Thursday, October 24, 2013

በሁለት የቀድሞ የህወሀት ባለስልጣናት ቤቶች በርካታ የጦር መሳሪያዎች መገኘታቸውን አቃቢ ህግ ገለጸ

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ህግ አንድ ግለሰብ ከመንግስት በማስፈቀድ አንድ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እንዲይዝ ቢፈቀደልትም ፣ በተግባር ግን አብዛኛው ህዝብ በመሳሪያ አሰሳ ስም የግል መሳሪያውን መቀማቱን በተለያዩ የመገናኛ ብሀን ሲዘገብ ቆይቷል።

በ1997 ምርጫ ወቅት የአንድ ብሄር አባላት በገዢው ፓርቲ ህወሀት  ራስን የመጠበቂያ መሳሪያ እንዲታደላቸው መደረጉ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል።

የፌደራል አቃቢ ህግ በቀድሞው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋ/ዳይሬክተር መላኩ ፋንታ መዝገብ ላይ ባቀረበው ክስ፣ በህወሀቱ አባል ምክትል ዳይሬክተሩር አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ መኖሪያ ቤት ውስጥ 2 ታጣፊና ባለእግር ክላሾች፣ 4 ማካሮቭ ሽጉጦች፣ 2 ኮልት ሽጉጦች፣እና አንድ ስታር ሽጉጥ በድምሩ 9 የጦር መሳሪያዎች መገኘቱን ጠቅሷል።በሌላው የህወሀት አባል በ24ኛው ተከሳሽ በቀድሞው የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አማካሪ በነበሩት በአቶ ወልደስላሴ /ሚካኤል ቤት ደግሞ 2 ባለሰደፍና ታጣፊ ጠመንጃዎች፣ አንድ ኡዚ ጠመንጃ፣ አንድ እስታር ሽጉጥ፣ አንድ የጭስ ቦንብ እና የተለያዩ ጥይቶችን ይዞ መገኘቱ ተገልጿል።

ግለሰቡ ከቀድሞው ጠ/ሚ አቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር የጠበቀ ቁርኝት እንዳላቸው  በተቃራኒው ደግሞ ከደህንነት ሚኒስትሩ ከአቶ ጌታቸው አሰፋ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ለእስር መዳረጋቸው በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ሲዘግብ ቆይተዋል።

 በተመሳሳይ ሴና ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ፋንታ ባለትዳር በማማገጥ ወንጀል አቃቢ ህግ ክስ እንደመሰረተባቸው ሰንደቅ ጋዜጣ ዘግባል። ዐቃቤ ህግ  አቶ መላኩ የስራ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ለስራ ጉዳይ የመጣችን ሴት፤ ትዳሯን ፈታና በትዳር ውስጥ ያፈራቻቸውን ሦስት ልጆች በትና አብራቸው እንድትሆን አድርገዋል ሲል ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ብሎአል።  ሰንደቅ አቃቢ ህግን ጠቅሶ እንደዘገበው ” ወ/ሮ መቅደስ ለማ የተባሉት እኚሁ ሴት የቀድሞ ባለቤታቸውን ንብረት የሆነውን ሳንክቸሪ ኢንተርናሽናል ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር በ2001 ዓ.ም የስራ ግብር ለመክፈል ወደገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሲሄዱ 144 ሺህ ብር እንዲከፍሉ በመጠየቃቸውና በዚህም ምክንያት አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ምስራቅ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ለአንድ አመት ከ4 ወር መጉላላታቸውን ለማስረዳትና መፍትሄ ለማግኘት ወ/ሮ መቅደስ ለማ የአቤቱታ ደብዳቤ ይዘው ወደተከሳሹ ዘንድ በቀረቡበት ወቅት የፍቅር ግንኙነት” ጀምረዋል።  ተከሳሽ የነበረውን ስልጣን መከታ በማድረግ ባለጉዳዩዋ ቀደም ሲል ከከፈሉት ብር ውስጥ አንድ መቶ ሺህ ብር ተመላሽ እንዲሆን አድርጓል፤ በትዳር ውስጥ ያለችን ሴትም አማግጧል ሲል አቃቢ ህግ ክስ አሰምቷል።

ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ “በጋብቻ ውስጥ ያለችን ሴት በመንግስት ተሽከርካሪና ነዳጅ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ክብረ በዓል ላይ እንድትገኝ ከማድረጉም በላይ ቀኑ በውል ባልታወቀበት ዕለትም፤ በጋብቻ ውስጥ የነበረችው መቅደስ ለማን በግል ሾፌሩ አማካኝነት ወደ ባህርዳር ከተማ እንድትሄድ በማድረግ ሰመርላንድ ሆቴል ለአንድ ሳምንት አብረው እያደሩ እና በሾፌሩ አማካኝነት ከተማ ውስጥ እንድትዝናና ” አድርጋል ብሎአል።

አቃቢ ህግ ባቀረባቸው በርካታ የወንጀል ዝርዝሮች ውስጥ የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲንና በጄኔራል ክንፈ ዳኘው የሚመራው በመከላከያ ውስጥ የሚገኘው የብረታ ብረት ኮርፖሬሽን እቃዎች ያለቀረጥ እንዲገባላቸው ቢደረግም፣ ሌሎች ኩባንያዎች ሲከሰሱ ሁለቱ ድርጅቶች እና የኩባንያው መሪዎች አልተከሰሱም። አቃቢ ህግ እነዚህ ሁለት ግዙፍ ኩባንያዎች በሙስናው ውስጥ እንዳሉበት መረጃ ቢኖረውም ለመክሰስ ለምን ፈቃደኛ እንዳልሆነ አልታወቀም።

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ከማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አንድነት አሳሰበ

October 23/2013

 አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ካለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አሳሰበ። ፓርቲው ከትናንት በስትያ ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ የአንድነትን እንቅስቃሴ ስም ለማጥፋት በመሞከራቸው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፣የሻዕቢያ መልእክት አድራሾች ናቸው ያሉት የራሳችን አጀንዳ እንዳለን ጠፍቷቸው ሳይሆን ሆን ብለውና አቅደው ስም ለማጥፋት እንዲሁም ህዝቡ ውስጥ ጥርጣሬ ለመጫር በመፈለግ ነው ብሏል።

ፓርቲው ተላላኪነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብና ይጠቅማል ብሎ ለቀረፃቸው የፖለቲካ ፕሮግራም ብቻ መሆኑን የገለፁ ሲሆን፤ እንዲህ አይነቱን ስም ማጉደፍም በቸልታ እንደማያልፈው ገልጿል። በተጨማሪም የሙስሊም ወገኖችን ጥያቄ በተመለከተ ፓርቲው በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ይመለስ፣ ዜጎች የመብት ጥያቄ ሲያነሱ መፈረጁ ይቁም እንዲሁም ካለአግባብ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ በማንሳታቸው ወደ እስር ቤት የተወረወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይፈቱ የሚል ጥያቄ ማንገቡን ፓርቲው ገልጿል። በመሆኑም ፓርቲው ከኢፍትሃዊት ጋር እንደማይደራደር እና እንደማይቀበለው አመልክቶ፣ ፓርቲውን ከሙስሊም ወገኖች ጥያቄ ጋር በማያያዝ ትርፍ ፍለጋ መሯሯጥ ወንጀል ነው ብሏል።
 
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሰላማዊ ሰልፍን በተመለከተ የተናገሩት በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን መብት በአደባባይ የጨፈለቀ ነው ብሏል ፓርቲው። ሰላማዊ ሰልፍ ለሚያደርጉ በቂ ጥበቃ የለንም በሚል ተልካሻ ሰበብ የዜጎችን መብት መንጠቅ እንደማይቻል የገለፀው ፓርቲው፤ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስትም ስልጣኑን ለህዝብ በማስረከብ ይቅርታ ጠይቆ መሄድ እንጂ ከአሁን በኋላ መብታችሁን አታገኟትም ብሎ መዛት ትዝብት ላይ ይጥላል ብሏል።
 
ፓርቲው አያይዞም የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው አይ ሲሲ ሊከሰን አይገባም ሳይሆን ማለት ያለባቸው፣ የዜጎቻቸውን እንባ ማበስ እና ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲረጋገጡ መጣር ነው ብሏል። መሪዎች በርካታ መፍትሄ ፈላጊ ችግሮች ባሉባት አፍሪካ ተሰብስበው እንግደል፣ እንሰር፣ እንጨፍጭፍ፣ ዘር እናጥፋ፣ ዜጎቻችንን እናሰቃይ ግን መታሰርም፣ መከሰስም የለብንም የሚለው አቋም አሳፋሪ በመሆኑ ፓርቲው እንደማይቀበለው ገልጿል። በመሆኑም ዜጎች ላይ ግፍና ስቃይ የሚፈፅሙ ሁሉ ሳይውል ሳያድር ወደ ፍርድ መቅረብ አለባቸው በማለት፤ አንዳንድ የአፍሪካ መሪዎች አይሲሲን በተመለከተ የሚያራምዱትን የአትክሰሱን አቋም ፓርቲው እንደማይቀበለውም ገልጿል።

Wednesday, October 23, 2013

የመከላከያው ሹመትና መዘዙ

October 23/2013

 የሰሞኑና የቀደሙት የመከላከያ አድሎአዊ ሹመቶች ከማሳሰብ በላይ እየሆኑ ነው:: ይህ ተደጋጋሚ ተግባር የህገ መንግስቱን አንቀጽ 12:1 ፣62:4፣87:1ና5 እንደዚሁም አንቀጽ 88:2ን በጽኑ ይጥሳል:: በተለይም በአንቀጽ 87:1 ላይ የተቀመጠውንና በመከላከያ ሰራዊቱ ተዋጽኦ ላይ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖር የሚጠይቀውን ግብ ሙሉ በሙሉ ይሽራል:: አጠቃላይ የማንኛውም ህገ መንግስት መንፈስ የሆነውን ፍትሀዊና በአንድ ማህበረሰብ ሊኖር የሚገባውን የነጻነት፣ እኩልነትና ወንድማማችነትን የማስፈንና የማበረታታት ተግባርን ያኮላሻል:: በህሊና ተጠያቂነትም ላይ ይሳለቃል::
ትልቁና ስልታዊ (ስስተሚክ) ሙስና ይህ ነው:: 400,000 ብር የቤት ኪራይ ለግርማ ወ/ጊዮርጊስ ቤት ተከፋለ አልተከፈለ ኢትዮጵያ በርካታ ጉድ ችላለች:: ትችላለችም! በተደጋጋሚ የምንሰማው በመካላከያ ሹመት ግን ከህወሐት አይን አውጣነት ያለፈ ነው::የምርም ስድብ ነው:: ንቀት ነው:: እንዲህ ያሉ አብሮ መኖርን የሚጋፉና ኢፍትሀዊ አሰራሮች መቆም አለባቸው:: ማንኛውም ለትክክለኛ ሰላም፣ አብሮ መኖርና ፍትህ የሚያስጨንቀው ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ይህ ይመለከተዋል:: ጥቂቶች ይጠቀሙ ዘንድ እንዲህ አይነት ግፍ ሲፈጸም እያዩ ዝም ማለት ተገቢ አይደለም:: አይሆንም::
የሀገሪቱ መከላከያ እንደግብ የተቀመጠለትን የብሔር ብሔረሰብ ተዋጽኦነት በአስቸኳይ ሊፈጽም የግድ ነው:: አለያ ይህ ሀገር ቅኝ ግዛት እየሆነ ነው:: በቅኝ ግዛት ያለ ህዝብ ነጻ መውጣቱ ግድ ይላል! የሕወሀት ሰዎች መሾም የለባቸውም የሚል የለም:: ህወሐት ከአንድ ብሔር የመጡ ሰዎች የመሰረቱት ድርጅት ነው::ድርጅቱ የኢህኣዴግ ባለውለታ ነው:: የሀገሪቱ ባለውለታነት ከነበረውም ጨርሶታል:: ቀሪ ሂሳቦዎ እየተባለ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው:: ያም ሆኖ እንደ አንድ አባል መሳተፍ እንጂ ከሁሉ ብሄር እንደሆነ ሁሉ ሁሉንም የተቋሙን የስልጣን እርከኖች ሹመቶች መቆጣጣር አይበጅም::
ይህ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ነው:: ኢትዮጵያም መከላከያ ሰራዊቱም የብዙ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ሀገርና ተቋም ናቸው:: ስለሆነም ብዙ ጊዜ በምክንያትነት የሚቀርበው የልምድ: የዕውቀት ማነስ ወዘተ እንኳን ከ22 ዓመት በኋላ ቀድሞም ምክንያትነቱ አይታመንምና ማብቃት አለበት:: እስካሁንም ይህን ለማድረግ እውነተኛ ጥረት አልተደረገም ምናልባት በተቃራኒው እንጂ::
ይህ አድሎአዊ አሰራር አሁን ባለው ሁኔታ ከልክ አልፏል:: በአስቸኳይም ሊገታና ማስተካከያ መወጠን አለበት:: ይህ ካልሆነ አገሪቱን ይጠብቃል ተብሎ የተዋቀረ ተቛም በአወቃቀሩ ኢፍትሃዊነትና በህወሐት ማን-አለብኝነት ምክንያት አገሪቱን ለማፍረስ የተጋረጠ አደጋ ሆኖ ይቀጥላል:: ስለዚህ የህወሐትና የማዕከላዊው መንግስት ባለስልጣናት በተለይ በመከላከያው ተቋም የብሔር ተዋጽኦ ላይ ጠንካራ የሆነ ክለሳ ተደርጎ በሚቀጥሉት አምስት አመታት የሚቆይ ፕሮግራም ካልነደፉና በአስቸኳይ በስራ ላይ ካላዋሉ ሀገሪቱን ወደ ከፋ አደጋ በማዝቀጥ እንደሚያፈራርሷት ግልጽ ነው::
ፖለቲካ የማህበረሰቡ ስልጣንና ሀብት በትክክል እንዲከፋፈል ፍትሃዊ መፍትሔ ማምጣት ነው ግቡ:: በየጊዜው የምናየው የሀገራችን ፖለቲካ ግን በፍጥነት አድሎአዊነቱ እየጨመረና በርካታ የተወከሉ የመሰላቸውን ብሄሮችንና ግለሰቦችን በማግለል ስራው ተጠምዷል::ይህ ከሶማሊያም የባሰ አደጋ አለው ነው መልክቴ! መንገዳችሁ ለእኛም ለናንተም አይበጅምና ህሊና ያላችሁና የኢትዮጵያ መኖር የሚጠቅማችሁ የህወሐት አባላት እንድትሰሙ እመክራለሁ::

Tuesday, October 22, 2013

ዶ/ር መረራ የፍንዳታውን ዜና “እንጠራጠረዋለን” አሉ

bole 1October 22, 2013 06:39 am 
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ሰፈር የደረሰውን ፍንዳታ አስመልክቶ ኢህአዴግ ያሰራጨውን ዜና የሚቃረኑ መረጃዎችና አስተያየቶች ቀረቡ። ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች የድጋፍ አስተያየት ሲሰጡ ዶ/ር መረራ “አትፍቶ ጠፊ አጥፍቶ ይጠፋል እንጂ በሜዳ ዝም ብሎ አያጠፋም” ሲሉ ጥርጣሬ እንዳላቸው ተናግረዋል። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ትህዴን/ በፍንዳታው የሞቱት ኢትዮጵያውያን ናቸው ሲል ስም ገልጾ የኢህአዴግን ዜና አጠጥሎታል።
በፓርላማ አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራ የጠየቁት ከኢህአዴግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የሚታሙ ፓርቲዎች “የጸረ ሽብርተኞች አዋጅ ሊጠናከርና ሊጠብቅ ይገባል” ሲሉ ተደምጠዋል። የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ያነጋገራቸው የኢራፓ፣ የኢሴዳፓ፣ ቅንጅትና አዲአን ተወካዮች በየተራ የኢህአዴግን ዜና የሚቃወሙና በጥርጣሬ የሚመለከቱትን አውግዘዋል። በወቅቱ የቴሌቪዥን ጣቢያውም አንድነትና የሰማያዊ ፓርቲ ጠርተውት በነበረው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ “የጸረ ሽብርተኛነት አዋጅ ለሌላ ተግባር መዋሉን እንቃወማለን” በማለት የተቃውሞ ድምጻቸውን ሲያሰሙ በማሳየት ዜናውን ለማጀቢያነት ተጠቅሞበት ነበር።
በግል አስተያየታቸውን የተጠየቁት ዶ/ር መረራ ጉዲና በቴሌቪዥን መስኮት ቀርበው “ብዙዎች፣ እኔም ጓደኞቼም በጥርጣሬ ነው ያየነው” ሲሉ ከተቆረጠው ንግግራቸው ተደምጧል። ዶ/ር መረራ “አጥፍቶ ጠፊ አጥፍቶ ይጠፋል እንጂ በሜዳ ዝም ብሎ ራሱን አያጠፋም” ካሉ በኋላ “ስለዚህ እውነት ተደርጓል?” የሚለው ትልቁ ችግርና የጥርጣሬው መነሻ እንደሆነ አመልክተዋል። ስለዚህ በሚል ድምዳሜ “ሰው አንዳንድ ጊዜ የኢትዮጵያ መንግስት ለራሱ ፖለቲካ ብሎ የሚያደርገው ያው የለመደው ስራ ነው” እንደሚል ዶ/ር መረራ በተቀነጨበው አስተያየታቸው ሲናገሩ ተሰምቷል። በተቃራኒ ከላይ በስም የተዘረዘሩት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ ኢትዮጵያ የሽብር ጥቃት ኢላማና የአልሸባብ ስጋት ላይ ያለች አገር በመሆኗ ኢህአዴግ ህዝብን የመጠበቅና ደህንነትን የማስጠበቅ አደራ ስላለበት እነሱን ጨምሮ እንዲጠብቃቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስሙ የሚነሳውና በታጣቂ ሃይሉ ፈርጣማነት የሚታወቀው የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ  /ትህዴን/ በቦሌ ክፍለ ከተማ በቤት ውስጥ ፈነዳ በተባለው ፈንጂ ህይወታቸው እንዳለፈ የተገለጸው ሁለት የሶማሌ ዜጎች አይደሉም ሲል ከሁሉም ወገን የተሰራጨውን ዜና በዜሮ አጣፍቶታ። በፈንጂው የሞቱት ሁለት ሰዎች ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ስማቸውም “ምክትል ኢንስፔክተር ሞላ መላኩ የተባሉ የፖሊስ አባልና አቶ ሞገስ አስቻለው የተባሉ ሲቪል ናቸው” ሲል የገለጸው ትህዴን የሟቾቹ ስም በመታወቂያ መረጋገጡን አመልክቷል።የመታወቂያውን ቅጂ ግን በገጹ አላተመም። ከአደጋው ጋር በተያያዘ በስፍራው ታይታችኋል በሚል በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን በመግለጽ የሶስት እስረኞችን ስም ይፋ ያደረገው ኦክቶበር 19 ቀን 2013 በራሱ ኦፊሳላዊ ድረገጽ ላይ ነው። ኢህአዴግም ቢሆን ሞቱ የተባሉትን ሰዎች ይህ ዜና እስከተጻፈበት ቀን ድረስ በሰነድ አስደግፎ አላቀረባቸውም።
በሌላ በኩል ኦክቶበር16 ለንባብ የበቃው ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 3ቀን 2006ዓ.ም. በቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ማዞሪያና ቦሌ ሚካኤል መግቢያ አካባቢ በቦምብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ያለፈው ሁለት ሶማሊያውያን ሽብርተኞች መሆናቸውን ማረጋገጡን፣ የፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ማስታወቁን ዘግቧል።
Bomb-Blast-Addisየአንድ ግለሰብ ሰርቪስ ቤት ተከራይተው ከነበሩት ሶማሊያውያኑ መካከል፣ አንደኛው ከ20ቀናት በላይ የቆየ ሲሆን፣ ሌላኛው ፍንዳታው ከመድረሱ ከሁለት ሰዓታት በፊት የደረሰ መሆኑን ግብረ ኃይሉ ማረጋገጡን ያመለከተው ሪፖርተር ሽብርተኛ የተባሉት ሶማሊያውያኑ ካፈነዱት ቦምብ በተጨማሪ መጠናቸው ያልተገለጸ ቦምቦችና አንድ ሽጉጥ ከሁለት ካርታ ጥይት ጋር መገኘቱን፣ የፈንጂ ማቀጣጠያና የአደጋ መከላከያ ጃኬቶች፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማሊያና ቀበቶዎች መገኘታቸውም ጠቁሟል፡፡ ከሶማሊያውያኑ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አላቸው የተባሉ ሦስት ተጠርጣሪዎችና የቤቱ አከራይ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄባቸው መሆኑንም ግብረ ኃይሉ አክሏል በማለት ሪፖርተር ዘግቧል። አዲስ አድማስ በበኩሉ አልሸባብ ለጥቃቱ ሃላፊነት መውሰዱን አድራሻው አልተመዘገበ የትዊተር ማረጋገጫ በማመላከት ከዚህ በታች ያለውን ዜና አስነብቧል።
ባለፈው እሁድ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ ከደረሰው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ ሁለት ተጨማሪ የፍንዳታ ጥቃት ለማድረስ አልሸባብ የተሰኘው የሶማሊያ ቡድን እንደዛተ የገለፀው የአሜሪካ ኤምባሲ፤ የዛቻው ተአማኒነት ባይረጋገጥም በኢትዮጵያ የሚገኙ አሜሪካዊያን ጥንቃቄ እንዳይለያቸው ሁኔታው አሳሳቢ እንደሆነ በመግለጽ ዜናውን የከፈተው አዲስ አድማስ፣ “የኢትዮጵያና የናይጄሪያ ቡድኖች ግጥሚያ በሚካሄድበት ሰዓት ጥቃት ለመፈፀም ሲዘጋጁ የነበሩ ሁለት ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ሲሆን በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት በማወጅና ሽብር ለመፈፀም በመዛት የሚታወቀው አልሸባብ “ድርጊቱ በኔ አባላት የተፈፀመ ነው” ብሏል በማለት አልሸባብ በቦሌ ሚካኤል ለተከሰተው ፍንዳታ ሃላፊነት እንደሚወስድ በትዊተር እንዳስታወቀ ማሰራጨቱን፤ በፒያሳና በቸርችል ጐዳና አካባቢ የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እንደዛተም ገልጿል፡፡
በቦሌ ሚካኤል በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተከሰተው ፍንዳታ ሁለት የሶማሊያ ተወላጆች መሞታቸውን የገለፀው ፖሊስ፤ ከሟቾቹ አንዱ የኢትዮጵያ ማሊያ በመልበስ ከኳስ ተመልካቾች መሃል የፍንዳታ ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጀ እንደነበር መጠቆሙን አዲስ አድማስ በዜናው አውጇል። አዲስ አድማስም ሆኑ ሪፖርተር ፖሊስ የነገራቸውን ከመዘገብ ውጪ ከሌሎች ሚዲያዎች፣ በተለያዩ ማህበረ ገጾችና በቅርበት ከህብረተሰቡ የሚሰጡትን አስተያየቶች አስመለክቶ ዜናውን ላቀበላቸው ክፍል አላቀረቡም።
የኢህአዴግ አንደበትና የንግድ ድርጅት የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ የደረሰው የፈንጂ ፍንዳታ በሁለት ሶማሊያውያን አሸባሪዎች የተፈፀመ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል አሰፋ አብዩን ጠቅሶ አስታውቋል። ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳለው ፍንዳታው የደረሰው በክፍለ ከተማው ወረዳ 01 ቀበሌ 01 በተለምዶ ሩዋንዳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በአንድ የመኖሪያ ቤት ውስጥ ነው። ፖሊስ ፍንዳታው ፈንጂ መሆኑንና በጥቅም ላይ የዋለው ቲ ኤም ቲ የተባለ የፈንጂ ዓይነት መሆኑን እንደደረሰበት አረጋግጧል። ፍንዳታውንም ሁለት ሶማሊያውያን ማቀነባበራቸውን ፖሊስ እንዳረጋገጠና ግለሰቦቹ የአሸባሪ ቡድኑ አልሸባብ አባል መሆናቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች መገኘታቸውን ጄኔራል አሰፋ አብዩ መናገራቸውን የጠቆመው ፋና ከሁለቱ አሸባሪዎች መካከል አንደኛው ወገቡ ላይ የታጠቀና ለአጥፍቶ ጠፊ ተግባር የተዘጋጀ መሆኑን ያመላክታል ብሏል።
ሌላኛው አሸባሪ በሻንጣ ፈንጂ የያዘ ሲሆን፥ የፈነዳውም ፈንጂ በሻንጣው ውስጥ የነበረ መሆኑን ነው ጀነራል አሰፋ ያስረዱት። ለአጥፍቶ ጠፊ ተግባር ሲዘጋጅ የነበረው ግለሰብ የታጠቀው ፈንጂ ግን እንዳልፈነዳ አመልክተዋል። አሸባሪዎቹ በአጠቃላይ ሶስት ፈንጂዎችንም ይዘው ነበር። አሸባሪዎቹ ህዝብ ባለበት ስፍራ አደጋ ለማድረስ ተከራይተው በነበሩበት ቤት ውስጥ ሲዘጋጁ ፍንዳታው ደርሷል ብሎ ፖሊስ እንደሚጠረጥር ነው የጠቆሙት። ከአሸባሪዎቹ ጋር ፖሊስ የእጅ ቦምቦችንና ሽጉጥ ከነጥይቱ አግኝቷል።
የፋናን ዜና ተንተርሶ የተሰነዘሩ አስተያየቶች እንደሚያመለክቱት ሪፖርተር በፈነዳው ፈንጂ ህይወቱ ያለፈው አንደኛው ሰው ሰውነቱ መበታተኑና የአይን እማኞችን ገልጾ መዘገቡን ያስታውሳሉሉ። ፈነዳ የተባለው ፈንጂ ከፈነዳ በሁዋላ አጥፍቶ ለመጥፋት የተዘጋጀው ሰው የታጠቀው ፈንጂ አለመፈንዳቱ መገለጹ ከሙያ አንጻር ጥያቄ የሚያስነሳ እንደሆነ፣ ከዚህም በላይ ድርጊቱን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ጋር ለማገናኘት የብሔራዊ ቡድን መለያ ሹራብ ተገኘ መባሉ ድርጊቱን ድራማ ያስመስለዋል ባይ ናቸው። (ፎቶ: ሪፖርተር)

መለስ የሚባል ራእይ የለም ሲሉ አቶ ስብሀት ነጋ ተናገሩ

October 21/2013

ጥቅምት (አስር)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በህዝባዊ ወያነ ሀርነት ትግራይ(ህወሀት) ውስጥ የተካረረ አለመግባባት እንደተፈጠረ በስፋት በሚነገርበት በዚህ ወቅት አቶ ስብሀት ነጋ ፣ የኢህአዴግ እንጂ የመለስ የሚባል ራእይ የለም ብለዋል።

የህወሀት መስራች የሆኑት አቶ ስብሀት ነጋ ይህን ያሉት ከጋዜጠኛ ደረጀ ደስታ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ነው።

አቶ ስብሀት ፦” መለስ የ ኢህአዴግን ራዕይ ለማስፈፀም ከፊት ሆኖ ብዙ ሥራ ሠራ እንጂ ራዕዩ የመለስ አይደለም። ራይዩ የድርጅቱ ነው”ብለዋል።

በዚሁ ቃለ-ምልልስ ከሟች ጠቅላይ ሚኒስትር ባለቤት ከወይዘሮ አዘዜብ መስፍን ጋር አለመግባባት ውስጥ ገብተው እንደነበርም አቶ ስብሀት በግልጽ ተናግረዋል።

አቶ ስብሀት በዚሁ አስገራሚ መልሶችን በሰጡበት ቃለ-ምልልስ የአቶ መለስን ሞት ተከትሎ ስለተሾሙት  33 ጀነራሎች ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለም ተናግረዋል።

አቶ መለስ ማረፋቸውን ተከትሎ ከ አራቱ የ ኢህአዴግ ድርጅቶች በተውጣጡ  አራት ምክትል ጠ/ሚ/ሮች  እየተመራች ያለችው ኢትዮጵያ፤ያም አልበቃ ብሎ  ከአራቱም ድርጅቶች የተውጣጡ አራት ከፍተኛ ካድሬዎች  አማካሪዎች ተብለው አቶ ሀይለማርያም አጠገብ እንዲሆኑ መደረጋቸው ይታወሳል።

አቶ ሀ ይለማርያም ደሳለኝም አመራራቸውን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ፦በጋራ፣በኮሚቴ እየመራን ነው ማለታቸው አይዘነጋም።

በቂ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስት ስልጣን ለህዝብ ማስረከብ አለበት” ሲል አንድነት ፓርቲ ገለጸ

October 21/2013


ጥቅምት (አስር)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ይህን የገለጸው ጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ ” በቂ ጥበቃ የለንም በሚል ሰላማዊ ሰልፍን እንደሚከለክሉ” መናገራቸውን ተከትሎ በሰጠው መልስ ነው። ” በቂ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስት ስልጣኑን ለህዝብ በማስረከብ ይቅርታ ጠይቆ መሄድ እንጅ ከአሁን በኋላ መብታችሁን አታገኟትም ” በማለት መዛት ትዝብት ውስጥ የሚጥል ድርጊት ነው ብሎአል አንድነት በመግለጫው፡፡

አንድነት  ” ተገዥነቱን ለህዝቡና ለህግ አድርጎ በአምባገነኖች ዛቻ ሳይበረግግ፤ ዘር፣ ፆታ፣ ሀይማኖት፣ ቀለም ሳይለይ ዜጎች የሚያነሱት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች እንዲመለሱ፤ የመንግስት በሐይማኖት ጣልቃ ገብነትም እንዲቆም ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያረጋግጣል”  ብሎአል።

ፓርቲው እንደ ኢትዮጵያ አሉ አንዳንድ የአፍሪካ መሪዎች በአለማቀፍ ፍርድ ቤት ላይ የያዙትን አቋምም ተችቷል።  ” የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው እንግደል፣ እንሰር፣ እንጨፍጭፍ፣ ዘር እናጥፋ፣ ዜጎቻችንን እናሰቃይ ግን መታሰርም መከሰስም የለብንም በሚል የያዙት አቋም አሳፋሪና ተቀባይነት የሌለው ነው፣ የሚለው አንድነት፣ ሕግ እየጣሱ በህግ አለመጠየቅ አይቻልም፡፡ ዘር እያጠፉ ያለመታሰር መብት አይኖርም፡፡ ማንም ሰው ከህግ በላይ የመሆን መብት የለውም፡፡” ሲል አክሏል።

የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው ማለት ያለባቸው አይሲሲ ሊከሰን አይገባም ሳይሆን የዜጎቻቸውን እንባ ማበስ ነው የሚለው አንድነት፣  አሁንም ሆነ ወደፊት በዜጎቻቸው ላይ ግፍና ሰቆቃ የሚፈፅሙ ሁሉ ሳይውል ሳያድር ወደ ፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ ያምናል ሲል አቋሙን ግልጽ አድርጓል፡፡

Monday, October 21, 2013

ONLF fighters attacked Ethiopian Officials at Kebridahar Airport: several Ethiopian Troops KILLED at the airport and destroyed two vehicles.



ONLF fighters attacked at Kebridahar Airport: ONLF official

Photo: Deputy Prime Minister of Ethiopia Demeke Mekonnen and his delegation landing on the Godey Airport

By Mohamed Faarah

October 21, 2013

(Ogadentoday Press)- Ogaden National Liberation Front “ONLF,” official have claimed that their fighters attacked on Kebridahar town Airport on last week.

Our aim for this attack was to disrupt the visiting delegation in Ogaden and send a clear message to the puppet administration that serves only the colonial agendas in our people and land. The official said to Ogadentoday Press on the phone.

Speaking on the attack the official said that they have killed several Ethiopian Troops at the airport and destroyed two vehicles.

This was a co-ordinated attack and went successfully, the official said.

The puppet administration was hiding the attack but the military leaders informed the delegation, said the official citing their intelligence in the Ogaden.

I can confirm to you that, it was midnight and they have been waiting to welcome the federal delegation in the morning.

There is no comment from Ethiopia government.

The Deputy Prime Minister of Ethiopia Demeke Mekonnen, nine regional leaders, domestic and foreign investors were visiting Ogaden Region last week.

According to Ethiopian government, the domestic investors are interesting to invest the agricultural sector in Ogaden.

Ogaden National Liberation Front, a secessionist group fighting for the independence of Ogaden warns the foreign oil companies in Ogaden, and attacked in 2007 a Chinese oil field in Ogaden.

According to the source, ONLF were watching closely the visit and Pro- ONLF site "Ogaden News Agency (ONA) published that, ONLF fighters are on the high alert.

The arid Somali (or Ogaden) region of Ethiopia, home to some 7-8 million ethnic Somalis has been isolated from the world since 2005, when the government imposed a ban on all international media and most humanitarian groups from operating in the area.

Ogadentoday Press

የኢህአዴግ ቀጣይ የፖለቲካ ሴራዎች – (ተመስገ ደሳለኝ)

October 21/10/20

ከ ተመስገ ደሳለኝ 

አዲስ አበባ

የሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ-ምህረት የመጀመሪያ ወር ተጠናቅቋል፤ አዳዲስ ክስተቶችም ታይተዋል፤ ያለፉት አስራ ሁለት ዓመታትንበጃንሆይ ቤተ-መንግስት ያሳለፉት ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ በኦህዴዱ ሙላቱ ተሾመ መተካታቸው አንዱ ነው፡፡ አባይ ፀሀዬና ዶ/ር ካሱ ኢላላም ከበረከት ስምዖንና ኩማ ደመቅሳ በተጨማሪ በሚኒስትር ማዕረግ የኃ/ማሪያም ደሳለኝ ‹‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር›› አማካሪ ሆነው መሾማቸው ሌላው ነው (በነገራችን ላይ ሹመቱን እንደተለመደው አይቶ ችላ ብሎ ለማለፍ የማያስችሉ ሶስት ምክንያቶች አሉ፤ የመጀመሪያው በሀገሪቱ ለአንድ የሥራ መደብ አራት ሚንስትር ተሹሞ አለማወቁ ሲሆን፤ ሌላው ተሿሚዎቹ፣ ኢህአዴግን ከመሰረቱት አራት ፓርቲዎች በኮታ የተወጣጡ መሆናቸው ነው፡፡ ሳልሳዊውና አስገራሚው ደግሞ ሰዎቹ ፖለቲከኞች እንጂ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ጥናትና ምርምር ያካሄዱ ምሁራን አለመሆናቸው ነው)
እነዚህ ሁሉ በግልፅ የሚታወቁ የዓመቱ መጀመሪያ ክስተቶች ናቸው፡፡ ለስርዓቱ ቅርበት ካላቸው ምንጮቼ ባገኘሁት መረጃ መሠረት፣ በቅርቡ ‹ሚዲያ›ን እና ‹የይቅርታ ስነስርዓት›ን የተመለከቱ አዳዲስ አዋጆች በተወካዮች ም/ቤት ለመፅደቅ ተዘጋጅተዋል፡፡ በተለይም ‹ሚዲያው›ን የሚመለከተው አዲሱ ህግ፣ ከአምስት ዓመት በፊት ተግባር ላይ የዋለውን የ‹‹ፕሬስ አዋጁ››ን የአፋና ጉልበት ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ፣ የነበረው አንፃራዊ ጭላንጭል ጭራሽ ሊዳፈን እንደሚችል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ‹‹የይቅርታ አዋጁ››ም ቢሆን ጥቂት የአገዛዙ ጉምቱ ባለስልጣናት ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ የአመራር አባላትና አንዳንድ የግል ጋዜጠኞች ብንታሰርም በይቅርታ እንፈታለን በሚል ግንባሩን እየተፈታተኑ ነው›› ሲሉ ደጋግመው መደመጣቸውን፣ ከአዲሱ ‹‹የይቅርታ አሰጣጥ እና አፈፃፀም ሥነ-ሥርአት አዋጅ›› ጋር ካያያዝነው፣ አንቀፆቹ ሊኖራቸው የሚችለውን አንድምታ መገመቱ ብዙ ከባድ አይሆንም፡፡

ለማንኛውም ኢህአዴግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጉልበታም በመሆን ቀጣዩን ምርጫ በስኬት ለማለፍ፣ በያዝነው ዓመት የተለያዩ አፋኝ ህጎችን በማውጣት ፓርቲዎቹን የማዳከም ስራ ለመስራት በተለየ መልኩ መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡ በአናቱም ኃ/ማርያም ደሳለኝ-ከመንግስት፣ ከፓርቲውና ከውስን የግል ጋዜጠኞች፤ ደመቀ መኮንን-ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ፤ ሽመልስ ከማል -ከኢዜአ ጋር ያደረጓቸው ቃለ-መጠይቆችም ይህንን መረጃ የሚያጠናክር ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም አገዛዙ በቀጣይ ሊኖረው የሚችለውን ባህሪ እና ‹አምስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ›ን አስቀድሞ ለማሸነፍ እየቀመረ ያለውን ሴራ መጠቆም ነው፡፡

የባለስልጣናቱ አንደበት

ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያምና ምክትሉ ደመቀ ሰሞኑን ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ላይ፣ በስሱም ቢሆን ከጀርባቸው ያደፈጡትን አንጋፋ ታጋዮች ቀጣይ ‹‹የፖለቲካ ሴራ›› (Political Conspiracy) አርድተውናል ብዬ አስባለሁ፡፡

ሁለቱ መሪዎች በዋናነት እንዲያተኩሩ የተደረገው በአራት ጉዳዮች ላይ ነው፡፡ በግንባሩ ውስጥ ክፍፍል መፈጠሩን መካድ፣ አመቱን ሙሉ ‹የመለስ ራዕይ› እየተባለ የተዘመረለትን ‹እሳት ማጥፊያ› ፕሮፓጋንዳ ማስተባበል፣ የሙስና ክሱን ሂደትና ውጤት መሸፋፈን እንዲሁም ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ማስፈራራት የሚሉ ናቸው፡፡ በአዲስ መስመርም እነዚህን አራት አጀንዳዎች ነጣጥለን ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡

ክፍፍሉን በተመለከተ

ከመለስ ህልፈት ማግስት አንስቶ በግንባሩ ግልፅ ክፍፍል መከሰቱ የአደባባይ ሀቅ ቢሆንም፣ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማሪያም ‹‹ፓርቲዎ ውስጥ ክፍፍል አለ ይባላል፤ የኃይል አሰላለፍ እየተጠበቀ ነው የሚኬደው የሚባሉ አሉባልታዎች ይሰማሉ፣ የፓርቲዎ ጤናስ እንዴት ነው?›› የሚል ጥያቄ ሲቀርብለት፡-

‹‹በፓርቲዬ ውስጥ ክፍፍል አለ የሚለው ጥያቄ የምኞት ነው፤ ብዙ ምኞቶች ሲሰሙ ነበር፤ ምኞት አይከለከልም፡፡ ስለዚህም ምኞት ይኖራል የሚል ሃሳብ ከማቅረብ በዘለለ እውነት ስለሌለው ምኞት ነው ብሎ ማለፍ ነው›› በማለት አስተባብሎ ሲያበቃ፤ ከደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ተገልብጦ ‹‹አሁን በቅርቡ እንደደረስንበት አንዳንድ ጊዜ በየቦታው ደባ የሚሰሩ ጥቂት የመሥሪያ ቤት ሰራተኞች አሉ›› ብሎ የራሱ ሰዎች በመንግስቱ ላይ እያሴሩበት እንደሆነ በመግለፅ ከላይኛው ንግግሩ ጋር መጣረሱ፣ በርግጥም የተጠቀሰው ችግር መኖሩን ለመረዳት አያዳግትም፡፡

ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተም ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ ምክትል ጠ/ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ከዚህ ቀደም ባልተለመደ መልኩ አጠንክሮ ጠይቆት ያስተባበለበት መንፈስም ለመሸሸግ የፈለገው ጉዳይ እንዳለ የሚያሳብቅ ይመስላል፡፡
‹‹አንድ ግልፅ መሆን ያለበት እንደ አቶ መለስ ያለ ታላቅ መሪ፣ ታግሎ የሚታገል ጠንካራ መሪን ማጣት ትልቅ ጉድለት ነው፡፡ ጉድለቱ እንዲሁ ዝም ተብሎ እዚያና እዚህ በዘመቻ የሚሞላ ጉዳይ አይደለም፡፡ …ስለዚህም ሁለት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደረጃ ኃላፊዎችን በመሰየም ክላስተር እንዲያስተባብሩ ማድረግ ያለመተማመን መገለጫ አይደለም፡፡››
የሁለቱ ሚኒስትሮችን ያልተጠበቀ ቃለ-መጠየቅ መግፍኤ ለመረዳት በተለይ ደመቀ መኮንን ለቀረቡለት ጥያቄዎች የሰጠውን ምላሾች በጥልቅ መፈተሽ አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም ተከስቶ የነበረውን መከፋፈልም ሆነ ‹ፓርቲው በጥቂት የህወሓትና የብአዴን ታጋዮች ነው

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

የሚሽከረከረው› መባሉን ለማስተባበል የሄደበት መንገድ፣ ከዚህ ቀደም ኢህአዴግ የሚከራከርባቸውን እምነቶቹን ጭምር እስከመናድ የደረሰ ነውና፡፡ ወይም እንዲንድ ታዝዟል ያስብላል (በነገራችን ላይ ከምንጮቼ ባገኘሁት መረጃ እነአባይ ፀሀዬና በረከት ስምዖንም ከመጋረጃው ጀርባ የሚሰራ ኃይል መኖሩን ማስተባበል ይፈልጋሉ፡፡ በተለይም ‹‹በነፃነት እንዲሰሩ አመቻቹላቸው›› እያሉ የሚወተውቷቸውን ምዕራባውያን ዲፕሎማቶች ማሳመኑ ከባድ ሥራ እንደሆነባቸው ሰምቻለሁ፡፡

የሰሞኑ የቃለ-መጠይቅ ጋጋታም ይህንኑ የሚያጠናክር ይመስላል፡፡ ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣም ለደመቀ መኮንን ያቀረባቸው ጥያቄዎች ከቀደመው ታሪኩ አኳያ ሲመዘን የግል እምነቱ አለመሆኑን መረዳት አያዳግትም፡፡ ‹‹ጋዜጣው እስከአሁን ያልነበረውን ‹የኤዲቶሪያል ነፃነት› ዛሬ አግኝቶ ነው ሰውየውን እንዲህ ያፋጠጠው›› የሚል ተከራካሪ ካልቀረበ ማለቴ ነው፡፡ ምናልባትም ጉዳዩን በሌላ አውድ እንየው ከተባለ ደግሞ የሚያያዘው፣ የድርጅቱ አመራሮች አልፎ አልፎ ህዝብ ዘንድ የደረሱ እውነታዎችን፣ በራሳቸው ጋዜጠኞች እንዲጠየቁ በማድረግ ለማስተባበል ከሚሞክሩበት የቆየ ልማዳቸው ጋር ብቻ ነው፡፡ በመስከረም 22፣ 23 እና 24 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው የ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ በተስተናገደው የደመቀ መኮንን ቃለ-መጠይቅ ላይ የተነሱትን ጥያቄዎች ብንመለከት ይህንኑ ያረጋግጡልናል፡፡ ‹‹ፓርቲው በጥቂት ሰዎች ስር ስለመውደቁ፣ ከመንግስት ኃላፊነት የተነሱ ባለስልጣናት በፓርቲው ውስጥ ስራ-አስፈፃሚ ሆነው ስለመቀጠላቸው፣ መተካካቱ የቦታ መቀያየር ብቻ ስለመሆኑ፣ ሥራ የማይሰሩ ደካማ መሆናቸውን በተወካዮች ም/ቤት ጭምር የተረጋገጠባቸው ከፍተኛ አመራሮች ዛሬም በኃላፊነት ቦታ ላይ ስለመቀመጣቸው፣ በብልሹ አሰራር /በሙስና/ የተጠየቁ ባለስልጣናት ጥቂት ብቻ መሆናቸው፣ በአቅም ማነስ የሚነሱ ኃላፊዎች ወይ ከነበሩበት የተሻለ አሊያም ተመጣጣኝ በሆነ ደረጃ ስለመመደባቸው፣ አንድ ጊዜ የላይኛውን የስልጣን እርከን የተቆናጠጠ ባለስልጣን ከፓርቲው ቁልፍ አመራሮች ጋር ካልተጋጨ በቀር አቅም ባይኖረውም እንደማይሻር፣ ለፓርቲው መስራቾችና እስከአሁንም ወሳኝ ለሆኑት አመራሮች ታማኝ የሆነ ኃላፊ ምንም አይነት ድክመትና ወንጀል ቢፈፅምም በስልጣን መቆየት መቻሉን፣ የሁለቱ ተጨማሪ ምክትል ጠ/ሚኒስትሮች ሹመት በአራቱ የብሔር ድርጅቶች መካከል ያለውን አለመተማመን ስለማሳየቱ፣ ሁሉም ፓርቲዎች እኩል አለመሆናቸውን፣ መለስ በሃያ ሁለት የሥልጣን ዓመታቱ ተተኪ ማፍራት አለመቻሉን፣ ‹የመለስ ራዕይ› የሚባል ነገር አለመኖሩን…›› እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ባልተለመደ ድፍረት የጠየቀው መንግስታዊው ዕድሜ ጠገብ ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ ነው)

ቃለ-መጠየቁ ከእነዚህ በተጨማሪም ቀጣዩን የኢህአዴግ አቅጣጫ አመላክቷል፡፡ የሆነው ሆኖ ክፍፍሉንና ከጀርባ ሆነው ያሽከረክራሉ የሚባሉትን አንጋፋ የአመራር አባላት አስመልክቶ ለቀረበለት ጥያቄ ከሰጠው ምላሽ ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፡-

‹‹ፓርቲው አንድ ሰው፣ ሁለት ሰው፣ ሶስት ሰው እጅ ጠምዝዞ ‹ይሄን አድርጉ› በሚል አንዳችም ጉዳይ የሚያስፈፅምበት አይደለም፡፡ …ኢህአዴግ በጥቂቶች የሚመራ ድርጅት አይደለም፡፡ …ጥቂት ግለሰቦችን በተለየ ሁኔታ የሚያይ፣ በእነርሱም ስር የሚሆን አይደለም፡፡ የጥቂቶች ነው የሚለው ከእውነት የራቀ ነው፡፡ …ማንም በራሱ ተቆጥሮ በተሠጠው ሥራ ሊወስን፣ ሊመራና ሊንቀሳቀስ ይችላል፡፡ በድርጅታዊ ዲሲፒሊንና አሰራር፣ የግልና የጋራ አሰራር በሚዛን ተቀምጦ በንቅናቄ የሚመራ እንጂ በግለሰቦች አይደለም የሚለው ቢሰመርበት ጥሩ ነው፡፡››

በርግጥ ይህንን ያነበበ ‹‹ሰውየው ስለየትኛው ኢህአዴግ ነው የሚያወራው?›› ቢል ላይፈረድበት ይችላል፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ የታሪክ ንባብም ሆነ የቀድሞዎቹ ስዬ አብርሃ፣ አለምሰገድ ገ/አምላክ፣ አውዓሎም ወልዱ፣ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ነጋሶ ጊዳዳ፣ ሀሰን አሊ፣ አልማዝ መኩን የመሳሰሉት የአመራር አባላት የነገሩን ‹ድርጅቱ በጣት በሚቆጠሩ ሰዎች ፍቃድ የሚያድር› መሆኑን ነው፡፡ ለነገሩ ራሱ ደመቀም ቢሆን ከኤርትራ ጋር ወደ ጦርነት ለመግባት ህወሓት በር ዘግቶ ብቻውን መምከሩንም ሆነ የግንባሩን አባል ድርጅቶች ነፃነት እንዳሻው መጋፋቱን አምኖ መቀበል ባይፈልግ እንኳን፣ በ1999 ዓ.ም መጨረሻ ከሱዳን ጋር የሚዋሰነው የጎንደር መሬት ላይ የተላለፈው ውሳኔ በምን መልኩ እንደነበረ ሊክደው አይችልም (በነገራችን ላይ በወቅቱ የአማራ ክልል አስተዳዳሪው አያሌው ጎበዜ ምክትል የነበረ በመሆኑ፣ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ጎንደርና ትግራይ አካባቢ፣ የሚወራበትን ውንጀል በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ)

የሰውየው መከራከሪያ ግን እውነት አለመሆኑን ‹ፍትህ›ና ‹ልዕልና› ጋዜጦች፤ ‹አዲስ ታይምስ›ና ‹ፋክት› መፅሄትን ጨምሮ የምዕራብ ሀገራት ብዙሃን መገናኛ እና ድርጅቱን በቅርብ የተከታተሉ ምሁራን በተለያየ ጊዜ ማስረጃ በማጣቀስ ደጋግመው ስላቀረቡ ተጨማሪ ማብራሪያ ያስፈልገዋል ብዬ አላስብምና ወደ ቀጣዩ ጉዳያችን አልፋለሁ፡፡

‹‹መተካካት›› ሲባል…

በአንድ ወቅት አቶ መለስ ብዙ ብሎለት የነበረው የመተካካት ዕቅድ ‹‹ቦታ ከመቀያየር ያለፈ አዲስ ፊት አላመጣም›› መባሉን በተመለከተ፣ ደመቀ መኮንን የሰጠውን ምላሽ፣ ከተለያየ አውድ ካየነው ከላይ የተጠቀሰውን ክፍፍል በሌላ በኩል ይነግረናል፡፡ ምክንያቱም መለስ በህይወት በነበረበት ዘመን ጉዳዩን አስመልክቶ የነገረን ‹መተካካቱ ከላይ ያሉትን ነባር የአመራር አባላት፣ በየተራ በጡረታ በማሰናበት አዲሱን ትውልድ (አዲስ ፊት) ወደመሪነት ማምጣት ነው› የሚል እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ደመቀ መኮንን ደግሞ በግልባጩ እንዲህ ይላል፡-

‹‹አዲስ ፊት ሲባል የማናውቀው ሰው ከጨረቃ ይምጣ? የሚመራው እኮ አገር ነው፡፡ አንድ ሰው አንድ ቦታ ላይ ሆኖ ሥራውን እየተወጣ፣ ሌላውንም እያበቃ ሥርዓቱ መቀጠል አለበት፡፡ በጣም የሚታወቅ ህዝባዊ አገልግሎት ላይ ያለ ሰው፣ ከያዘው ኃላፊነት ሌላ፣ በሌላ ጊዜ ሌላ ተክቶ ሊቀርብ ይችላል፡፡ አዲስ ፊት የለም፤ የማናውቃቸው ሰዎች ይምጡ ማለት፣ ሀገር የሙከራ ቦታ ይሁን ማለት ነው፡፡››

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ የሚደክመው በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ኩማ ደመቅሳ፣ ሽፈራው ጃርሶ፣ ካሱ ኢላላ፣ ሙላቱ ተሾመን… የመሳሰሉ አንጋፋ መሪዎች ከዚህ ቀደም ለአባላቶቻቸው የገቡትን ቃል ጠብቀው በክብር ከመሰናበት ይልቅ ስልጣን መቀያየራቸውን ለማስተባበል ይመስለኛል፤ በርግጥ ጉዳዩን ከለጠጥነው ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአንጋፋዎቹ መካከልም ሊሆን ይችላል እያለን ይሆናል፡፡ ይሁንና ሰውየው ያስተባበለበት መንገድ ግን በውስጡ ካለው እውነታ ጋር የተቃረነ በሚመስል መልኩ
የመተካካቱ አንድምታ የተቀየረው በመካከል የተፈጠረውን የኃይል ልዩነት አርግቦ፣ ስርዓቱ ከገጠመው መንገራገጭ ወጥቶ በሁለት እግሩ ቀጥ ብሎ ቆሞ እንዲቀጥል ለማስቻል መሆኑን ፍንጭ ይሰጣል፡፡

‹‹መተካካት ግለሰብን አይደለም የሚተካው፤ የስርዓት ቀጣይነትን ማረጋገጥ ነው!››

ይህ ሁናቴ በደንብ የሚፍታታው አቦይ ስብሃት ነጋ በተለይ ህወሓት ውስጥ የተካሄደው መተካካት ከተፈጠረው ልዩነት ጋር ተያይዞ መሆኑን ለ‹‹ውራይና›› መፅሄት የሰጡትን ቃለ-መጠየቅ ስናነብ ነው፡-

‹‹ጉባኤው ከማዕከላዊ ኮሚቴ ለተሰናበቱ ሰዎች ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገው፣ አሰራር ለምን እነሱን በሌሎች መተካት እንዳስፈለገ፣ ተራ በተራ እየጠቀሰ አስተያየት (ማብራሪያ) መስጠት ነበረበት፡፡ ይህ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ ከተሰናባቾቹ መካከል ማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ መቆየት (መቀጠል) የሚገባቸው በተገኙ ነበር፡፡ ከተመረጡት ውስጥ ደግሞ መሰናበት (በሌላ መተካት) የሚኖርባቸው ሊገኙ ይችሉ ነበር፡፡ ስለዚህ አካሄዱ ስህተት ስለሆነ ውጤቱም እንደዚያው ሊሆን ችሏል፡፡ እነማን መሰናበት፣ እነማን መቆየት እንደነበረባቸው በዝርዝር ስም ጠርቼ መናገር እችል ነበር፡፡ ግን ምንም ለውጥ ስለማያመጣ ስም መዘርዘሩ አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡››

የ‹‹ራዕዩ›› ጉዳይ…

በፋክት መፅሄት ቁጥር 5 ላይ ኢህአዴግ ‹የመለስ ራዕይ› እያለ ይደሰኩርለት የነበረውን አጀንዳ በወራት ጊዜ ውስጥ ገልብጦ በማጠቋቆር ሊቀየረው መዘጋጀቱ ተጠቅሶ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በደመቀ መኮንን ቃለ-መጠይቅ ላይም፣ መለስ ሥልጣን ላይ በነበረበት ዘመን ተገምግሞ መንግስታዊ ተቋማትንና የልማት ዕቅዶችን በአግባቡ መከታተልና መቆጣጠር አለመቻሉ ተገልጿል፡፡

‹‹ያለፉት ዓመታት ሥራዎቻችንን ስንገመግም ጠቅላይ ሚኒስትራችን ብዙ ሥራ ተሸክመው ይሰሩ በነበረበት ዋና ዋና የልማት ሥራዎቻችን ላይ በማተኮር አንዳንድ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችና የልማት መስኮችን በሚፈለገው ደረጃ ያለመፈተሽ፣ በዝርዝር ዕቅድ ግምገማና ድጋፍ ያለማድረግ ክፍተቶች እንደነበሩ እንደ ችግር በጋራ ያገኘናቸው ነጥቦች አሉ፡፡››

እንዲያ ሀገር-ምድሩ ‹ካልዘመረለት ተደፍረናል!› ሲሉለት የነበረው ‹‹የመለስ ራዕይ››ም ቢሆን የኢህአዴግ እንጂ የመለስ አለመሆኑን እየነገሩን ነው፡፡ አቶ ደመቀም፣ መለስ የነበረው ‹‹ራዕይ›› ሳይሆን ኃላፊነት ነው ወደ ማለቱ አዘንብሏል፡፡
‹‹ይሄን የዕድገት መንገድ ከኢህአዴግ አባላትና ከመሪዎቹ ጋር በመሆን በግንባር ቀደምነት የመሪነት ቁልፍ ሚና የተጫወቱ መሪ ናቸው፡፡››

በጥቅሉ በወቅታዊው የድርጅቱ ፖለቲካዊ አተያይ ‹‹የመለስ ራዕይ›› የሚለው ሀረግ ከየት እንደመጣ የተተነተነበትን አውድ ለመረዳት ከጋዜጣው ላይ አንድ ተጨማሪ ጥያቄና መልስ እንደወረደ ልጥቀስ፡-

‹‹አዲስ ዘመን፡- በየዘርፉ ራዕያቸው ተብለው የሚነገሩት መልእክቶችና መሪ ቃሎች ጋር በተያያዘ የተለጠፈባቸው ራዕይ እንዳለ ነው የሚነገረው፤ አገሪቱን ከመሩበት 22 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ምናልባት አንድ ጊዜ በንግግር መሀል የተናገሯት ወይም ለጋዜጠኞች የሰጡት ምላሽ ራዕይ ተደርጎ እየቀረበ ነው ስለሚባለውስ?

‹‹አቶ ደመቀ፡- እነዚያ መልዕክቶች ያንን ራዕይ የሚገልፁ፣ የሚያስታውሱ ምልዕክቶች ናቸው፡፡ ከማንኛውም ጉዳይ ጋር የተያያዙ መልዕክቶች ይኖራሉ፡፡ እነዚያ ያንን ትልቁን ራዕይ የሚመግቡ መልዕክቶች እንደሆኑ አድርጎ መመልከት ይቻላል፡፡››
ይኸው ነው፤ በቃ፡፡ መለስ ራዕዩን በጥሩ ቋንቋ ከመግለፅ ባለፈ የብቻው የሆነ ነገር የለውም፡፡ በክፍፍሉ ወቅት ከ‹አዲስ አበባው-ህወሓት› ጎን የተሰለፉት አቦይ ስብሃት ነጋ በጉባኤ፣ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች እንዲሁም አርከበ እቁባይ በህወሓት ጉባኤ ላይ የመለስ ‹ራዕይ› የሚባል ነገር አለመኖሩን በመግለፅ፣ በወቅቱ በአሰላለፍ የተመሳሰሉት ‹የመቀሌው-ህወሓት› እና ብአዴን በ‹ራዕይ› ስም ኃይል የማጠናከር እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን ለመተቸትና ለማደናቀፍ መሞከራቸው ይታወሳል፡፡ ይህ ሁናቴም ልዩነቱ ከተገለፀባቸው ምልክቶች አንዱ ተደርጎ ተወስዷል፡፡ ሌላው እዚህ ጋ መነሳት ያለበት ጉዳይ በዚህ ዓመት በዚሁ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ርዕስ የቀረበው ፅሁፍም ‹‹የመለስ ራዕይ››ን የማይቀበለው ቡድን እያሸነፈ በመምጣቱ፣ የእነ አዜብ-አባይ ወልዱ ህወሓትን አዳክሞ፣ የእነ በረከት-ብአዴንን ከጎኑ ማሰለፍ መቻሉን የተተነተነበትን ጉዳይ የሚያጠናክር መሆኑን ነው፡፡

የሆነው ሆኖ አሁን መለስን የሚያመልኩት ሄደዋል፤ በቦታውም እርሱ የሚያርቃቸው፣ እነርሱም ይፈሩት የነበረ ተተክተዋል፡፡ እናም በህልፈቱ ማግስት ድጋፍ ማሰባሰቢያ እና ኃይል ማጠናከሪያ ከመሆን አልፎ ሀገሪቱን ወደ ብልፅግና ሰማይ የሚያከንፍ፣ መና የሚያዘንብ ተደርጎ የነበረውን ‹‹የመለስ ራዕይ›› ታሪክ በማድረጋቸው፣ አርቀው መስቀል ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ አነጋገር በፋውንዴሽኑ አጥር ክልል ተወስኖ ይቀመጥ ዘንድ በይነዋል (በነገራችን ላይ ይህን ጉዳይ በዚህ ደረጃ ያነሳሁት የስርዓቱ መሪዎች ‹‹እንመራዋለን›› የሚሉትን ህዝብ በአደባባይ ሲዋሹ ቅንጣት ያህል ሀፍረት እንደማይሰማቸው ለማሳየት እንጂ፣ በግሌ መለስም ሆነ ጓደኞቹ ለስልጣናቸው ካልሆነ በቀር ሀገር የሚጠቅም ራዕይ አላቸው ብዬ አላምንም)

የ‹‹ሙስና››ውን ክስ ሂደት መሸፋፈን

የእነ መላኩ ፈንቴን እስር ተከትሎ ‹‹ሙስና›› ዋነኛ አነጋጋሪ አጀንዳ ሆኖ ነበር፡፡ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃ/ማሪያምም ‹ጉዳዩን ራሴ እከታተለዋለሁ› የምትል ፉከራ ብጤም ሞካክራው ነበር (ቀደም ሲል በዚሁ መፅሄት የ‹ሙስና›ው ክስ በፖለቲካው የኃይል አሰላለፍ ላይ የበላይነትን ለመጨበጥ በአዲስ አበባው ህወሓት የተመዘዘ ‹‹ካርድ›› እንደሆነ መገለፁ ይታወሳል)
ባለሥልጣናቱ የታሰሩ ሰሞን ‹‹የመለስ ራዕይ›› ገና አልከሸፈም ነበርና ‹‹የፀረ-ሙስና ኮሚሽን›› ኮሚሽነር አሊ ሱለይማንም ጉዳዩን አቶ መለስ ራሱ ጀምሮት ለሁለት ዓመት ያህል ሲከታተለው ከቆየ በኋላ፣ በመጨረሻ ህይወቱ እንዳለፈ እያለቃቀሰ ነግሮን ነበር፡፡ 
ይሁንና
ከእስራ አምስት ቀን በፊት ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ባደረገው ቃለ-መጠይቅ፣ የታሰሩትን ሰዎች አስመልክቶ ከጊዜ ቀጠሮ ያለፈ ቁርጥ ያለ ነገር አለመኖሩ፣ በሌሎች ላይ ስጋት ስለመፍጠሩ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ ‹ገድሉ›ን ከመለስ ወደራሱ (ከኋላው ወደአሉ ሰዎች) መልሶታል፡፡

‹‹በቅርቡ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን አካባቢ የተፈጠረውን ችግር ለማቃለል በሙስና የተጠረጠሩ የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና በሙስና ተግባሩ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተጠያቂ የሚሆኑበት ስርዓት ተዘርግቶ የመንግስት አካል የሆነው የፌደራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ክስ መስርቷል፡፡››

ጥያቄውም ይህ ነው፡፡ ‹‹የአሊ ሱሊማንን ‹መለስ የጀመረው…› መግለጫንስ ምን እናድርገው?››

…ደመቀ መኮንንም ‹‹እዚያም እዚያም ከኃላፊነት የማውረድ፣ በሕግ የመጠየቅና ሕጋዊ እርምጃዎች ደረጃቸውን ጠብቀው ይቀጥላሉ›› ቢልም በመሬት ያለው ተጨባጭ እውነታ ግን የሚያሳየው ሙስና የተዘጋ አጀንዳ መሆኑን ነው፡፡ የ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ የፊት ገፆችም ‹‹ሚኒስትር እገሌ…››፣ ‹‹ዳይሬክተር እገሌ… በሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ›› ከሚል ዜና በብርሃን ፍጥነት ‹‹በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 10 የዲዛይንና ግንባታ ፍቃድ ጽ/ቤት፣ የግንባታና ዕድሳት ባለሙያ የነበረችው ግለሰብ መስከረም 21 ቀን 2006 ዓ.ም አራት ሺ ብር ጉቦ ስትቀበል በፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሠራተኞች እጅ ከፍንጅ ተያዘች›› ወደሚል ቧልት ተቀይረዋል፡፡

አቦይ ስብሃት ነጋ ከላይ በጠቀስኩት መፅሄት የሙስናውን ጨዋታ የገለፁት እንዲህ በማለት ነበር፡-
‹‹አሁንም ድረስ ያልተፈቱ የአካሄድ (የአሰራር) ችግሮች አሉ፡፡ ለምሳሌ ‹ሙስና አለ› ብትል፣ ሙስና በስርዓቱ ላይ በሚያደርሰው አደጋ ላይ ከማተኮር ይልቅ ‹አንተስ ከሙሰኛነት ነፃ ነህ ወይ?› በማለት ዋናው ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ የሚቸልሱ ሰዎች ጥቂት አይደሉም፡፡ አሁንም ቢሆን ይህንን የከፋ ድርጅታዊ ጉዳይ (ችግር) በመጋረጃ ሸፋፍኖ ለማለፍ ‹ስብሃት ለምን በጊዜው ጉባኤው ላይ አላቀረበውም ነበር› የሚሉ አይጠፉም የሚል ግምት አለኝ፡፡ በበኩሌ ይህ ነገር በሌላ ላይ ጊዜው ሲደርስ የሚነሳ ይሆናል ነው የምለው:፡››

በርግጥ የአቦይ ወቀሳ እውነት ነው፡፡ ይሁንና ጉዳዩን በጉባኤው ላይ ያላነሱበት ምክንያት ‹‹በሌላ ላይ ጊዜው ሲደርስ የሚነሳ ይሆናል›› በሚል እንደሆነ ለመናገር መሞከራቸው ግን የክፍለ ዘመኑ አስቂኝ ቀልድ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ የለውም፤ ባይሆን ‹‹አንተስ ከሙሰኛነት ነፃ ነህ ወይ?› ይሉኛል ብዬ ተውኩት›› ቢሉን፣ ቢያንስ ለግልፅነታቸው ባርኔጣ እናነሳ ነበር፡፡ ምክንያቱም በኢትዮጵያ ሰማይ ስር የኢህአዴግ ሰዎችን የሙስና ወንጀል በህግ የሚያስጠይቅ ከሆነ አቦይ ስብሃት ከፊት መስመር መሰለፋቸው አይቀርምና፡፡ ሌላው ቀርቶ አርከበ እቁባይ ለጊዜው ገለል እንዲል (ከሀገር እንዲወጣ) የተደረገው ከዚሁ ጋር በተያያዘ እንደሆነ የመረጃ ምንጮቼ ነግረውኛል፡፡ አርከብ፣ አቦይን ጨምሮ ከታሰሩት ባለሀብቶች ውስጥ ጥቂቶቹ በስጋ ዝምድናና በጋብቻ የተሳሰሩት የመሆኑ ጉዳይ ይመስለኛል ‹ማዕበሉ እስኪረጋ› ከዕይታ እንዲርቅ የተደረገበት ምስጥር፡፡ በተቀረ አርከበ ሀገር ጥሎ ኮበለለ፣ ኢህአዴግን ከዳ… ጂኒ ቁልቋል የሚሉት የፒያሳ ወሬዎች፣ አንድም ወቅታዊውን የኢህአዴግ አሰላለፍ ካለመረዳት ሊሆን ይችላል፤ አሊያም የጉዳዩ ባለቤቶች ስራዬ ብለው የተሳሳተ መረጃ በሚያስተላልፉበት በተለመደው ሰርጥ ያሰራጩት ማስቀየሻ ነው የሚሆነው፤ አርከበ የሄደው አቦይ እንዳሉት ‹‹አንተስ ከሙስና ነፃ ነህን?›› የማለቱ አቅም ያላቸውን አጉረምራሚ ሰዎችን ለማለዘብ ነው፡፡ ምናልባት የመቀሌው ህወሓት አሸንፎ ቢሆን ኖሮ እውነትም አርከበ ከቃሊቲ ይልቅ አሜሪካ ይሻለዋል ማለታችን አይቀርም ነበር፡፡ እነርሱም ቢሆኑ በእጁ ላይ ካቴና ለማጥለቅ አያመነቱም፡፡ ግና! የሆነው በተገላቢጦሹ ነው፡፡ …ማን ነበር ‹‹አባቱ ዳኛ…›› ያለው? (በነገራችን ላይ ኢህአዴግ የሙስና አዋጁንም በዚሁ ዓመት የማሻሻል ዕቅድ አለው፡፡)

የአፈናው ዝግጅት

ስርዓቱ በሚቀጥለው ዓመት የሚደረገው አምስተኛ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫን ከወዲሁ ‹የቤት ስራን በማጠናቀቅ› ካልተዘጋጀንበት፣ ያልተጠበቀ አደጋ ሊያመጣብን ይችላል ወደሚል ጠርዝ የተገፋው አንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ በተለያየ ጊዜ በጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የተገኘው ህዝብ ቁጥር አሳስቦት ብቻ አይመስለኝም፡፡ ይልቁንም ኢህአዴግ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ ያለ መለስ ዜናዊ የሚጋፈጠው የመጀመሪያው ምርጫ በመሆኑም ጭምር ነው፡፡ እንደሚታወሰው አቶ መለስ ሁሉንም የሥልጣን ምንጮች ጠቅልሎ የያዘ ‹ጠንካራ ሰው› (Strong Man) በመሆኑ፣ በእንዲህ አይነት ወቅት የሚመጡ ድንገቴ አደጋዎችን ለመቋቋም ብዙም ሲቸገር አይስተዋልም ነበር፡፡ ይሁንና በቀጣዩ ምርጫ አንድም በድርጅቱ ውስጥ የእርሱ አይነት ተተኪ ሰው አለመኖሩ፣ ሁለትም ምንም እንኳ ከህልፈቱ በኋላ የተፈጠረው ልዩነት በአንፃራዊነት የተረጋጋ ቢመስልም፣ ለሌላ ዙር የክፍፍል አደጋ አለመጋለጡ አስተማማኝ ባለመሆኑ ስጋት መፍጠሩ የሚጠበቅ ነው፡፡ በአናቱም ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር የተከሰተው አለመግባት እና በማህበረ ቅዱሳን ላይ ተፅእኖ ለማድረግ የመሞከሩ ጨዋታም ለተቀናቃኞች ያልተጠበቀ ኃይል ሊሆን የሚችልበት ዕድል ቢፈጥርስ የሚል ስጋት አለ፡፡

የባለሥልጣናቱ በአደባባይ የማስፈራራት መግፍኤም ይኸው ነው፡፡ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማሪያም በቃለ-መጠይቁ ላይ ተቃዋሚዎችን (አንድነትና ሰማያዊን) እና የሀይማኖት ማህበራትን ለማስፈራራት ከሰባት ጊዜ በላይ የመለስን ‹‹ቀይ መስመር›› አገላለፅ ተጠቅሞበታል፡፡ በተለይም ሁለቱ ፓርቲዎች የያዙት በሠላማዊ ሠልፍ ተፅዕኖ የመፍጠር መንገድ ተከታዮቻቸውን እያበዛ እና የፈዘዘውን የፖለቲካ ተሳትፎ እያነቃቃው መሆኑን ግንባሩ ጠንቅቆ የተረዳው ይመስለኛል፡፡ በኃ/ማሪያምም በኩል ያስተላለፈው መልዕክትም ቀጣዩን የፖለቲካ ሴራ አመላካች ነው፡-

‹‹መታወቅ ያለበት አንድ ጥያቄ በተደጋጋሚ የሚጠየቅ ከሆነ፣ እኛም አንድ ቦታ ስንደርስ ‹ለዚህ ጥያቄ ብዙ ጊዜ መልስ ሰጥተናል፤ ጥያቄው ይህ ከሆነ የሠልፍ ትርጉም ምንድነው?› ብለን የምናቆምበት ደረጃ እንደርሳለን፡፡ ምክንያቱም ሠልፍ ለዘላለም የሚካሄድበት ሀገር ያለ አይመስለኝም፡፡››

በተመሳሳይ መልኩ የሃይማኖት ማህበራት የሚያነሱትን የመብት ጥያቄም ወዴት ሊገፋው እንደሚችል ጥቁምታ ሰጥቷል፡-
‹‹የሀይማኖት ግብንም አክራሪዎች በምድር ላይ ሊሰሩ የሚፈልጉትን ግብ ሁለቱን የሚያምታቱ ሰዎች አሉ፤ የሌላውን ግብ በምድራዊ ዓለማዊ ማሳካት ስለማይቻል፣ እነዚህ ፖለቲከኞች ይዘዋቸው እንዳይነጉዱ፣ ከህዝብ እንዲነጠሉ ምክር ማስተላለፍ እፈልጋለሁ፡፡ የሚታወቁ ስላሉ፡፡ በተለይ ወጣቶች፣ ከወጣቶችም ወጣት ሴቶች በአሁኑ ወቅት በዚህ ውስጥ ተሳትፈው የሚጓዙ እንዳሉ በግልፅ ይታወቃሉ፡፡ መንግስት በዚህ ደረጃ ለእነዚህ አካላት መልዕክት ማስተላለፉ ጠቃሚ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡››
የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤትን በሚንስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚመራው ሽመልስ ከማልም ከ‹‹ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)›› ጋር ያደረገውና ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም በታተመው ‹‹አዲስ ዘመን›› ጋዜጣ ላይ በወጣው ቃለ-ምልልስ እንደተለመደው ጉዳዩን በተመለከተ ጠንከር ያለ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ ለማስተላለፍ የፈለገ (የታዘዘ) መስሎ አግኝቸዋለሁ፡-
‹‹አንዳንድ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሕጉን እናሰርዛለን፣ ሕጉ ሰብዓዊ መብት የሚጥስ ነው ብለው በአደባባይ የቅጥፈት ፕሮፓጋንዳ ሲያሰሙ የሚታዩና በተዘዋዋሪ መንገድ ከሽብርተኞች ጋር ለሽብርተኞች የሞራል ድጋፍ ሲሰጡና ሲቸሩ የምናያቸው አንዳንድ ወገኖች ሳያውቁ፣ ግንዛቤ ሳይኖራቸው በቀና መንገድ ተሳስተው ነው የሚል ግምት ሊኖር የሚገባው አይመስለኝም፡፡ 

እነዚህ ወገኖች አውቀው ነው ይህንን ሥራ የሚሰሩት፤ በስሌት ነው ይህን የሚከናውኑት፡፡››

በእርግጥም የስርዓቱ የሴራ ቀማሪዎች ‹‹አንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ የፈጠሩት መነቃቃት፣ በጊዜ ካልተቋጨ በሚቀጥለው ዓመት በሚደረገው ምርጫ ‹ባልታወቀ ስፍራ የተኛ ሰይጣን ቀስቅሶ፣ ድንገቴ ማዕበል ሊያስነሳ ይችላል›› የሚለው ትንተናቸው ይመስለኛል ቀድሞም የጠበበውን ምህዳር ይበልጥ ለማጥበብ (ለመድፈን) ከወዲሁ እላይ-ታች እንዲሉ ያስገደዳቸው፡፡

እንደ መውጫ

ስርዓቱ በብዙ መልኩ ያለ ስኬት ከሃያ ሁለት ዓመታት በላይ መጓዙ እርግጥ ነው፡፡ በተቃውሞ ሰፈርም ይህንን ሁናቴ ለመለወጥ አብዛኛውን ዓመታት የበረዶ ያህል ቢቀዘቅዝም፣ አልፎ አልፎ እየጋመ ለውጥ ለማምጣት ያደረገው ሙከራ፣ አገዛዙ ካከማቸው ኃይል ጋር ባለመስተካከሉ ደጋግሞ መምከን አሳዛኝ ዕድል ፈንታ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በዚህ ዓመት የተያዘው ዕቅድም ከቀድሞ በባሰ መልኩ፣ ለመደራጀት የሚውተረተረውን ኃይልም ሆነ ተበታትኖና ተከፋፍሎም ቢሆን ለውጥ የሚጠይቀውን ህዝብ በተለያየ መንገድ ማቀዝቀዝ ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ጉዳዩን በደንታቢስነት ማየቱ ይህ እውን ሆኖ የ2002ቱ የምርጫ ድል፣ በ2007 ዓ.ምም ይደግም ዘንድ ፍቃድ የመስጠት ያህል ነው የምለው፡፡

አሁንም አረፈደም፡፡ ነገር ግን ፈረንጅኛው እንደሚለው ‹‹እውነቱ ግድግዳው ላይ ተፅፏል›› የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ለውጥ ፈላጊ ዜጎች… ስርዓቱ ለህዝብ ፍላጎት ይገዛ ዘንድ ከዚህ ቀደም ያልተሞከሩ (በሰላማዊ ትግል ማዕቀፍ ውስጥ ያሉ) አማራጮችን ከመተግበር ውጪ ጠረጴዛው ላይ የተቀመጠ ተጨማሪ ‹የዕድል ቁጥር› አለመኖሩን መቀበል ይኖርባቸዋል፡፡

በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ውጥረት አይሏል::

ethiopian_troops_pickupOctober 21/2013


ሌ/ጄ ሳሞራ የኑስ በሜ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀል ለመተካት የሚደረገው ሩጫ ተቃውሞ ገጥሞታል::
ከፍተኛ ጄኔራሎች ምስጢራዊ ስብሰባዎችን አብዝተዋል::የምስጢራዊ ስብሰባ ቃለ ጉባዬ የምትይዝ የሆነችው የአንድ ከፍተኛ ጄነራል ጸሃፊ ትክዳ ወይም ትገደል አልታወቀም::ለሜ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀል የተሰጠው የሌ/ጄ ማእረግ የታሰበው ሌ/ጄ ሳሞራን ይተካሉ ተብለው ለነበሩት ለሜ/ጄ አበባው ታደሰ የነበረ ቢሆንም በምን ምክንያት እንደተዘዋወረ አልታወቀም::

በሰሜን እዝ እና በምስራቅ እዝ የተከሰተው የሰራዊቱ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና የጥቅማ ጥቅም አቤቱታ በመላው ሃገሪቱ ተስፋፍቶ በከተማ እና በሌሎች የእዝ መምሪያዎችም መቀጠሉን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቁመዋል::በተለያዩ ጊዜያት እየተንከባለለ የመጣው ይህ የሰራዊቱ አቤቱታ እጅግ አደገኛ አዝማሚያ እያሳየ ሲሆን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እንዲወገድ እና ህገመንግስታዊ መብቶች እንዲከበሩ ጥያቄዎች ገፍተው መምጣታቸው ሲታወቅ ከፍተኛ የሕወሓት ጄኔራሎች በየቀኑ ካለማቋረጥ ምስጢራዊ ስብሰባዎችን እያደረጉ ከመሆኑም በላይ ከየእዙ የሚመጣላቸው ሪፖርት መፍታት የሚቻልበትን ጉዳይ እየተወያየኡ መሆኑ ተጠቁሟል::

ሰራዊቱ በኑሮ ውድነት እና በተቃዋሚዎች ህገመንግስታዊ መብቶች ላይ ያነሳው ጥያቄ አዛዦቹን ያስደነገጠ ከመሆኑም በላይ በአንድ ብሄር ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እስከመቼ የሚለውም ጥያቄ መመለስ አለበት በሚል የእግር እሳት እየሆነባቸው ነው:: በቅርቡ ከስልጣን ይነሳል የሚባለው ሌ/ጄ ሳሞራ የኑስን በሜ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀል ለመተካት የሚደረገውን ጥረት የብኣዴን ታጋይ መኮንኖች የተቃወሙት ሲሆን እኛም ከማንም ያላነሰ የታገልን ስለሆነ ለቦታው ብቁ የሆነ ሰው ብኣዴን እያለው ለምን እንዲህ ይደረጋል የሚል ጥያቄ አንስተዋል::

ከፓርቲ አጣብቂኝ ያልተላቀቀው የመከላከያ ሰራዊቱ የበላይ አመራር ህገመንግስታዊ መዋቅር እንዲይዝ ለማድረግ ምንም አይነት ስራ አለመሰራቱ በሰራዊቱ አዳዲስ መኮንኖች ዘንድ አቤቱታ ቢያስነሳም ጄኔራሎቹ የሚያደርጉት ምስጢራዊ ስብሰባ እንዴት መፍታት ሳይሆን ማክሸፍ እንደሚቻላቸው እየመከሩ ሲሆን አዳዲስ ወታደራዊ ደህንነቶችን በየእዙ አስርጎ በማስገባት እንዲሁም የሰራዊቱን አቤቱታ ያስተባብራሉ የሚባሉትን በስራ ምክንያት በየማእዘኑ በመበተን ለመስራት የታቀደ ሲሆን የአበታተኑን ሁኔታ በማስጠናት ላይ መሆናቸው ታውቋል:: በተጨማሪ የሚደርስባቸውን ጥቃት ለመከላከል ይረዳቸው ዘንድ ኮማንዶዎችን እና ንቁ የደህንነት ጠባቂዎችን ለራሳቸው እና ለቤተሰቦቻቸው ለመመደብ ተነጋግረዋል::

መከላከያ ሚኒስቴር ውስጥ ምዽር ጦር መምሪያ እንዲሁም ደብረዘይት እና አስፈላጊም ሲሆን በመኖሪአ ቤቶቻቸው የሚያደርጉትን ስብሰባ ቃለጉባዬ የምትይዘው የአንድ ጄኔራል ጸሃፊ ከድታ ይሁን ተገድላ ሳይታወቅ ካለፈው ሳምንት ጀምራ በስራ ገበታዋ ላይ ያልተገኘች እና የት እንዳለች የማይታወቅ ሲሆን ስልኳም መዘጋቱን ምንጮቹ አያይዘው ጠቁመዋል::

ምንሊክ ሳልሳዊ

Systematisk tortur av politiske fanger i Etiopia


  • October 20/2013

    Etiopisk opprørspoliti slo hardt ned på opptøyene i landet i 2005. Siden den gang av menneskerettighetssituasjonen i landet forverret seg kraftig, ifølge Human Rights Watch.
    FOTO: ANDREW HEAVENS, REUTERS

Systematisk tortur av politiske fanger i Etiopia

Opposisjonspolitikere, journalister og regimekritikere blir utsatt for systematisk tortur på en politistasjon i Addis Abeba, viser ny rapport
Torturmetodene som brukes er blant annet slag mot kroppen med harde gjenstander og pisking. Fanger blir også hengt fra taket i svært smertefulle posisjoner.

Human Rights Watch-rapporten, som presenteres i dag, gir et detaljert bilde av mishandlingen som foregår i landets beryktede Federal Police Crime Investigation Sector. Politistasjonen, som er kjent under navnet Maekelawi, ligger i hjertet av hovedstaden Addis Abbeba.

Flere menneskerettighetsaktivister har tidligere meldt om grufulle forhold ved Maekelawi. Denne ferske rapporten har gått systematisk til verks og intervjuet 35 tidligere innsatte ved Maekelawi og deres familiemedlemmer.

- Sparket meg i munnen med støvelen

En tidligere innsatt har fortsatt arr etter torturen.
- De sparket meg i munnen med støvelen, og da mistet jeg fire tenner, sier han.

En annen beskriver hvordan han ble holdt i en smertefull posisjon og så slått.
 
- De tok av skoene og sokkene mine og plasserte en pinne bak knærne mine. Så rullet de meg rundt og slo mot fotsålene mine, sier han.


Les også



– Svenske journalister i Etiopia holdt på å bli skutt

De to svenske journalistene som ble tatt til fange i Etiopia, skal nesten ha blitt skutt av soldater, ifølge Sveriges ambassadør til landet.

Flere beskriver å ha blitt dynket med iskaldt vann og hengt med hendene i taket slik at kun tåspissene nådde gulvet. Human Rights Watch og andre menneskerettighetsorganisasjoner har ikke tilgang til fengselet, men har sjekket de innsattes historier opp mot hverandre for verifisering.

Politisk styrt rettsvesen

Etiopias regjeringsparti – Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) – har styrt landet i over 20 år. Etter det omstridte valget i 2005, har myndighetene slått knallhardt ned på opposisjon og dissens.
Anti-terrorlovene fra 2009 er blitt brukt til å fengsle både journalister og opposisjonelle.
Samtidig som menneskerettighetssituasjonen i landet er blitt vanskeligere de siste årene, har landet hatt en stabil, økonomisk vekst i mange år.

Landets nå avdøde statsminister Meles Zenawi hadde et godt forhold til vestlige ledere, blant annet den norske regjeringen. Etiopia fikk i 2012 228 millioner kroner i bistand fra Norge.

Den siste rapporten forholdene på politistasjonen i Addis Abeba står i grell kontrast til beskrivelser av Etiopia som løfter millioner ut av fattigdom. Etiopias rettssystem er ikke uavhengig av regjeringspartiet, noe som blir ekstra tydelig i behandlingen av politiske fanger.

Torturen har ofte til hensikt å få fanger til å signere forklaringer og falske tilståelser. Blant fangene som ble bedt om å signere slike papirer var de svenske journalistene Johan Persson og Martin Schibbye som satt fengslet i det beryktede fengselet i 2011.

source,,,http://www.aftenposten.no/nyheter/uriks/Systematisk-tortur-av-politiske-fanger-i-Etiopia-7343315.html#.UmS9qHAWL_Y

Sunday, October 20, 2013

Eritrean Norwegian 23 Left a Wife and a Newborn to Fight a Jihad War in Syria


Islamic Jihad
Eritrean Norwegian 23 Left a Wife and a Newborn to Fight a Jihad War in Syria
How did 23-year-old's life from pike fishing to holy war
As a youth he loved pike fishing. Now he is fighting in Syria.
By kadafi Zaman | www.tv2.no
According to the Police Security Service (PST) has at least 30 to 40 people traveled from Norway to fight in Syria. Now, TV2 tell the story of one of them, 23-year-old "Ali".
He came from Eritrea to Norway as an unaccompanied migrant on September 9th 2003. When he was only 13 years.
The first residence was a reception center just outside Oslo. After a short time he had a Norwegian foster family in Bærum. Tor Bach in the multicultural outdoor organization Wild X was often visited by Norwegian-Eritreans.
- I remember him as a happy, well-adjusted and securely boy who got along with everyone, says Bach.
23-year-old "Ali" came to Norway as an unaccompanied asylum seeker in 2003.23-year-old "Ali" came to Norway as an unaccompanied asylum seeker in 2003. © Private
He says that the boy was with several fishing trips arranged by leisure organization.
- We were ice fishing and pike fishing. He got one six-pound pike. He was brilliant bland and very proud to have received the pike is, says Bach.
- Talked about shooting Jews
For five years the boy lived with his Norwegian foster family. He played football and got good grades from high school.
TV 2 has spoken to several sources familiar with Norwegian-Eritreans. They will not stand up, but describes him as a dutiful and kind person.
In 2010 he worked as a nursing staff member at an institution in Bærum. He worked for a time as well as a student assistant at a school in Drammen.
Right after high school he moved to Volda to study.
According to TV2's sources, he changed himself after he left home. They say that he came back shortly with a more conservative approach to the religion of Islam.
Spring 2012 called Norwegian-Eritreans to Tor Bach and asked if he could take hunting test with three friends. Bach welcomed him, but said he was surprised when they met.
According to TV2's sources changed the 23-year-old "Ali" after he left home.According to TV2's sources changed the 23-year-old "Ali" after he left home. © Private
- I saw a completely different boy. Then I saw a guy with a long beard and angry eyes, and friends who talked about shooting Jews, says Bach.
Do you have tips about this matter? Contact us attips@tv2.no
Radicalized in a short time
TV 2 is known that the three individuals Norwegian-Eritreans had with them are key figures in the extreme grouping Prophet's Ummah.
- They would have access to weapons and thought that hunting proficiency test course was a great way to arrange it. We managed to sabotage so that none of them had access to weapons, says Tor Bach.
From January 2011 to September 2012 worked the then 22 year old man as a parking guard in Oslo. During this period he also married a Norwegian-Eritrean woman.
According to TV2's sources were Norwegian-Eritreans radicalized within a very short time. He was greatly inspired by jihadist propaganda films from Syria.
In December 2012 left the 23-year-old Norway and headed for Syria. Back set one wife and one just a few weeks old baby.
Deleted Facebook account
For the first time tells the Police Security Service about how many people have traveled from Norway to fight in Syria.
- We assume that there may be between 30 and 40 people, but it is unrecorded and figures may be higher, says the PST-head Benedicte Bjørnland to TV 2
For ten months, the 23-year-old fought in Syria. TV2 know that he is alive and that he is in jihadistbrigaden, Kataib al-Muhajereen. It is associated with the so-called al-Nusret-front.
- We are seeing a worrying increase in traveling from Norway to conflict areas. Previously we have not seen so many go at once so adapted to the same place, says Bjørnland.
- Where do they travel?
- It is primarily Syria, says PST boss.
Norwegian-Eritreans deleted a short time ago his Facebook account and there is almost no trace of him on the internet. It has not succeeded TV 2 to get in touch with the man.

Saturday, October 19, 2013

የ 2013 የዓለም የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት፡- ኢትዮጵያ

October 19/2013
ኢትዮጵያን ለረጅም ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩትና ሰፊ ስልጣን የነበራቸው መለስ ዜናዊ በነሃሴ ወር በድንገት መሞት በሃገር ውስጥም ሆነ በኢትዮጵያ ዓለማቀፍ አጋሮች ዘንድ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ ሽግግር የሚመለከቱ ጥያቄዎችንና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን አስነስቶ ነበር።በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተለይ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እየከፋ ሄዷል።አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በመስከረም ወር ስልጣኑን የተረከቡ ቢሆንም መንግስት በርሳቸው አመራር ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ለውጦች ያደርግ ወይስ አያደርግ እንደሆነ ገና የሚታይ ነው።
እ.ኤ.አ በ2012ም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት መሰረታዊ የሆኑትን ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች በጥብቅ መገደባቸውን ቀጥለዋል።ለኣሻሚ ትርጉሞች በተጋለጠውና በ2002 ዓ.ም በወጣው የሀገሪቱ የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ 30 ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።በዋና ከተማዪቱ አዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል የእስልምና እምነት ተከታዮች ላካሄዷቸው የተቃውሞ ሰልፎች የጸጥታ ሃይሎች የሰጡት ምላሽ የዘፈቀደ አፈሳ፣ እስር እና ድብደባ ነበር።
የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ክልሎች የሚኖሩ የገጠር ነዋሪዎችን የተሻለ የመሰረታዊ ግልጋሎቶች አቅርቦት ሊያገኙ ወደሚችሉባቸው አካባቢዎች ለመውሰድ በሚል ምክንያት 1.5 ሚሊዮን የገጠር ነዋሪዎችን መልሶ ለማስፈር የሚያካሂደውን የሰፈራ ፕሮግራም ቀጥሎበታል።በጋምቤላ ክልል የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች ከፍላጎታቸው ውጭ በሃይል እንዲፈናቀሉ በመደረጋቸው ለከፍተኛ ችግሮች ተጋልጠዋል። ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ለሚያካሂደው ሰፊ የስኳር ልማት መሬት ለማስለቀቅ ሲባል በኢትዮጵያ የታችኛው ኦሞ ሸለቆ ነዋሪ የሆኑትን አርብቶ አደር ማህበረሰቦች ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው።
ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች
መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶችን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር የበጎ አድራጎት ደርጅቶች እና ማህበራት አዋጅ እንዲሁም የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ በ2002 ዓ.ም ከታወጁ ወዲህ በኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ከፍተኛ ገደብ ተጥሎባቸዋል። እነዚህ ሁለት ሕጎች መንግስት በሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች፣በጋዜጠኞች እና በሌሎችም የመንግስትን ፖሊሲ በሚተቹና መንግስት እንዲነሱ በማይፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳባቸውን በሚገልጹ ሰዎች ላይ ካካሄደው ሰፊ እና የማያቋርጥ ማዋከብ፣ዛቻ እና ማስፈራራት ጋር ተዳምሮ ያስከተሉት ውጤት የከፋ ነው።
ኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ የጎላ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች እንቅስቃሴዎቻቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንሱ ወይም ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ከስራ ዝርዝራቸው ውስጥ እንዲያወጡ የተገደዱ ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቀ ድርጅቶችም ጭራሹኑ ተዘግተዋል። በደረሰባቸው ማስፈራሪያ ምክንያት ሰፊ ልምድና መልካም ስም የነበራቸው ብዙ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ሃገሪቱን ለቀው ሄደዋል። አሁን ሰፍኖ የሚገኘው ሁኔታ ለነጻ ፕሬስ እንቅስቃሴም እንዲሁ የተመቸ አይደለም።ባለፉት አስር ዓመታት በደረሰባቸው ዛቻ እና ማስፈራራት ሳቢያ ሃገራቸውን ለመልቀቅ በተገደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር በዓለም ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ናት። የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሆነው ድርጅት ሲፒጄ እንደሚገልጸው ቢያንስ 79 ጋዜጠኞች ሃገራቸውን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል።
የጸረ ሽብርተኝነት አዋጁ፣ ተቃዋሚ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሰዎችን ዒላማ ለማድረግ፣ተቃውሞን ለማፈን እና ጋዜጠኞችን ዝም ለማሰኘት ስራ ላይ እየዋለ ነው። እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም 30 የፖለቲካ መሪዎች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንዲሁም ጋዜጠኞች በግልጽ ባልተብራሩ የሽብርተኝነት ወንጀሎች ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።ከ2011 ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ 11 ጋዜጠኞች በዚሁ ሕግ ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።
ጥር 17 ቀን 2004 ዓ.ም አሁን የተዘጋው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ በነበረው ውብሸት ታዬ እና የጋዜጣው ዓምደኛ በነበረችው ርዕዮት ዓለሙ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኝ ፍርድ ቤት የ 14 ዓመታት እስር ፈርዶባቸዋል።የርዕዮት ዓለሙ ፍርድ በኋላ በይግባኝ ወደ አምስት ዓመታት የተቀነሰ ሲሆን ከቀረቡባት ክሶች ውስጥም አብዛኞቹ ተሰርዘዋል።
ከፍተኛ ክብር ያለውን የፔን አሜሪካ ፍሪደም ቱ ራይት ሽልማት በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ያሸነፈው አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ብሎገር እስክንድር ነጋ ሐምሌ 6 ቀን 2004 ዓ.ም ከሌሎች ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር በቀረበበት ክስ የ 18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበታል። በስደት ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች አብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽም እስካሁን ድረስ ጋዜጠኞች ላይ ብቻ ተግባራዊ በተደረገው የጸረ ሽብርተኝነት ሕጉ አንቀጽ መሰረት ጥፋተኛ ተብለው እያንዳንዳቸው የ 8 ዓመታት እስራት ተፈርዶባቸዋል። በይፋ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀሰው ተቃዋሚ ፓርቲ አንድነት ለፍትሕ እና ለዲሞክራሲ አባል የሆነው አንዷለም አራጌ በስለላ፣ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በመናድ እንዲሁም የሽብር ተግባር ለመፈጸም ምልመላ እና ስልጠና በማካሄድ ወንጀሎች ጥፋተኛ ተብሎ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል።
በመስከረም ወር 2004 ዓ.ም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእስክንድር ነጋ እና በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ አበበ በለው እንዲሁም የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባሉ አንዷለም አራጌ ንብረቶች እንዲወረሱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ፍትሕ ጋዜጣ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያካሂዱትን ተቃውሞ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጤንነት ሁኔታ አስመልክቶ ያዘጋጃቸው ዘገባዎች የሃገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው በማለት መንግስት ሀምሌ 20 ቀን ጋዜጣው እንዳይሰራጭ አግዷል። ነሃሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ በቁጥጥር ስር ውሎ ዋስትና ተከልክሏል። ተመስገን ነሃሴ 24 ቀን ከእስር የተለቀቀ ሲሆን ተጨማሪ ምርመራ እስኪካሄድ ድረስ ሁሉም ክሶች ተነስተውለት ነበር።
ሀምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ የተሰኘው ተወዳጅ የሙስሊሞች መጽሄት ዋና አዘጋጅ የሆነው የሱፍ ጌታቸው ቤት በፖሊሶች የተፈተሸ ሲሆን በዚያው ዕለት ምሽትም የሱፍ በቁጥጥር ስር ውሏል። መፅሄቱ ከዚያ በኋላ መታተም ያቆመ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከሚዘጋጅበት ጊዜም የሱፍ በቁጥጥር ስር ይገኛል።
በሕገ ወጥነት ከተፈረጀው አማጺው የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ጋር በምስራቃዊ ኢትዮጵያ ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ማርቲን ሺብዬ እና ዮሃን ፒርሰን የተባሉ ሁለት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ለሽብርተኛ ድርጅት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል ታህሳስ 17 ቀን 2004 ዓ.ም የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል። በተጨማሪም በሕገ ወጥ መንገድ ወደሃገሪቱ በመግባት ጥፋተኞች ተብለዋል።ፍርድ ቤቱም በ 11 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኗል። ሁለቱ ጋዜጠኞች አዲሱን ዓመት በማስመልክት በየዓመቱ ለእስረኞች በሚሰጠው ምህረት ከሌሎች 1950 በላይ ከሚሆኑ እስረኞች ጋር ምህረት ተደርጎላቸው ጳጉሜ 5 ቀን 2004 ዓ.ም ከእስር ተለቀዋል።
መንግስት በሃገሪቱ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ጉዳዮች ምክር ቤት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ለታቃውሞ የወጡ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ለመበተን በሐምሌ ወር 2004 በተለያዩ ቀናት የፌደራል ፖሊስ ድብደባን ጨምሮ ከልክ ያለፈ ሃይል ተጠቅሟል።ሀምሌ 6 ቀን አዲስ አበባ ወደሚገኘው የአወሊያ መስጊድ በሃይል በመግባት ፖሊሶች መስኮቶችን የሰባበሩ ሲሆን በመስጊዱ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ ተኩሰዋል። ሐምሌ 14ም በመስጊዱ ለተቃውሞ ተቀምጠው የነበሩ ሰዎችን ሃይል በመጠቀም እንዲበተኑ አድርገዋል። ከሐምሌ 12 እስከ 14 በነበሩት ቀናትም በርካታ ሰዎች የታፈሱ ሲሆን 17 ከፍተኛ የእምነቱ መሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ክስ ሳይመሰረትባቸው ከአንድ ሳምንት በላይ በእስር ቆይተዋል።ብዙዎቹ ታሳሪዎች በእስር ላይ እያሉ ማንገላታት እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።
ተገዶ መፈናቀል
ሰፈራ በሚባለው ፕሮግራሙ የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ቆላማ ክልሎች ማለትም በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣በአፋር፣ በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች እና ሕዝቦች እንዲሁም በሶማሌ ክልሎች የሚኖሩ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎችን የተሻለ የመሰረታዊ አገልግሎቶች አቅርቦት ወደሚያገኙባቸው አካባቢዎች ለማዛወር በሚል ወደሌሎች ቦታዎች ወስዶ ለማስፈር እቅድ አለው።
በጋምቤላ እና በደቡብ ኦሞ ሸለቆ ከነዋሪዎች ጋር በቂ የቅድሚያ ምክክር ሳይደረግ እና የካሳ ክፍያ ሳይፈጸም አስገድዶ የማፈናቀል ተግባር እየተፈጸመ ነው።ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳረጋገጠው በተለይ በጋምቤላ ወደሌሎች አካባቢዎች አዛውሮ የማስፈሩ ሂደት የሚከናወነው ብዙ ጊዜ ነዋሪዎቹን ለም የሆኑ መሬቶቻቸውን በማስለቀቅ አነስ ያለ ለምነት ወዳላቸው መሬቶች በማስፈር ነው።ወደ አዳዲሶቹ መንደሮች እንዲሰፍሩ የሚላኩት ሰፋሪዎች አብዛኛውን ጊዜ መሬታቸውን መመንጠር እና ጎጆዎቻቸውን መስራት ያለባቸው ሲሆን ይህንንም በወታደሮች ተቆጣጣሪነት ያከናውናሉ።ቃል የተገቡላቸው አገልግሎቶች ማለትም ትምህርት ቤቶች፣ክሊኒኮች እና የውሃ ፓምፖች የተሟሉ አይደሉም።
በደቡብ ኦሞ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ ሺህ የሚደርስ ተወላጅ ሕዝቦች መንግስት ለሚያካሂደው የስኳር ልማት ቦታ ለማስለቀቅ ሲባል መሬታቸው ተወርሶ ወደሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍሩ እየተደረገ ነው። ነዋሪዎቹ ከመሬቶቻቸው ላይ በሃይል እነደሚነሱ፣የግጦሽ መሬቶቻቸው በጎርፍ እንዲጥለቀለቁ እንደሚደረግ፣ ማሳዎቻቸው እንደሚገለበጡ እንዲሁም ለህልውናቸው እና ለአኗኗር ዘይቤአቸው እጅግ አስፈላጊ የሆነውን የኦሞ ወንዝ ውሃ እንዳያገኙ እንደሚከለከሉ ተናግረዋል።
ሕገ ወጥ ግድያ፣ማሰቃየት እና በቁጥጥር ስር ባሉ ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ጥሰቶች
በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጋሸሞ ወረዳ ራቅዳ በተባለች መንደር ከነዋሪዎች ጋር የተፈጠረን ግጭት ተከትሎ ‘ልዩ ሃይል’ በሚል ስያሜ የሚታወቅ፣ በኢትዮጵያ መንግስት የሚደገፍ ታጣቂ ቡድን በቁጥጥሩ ስር የነበሩ 10 ሰዎችን እና ሌሎች 9 የመንደሩ ነዋሪዎችን የገደለው መጋቢት 7 እና 8 ቀን 2004 ዓ.ም ነበር።
በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ማንነታቸው ያልታወቀ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች በጋምቤላ ክልል በሚገኝ እና ባለቤትነቱ የሳውዲ ስታር ኩባንያ በሆነ ሰፊ እርሻ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል። ይህ የእርሻ ልማት በክልሉ የሰፈራ ሂደት በተካሄደበት ወቅት የከፋ የመብቶች ጥሰቶችና ማንገላታት ከተፈጸመባቸው አካባቢዎች በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። ለዚህ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት የኢትዮጵያ ወታደሮች ቤት ለቤት በመዞር ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን የፈለጉ ሲሆን የአካባቢውን ነዋሪዎችም ‘አማጺያኑ’ የሚገኙበትን ቦታ አጋልጡ በማለት ሲያስፈራሯቸው ነበር። ወታደሮቹ በርካታ ወጣት ወንዶችን በዘፈቀደ ከማሰራቸውም በላይ ስለ ጥቃቱ መረጃ ለማግኘት ባደረጉት ሙከራ ማሰቃየት፣አስገድዶ መድፈር እንዲሁም ሌሎች ጥሰቶችን በብዙ ነዋሪዎች ላይ ፈጽመዋል።
ሂዩማን ራይትስ ዎች በአዲስ አበባ ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጣቢያ እና በክልሎች በሚገኙ የእስር ቦታዎች እንደዚሁም በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በጋምቤላ ክልሎች በሚገኙ ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ የሚፈጸሙ የማሰቃየት ድርጊቶችን የሚመለከቱ መረጃዎችን ማሰባሰቡን ቀጥሏል። በእነዚህ የእስር ጣቢያዎች ከፖለቲካ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተያዙ ታሳሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበት እድል በጣም የመነመነ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ከፍርድ ሂደት በፊት እና በፍርድ ሂደት ወቅት ሊከበሩላቸው የሚገቡ መብቶችን ለማክበር ያለው ፍላጎትም በጣም አናሳ ነው። ይህም ታሳሪዎቹን ለከፉ ጥሰቶች ያጋልጣቸዋል።
የስደተኛ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች አያያዝ
በሊባኖስ የቤት ሰራተኛ የነበረቸው ኢትዮጵያዊት ዓለም ደቻሳ ደሲሳ ድብደባ ሲፈጸምባት የሚያሳየው ቪዲዮ ከተሰራጨና ይህነኑ ተከትሎም ዓለም መጋቢት 5 ቀን 2004 ዓ.ም ሕይቷን ካጠፋች በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት በመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት በቤት ሰራተኝነት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የሚደርስባቸው መከራ የተጠናከረ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ብዙ በስደት የሚሰሩ የቤት ሰራተኞች ወደ ውጭ ሃገራት ሄደው ከመቀጠራቸው በፊት ከባድ የገንዘብ ዕዳ ውስጥ ይገባሉ፤ እንዲሁም ከቅጥር ሂደቱ ጋር የተያያዙ ሌሎች ማንገላታቶች ይፈጸሙባቸዋል።ውጭ ሀገር ሄደው ስራ ከጀመሩም በኋላ ለረጅም ሰዓታት ከመስራት በተጨማሪ ባርነት በሚመስሉ የስራ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሰሩ ይደረጋሉ፣ እንዲሁም ሌሎች መጠነ ሰፊ ጥቃቶች ይደርሱባቸዋል።(የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ሳኡዲ አረቢያ እና ሊባኖስን የሚመለከቱትን ምዕራፎች ይመልከቱ)።
ዋና ዋና ዓለማቀፍ አጋሮች
በመለስ ዜናዊ አመራር ኢትዮጵያ በአካባቢ ጉዳዮች ላይ የጎላ ሚና ትጫወት ነበር።ወደ አወዛጋቢው የሱዳን አቢዬ ክልል በተባበሩት መንግስታት ስር የሰላም አስከባሪ ሃይሎችን አሰማርታለች፣በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካከል የነበረውን አለመግባባት ሸምግላለች እንዲሁም አል ሸባብን ለመውጋት የተደረገውን ዓለማቀፍ ጥረት ለማገዝ ሰራዊቷን ወደሶማሊያ ልካለች። እ.ኤ.አ ከ 1998-2000 ድረስ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደውን ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጎረቤቷ ኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት መልካም አይደለም። ኤርትራ ለግጭቱ መነሻ የነበሩ ቦታዎች ለኤርትራ እንደሚገቡ የወሰነውን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ የተቀበለች ሲሆን ኢትዮጵያ ግን ውሳኔውን አልተቀበለችም።
ኢትዮጵያ ለምዕራብ መንግስታት ጠቃሚ ስትራተጂያዊና የደህንነት አጋር ስትሆን ከእነዚህ መንግስታት በአፍሪካ ከፍተኛውን የልማት እርዳታ የምታገኝ ሀገርም ናት።በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓመት ወደ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ የአሜሪካን ዶላር በረጅም ጊዜ የልማት እርዳታ መልክ ታገኛለች።የለጋሽ ሃገራት ፖሊሲዎች በሀገሪቱ እየከፋ ከሄደው የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጋር በተያያዘ ብዙም የተለወጡ አይመስሉም።
እ.ኤ.አ በመስከረም ወር 2012 የዓለም ባንክ ራሱ እና ሌሎችም የልማት ተቋማት ዘለቄታ ላለው ልማት እጅግ አስፈላጊ ናቸው የሚሏቸውን የሰብአዊ መብቶች እና የመልካም አስተዳደር መርሆች ብዙም ከግምት ውስጥ ያላስገባ አዲስ ብሔራዊ የጋራ ሰትራተጂ ባንኩ አጽድቋል።ባንኩ በተጨማሪም ሦስተኛውን ዙር የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥበቃ ፕሮግራም (ፒቢኤስ 3)ያለፈቃድ የሚደረግ ሰፈራን የሚከለክሉ እና ለተወላጅ ሕዝቦች ጥበቃዎችን የሚያደርጉ ድንጋጌዎችን ሳያካትት አጽድቋል።

Police Abuse Journalists, Opponents to Extract Confessions – Human Rights Watch

October 18/2013

Ethiopia: Political Detainees Tortured

Police Abuse Journalists, Opponents to Extract Confessions

“They Want a Confession” Torture and Ill-Treatment in Ethiopia’s Maekelawi Police Station
- Full report in English
- Summary and recommendations in Amharic
- Press release in Afan Oromo

(Nairobi) – Ethiopian authorities have subjected political detainees to torture and other ill-treatment at the main detention center in Addis Ababa. The Ethiopian government should take urgent steps to curb illegal practices in the Federal Police Crime Investigation Sector, known as Maekelawi, impartially investigate allegations of abuse, and hold those responsible to account.

The 70-page report, “‘They Want a Confession’: Torture and Ill-Treatment in Ethiopia’s Maekelawi Police Station,” documents serious human rights abuses, unlawful interrogation tactics, and poor detention conditions in Maekelawi since 2010. Those detained in Maekelawi include scores of opposition politicians, journalists, protest organizers, and alleged supporters of ethnic insurgencies. Human Rights Watch interviewed more than 35 former Maekelawi detainees and their relatives who described how officials had denied their basic needs, tortured, and otherwise mistreated them to extract information and confessions, and refused them access to legal counsel and their relatives.


 Aerial view of “Maekelawi” compound, the main federal police investigation center, in
Central Addis Ababa, on February 18, 2013.
 
“Ethiopian authorities right in the heart of the capital regularly use abuse to gather information,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Beatings, torture, and coerced confessions are no way to deal with journalists or the political opposition.”

Since the disputed elections of 2005, Ethiopia has intensified its clampdown on peaceful dissent. Arbitrary arrest and political prosecutions, including under the country’s restrictive anti-terrorism law, have frequently been used against perceived opponents of the government who have been detained and interrogated at Maekelawi.

Maekelawi officials, primarily police investigators, have used various methods of torture and ill-treatment against those in their custody. Former detainees described to Human Rights Watch being slapped, kicked, and beaten with various objects, including sticks and gun butts, primarily during interrogations. Detainees also described being held in painful stress positions for hours upon end, hung from the wall by their wrists, often while being beaten.

A student from Oromiya described being shackled for several months in solitary confinement: “When I wanted to stand up it was hard: I had to use my head, legs, and the walls to stand up. I was still chained when I was eating. They would chain my hands in front of me while I ate and then chain them behind me again afterward.”

Detention conditions in Maekelawi’s four primary detention blocks are poor but vary considerably. In the worst block, known as “Chalama Bet” (dark house in Amharic), former detainees said their access to daylight and to a toilet were severely restricted, and some were held in solitary confinement. Those in “Tawla Bet” (wooden house) complained of limited access to the courtyard outside their cells and flea infestations. Investigators use access to basic needs and facilities to punish or reward detainees for their compliance with their demands, including by transferring them between blocks. Short of release, many yearn to be transferred to the block known as “Sheraton,” named for the international hotel, where movement is freer.
'
Detainees held in Chalama Bet and Tawla Bet were routinely denied access to their lawyers and relatives, particularly in the initial phase of detention. Several family members told Human Rights Watch that they had visited Maekelawi daily but that officials denied them access to their detained relative until the lengthy investigation phase was over. The absence of a lawyer during interrogations increases the likelihood of abuse, and limits the chances for documenting abuse and obtaining redress.
“Cutting detainees off from their lawyers and relatives not only heightens the risk of abuse but creates enormous pressure to comply with the investigators’ demands,” Lefkow said. “Those in custody in Maekelawi need lawyers at their interrogations and access to their relatives, and should be promptly charged before a judge.”

Human Rights Watch found that investigators used coercive methods, including beatings and threats of violence, to compel detainees to sign statements and confessions. These statements have sometimes been used to exert pressure on people to work with the authorities after they are released, or used as evidence in Court.

Martin Schibbye, a Swedish journalist held in Maekelawi in 2011, described the pressure used to extract confessions: “For most people in Maekelawi, they keep them until they give up and confess, you can spend three weeks with no interviews, it’s just waiting for a confession, it’s all built around confession. Police say it will be sorted in court, but nothing will be sorted out in court.”
Detainees have limited channels for redress for ill-treatment. Ethiopia’s courts lack independence, particularly in politically sensitive cases. Despite numerous allegations of abuse by defendants, including people held under the anti-terrorism law, the courts have taken inadequate steps to investigate these allegations or to protect defendants complaining of mistreatment from reprisals.
The courts should be more proactive in responding to complaints of mistreatment, but that can happen only if the government allows the courts to act independently and respects their decisions, Human Rights Watch said.

Ethiopia has severely restricted independent human rights investigation and reporting in recent years, hampering monitoring of detention conditions in Maekelawi. The governmental Ethiopian Human Rights Commission has visited Maekelawi three times since 2010 and publicly raised concerns about incommunicado detention. However, former detainees told Human Rights Watch that Maekelawi officials were present during those visits, preventing them from talking with commission members privately, and questioned their impact.

Improved human rights monitoring in Maekelawi and other detention facilities requires revision of two repressive laws, the Charities and Societies Proclamation and the Anti-Terrorism Proclamation. These laws have significantly reduced independent human rights monitoring and removed basic legal safeguards against torture and ill-treatment in detention.

Ethiopia’s constitution and international legal commitments require officials to protect all detainees from mistreatment, and the Ethiopian authorities at all levels have a responsibility both to end abusive practices and to prosecute those responsible. While the Ethiopian government has developed a three-year human rights action plan that acknowledges the need to improve the treatment of detainees, the plan does not address physical abuse and torture; it focuses on capacity building rather than on the concrete political action needed to end the routine abuse.

“More funds and capacity building alone will not end the widespread mistreatment in Maekelawi and other Ethiopian detention centers,” Lefkow said. “Real change demands action from the highest levels of government against all those responsible to root out the underlying culture of impunity.”

Source:http://www.hrw.org/
 

ከሙስና ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ ችግር ውስጥ መሆኑን አቶ ሰብሃት ተናገሩ

October 18/2013

ጥቅምት (ስምንት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከሙስና መንሰራፋት ጋር በተያያዘ የገጠመውን ፈተና በድል ለመወጣት ሕዝቡን ማሳተፍ እንዳለበትና ያለሕዝቡ ተሳትፎ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ የማይመለስ ጥፋትን ያስከትላሉ ሲሉ አቶ ስብሃት ነጋ ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮችን ምክር ለግሰዋል።

የጸረ ሙስና ኮምሽን በሸራተን ሆቴል ያዘጋጀውና በምክትል ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር እና የፓርላማው አፈጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ በመሩትና ዛሬ በተጠናቀቀው ስብሰባ ላይ የተገኙት የቀድሞ የህወሃት ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ስብሃት ነጋ ፣ በጸረ ሙስና ትግሉ ሕዝብ እንዲካፈል መጀመሪያ መታወቅ አለበት ካሉ በኃላ ” እኛ ህዝቡን አሳውቀነዋል ወይ?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

አንድ መ/ቤት 200 ሰራተኞች ቢኖሩት እነዚህ ሰራተኞች በመ/ቤታቸው ጉዳይ የመጨረሻ አዋቂ መሆናቸውን በምሳሌነት የጠቀሱት አቶ ሰብሃት፣  ይህ አዋቂ ሕዝብ እንዳይታዘበን፣ የማይቀበለውን ቃል ተናግረን እንዳናጭበረብረው መጠንቀቅ አለብን ብለዋል፡፡

ኢህአዴግ ይህን አዋቂ ሕዝብ ካልያዘ የሚገጥመው ችግር ለመመለስም የማይቻል ነው ሲሉም አስጠንቅቀዋል፡፡

ሙስና በአሁኑ ወቅት የሌለበት አንድም መንደር የለም የሚሉት አቶ ስብሃት ፣ “ለመሆኑ የሙስናን መንስኤ ታውቁታላችሁ ወይ፣ መንስኤው ፓርቲው ነው፣ ነጋዴው ነው፣ የውጪ ኃይሎች ናቸው?’ ለመሆኑ መጠኑስ ስንት ነው፣ በመቶኛ ስሌት ስንት ነው፣ ስንት ሚሊየን ብር ጠፋ?” ሲሉ እነአቶ ሙክታርን በጥያቄ አፋጠዋል፡፡

መንስኤው ካልታወቀ ቀጣዩ ምንድነው ያሉት አቶ ስብሃት፣  በማታውቀው ነገር ልትታገል፣ ለውጥም ልታመጣ አትችልም በማለት የሙስና ሁኔታ በተጨባጭ ጥናት እንዲደገፍ ጠይቀዋል፡፡

የደረንስንበት የሙስና ሁኔታ ቀላል ስላልሆነ ይህን ጠርገን ንጹህ መሬት መቼ እናገኛለን ሲሉ ጥያቄ አዘል አስተያየታቸውን አክለዋል።
አቶ ሙክታር ከድር የተነሱትን ሃሳቦች በገንቢነቱ እንቀበላለን ካሉ በኃላ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም በመባል የሚታወቀው ፕሮግራም የታሰበውን ያህል ለውጥ አለማምጣቱን በመጥቀስ ይህ ችግር ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነትን ለመዋጋት አዳጋች ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡

በዛሬው ስብሰባ ስለሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት አሳሳቢነት ትምህርት ሲሰጡ ከዋሉት ባለስልጣናት መካከል አቶ አባዱላ ገመዳ በአንድ ወቅት በሙስናና ብልሹ አሰራር በፓርቲያቸው ሰብሰባ ላይ ተገምግመው በትርፍነት የያዙትን መኖሪያ ቤት ለኦህዴድ እንደሚያስረክቡ ቃል በመግባታቸው በሕግ ሳይጠየቁ የታለፉ ሲሆን ቤቱን ግን በገቡት ቃል መሰረት ለፓርቲው አለማስረከባቸው ታውቆአል፡፡

እንዲህ ዓይነት በሙስና የተጨማለቁ ባለስልጣናት ስለሙስና አስተማሪና መድረክ መሪ ሆነው መታየታቸው ኢህአዴግ አሁንም ከባድ ችግር ውስጥ ስለመኖሩ ጠቋሚ ነው በማለት አንዳንዶች ለዘጋቢው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ የተባለው ተቋም በኢትዮጵያ  እስከ 3 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በእየአመቱ ወደ ውጭ ተዘርፎ እንደሚወጣ ከአመት በፊት ባወጣው ሪፖርት መጥቀሱ ይታወቃል።
አቶ ስብሀት ነጋ በአንድ ወቅት ይመሩት የነበረው ኢፈርት የተባለው ግዙፉ የህወሀት ኩባንያ እንዲሁም የህወሀት ባለስልጣኖች እና የመከላከያ ሰራዊት መኮንኖች በአገሪቱ ውስጥ በተንሰራፋው ሙስና ዋነኞቹ ተዋናዮች መሆናቸው በተደጋጋሚ ይዘገባል።

ኃ/ማሪያም ደሳለኝ “መንግስት ፈርቷል እያላችሁ ራሳችሁን አታሞኙ” ሲል ማሾፉ ተሰማ

October 18/2013

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት አንዴ “ቀይ መስመር ረገጣችሁ” አንዴ ሰላማዊ ሰልፍ እከለክላለሁ፤ ሌላ ግዜ ደግሞ ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ጥያቄ መልስ ሰጥቷል እያለ የባጥ የቆጡን ሲቀባጥር የሰነበተዉ የወያኔዉ ሎሌ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በዚህ ሳምንት ደግሞ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝቶ ““መንግስት ፈርቷል እያላችሁ ራሳችሁን አታሞኙ” ብሎ በመደንፋት “ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም” የሚባለዉን የአገራችንን ተረት የሚያስታዉስ የፈሪ ንግግር አድርጓል። ጠ/ሚኒስቴር ተብዬዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ከዚያ እንቅልፋም ፓርላማ አባላት ለቀረቡለት ጥያቄዎች መልስ ሲሰጥ መንግስት የጎዳና ላይ ነውጥ ከሚያሰቡት ሀይሎች ጋር ለመነጋገር የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል። ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር እንኳን መነጋገር እነሱ ባለፉበት መንገድ ማለፍ የሚፈራዉ ኃ/ማሪያም የጎዳና ላይ ነውጥ ከሚያሰቡት ሀይሎች ጋር ካሁን በኋላ አንነጋገርም ማለቱ አንዳንዶችን ያስገረመ ቢሆንም ብዙ የፖለቲካ ተንታኞች አባባሉን የተለመደ የወያኔ የቃላት ጨዋታ ነዉ ብለዉ የኃይለማሪያምን ንግግር አጣጥለዉታል።

በተቃዋሚዎች ፓርቲዎች በኩል የሚቀርበው ጥያቄ ሁሉ ቅጥ ያጣ ፍረጃና የጥላቻ ፖለቲካ ብቻ ነዉ ያለዉ ሎሌዉ ሀይለማርያም ደሳለኝ የጎዳና ላይ ነውጥ እናደርጋለን ብለዉ የሚያስቡ ሀይሎች ሀሳባቸውን እንዲያቆሙ ጠይቋል። በመቀጠልም የጎዳና ላይ ነውጥ ለማስነሳት ስለሚያስቡ ኃይሎች በቂ መረጃ አለን ስንል “መንግስት ፈርቶ ማስፈራራት ጀመረ” እንባላለን ሆኖም ይህ መንግስት አይፈራም፣ ታሪኩም ባህሪውም እንደዛ አይደለም በማለት የሚያዉቀዉን የኢትዮጵያዉያንን የጀግንነትና የአይበገሬነት ታሪክ ትቶ የማያዉቀዉን፤ የሌለዉንና በታሪክ ያልተመዘገበዉን የወያኔን አለመፍራት “ይህ መንግስት ፈርቷል እያላችሁ እራሳችሁን አታሞኙ፣ መንግስት አይፈራም የህዝብ መንግስት ነው” እያለ ያለ ሀፍረት ተናግሯል። ዘረናዉ የወያኔ አገዛዝ ወይ እሱ እራሱ አይጫወትበት ወይ ሌሎቹን አያጫዉት ብቻዉን ጨምድዶ የያዘዉን ኳስ የወያኔዉ ተላላኪ ኃ/ማሪያም ጌቶቹ ሄደህ ተናገር ያሉትን ትእዛዝ ለመፈጸም ብቻ ሲል ብቻ “ኳሱ እናንተ እጅ ላይ ነው” በማለት አባባሉን እንኳን በዉል ያልተረዳዉን ምሳሌ ተናግራል።

የሞኝ ዘፈን አሁንም አሁንም አበብዬ

October 18/2013

ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ከዚህ ቀደም በቁንጯቸዉ በመለስ ዜናዊ በኩል እንኮረኩማለን፤ ምላስ እንቆርጣልን ወይም እጅ እናስራለን እያሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላልፉ የነበረዉን የማስፈራሪያ ቃላት ጋጋታ ባለፈዉ ዐርብ መስከረም 26 ቀን ለዚሁ እኩይ ተግባራቸዉ በቀጠሩት ታማኝ ሎሌያቸዉ በኃ/ማሪያም ደሳለኝ በኩል ሲያስተላልፉ ተደምጠዋል። እንዳሰለጠኑት ጌኛ ፈረስ ወያኔ ባሳየዉ አቅጣጫ ሽምጥ የሚጋልበዉና ከጭንቅላቱ ወጥቶ የሚነገር ምንም ነገር የሌለዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝም የአሜሪካዉን ፕሬዚዳንት የባራክ ኦባማን አባባል እንዳለ በግርድፉ ወስዶ “ከቀይ መስመር በላይ መሄድ የሚፈልግ ይቆነጠጣል” ሲል በዚያ ባልተቆነጠጠ አፉ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ደንፍቷል። የወያኔዉ ተላላኪ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አልገባዉም እንጂ ይህ ቀይ መስመር ታልፉና ወዮላችሁ የሚሉት ዛቻ አንኳን በአንድ ጀምበር ትርምስምሱ ሊወጣ በሚችል የጦር ኃይል ለሚተማመነዉ ወያኔን ለመሰለ ፀረ ህዝብ ኃይል ቀርቶ በህዝብ ሙሉ ፈቃድ የተመረጠዉና የአለማችንን አስፈሪና እጅግ ጠንካራ ጦር የሚመራዉ ባራክ ኦባም ከተናገረና ከዛተ በኋላ ዛቻዉ አላዋጣ ስላለዉ ሌሎች አማራጮችን ለመመልከት ተገድዷል።

ባለፈዉ ዐርብ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ የተናገራቸዉን ተራ ንግግሮች ሁሉ እንመልከት ብንል እንደሱ ስራ ፈቶች አይደለንምና ግዜዉም ፍላጎቱም የለንም፤ ሆኖም አንዳንድ ንግግሮቹ የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱና ለነጻነቱ የሚያደርገዉን ትግል በንቀት አይን የተመለከቱ ናቸዉና ግንቦት 7 የሚያካሄደዉ የነጻነት ትግል ኃ/ማሪያም ደሳለኝን ከወያኔ ባርነት ነጻ ማዉጣትንም ያጠቃልላልና ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ይህንን ምክር አዘል መልዕክታችንን እንዲያዳምጥ እንጋብዘዋለን። ደግሞም የግንቦት ሰባትን እንቅስቃሴ እከታተላለሁ ብሎ ሲናገር ከራሱ አንደበት ሰምተናልና ምክራችንን ይሰማል የሚል ሙሉ እምነት አለን።

ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አገር ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያነሷቸዉን ጥያቄዎች አስመልክቶ ከጋዜጠኞች የቀረበለትን ጥያቄ ሲመልስ ኢትዮጰያ ዉስጥ ወደ ዘጠና የሚጠጉ ፓርቲዎች ስላሉ ዘጠና እሁዶችን መጠበቅ አለብን በማለት ከተጠየቀዉ ጥያቄ ጋር በፍጹም የማይገናኝና እንኳን ከአገር መሪ ከሦስተኛ ክፍል ተማሪም የማይጠበቅ ተራ መልስ መልሷል። ከዚህ በተጨማሪ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እሁድ እሁድ በሚያደርጓቸው ሰላማዊ ሠልፎች የሚያቀርቡት ጥያቄ ተመሳሳይ ስለሆነ መንግሥት ምን ምላሽ መስጠት እንዳለበት ሊገባው አልቻለም በማለት ኃ/ማሪያም የእሱን የራሱን ብቻ ሳይሆን እሱ የሚመራዉ መንግስትም ምን ያክል ጨቅላ መንግስት አንደሆነ በግልጽ ተናግሯል። የኃ/ማሪያምና የጌቶቹ ጨቅላነትና ባዶነት ደግሞ አገር ያወቀዉና ፀሐይ የሞቀዉ እዉነት ነዉና ብዙ መረጃ የሚያስፈልገዉ አይመሰለንም።ከሰሞኑ አማካሪ ተብለዉ ኃ/ማሪያምን የከበቡትን ሰዎች መመልከቱ ይበቃል። የጭንቅላቱ ዝገት ለይቶለት በመለስ ዜናዊ ግዜ ስኳር እንዲቅም መተኃራና ወንጂ የተላከዉ አባይ ፀሐዬ እሱ እራሱ ይመረመር እንደሆነ ነዉ እንጂ አባይ ፀሐዬ እንኳን ለፖሊሲ ምርምር የተመራማሪዎችን ዶሴ ለመሸከም የማይበቃ ሰዉ ነዉ . . . ችግሩ “ግም ለግም አብረህ አዝግም” ነዉና ከምሁርና ከአዋቂ ጋር የተጣሉት የወያኔ መሪዎች አንዱን ጅል የሌላዉ ጅል አማካሪ እያደረጉ የፈረደባትን አራት ኪሎን የጅሎች መንደር አደረጓት።

ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ባለፈዉ ዐርብ ከአንድ ሰዐት በላይ በፈጀዉ ጋዜጣዊ መግለጫዉ ወቅት የተናገረዉ አንድ ብቸኛ እዉነት ቢኖር “መንግስት ተቃዋሚዎች ለሚያቀርቡት ጥያቄ ምን አይነት ምላሽ መስጠት እንዳለበት ሊገባዉ አልቻለም ብሎ የተናገረዉ ንግግር ብቻ ነዉ። አዎ በተራ የመንገድ ላይ ፖለቲከኞችና ዘራፊዎች የሚመራዉ የወያኔ /ኢህአዴግ አገዛዝ ከኢትዮጵያ ህዝብ የሚቀርብለትን የመብትና የነጻነት ጥያቄ ቀርቶ በአገዛዙ በራሱ መሃል የሚነሱ ጥያቄዎችን በቅጡ ተረድቶ የመወያየት ብቃትም ችሎታም ያለዉ አገዛዝ አይደለም። ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በአንድ በኩል ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለህዝብ ማለት የፈለጉትን ብለዋል፤ ህዝብም በሚገባ ሰምቷቸዋል በማለት፤ በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚዎች ለጠየቁት ጥያቄ መንግስት ተገቢዉን ምላሽ ሰጥቷል አሁን እየጠየቁ ያሉት ተመሳሳይ ጥያቄ ነዉ በማለት እሱም ሆነ ፈላጭ ቆራጩ የወያኔ አገዛዝ እንመራለን የሚሉትን ህዝብ የፖለቲካ ምጥቀት በፍጹም የማይመጥኑና ቀድሟቸዉ የሄደዉን ህዝብ ከኋላ ሆነዉ የሚመሩ ኋላ ቀሮች መሆናቸዉን በግልጽ አሳይቷል። ኃ/ማሪያም በሰላማዊ ሰልፍና በህዝብ መካከል ያለዉ አንድነትና ልዩነት የገባዉ ሰዉ አይመስልም፤ ለዚህ ነዉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያቀረቡት ጥያቄ ለህዝቡ መስሎት ህዝብ ሰምቷቸዋል ብሎ የተናገረዉ፡፡

ኃ/ማሪያም እንደሚለዉ መንግስት የህዝብን ጥያቄ መልሶ ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያ ከዘረኞች ተላቅቃ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት አገር ትሆን ነበር፤ ወይም ኃ/ማሪያም እራሱ የሞተ ሰዉ ራዕይ መሸከሙን አቁሞ የራሱ ጭንቅላት ያመነጨዉንና በራሱ እይታ ያየዉን ራዕይ ያጋራን ነበር። ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ፍትህ፤ ነጻነት፤ እኩልነትና ዲሞክራሲ እያሉ የሚጮሁት እነዚህ ጥያቄዎች ካልተመለሱ በሚወክሉት ህዝብና በአገራቸዉ በኢትዮጵያ ላይ ሊደርስ የሚችለዉን መጠነ ሰፊ ችግር ከወዲሁ ስለሚታያቸዉ ነዉ። እርግጠኞች ነን፤ ኃ/ማሪያም ደሳለኝም እንደ ተቃዋሚዎች አገሩን የሚወድ ኢትዮጵያዊ ነዉና ዘረኞች ያጠለቁለትን ማስክ አዉልቆ በራሱ አይን ማየት ሲጀምር እሱም እንደ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከተቃዋሚዎች ጋር ተሰልፎ ለነጻነቱ መጮህ ይምራል ብለን እናምናለን።

በእርግጥ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ከፖለቲካ ብስለቱና ካለዉ ልምድ አኳያ ሲታይ ብዙዎቹ አገር የመምራት ዉስብስብ ነገሮች ላይገቡት ይችሉ ይሆናል፤ ሆኖም ግን የአገርና የመንግስት መሪ ነኝ የሚል ሰዉ ህዝብ ላቀረበለት ጥያቄ ምን አይነት ምላሽ መስጠት እንዳለብን ሊገባን አልቻለም ማለቱ የሚያሳየን አገራችን ኢትዮጵያ የምትመራዉ ለዕድር ዳኝነትም በማንመኛቸዉ ባዶ ሰዎች መሆኑን ነዉ። በተለይ 99.6% የህዝብ ድምጽ አገኘሁ ብሎ የሚመጻደቅ መንግስት የዚሁኑ መረጠኝ የሚለዉን ህዝብ ጥያቄ እንዴት መመለስ እንደሚገባዉ ካላወቀ ሌላ ምን ሊያዉቅ ይችላል!

ኢትዮጵያ ከ90 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ትልቅ አገር ናት፤ በእርግጥ 90 ሚሊዮን ህዝብ የሚጠይቀዉን ጥያቄ ማስተናገድ ለማንም አገር መንግስት አዳጋች ሊሆን ይችላል ፤ ነገር ግን መልስ የለንም ወይም ጥያቄዉ አልገባንም እየተባለ የህዝብ ጥያቄ ቆሻሻ ቅርጫት ዉስጥ አይጣልም ። በእርግጥ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በጠ/ሚኒስቴርነቱ ጥርስ የለሌዉ አንበሳ ነዉና የህዝብን ጥያቄ መመለስ አይችል ይሆናል፤ ሆኖም ኃ/ማሪያምን በቅርብ የሚያዉቁት ሰዎች ሐይማኖታዊ ስነምግባሩንና አንደበተ ጨዋነቱን ተመልክተዉ ሌላ ሁሉ ቢቀር በእነዚህ ሁለት ባህሪይዎቹ ብቻ የተቀመጠበትን ወንበር ይመጥናል ብለዉ ገምተዉ ነበር። ችግሩ “ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር ፈስ ተምራ ትመጣለች” ነዉና ዛሬ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አንደ ገለባ ቀልሎ የሚታየዉ በዚሁ በተነገረለት ጠንካራ ጎኑ በኩል ነዉ። ለመሆኑ መቼ ነዉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እትዮጵያ ዉስጥ በየእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉት? ደግሞስ የወያኔ አገዛዝ ሰላማዊ ሰልፍ በተጠራ ቁጥር የሰላማዊ ሰልፉን አስተባባሪዎችና ሰልፈኛዉን የሚደበድብ ኃይል ነዉ የሚያሰማራዉ እንጂ ከመቼ ወዲህ ነዉ ወያኔ ለህዝብ ደህንነት አስቦ የጥበቃ ኃይል አሰማርቶ የሚያዉቀዉ? ካለፈዉ ግንቦት ወር ጀምሮ ሰማያዊ ፓርቲና አንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ዉስጥ የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ ሦስት ወይም አራት ቢሆን ነዉ፤ በዚህ ግዜ ዉስጥ ደግሞ ማንን እንደሚቃወም ባይታወቅም ገዢዉ ፓርቲም ሰላማዊ ሰልፍ አድርጓል። ታድያ የቱን ሰላማዊ ሰልፍ ነዉ ኃ/ማሪያም በየሳምንቱ የሚደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ሰለቸን ብሎ የተናገረዉ? ወይስ የጌታዉን የመለስ ዜናዊን ራዕይ ከግቡ ማድረስ እንደጌታዉ መዋሸትንም ያጠቃልላል?
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎችና አንደቤት መኪናቸዉ የሚዘዉሩት ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በተፈጥሯቸዉ የህዝብ ጥያቄ የማይገባቸዉ ግዑዞች ሆነዉ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት መብቴንና ነጻነቴን አክብሩልኝ ብሎ የጠየቀዉ በየእሁዱ ብቻ ሳይሆን በየቀኑ ነዉ። ሆኖም ይህ ህዝባዊና ህጋዊ ጥያቄዉ ከወያኔ በኩል ያገኘዉ ምላሽ ድብደባ፤ እስር፤ ግድያና ስደት ብቻ ነዉ።

ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ሚኒልክ ቤ/መንግሰት ከገባ ገና አመት ከመንፈቅ አልሞላዉም፤ ችግሩ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሚኒልክ ቤ/መንግስት የሚገቡ ሰዎች ሁሉ የሚያስቡት በጭንቅላታቸዉ ሳይሆን በጡንቻቸዉ ነዉ፤ የኃ/ማሪያም ደሳለኝ የሰሞኑ ከቀይ መስመር በላይ መሄድ ያስቆነጥጣል የሚለዉ ማስፈራርያ የሚያሳየዉ እሱም እንደ ጌቶቹ በጡንቻዉ ማሰብ መጀመሩን ነዉ። የሚገርዉ ኃ/ማሪያም ጡንቻ ያላቸዉ ሰዎች የሚጠቀሙበት መሳሪያ ነዉ እንጂ የራሱ የሆነ ጡንቻ ያለዉ ሰዉ አይደለም። ይህ ጡንቻ ቀርቶ የራሱ የሆነ ራዕይ የሌለዉ ሰዉ በስልጣን ዘመኑ አዲስ አበባ ዉስጥ ያያቸዉ ሰላማዊ ሰልፎች አምስት አይሆኑም። እንግዲህ ይታያችሁ አመት ከመንፈቅ አገር እየመራ አምስት ሰላማዊ ሰልፎች ባልተደረጉበት ከተማ ዉስጥ ነዉ በየእሁዱ የሚደረጉት ሰላማዊ ሰልፎች ይሰለቻሉና ለማቆም እንገደዳለን ያለዉ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ሃያ ሁለት አመት ሙሉ ጥያቁ በጠየቀ ቁጥር እየታሰረ፤ እየተደበደበና እየተገደለ ሰለቸኝ አላለም። ደግሞስ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረግ ህገ መንግስቱ የፈቀደዉ መብት ነዉ፤ የዲሞክራሲም አካል ነዉ እያለ ያቅራራዉ ኃ/ማሪያም ለመሆኑ እሱ እራሱ ማነዉና ነዉ ሰላማዊ ሰልፎችን ለማቆም እንገደዳለን ያለዉ?

ሌላዉ አንደ ሰነበተ የድሃ ድሪቶ እምቅ እምቅ የሚሸትተዉ የኃ/ማሪያም ንግግር የአገር ዉስጥ ተቃዋሚ ድርጅቶች ያነገቡት ጥያቄ የግንቦት 7 ጥያቄ ነዉ ብሎ የተናገረዉ እርባና ቢስ ንግግር ነዉ፤ ለመሆኑ ወያኔን የመሰለ ዜጎችን በየአደባባዩ የሚገድል ወንጀለኛ መንግስት ባለበት አገር የሚኖሩ ተቃዋሚ ድርጅቶች ምን ጎድሏቸዉ ነዉ የራሳቸዉ ያልሆነ ጥያቄ አንግበዉ የሚታገሉት? ኃ/ማሪያምም ሆነ ጌቶቹ የወያኔ ዘረኞች አንድ ሊረዱት የሚገባ ነገር ቢኖር ኢትዮጵያን ህዝብ በተመለከተ የአገር ቤትና የዉጭ አገር ወይም ህጋዊና ህጋዊ ያልሆኑ ተቃዋሚ ድርጅቶች የሚባል ክፍፍል የለም። ሁሉም ተቃዋሚ ድርጅቶች ጥያቄያቸዉ አንድና ተመሳሳይ ነዉ፤ እሱም የህዝብ የመብትና የነጻነት ጥያቄ ይመለስ የሚል ጥያቄ ነዉ።

የአዛኝ ቅቤ አንጓቹ ኃ/ማሪያም ኬንያ ዉስጥ የደረሰዉ የሽብር ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ እንደደረሰ ይሰማናል ብሎ ሲናገርም ተደምጧል፤ ይህ አባባል ፖለቲካ፤ ቋንቋ፤ ዘርና ሀይማኖት ሳይለይ የሁሉም ኢትዮጵያዊ እምነት ነዉ። ሆኖም የጎረቤቱ ህዝብ አደጋ ሲደርስበት ኃዘን የሚሰማዉ መሪ የራሱን አገር ህዝብ ለጦር ሜዳ በሰለጠነ ኮማንዶ አያስጨፈጭፍም። ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ለኬንያ ህዝብ መራራቱና ሀዘናቸዉን መጋራቱ መልካም ነዉ፤ ነገር ግን ባለፈዉ ሐምሌ ወር ኮፈሌ ዉስጥ በዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ለተጨፈጨፉት ሃያ አምስት ሰላማዊ ኢትዮጵያዉያንስ ማን ይዘንላቸዉ፤ ማንስ ሞታችሁ ሞቴ ነዉ ይበላቸዉ? ወይስ ወያኔና ኃ/ማሪያም ደሳለኝ የሚያሳስባቸዉና የሚያሳዝናቸዉ አገር ዉስጥ እነሱ የሚጨፈጭፉት ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ጎረቤት አገር ዉስጥ የሚሞተዉ ሰዉ ብቻ ነዉ!

ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሐይማኖት ተቋሞች የሚያነሱት ጥያቄ የፖለቲካ ጥያቄ ነዉና መንግስት የሚሰጠዉ ምላሽም የፖለቲካ ምላሽ ነዉ ብሏል። መቼም እንዲህ አይነቱ ንግግር በህዝብና በአገር ላይ የሚደረግ ሽሙጥና ስድብ ነዉ እንጂ ከአገር መሪ የሚጠበቅ አስተያየት አይደለም። ለዚህም ይመስለናል ባለፈዉ አመት መለስ ዜናዊ ሞቶ ኃ/ማሪያም ብቅ ሲል የኢትዮጵያ ህዘብ “የዘንድሮዉ ሐምሌ ምንኛ ቅጥ አጣ ተሳዳቢዉ ሲሄድ አሽሟጣጩ መጣ” ብሎ የተረተዉ። መለስ ዜናዊ ሃያ አንድ አመት ሙሉ ህዝብና አገር እንደሰደበ ተገላገልነዉ፤ አሁን ደግሞ እሱን የተካዉ ሰዉ እስከመቼ ይሆን እያሽሟጠጠ የሚኖረዉ? ደግሞስ የሐይማኖት ተቋሞች ለሚያነሱት ጥያቄ ያለን መልስ የፖለቲካ መልስ ነዉ ሲባል እየተላለፈ ያለዉ መልዕክት አናስራለን ነዉ? እንቆነጥጣለን ነዉ ወይስ እንገላለን ነዉ? ኃ/ማሪያምም ሆነ ጌቶቹ ከዚህ የተለየ መልስ ካላቸዉ ይንገሩን። እስሩ፤ ዱላዉና ግድያዉማ ድሮም የምናዉቃቸዉ የወያኔ የቀን ከቀን ድራማዎች ናቸዉ።

ወያኔ የዛሬ ሃያ አመት ሰላማዊ ዜጎችን ይገድል ነበር ዛሬም ይገድላል፤ አዲስ አበባ ዉስጥ አንዴ ቦምብ እያፈነዳ ሌላ ግዜ ደግሞ እራሱ መሬት ቆፍሮ የቀበረዉን ፈንጂ የቴሌቪዥን ካሜራዉን ደርድሮ እራሱ እያወጣዉ በተቃዋሚዎች ላይ እያሳበበ ኖሯል፤ ዛሬም ከዚህ ርካሽ ተግባሩ አልተቆጠበም። ዛሬማ ጭራሽ ኢትዮጵያ ዉስጥ ነጻነትና ዲሞክራሲ እያለ የጮኸዉን ሁሉ ግንቦት 7 ነህ እያለ እስር ቤት እየወረወረ ነዉ። ባለፈዉ አመት መለስ ዜናዊን የተካዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝም እንደዚሁ ነዉ። እንዳዉም ኃ/ማሪያም ሂድ ሲሉት የሚሄድ፤ ተናገር ሲሉት የሚናገር፤ ዝም በል ሲሉት ደግሞ አፉን ዘግቶ የሚቀመጥ ተንቀሳቃሽ ዕቃ ነዉ። ይህ ሰዉ በጌቶቹ እየታዘዘ ከአመታት በፊት በክልል ደረጃ በሲዳማ ህዝብ ላይ የፈጸመዉን ይህ ነዉ የማይባል በደል ዛሬ በብሔራዊ ደረጃ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ነዉ። ኃ/ማሪያም ባለፈዉ ዐርብ መስከረም 26 ቀን በየሳምንቱ የሚደረገዉ ሰልፍ ሰለቸኝ እያለ በህዝብና በአገር ላይ አሽማጥጧል፤ ይህ ማንነታችን ያልገባዉ ሰዉ እሱና ጌቶቹ የማምለክ መብቴ ይከበር ያለዉን አክራሪ፤ መብቴና ነጻነቴ ይከበር ያለዉን ሽብርተኛ፤ ፍትህና ዲሞክራሲ ናፈቀኝ ያለዉን ደግሞ ግንቦት ሰባት ናችሁ እያሉ የሞኝ ዘፈን ሲዘፍኑ የኢትዮጵያ ህዝብ መሰልቸት ብቻ ሳይሆን ቋቅ እንዳለዉ ማወቅ አለበት። ሞኝን ሞኝ ብለን የምንጠራዉ አንድን ነገር ሺ ግዜ ስለሚደጋግም ወይም ዘፈኑ አሁንም አሁንም አበብዬ ስለሆነ ነዉ። ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ሞኝ ብለን እንዳንጠራዉ የሚፈልግ ከሆነ ይህንን ከወያኔ መዝገብ እየተዋሰ የሚዘፍንብንን “ሁል ግዜ አበብዬ” ዘፈኑን ማቆም አለበት። አለዚያ “ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ” ነዉና ግንቦት ሰባትና የኢትዮጵያ የነጻነት ኃይሎች ኃ/ማሪያምንና ዘረኞቹን የወያኔ መሪዎች ጠራርገዉ አራት ኪሎንና የሚኒልክ ቤ/መንግስትን የሚያጸዱበትን ግዜ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በህልሙ ሳይሆን በዉኑ ያየዋል።