ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድን ነው? የተቃውሞ ጎራውም ቢሆን እስካሁን የሚመራው በ1960ዎቹ ፖለቲከኞች ነው፡፡ አሁን የአሜሪካ መንግስት ይህን እድል ለእርስዎ እንደ መሪና ለሰማያዊ እንደ ወጣት ፓርቲ ሲሰጥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚኖረው አንድምታ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እንግዲህ ይህን ጉዳይ ህዝቡም ሆነ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ማህበረሰቡ እየተረዳው የመጣ ይመስለኛል፡፡ ባለፈው አርባ አመት በገዥውም ሆነ በተቃዋሚው ያለው በአንድ አይነት እድሜና የግራ ርዕዮት የሚሽከረከር ነበር፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ፖለቲካም ሆነ ኢትዮጵያን በሁሉም መመዘኛዎች ወደ ፊት ሊያራምድ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ጥላቻ፣ ቂምና ቆርሾ፣ የእስር በእርስ መጠላፍና የዜሮ ድምር ፖለቲካ ሆኖ ቆይቷል፡ ፡ ያ ትውልድ ያላመጣውን ውጤትም ወጣቱ ያመጣዋል የሚል ነው፡ ፡ ኢትዮጵያ የወጣት አገር ነች፡፡ 70 ከመቶ የሚሆነው ከ35 አመት በታች ነው፡፡ ይህ የህብረተሰብ ክፍል በውክልና ደረጃም ሆነ አዲስ አስተሳሰብና ከበድ ያለ ነገር ይፈልጋል፣ ከዓለም ከተለያየ አቅጣጫ መረጃ ያገኛል፣ በአስተዳደጉም አንጻራዊ ነጻነት አለው፣ በአመለካከትም ቢሆን ይህ የህብረተሰብ ክፍል ወደ ፊት እየመጣ ነው፡፡ ከዚህም አንጻር በታክቲክም ሆነ በአመለካከት ይህን የህብረተሰብ ክፍል መደገፍ የሚያዋጣና አይቀሬነቱን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡
ዋናው የኢህአዴግ የፖሊሲ መሰረት ማታለል ነው፡፡ ‹‹እኔ ከሌለሁ ኢትዮጵያ ትበታተናለች፡፡›› በሚል የምስራቅ አፍሪካንም ሆነ የሶማሊያን የሽብር ሁኔታ እንደ ማታለያ እየተጠቀመ፤ እነሱ የስጋት ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸውን ስለሚያውቅ እሳት የማጥፋት ስራ ነበር የሚሰራው፡ ፡ ይህ ግን መሰረታዊ መፍትሄ የሚያመጣ ሳይሆን ነገሮችን እያዳፈነ፣ ችግሩን እያባባሰ በመሆኑ እንዲሁም የጠቅላይነት ፖለቲካን ለቀጠናውም ሆነ ለኢትዮጵያ እየጠቀመ አለመሆኑ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ኃይሎች ተረድተውታል፡፡ አማራጭ የፖለቲካ ኃይልና መሰረታዊ የሆኑ የዴሞክራሲ መመዘኛዎችን ማምጣት፣ መሰረታዊ የሆኑ የዜጎች ልማትና ዴሞክራሲ ማፋጠን፣ በአቻነት የተመሰረተ ግንኙነትን ካልሆነ በስተቀር በጉልበትና በጠብመንጃ የሚደረገው አገዛዝ እንደማያዋጣ የተረዱበት ጊዜ ነው፡፡ አሜሪካኖች አባቶቻቸው የሞቱበት ነገር (the ideals of ower founding fa­thers) የሚሉት የሰውን ልጅ መብትና የሰብአዊ መብት ማክበር ለሁሉም አገራት መድሃኒት መሆኑን ራሳቸው አፍጋኒስታንና ኢራቅ ውስጥ በነበሩበት ወቅት አይተውታል፡፡ በየመን፣ በምስራቅ አፍሪካዋ ሶማሊያም ቢሆን ተመሳሳይ የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ለውጥ እንዳላመጣ ተገንዝበውታል፡፡ በየ ደረጃው በህዝብ ተሳትፎ የሚያድግ ዴሞክራሲና በዜጎችም ይሁን በአገራት መካከል በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት መምጣት ካልቻለ አፋኝነት እንዳልጠቀመ የተረዱበት ጊዜም ይመስለኛል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- እስካሁን ድረስ ዲያስፖራውም ሆነ አገር ውስጥ ያው የተቃውሞ ኃይል ድምጹን ለማሰማት ሲሞክርም የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ትኩረት አናሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡ እናንተ ይህንን አጋጣሚ ስታገኙ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በስርዓቱ ላይ ትኩረት እንዲሰጥ በአጽንኦት የምታስረዱት ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አንደኛ ከመንግስት ጋር መስራት በሚሉት መርህ ላይ ኢህአዴግ ስልጣን ስላለው ብቻ በአጭር ጊዜ የጮሌነት ግንኙነት፣ ከዛም በኋላ ለአሸነፈውና የኃይል ሚዛኑ ካደላው ጋር ግንኙነት የማድረግ ዋናው የዘመኑ መገለጫ፣ ስግብግብነትን መሰረት ያደረገ የካፒታሊዝም መርህ ስለሆነ በየትኛውም መንገድ ተሂዶ የአገርን ጥቅም ማስጠበቅ የሚባለው እንደማይጠቅም ማስረዳት እንፈልጋለን፡፡ መንግስት ቢያልፍም በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍን እያዩ እንዳላዩ ማለፍ ለዘላቂ የአገራቸው ጥቅም እንደማይበጅ፣ ሁል ጊዜም ቢሆን ግንኙነት መመስረት ካለበት ከአገሪቱና ከአገሪቱ ህዝብ ጋር እንደሆነ፣ ግንኙነቱ ታሪካዊና የህዝብን መሰረታዊ መብቶች ጠብቆ የሚደረግ እንጅ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ ግንኙነት ኢትዮጵያን ለመሰለ ታሪክና ክብሩን ለሚወድ ህዝብ ውሎ አድሮ የማይጠቅም መሆኑን፣ በአጠቃላይም የኢትዮጵያ የዴሞክራሲ፣ መሰረታዊ መብቶችና ሀሳቦች በሚከበርባቸው መልኩ የሚያራምድ አይነት አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ ግንኙነት እንዲያደርጉ ነው በዋነኛነት ማሳሰብ የምንፈልገው፡ ፡ ከአንድ ቡድን ጋር የሚደረግ የአጭር ጊዜ ግንኙነት ራሳቸውንም እንደሚጎዳቸው፣ በቀጠናው ይገኛል የሚባለውን መረጋጋትና ሰላምም ሊያመጣ እንደማይችል እንዲረዱት እንፈልጋለን፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከዲያስፖራው ጋር በመገናኘት የምትሰሩት ሌላ ድርጅታዊ ስራስ ይኖር ይሆን?
ኢንጅነር ይልቃል፡- አሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባደረገልኝ ግብዣ ላይ ለሶስት ሳምንት እቆያለሁ፡፡ የትኬትና ተመሳሳይ ጉዳዮችን ከሚሰሩት የአሜሪካ ሰዎች ጋር ስንነጋገር ከዚህ ውጭ አንድ ወር ያህል አሜሪካን አገር እንደምቆይ ገልጨላቸዋለሁ፡፡ በዚህም አጋጣሚ ባለፈው በአየር ንብረትና በድካም ምክንያት ያላዳረስኳቸው ቦታዎች ላይ ስብሰባ የማካሄድ ሀሳብ አለኝ፡፡ ምን አልባትም ወደ ለንደንና ካናዳ ልሄድ የምችልበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ ይህ እንግዲህ ከዚህ ካለው ስራ፣ ከጉዞ ሰነዶችና ከጊዜም ጋር ተደማምሮ በሂደት የምናየው ይሆናል፡፡ በድርጅታዊ ጉዳይ ላይ ለመስራት እቅዱም ሀሳቡም አለን፡፡ እዚያው ያሉት ደጋፊዎቻችንም በጉዳዩ ላይ እየሰሩበት ይገኛሉ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ወደ ሌላ ርዕሰ-ጉዳይ ልውሰድዎትና፣ ባለፈው እሁድ ሴቶች በተሳተፉበት የታላቁ የጎዳና ላይ ሩጫ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስታችኋል በሚል ከተያዙ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ‹‹መረጃን ለማሰባሰብ›› በሚል ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ይህን እንዴት ያዩታል?
ኢንጅነር ይልቃል፡- በዚህ ጉዳይ ከማዘንና ከማፈር ውጭ የምለው ነገር አይኖርም፡፡ ኢህአዴግ በዴሞክራሲ እየማለ፤ ለዜጎች እኩልነት፣ ለጎሳና ሀይማኖት እኩልነት፣ ለሴቶች እኩልነት ጠብመንጃ አንስተን በመዋጋት የልጅነት እድሜያችንን በበርሃ አጥፍተናል እያሉ፤ 23 አመት ቆይተው ግን ሴቶች ለነጻነት በተሰለፉበት ቀን ስለ አገራቸው አንድነትና ስለ መሰረታዊ መብቶች የጠየቁ ሰዎችን እስር ቤት ሲያጉሩ ምን ያህል የማይማርና ወደ ኋላ እየተንደረደረ የሚገኝ፣ የራሱን ሞት እየጠበቀ ያለ መንግስት እንደሆነ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ከዚህ ውጭ ምንም አዲስ ነገር ባላይበትም ትግሉ ውስጥ መግባታችን ምን ያህል ትክክል እንደሆነ ግን አረጋግጦልኛል፡፡ እሱ የማይፈልገው ሀሳብ ከሆነ ለምንም ነገር የማይመለስና ሴት፣ ህጻን፣ ህጋዊም ሆነ አልሆነ ለእሱ ምኑ እንዳልሆነ፣ በስልጣኑ ላይ ለመጣ ወደኋላ የማይመለስ መንግስት መሆኑን ተረድተንበታል፡፡ ይህም ዘላለም ለመጨቆን የተዘጋጀ መንግስት በመሆኑ ወደ ትግል መግባታችን ትክክል መሆኑ እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ ይህም ለትግሌ መሰረት ስንቅ ከመሆኑ በተጨማሪ በኢህአዴግ ላይ አዝኛለሁ፣ አፍሬያለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ባለፉት ሁለት አመታት አረቦቹ አብዮት አካሂደዋል፡፡ ዩክሬን ውስጥ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለውጥ ነበር፡፡ ለባለፈው አንድ አመት ተኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥም የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በአንጻራዊነት እየተጠናከረ ነው፡፡ አመጽ እየተለመደ ከመምጣቱ፣ የኑሮ ውድነትና ጭቆናው ከመባባሱ ጋር ተዳምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣይነት የሚመጣውን ለውጥ እንዴት ነው የሚያዩት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- መቼም እኔ የምናገረው ምኞቴንና የምሰራበትን ነገርም ነው፡፡ ከዛ ውጭ ያለውን ነገር ብንወደውም ባንወደውም ራሱ መምጣቱ ስለማይቀር፣ ስለ እሱ መናገር ለእኛ አወንታዊ አስተሳሰብ ስለማይበጅም ሆነ እርግማት ተናጋሪ ስለሚያሰኝ ማድረግ የሚቻለውን በጎ ነገር እያደረግን ብንሄድ የተሻለ ነው የሚሆነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ አይነት በዓለም የመጨረሻ ድሃ ለሆነ፣ ብዙ የጎሳና የእምነት መቃቃር በተፈጠረበት አገር፣ በሩቅም በቅርብም የኢትዮጵያን መረጋጋት የማይወዱ አካላት ባሉት ቀጠና ላይ ሆነን፣ እርስ በራሳችንም በተለያዩ የታሪክ ግጭቶች ውስጥ እያለን እንዲህ አይነቱ ለውጥ ባይኖር ደስ ይለናል፡ ፡ ነገር ግን አልፈለግነውም ማለት አይከሰትም ማለት አይደለም፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲህ አይነት ጉዳይ እንዳይከሰት የተጠና፣ አስቀድሞ በድርጅቱ የተመራ፣ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ የሚካሄድ የስልጣን ሽግግር እንዲኖር ሌት ተቀን ይሰራል፡ ፡ ሆኖም ገዥው ፓርቲ በጠቅላይነትና ባታላይነት እቀጥላለሁ ካለ ህዝቡ ውስጥ መሰላቸት በግልጽ ይስተዋላል፣ ችግሮች ከዕለት ዕለት እየተደራረቡ ነው፣ ህዝብ አገሩ ውስጥም ሆነ በአካባቢው የለውጥ ምሳሌዎችን እያየ ነው፣ ችግሩ መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኖበታል፡፡
በመሆኑም እነዚህ ለለውጥ መሰረት የሆኑ ነባራዊ ሁኔታዎች እየመጡ ስለመሆኑ የፖለቲካ ተንታኝ መሆን አያስፈልግም፡፡ በዚህ ሁኔታ አገዛዙ ውስጥ ያሉት ሰዎች የሚፈተኑት ከመግዛትና ከመጨቆን አስተሳሰባቸው ወጥተው ወደ እውነታው ቀርበው ለለውጥ ይዘጋጃሉ ወይንስ በተለመደው ግትርነት ይቀጥላሉ? በሚለው ነው፡፡ በሌላ በኩል እኛም ደግሞ አማራጭ ሆነን፣ እነሱን ሳናስደነብር፣ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲፈጠር መቻቻልና ይቅር ባይነቱ ኖሮን አገራችንን ማዳን የምንችልበት ሆደ ሰፊነትና አስተዋይነት ፖለቲካ በሁለታችንም በኩል ይጠበቃል፡፡ ግን ይህን ታሪካዊ ጉዳይ ከሁለታችን አንዳችን ከሳትነው ሂደት በተፈጥሮ የሚያመጣው ጉዳይ አለ፡፡ ሁሌም ታሪክም፣ ስልጣኔም፣ የሰው ልጅም ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይለወጣል፡፡ ልቡን የደፈነ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለውጥ አይቀሬ ስለመሆኑ የሚጠራጠር ያለ አይመስለኝም፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ምን ያህል ንብረት ይወድማል፣ ምን ያህል የሰው ነፍስ ይጠፋል፣ በሂደቱ ምን ያህል የተጠና እና ለአገራችን የሚጠቅም ለውጥስ ይመጣል የሚለው ነው እንጂ የሚያስጨንቀኝ ለውጡ እንደቀረበ ጥርጥር የለኝም፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ይህ ለውጥ ቢከሰት ለውጡን በሚገባው መልኩ ለማስተናገድና ለመምራት ትክሻ ያለው አካልስ አለ ብለው ያስባሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ ሰማያዊ ይህን ለውጥ መሸከም የሚችል ትክሻ አለው ብለን ነው የምናምነው፡፡ በእኛ አገር ይህንን አይነት ነገር ደፍረን ስንናገር በሁሉም ወገኖች ዘንድ አይወደድልንም፡ ፡ ለምን እንደማይወደድም ይገባናል፡፡ ባይወዱትም መናገር አለብን፡፡ ከማይወደድበት ምክንያት የመጀመሪያው በጭቆና መንፈሳችን መላሸቁ ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ይቻላል!›› ማለት እንደ ቅዠትና እብደት ይቆጠራል፡፡ ይህም ‹‹ይቻላል›› የሚለውን ከመጥላት፣ ከጭቆናው መብዛት፣ በተደጋጋሚ ከመክሸፍ የመጣ የአቅመ ቢስነት ችግር እንጅ የእኛ ችግር አይደለም፡፡ እነዚህ በጭቆና አስተሳሰብ ስር የወደቁት የእኛን አመለካከት እንዲይዙ ጥረት በማድረግ በተደጋጋሚ ስለ ጉዳዩ እንናገራለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ድርጅት ሆነን ስንቋቋም እኛ የተሻለ አማራጭ አለን፣ አገርና ህዝብን ወደተሻለ ደረጃ እናደርሳለን ብለን ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ራሳችን ስለ ድርጅታችን በሙሉ ልብ ‹‹እንችላለን!›› ስንል፣ ሌሎች ድርጅቶች ቅር ይላቸዋል፡፡ ይህ ከፖለቲካ እውቀት ማነስ የመጣ ነው፡፡ እኛ እንደ ድርጅት ተቋቁመን ‹‹እንችላለን!›› ካላልንና ህዝብና አገርን ወደ ተሻለ ደረጃ እንደምናደርስ መናገር ካልቻልን ህዝቡ እንዴት ሊከተለን ይችላል? ለምንስ ጊዜያችንን እናጠፋለን?
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው አንድ አመት ተኩል የፖለቲካ ነገር በቀላሉ የማይመዘን ሆኖ እንጅ መብት መጠየቅን፣ መነቃቃትን፣ ከአይቻልም ባይነት ይቻላል ባይነትን፣ አዲሱ ትውልድ የራሱን እጣ ፈንታ ለመወሰን በድርጅት የመታቀፍንና የመታገልን በአዲስ መልክ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ይህም ለረዥም ጊዜ በወደቀና በከሸፈ የፖለቲካ አመለካከት ውስጥ በጣም ረዥም ጊዜን የሚጠይቅ ስራ ነው፡ ፡ ይህም በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን በርካታ የሰማያዊ ወጣቶች የራሳቸውን የህይወት አማራጭ ትተው በዚህ ጉዳይ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰው፣ በግልጽ የፖለቲካ አመለካከት ሌት ተቀን ከአገዛዙ ጋር እየተጋፈጡ፣ እየታሰሩ፣ ዋጋ እየከፈሉ የመጣ ነገር ነው፡፡ በዚህ ሂደታችን ውስጥ ወጣቶች ወደ ፖለቲካው እንዲመጡ ማነቃቃት ችለናል፡ ፡ ከትልልቅ የአደባባይ ምሁራን፣ ከዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮች፣ ከውጭም ከአገር ውስጥም ክብርና ይሁንታን አግኝተናል፡፡
ከክርስትናም ሆነ እስልምና ሀይማኖት መሪዎችና አማኞች አካባቢም መከበር ችለናል፡፡ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም ቢሆን እንደሚታየው ወጣትና ወደፊት አገራቸውን መምራት የሚችሉ ተብለን መወደስና መሸለም ችለናል፡፡ የዓለም አቀፉም ሆነ የአገር ውስጥ ሚዲያው እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል አይቶናል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ለስልጣን መሰረት የሆኑት ነገሮች እነዚህ ናቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ወጣቶች፣ የአደባባይ ምሁራን፣ ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡና ሚዲያው ሰማያዊን እንደ አንድ የፖለቲካ ኃይል ማየት ችሏል፡፡ በእነዚህ ኃይሎች ተቀባይነት ካገኘ አገሪቱን ለመምራት የሚያቅተው ምንም ነገር አይኖርም ማለት ነው፡፡ የራሱ አላማ፣ የራሱ ፕሮግራም አለው፡፡ ይህን ለማስፈጸም የሚችል ቆራጥ አመራር አለው፡፡ በእርግጥ ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ብትሆንም ሰማያዊ ለውጥን በአግባቡ ለመረከብና ለመምራት የሚያስችል አቅም እንዳለው መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ዲያስፖራው የገንዘብም፣ የመረጃና የእውቀትም አቅም እንዳለው ቢታመንም ከ1997 በኋላ ግን ለአገሪቱ ፖለቲካ አሉታዊ ጎን እንደነበረው በስፋት እየተጠቀሰ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት እናንተ ከዲያስፖራው ተቀባይነት እያገኛችሁ ነውና መልካም ጎኑንና ፖለቲካውን ላይ አለው የሚባለውን አሉታዊ ተጽዕኖ እንዴት ነው የምታስታርቁት?
ኢንጅነር ይልቃል፡- ሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ አንድን አካል በቅራኔ መድቦ መታገል የተለመደ ባህል አይደለም፡፡ ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ ወጣቱ ላይ ያተኩራል ሲባል፤ በየትኛውም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ግን የሽማግሌዎችን፣ የአደባባይ ምሁራንንና የትልልቅ ሰዎችን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የሰማያዊ አመራር አገር ውስጥ ቢሆንም የራሳቸው የፖለቲካ ፋይዳ፣ ካፒታል፣ አንጻራዊ ነጻነት ያላቸው፣ የአገራቸውን ነጻነት በቀናነት የሚመኙ፣ በመረጃው በኩል ቅርብ በመሆናቸው በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ እገዛ ከሚያደርጉት በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ተቀባይነት አለው፡፡ ይህን ጉዳይ ሚዛናዊ በመሆነ መልኩ የመምራት ችግር ካልሆነ በስተቀር በውጭ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ከሚገኙት የተለዩ አይደሉም፡፡ አገር ውስጥ እንዳለው ሁሉ ውጭ ያለውም የአገሩ ሁኔታ ያሳስበዋል፡፡ የአገር ውስጡ የራሱ ሚና ይኖረዋል፡ ፡ በውጭ የሚኖረው ደግሞ የራሱ የሆነ ሚና ይኖረዋል፡፡
እነዚህን ሁለት ጉዳዮች አገር ውስጥ ያለው በተገቢው መንገድ ማስተባበር ይኖርበታል፡፡ አገር ውስጥም ውጭም ያለውን አጣጥሞ የማስኬድ ስራ ነው የምንሰራው፡፡ መሪነት ሲባል እኮ የሰዎችን አቅም ለግብ መጠቀም ነው፡፡ የትኛውም የማህበረሰብ ክፍል፤ አርሶ አደር፣ ነጋዴ፣ ውጭ ያለ፣ አገር ውስጥ የሚገኝ፣ የተማረም ይሁን ያልተማረ፣ ሁሉ ጥቅምና ፍላጎት አጣጥሞ ወደፊት መምራት ነው ዋናው ስራችን፡፡ ዲያስፖራውንም እንደ አፈንጋጭ፣ እንደ አጥፊና ለኢትዮጵያ ችግር ተጠያቂ አድርጎ ማየት በሰማያዊ ፓርቲ የተለመደ አይደለም፡፡
ባለፈው ጉብኝት ባደረኩበት ወቅት የዲያስፖራውን ድክመትና ስህተቶች ያልኳቸውን በአደባባይ ተናግሬያለሁ፡፡ እነሱም ከጊዜ ብዛትና ከመውደቅ መነሳት ብዙ የተማሩት ነገር አንዳለ ተረድቻለሁ፡፡ ይህን ጉዳይ አጣጥሞ የሚመራ አስተዋይ፣ ብልህና ሆደ ሰፊ መሪ ያስፈልጋል፡፡ ይህ እኛ እንደ ድርጅት አዲስ ብንሆንም በፖለቲካው መውደቅ መነሳት ከ1997 ዓ.ም ጀምረን የነበርን ሰዎች በመሆናችን የተፈጠሩትን ነገሮች በቅርበት እናውቃቸዋለን፡፡ ባገኘነው በቂ ልምድም ጉዳዩን በጥበብ መያዝ ችለናል፡፡ ወደፊትም በጥሩ ሁኔታ እንሄዳለን የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- የዲያስፖራውን ጉዳይ ካነሳን አይቀር፤ ከ1997 በኋላ በነበረው ፖለቲካ ተስፋ ከመቁረጡም ባሻገር በቅንጅት አባል ፓርቲዎች መካከል ተከፋፍሎ እንደነበር ይነገራል፡፡ ባለፈው ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ዲያስፖራውን እንዴት አገኙት? አሁንስ ምን አዲስ ነገር ይጠብቃሉ?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔ ስሄድ የምጠብቀው አነስ ያለ ነገር ነው፡፡ ትግል ውስጥ ስትገባ ያለውን አስቸጋሪ ነገር ቀይሬ ከዚህኛው ወደዚህኛው አሻሽለዋለሁ ነው እንጂ፣ ይህኛው አለኝ ብለህ አትኩራራም፡፡ የዓለም የመጨረሻ ድሃ አገር ነን፡፡ የፖለቲካ ባህላችን አስቸጋሪ ነው፡፡ የእምነት አገር ነው፡፡ የ1966 አብዮት የፈጠረው ችግር አለ፣ 1997 የፈጠረው ችግር አለ፡፡ እንደ ፖለቲከኛ ይህን ችግር እለውጣለሁ የሚል እምነት ይዤ ነው የተነሳሁት፡ ፡ ከላይ የተጠቃቀሱት ችግሮች በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት መኖራቸውን ብገነዘብም አንድ መልካም ነገር መኖሩ ሌሎቹን ችግሮች ያቃልላቸዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል የኢሳት መኖር በአገሩ ጉዳይ ተስፋ ቆርጦ የነበረውን የዲያስፖራ ማህበረሰብ መረጃ እንዲኖረውና ተነቃቅቶ እንዲጠብቅ በማድረግ መልካም ስራ አከናውኗል፡፡ በተለይ የሰማያዊ ወጣቶች ‹‹አይቻልም!›› በተባለበት አገር ትንሽም ነገር ሲሰሩ ሲታይና ይህም የማህበረሰባዊ ድህረ- ገጾችን ጨምሮ ለበርካታ ሰዎች መድረሱ አድናቆት አስገኝቶልናል፡፡
እንዲያውም እኛን ከልክ በላይ የማወደስና ነጻ አውጭ አድርጎ የማየት እንጂ በእኛ ላይ ቅሬታ ያለው ሰው የለም፡፡ ለዚህም እድሜያችን እንደመልካም አጋጣሚ ሊታይ የሚችል ነው፡ ፡ እድሜያችን፣ በኢህአፓ፣ በደርግ፣ በመኢሶን የተቋሰለው ትውልድ አለመሆናችን ለፍረጃ ክፍተት አልሰጠም፣ ሰውም እንዲጠላን ምክንያት አልሆነም፡፡ ይህ በእኛ ስራ ሳይሆን በትውልድ ያገኘነው መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ እንዲያውም በሰማያዊ በኩል እንደ ችግር ይቆጠራል ከተባለ ሁሉም ኃይል የራሱ ለማድረግ ስለሚሞክር ሚዛን የማስጠበቅና ማዕከል ላይ ሆኖ የማሰባሰብን ሚና ነው እየተወጣ የሚገኘው፡፡
ከዚህ ውጭ ከርቀት ሆነው ወጣትነታችን ሲያዩ የቆዩና ትውልዱ ጫታም፣ ስደተኛና ይህ ነው የሚባል ቁም ነገር የማይሰራ የሚመስላቸው የነበሩ ሰዎች ስንቀራረብ ትልቅ አድናቆት ችረውናል፡፡ መጀመሪያ ላይ በሆይ ሆይታና በጮኸት የተሰባሰብን ቢመስላቸውም ስለ እኛ ካወቁ በኋላ ‹‹እንዲህ አይነት ወጣትም አለ?›› በሚል ተገርመውብናል፡፡ በመልካም ሁኔታም ነው የተቀበሉን፡፡ እስካሁን ያለው ተስፋ ሰጭ ቢሆንም አሁንም ትልቅ ስራ ይጠይቃል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ያለፉት የፖለቲካ ውድቀቶች በመፍራት ወጣቱም ሆነ ዲያስፖራው ፓርቲዎችን ለመቅረብ ይፈራል፡፡ ‹‹ምንድን ነው ማረጋገጫችን?›› የሚል ጥያቄም በስፋት ሲነሳ ይስተዋላል፡፡ ለዚህ ጥያቄ እናንተስ መልሳችሁ ምንድን ነው?
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኛ የምንሰራው ለአገራችን ብለን እንጂ ማንም እንዲያወድሰንና እንዲያምነን ብለን አይደለም፡፡ የሰራነው ነገር ሲያሳምነው ይከተለናል፤ ያምነናልም፡፡ ባለፈው 10 አመት ውስጥ ፖለቲካው ውስጥ ስለነበርን በመውደቅ በመነሳቱ ላይም አልፈናል፡፡ የራሳችንን ታሪክ ያለን እንጂ ከምንም ዱብ ያልን ፖለቲከኞች አይደለንም፡፡ የሚያከብሩን ሰዎች አሉ፣ በቅርብ የተማርንባቸው ሰዎችም አሉ፣ በተግባር ውጣ ውረድ ውስጥም አልፈናል፡፡ ይህ ለመታመን በቂ ይመስለኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሰማያዊን የመሰረትን ሰዎች ስብሰባ ላይ በአጋጣሚ የተገናኘን ሳይሆን ከእነ ድክመትና ጥንካሬያችን ለረዥም ጊዜ የምንተዋወቅ ሰዎች ነን፡፡ በጎሳ፣ በወንዝ ልጅነት ሳይሆን ነጻ በሆነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተገናኝተን በደንብ የተዋወቅን ሰዎች በመሆናችን በቀላሉ እንዳንፈርስ መልካም እድል ይሰጠናል፡፡
በተጨማሪም ይህ አስተሳሰብ ከመውደቅ የመጣ እንጂ ከእኛ ጥፋት የመጣ አይደለም፡፡ ስጋቱ ቢኖርም እኛ በመታመን እንሰራለን እንጂ አያስጨንቀንም፡፡ ምክንያቱም ችግሩ ከእኔ አሊያም ከአንዱ ጓደኛዬ ድክመት የመነጨ ስላልሆነ ነው፡፡ አገራችን ውስጥ አለመተማመን በመኖሩ፣ ሰዎች ደጋግመው በመውደቃቸው፣ አጠቃላይ ክሽፈት በመብዛቱ የተፈጠረ የወል ስነ ልቦና ነው፡፡ ይህ እንደ አገር የጋራ ችግራችን በመሆኑ ይህን ባህል ለመቀየር እንሰራለን እንጂ አንድ ሰው ለምን አላመነኝም ብዬ አልጨነቅም፡፡ ይህን የወል ስነ ልቦና በድፍረት፣ ከራስ ወዳድነትና ከዝርክርክነት ወጥተን፣ አርዕያና ታማኝ በመሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥም ሆነ የገንዘብ አወጣጥን ተጠያቂነት በተሞላበት መንገድ በመፈጸም፣ ከአባላት ጋር የቅርብ ግንኙነት በመመስረት፣ የስልጣን ልዩነትን በማጥፋት ሰው ከአሉባልታ ይልቅ በሳይንስና በምክንያታዊ ነገር እንዲመዘን ማድረግ ይቻላል፡፡
እኛ ልናደርግ የምንችለው ሰውን ተስፋ ያስቆረጡትንና ለመለያየት ምክንያት የነበሩትን ነገሮች መቀነስ ነው፡፡ አለመተማመኑ ግን ደጋግሞ የመክሸፉ ችግር እንጂ የሰማያዊ ልጆች ችግር አይደለም፡፡ የሰማያዊ ልጆች ከአሁን በኋላ ምንም ይምጣ እስካሁን ባደረጉት ነገር ብቻ ሊደነቁ ይገባቸዋል፡፡ ባለፈው አስር አመት ውስጥ የግል ህይወታቸውን መኖር እየቻሉ ለአገርና ለወገን ሲሉ ብዙ ስቃይን የሚቀበሉ ልጆችን ማፍራት ችለናል፡፡ ለነጻነታቸው የሚዘምሩ ወጣት ሴቶችን ማፍራት ችለናል፡፡ የወደቀውንና አይቻልም የሚለውን መንፈስ ማነቃቃት ተችሏል፡፡ የወደፊቱ እንዳለ ሆኖ በእስካሁንም ቢሆን ሊመሰገኑ ይገባቸዋል፡ ፡ አለመተማመኑ በውድቀት የመጣ እንደመሆኑ እሱን መቀየር የሚቻለው በስራ ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ፡- ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሁ::
ኢንጅነር ይልቃል፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡

Thursday, March 27, 2014

“ኢህአዴግ ከምሆን ሞቴን እመርጣለሁ” – ኢ/ር ዘለቀ ረዲ (ቃለምልልስ ከሎሚ መጽሔት ጋር)

March 27/2014



ኢ/ር ዘለቀ ረዲ ከወራት በፊት በተዋቀረውና አዲስ አመራሮችን በመረጠው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ውስጥ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል፡፡ የሎሚ መፅሔት እውነትን ለህዝብ ለማድረስ ካለባት የሞያ ግዴታ አንፃር በኢ/ር ዘለቀ ዙሪያ በሚነሱ ሀሳቦች ላይ ተንተርሶ የሎሚ ም/አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገውን ቆይታ የመጀመሪያ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሎሚ፡- አዲሱ የአንድነት ካቢኔ ሥራዎች እንዴት እየተከናወኑ ነው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በጣም ጥሩ ነው፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ አዳዲስ ሰዎችን ነው ያመጣው፡፡ ከዛ አኳያ ጠንካራ ወይም ለቦታው ይመጥናሉ የተባሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ ከዚህ ቀደምም ጠንካራ ሠዎች ነበሩ፡፡ አሁን ደግሞ የበለጠ ጠንካራ ሆነው ሊሠሩ የሚችሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ እንደሚታወቀው አንድነት መሬት የረገጠ ፓርቲ ነው፡፡ ዝም ብሎ አየር ላይ የተንጠለጠለ ፓርቲ አይደለም፡፡ ከዛ አንፃር ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው፡፡ አሁን ያለው አሠራር በዚሁ ከቀጠለ ጥሩ ውጤት ይመጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ሎሚ፡- በርካቶች ግን አዲሱን የአንድነት ካቢኔ አወቃቀር አልወደዱትም ይባላል፤
ኢ/ር ዘለቀ፡- ከምን አንፃር?…ግልፅ አድርግልኝ?

ሎሚ፡- አንተን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ሶስት ሰዎችን ማካተቱ ትክክል አይደለም የሚሉ ሂሶች ተሰንዝረዋል፡፡ ለምሳሌ፡- አንተን ከፓርቲው ለረጅም ጊዜ ርቆ ነበር፤ ራሱንም ማግለሉንም ተናግሮ ነበር፡፡ ቀደም ሲል በአመራርነት በነበረበት ጊዜ ድክመት ታይቶበት ነበር፡፡ እንደዚህ ዓይነት ችግሮች ያሉበት ሠው እንዴት በአመራር ደረጃ ሊመረጥ ይችላል የሚሉ ወገኖች አሉ፤

ኢ/ር ዘለቀ፡- አንዳንድ ነገሮችን ግልፅ ላድርግልህ፡፡ በመጀመሪያ ከፓርቲው ርቆ ነበር የሚለው ስህተት ነው፡፡ የፓርቲው አባል ነኝ፤ ከፓርቲውም ራሴን አላገለልኩም፤ ከስራ አስፈፃሚነት ራሴን አግልዬ ነበር፤ ከፓርቲው ግን አላገለልኩም፡፡ በብሔራዊ ም/ቤት ውስጥ እሰራ ነበር፡፡ በአባልነትም ቢሆን እሰራ ነበር፡፡ ሁልጊዜ ከፓርቲው ጋር እሰራ እንደነበር ነው የማስበው፡፡ ከፓርቲው ርቆ ፓርቲውን ለቆ ተመልሶ ወደ አንድነት መመለስ ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አንድነት እንደ ሌሎች ፓርቲዎች አይደለም፡፡ አንድነት በጣም በነፃነት የሚሰራበት ፓርቲ ነው፡፡ እውነት ነው የምነግርህ፤ እኔ አንድነትን ለማስተዋወቅ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ኢ/ር ግዛቸው ዛሬ ተነስቶ እኔ መስራት አይችልም ቢል ለምን የሚል ጥያቄ እንኳን አይቀርብበትም፡፡ እሺ ነው የሚባለው፡፡ ከአንድነት ሥራ አስፈፃሚው እለቃለሁ ሲል ለምን ትለቃለህ ብሎ የሚጠይቅ አልነበረም፡፡ መብትህ ነው፡፡ ማንም ሰው ከአባልነት እለቃለሁ ካለ የመልቀቅ ሙሉ መብት አለው፡፡ እመለሳለሁ ካለም ደግሞ ትቀበለዋለህ፡፡ ከፓርቲው ርቆ የነበረ ሰው ድጋሚ ልመለስ ቢል ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አባላቱ ከባድ ናቸው፡፡ ብሔራዊ ም/ቤቱም እንደዚህ እንደምንገምተው አይደለም፡፡

ሎሚ፡- ከዚህ ቀደም ለሰንደቅ ጋዜጣ በሰጠኸው ቃለ ምልልስ ከስራ አስፈፃሚነት በራስህ ፍቃድ መልቀቅህን ተናግረህ ነበር፡፡ የፓርቲው ሊ/መንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ደግሞ አንተን ከቦታው ያነሱት እርሳቸው መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ይሄን ነገር እንዴት ተመለከትከው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በዚህ ጉዳይ ምንም ባልል ደስ ይለኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በእናንተ መፅሔት ላይ እርሳቸው ያሉትን አይቼዋለሁ፡፡ የመፅሔታችሁ ደንበኛ ነኝ፡፡ እርሳቸው እኔ ነኝ ያነሳሁት ብለዋል፡፡ ጥሩ፤ እርሳቸውም ያባሩኝ እኔም ልልቀቅ ችግር የለውም፡፡ አንድነት በነበሩበት ጊዜ ስለሰሩት በጎ ነገር አውርተዋል፡፡ ከበጎ ነገሮች አንዱ ደግሞ እኔን ማባረር ነው፡፡ ከዚህ ላይ ሊያገኙት የሚችሉት ትርፍ ምንድን ነው? እኔን የመሰለ ሠው፣ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ፣ የራሱ ሥራ ያለው፣ ፓርቲውን ሊደግፍ የሚችል ሰው ማባረራቸው ነው ውጤታማ ሥራቸው? በጣም በርካታ ሠዎችን አስገብተው እነገሌን አምጥቻቸዋለሁ ማለት ነው የሚሻለው ወይስ ኢ/ር ዘለቀን አባርሬዋለሁ?! እሺ እርሳቸው አባረሩኝ ብዬ ልውሰድ፤ ሰንደቅ ጋዜጣ በገዛ ፈቃዴ መልቀቄን ተከትሎ ጠይቋቸው ነበር፡፡ ያኔ “ኢ/ር ዘለቀ አለቀቀም፤ ሥራ እየሰራ እንደሆነ ነው የምናውቀው፡፡ አልሄደም አለቀቀም” ብለው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በርሳቸው ዕድሜ ያለ ሰው ያንን ምስክርነት መካድ ይችላል?…ያኔ የተናገሩት ነገር መረጃ ነው፡፡ ወደኋላ ተመልሰው እኔን አባረውኝስ ቢሆን? መናገራቸው ምንድነው ትርፉ? እኔና እርሳቸው በዕድሜ በእጥፍ እንለያያለን፡፡ በዕድሜያቸው ብዙ ችሎታ አላቸው፤ ብዙ ለፍተዋል፡፡ ውጤት ማምጣት አለማምጣት የራሱ ጉዳይ ሆኖ ማለት ነው፡፡ እኚህ ሠው እኔ እንኳን በጣም መጥፎ ሠው ሆኜ ባስቸግር እንኳን መልሰው በጣም መጥፎ ሰው ነበር፤ እኔ ነኝ ያስተካከልኩት ቅርጽ ያስያዝኩት ቢሉ ነበር የሚሻለው፡፡ ኢ/ር ዘለቀን ያባረርኩት እኔ ነኝ ማለት ጀብደኝነትም አይደለም፡፡

አንድ ሰው ሊቀ-መንበር የሚሆነው ሰዎችን ለማባረር አይደለም፡፡ ደካማውን ማጠንከር ይጠበቅበታል፡፡ ማንም ሠው ደካማ ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ በተፈጥሮዬ ደካማ አይደለሁም፡፡ ደካማ ብሆን ኖሮ አሁን ያለሁበት ቦታ ላይ አልገኝም ነበር፡፡ በትንሹ 150 ሠራተኞችን በስሬ አስተዳድራለሁ፡፡ ከ40 በላይ ቋሚ ሠራተኞች አሉኝ፡፡ ከ200 ሺህ ብር በላይ የወር ደመወዝ እከፍላለሁ፡፡ ይሔን ሁሉ የሚሰራ ሰው ደካማ ነው? ቤተሰቤንም ሆነ ሌሎች ሠዎችን ማስተዳደር የምችል ሠው ነኝ፡፡ ደካማ ብሆንም ከዶ/ር ነጋሶ የምጠብቀው “እንደዚህ ያለ ደካማ ነበር፤ እኔ ነኝ ጠንካራ ያደረግኩት” የሚል ምላሽ ነበር፡፡

ሎሚ፡- የአንድነት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀጣህ የነበረበትና እንዲቀጣህ መመሪያ የተላለፈበት ሁኔታ ነበር?…

ኢ/ር ዘለቀ፡- ዶ/ር ነጋሶ ያላወቁት ነገር ሰው ወንጀለኛ ነው ጥፋተኛ ነው ተብሎ ሊከሰስ እንደሚችል ነው፡፡ አንድ ሌባ ፍርድ ቤት እስከሚፈርድበት ድረስ ተጠረርጣሪ እንጂ ወንጀለኛ አይባልም፡፡ ፍ/ቤቱ ትክክለኛ ውሳኔ እስከሚሰጠው ማለት ነው፡፡ የኔ ጉዳይም በዲሲፕሊን ያስቀጣል አያስቀጣም የሚለውን ማየት የነበረበት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ነው አይደል? ያንን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ደግሞ ማጠናከር የነበረባቸው ዶ/ር ናጋሶ ናቸው፡፡ እርሳቸው ያዳከሙትንና እርሳቸው የሌላቸውን ዲሲፕሊን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊሰራው አይችልም፡፡ መጥተው ማቋቋም ይችላሉ፤ በሩ ክፍት ነው፡፡ እመጣለሁ ሲሉ አንድነት ይቀበላል፤ እሄዳለሁ ሲሉ ደህና ሁኑ ይላል፡፡ ጥፋት ኖሮብኝ ቢሆን ኖሮ እቀጣ ነበር፡፡ እርሳቸው ግን ውጭ ሆነው ይቆጫቸዋል፡፡ የኔ አለመቀጣት ትርፉን አላውቀውም፡፡ ፍ/ቤትም አለ እኮ፤ ከዛ ባለፈም እኔን መክሰስ ይቻላል፡፡ እኔ በእውነቱ የዲሲፕሊን ግድፈት አልነበረብኝም፡፡ ም/ቤቱ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ይየው ብሏል አይደል? ይሄ ማለት ደግሞ ዘለቀ የዲሲፕሊን ግድፈት አለበት ማለት አይደለም፡፡ ዲሲፕሊን ኮሚቴውን አጠናክሮ እኔን ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ የነበረባቸው እርሳቸው ነበሩ፡፡ እውነት ለመናገር በእናንተ መፅሔት ላይ እንዳየሁት እኔ በፓርቲ መቀጠሌ ደስተኛ አላደረጋቸውም፡፡ እኔ ለቅቄ እወጣላቸዋለሁ፤ ችግር የለውም፡፡ ውጭ ሆኜ ፓርቲዬን መርዳት እችላለሁ፡፡ ዋናው ግን የሚያገኙት ትርፍ ምንድነው የሚለው ነው፡፡

ከመንግስት በኩል ብዙ ጫና አለብኝ፡፡ የኮንስትራክሽን ድርጅቴ ስምንት ዓመት ሆኖታል፡፡ እስካሁን ድረስ ግን ከመንግስት ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የስራ ዕድል ያገኘሁት፡፡ ማንኛውም ኮንትራክተር የኮንደሚኒየም ሥራ የሚሰጠው ተጠርቶ ነው፡፡ የእኔ ድርጅት ግን ኮንዶሚኒየም ላይ አንድ ጠጠር አልጣለም፡፡ ለምን ቢባል ሊያዩኝ ስላልፈለጉ ነው፡፡ የኔ አንድነት ውስጥ መቀጠል ለምን ዶ/ር ነጋሶን ያበሳጫቸዋል? የሶስት ወር ጊዜ ነው የተሰጠን፡፡ አቅም ከሌለኝ የአንድነት ድርጅት አመንክም አላመንክም በሶተኛው ወር ዘለቀ አቅም የለውምና ይውጣ ይላል፡፡ ያንን ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ከኢህአዴግ ጎራ የወጡ ሰዎችን የዲሞክራሲው ትግል አጋር ማድረግ ነበረባቸው፡፡ እንጂ እኔም ላግዝ ብሎ የመጣውን የኔ ዓይነት ሰው አባረርኩት ማለት አይጠበቅባቸውም ነበር፡፡

ሎሚ፡- የአንድነት ፓርቲ የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ነህ፡፡ ቦታው ትልቅ ነው፤ ይህንን ትልቅ ቦታ ያገኘኸው ደግሞ ፓርቲያችሁ አንድነት የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት የሚለውን እንቅስቃሴ ባዘጋጀበት ወቅት የገንዘብ ልገሳ ስላደረገ ለውለታው የተሰጠው ነው እንጂ ለቦታው የሚመጥን ሆኖ አይደለም ሲባል ነበር፤

ኢ/ር ዘለቀ፡- በርግጠኝነት ይሄን የሚሉ አዕምሮ ያላቸው ሠዎች ይኖራሉ ብዬ አልገምትም፡፡ ይሄ አንድነትን መናቅ ነው፡፡ አንድነት የት ቦታም እንዳለም አለማወቅ ነው፡፡ እውነቴን ነው የምነግርህ አንድነት ለብር ብሎ በህልውናው ላይ የሚደራደር ፓርቲ አይደለም፡፡ ይሄ የአዕምሮ ማነስም ጭምር ነው፡፡ ይሄ ማለት ዘለቀ አንድነትን በብር ይገዛዋል ብሎ ማሰብ ነው፡፡ አንድነትንም ማናናቅና መወንጀልም ጭምር ነው፡፡ የአንድነት ም/ቤት በሃገር፣ በህዝብ፣ በህልውና ላይ የማይደራደር ም/ቤት ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ሊቀ-መንበር በነበሩበት ጊዜ በአብላጫ ድምፅ የሚወሰነውን ነገር የመስራት ግዴታ አለባቸው አይደል? የራሳቸውን ልዩነት ግን በጋዜጣ ሁሉ ያራግቡ ነበር፡፡ ስለመድረክ ጉዳይ ልዩነት አለኝ ብለው ይፅፋሉ፡፡ ልዩነታቸውን እየፃፉ በአብላጫ ድምፅ ለመገዛት ደግሞ ህጉ ያስገድዳቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ዘለቀ ለሚሊዮኖች ድምፅ ገንዘብ ስላወጣ ነው የተመረጠው ብሎ አንድነትን መናገር አሳፋሪ ነው፡፡

ሎሚ፡- ኢ/ር ዘለቀ የኢህአዴግ መልዕክተኛ ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፤ ለዚህ አባባላቸው ደግሞ ካሉት ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር የቅርብ ወዳጅና ከወዳጅነትም በላይ በአንድነት ውስጥ የማዳከምና የአንድነትን እቅስቃሴ ለመቅጨት ሰርጎ እንዲገባ የተደረገ መልዕክተኛ ነው ይባላል፡፡ አንተስ ሰምተሃል? ምንስ ትላለህ?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በመሠረቱ እነዚህን ነገሮች በሁለት ከፍዬ ማየት ነው የምፈልገው፡፡ እኔ የሙክታር ከድር ወዳጅ ብሆን እፈልገው ነበር፡፡ ለምን መሰለህ ሙክታርን እያነጋገርኩኝ መንግስት ያለውን አቋም ማወቅ እችል ነበር፡፡ እውነት ለመናገር እንደዚህ ያሉ ሠዎችን አጥተን ነው እንጂ ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጓደኛ ብንሆን እኮ ብዙ ነገር ታወራለህ፡፡ ድክመቱንም የምታገኘውም በዛ ነው፡፡ ኢህአዴግ እኮ ደርግን ያሸነፈው በደህንነቱ በእነ ተስፋዬ ወ/ስላሴ አማካይነት ነው፡፡ ቁልፍ ሰዎችን መያዝ ያስፈልጋል፡፡ ብንይዛቸው ደግሞ ይህ የድክመት ምልክት አይደለም፡፡ ምናልባት እንግዲህ ሙክታርም የጅማ ልጅ ነው፤ እኔም የጅማ ልጅ ነኝ፤ ያው መላ ምት ነው፡፡

እንደ ዶ/ር ነጋሶ ያሉ በርካታ ሠዎች የሚጎነትሉህ ቦታ ቁጭ ብለህ የኢህአዴግ መልዕክተኛ ከምትሆን የኢህአዴግ ካድሬ አትሆንም? የአንድ ዞን አስተዳዳሪነት ቦታ ይሰጥሃል እኮ፡፡ አሁን ካሉት ሠዎች በአቅም ላልተናነስ እችላለሁ፡፡ ኦህዴድ ብሆን ደረጃዬን ጠብቄ መጥቼ ሙክታር ያለበት ደረጃ መድረስ እችል ነበር፡፡ በርግጠኝነት ዛሬ ሄጄ ብጠይቀው ኢህአዴግ ይሄን የሚነፍግ ንፉግ አይመስለኝም፡፡ እንደውም ጠላት መቀነስ ነው፡፡

ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ያደሩ ጋዚጠኞችም አሉ፡፡ አንድ ሁለት ሶስት ጋዜጠኞች ደውለውልኝ አንድ ጥያቄ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ በጣም የወረደ ጥያቄ ማለት ነው፡፡ እኔ ብዙ አልፈራም፤ ሠዎች ይመጡና አንድ ነገር እንስራ ይሉሃል፡፡ በሁለተኛው ቀን ሌላ ነገር ይጠይቁሃል፡፡ ይሄማ ትክክል አይደለም ስትላቸው እንደዚህ ነህ እንልሃለን ይሉሃል፡፡ ምንም ይበሉህ ምን ጊዜውን ጠብቆ እውነት ያወጣዋል፡፡ እኔ ከአንድነት ስራ አስፈፃሚ እንደወጣሁ ኢህአዴግ ሊሆን ነው ምናምን ይሉ ነበር፡፡ ኢህአዴግ እኔ የማስበውን የሚያስብ ከሆነ እንደኔ አንድነት የሚያጠናክር ከሆነ ልናግዘውና ልናጠናክረው ነው የሚገባው፡፡ እንደኔ ዓይነት ኢህአዴጎች ካሉ ለምንድነው የማንሠበስባቸውና የማናመጣቸው? ዘለቀ የኢህአዴግ አባል ሲሆን መታወቂያ ይኖረዋል አይደል፡፡ ኢህአዴግ አንድነትን ለመሠለል ከበቃ አድገናል ማለት ነው፡፡ ይቺ አሉ የሚባሉትን ሠዎች ከስር ሆኖ መቀንጠሻ ናት ዘዴ ናት፡፡

ስለ አንድ ሰው ልንገርህ፤ የባንክ ሠራተኛ ነው፤ ስሙን አልገልፅልህም፤ መሃንዲስ ነው፡፡ አንድ ቀን በራሴ ፅሁፍ በይፋ እገልጸዋለሁ፡፡ አንዱን ጋዜጠኛ ምን ብሎ ያሳስተዋል መሠለህ? አርሲ ነገሌ “መንገድ ስራ” ወስደነው ነበር፡፡ መንገዱ ፈርሶ ተበላሻሽቶ ከፍተኛ ብጥብጥ ተነስቷል ብሎ ይነግረዋል፡፡ ይሄን የሰማው ልጅ ይደውልልኝና “ኢ/ር ዘለቀ ነህ አዎ…አርሲ ነገሌ የምትሠሩት መንገድ ተበላሽቷል ወይ? ምናምን ብሎ ይጠይቀኛል፡፡ ማን ነገረህ? አልኩት፡፡ ጥቆማ ደርሶን ነው አለ፡፡ ዓይተህ ማውጣት ትችላለህ፤ ይህን ካላደረግክ እኛ ህጉን ጠብቀን እንከስሃለን ብዬ መለስኩለት፡፡ ከ15 ቀን በኋላ መንገዱ ይመረቅ ነበር፡፡ ከመመረቁ በፊት ተዟዙሮ የተመለከተው የከተማው አስተዳደር “የመጀመሪያ ኮንትራክተር ነው” ብሎናል፡፡ ሞያውን ተጠቅሞ ስራውን በአግባቡ ሰርቶልናል ተብሎ የከተማ አስተዳደሩ “ቡልኮ” ሸልሞኛል፡፡ በኦሮሞ ባህል ቡልኮ የተሸለሙት እነ አባዱላ ናቸው፡፡ ጋዜጠኛው እዛ ነበርና በጣም ነው የደነገጠው፡፡ ስለዚህ እዚህ መጥተው የተለየ ጥቅም የሚያገኙ ሠዎች ሄደው ስም ያጠፋሉ፡፡ ኢ/ር ግዛቸውን ብዙ ነገር ይሉታል፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በተፈጥሮው ጠንካራና እያጣራ ማለፍ የሚወድ ሠው ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ቢሆኑ በዚህ ፈተና ይወድቁ ነበር፡፡

ዶ/ር ነጋሶ ጋር ቀድሞ ሄዶ የነገራቸው ሰው አሸናፊ ነው፡፡ እኔ አንተን ቀጥቅጬህ ቀድሜ ሄጄ ከነገርኳቸው ቁስልህን ብታሳይ አይሰሙህም፡፡ ኢ/ር ግዛቸው ግን ይህንን ሁሉ ነው የተቋቋመው፡፡ እነዚህ ሠዎች ካንተ ጥቅም ሲያጡ ፓርቲ ውስጥ ስትገባ የምትጠቀም ይመስላቸዋል፡፡ ለሃገርህ የሆነ አስተዋፅዖ ለማበርከት የሄድክ አይመስላቸውም፡፡ ከዚህ አንፃር ብዙ ነገር ሊወራብህ ይችላል፡፡ በመረጃ “ኢህአዴግ ነው ብሎ” የሚሞግተኝ ካለ ምንም ችግር የለብኝም፡፡ አሉባልታ ግን አሉባልታ ነው፡፡ የኔ ማረጋጋጫ ስራዬ፡፡ ኢህአዴግ ብሆን ኖሮ አንዲት ሴትዮ 400 ሺህ ብር በልታኝ አትቀርም ነበር፡፡ ኢህአዴግ ሆኜ ይሄ ነው የኮንዶሚኒየም ግንባታ ላይ እንዳልሳተፍ (እንዳልሰራ) አልደረግም ነበር፡፡ ኢህአዴግ የሆኑ ሰዎችን እናውቃቸዋለን፡፡ ቢጠሯቸው አይሰሙም፡፡ ገንዘባቸው የት ነው ያለው? እኛ እኮ NGO እየለመንን ነው የምንሰራው፡፡ ያውም ደግሞ ጠንካራ ጠንካራ NGOዎች ናቸው እንጂ አነስ አነስ ያሉት ዝም በሉ ሲባሉ ዝም ይላሉ፡፡ በርካታ NGOዎች ናቸው ጨረታ ካለፍን በኋላ የሰረዙብን፤ ደህንነቶች እያስፈራሯቸው ማለት ነው፡፡ ዘለቀ ኢህአዴግ ነው የሚባለው ከአንድነት ከፓርቲ አገልግሎት ለማስወጣት ሲባል ነው፡፡ ኢህአዴግ መሆን ብፈልግ በአንድነት በኩል መዞር የሚጠበቅብኝ አይመስለኝም፡፡ ለሰራተኞቼ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ኢንሹራንስ የምገዛ ሰው ነኝ፡፡ አንድ ሚኒስትር የሚከፈለው ደመወዝ ስንት ነው? እኔ እኮ 38 ሺህ ብር ነው ለአንድ መሃንዲስ የምከፍለው፡፡ ምን አጥቼ ነው ኢህአዴግ ስር የምሸጎጠው? በህልሜም የኢህአዴግ አባል ሆኜ ማየት አልፈልግም፡፡ እስካሁን ባለኝ አቋም የኢህአዴግ አባል አይደለሁም፡፡ የአይዲዎሎጂ አስተሳሰብ ጊዜውን ጠብቆ የሚቀየር ነገር ነውና ወደፊት ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፡፡ ምኒልክም “ሃገሬ ስትወረር ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ” እንዳሉት እኔም ኢህአዴግ ከምሆን ሞቴን ነው የምመርጠው፡፡ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነጻነት የሚለውን የአንድነት ዘመቻ ረዳህ ተባልኩ፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያ ጥቅም ሲሰራ እደግፋለሁ፡፡ ኢህአዴግ የፖለቲካ ቅስቀሳ ስለሚያደርግበት አንድም እርዳታ አድርጌበት አላውቅም፡፡ የአባይ ግድብ የኔ ገንዘብ የለበትም፡፡ ለምን? ለፖለቲካ ቅስቀሳ እያዋለው ስለሆነ፡፡ ለህዝብ አሳልፎ ስላልሠጠ፤ ለህዝብ ስጥ እያልኩ እየፃፍኩበት ነው፡፡ ለህዝብ ሲሰጥ ግን አንደኛ የምረዳው እኔ ነኝ፡፡ አሁን ግን ለአባይ ግድብ የአንድ ብር ቦንድ አልገዛሁም፡፡

ሎሚ፡- ከዚህ ቀደም የፓርቲያችሁ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነፃነትን “አዲስ ዘመን” ብለህ ዘልፈኸዋል፤ አዲሱ ካቢኔ ሲዋቀርም በአንተ መመረጥ ዙሪያ ከተነሱ ቅሬታዎች አንዱ ይሄነው፤ እንዲህ ልትል የቻልክበት ምክንያት ምንድነው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- ምን መሰለህ? በወቅቱ አንድ ዜና ሰርተው ነበር፡፡ እኔን የሚመለከት ዜና ም/ቤቱ ሲሰጣቸው ሚዛናዊ ለማድረግ ሀሳቤን አላካተቱም ነበር፡፡ ስላልጠየቁኝ “ፍኖተ ነፃነት” ትልቅ የህዝብ ሚዲያ ናት፤ ግን ምንድነው ከአዲስ ዘመን የተለየ የሚያደርገው?…አዲስ ዘመን ዜና ሲሰራ የጉዳዩን ባለቤት አይጠቅም አይደል?…ፍኖተ ነጻነትም እንደዚያ ስላደረገ አዲስ ዘመን ብዬው ነበር፡፡ እኔን መጠየቅ ነበረባቸው፡፡ በአንድነት ባህል አንድ ግለሰብ ከፕሬዚዳንቱ እኩል መብት አለው፡፡ ያንን መብቴን አልሰጣችሁኝም የሚል ቅሬታ ነው ያነሳሁት፡፡ ከጋዜጠኛው ጋርም ተነጋግረናል፡፡ ዜናውን ስትሰሩ ሚዛናዊ ማድረግ አለባችሁ በሚል ተወያይተናል፡፡ ችግሩም በሰላም ተፈትቷል፡፡

ወያኔ ኢህአዲግ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም የቆመ መንግስት አይደለም :: (ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)

ወያኔ ኢህአዲግ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም የቆመ መንግስት አይደለም :: ሀገር ማለት የተለያዩ ብሄሮች ፣ የተለያዪ ጓሳዎች እና የተለያዩ ሃይማኖቶች ያሎቸው ሰዎች መኖሪያ ናት :: እኛም ሀገራችን ብለን የምንጠራት ሀገራችን ኢትዮጵያ አኩሪ ታሪክ ያላት የተለያዩ ህዝቦች መኖሪያ ሀገር ስትሆን ሕዝቦቾም ለዘመናት በፍቅር፣ በመተሳሳብ ፣ በመከባባር እና በመተባባር አብሮ ሲኖር የነበሩ ህዝቦች እንደነበሩ ከታሪክ መረዳድ እንችላላን::ይችን ሀገራችንን ኢትዮጵያን በተለያዩ ጊዜና ዘመናትም የተለያዩ መንግስታቶች ለዘመናት በመፈራረቅ መርተዋታል

መንግስታቶችም የኢትዮጵያን አንድነት እና ሎአላዊነትን ጠብቀው ህዝቡም ኢትዮጵያዊነቱን ጠብቆ እና አስከብሮ እንዲኖር የበኩላቸውን አስተዋጹ አብርክተው አልፈዋል:: ጀግኖች አባቶቻችንም የኢትዮጵያ ሕዝብም ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ አንድነት ሲሉ ደማቸውን አፍስሰዋል፣ አጥንታቸውን ከስክሰዋል ፣ ህይወታቸውንም መሰዋት አድርገው አሳልፈው ሰተዋል :: ምክንያቱም ኢትዮጵያውነት ኩራት ኢትዮጵያውነት ፍቅር ኢትዮጵያውነት አንድነት መሆኑን ከመሪያቸው ተምረውታልና:: በአሁን ሰአት በስልጣን ላይ ያለው እና የኢትዮጵያን ሕዝብ እየመራው ነው የሚለው የኢህአዴግ ወያኔ መንግስት ወደ ስልጣን ብቅ ካለበት ቀን ጀምሮ ሀገርን በመሸጥ ፣ በመገንጠል እና ሕዝብንም በዘር፣በብሔር፣ በጓሳ እና በቋንቋ በመከፋፈል ኢትዮጵያዊነትን የማጥፋት ርኩስ ተግባሩን እየገፋ ባለበት በእነዚህ አስርት አመታት ውስጥ ግን ኢትዮጵያውነት ኩራት መሆኑ ቀርቶ ውርደድ፣ ስደት መከራ እና ስቃይ መሆኑ እየጨመረ መጥቶል::

 በእነዚህ አመታቶች ኢትዮጵያውነት የሀገር ስሜትና ወኔ ከህዝብ ዘንድ የጠፋበት እና ሕዝቡም እንደ ዜጋ መኖር በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ይገኛል ::በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ለሕዝቡና ለኢትዮጲያዊነት ግድ በሌለው በዚህ ሰይጣናዊ እና አረመናዊ አገዛዝ ስር ብዙዎች ታስረዋል፣ ተገለዋል፣ ወላጆች እንዳይወልዱ መካን ተደርገዋል ሕዝቦች ቄያቸውን መሬታቸውንና ሀብት ንብረታቸውን በግፍ ተነጥቀው ለስደት እና ለመከራ ተዳርገዋል፣እናቶች ልጆቻቸው በግፍ ተገሎባቸዋል ይህ ነው የማይባል ብዙ ብዙ ግፍ በሕዝብ ላይ ተፈጽሞል :: ከእለት ወደ እለትም ሕዝባችን በሀገሩ ላይ መኖር በማይችልበት አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ይገኛል::

 ከሰሞኑ እንኮን እንዳየነው የወያኔ ስርአት ባመጠው በዘር እና በጎሳ ፖለቲካ ችግር ምክንያት ድብድባ እና ስቃይ ደርሶባቸው ከምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ የተፈናቀሉ ገበሬዎች አዲስ አበባ ገቡ የሚለወን ዜና  ከድህረ ገጹች ላይ ባነበብኩኝ ጊዜ ውስጤ ምን ያክል በሀዘን እንደተሞላ ልነግራቸው አልችልም እነዚህ ወገኖቻችን አዲስ አበባ በመግባት  በአካባቢው የደረሰባቸውን ችግር በጊዜው ሀገሪቷን እያስተዳደርኩኝ ነው ለሚለው ለወያኔ ባለስልጣኖች ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት በመጎዝ ቢያስታውቁም በተገቢው መንገድ አቤቱታቸው ሊሰማ ባለመቻሉ እ ነዚህ ተፈናቃዩቹ “ብንመለስ ሊገድሉን ይችላሉ” በማለት ወደ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ጽ/ቤት በመሂድ ‹‹ፍትህ እንድናገኝ ለኢትዩጵያ ህዝብ ሰቆቃችንን አሰሙልን››በማለት የተማጽኖ ድምጻቸውን ሲያሰሙ ተመለክተናል፡፡

 ዛሬ በየቤቱ በዚህ ጨቋኝ ስርዓት የማይማርር የለም:: የሕዝብም የመኖር ሁኔታ ጥያቄ ውስጥ ነው :: የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ለሕዝብ ምንም የጠቀመው ነገር የለም:: ይልቁንስ በሀገር ሀብት እና ንብረት በማን አለብኝነት እንደፈለጋቸው ሲፈነጥዙ ኖረዋል አሁንም እየኖሩ ይገኛሉ:: መንግስታት ሀገርን ሊያስተዳድሩ እና ሊመሩ ወደ ስልጣን ሲመጡ የሀገርን ሉአላዊነትን እና የሕዝብን ጥቅም ለማስከበር ነበር በተቃራኔው ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ሀገራችን ኢትዮጵያ ሕዝቦቿም ለዚህ ባለመታደል መብታቸውን እና ነጻነታቸውን ለመስከበር እንደ ሰው መኖር በሚችሉበት ሁኔታ በነጻነት ለመኖር በመፈለግ በየቀኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሕዝቦች ሀገራቸውን በመልቀቅ ወደተለያዩ ሀገሮች ለስደት ይዳረጋሉ :: በብዛት ወደየ ሃረብ ሀገሩ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ዜጎቻችን ለተለያየ እንግልት መከራ እና ስቃይ እንዲሁም ለሞት የሚዳረጉ ሲሆን በየቀኑ የብዙዎቹ ህይወት እንደዋዛ ያልፋል::

 ነገር ግን ሕዝባችን በየቦታው እና በየአረብ ሀገሩ አሰቃቂ ድብደባ ግፍ እና ግድያ ሲፈጸምበት ሀገርን እየመራው ነው ሕዝብንም እያስተዳደርኩኝ ነው የሚለው የወያኔ ኢህአዴግ መንግስት አንድም ቀን የዚህ ሕዝብ መከራ እና ችግር ግርፋት  ሰቃይ እና ሞቱ ግድ ሲለው እና ለሕዝቡ አለኝታነቱ ሲቆም አይተን አናውቅም::ስለዚህ የኢህአዲግ መንግስት ለኢትዮጵያም ለኢትትዮጵያ ሕዝብም እስከ አሁንም ምንም የጠቀመው ነገር የለም አሁንም ወደፊትም አይጠቅምም ::ስለዚህ ማንኛችንም ኢትዮጵያኖች ከወያኔ መንግስት ምንም ነገር ልንጠብቅ አይገባም ባይ ነኝ ነገር ግን መብታችንን እና ጥቅማችንን የሚያስከብርልንን መንግስት ለመፍጠር  በመነሳት ለወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ግን ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያውነትን ሊወክል እንደማይችል ልንነግረው ይገባል ባይ ነኝ:: ለሀገር እና ለሕዝብ ጥቅም ቆሚያለው የሚል መንግስት የሀገርን ሉአላዊነት ሲያስከብር የሕዝብን ደህንነት እና ጥቅም ሲያስከብር ብቻ ነው እንደ መንግስት በሕዝብ ዘንድ ሊታይ የሚችለው በማለት ጹሁፌን ላጠቃል::

         ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖር!!!

ማንኛውም አስተያየት ካሎት gezapower@gmail.com

      

Wednesday, March 26, 2014

“ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚደረገው ውህደት በግለሰቦች ደረጃ እንጂ በተቋሞቹ ውስጥ አልሞተም”

March 26/2014
አቶ አበባው መሐሪ
የመኢአድ ፕሬዝደንት

መጋቢት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መካከል የነበረው የቅድመ ፓርቲዎች ውህደት ሳይፈጸም ቀርቷል። ሁለቱም ፓርቲዎች አንዱ አንዱን እየከሰሱ ይገኛሉ።

በተለይ አንድነት በአመራሩ በኩል ከመድረክ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን መግለፁ ለውዝግቡ መፈጠር በአይነተኛ ምክንያትነት ይጠቀሳል። መኢአድ በበኩሉ በብሔር ከተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንደሌለው ከበፊቶቹ አመራሮች እስከ አሁን ፓርቲውን ከሚመሩ አመራሮች ጭምር ወጥ አቋም ሲያንፀባርቁ ይሰተዋላል። ከዚህ መነሻነት ከአንድነት ፓርቲ ጋር ውህደት ለመፈጸም የጀመሩት ጉዞ በአንዳንድ የአንድነት አመራሮች ተጨናግፏል በማለት መግለጫ አውጥቷል። እኛም ይህን የውህደት ልዩነት ከግምት በመውሰድ የመኢአድ ፕሬዝደነት የሆኑትን አቶ አበባው መሐሪን አነጋግረናቸዋል።

ሰንደቅ፡- ድርድሩ ለምን በተፈለገው ፍጥነት አልሄደም? ለድርድሩስ አለመሳካት በመሰረታዊነት የሚያነሷቸው ነጥቦች ምንድን ናቸው?

አቶ አበባው፡-በመጀመሪያ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ የምፈልገው ድርድሩ አሁን በያዘው ቅርጽ ይሄዳል የሚል እምነት አልነበረንም። ሁሉም ነገር በቀና መንገድ ይጓዛል የሚል ጤናማ አመለካከት ይዘን ነበር ወደ ድርድሩ የገባነው። ሆኖም በእኛ ቀናነት ብቻ የሚሆን ነገር ባለመሆኑ ውህደቱ አለመሳካቱን ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል የሚል እምነት አለን።

ለድርድሩ አለመሳካት ቢያንስ ሶስት መሰረታዊ ነገሮች ማስቀመጥ ተገቢ ነው። አንደኛው፤ አንድነት ፓርቲ ከመድረክ ጋር በግንባር ለመስራት ፈቃድ የወሰደው ከምርጫ ቦርድ ነው። ይሄውም ከሌሎች ሶስት ፓርቲዎች ጋር በጋራ በምርጫ ሕጉ መሰረት ለመስራት አመልክተው ተፈቅዶላቸው እየሰሩ የሚገኙበት ሁኔታ ነው ያለው። ስለዚህም በመጀመሪያ ደረጃ ከመኢአድ ጋር ውህደት ለመፈጸም አንድነት ከመድረክ የግንባር አደረጃጀት መልቀቅ ይጠበቅበታል። አንድነት ከመድረክ መውጣት እስካልቻለ ድረስ ሕዝቡም እንደሚያውቀው ከመኢአድ ጋር መዋሃድ አይችልም። ምክንያቱም መኢአድ ከመድረክ ጋር ያለው ልዩነት ግልፅ በመሆኑ ነው። በእኛ በኩል በመጀመሪያ ከመድረክ ሙሉ ለሙሉ መውጣታችሁን የሚገልጽ መረጃ ስጡን የሚል ጥያቄ አቅርበናል። አያይዘንም ከእኛ ጋር ውህደት ከፈጸሙ፣ ከመድረክ ጋር በጋራ ሊሰሩ እንደማይችሉ አቋማችንን ግልጽ አድርገናል። እነሱም እንደሚገነዘቡት ውህደት ፈጽመን ወደ መድረክ በጋራ ልንሄድበት የምንችልበት አንዳችም ውለታ የለንም። ይህን መስመር ሊያጠራ የሚችል በአንድነት በኩል የቀረበ ማስረጃ የለም። ይህ በሆነበት ሁኔታ በጥድፊያ የቅድመ ፓርቲ ውህደት ፊርማ የምናኖርበት ሁኔታ ሊኖር እንደማይችል ገልጸንላቸዋል።

ሁለተኛው ነጥብ፤ በውህዱ ፓርቲ ውስጥ አስራ ዘጠኝ የሥራ አስፈፃሚ ቦታዎች ላይ እኩል ሃምሳ ሃምሳ ቦታ ይኑረን ብለናል። መኢአድ መዋቅራዊ አደረጃጀትና ስፋቱ የተሻለ መሆኑ ሁሉም ቢያውቀውም በመርህ ደረጃ ይህን ጥያቄ አቅርበናል። ሌላው፣ ለሊቀመንበሩ ቦታ ግልፅ መስፈርት ይውጣለት ለሚለውም ጥያቄ በምንም መልኩ መስፈርት ሊወጣ አይችልም የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን። በአጠቃላይ ሲታይ የድርድሩ ነጥቦቹ በግልፅ ሳይቀመጡ እና ውይይት ሳይደረግባቸው እንፈራረም ነው የሚሉት።ይህን መሰል አካሄድ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ከዚህ በፊት ብዙ ተሞክሮዎች ስላሉ አልተቀበልነውም። ተመሳሳይ ስህተትም ለመፈጸም ዝግጁ አይደለንም።

ሰንደቅ፡- በውህደቱ ላይ የጊዜ ጥያቄ ብቻ ነው ያላችሁ?

አቶ አበባው፡- የጊዜም የሕግም ጥያቄ ነው ያቀረብነው። ጊዜ ለምትለው በአንድነት በኩል እነአቶ ብሩ ቢያንስ የቅድመ ፓርቲው ፊርማ ለመጋቢት 18 ይሁን የሚል መቃወሚያ አቅርበው ነበር። ኢንጂነር ግዛቸው ፈጽሞ አይሆንም የሚል ምላሽ አቅርበው በግድ ለመጋቢት 11 ነው የሆነው። መሰረታዊ ነጥቡ ግን አንድነት በመድረክ ላይ የሚከተለው ግልፅ ያልሆነ አካሄድ ነው። የሚገርመው የተፈጠሩትን ችግሮች ለመመልከት ከሥራ አስፈፃሚዎች መካከል አቶ ካሳሁን አበባ፣ አቶ ሲራክ አጥናፉ እና አቶ ገለቱ ጀጀርሳ የደቡብ ቀጠና አስተባባሪን ልከን ከኢንጅነሩ ጋር ውይይት እንዲያርጉ አድርገናል። በውይይቱም ከስምምነት ለመድረስ የቻሉ ቢሆንም፣ ከተስማሙ በኋላ መኢአድ ድርድሩን አፈረሰው የሚል መግለጫ ማምሻውን ማውጣታቸው በጣም አሳዛኝ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። በተለይ ይህን መሰል ጥድፊያ የሚያሳየው፣ ከጀርባቸው የተለየ ተንኮል መኖሩን ነው።

ሰንደቅ፡- ከእርስዎ መረዳት አንፃር፣ የአንድነት ፓርቲ አቀራረብ ስትራቴጂክ ወይንስ ስልታዊ ነበር?

አቶ አበባው፡-እየተፈጸመ ካለው ሁኔታ የተረዳሁት ሂደቱ በሙሉ የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ ወይም የምክር ቤቱ አካሄድ አይደለም። የግለሰብ እርምጃ ነው ጎልቶ የወጣው። በግለሰቦች እይታ ድርድሩ የሞተ ነው የሚመስለው። በፓርቲዎቹ በኩል ግን የሞተ ነገር አለ፣ የሚል እምነት የለኝም። በተለይ የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እየሆኑ ያሉትን ነገሮች በጥልቀት ያወቃቸው አልመሰለኝም። የግለሰቦች ማፈግፈግ፣ መቁነጥነጥ ከተመለከትነው ግን የአንድነት አካሄድ ስልታዊ እንጂ ስትራቴጂካዊ አካሄድ አድርጎ ለመቀበል በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ነው ያለው።

ሰንደቅ፡- በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል አደራዳሪዎች መኖራቸው ይታወቃል። አደራዳሪዎቹ ይህን ችግር ሊፈቱት አልቻሉም? በምንስ አግባብ ነው የአደራዳሪነት ሚና የወሰዱት?

አቶ አበባው፡- መታወቅ ያለበት እነዚህን አደራዳሪዎች ኢንጅነር ግዛቸው ናቸው መርጠው ያመጧቸው። ቤታችንን አንኳኩተው የገቡት እራሳቸው ናቸው። እኛ አልመረጥናቸውም። እናሸማግላችሁ ሲሉን ነው ያየናቸው። መልካም፣ ለማሸማገል ከሆነ ብለን ተቀበልናቸው። በሂደት ግን ነገሩ ሁሉ የተገላቢጦሽ ነው የሆነው። ይህን ስል ግን ሁሉንም ሽማግሌዎች ማለቴ አይደለም።
ሰንደቅ፡- መኢአድ ባልመረጣቸው ሽማግሌዎች ለመደራደር መዘጋጀቱ በየዋህነት የሚወሰድ ነው ወይንስ የፖለቲካ ስህተት መሆኑን ይቀበላሉ?

አቶ አበባው፡-በእኛ በኩል የነበረው፤ እነዚህ ሰዎች ሙሁራን ናቸው። ለሀገር አስበው ነው ከሚል ቀና መነሻ ነው የተቀበልነው። በጀርባ በኩል የሚመጣ ነገር አለ ብለን አላሰብንም። እየወቀስኩ አይደለም፣ መጡብን ብቻ ለማለት ነው። በቀና ልቦና ነገሮችን መውሰድ በእኔ እምነት የፖለቲካ ስህተት አይደለም።

ሰንደቅ፡- በሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚቀርበው ውህደቱ ሀገር በቀል ሳይሆን ውጭ ባሉ አካላት የተፈበረከ በመሆኑ ነው፣ ለአለመስማማት የዳረጋቸውም ከውጪ የመጣ ስለሆነ ነው እየተባለ ነው። በዚህ ላይ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው?

አቶ አበባው፡- ትክክል ነው። ሆኖም ውህደቱን ሕዝቡ ይፈልገዋል። ዋናው ነጥብ መታየት ያለበት ይህ ይመስለኛል። ነገር ግን ከሁኔታዎች መነሻነት ከተመለከትነው የውህደቱ ጥንስስ ከውጪ ተቀምሮ የመጣ ነው የሚለው ጥርጣሬ ሚዛን የሚደፋ ነው። ስትራቴጂው የተነደፈው ውጪ ነው። ሀገር ውስጥ ያሉት አስፈፃሚዎች ናቸው። በእውነተኛ ፍላጎት የመጣ የድርድር ሂደት ቢሆን ስህተት ማንም ይስራ ማንም በትዕግስት ውህደቱን መፈጸም እንጂ ይቋረጥ የሚል የተጣደፈ የአደባባይ ምላሽ አይሰጥም። በእኛ በኩል ውይይቱ ይቀጥል እያልን እየጠየቅን በር ዘግተውብን ጥለውን ባልሄዱ ነበር። ስለዚህ የውህደቱ ቅመራው ያለው ውጪ ሀገር ነው።

ሰንደቅ፡- ቅመራው ውጪ ነው ብለው የሚያምኑ ከሆነ፣ እንዴት በዚህ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ ይሆናሉ?

አቶ አበባው፡- ይህን ነጥብ በትክክል መመልከት ተገቢ ነው። የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እና የምክር ቤት አባላት ሁኔታውን በጥልቀት ሳይመለከቱት በቀናነት በተቆርቋሪነት እየሰሩ ነው የሚገኙት። የቅመራው ባለቤቶች አንዳንድ ግለሰቦች ናቸው። መታወቅ ያለበት ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚደረገው ውህደት በግለሰቦች ደረጃ እንጂ በተቋም ደረጃ አልሞተም። በርግጠኛነት ሁለቱ ፓርቲዎች ይህን ስልታዊ ቅመራ በጋራ በመሆን እናከሽፈዋለን። ምክንያቱም ይህ አሁን እየተቀነቀነ ያለው አስተሳሰብ የግለሰቦች በመሆኑ ነው። እንዲሁም የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ የምክር ቤት አባላት ፍላጎት እንዳልሆነ ስለምንረዳ ነው።

ሰንደቅ፡- በእናንተ አባላት የሚቀርበው ቅሬታ፣ አንድነት የመኢአድን መዋቅር ጠቅልሎ በመውሰድ ራሱን የበለጠ ለማደራጀት የሚፈልግ ፓርቲ ነው የሚል ነው፤ በዚህ ነጥብ ላይ ምን አስተያየት አልዎት?

አቶ አበባው፡- አንድነት መዋቅር አለው፣ የለውም የሚለው ክርክር እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መኢአድ ያለውን መዋቅር ሰጥቶም ቢሆን ለሕዝባችን አማራጭ ፓርቲ መሆን በጋራ እስከቻልን ድረስ ብዙ ችግር የለውም።

ሰንደቅ፡- ሌሎች ወገኖች በበኩላቸው ገዢው ፓርቲ ሁለቱ ፓርቲዎች እንዳይስማሙ ሰርጎ ገብቷል እያሉ ነው የሚገኙት። ይህን ሃሳብ ምን ያህል ይጋሩታል?

አቶ አበባው፡- እንዲህ እንደሚባል እኛም እንሰማለን። የሚገርመው እኛ የተስማማነው ነገር ሳይኖር ገዢው ፓርቲ ምኑን ነው የሚያፈርሰው። አንድነት ከመድረክ ሙሉ ለሙሉ መውጣት አለበት ለሚለው ጥያቄ፣ አንድነት እንጂ ገዢው ፓርቲ ምላሽ መስጠት ያለበት አልመሰለኝም። መጠራጠሩ ግን ክፋት የለውም፣ ተጨባጭ ለማድረግ ግን ብዙ መስራት ይፈልጋል።

ሰንደቅ፡- በተደጋጋሚ ግለሰቦች እያሉ ነው። እነዚህ ግለሰቦች ለምን በይፋ በማሳወቅ አትታገሏቸውም?

አቶ አበባው፡- ጋዜጠኛ እንዲህ ብሎ አይጠይቅም። ከዚህ በፊት የነበረውን ቅንጅት ማን እንዳፈረሰው ታውቃላችሁ። ለምሳሌ ብርቱካን በእስር በነበረችበት ጊዜ ብርቱካን የታሰረችው በራሷ ችግር እንጂ በፓርቲ አይደለም። አዲስ ሰው መሾም አለበት ያለው ማነው? ከዚህ በፊት አንድነትን ከመድረክ ጋር ለማዋሃድ ሽማግሌ የነበሩት ሰዎች እነማን ናቸው? ከዶክተር ነጋሶ ጋር ከስምምነት የደረስንበትን ሰነድ አልፈርምም ያለው ማን ነው? ለምንስ ተደራዳሪ የነበሩት እንዲነሱ ተፈለገ? ድርድሩ ከቆመበት መጀመር ሲገባው ለምን እንደአዲስ እንዲጀመር ተፈለገ? ከመድረክ ውጪ ሆነናል ተብሎ በአደባባይ ከተናገሩ በኋላ፤ መለስ ብሎ ጋዜጦችን ጠርቶ ከመድረክ ጋር እንሰራለን ማለት ምን ማለት ነው? የአንድነት ወጣት አመራሮች መድረክን በአደባባይ እየተቃወሙ፣ ግለሰቦች ግን ከመድረክ ጋር እንሰራለን ለምን ይላሉ? ስለዚሀም የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እና ምክር ቤት ይህን እውነት ፈትሾ የውህደቱን ሂደት እንደሚቀጥል ተስፋ አለኝ። ይህ የማይሆን ከሆነም እንደበፊቱ በትብብር ለመስራት ዝግጁ ነን።

TPLF tapping your phone & internet

March 26, 2014

Ethiopia uses foreign kit to spy on opponents – HRW

Ethiopia’s government is using imported technology to spy on the phones and computers of its perceived opponents, a Human Rights Watch report says.
The New York-based rights group accuses the government of trying to silence dissent, using software and kit sold by European and Chinese firms.
The report says the firms may be guilty of colluding in oppression.Ethiopian government is accused of installing spyware on dissidents' computers
An Ethiopian government spokesman, quoted by AFP, dismissed the report as a part of a smear campaign.
“There is nothing new to respond to,” Ethiopian Information Minister Redwan Hussein told the agency.
Human Rights Watch (HRW) says its report is based on more than 100 interviews with victims of abuses and former intelligence officials, conducted between September 2012 and February this year.
Rights groups frequently accuse the Ethiopian government of cracking down on opposition activists and journalists.
The government denies the claims.
‘Overseas surveillance’
All phone and internet connections in Ethiopia are provided by a state-owned company. According to HRW, this has given the government unchecked power to monitor communications.
“Security officials have virtually unlimited access to the call records of all telephone users in Ethiopia,” the report said. “They regularly and easily record phone calls without any legal process or oversight.”
Recorded conversations are also alleged to have featured in abusive interrogations of suspected dissidents.
The technology used by to monitor the communications is said to have been provided by companies based in China, the UK, Italy and Germany.
“The foreign firms that are providing products and services that facilitate Ethiopia’s illegal surveillance are risking complicity in rights abuses,” HRW’s business and human rights director, Arvind Ganesan, said.
According to the report, the government has extended its surveillance to Ethiopians living overseas.
Ethiopians living in the UK and the US have accused the authorities in Addis Ababa of planting spy software on their computers.
Both countries have been urged to investigate the claims, on the grounds that they may have violated domestic laws against invasions of privacy.
HRW says the firms that sell surveillance technology to governments also have a duty to ensure that their products are not helping to suppress human rights.
“The makers of these tools should take immediate steps to address their misuse,” Mr Ganesan said.
Source: BBC

እውነተኛው አ.ኢ.ግ.ተ. (EITI) ወይስ የማዳም ክላሬ የሙስና ማጋበሻ ቡድን? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

March 26/2014

March 26, 2014
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ማዳም ክላሬ አሸንፈዋል! እንኳን ደስ ያለዎት፣ ማዳም ክላሬ!
ባለፈው ሳምንት የ “አምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት/Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ሊቀ መንበር የሆኑት ማዳም ክላሬ ሾርት ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም እና በማስፈራራት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የሙስና ማጋበሻ ቡድናቸው አባል እንዲሆን ለማስቻል የEITI የቦርድ አባላት ድምጻቸውን እንዲሰጡ በማድረጉ ጥረት ሲያካሂዱት የቆዩት ዥዋዥዌ ጨዋታ ተሳክቶላቸዋል፡፡ ማዳሟ አሮጌውን እና ያረጀ ያፈጀውን የአሰራር ሂደትን ማለትም እጅ በመጠምዘዝ፣ በኃይል በማስፈራራት፣ ስልጣንን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም በማስገደድ፣ ከኋላ ሆኖ በማስተኮስ፣ ስልጣንን መከታ በማድረግ ከህግ አግባብ ውጭ በግድ እንዲያምኑ በማድረግ፣ አሰልች እና የምጸት ቃላትን በመጠቀም እና የህጻናት ዓይነት እሽሩሩ ዘይቤ ቁጣን በመከተል ለርካሽ ጥቅም ሲባል የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ሀቅን በመደፍጠጥ በሸፍጥ ለጊዜውም ቢሆን ሀሳባቸውን አሳክተዋል፡፡ ማዳሟ በእንደዚህ ዓይነት እኩይ ምግባራቸው የተካኑ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ2003 እንግሊዝ እና አሜሪካ በኢራቅ ላይ ወረራ ለማካሄድ በተዘጋጁበት ጊዜ ማዳም ሾርት በቶኒ ብሌር ላይ ጠንካራ የሆነ ትችት በማቅረብ ከመንግስታቸው ዓለም አቀፍ የልማት ጸሐፊነት ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንደሚለቁ በማስፈራራት ሁኔታውን በመቃወም የኃይል ትችት አቅርበው ነበር::   ብሌርንና የአሜሪካን መንግስት ሲተቹ አንዳሉት “ሆኖም ግን በዚያም ተባለ በዚህ የጦርነቱ መካሄድ አይቀሬነት በተረጋገጠበት ወቅት፣ ሌሎችን አገሮች በኃይል እና በማስፈራራት ለጦርነቱ መካሄድ ድጋፍ እንዲሰጡ ያስገድዱ ነበር፡፡“EITI board chairwoman
አንደ ኢራቁም ጉዳይ: ማዳም ክላሬ “በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ድምጽ በማግኘት የEITI አባል እንዲሆን ከህግ አግባብ ውጭ ስልጣንዎን በመጠቀም  የቦርድ አባላትዎን ያስገድዱ እና ያሳምኑ እንደነበር እናውቃለን፡፡“ እንኳን ደስ ያለዎት! ድል ተቀዳጅተዋል፡፡ የድል ደረጃ አድርገው ይውሰዱት፣ ጣራውን ከፍ ያድርጉት፡፡ “ለሰብአዊ መብት የሚሟገቱትን ድል አድርገዋል፣ በእራስዎ ቦርድ ያሉትን የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን በመላው ዓለም ፊት አዋርደዋል፣ እናም ዕድለቢሶችን እና ድምጽ አልባ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን አባርረዋል፣ “መብቶቻቸውንም” ደፍጥጠዋል፣ አሁን አዲስ አበባ በመሄድ የስኬት በዓልዎን ቸበርቻቻ ማክበር ነው፡፡ በትግል ያገኙት ውጤት ነውና፡፡ ቻምፓኝ እና ኮኛክ እንደ ጅረት ውኃ ይፍሰስ፡፡ አሁን EITIን የእርስዎ የግል ንብረት አድርገውታል፡፡ የእራስዎ ህጻን ነው! ለ EITI አዲስ ስም ያውጡለት፡፡ የማዳም ክላሬ የሙስና ማጋበሻ ድርጅት በሉት? ጥሩ የእምነተቢሶች የመጠሪያ ስምን ይዟል፡፡
በጣም የሚያስደንቀው እውነታ ግን የማዳም ሾርት ፍልስፍና (እራሳቸው “መርህ” እያሉ የሚጠሩት) በብዙ በሙስና በተዘፈቁ አገሮች የማዕድን እና አምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ላይ ዕዉን እየሆነ መጥቷል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ገዥ አካል የEITI አባል በማድረጉ እረገድ ማዳም ሾርት የማዕድን ሙስናን ለመቆጣጠር የሚያስችል ቀላል እና በሚከተለው ዳህራ ላይ ትኩረት ያደረገ በአጭር ርቀት ላይ የተመሰረተ ድሁር ህልዮት ቀምረዋል፤ ህልዮቱም እንዲህ ይላል፣ “በዓለም ላይ በጣም በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት የይስሙላ የግልጽነት እና ተጠያቂነት ካባን ደርበው የEITI አባል እንዲሆኑ መፍቀድ፡፡“ ከዚያም እግሮችን በማንሸራተት መደነስ እና ማቀንቀን፡፡ ስለግልጽነት እና መልካም አስተዳደር ጥቂት አስመሳይ ቃላትን እና ሀረጎችን በማነብነብ የህዝብ እምነትን ለማግኘት የማታለያ ጥረት ማድረግ፡፡ የውሸት በእመኑኝ ላይ የተመሰረቱ ጥሩ የሚመስሉ የቢሮክራሲ ፍሬ ከርስኪ የታጨቁበት የማመልከቻ ቅጽ መሙላት፡፡ ከዚያም በማዕድን ዘርፍ ስራው ጥሩ ተሞክሮ እና ታማኝ መሆናቸውን በመግለጽ የአባልነት ጥያቄውን የምስክር ወረቀት ለማግኘት መጠየቅ፡፡ በመጨረሻም ከደስታ የመጨረሻው ከፍተኛ እርከን ላይ በመድረስ ሰርግ እና ምላሽ ማድረግ ትልቁ ግባቸው ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ ማዳም ክላሬ ሾርት ገዥውን አካል የጸረ ሙስና ተዋጊ ጦር አስመስሎ በማቅረብ እንዲሁም ወሮበላ ዘራፊዎችን እና ሸፍጠኛ ወንጀለኞችን በእራሳቸው ተለክቶ የተሰፋ የማስመሰያ ካባ በማልበስ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፊት የተከበሩ የአገር መሪዎች አስመስሎ ለማሳየት እና ለቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ያለምንም እንከን የጥሩዎች ሁሉ ተምሳሌት አድርጎ ለማቅረብ የተቀመረ ስሌት ነው፡፡ እንግዲህ በዚህ መንገድ ነው በአፍሪካ እና በሌሎች አገሮች ያለው በሙስና የበከተው የማዕድን እና የተፈጥሮ ጋዝ ዘርፍ በማዳም ክላሬ ሾርት ከሙስና የማጽዳት የአሰራር ዘይቤ የተቃኘው፡፡
በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የEITI አባል እንዲሆን የተሰጠው ውሳኔ ፍጹም በሆነ ሙስና የተደረገ እና የማስመሰያ የአባልነት ተውኔት ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2010 ገዥው አካል ለአባልነት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ በተደረገበት ጊዜ የተሰጠው ምክንያት:- “የኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ’ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች በነጻነት እንዳይንቀሳቀሱ በሂደትም ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዳያደርጉ ደንቃራ ሆኗል ወደፊትም ይሆናል፤ ስለሆነም የበጎአድራጎትእናማህበራትአዋጅ’ እስካልተወገደድረስኢትዮጵያEITIአባልእንድትሆንእንደማይወስን በተጨባጭ ገልጾ ነበር፡፡ በ EITI ታሪክ በእንደዚህ ያለ የአፋኝነት ህግ መሰረት ከሰብአዊ መብት አጠባበቅ ጋር በተያያዘ መልኩ አንዲት አገር የድርጅቱ አባል እንዳትሆን የአባልነት ጥያቄው ውድቅ ሲደረግ የመጀመሪያው እና ብቸኛው ክስተት ነው፡፡ (የተሰመረው አጽንኦ ለመስጠት ነው)፡፡
ታዲያ ኢትዮጵያን በአሁኑ ጊዜ በአባልነት ለመቀበል የተቻለው በስራ ላይ እየተተገበረ ያለው “የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ” ተለውጦ ነው? እ.ኤ.ኤ ከ2010 ጀምሮ በኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ እንቅስቃሴ ላይ ምን የተለወጠ ነገር አለ? “በአዋጁ” መውጣት እና በስራ ላይ መዋል ቀጥተኛ እንደምታ ምክንያት እ.ኤ.አ በ2010 ብዛታቸው 4,600 የነበሩት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በአስደንጋጭ ሁኔታ ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ በዓመቱ መጀመሪያ አካባቢ 1,400 ሊሆኑ  ችለዋል፡፡ “ከእነዚሁ ከተረፉት እና በሞት የሽረት ትግል ውስጥ በመንፈራገጥ ላይ ከሚገኙት ድርጅቶች ውስጥ ደግሞ በአዋጁ አሳሪነት ምክንያት 90 በመቶ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆነውን የሰው ኃይላቸውን እንዲቀንሱ ተገደዋል፡፡”
በሶስት ወራት ውስጥ በአንድ ጊዜ እርምጃ ብቻ “አዋጁ” በኢትዮጵያ 70 በመቶ የሚሆኑትን የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን ከስራ ውጭ አድርጓቸዋል፡፡ እ.ኤ.አ በፌብሯሪ 2010 ገዥው አካል ከተመሰረተ ብዙ ጊዚያትን ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤን እና የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበርን በተጨባጭ የእነዚህን ሁለት ጠንካራ ተቋማት አቅም ሽባ ለማድረግ፣ እንዲሁም ደግሞ ሊያሳኩ የሚያስቧቸውን የተቋቋሙባቸውን ዝንባሌዎች እና ዓላማዎች ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ መልኩ ለማስተጓጎል በማሰብ ሀብታቸውን እንዳያንቀሳቅሱ አገደ፡፡
የEITI የቦርድ አባላት እ.ኤ.ኤ በ2010 የገዥውን አካል የአባልነት ጥያቄ ውድቅ ካደረገ በኋላ በእርግጠኝነት አንድ ነገር ተለውጧል፡፡ እ.ኤ.አ በማርች 2011 ማዳም ክላሬ ሾርት የEITI የቦርድ ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ማዳም ሾርት ለብዙ ጊዜ ተደናቂ መሪ እና በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል ሻምፒዮን እንዲሁም በቅርቡ የአረፉት የአቶ መለስ ዜናዊ  ከፍተኛ አድናቂ ናቸው፡፡ በአቶ መለስ ዜናዊ ላይ ያመልካሉ፡፡ የሚያመልኳቸው ግን በጥሩ ነገር ተምሳሌትነታቸው አይደለም፡፡ ምናልባትም እ.ኤ.አ በ2010 ገዥው አካል የድርጅቱ አባል እንዳይሆን ውድቅ ያደረጉትን የEITI የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እና የስራ ባልደረቦቻቸውን ክብር እና ሀሳብ ለማንኳሰስ እንዲሁም በወሰንየለሽ አፍቅሮ የተዘፈቁበትን ገዥ አካል ሽንፈት ለመበቀል ያደረጉት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይገመታል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ የገዥው አካል የአባልነት ጥያቄ ውድቅ በተደረገበት ጊዜ በ EITI ታሪክ በእንደዚህ ያለ የአፋኝነት ህግ መሰረት “በግልጽ ከሰብአዊ መብት አጠባበቅ” ጋር በተያያዘ መልኩ አንዲት አገር የድርጅቱ አባል እንዳትሆን ውድቅ ሲደረግ የመጀመሪያው እና ብቸኛው ክስተት  ስለነበረም ነው፡፡ ማዳም ሾርት በአቶ መለስ ዜናዊ እና ኩባንያቸው ላይ የደረሰውን “ውርደት” ለመበቀል ዕቅድ በማውጣት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፊት የአቶ መለስን የመጀመሪያ የአባልነት ጥያቄ ውድቅ በማደረግ ቁልፍ ሚና የተጫወቱትን የEITI የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮችን ማዋረድ ላይ ያጠነጠነ ነበር፡፡ ማዳም ክላሬ፣ በቀልተኛዋ አሁን የበቀል እርምጃዎን ወስደዋል፡፡!
ማዳም ክላሬ በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል በመወገን እ.ኤ.አ ማርች 11/2014 ግልጽ ደብዳቤ በመጻፍ ድፍረት የተሞላበትን የዘመቻ ውትወታ (በማስገደድ አላልኩም) ሲጀምሩ በEITI በቦርድ አባልነት ባሉት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እንደ አላዋቂ ልጅ አጥፊዎች ያህል አውርደው በመመልከት የቁጣ ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ አምባርቀውባቸዋል፡፡ እብደትን የተላበሰ የሚያስገርም ምልከታም አድርገዋል፡፡ እንዲህ የሚል ምልከታ፣ “የEITI መርሆዎችን የሚተገብሩ አገሮችን ሁኔታ በመምለከትበት ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጀቶች ሁኔታ በሌሎች አገሮች ከሚታየው በብዙ መልኩ የከፋ ነው የሚለውን አባባል አልቀበለውም፣“ በማለት ለእራስ ታላቅ ክብርን የሰጠ የድንፋታ ንግግር አሰምተዋል፡፡ ማዳሟ ይህንን ንግግር ሲያደርጉ ምን ለማለት ፈልገው ነው? ለመሆኑ የEITI አባላት እነማን ናቸው?
EITI በአሁኑ ጊዜ 40 ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ አባል አገሮች አሉት፡፡ ብዙዎቹ አባል አገሮችም በዓለም ላይ በሙስና በበከቱ እና ጨቋኝ መንግስታት መዳፍ ስር እግር ከወርች ተተብትበው የሚገኙ ናቸው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አፍጋኒስታን፣ ቡርኪናፋሶ፣ ካሜሩን፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ፣ ቻድ፣ የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑብሊክ፣ ጊኒ፣ ካዛኪስታን፣ ላይቤሪያ፣ ማሊ፣ ማውሪታንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ኒጀር፣ ናይጀሪያ፣ የኮንጎ ሬፑበሊክ፣ ሴኔጋል፣ ሴራሊዮን፣ ታዣኪስታን እና የመን ይገኙበታል፡፡ “የኢትዮጵያ ሁኔታ ከሌሎች የከፋ አይደለም” ከሚለው ማነጻጸሪያቸው አንጻር ማዳም ሾርት በእርግጠኝነት አንድ ሊካድ የማይችል ሀቅን ተናግረዋል፣ ይኸውም በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ከሌሎች በገፍ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ከሚፈጽሙት የEITI አባል አምባገነን አገሮች የከፋ አይደለም፣ ወይም ደግሞ ከብዙዎቹ የተለየ አይደለም ብለዋል፡፡ ሁሉም በሙስና የበከቱ ናቸው፡፡ ሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማትን ህልውና ግብአተ መሬት የፈጸሙ ናቸው፡፡ እናም የመመንተፊያ የቆዳ ቦርሳዎችን ተሸክመው ክው ክው የሚሉ ዘራፊዎች እና ወሮበሎች ናቸው፡፡ ማዳሟ ለቦርድ አባላቱ፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ለኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ለማስተላለፍ የፈጉት ትክክለኛው መልዕክት ግልጽ ነበር፡፡ “ሁሉንም ጸጥ ለማድረግ” ነው፡፡ ከተሰጣችሁ ቁመት በላይ አትንጠራሩ፡፡ በሙስና የበከቱ ዘራፊዎችን ሊፒስቲክስ በመቀባት የተለመደውን የቢዝነስ ስራ እናስቀጥል፡፡ በዚህ መንገድ መጓዝ አንችልምን?
ባራክ ኦባማ እጩ ፕሬዚዳንታዊ ተመራጭ በነበሩበት ጊዜ ከተናገሩት ጋር እስማማለሁ፣ “አሳማን ለማቆንጀት ሊፒስቲክ (የከንፈር ቀለም) መቀባት ይቻላል፣ ሆኖም ግን አሁንም ያው አሳማ ነው፡፡ አንድን ትልቅ አሳ በወረቀት መጠቅለል ይቻላል፣ እናም ለውጥ ብለን ልንጠራው እንችላለን፣ ሆኖም ግን መጠንባቱን አያቆምም ፡፡“ EITI ለዘራፊዎች በልክ ዩኒፎርም አሰፍቶ ማስመሰያ በማልበስ “ግልጽነት” እና “ተጠያቂነት” ብሎ ሊጠራቸው ይችላል፣ ሆኖም ግን ያው አሁንም ዘራፊዎች ናቸው፡፡ ሙስናን በEITI አርማ መጠቅለል ይቻላል እናም ንጹህ ብሎ መጥራት ይቻላል፣ ሆኖም ግን እስከ አሁንም መጠንባቱን አያቆምም ፡፡ EITI የአፍሪካ ዘራፊ ገዥዎችን ንጹህ እና ጨዋ ለማስመሰል የሚቀባ ሊፒስቲክ ነው፡፡
አዲስ በሆነ መልኩ ማዳም ሾርት በእርግጠኝነት ትክክል ናቸው፡፡ ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ እጠይቃለሁ! ብዙዎቹ በEITI አባል የሆኑ የአፍሪካ አገሮች በተኩላ ዘራፊ ሙሰኛ ገዥ ቡድኖች የሚሽከረከሩ ናቸው፡፡ “ዘራፊነት የአፍሪካ አምባገነናዊነት ከፍተኛው ደረጃ” በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ትችት ህልዮት ቀምሬ ነበር፡፡ ማዳም ሾርት በገንዘቡ በኩል ትክክል ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ዘራፊ ገዥ አካል በEITI ካለው ከትክክለኛ ቦታው ታላቁ የሙስና ጠረጴዛ ላይ ለምን ነጠሉት? በእውነት ይህ ጉዳይ ፍትሀዊ አይደለም፡፡
የበለጠ ከዚህ በተለየ መልኩ ማዳም ሾርት የእኔን ነጥብ በትክክል አረጋግጠውታል፡፡ በእርግጥ EITI ማዕከላዊ የማዕድን ሙስና ቡድን ነው፡፡ አሊባባን እና 40ዎቹን ሌቦች አስታወሰኝ፡፡
አሁንም በጣም በተለየ መልኩ ማዳም ሾርት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የአባልነት ጥያቄው ተቀባይነት እንዲያገኝ እና በEITI ሲስተም እንዲገባ ለማድረግ በግልጽ ደብዳቢያቸው ላከናወኑት የሞት የሽረት ትግል በጣም ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ፡፡ ከልብ በመነጨ መልክ ላደረጉት የትግል መንፈስ አደንቃቸዋለሁ፡፡ ማዳም ሾርት በእርሳቸው መንገድ የማይቆሙትን ማንንም ቢሆን የማዋረድ ስብእና ያላቸው ሰው ናቸው፡፡
የገዥውን አካል የአባልነት ጥያቄ ቦርዱ እንዲያጸድቀው በማስገደድ ማዳም ሾርት ታላቅ አገልግሎት አበርክተውልናል፡፡ ምንም በውል ሳያጤኑት EITI በእውን ምን ዓይነት ተቋም እንደሆነ እንዲሁም በህገወጥ መንገድ ጥቅም ለማግኘት የማስጠበቂያ የጫጫታ ቡድን መሆኑን አጋልጠዋል፡፡ በተደራጁ የወንጀለኞች ድርጅቶች የጥቅም ማስጠበቂያ የጫጫታ ቡድኖች የፖሊስ እና የፍትህ አካላቱ በትክክል ህዝቡን ማገልገል ሲሳናቸው ወይም ደግሞ ለማህበረሰቡ የህግ ጥበቃ ማቅረብ ሳይችሉ ሲቀሩ የሚከሰቱ ናቸው፡፡ “በጥቂት የክፍያ ገንዘብ” ሰበብ በሸፍጥ የተካነው ወንጀለኛ ለደንበኞቹ “ህግ እና ስርዓትን” ያስከብራል፣ እናም በሌሎች ወሮበሎች እና አዲስ ወንጀለኞች እንዳይዘረፉ ጥበቃውን ሊያረጋግጥ ይችላል፡፡
አብዛኞቹ የEITI አባል አገሮች በራሳቸው የህግ ተቋማት ሙስናን የመቆጣጠር አቅሙ የላቸውም፡፡ ብዙዎቹ አባል አገሮችም የአንድ ሰው፣ የአንድ ፓርቲ የፈላጭ ቆራጭነት ስርዓትን የሚያራምዱ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ተቋማቱ እስከ አጥንታቸው ድረስ በዘለቀ የሙስና ነቀርሳ የበከቱ ናቸው፡፡ የይስሙላ ፓርላሜንታሪ ስርዓቶች አሏቸው፡፡ አቃቢያነ ህጎቻቸው በትምህርት፣ በማህበራዊ እና በሞራል ስብዕና አቅመቢስ የሆኑ ድሁር ወሮበላ ዘራፊዎች እና ጽናት የሌላቸው የእመኑልኝ የህግ መጽሐፍትን በብብታቸው ሸጉጠው የሚዞሩ የፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ የፍትህ ስርዓቱ ከገዥው አካል አመራሮች የኋላ ኪስ የሚገኝ ስርዓት ነው፡፡ የጸረ ሙስና ኮሚሽኖች የፖሊቲካ ተቀናቃኞቻቸውን፣ በገዥው አካል ላይ የሚነሳሱትን ሰላማዊ አመጸኞችን ጨምሮ ለማጥቂያነት በእራስ የተሞሉ የርቀት አነጣጣሪ ሚሳይሎች ናቸው፡፡ የህግ የበላይነት የለም፣ ያለው የደናቁርት የዘራፊዎች ህግ ብቻ ነው፡፡
በአሁኑ ጊዜ EITI  በአፍሪካ እና በሌሎችም አገሮች ለዘመናት የሚዘልቅ የማዕድን ሙስና የተንሰራፋበት አዲስ ዓለም አቀፋዊ ስርዓት ለማንበር ዝግጅቱን አጠናቅቋል፡፡ ላለፉት አስርት ዓመታት EITI ያከናወናቸው ተግባራት እንግዲህ ይህንን ጉዳይ እውን ለማድረግ ነው፡፡ እውነት ለመናገር EITI  በእራሱ የሙስና ቡድን በሙስና የተዘፈቁ ገዥዎችን ለመከላከል የተቋቋመ ቡድን ነው፡፡ የአገራቸውን የተፈጥሮ ሀብት የዘረፉትን እና የመዘበሩትን ወሮበላ ዘራፊዎች መልሶ ለመዝረፍ የተቋቋመ ሰላማዊ ድርጅት ነው፡፡ ሁሉም በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት እንደገና ለመወለድ እና የEITIን ስርዎ መንግስት ለመቀዳጀት የሚከተሉትን ሂደቶች መከተል ይጠበቅባቸዋል፡፡ 1ኛ) የአባልነት መጠየቂያ ቅጹን መፈረም እና የEITIን የጥያቄ እና መልስ መዝሙሩን ደጋግሞ ማነብነብ፣ 2ኛ) መጠመቅ እና በ EITI ቄሶቹ መቀባት፣ 3ኛ) ቀደም ሲል ለተሰሩት ጥፋቶች በህዝብ ፊት ጥቂት ንስሀ የመግባት ተግባራትን ማከናወን፣ 4ኛ) ቀደም ሲል ለተፈጸሙ የሙስና ተግባራት ሁሉ ይቅርታ ማድረግ፣ 5ኛ) ከሙስና ወደ ንጹህነት እስኪመለሱ ድረስ የሶስት ዓመታት የዝግጅት ጊዜ መስጠት የሚሉት ናቸው፡፡
ለዘራፊ ገዥ አካላት ይህ ታላቅ ቅሌት ነው፡፡ የEITIን የከሀዲነት ባጅ ለማጥለቅ እና ከሙስና ምን ያህለ ነጻ እንደሆኑ በባዶ ኩራት በታጀለ መልኩ ለማሳመን በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡  የEITI ባጅ በኢትዮጵያ ላሉት በሙስና የተዘፈቁ ዘራፊዎች የባዶ ዲስኩር የጉራ ችርቸራ  መብትን ያጎናጽፋቸዋል፡፡ የEITIን የአባልነት ፈቃድ በማግኘት በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና በኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ላይ በእውነተኛነት ላይ ተመስርቶ የተገኘ ፈቃድ አስመስሎ ለመቅረብ በሸፍጥነት መጠቀሚያ ያድርጉታል፡፡ ” ሂዩማን ራይትስ ዎች አፍንጫችሁን ላሱ! የኢትዮጵያ የዲያስፖራ አፍንጫችሁን ላሱ! እዩ እንግዲህ ተመልከቱ እንደ አዳኝ ውሻ ጥርስ ንጹህ ነን እናም ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም ይህንን ልናረጋግጥላችሁ እንችላለን!“:: የማዕድን ሙስናውን ከጥርጣሬም በላይ ከተጨባጩ ሁኔታ በላይ፣ ከቦርዱ በላይ እና ከህግ በላይ አጠናክረው ይቀጥሉበታል፡፡ የEITI የአባልነት ፈቃድ በመስጠት ለመስረቅ፣ የተፈጥሮ ሀብትን ታማኝነት በጎደለው የጮሌነት አካሄድ ጥቅምን ለማግበስበስ ለማይጠረጠሩ ባለሀብቶች በመስጠት የሞራል ልዕልና በጎደለው መልኩ ተበዳሪዎችን እና ለጋሽ ድርጅቶችን በመጭመቅ ሌላ ተጨማሪ ገንዘብ ማጋበስን የሚያስችል መብትን ይሰጣቸዋል፡፡
የEITI አባል ለመሆን የተዘጋጁት ደረጃዎቹ እና መስፈርቶቹ ጸጥ የማድረጊያ የማስመሰያነት ዘዴዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ጸጥ የማድረጊያ ስልቶች ከውጭ የሚሰነዘሩባቸውን ትችቶች ለመሸበብ ብቻ አይደለም የተዘጋጁት ሆኖም ግን ከውስጥ ለሚነሱባቸው ሰላማዊ አመጾች ማዳፈኛ  እንዲሆኑ ጭምር እንጅ፡፡ EITI በአሰልች እና ተደጋጋሚነት ባለው የቢሮክራሲ ውጣውረድ የተተበተበ ፍሬከርስኪ የበዛበት የአባልነት መቀበያ መስፈርቶች፣ ተጠያቂነት እና ግልጸኝነት ያለው መሆኑን ከጉራ ባልዘለለ መልኩ ዲስኩር ሲያደርግ ይደመጣል፡፡ ማዳም ሾርት ግልጽ ደብዳቤ ብለው አዘጋጅተው በለቀቁት ደብዳቤ ላይ ለድርጅቱ እጩነት ለመብቃት “ከEITI ጋር አብሮ ለመስራት በግልጽ እና በቀላል መንገድ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርቶች በቂ ምህዳር መኖር አለመኖሩ” ሁሉንም የህዝብ ግንኙት ስራዎች ሁሉ አፈር ድሜ አብልተውታል፡፡ ሌሎችስ በጣም አስመሳይ የሆኑ የባለስልጣን መስፈርቶች እንዴት ይታያሉ? እንዲሁ ዝም ብሎ የባህላዊ ጭፈራ እና ዳንስ ነውን?
በማንኛውም ትክክለኛ በሆነ መለኪያ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የEITI አባልነት ተቀባይነት ማግኘት የድርጅቱ መስፈርቶች ባዶ እና ወና መሆናቸውን ያመላክታል፡፡ EITI የእራሱን ቡድን ለመቀላቀል “አንድ መንግስት የድርጅቱ አባል ሲሆን ምን መስራት እንዳለበት እምነቱን የሚገልጽ እና EITIን ለማጠናከር ያለውን ጽኑ የሆነ መግለጫ አዘጋጅቶ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡” እውነት! ትልቅ ነገር! በመቀጠልም መንግስት “የEITIን ተግባራት ለማከናወን ሃላፊነት ያለው ከፍተኛ ባለስልጣን መሾም አለበት፡፡” እርግጥ ነው ሙሰኛ አሻንጉሊት የድርጅቱን ተግባራት መከናወናቸውን የሚከታተል ሌላ ሙሰኛ አሻንጉሊት ይሾማል፡፡ መንግስት “ከሲቪል ማህበረሰቡ ጋር መስራት ይጠበቅበታል፡፡” የትኛው ሲቪል ማህበረሰብ? ምንም ችግር የለም፡፡ ሙሰኛ ዘራፊዎች በሀገሮቻቸው ውስጥ እውነተኛ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ስለሚያጠፏቸው እነዚህ ዘራፊዎች ለእነርሱ የሚበጁትን የይስሙላ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መቀፍቀፍ እንዲችሉ የፈቃድ ሰርቲፊኬቱን EITI ይሰጣቸዋል፡፡ ለዚህም ነው በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የ “ኢትዮጵያ ብሄራዊ የጋዜጠኞች ህብረት” የሚል ሆድአደር ተለጣፊ ድርጅት በመፍጠር ሌሎችን እያሳደደ በማጥፋት ላይ ያለው፡፡ እንዲህ ያለ ቀልድ!
ከመሀል አዲስ አበባ ወጣ ብሎ የሚገኘው የአቶ መለስ የቃሊቲው የእስረኞች የማጎሪያ ማዕከል እውነተኛ ለፍትህ እና ለሀቅ የቆሙ ዕውቅናን ያተረፉ ጋዜጠኞች እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድ እና ላቅ ያለ ደረጃ ያላቸውን ዓለም አቀፍ ሽልማቶች እየተቀበሉ የሚገኙት በርካታ ጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ የመሳሰሉትን ጀግና ጋዜጠኞች ውጦ የምጻት ቀኑን የሚጠባበቅ የሰላማዊ ዜጎች የማሰቃያ ተቋም ነው፡፡ እስክንድር ነጋ በቅርቡ በህይወት በተለዩት በአቶ መለስ ዜናዊ ላይ ትችት በማቅረቡ እና በአረቡ ዓለም እየተካሄደ ባለው የጸደይ አብዮትን በማስመልከት በሰጠው ትንታኔ ብቻ ለ18 ዓመታት በእስር ቤት እንዲማቅቅ ያለምንም ሀፍረት ተበይኖበታል፡፡ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ በየሳምንቱ በሚወጣ መጽሄት ላይ ሀሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ እያንዳንዳቸው በ14 ዓመታት እስር እንዲቀጡ በማንአለብኝነት በይስሙላው/የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ህሊናየለሽ ውሳኔ ተበይኖባቸዋል፡፡
ከተለጣፊው “ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የጋዜጠኞች ህብረት” ስለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ የተጠያቂነት እና ግልጸኝነት ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት መጠበቅ ማለት የዶሮዎችን መጠለያ ቤት እንዲጠብቅ ኃላፊነት ከሚሰጠው ቀበሮ አንድም ዶሮ ላለመጥፋቱ ትክክለኛ የሂሳብ ሪፖርት እንዲያቀርብ መጠየቅ እንደማለት ነው፡፡ በEITI ገዥ አካሎች መሰረታዊ ሀሳብ መሰረት ህብረተሰቡን ያለምንም ተጽዕኖ የበላይ ተመልካችነት እና የተቆጣጣሪነት ስልጣን በመስጠት በቀጥታ ተሳታፊ በማድረግ በማዕድን እና በተፈጥሮ ጋዝ ዘርፉ ላይ ትክክለኛ እና በዘርፉ ሊረጋገጥ የሚችል መረጃን አዘጋጅቶ የማውጣት ስራን በማቀላጠፍ ሂደቱን የማሳለጥ ተግባራትን የማከናወን ስራ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ የመጨረሻው ግቡ ደግሞ “ከተፈጥሮ ሀብት ተፈብርኮ የሚገኘው የምርት ገቢ በትክክል ያለምንም ሙስና ለህዝቡ ጥቅም እንዲውል መራጋገጫ የሚሰጥ ነው፡፡”
መረጃን በተመለከተ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል አስቀያሚ የመረጃ መቀቀያ ቶፋ አለው፡፡ “የአቶ መለስ ዜናዊ ምዕናባዊ የምጣኔ ሀብት“ እና “የአቶ መለስ ዜናዊ የውሸት የምጣኔ ሀብት” በሚሉ ርዕሶች ሳቀርብ እንደነበረ ሁሉ የአቶ መለስ ዜናዊ አገዛዝ በእርሳቸው አመራር ኢትዮጵያ አስር ዓመት  ሙሉ ያለምንም ማቋረጥ “ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ መጣኔ ዕድገት አስመዘገበች” በማለት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ብቻ የውሸት መረጃ በመረጃ መቀቀያው ቶፋ እየታጨቀ የሀሰት መረጃ ሲሰራጭ ቆይቷል፡፡ እውነታው ግን ላም አለኝ በሰማይ ነው፡፡ ብዙሀኑ የኢትዮጵያ ህዝብ አይደለም በቀን ሶስት ጊዜ አንድ ጊዜ እንኳን ለመብላት እየተቸገረ ነው ያለው፡፡
በጣም የሚያስደንቀው ነገር ደግሞ አቶ መለስ በብልጣብልጥነት የእራሳቸውን የቅጥፍና የኢኮኖሚ የዕድገት መረጃ አሀዝ ለዓለም ባንክ እና ለዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የመመገባቸው ጉዳይ ይህንንም ተከትሎ እነዚህ ዓለም አቀፍ ተቋማት የእርሳቸውን ጥሩንባ የመንፋታቸው ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከማንም በተሻለ መልክ ግንዛቤው ያላቸው ቢሆንም የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ታላቅ እና ድፍረት የተሞላበት የውሸት የኢኮኖሚ ዘገባ በማቅረብ ወንጀለኛ ገዥ አካላት ዕኩይ ድርጊታቸው የሀሰት ዘገባዎችን እንዲያቀርቡ እየገዟቸው ይገኛሉ፡፡
በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል  በEITI የቀሚስ ጉንፍ ውስጥ ተወሽቆ በማዕድኑ ምርት እና ገቢ ሁሉምን ዓይነት የሀሰት የመረጃ አሀዞችን በመቀፍቀፍ እንዲሁም በሚሊዮኖች የሚቆጠር አንጡራ የሀገሪቱን ሀብት ወደ ውጭ በማሸሽ ውጭ አገር በሚገኙ የግል የባንክ ሂሳቦቻቸው ላይ በማስቀመጥ ላይ እንደሆኑ እና እንደዚህ ያሉ ተመሳሳይ የማታለል ድርጊቶችን በመፈጸም ላይ እንደሚገኙ የክርክር ጭብጤን ላቀርብ እችላለሁ፡፡ ወደፊት “በEITI ጋሻጃግሬነት እየተካሄደ ያለ የኢትዮጵያ የማዕድን ሙስና ተምኔታዊ የመረጃ አሃዞች” በሚል ርዕስ ስር ትችት አቀርባለሁ የሚል ዕቅድ አለኝ፡፡
EITI  ጥሩ የሚመስሉ መስፈርቶችን በማቅረብ ሆኖም ግን በአፍሪካ እና በሌሎች ታዳጊ አገሮች ለሚካሄዱት የአምራች ኢንዱስትሪዎች ሙስና የህጋዊነት ሽፋን በመስጠት የህጋዊነት ሀሳባዊነትን፣ ታማኝነትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ EITI “የድብቅ ቴክኖሎጅን” የሚጠቀም በመሆኑ በአፍሪካ እና በሌላው ዓለም ያሉ በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት ያለምንም ስጋት እና ጥርጣሬ የህዝቦቻቸውን ሀብቶች ለመዝረፍ ሲሉ ተቋሙን መቀላቀል ይፈልጉታል፡፡ EITI እምነት ከማይጣልባቸው፣ በሙስና ከተዘፈቁ እና አስጸያፊ ባህሪያትን የተላበሱ፣ እንዲሁም ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በዓለም መድረክ ላይ በመጀመሪያ እምነቱን በማግኘት በኋላ የሚከዳበት ዓይነት ጨዋታ ከሚደረግባቸው ድርጅቶች መካከል አንደኛው ነው ማለት ይቻላል፡፡
ሁለት ጊዜ ይቅርታ መጠየቅ እና አንዱን በጽናት መያዝ፣
“የማዕድን ሙስና በኢትዮጵያ፡ ለማዳም ክላሬ የተሰጠ መልስ” በሚለው የመጀመሪያው ትችቴ ላይ ማዳም ክላሬ የኢትዮጵያን የEITI አባል መሆን አስመልክቶ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ከጉዳዩ ውጭ እንዲሆኑ ስላደረጓቸው አሰልች ቀኖናዊ ህጎች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ይቅርታ እንዲያቀርቡ ሀሳብ አቅርቤ ነበር፡፡ ማዳሟ “የቦርድ አባላቱ የኢትዮጵያን የተባበረ የሲቪል ማህበረሰብ ድምጽ እንጅ የተቃዋሚ ዲያስፖራ ድምጾችን መስማት እንደሌለበት ተማጽዕኖ አቅርበው ነበር፡፡” ውጤታማ በሆነ መልኩም የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ድምጽ መዘጋት  እንዳለበት ሞግተዋል፡፡
“ግልጽ እና የተባበረው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ” የማዳም ሾርት ፍጹም የሆነ ምዕናባዊ የሆነ እና የተረጋጋ ስሜት እንዳይኖር በማድረግ ዓላማ ላይ የሚሽከረከር ሆኖ ይገኛል፡፡ ትክክለኞቹ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከዓመታት በፊት ጀምሮ ታፍነው ተሸብበው  ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን ማዳም ሾርት በአንድ ወይም በሌላ ምክንያት በኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ የሌለውን አለ የሚል ቅዠት ለማንበር ይፈልጋሉ፡፡ ምናልባትም የእርሳቸው የስሜት ጓደኛ እንደሆኑት እንደ አቶ መለስ ዜናዊ የመኝታ ጊዜ ትረካዎችን መናገር መውደድ አለባቸው፡፡ እኔ በትረካዎች ላይ በእርግጠኝነት ትዕግስት ማድረግን እከተላለሁ፣ እንደ ዶ/ር ሰውስ ተረት:- “ ተረት ተረት የላም በረት: አንድ ዓሳ፡፡ ሁለት ዓሳዎች፡፡ ቀይ ዓሳ፡፡ ሰማያዊ ዓሳ፡፡” ተረት ተረት አንድ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፡፡ ሁለት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፡፡ ሰማያዊ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፡፡
በእርግጠኝነት ለተቀደሰ ተግባር፣ የተከበረ እና ሩህሩህነት የተንጸባረቀበት ሀሳብ ሲባል ማዳም ሾርት ለዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን/ት የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባት ይኖርባቸዋል የሚል ተስፋ ነበረኝ፡፡ ምናልባትም “ከተናገርኩት ውጭ የስህተት ግንዛቤ ተይዟል ይቅርታ” ሊሉ ይችሉ ይሆናል፡፡ እንደ ቆንጆ የህዝብ ግንኙነት ስራ በእርግጠኝነት ላይሉም ይችላሉ፡፡ ማዳም በእርሳቸው የተዛባ ጥላቻ  ሰበብ የጥቃት ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ይቅርታ ለመጠየቅ ለጋስነቱ ያላቸው አይመስልም፡፡ የዘመኑን የወጣቶችን ንግግር ለመጠቀም ማዳም ሾርት ሰዎችን በመበጥበጥ ከዘራፊዎች ድንበር ተርታ ጋር የሚያመሳስል የረዥም ጊዜ እውቅና አላቸው፡፡ ማዳም ሾርት በብርሀን ፍጥነት ተናዳጅነታቸው እና ግንፍልተኝነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ሪቻርድ ዶውደን የተባለው የእንግሊዝ ታዋቂ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ በ2011 ከማዳም ሾርት ትረካውን እንዲህ አቅርቦታል፡፡ “በአንድ ወቅት በአውሮፕላን ላይ ቃለ መጠይቅ እያደረግሁላቸው ሳለ እና ስለሩዋንዳ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ትኩረት በመስጠት ጥያቄዬን ሳቀርብ ማዳሟ እኔን ለመወርወር በሚያስችል ዓይነት ሁኔታ አስፈራሩኝ፡፡ በዚያን ወቅት በጊኒ የአየር ክልል ላይ ስለነበርን ከዚያ በኋላ አቆምኩ፡፡ አሁን ደግሞ የተዋበ፣ ሰላም እና መረጋጋት በሰፈነበት በለንደን የጋራ ሀብት ክለብ ተገናኘን፣ እናም ማዳሟ እርጋታ የሚታይባቸው እና ሀሳብ የሚሰጡ ሆኖም ግን በማንም ዘንድ ጠንካራ ትችት የሚያቀርቡ የሚያደርጉትንም በብልኃት መያዝ የማይችሉ ሆነው ነው ያገኘኋቸው፡፡“ ማዳም ሾርት ቀልድ አያውቁም! ቶኒ ብሌር ሃሰባቸውን እንዳይገልጹ ለማድረግ በሀይል አፋቸውን ያስይዟቸው ነበር፡፡ (ብሌር የተናገሩት አያስደነቅም:- ”እንደተዋረደች እና ሀሳቧን እንዳትገልጽ በኃይል እንደተያዘች ሚስት ነው የተሰማኝ፡፡” ያሉት ሲያመናጭቁአቸው:: ይህ አካሄድ የማዳም ሾርት አጭሩ ጎዳና ነው! ቢሆንም ለማዳሟ ክብር እሰጣቸዋለሁ፡፡ ለሚያምኑት ይቆማሉ: ይዋጋሉ:: በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት ገዥ ዘራፊዎች በጽናት ይቅርታ የሚያቀርቡ ሴት ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን ይቅርታ መጠየቅ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን ማዳም ሾርት በድርጅታቸው ያሉትን የሰቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካዮችን ማለትም ዓሊ ኢድሪሳን፣ ንዋዲሺን ጂን ክላውዲ ካቴንዴን እና ሌሎችን የከፈለህን አትም አባላት ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ ይህንን በጥብቅ እጠይቃለሁ! ማዳሟ “በግልጽ ደብዳቢያቸው” ፍትህዊነትን በጣሰ መልኩ አስደናቂ ተዋንያን በመሆን በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ አምባርቀውባቸዋል፡፡ “የተለየ ፍላጎት ያላቸው ቡድኖች ጠንካራ ድምጾችን በማሰማት ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚደረግ ጥረት እንዳለ እና እንዲያውም የሰሜን ደቡቡን እንዲወስንለት በታቀደ ዘይቤ የሚመሩ ናቸው በማለት ክስ አቅርበውባቸዋል፡፡” የኢትዮጵያ ገዥው አካል የEITI አባል እንዳይሆን ተቀዋሚዎች ተቃውሞ በማሰማት የEITIን ዕድል ተፈታትነዋል በማለት ማዳሟ ጩኸታቸውን አሰምተዋል፡፡
ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴን በማክበር ለማዳም ሾርት ግልጽ ደብዳቤ ግልጽ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ እንዲህም ብለዋል፣ “የኢትዮጵያ የEITI የአባልነት ጥያቄ በቀጣናው ስብሰባ እዲቀርብ በአጀንዳችን ውስጥ አልነበረም በእርግጥ ይህ ጉዳይ የከባቢ ሁኔታ ግምገማዎችን እያደረግን ባለንበት ሁኔታ ነው የመጣው፡፡“ በወቅቱ ሁለት ገዥ ሀሳቦች ተነስተው አንደኛው በመቃወም ሁለተኛው ደግሞ በመደገፍ ክርክር እንደነበር ገልጸዋል፡፡ “ገለልተኛ” በሆነ መልኩ ማዳሟን እንዲህ በማለት ሞግተዋል፣ “ኢትዮጵያ የEITI አባል እንድትሆን ግልጽ አቋም በመያዝ  ወገንተኝነት አሳይተዋል፣ ከገለልተኝነት መርህ ጋር በተጻረረ መልኩ በድርጅቱ ሊቀመንበርነትዎ ላይ ጥያቄ ሊያስነሳ የሚችል ድርጊትን ፈጽመዋል፡፡ የድርጅቱ ታማኝ የመሆን ጠቀሜታ መሰረት የሚለካው በዚህ ጠቃሚ መርህ ነው፡፡” በዚህ አስፈሪ ግልጽ ደብዳቤ እንቆቅልሽ የሆነባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ “በዚህ ጉዳይ ላይ ግልጹ ደብዳቤ ለተውሰኑ ጥቂት ሰዎች ማሳወቅ ሲገባ ለምን ለህዝብ ይፋ እንደተደረገ ግልጽ አለመሆኑን ለመጠቆም እንፈልጋለን… እንደዚሁም የእኛም ደብዳቤ እርስዎ ለህዝብ ለአደባባይ እንዳቀረቡት ሁሉ በEITI ድረ ገጽ ላይ እንዲታተም እንጠይቃለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች ዓለም አቀፍ ድረ ገጽ ለጥምረት አባሎቻችን በሙሉ ሊለቀቅ ይገባል፡፡“ የሚል ነው፡፡
ማዳም ሾርት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ በቀጥታ ሳይሆን በጸሐፊያቸው በጆናስ ሞበርግ በኩል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የተሰጠው መልስ በቁስል ላይ ጨው  መነስነስ ያህል ነበር፡፡ ማዳሟ በግልጽ ደብዳቢያቸው ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ደብዳቤ መጻፉ ችግር እንደሌለባቸው በመጮህ የተናገሩ ሲሆን ቀደም ሲል የዓለም ማህበረሰብ ከማወቁ በፊት መደረግ እንደነበረበት ተናግረዋል፣ ሆኖም ግን በኋላ ደፍረው ሲመልሱ አንዴት ተደርጎ!? በተለመደው ቦታቸው አርፈው እንዲቀመጡ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሞበርግ ይህንን ቆሻሻ ስራ የተሰጠው ሰው ነው፡፡ እኔ በግሌ የሚከተለውን ሳነብ እንደተዋረድኩ እቆጥረዋለሁ፣
“ማዳም ክላሬ ለእናንተ ደብዳቤ ምላሽ እንድጽፍ ጠይቀውኛል፡፡ ያቀረባችኋቸው ነጥቦች በሙሉ ማስታወሻ ተይዞባቸዋል፣ የሊቀመንበሯን ገለልተኛነት ተብሎ ከሚጠራው ነጥብ በስተቀር፡፡ ለጂን ክላውዴ እንደገለጽኩት ሁሉ ሊቀመንበሯ ገለልተኛ እንዲሆኑ አይጠበቅባቸውም፡፡ እንደማንኛቸውም የእኛ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች ሁሉ ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸው አይነት በመሆን ሊሰሩ አይችሉም፡፡ ሊቀመንበሯ EITIን ነው የሚያገለግሉት ምክንያቱም በድርጅቱ መርሆዎች ላይ እምነት ስላላቸው ነው፡፡ እነዚህን መርሆዎች የመጠበቅ ኃላፊነት እና የEITIን ጥቅም ማስጠበቅ አለባቸው፣ እናም ለእናንተ ደብዳቤ በጻፉበት ወቅት ያደረጉት ነገር ቢኖር ይህንኑ ነው፡፡ በደብዳቢያቸው ላይ የሊቀመንበሯን ሚና የሚጥስ ነገር አልታየም፡፡”
ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ከክብርትነታቸው በቀጥታ የሚጻፍ ደብዳቤ እንደክብርቷ አመለካከት ከሆነ አይመጥናቸውም፡፡ በሌላ አገላለጽ የማዳሟን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ነገር ነው፡፡የሞበርግን ደብዳቤ በድጋሜ ሳነበው በጫካ እንደሚኖረው ባለረዥም ጅራት ቆርጣሚ አውሬ በንዴት ብግን ነው ያልኩት፡፡ ማዳም ሾርት ምን ያህል ደፋር መሆናቸውን የሚያሳየው በጸሐፊው አማካይነት ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ስናስተውል ነው! ማንም ጭራቃዊነት የሰራው እርሳቸው አይደሉምን?! በፍጹም የማለት ሞገስ ሊኖራቸው አይችልምን! ቀላሉ ዘዴ በጸሐፊያቸው አማካይነት የማርቀቅ እና እርሳቸው ፈርመው መላክ ነው፡፡ በግልጽ ለመናገር ማዳም ሾርት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ግልጽ መልዕክት ማስተላለፍ ፈልገዋል፡፡ ማን አለቃ እንደሆነ እና አጠቃላይ ሁኔታውን ለማሳወቅ ፈልገዋል፡፡ እርሳቸው አለቃ ናቸው፣ ስለሆነም ስለማንኛውም ነገር ደንታ የላቸውም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ማዳም ሾርት ስለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ስለካቴንዴ ጉዳይ ደንታ የላቸውም!
ስለሰው ልጅ ስብዕና፣ ክብር እና ሞገስ ስል በኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ስም እኔ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ተገናኝቸ ወይም ደግሞ ተነጋግሬ አላውቅም፡፡ ሆኖም ግን እንደ አንድ አፍሪካዊ ወገኖቼ የእነርሱ ውርደት የእኔም ውርደት እንደሆነ እንዲገነዘቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡ በእንደዚያ ዓይነት አያያዝ ሲስተናገዱ ስመለከት እንደ አፍሪካዊ የእኔ ኩራት ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ሆኖም ግን እንዲያውቁልኝ የምፈልገው ነገር ቢኖር ጠንካራ ኩራት እና ኃይል ይሰማኛል፡፡ ለማዳም ሾርት አስደንጋጭ ግልጽ ድብዳቤ የሰጡት ምላሽ የአስተዋይነት፣ የምክንያታዊነት እና የተለምዷዊ በጎ ምግባር ተምሳሌት ነበር፡፡ እነዚህ አፍሪካውያኑ በምላሻቸው ላይ ቁጥብነትን፣ ባለሞያነትን፣ታጋሽነትን እና ታማኝነትን አሳይተዋል፡፡ እንደዚሁም ደግሞ “አፍሪካዊ ትውልዶቻቸው እሺ! አቤት ወዴት! እርስዎ እንዳሉት ጌታዬ!” እያሉ ስብዕናቸውን ዝቅ ማድረግ በፍጹም እንደሌለባቸው በተጨባጭ አሳይተዋል፡፡ ማዳም ሾርት እና መሰሎቻቸው አዲሱ የአፍሪካ ትውልድ ለማንም ሎሌ እንደማይሆን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሰውን ባለቃነቱ ብቻ “አዎ አዳኙ ጌታዬ” የሚባለው ተረት ተረት ጊዜው ያለፈበት እና ያፈጀበት ዘመን ላይ ነን፡፡ ሁላችንም አፍሪካውያን በጀግኖቹ ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ልንኮራ ይገባል፣ ምክንያቱም ክብርን በደፈጠጠ እና ባዋረደ ጭራቃዊ መንፈስ ላይ የብዕር ጦራቸውን በመስበቅ ክብር እና ሞገስን እንድንቀዳጅ አስችለውናል፡፡ በከፍተኛ ደረጃ የፈጸሙት ተግባር ነው፡፡ ይሄ ነው ጀግኖች! እናደንቃችኋለን ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ፡፡
በተጨማሪም ማዳም ሾርት በተደጋጋሚ በተናገሩት አቁሳይ እና ከስልጣን ገደባቸው ውጭ በመሄድ ላሳዩት ትዕቢት በተቀላቀለበት ድንፋታ ስሜታቸው እንዳይጎዳ መጽናናትን እንዲያደርጉ እማጸናለሁ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ማዳም ሾርት በቅርቡ በህይወት የተለዩት የአቶ መለስ ዜናዊ አምላኪ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በኤፕሪል 2013 ማዳም ሾርት በአንድ የመታሰቢያ በዓል ላይ በመገኘት አቶ መለስ “ታላቁ” ሰው በማለት አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡  እንዲህም ብለዋል፣ “አቶ መለስ በህይወት ዘመኔ ካየኋቸው ሁሉ የመጠቀ እውቀት ያላቸው ፖለቲከኛ ናቸው” በማለት አሞካሽተዋቸዋል፡፡ (ቶኒ ብሌር፣ ጎርደን ብራውን፣ ሃሬት ሃርማን፣ ኢድ ሚሊባንድ፣ ዴቪድ ካሜሩን፣ ጆህን ሜጀር፣ ታቼርን ቅርጫት ደፉባቸው፡፡ ማዳም ሾርት ደስ ያላልዎትን የሚያስጨንቀዎን ነገር መግለጽ ይችላሉ!) እኔ በበኩሌ “አቶ መለስ ሁሉን ነገር አዋቂ” መሆናቸውን አላውቅም፣ ይልቁንም አነጣጥሮ ገዳይ እና አስገዳይ ተራ እርባናቢስ ለሰው ክብር የሌላቸው ዉዳቂ የነበሩ ለመሆናቸው ቅንጣት ያህል ጥርጣሬ የለኝም፡፡ እስቲ አካባቢያችሁን ተመልከቱ፣ ሁሉም ጭራቸውን ይቆላሉ፡፡
አቶ መለስ እንደ ማዳም ሾርት ሁሉ እርሳቸውን የተቃወሟቸውን ወይም በእርሳቸው ላይ ትችት ያቀረቡትን ሁሉ “ድራሻቸውን የሚያጠፉ” በእብሪት የተሞሉ ሰው ነበሩ፡፡ የእርሳቸውን ተቀናቃኞች በተደጋጋሚ “ደደቦች”፣ “ቆሻሾች”፣ “የጭቃ ጅራፎች”፣ “ስግብግቦች” እና “ለምንም የማይጠቅሙ እርባና ቢሶች” በማለት ይፈርጇቸው ነበር፡፡ እንደዚሁም በሰለጠነ ህብረተሰብ አጠራር መሰረት ደግሞ ለመጥራት ጸያፍ የሆኑ ስሞችን ይለጥፉ ነበር፡፡ አቶ መለስ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ሊቀመንበር የነበሩትን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን ወደ እስር ቤት ወርውረው ለብቻ በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲታሰሩ ካደረጉ በኋላ እንቅስቃሴ ባለማድረጓ ምክንያት የመወፈር ነገር ይታይባታል የሚል ምጸት አሰምተዋል፡፡ አቶ መለስ በፓርላሜንት ጉባኤ ላይ የሚገዳደሩ ጥያቄዎችን በማንሳት ወይም ሌላ ለየት ያለ አካሄድ እንዳለ ለማሳየት ሀሳብ የሚያቀርቡ ተወካዮችን በማዋረድ እና በመዘለፍ በሚፈጽሟቸው ጭራቃዊ ድርጊቶቻቸው ይደሰቱ እና እርካታን ያገኙ ነበር፡፡ የእርሳቸው ሰውን አሳንሶ የመመልከት፣ ምጸታዊ ንግግር፣ እና ለሚጠየቋቸው ጥያቄዎች የሚሰጧቸው ንቀት የተሞሉባቸው መልሶች በጣም አዋራጅ እና የተጠየቁ ጠቃሚ ነገሮችን ነቅሰው በማውጣ መልስ እንዳያገኙ የመዝለል ሁኔታዎች አንዳንድ ድፍረት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ተወካዮች በድፍረት ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች የሚሰጧቸው ምላሾች እና የመድረክ ተውኔቶች ነበሩ፡፡ እ.ኤ.አ በሜይ 2010 የተደረገውን ሀገር አቀፍ ምርጫ 99.6 በመቶ የተገኘው የድምጽ ውጤት በመጭበረበሩ ምክንያት የተገኘ መሆኑን የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን አቶ መለስን ከእውነታው ጋር አፋጥጠው ሲይዟቸው አቶ መለስ የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድንን ዘገባ “ወደ ቅርጫት መጣል ያለበት ቆሻሻ ነው” በማለት በጅምላ አውግዘዋቸዋል፡፡ ምን ማለት እችላለሁ?  እራስን በአምላክነት ሰይሞ ተከታይ እንዲኖር መፈለግ!
ማዳም ሾርት EITI መርሆዎች እሰከብረዋል ወይስ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ተሟጋች/ወኪል ነበሩ?
ማዳም ሾርት በሞበርግ አማካይነት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ በሰጡት ምላሽ ለኢትዮጵያ ወገንተኛ ያልነበሩ ብቻ ሳይሆን የEITIን መርሆዎች ለማስጠበቅ እና ለEITI ጥቅም ተግተው በመስራት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ የሚገልጽ ነበር፡፡ እርግጠኛ ነዎትን?
ማዳም ሾርት “የEITIን መርሆዎች አስጠብቀው” ነበር ወይስ ደግሞ በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል ወግነው ነው ይህን የሚከተለውን ግልጽ ደብዳቤ የጻፉት የሚለውን ማየት ለግንዛቤ የበለጠ ይረዳል፡፡
በኢትዮጵያ ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ሁኔታ ከሌሎች በርካታ አገሮች የከፋ ነው የሚለውን አልቀበለውም፡፡
በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ያለው ውይይት ጠቀሜታ በሌለው መንገድ የተለየ ፍላጎት ባላቸው እና ሙሉ ትርጉም ባለው “የሰሜኖች ለደቡቦች መናገር አለባቸው በሚለው የአሰራር ዘየ” በተገመደ ጠንካራ ድምጽ ተጽዕኖ ስር የወደቀ በመሆኑ ላይ መናገር አለብኝ፡፡
የአትዮጵያን የአባልነት ጥያቄ ውድቅ ማድረግ ማለት የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ የትም እንዳይሄዱ ማድረግ ማለት ነው፡፡
ከኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማህበረሰብ ተቃውሞዎችን ከመስማት ይልቅ በኢትዮጵያ ግልጽ እና የተባበሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ድምጽ መስማት ያለብን በመሆኑ ላይ ያለኝን እምነት መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡
በጥሩ ሁኔታ መስራት የሚችሉ በጣም ጠንካራ የሆኑ ሌሎችን የአፍሪካ አገሮች ሊቀላቀሉ የሚችሉ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች እንዳሉ ከሀሳባዊነት በራቀ መልኩ ምንም ዓይነት ጥርጥር የለኝም
አንድ ዓይነት ወጥነት የሌላቸው መስፈርቶች መኖርም ሌላው ታላቅ ችግር ነው፡፡ ለምሳሌ በሀገሬ የቅዱስ ፓውሎስ ካቴድራል ውጫዊ ክፍልን በኃይል የተቆጣጠሩትን ተቃዋሚዎች ማባረረን አስመልክቶ የሚነገር ጉምጉምታ አለ፡፡ የጓንታናሞ መኖር እና ማሰቃየትን የመተግበር ሁኔታ አስመልክቶ ዩናይትድ ስቴትስ ጉዳይ ለአባልነት ጥያቄ ሲቀርብ አልተነሳም፡፡
EITI የዘመቻ አድራጊዎች መሳሪያ ተደርጎ የሚታይ ከሆነ ውጤታማ እና ድጋፍ የሚኖረው ሊሆን አይችልም፡፡
ጎራዴው ለምን ማጥቂያነት ይውላል?
ማደም ሾርት ገዠው አካል የEITI አባል መሆን እንዲችል ጉሮሮ ለጉሮሮ በመተናነቅ ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡ በግልጽ ድብዳቢያቸው በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል አባል እንዲሆን ሽንጣቸውን ገትረው የውትወታ ተግባራቸውን አከናውነዋል፡፡ ማንም ሽንጡን ገትሮ ላመነበት ጉዳይ ትጋድሎ የሚያደርግን ሰው በሀሳብ የማንግባባ ቢሆንም እንኳን አከብራለሁ፡፡ ማዳም ሾርትም ላመኑበት ጉዳይ በጽናት መቆማቸውን አደንቃለሁ፡፡ ሆኖም ግን እደነቃለሁ፣ በእርግጥም በጣም እደነቃለሁ! ማዳሟ ላደረጉት የጽናት ተጋድሎ ዋጋቸው ምን ሊሆን ይችል ይሆን? በኢትዮጵያ ላሉ ዘራፊዎች ማዳም ሾርት ያደረጉት ተጋድሎ ዋጋ ምን ያህል ይሆን? የማዳም ነብስ ዋጋው ምን ያህል ይሆን?
በእርግጠኘነት ስለEITI ከልብ የሚቆረቆረው ማን ነው?
EITI፣ CCC፣ EEITI  ማንም ይሁን! ማን ነው ያገባኛል የሚለው? ማን ነው ትኩረት አድርጎ የሚይዘው!? አሳማን ሊፒስቲክ መቀባት ይቻላል፣ ሆኖም ግን አሁንም ያው አሳማ ነው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ሁሉንም የአፍሪካ ዘራፊ አምባገነኖች የEITI አባል ማድረግ ይቻላል፣ እናም ግልጸኝነት እና ተጠያቂነት ብሎ መጥራት ይቻላል፡፡ በቀኑ መጫረሻም ያው አንድ ዓይነት ዩኒፎርም የተሰፋላቸው የዝርፊያ ቦርሳዎችን ይዘው የሚዞሩ ዘራፊ አምባገነኖች ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ መሰቃየት፣ ኃይልን መጠቀም እና ጭካኔ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመቀጠል ላይ ይገኛል፣
ማዳም ሾርት ለአንድ አፍታ እንዲህ በማለት አሰቡ፣ ”እኔ እንደማስበው መሰቃየቱ፣ በኃይል መጠቀም እና ጭካኔ የተሞላበት ሁኔታዎች በጓንታናሞ እስር ቤት እና በኢራቅ ላይ ቀጥለዋል፡፡“ ደህና፣ እንዲሁም ለኢትዮጵያ በተመሳሳይ መልኩ አስባለሁ፡፡ በኢትዮጵያ የሚደረገው ማሰቃየት፣ የኃይል እርምጃ እና ጭካኔ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀጠለ ነው፡፡ ጋዜጠኞች ይታሰራሉ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይዘጋሉ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት መሪዎች እንዲሸማቀቁ እና በፍርሀት ቆፈን እንዲጠመዱ እና እንዲታሰሩ ይደረጋሉ፣ ሰላማዊ አመጸኞች በኃይል እንዲጨፈለቁ ይደረጋሉ፣ እንዲሁም ምርጫዎች በጠራራ ጸሐይ ይጭበረበራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ግን ሰላማዊ የሽግግር ለውጡን ሊያቆመው አይችልም፡፡ ያ ሁኔታ ይቀጥላል፣ ይቀጥላል… የኢትዮጵያ ወጣት ሴቶች እና ወንዶች ይነሳሉ እናም ለነጻነታቸው እንዲህ በማለት ይጮሃሉ፣
“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ተርበናል! ነጻነት እንፈልጋለን! ነጻነት እንፈልጋለን! እስክንድር ይፈታ! አንዷለም ይፈታ! አቡባከር ይፈታ! ርዕዮት ትፈታ! የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ይፈቱ! ፍትህ እንፈልጋለን! ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! አትከፋፍሉን! ኢትዮጵያ አንድ ነች! አንድ ኢትዮጵያ! ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ውኃ ናፈቀን! መብራት ናፈቀን! ተርበናል!…“
በጓንታናሞ እና በኢራቅ ውስጥ የሚካሄዱትን ስቃዮች፣ የኃይል እርምጃዎች እና ጭካኔዎች በሚመለከት ማዳም ሾርት የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶችን ተጠያቂዎች እንዳደረጓቸው ሁሉ እኔ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጠቅላላ ከጠፉ በኋላ ማዳም ሾርትን ተጠያቂ አደርጋለሁ፡፡
ማዳም ክላሬ ሾርት፣ “ተከሰዋል…!”
“እውነትን በዘጉ ጊዜ እና ከመሬትውስጥበቀበሯትቁጥር ድርጊቱን ማድረግ ይቻላል፣ ሆኖም ግን እውነት እያደገች፣ እየጠነከረች ትሄዳለች፣ እናም በአንድ ላይ ተሰባስባ የሚፈነዳ ኃይል ትፍጥራለች፣ በምትፈነዳበት ዕለት ሁሉም ነገር እራሷ በቀየሰችው መንገድ ይፈነዳል፡፡“ ኢሚሌ ዞላ
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
መጋቢት 16 ቀን 2006 ዓ.ም