Monday, May 13, 2013

ሰበር ዜና፣ በባህር ዳር ከተማ ከ16 በላይ ሰዎች ተገደሉ

እሁድ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ የአባይን ድልድይ እንዲጠብቅ የተመደበ የፌደራል ፖሊስ አባል እያነጣጠረ ሰዎችን ሲገድል አምሽቷል። የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከ16-18 ንጹሀን ዜጎች ያለምንም ምክንያት ከፌደራል ፖሊሱ በተተኮሱ ጥይቶች ተገድለዋል።

የፌደራል ፖሊሱ እያነጣጠረ ንጹሀን ዜጎችን ሲገድል በአቅራቢያው የነበሩ የብአዴን ጽ/ቤት ጠባቂዎች እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥበው እንደቆዩ በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች ገልጸዋል።
የብአዴን ጽ/ቤት ጠባቂዎች በግለሰቡ ላይ አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን ህይወት ሊታደጉ ሲገባቸው ይልቁኑም ሰውየውን ለመያዝ በመፈለግ ላይ ትኩረታቸውን በማድረግ ግለሰቡ ያገኘውን ሰው እየተኮሰ ሲገድል እንደነበር በአቅራቢያው የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል።

ሁኔታው በባህር-ዳር ከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ መረበሽ መፍጠሩ ታውቋል። የከተማው ነዋሪዎች የሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ የተካሄደውን ኢሰብአዊ ድርጊት ለማውገዝ እንደሚፈልጉም ዜናውን ያቀበሉን የባህር-ዳር ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ኢሳት (የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በበኩሉ ዜናውን እንዲህ ዘግቦታል)


ESAT Ethiopian News Weekly May 12, 2013

                                 

 
  ESAT is the first independent Ethiopian Satellite Television service and Radio Station who broadcast to Ethiopia and the rest of the world. ESAT Ethiopian News Weekly May 12, 2013.          

Our reports of growth are false: Somali Region President

ESAT News May 11, 2013

Abdi Mohammed, the President of the Somali Regional State of Ethiopia, told members of the Region’s ruling Party and officials of the Cabinet that the reports they submit to the Government as if the Region has developed was full of lies only aimed at passing evaluations.

The President with emotions said “The reports presented as if we grew and reached better status are false. We are not sure if the report that you see in my hand is at all true. The same is with the previous reports. The reports are submitted only for the sake of evaluations”.

“We have reported that 10 million animals have been vaccinated, but the Head of the Farming Bureau cannot confirm that. There is no evidence that let alone 10 million, 500,000 have been vaccinated. Don’t the people see when this many are vaccinated?” said Abdi confirming that the reports were all false.

The President also condemned that Addis Abeba Radio and Radio Fana don’t report about Ogaden region while they do with the rest of the country. He said the Radio stations should have interviewed the zonal and Woreda heads.

Abdi said that officials of the Regional State do even report their daily routines to the government.
In a secret video clip that ESAT aired last week, the President was heard as saying to the Region’s clan chiefs “Tigreans don’t want Amhara to come to power. They want to arm us and lead the Country with us but we considered them as Amharas and began firing at them. Amara and Tigre, Amara and Oromo will never reconcile and cooperate thus we need to stand with Tigreans and stop lumping the Tigres, Oromos and Amharas together as Amhara.”
Although ESAT phoned the President of the Region, we were unable as his Secretary said he was in a meeting.

Saturday, May 11, 2013

Ethiopian Justice Minister Ato Brehan Hailu Fired – Addis Fortune


Brehan-Hailu_lost-his-job-as-Minister-of-Justice1Ethiopian Justice Minister Ato Brehan Hailu has been fired from his job on Friday, May 10, 2013, reliable sources disclosed to Fortune. Brehan has received a letter from the Prime Minister’s Office, signed by Hailemariam Desalegn, late on Friday, according to these sources. Brehan has been serving in this capacity since 2005. He was moved to Justice after his previous ministry, Ministry of Information, was dissolved by law.

However, the decision to remove the Minister from Office has come as little surprise in the government circle. He has lost his position in the powerful executive committee of the ruling EPRDF, when elections were held back in March 2013. He was under fire during a convention of his party, the Amhara National Democratic Movement (ANDM), held in Bahir Dar in March, held as a prelude to the EPRDF congress, which was held in the same city.

Seconded by a member to the central committee seat in the ANDM, Brehan was harshly criticized by the bigwigs of the party for his failure and incompetence while serving at the Justice Ministry.
Brehan has not been immediately available for comment, despite Fortune’s repeated attempts.

Source Addis Fourtune

የፍትህ ሚኒስትሩ ከስራቸው ተባረሩ!

የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃነ ኋይሉ ከሃላፊነት ቦታቸው ተነሱ፡፡ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃነ ኃይሉ ትናንተ ከሰአት በኋላ በጠቅላይ ሚኒስቴር ኋይለማርያም ደሳለኝ በተጻፈ ደብዳቤ መሰናበታቸው እውን መሆኑ ታውቋል፡፡ በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ክስ የመሰረቱት አቃብያን ሕጎች እና የችሎቱን ድራማ የሚዘውሩት ግለሰቦች አቶ ብርሃነ ኋይሉ በሚመሩት የፍትህ ሚኒስቴር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

ግለሰቡ ከ1997 ጀምሮ በዚሁ ቦታቸው ላይ የነበሩ ሲሆን ከዚያ ቀደም ብሎ በቀድሞ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ ሰርተዋል፡፡ አቶ ብርሃነ ኃይሉ የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) አባልና ከፍተኛ አመራር ሲሆኑ የኮሚቴዎቻችንን እና የሌሎች ግለሰቦችን ክስ አስመለክቶ ተደጋጋሚ መግለጫ ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ በዚህ ላይ ተጨማሪ መረጃ ካገኘን ለማቅረብ ጥረት እናደርጋለን፡፡

አላሁ አክበር







ማን ነው ወንጀለኛው?


በከፍተኛ ደረጃ የህዝብ እምነት ያጣው የካንጋሮው ፍርድቤት ምንም አይነት የህግ ወይም የሞራል የበላይነት ሳይኖረው፤ የህሊና እስረኞቹን የእድሜ ልክና እና ሌሎች ቅጣቶችን እንዴት ሊሰጥ ይችላል? ማነው ፈራጁ? ማንስ ነው ተፈራጁ? ማን ነው ጥፋተኛው። ህግን ያዋረደ? ወይስ ስለነጻነት፣ ስለ ዲሞክራሲ አቤት ያለ?

በፍትህ እና በፍትህ ፈላጊዎች ላይ እየቀለደ እና ተቋሙን እያዋረደ የሚገኘው ወያኔ ዛሬም እንደትላንቱ ሌላ የበደል ጩኸት ከተባዳዮቹ ለበዳዮቹ እንዳይሰማ በጉጅሌ “ዳኞ” ተብየዎች አማካኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። እውነተኛ ፍትህ ሀገራችን ውስጥ ጠፍቶ መቀበሩን ለማሳየት ሲል ባስቀመጣቸው የፍትህ ተወናያን ዳኞች አማካኝነት አረፍን እንቀመጥ ዘንድ ፍትህን ትመኙታላችሁ እንጅ አታገኙትም ሲል መልክቱን በአሻንጉሊቶች ፍርድቤቶች አማካኝነት አስተላልፏል።

የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚ ዳኞች ሰሞኑን የሰጡት ፓለቲካዊ ውሳኔ የአገልጋይነታቸውን ታማኝነት ማረጋገጫ እንጅ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ህወሃት እያለ ፍትህና ፍትህ ፈላጊዎችን ማገናኘት የማይታሰብ መሆኑን በድጋሜ ተረጋግጧል፡፡ ፍትህ የነፃነትና የእኩልነት ማረጋገጫ፤ ግለሰቦችና ቡድኖች በሥርዓት እንዲኖሩ ማድረጊያ እና የአንድ ማኅበረሰብ የሞራል እሴቶች ተፈፃሚነት ማሳያ ነበር፡፡ ፍትህ በሌለበት ነፃነት፣ እኩልነት፣ ሰላም፣ ልማት እና ዲሞክራሲ ትርጉም የላቸውም፡፡

ለዚህም ነው ራሱ የፍትህ ስርአቱ ተቋም የካድሬዎች እስረኛ ነው የምንለው። ተቋማት ነጻ አልወጡም፣ ህዝባችን በጎጠኝነት የአገዛዝ አባዜ ይሰቀያል። በማንነቱ ይሰደዳል፣ ይታሰራል። ታዲያ ማን ነው ጥፋተኛው? በዳዩ ወይስ ተበዳዩ?
ዜጎች በሀገራቸው የመኖር፣ የመናገር ፍትህ የማግኘት ተስፋቸው እንደገና ተቀብሯል። ተዋርደናል፤ ውርደት እስከ መቼ? ኢትዮጵያዊ እምቢተኝነታችን፣ ክብርና ኩራታችን፣ ታሪካችን በወያኔዎች ተደፍሯል። በፋሲካ የጀግናው ሰማእታት የአቡነ ጴጥሮስ የመታሰቢያ ሀውልት ለረጅም ጊዜ ከተቀመጠበት፣ ከመታሰቢያነቱ ስፍራ አሻራነቱ ተነስቷል። በዚሁ ዋዜማ እነ አንዷለምአራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ክንፈሚካኤል ደበበ፣ ናትናኤል መኮነን፣ ምትኩ ዳምጤ፣ ዮሃንስ ተረፈ እና ሻምበል የሺዋስ ይሁን አለም ላይ በፋሲካ ዋዜማ አይሁዶች የህሊና እስረኞቹ ይሰቀሉላቸው ዘንድ ፈረዱ።

በፋሲካ በወያኔ ጨለማ ቤት ውስጥ የተዘጉ፣ የተረሱ ዜጎችም አሉ እነ በቀለ፣ ርእዮት፣ ውብሸት እና እነ ጀኒራል ተፈራ ማሞ እና ሌሎቹም። አሁንም በፋሲካ ህዝቡ እየተሰደደ፣ እየተፈናቀለ ነው። በአንጻሩ አይሁዶች እጃቸውን በደም እየታጠቡ ከደሙ ንጹህ ለመሆን ሲሉ ውስኪ ሲራጩ ይታያሉ። ማን ነው ወንጀለኛው?

ኢህአዴግ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በሾማቸው “ዳኞች” ተብየዎች ስም እያፈራረሳት ነው። ትውልድን የቁም እስረኛና አንገቱን እንዲደፋ እንዲሸማቀቅ እያደረጉት ነው። ሀገራችን በወረበሎች አንገቷን ደፍታ የወያኔዎች መሳለቂያ ሆናለች። እናድናት።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡ የበደል ትልቅና ትንሽ የለውም። በወያኔ ያልተገረፈ፣ ያልተሰደደ፣ ያልተገደለ፣ ያልታሰረ፣ ያልቆሰለ፣ ሀብት ንብረቱን ያልተወረሰ፣ ያልተዋረደ፣ አንገቱን ያልደፋ፣ ያልተበደለ፣ ፍትህን ያልተነፈገ፣ የእምነት ነጻነቱን ያልተገፈፈ ዜጋ የለም። ያጣነው ብዙ ነው። ያጣነውን የማስመለስ ኢትዮጵያዊ ግዴታ አለብን። ሀገራችን ኢትዮጵያ ይህን ውርደትና መከራ እና አይን ያወጣ ጭካኔ ዘረኝነት ብዝቶና ተባብሶ ህልውናዋ ከመጥፋቱ ዜጎቿ የህሊና እስረኞች ሁነው ፍትህ አጥተው ከማለቃቸው በፊት የሚደርሱላት ጀግኖችን ትሻለች።

ወጣቱ ትውልድ ከገባበት የፍርሃት አረንቋ ወጥቶ፣ ፍርሃቱን በጀግነነቱ በጥሶ ኢትዮጵያንና ወገኑን ለማዳንና ነጻነትን በመሰዋእቱ ከፍሎ ለሀገራችን ብርሃን የመሆኛ ጊዜው አሁን ነው። እምቢ ብለህ የነጻነት ተስፋ የሆኑ ህዝባዊ ሃይሎችን ተቀላቀል። ትግል በአንድ ጀምበር የሚያልቅ አይደለም። በርካታ ረጅምና አስቸጋሪ ፈተናዎች ያሉበት፣ የሚጠበቁበት ነው። ቁም ነገሩ ይህንን የተጋረደብህን ፈተና ተፈትነህ ማለፉ ላይ ነው ጀግንነቱ። እንዲህ አይነት ፈተና አምባገነን መንግስት እሰከ አለ ድረስ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለፍትህ መከበር በሚነሱ ሃይላት ላይ የሚኖርና የሚቀጥል በመሆኑ፤ በወያኔ በሚደርስብን የስቃይ ውርጅብኝ ሳንበረከክ ለፍትህ ስርአት መከበር ለህግ የበላይነት መስፈን ለሀገር አንድነት የምናደርገውን ትግል በማጠናከር መቀጠልና ግንባር ቀደም ታጋዮች መሆን ይኖርብናል።

ግንቦት 7 የፍትህ የዲሞክራሲና የነጻነት ንቅናቄ ለፍትህ መቆም ሲል ነፃነቱንና ሀገሩን የሚወድ ዜጋ ሁሉ በማናቸውም መንገድ ወያኔን የመታገል ሞራላዊ ግዴታ አለበት ይላል፡፡ ከትግሉ ባሻገር በነጻነት ታጋዮች ላይ የሀሰት ምስክር የሚሰጡትን፣ ፍትህን የሚየዛቡ ዳኞችና አቃቤዓነ-ህግን የክህደት ሥራዎቻቸውን መዝግቦ መያዝ፣ በዓይነ ቁራኛ መከታተል የሁላችንም ግዴታ ነው፡፡

ህዝብ በሃሰት ምስክሮች፣ ዳኞችና አቃቢያነ-ህግ ላይ ቁጣውን የሚገልጽበት ጊዜ ተቃርቧል፡፡ በወያኔ ወኔ ቢስ አድርባዮች ፍትህ ስትቀበር፣ ዘረኝነት ሲወደስ፣ ታጋዮቻችን ሲገደሉ፣ ሲንገላቱና ሲበደሉ ሲታሰሩ ማየት በቃን ብለናል፡፡ ፍትህን የሚያረክሱትን የወያኔ ቅጠረኞችን በቁርጠኛነት፣ አምርረን እንታገላለን፡፡ የወያኔ ቡችላ ፍርድቤት አገልጋዮች ወዮላችሁ! ያላገጣችሁበት ፍትህ እናንተን ባልጠበቃችሁት ሁኔታ፣ ግዜና ቦታ ትጠየቃችኋለች፡፡ ስለዚህ ራሳችሁን ከቁም እስረኝነትና አገልጋይነት፣ አሽከርነትና ከአደርባይነት ታወጡ ዘንድ ጊዜው አልረፈደባችሁም። እድሉን የመጠቀም ሃላፊነት የእናንተ ነው። እኛ ግን በቃ ብለናል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

የፍትህ ሚኒስትሩ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም አሉ

ግንቦት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ከብአዴን እና ከኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚነት በቅርቡ በተካሄዱት ጉባዔዎች የተነሱት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖሩን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የመብት ጥሰት የለም ሲሉ ተናገሩ።
በዛሬው ዕለት የመ/ቤታቸውን የ9 ወራት ሪፖርት ለፓርላማ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ ከብቸኛው የአንድነት ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡
...
አቶ ግርማ ባቀረቡት ጥያቄ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብቶች እየተከበሩ መሆኑን በተካሄዱ ጉብኝቶች ማረጋገጣቸውን መጥቀሳቸውን በማስታወስ በጉብኝቱ ምን እንዳገኙ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አይይዘውም ባለፈው ቅዳሜ ዕለት የታሰሩ ሰዎችን ለመጠየቅ ወደማረሚያ ቤት ሄደው ተከልክለው መመለሳቸውን በማስታወስ ይህ ፓርላማ እንኳን መጣስ የማይችለውን ሕገመንግስት ማረሚያ ቤት እየጣሰ ነው ሲሉ ምሬት አዘል አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በማረሚያ ቤቶች ጉብኝታቸው የታራሚዎች መብዛት ጋር ተያይዞ መጨናነቅ መኖሩን፣የመገልገያ ዕቃዎችና እንደንጹህ መጠጥ ውሃ ያሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውን ማስተዋላቸውን እና ይህ ችግር እንዲፈታ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

የማረሚያ ቤቶች ተጠሪነታቸው ለፍትህ ሚኒስቴር ሳይሆን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በሰብዓዊ መብት አያያዝ በኩል ችግር እንደሌለና፤ አለ እንኳን ቢባል ሕገመንግስት ተጥሶአል ለማለት እንደማይቻልና የተፈጠረ የአሰራር ችግር ካለ ሊስተካከል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡


 በማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ መሪዎች፣የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አባላትና ሌሎችም በየጊዜው በሕገመንግስቱ የተረጋገጠው የሰብዓዊ መብቶቻቸው ማለትም በቤተሰቦቻቸውና በወዳጆቻቸው የመጎብኘት፣ ከጠበቆቻቸው ጋር ያለችግር የመገናኘትና ሃሳብ የመለዋወጥ፣ ከሃይማኖት አባቶቻቸው ጋር የመገናኘት መብቶቻቸው በማረሚያ ቤት
ኃላፊዎች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተና ብዙውን ጊዜ የሚጣስ መሆኑን እየገለጹና በመግለጽ ላይ የሚገኙ ከመሆኑ አንጻር የሚኒስትሩ አባባል ግልጽ ክህደት መሆኑን አንድ ያፓርላማ አባል ተናግረዋል።


 ሚኒስትሩ ያቀረቡትን ሪፖርት ተከትሎ ከፓርላማ አባላቱ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በይቅርታ ከማረሚያ ቤት የሚለቀቁ ሰዎች መስፈርቱን ያሙዋሉት እያሉ ያላሙዋሉት ይለቀቃሉ፣ይህ ለምንድነው በሚል ለተነሳው ጥያቄ ይቅርታ የታራሚው ጉዳይ ሳይሆን መንግስት በራሱ ፍላጎት የሚያደርገው ነው፡፡እንደመብት ሊጠየቅ አይችልም ሲሉ የፓርላማ
አባላቱን ጥያቄ አጣጥለዋል፡፡

በፍትህ ሚ/ር ስር የሚገኘው የይቅርታ ቦርድ ጥያቄው ሲቀርብ የታራሚው ጠባይ፣ለመሻሻል ያለው ፍላጎት ታይቶ በማረሚያ ቤት በጎ አስተያየት ሲቀርብ እንደሚለቀቁ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡


 ይህ የሚኒስትሩ ማብራሪያ ግን በሌላ የፓርላማ አባል ተተችቶአል፡፡ አባሉ በሰጡት አስተያየት ሚኒስትሩ ሲናገሩ ይቅርታ እና አመክሮን መደበላለቃቸውን በመጥቀስ ይቅርታ ልክ እንደአመክሮ ጠባይ የሚመዘንበት አይደለም፡፡ቀደም ሲል የቅንጅት እስረኞች ጠባያቸው ታይቶ አልተፈቱም ሲሉ የሚኒስትሩን ንግግር ተችተዋል፡፡
ባለፉት 9 ወራት 2 ሺ 958 የይቅርታ ጥያቄዎች ቀርበው 2 ሺ 149 ያህሉ በይቅርታ መለቀቃቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል፡፡


የፍትሕ ሚኒስትሩ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም አሉ
ግንቦት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ከብአዴን እና ከኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚነት በቅርቡ በተካሄዱት ጉባዔዎች የተነሱት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መኖሩን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የመብት ጥሰት የለም ሲሉ ተናገሩ።
በዛሬው ዕለት የመ/ቤታቸውን የ9 ወራት ሪፖርት ለፓርላማ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ ከብቸኛው የአንድነት ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡

አቶ ግርማ ባቀረቡት ጥያቄ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው በማረሚያ ቤቶች የሰብዓዊ መብቶች እየተከበሩ መሆኑን በተካሄዱ ጉብኝቶች ማረጋገጣቸውን መጥቀሳቸውን በማስታወስ በጉብኝቱ ምን እንዳገኙ ጠይቀዋቸዋል፡፡ አይይዘውም ባለፈው ቅዳሜ ዕለት የታሰሩ ሰዎችን ለመጠየቅ ወደማረሚያ ቤት ሄደው ተከልክለው መመለሳቸውን በማስታወስ ይህ ፓርላማ እንኳን መጣስ የማይችለውን ሕገመንግስት ማረሚያ ቤት እየጣሰ ነው ሲሉ ምሬት አዘል አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በማረሚያ ቤቶች ጉብኝታቸው የታራሚዎች መብዛት ጋር ተያይዞ መጨናነቅ መኖሩን፣የመገልገያ ዕቃዎችና እንደንጹህ መጠጥ ውሃ ያሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውን ማስተዋላቸውን እና ይህ ችግር እንዲፈታ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

የማረሚያ ቤቶች ተጠሪነታቸው ለፍትህ ሚኒስቴር ሳይሆን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትሩ በሰብዓዊ መብት አያያዝ በኩል ችግር እንደሌለና፤ አለ እንኳን ቢባል ሕገመንግስት ተጥሶአል ለማለት እንደማይቻልና የተፈጠረ የአሰራር ችግር ካለ ሊስተካከል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
በማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ መሪዎች፣የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አባላትና ሌሎችም በየጊዜው በሕገመንግስቱ የተረጋገጠው የሰብዓዊ መብቶቻቸው ማለትም በቤተሰቦቻቸውና በወዳጆቻቸው የመጎብኘት፣ ከጠበቆቻቸው ጋር ያለችግር የመገናኘትና ሃሳብ የመለዋወጥ፣ ከሃይማኖት አባቶቻቸው ጋር የመገናኘት መብቶቻቸው በማረሚያ ቤት
ኃላፊዎች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተና ብዙውን ጊዜ የሚጣስ መሆኑን እየገለጹና በመግለጽ ላይ የሚገኙ ከመሆኑ አንጻር የሚኒስትሩ አባባል ግልጽ ክህደት መሆኑን አንድ ያፓርላማ አባል ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ ያቀረቡትን ሪፖርት ተከትሎ ከፓርላማ አባላቱ ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በይቅርታ ከማረሚያ ቤት የሚለቀቁ ሰዎች መስፈርቱን ያሙዋሉት እያሉ ያላሙዋሉት ይለቀቃሉ፣ይህ ለምንድነው በሚል ለተነሳው ጥያቄ ይቅርታ የታራሚው ጉዳይ ሳይሆን መንግስት በራሱ ፍላጎት የሚያደርገው ነው፡፡እንደመብት ሊጠየቅ አይችልም ሲሉ የፓርላማ
አባላቱን ጥያቄ አጣጥለዋል፡፡

በፍትህ ሚ/ር ስር የሚገኘው የይቅርታ ቦርድ ጥያቄው ሲቀርብ የታራሚው ጠባይ፣ለመሻሻል ያለው ፍላጎት ታይቶ በማረሚያ ቤት በጎ አስተያየት ሲቀርብ እንደሚለቀቁ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ይህ የሚኒስትሩ ማብራሪያ ግን በሌላ የፓርላማ አባል ተተችቶአል፡፡ አባሉ በሰጡት አስተያየት ሚኒስትሩ ሲናገሩ ይቅርታ እና አመክሮን መደበላለቃቸውን በመጥቀስ ይቅርታ ልክ እንደአመክሮ ጠባይ የሚመዘንበት አይደለም፡፡ቀደም ሲል የቅንጅት እስረኞች ጠባያቸው ታይቶ አልተፈቱም ሲሉ የሚኒስትሩን ንግግር ተችተዋል፡፡
ባለፉት 9 ወራት 2 ሺ 958 የይቅርታ ጥያቄዎች ቀርበው 2 ሺ 149 ያህሉ በይቅርታ መለቀቃቸውን ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ጠቅሰዋል፡፡

Friday, May 10, 2013

ሲጠበቅ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ በደቡብ አፍሪካ ዛሬ ተካሄደ

ክራንቻ፣ ከደቡብ አፍሪካ
በዛሬው ዕለት የተደረገውን ሰልፍ ለማደናቀፍ የወያኔ መንግስት ጭፍሮች ለዲፕሎማቶች እና ለፖሊስ የሰጡት የሀሰት ውንጀላ በትላንትናው ዕለት ውድቅ ተደርጎ ዛሬ በደቡብ አፍሪካ የሰላማዊ ሰልፍ ተደርጓል።

ተቃዋሚ ሀይሎች የሚያደርጉትን የሰላማዊ ሰለፍ እጅግ የፈራው ወያኔ ሰልፉን የጠሩት አሸባሪዎች ናቸው፣ ከዚህ በፊትም ቴዎድሮስ የሚባለውን የኢትዮጵያ ባለስልጣን በደርባን ርዕሰ ከተማ የጠለፋ ሙከራ ሊያካሂዱበት ነበር የሚልና መሰል የሀሰት ውንጀላዎችን በመደርደር ቢሟገትም ጉዳዩ የሚመለከተው አካል የደቡብ አፍሪካን ዲሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት የሚጻረር ስህተት ላለመፈጸም ሲል የሰላማዊ ሰልፉን ፈቃድ በደቡብ አፍሪካ ነዋሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ሰጥቷል።

በመሆኑን ዛሬ አርብ ሜይ 10፣ 2013 ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ በጆሀንስበርግ የተሰበሰበው ህዝብ ወደ ፕሪቶሪያ ጉዞውን በማድረግ የስብሰባው ስፍራ ተገኝቶ መልዕክቱን በቃልና በደብዳቤ ለተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ልዑክ እና ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ቃል-አቀባይ፣ በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ተወካይ አቶ ደረጀ አማካኝነት አስረክቧል።

ሌላው በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የተፈጠረ አስገራሚ ነገር ቢኖር፣ የኦጋዴን ተቃዋሚ ሀይሎች በስፍራው በመገኘት “ከወያኔ እንጂ ከኢትዮጵያ ህዝብ የመገንጠል ሀሳብ የለብንም… ወያኔ ይወገድ!” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ከ ኦጋዴን ወገኖቻችን መካከል አንዲት እህታችን ይዛ የነበረው መፈክር የብዙዎችን ቀልብ የሳበ ነበር። እንዲህ ይነበባል፣

የግምሩክ ዳይሬክተር እና ምክትሉ በቁጥጥር ስር ዋሉ

(EMF) – በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታ እና አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ በዛሬው እለት በሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል። ሁለቱ በሙስና የታሰሩት ባለውልጣናት የግምሩክ ዳይሬክተር እና ምክትል ዳይሬክተሮች ናቸው። አቶ መላኩ ፈንታ ትውልድ እና ዕድገታቸው በጎንደር ከተማ ሲሆን፤ ስብሰባ ሄደው አያውቁም እንጂ፤ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል ናቸው። ባለፉት አመታት የኢህአዴግ ታማኝ አገልጋይ በመሆን የፌዴራል ጉዳዮች ሚንስትር ደኤታ ሆነው አገልግለዋል። አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ ደግሞ የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ፤ በሙያ ችሎታ ሳይሆን በህወሃት አባልነታቸው ስልጣን እንዳገኙ ተደርጎ ሲነገር ነበር የቆየው።
(Left to right) Gebrewahed Deputy director and  Director Melaku Fenta
 

ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ የሙስና ምንጮች ተብለው ከተጠቀሱት 3 ድርጅቶች ውስጥ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በዋናነት ሲጠቀስ ቆይቷል። ይህ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ታክስ በነጋዴው ላይ በመጨመር ህብረተሰቡን ሲያማርር የቆየ ሲሆን፤ ሌሎችን በሙስና በመክሰስ ከአንድ ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከ6 ወራት እስከ 25 አመት በሚቆይ እስር እንዲፈረድባቸው ማድረጋቸው ይታወሳል። ከነዚህ ውስጥ በርግጥ በጥፋት የታሰሩ ቢኖሩም፤ ምንም ያላጠፉ እና የኢህአዴግን አስተዳደር ያልደገፉ፤ መዋጮ እንዲያደርጉ ተጠይቀው ያላደረጉ ሰዎች ሆን ተብሎ ከፍተኛ ታክስ ተጨምሮባቸው፤ መክፈል ባለመቻላቸው ጭምር ለእስር የተዳረጉ አሉበት።

እስካለፈ አመት ድረስ የግምሩክ ባለስልጣን ከ3 ሺህ በላይ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ክስ መስርቶ ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ነበር። አሁን የተሰማው አዲስ ወሬ እና ዜና ግን በተለይ የንግዱን ህብረተሰብ ያስገረመ ነገር ሆኗል። በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታ እና አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ እንዲሁም ከነሱ ጋር በመተባበር ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ 15 የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት።
እንደደረሰን ዘገባ ከሆነ የግለሰቦቹ ቤት፣ ቢሮ ተበርብሯል። በስልክ እና በኢሜይል ሲያደርጉ የነበረው ግንኙነት ጭምር በህወሃቱ አቶ ደብረጽዮን የኤሌክትሮኒክስ ስለላ ስር ወድቆ ነበር። እናም መቆየት ደግ ነው “ኢህአዴግ ልጆቹን መብላት ጀመረ” የሚያሰኝ ወቅት ላይ ተደረሰ።

የቃሊቲው ደብዳቤና የርዕዮት እውነቶች

በስለሺ ሀጎስ

ሚያዝያ 23 2005 ዓ.ም ሪፖርተር ጋዜጣ በቅጽ 18 ቁጥር 44/1356 ዕትሙ “በህግ ታራሚ ርዕዮት ዓለሙ ላይ የደረሰ አንዳችም አይነት ችግር የለም!” በሚል ርዕስ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት አስተዳደር የተላከ ደብዳቤ አስነብቧል፡፡ ደብዳቤው በቅጥፈትና በክህደት የተሞላ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ባልተነሳ ጥያቄና ባልተባለ ነገር ላይ በማተት የተነሳበትን ሀቀኛ ጥያቄ አደናብሮ ለማለፍ ከአንድ ህገ መንግስታዊ ተቋም የማይጠበቅ ጥረት አድርጓል፡፡ ይህ የሆነውም ርዕዮት ራሷን በማትከላከልበት ሁኔታ ውስጥ መሆኗን እንደ መልካም አጋጣሚ በማየት ይመስላል፡፡ በመሆኑም በደብዳቤው ላይ የሰፈሩትን አብዛኞቹን ጉዳዮች በቅርብ ስለማውቃቸው የርዕዮትን እውነቶች የማስረዳት ሞራላዊ ኃላፊነት እንዳለብኝ በማመኔ ይህን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ተገድጃለሁ፡፡

Reeyot-Alemu

በደብዳቤው ከታጨቁ ቅጥፈቶችና ማወናበዶች መሐከል ጸሐፊውን ጠልፈው የሚጥሉ እውነቶች ተሸሽገው ቀርበዋል፡፡ ከነዚህም መሐከል አንደኛው ርዕዮት ለብቻዋ እንድትታሰርና በጠያቂዎቿ እንዳትጎበኝ ለማድረግ ማረሚያ ቤቱ እንደተዘጋጀ ማረጋገጡ ነው፡፡ በደብዳቤው መጨረሻ ላይ፣

‹‹በማረሚያ ቤት አብረዋት ከሚኖሩ ታራሚዎች ለመረዳት እንደቻልነው ርዕዮት ያለምንም ጥረትና ልፋት ዝናን ለማግኘት በመሻቷ ከታራሚዎችና ከጥበቃ አባሎች ጋር በየጊዜው ትጋጫለች፡፡ ጤናማ የሆነ ግንኙነት የላትም፡፡ በተለያየ ጊዜ በታራሚዋ ላይ የዲሲፒሊን ግድፈት በመታየቱም ማረሚያ ቤቱ ጥፋቱን በማጣራት ላይ ይገኛል፡፡ ጥፋተኛ ሆና ከተገኘችም በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የሕግ ታራሚዎች መተዳደሪያ ደንብ ቁጥር 138/1999 መሠረት ተገቢውን የዲሲፒሊን እርምጃ ተቋሙ እንደሚወስድ ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡›› የሚል ሀሳብ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

በጽሑፉ ላይ እንደሚታየው ርዕዮት የዲሲፒሊን ግድፈት ማሳየቷን ማረሚያ ቤቱ ደምድሟል፡፡ ከዚህም በላይ ከጥበቃ አባሎችና ከታራሚዎች ጋር እየተጋጨች የዲሲፒሊን ግድፈቱን የምትፈጽመው ለምን እንደሆነ ሲገልጽ “ያለምንም ጥረትና ልፋት ዝናን ለማግኘት በመሻቷ ከታራሚዎችና ከጥበቃ አባሎች ጋር በየጊዜው ትጋጫለች፡፡ ጤናማ የሆነ ግንኙነት የላትም፡፡” በማለት በልቧ ምን አስባ ድርጊቱን እንደምትፈጽም ሁሉ መቶ በመቶ እርግጠኛ ሆኖ ነግሮናል፡፡ ታዲያ ማረሚያ ቤቱ የሚያጣራው ምንድን ነው? ጥፋተኝነቷን ከነ መንስዔው እርግጠኛ ሆኖ እየነገረን፤ መልሶ ደግሞ ጥፋተኛ ሆና ከተገኘች እርምጃ እወስዳለሁ ማለቱ አልሞ ለመተኮስ ሳይሆን፣ የሚፈልገው ላይ ተኩሶ ዒላማ ለማክበብ መዘጋጀቱን ያሳብቃል፡፡

አርሶ መራብና ተኩሶ መሳት፣
እያደር ይፈጃል እንደእግር እሳት! ሆነበት እንጂ ነገሩ፡፡

ማረሚያ ቤቱ ከሳሽም፤ አጣሪም፤ ፈራጅም፤ እርምጃ ወሳጅም ሆኖ መቅረቡ ደግሞ “በህግ ሽፋን ርዕዮት ብቻዋን እንድትታሰርና ጠያቂዎቿ እንዳይጎበኟት ለማድረግ እየሰራ ነው” የሚለው ስጋት እውነት መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሲፒጄም ቢሆን ያለው ይህንኑ ነው፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በደብዳቤው ላይ፤

በአንዳንድ ሚዲያዎች የተገለጸው ሌላው ጉዳይ ለሁለት ወራት በአንድ ክፍል ውስጥ ለብቻዋ እንደታሰረች የሚገልጸው ዘገባ ነው፡፡ ይህ ዘገባ ከርዕዮት ጋር የሚኖሩ የህግ ታራሚዎችን ከመናቅ ወይም እንደሰው ካለመቁጠር የመነጨ ይመስለናል፡፡ ሀሳቡ የርዕዮት ከሆነም ለራሷ ካላት የተጋነነ ግምት ወይም ማንነት የመነጨ ሊሆን ይችላል፡፡ የሚል ውንጀላ ቀርቧል፡፡
እግዜር ያሳያችሁ! “ሊሆን ይችላል” ነው ያለው፡፡ ግምት ብቻ ተይዞ “ለራሷ ካላት የተጋነነ ግምት… እንደሰው ካለመቁጠር የመነጨ” የመሳሰሉ ሥነልቡናዊ ትንታኔዎች ውስጥ እንዴት ይገባል? ኧረ ጎበዝ አታሳፍሩን!

እርግጥ ነው ርዕዮት ለብቻዋ እንድትታሰር ሊያደርጋት በሚችል አንቀጽ (በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የሕግ ታራሚዎች መተዳደሪያ ደንብ ቁጥር 138/1999) ክስ ተመስርቶባት ውሳኔውን (ውሳኔው ተግባራዊ የሚሆንበትን ዕለት) በመጠባበቅ ላይ ናት እንጂ በአሁኑ ሰዓት ለብቻዋ አልታሰረችም፡፡ ለዚህ ጉዳይ ሽፋን ከሰጡ በርካታ የሀገር ውስጥ የህትመት ውጤቶች መሐከል አንዱ (ሪፖርተር ጋዜጣ ቅጽ 18 ቁጥር 42/1352) ‹‹ርዕዮት ለብቻዋ ታስራ ትገኛለች›› ብሎ ሲፒጄ መናገሩን ጽፏል፡፡ ማረሚያ ቤቱን ለግምታዊ ስህተት የዳረገውም ይሄው ዘገባ ነው፡፡ ነገር ግን እንኳን አንድ ትልቅ ተቋም ቀርቶ፤ የዘገባው ስህተት ከምን የመነጨ እንደሆነ ማረጋገጥ የሚፈልግ ሰው የሲፒጄን ኦርጂናል መግለጫ ማንበብ፤ አሊያም ጋዜጣውን መጠየቅ ብቻ ይበቃዋል፡፡

እኔ ያነበብኩትና ለፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን በአድራሻው የተላከት የሲፒጄ ደብዳቤ “ርዕዮት ለብቻዋ ታስራለች” አይልም፡፡ በጉዳዩ ላይ መረጃ የሰጡ የርዕዮት ቤተሰቦችም በአንድም ሚዲያ ላይ ይህን አላሉም፡፡ ታዲያ ሪፖርተር ከየት አመጣው? የሚለውን ጥያቄም ከጋዜጣው በስተቀር ርዕዮትም ሆነች ማንም ሰው ሊመልሰው አይችልም፡፡

ከዚህ ሌላ ርዕዮት ማረሚያ ቤቱ እንዳለው አይነት ሰው አለመሆኗን ዓለም የሚያውቀው እውነት በመሆኑ ይህን ለማስረዳት አንዲትም ቃል ሳላባክን ወደ ቀጣዩ ርዕሰ ጉዳይ ልለፍ፡፡

ህክምናዋን በተመለከተም ምንም አይነት ችግር እንዳላጋጠማት በደብዳቤው ላይ ተገልጿል፡፡ “ማረሚያ ቤት በቆየችባቸው ጊዜያት በተለያዩ ቀናት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተልካ ሕክምና ማግኘቷን ከግል ማህደሯ ማረጋገጥ ይቻላል” በማለትም እማኝ ይጠቅሳል፡፡

በተለያዩ ቀናት፣ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መሄዷ እውነት ነው፡፡ ነገር ግን በጡቷ ላይ ሕመም እንደሚሰማት ተናግራ ሪፈር እንዲጻፍላት ብትጠይቅም፣ ከመንፈስ ጭንቀት ውጪ ምንም በሽታ እንደሌለባትና የእጅ ሥራ እንድትሰራ፤ ጥልፍ እንድትጠልፍ ስትመከር መሰንበቷ፤ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሄዳ ህክምናዋን ለመከታተል የቻለችውም ከብዙ አቤቱታ በኋላ ኦማር የተባለ የአፍሪካ ጋዜጠኞች ፌዴሬሽን ተወካይ ከአንድ ኢትዮጵያዊ ጋር ቃሊቲ ድረስ ሄደው በጎበኟት ወቅት በእነሱ በኩል በቀረበ አቤቱታ በማረሚያ ቤቱ ዋና አስተዳዳሪ ትዕዛዝ መሆኑ ቢታከልበት የተሻለ እውነት ይሆን ነበር፡፡

ሕክምናዋን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መከታተል ከጀመረች ወዲህም ብዙውን ጊዜ በቀጠሮዋ መሠረት ተገኝታ መታከም አለመቻሏ፤ ህመሟ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ የተለየ ህመም ካጋጠማት ቀጠሮዋን ሳትጠብቅ ወደ ሆስፒታል እንድትመጣ በሀኪሞቹ ቢታዘዝም፤ ከጥር 10 ቀን ጀምሮ ክፍተኛ ደም ከጡቷ እየፈሰሰ እስከ የካቲት 07 ድረስ ህክምና ሳታገኝ በስቃይ መክረሟ፤ ከዚያ በኋላም ሀኪሟ በአስቸኳይ የናሙና ምርመራ ተደርጎ የዕጢው ደረጃ ከታወቀ በኋላ መለስተኛ ቀዶ ጥገና ማድረግ እንደሚኖርባት በመግለጽ ለየካቲት 13 ቀጠሮ ቢሰጥም መኪና የለም በሚል ሰንካላ ሰበብ እስከ መጋቢት 2 ድረስ፣ ከነስቃይዋ እንድትቆይ መደረጓና ሌሎች ታራሚዎች ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቀጠሯቸው ቀን ከፍርድቤትና ከሌሎች ቀጠሮዎች ጋር እንዳይጋጭ የህክምና ቀጠሯቸውን እዚያው ሆስፒታል እያሉ እንዲያውቁት የሚደረግበት አሰራር የተለመደ ሆኖ እያለ ርዕዮት ከመጋቢት 2 ወዲህ መቼ ምን አይነት የሀኪም ቀጠሮ እንዳላት ለማወቅ ብትጠይቅም፣ በግልጽ ‹‹ለአንቺ አይነገርሽም›› መባሏ ተገልጾ ቢሆን ኖሮ ሙሉ እውነት ይሆን ነበር፡፡

ፍጹም እውነት እንዲሆን ደግሞ… እንጂማ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መሄዷ ብቻ ሳይሆን መለስተኛ ቀዶ ጥገና አድርጋ ከጡቷ ላይ ዕጢ ማስወጣቷም ጭምር ከወራት በፊት ሁሉም የሰማውና ያረጀ ዜና ነው፡፡

የትምህርቷን ጉዳይ በተመለከተ ከመነሻው ጀምሮ እስከ ክልከላው ድረስ እኔ ራሴ ስከታተለው የነበረ በመሆኑ፣ ማረሚያ ቤቱ ላከ በተባለው ደብዳቤ ላይ ያነበብኩት ነገር ክፉኛ አስደንግጦኛል፡፡ ጸሐፊው ትክክለኛ መረጃ ሳያገኝ በየዋህነት ተሳስቶ ካልሆነ በቀር እንዲህ አይነት አይን ያወጣ ቅጥፈት በአደባባይ እንዲነበብ ለመጻፍ በገዛ ህሊናው ላይ የሰለጠነ ልዕለ ኃያል ሰው መሆን ይጠይቃል፡፡

የሆነው ሆኖ “ትምህርቷን እንድትከታተል የሴቶች ቀጠሮና ማረፊያ ቤት ተገቢውን ድጋፍ እያደረገላት ይገኛል፡፡” ተብሎ የተገለጸው ፍጹም ሀሰት ሲሆን እውነቱ የሚከተለው ነው፡፡

የማረሚያ ቤቱን ይሁንታ ጠይቃ ካገኘች በኋላ ህዳር 29 2012 እ.ኤ.አ ያስመዘገብኳት እኔው ራሴ ነበርኩ፡፡ መመዝገቧን ካሳወቀች በኋላም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የማረሚያ ቤቱ ባልደረቦች ት/ቤቱ ድረስ በመሄድ እንዳረጋገጡ የሰማሁት ከራሳቸው አንደበት ነው፡፡ በየካቲት ወር መጨረሻ ትምህርቱ ሲጀመር የመማሪያ መጻህፍቶቿን ይዤ በሄድኩበት ጊዜ ግን የተሰጠኝ “እሷ እንድትማር አልተፈቀደላትም” የሚል ምላሽ ነው፡፡ ጉዳዩ እስካሁን ድረስ እልባት ባለማግኘቱ ትምህርቷን መጀመር አልቻለችም፡፡ የመማሪያ መጻሕፍቱም እስከ ዛሬ ድረስ በእጄ ይገኛሉ፡፡

በመጨረሻም መሽቶ በነጋ ቁጥር በሁሉም መስክ የባሰ ነገር መጋፈጥ ልማዳችን ነውና ለማረሚያ ቤቱ ደብዳቤ ይህን ያህል ጊዜና ጉልበት ከፈጀን በቂ ነው፡፡ ነገ ለሚመጣው የባሰ ነገር ጊዜና ጉልበት መቆጠብ፣

ያምናን ቀን አማሁት ላፌ ለከት የለው፤
የዘንድሮው መጣ እጅ እግር የሌለው፡፡

የሚል ቁዘማ ውስጥ ከመዘፈቅ ሳያድነን አይቀርም፡፡

ቺርስ!!

ወያኔ ሕወሃት ያልከበደው ኢትዮጵያዊ ማነው?

ይኸነው አንተሁነኝ
ሌቱ መሽቶ ይነጋል፤ ሳምንታት ወራት ዓመታት በፍጥነት መንጎዳቸውን አላቋረጡም፤ ክረምትና በጋ ይፈራረቃሉ፤ ወቅቶችም ማንም ሳይረብሻቸው ጊዜያቸውን ጠብቀው እያለፉ ነው፤ አፍጣጭ ገላማጭ ያለባቸውም ማዘዣ ጣቢያቸው ከእኛ አይደለምና። የክረምቱን ዝናብ ቀድሞ ለማምጣት፤ ፀሐይዋን ትንሽ ቀደም ወይም ዘግየት ብላ እንድትወጣና እንድትገባ ለማድረግ፤ የምንተነፍሰው አየር ባንድ አካባቢ ብቻ እንዲነፍስ ለማዘዝ፤ ብርሃን ብቻ እንዲሆን ወይም ጨልሞ እንዲቀር ማድረግ የሰው ልጅ የሚችል ቢሆን በተለይ እኛ ኢትጵያዊያን ምን ይውጠን ነበር? ለሀገርም ለሕዝብም ለታሪክም ለባህልም እንዴው ለምንም የማይጨነቅ ገዥ ሕወሃት ለተጫነብን።

“ሲለምኑ ማፈር ድሮ ቀረ” አሉ አድስ አበቤዎች። እንዴው ግን ሰራተኛው፣ ገንዘብ አስገቢና መላሹ፣ የሙስና ዘዋሪውና አስዘዋሪው፣ ቀጣሪውና አባራሪው፣ ባለስልጣኑና ባለፋብሪካው፣ ኢንቨስተሩና ነጋዴው፣ አምራቹ አከፋፋዩና ቸርቻሪው፣ መሬት ሰጭና ነሽው፣ አራሹና አሳራሹ ባጠቃላይ ሁሉም በሕወሃትና የአገዛዙ አባላት ቁጥጥር ስር በሆነበት ሀገራችን “ሲለምኑ ማፈር ቀረ” ቢባል የሚያስደንቅ አይሆንም። ህግን አክብሮ በራስ መንገድ መስራትና እራስን መደጎም አይቻልማ፣ ከህሊናው ጋር ሆኖ ከወያኔ ጋር መስራት የመጨረሻ እጣው ከስራ መባረርና ልመና ነዋ። ድሮ እኮ መስራት የማይወድ ነው የሚለምነው፣ ያኔ እኮ ቀን ከሌት ደክሜ በላቤ በደሜ ሀገሬን ሕዝቤን እራሴንም ላሻሻል የሚለው ሳይሆን መድከምን እየጠላ መጎሳቆልን እየሸሸ በምላሱ ስንቱን አውለብልቦ እራሱም ተውለብልቦ በመሽሞነሞን ለመኖር የሚፈልገው ነበር የሚለምነው። ስለዚህም በዚያ ዘመን መለመን ያሳፍር ነበር። አሁን ግን ቀረ።

ለነገሩ እኔ ልመናን አነሳሁ እንጅ በወያኔ ዘመን ምን ያልቀረ አለ፤ ድሮ ጀግና ያስብሉ ያስከብሩ ስለነበሩት የሀገር አንድነትና የባንዲራ ክብር ባደባባይ ማውራት ቀርቶ ማሰብ በራሱ ባሸባሪነት እያስከሰሰ ዘብጥያ ማውረድ ከጀመረ ወዲህ ባንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድ በቀር መነገር ካቆመ ቆየ። ለስራ ለትምህርትና ለመሳሰሉት ካልሆነ በቀር ካገር መውጣት ማስገዘቱ ቢቀር ዘመድ አሰብስቦ ያሳዝንም የስለቅስም ነበር አሁን እቴ ሁሉ ቀርቷል። ወያኔ ከመጣ ምን ያልታየ አለ፤ አንድ ከተማ ነቅሎ የሚወጣ ያህል በየእለቱ ይሰደዳል። የአረብ አገር ጎረመሶች የግርፋት ስቃይና መከራ መለማመጃ ብንሆንም፣ ስቅላቱ ከፎቅ መወርወሩ በፈላ ውሃና ዘይት መተበሱ ሳያባራ ቢቀጥልም ሕወሃት ያማረረው ሕዝባችን ዛሬም ይሰደዳል። የሜድትራኒያንና የቀይ ባህር የአሳ ሲሳይ ብንሆንም በሕወት ብልሹ አገዛዝ ምክንያት ርሃብ የገረፈው መታረዝ የጠበሰው ማጣት ያንገበገበው ሕዝባችን አላቆመም ይሰደዳል። “ስደት ድሮ ቀረ” በወኔ ሕወሃት ዘመን አይሰራም ባገዛዙ እንደባህል እየተወሰደ ያለ ነገር ነውና። ሀገሮች በኢኮኖሚ ሲያድጉና ሲሻሻሉ ባለሙያም ሆነ ጉልበት ሰራተኛ ከውጭ ያስገባሉ እንጅ የራሳቸውን አንቱ የተባሉ ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞችን አያባርሩም። ሕወሃት የተሻለ ፕሮፓጋንዳ ማዘጋጀት ሳይጠበቅበት አይቀርም።

“No free lunch” ይላሉ አሉ ፈረንጆች። ምንም ነገር በነጻ አታገኝም፤ አንድ ነገር ለማግኘት መስራት አለብህ መድከም አለብህ ለማለት ይመስላል አባባሉ። በኢትዮጵያችንና በወያኔ አገዛዝ ግን ይህን የሚሉት የአስፋልት ዳር ነጋዴዎች ናቸው። ከሚነፍሰው ንፋስ ጋር ከግራ ከቀኝ የሚመጣውን የተዘበራረቀ ሽታ እየማጉ፣ የሙሉ ቀን የፀሐይ ግለቱን ተቋቁመው፣ አቧራ ብርድና ዝናቡን ታግሰው ትነስም ትብዛ የዕለት ጉሮሯቸውን ለመድፈን፣ ቁርስ ያልበሉ ልጆቻቸውን ምሳ ወይም እራት አጉርሰው ለማደር ደፋ ቀና ከማለት በተጨማሪ ያችን የሚውሉባትን የአስፋልት ጥግ ቦታ ለማግኘት ወያኔ መሆን እንደ መስፈርት ሲቀርብላቸው “No free lunch” ቢሉ ችግሩ ያለው ሳይፈልጉ ከተጫነባቸው ሕወሃት እንጅ ከእሳቸው አይደለምና አያስፈርድም። የሚደንቀው ግን ከዚህ ሁሉም በሗላ ወያኔ ሕወሃት ከልክ በላይ የስራ እድል የከፈትኩ፣ የኢትዮጵያዊያንን በተለይም የሴቶችን መብት ያስጠበቅኩ እኔ ነኝ እያለ መዘባረቁ ነው።

ለድሮው ክቡር የነበሩት ገዳማትና መስጊዶች ሳይቀሩ በወያኔ ዘመን ተደፍረዋል። ሳንፈልግ የወደቀብን ሕወሃት ያልከበደው ኢትዮጵያዊ ወገን የለም። ሕወሃትም በአገዛዙ ያላሸበረው የህብረተሰብ ክፍል ያልቀወጠው አካባቢ ተፈልጎ አይገኝም። ለባለራዕዩ ሬሳ ሽኝት ኮልኮሎ ያቀረባቸው የጎዳና ተዳዳሪዎችና የኔቢጤዎች ሳይቀሩ እንደ ነጋዴ መጋዘን ካርቱን አንዴ በዚያ በኩል ሌላ ጊዜ በዚህ እየተባሉ ይዋከባሉ። እነዚህ ሁሉ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ሕወሃት ማስታወስ አይፈልግም። እርዳታ መስጠትም አያስብም። ያቅም ማነስ ነው እንዳንል ደግሞ ሌሎች ወገኖች ለረዷቸው ላጎረሷቸው ሕወሃት ሲያውክ ማስተዋላችን ለምን ይሆን? ይህ እጣ ለቆሸ ሰፈር ገንዳ አራጆችም አልቀረላቸውም። ከሌሎች የአዲስ አበባ ክፍሎች ያገለገሉ እቃዎችንና የሆቴል ትርፍ ምግቦችን የያዙ ገንዳዎችን ከበው የሚያወራርዱት የቆሽ ሰፈር ገንዳ አራጆች ከወያኔ የሰፈር ጥበቃና ከፌደራል ፖሊስ የሚደርስባቸው ወከባ ቀላል አይደለም።

በእርግጥ ከነኝህ ገንዳዎች የሚገኝ ትርፍ ምግብ ለምግብነት የሚውል ሆኖ አልነበርም፤ ግን ምን ይደረግ ሰው የወደቀ ምግብ ይቅርና እራሱን ይበላል። ሕዝባችን እኮ እራሱን በልቶ በልቶ ጨርሶ በጠኔና በክሳት እየተንጠራወዘ ነው ያለው። ከቁጥር ስላልጎደለ አልተጮኸም እንጅ ሞቷል ተብሎ ሊለቀስለት የሚገባው የማህበረሰባችን ክፍል ጥቂት አይደለም። ይህ ሁሉ በግፍ በወደቀብን ሕወሃት እየተሰፈረልን ያለ መከራ ነው። ግን ለምን? አንዳንዱ የሕወሃት ሰው ከትግራይ በመጣ በነጋታው የውስጥ ሱሪ እንኳ ለምንና እንዴት ማድረግ እንዳለበት ገና በቅጡ ሳያውቅ በዘረኛ ባለስልጣን ወገኑ በተሰጠ ቀጭን ትእዛዝ በሽዎች የሚቆጠር ኩንታል ሲሚንቶ ወይም ስኳር ያለ ወረፋ እንዲወስድ ይፈቀድለትና የፈቃድ ደብዳቤዋን ብቻ ለመርካቶ ነጋዴ በመሸጥ ፋብሪካዎቹን እንኳ ሳያይ ባንድ ቀን ባለ ሚሊዮን ይሆናል። ሌላው ደግሞ ከሊስትሮነት ስራው፣ ከቆሸ ሰፈር ትርፍ ምግብ ለቀማው፣ ከአስፋልት ዳር ልመናና ጎዳና ተዳዳሪነት ሲባረርና ሲዋከብ እናያለን። ለምን ብለን መጠየቅ የለብንም? ከዚህ የባሰ የመብት መደፈርስ አለ እንዴ? ሁላችንም ልናስተውል ይገባናል።

ችግሮች እንዲቆሙ የተመኘንባቸው ወይም የሞከርንባቸው ዘመናት ገና ያኔ ያኔ አልፈዋል። ወያኔ ግን በችግር ላይ ችግር በመከራ ላይ መከራ ደራረበብን እንጅ መፍትሄ አላገኘንም። “እምብዛም ዝምታ ለበግም አልበጃት ሃምሳ ራሷን ሆና አንድ ነብር ፈጃት” ነው ብሂሉ። እኛ ለመብታችን መከበር እስቃልቆምን ድረስ ሕወሃት በየጊዜው ሌሎች አዳዲስ ምክንያቶችን እየፈጠረ ለማሰር ለማሰደድና ለመግደል አይቦዝንም። በፊት በፊት በ ኦነግ፣ በግንቦት 7፣ በአሸባሪነት፣ በአልቃይዳና በሌሎችም እያመካኘ የስርና ያንገላታ የነበረው ሕወሃት አሁን ደግሞ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል መመስረትን ተከትሎና በዚሁ ሃይል እያመካኘ ወጣቱን እያሰረና እያሰደደ መሆኑ ይሰማል። እና እኛስ እስከ መቼ ነው እንደተገረፍንና እንደተሰደድን የምንቀጥለው? አንተም ከማባረር አልተመለስክ እኔም ሁሌ መባረር መሮጥ ሰለቸኝ የምንለውስ ዛሬ ሊሆን ካልቻለ ለመቼና ለእንዴት ያለ ጊዜ ይቆጠባል?

ህወሃት ከበቂ በላይ የስቃይና የጥፋት ማስጠንቀቂያዎችን ሰጥቶናል። የግድ በግል በራሳችን ለይ ደርሶ ማየት እንሻለን እንዴ? ለዚያውም ባለፉት የሕወሃት ያገዛዝ ዘመናት ችግር ያልዳሰሰው ቤት ካለ መለቴ ነው። ይህን የጥፋት ሃይል አንድ ሆነን ቆመን መመከት ካልቻልን ዝምታን ከመረጥናና ወያኔ ባዘጋጀልን ወጥመድ ተጠልፈን ከገባን ኢትዮጵያ የምትባልን ሀገርም ሆነ የሕዝባችንን ከብር እንደገና ለመመለስ በጣም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው። “ለሁሉም ጊዜ አለው” ሀገርንና ሕዝብን ለማዳንም ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ረፍዷል ካልተባለ ጊዜው አሁን ነው። አንድ ላይ በመተባበር በውስጥ ሽኩቻ በአመራር ብቃት ማነስ በሕዝብ በመተፋት እና መጠላት የዘመመውን ሕወሃት ገፍተን እንጣለው።

Thursday, May 9, 2013

ENTC Norway chapter held talks with Norwegian officials about illegal bond sales by the Woyanne junta

Ethiopian National Transitional Council (ENTC) representative in Norway, Ato Girum Zeleke, and other members of the ENTC chapter spoke with officials of the Norwegian Ministry of Finance and Financial Supervisory Authority of Norway to find out about legality of diplomats selling bonds in Norway.

1st breach of the law:
Both Norwegian agencies have confirmed to the ENTC chapter that it is forbidden to sell unregistered bonds in Norway and in the European Union. Before bonds can be offered for sale to the public, they first must be registered with the Securities and Exchange Commission at the Financial Supervisory Authority of Norway. Any bond that does not have an effective registration statement on file with the authority is considered "unregistered." To sell or attempt to sell bond before it is registered is considered a felony in Norway.

2nd breach of law:
Woyanne junta representative Wzr. Mebrat Beyene has diplomatic status, but she is running a regular investment activity by selling bonds that requires a work permit from the Norwegian Immigration Directorate in Oslo. Carrying out an investment business by any diplomat is forbidden by the law. The Norwegian immigration officials affirmed to the ENTC chapter in Norway that Mebrat, who is a diplomat appointed by a government to conduct diplomacy with another government, has functions of diplomats revolving around the representation and protection of the interests and nationals of the sending state, as well as the promotion of information and friendly relations. According to the definition of the Financial Supervisory Authority of Norway, what Mebrat was doing (selling bonds) could not be defined as a diplomatic mission.

The ENTC Chapter of Norway has taken actions against these illegal acts into the Norwegian court through their lawyer Mr Christian Faye who filed a charge against the Ethiopian Ministry of Foreign Affairs.

The Norway ENTC chapter has also formed a special task force composed of Naod Kebede Geleta, Helen Deresa Wame, Argaw Kebede Feleke, Sebhat Amare Tefera, Nigus Tilu Gedefu, Ingdu Werku Kebede, and Addis Mamo Ghebremedihin to pursue the matter and make sure that the Woyanne junta will not be able to conduct any more illegal activity in Norway and through out Europe.

ethiopian review http://www.ethiopianreview.com/forum/viewtopic.php?f=2&t=52621

Wednesday, May 8, 2013

ጋዚጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤቱን እንዲለቅ ተገደደ

ሚያዚያ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ለጋዜጠኛው ቅርበት ያላቸው ወገኖች ለኢሳት በላኩት መረጃ እንደገለጹት ጋዜጠኛ ተመስገን ተከራይቶ በሚኖርበት ቀበና አካባቢ ያለው ቤቱን እንዲለቅ በአከራዩ የተነገረው አንድ የመስተዳድሩ ባለስልጣንና አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ አከራዩ ቤቱን እንዲያስለቀቁት ማስጠንቀቂያ ከ...ሰጡዋቸው በሁዋላ ነው።

የቤት አከራዩ “ ሁለቱ ሰዎች መጥተው ለመሆኑ ተመስገን ምን እንደሚሰራ ያውቃሉ ወይ? ተመስገን ማን እንደሆነስ ጠንቅቀው ያውቃሉ ወይ? ለማንኛውም ዛሬ የምናሳውቅዎት እርሱ ለአካባቢው ሰላም ያሰጋል፣ ከዚህ በሁዋላ እንዳያስቀጥሉት ” ብለው እንዳስጠነቀቁዋቸው ለጋዜጠኛው በመንገር በአስቸኳይ ቤት እንዲፈልግ ተማጽነዋል። ጋዜጠኛ ተመስገንም ቤቱን በፍጥነት ለቆ ለመውጣት እንደሚቸገርና የአንድ ወር የቤት መፈለጊያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የፍትህ ጋዜጣ አዘጋጆች ለራሳቸው አሲምባ የሚል ስም በሰጡት የጋዜጠኛው መኖሪያ ቤት ውስጥ የኢዲቶሪያል ስብሰባዎችን እና ጽሁፎችን ያዘጋጁ እንደነበር ለማወቅ ተችሎአል።

ጋዜጠኛ ተመስገን የሚያዘጋጀው ፍትህ ጋዜጣ በመንግስት ጫና እንዲቋረጥ ከተደረገ በሁዋላ ጋዜጠኛው ህተመቱን ሊያስቀጥል የሚችልበትን ፈቃድ እስካሁን አላገኘም። ከ106 በላይ ክሶች ያሉበት ተመስገን ፣ አሁንም ጽሁፎችን በፌስቡክና በተለያዩ ድረገጾች በመጻፍ ላይ ይገኛል።

Monday, May 6, 2013

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት አንዷለም አራጌን እንዳይጠይቁ በልዩ ሀይል ተባረሩ

andinet
 
የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ወጣቱን ፖለቲከኛና የፓርቲው አመራር አንዷለም አራጌን እንዲሁም ሌሎችን የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ለመጠየቅ ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ቃሊቲ ቢሄዱም ለመጠየቅ እንዳይችሉ መደረጋቸውንና እስካፍንጫቸው በታጠቁ ልዩ ሃይሎች በግድ ከአካባቢው እንዲርቁ መደረጋቸውን የህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አስታወቀ፡፡
 
እንደፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ገለፃ ከፍተኛው ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ወጣቱን ፖለቲከኛና ከፍተኛ አመራር አንዱአለም አራጌና ናትናኤል መኮንን ሽብርተኞች እንደሆኑና በሰላማዊ ትግል ሽፋን ሽብርተኝነትን እንደሚያራምዱ ተደርጎ የቀረበው ሀተታና ውሳኔ እጅግ ያሳዘናቸው በርካታ አመራሮችና አባላቱ በከፍተኛ መነሳሳትና ቁጭት ከ 20 በላይ የሚሆኑ የፓርቲው ሰዎች ከ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እንኳን አደረሳችሁ ለማለት ቢገኙም የተሰጣቸው ምላሽ አንዷለምን ምግብ ከሚያመላልሱለት ጥቂት ቤተሰቦቹ ውጭ ማንም መግባት እንደማይችል ተገልፆላቸው በታጠቁ ሃይሎች ከአካባቢው እንዲርቁ ተደርገዋል ብሏል፡፡
 
በዕለቱ ቃሊቲ እስርቤት ለመጠየቅ ከተገኙት መካከል ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፣ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ዶ/ር ያዕቆብ ሀይለማርያም፣ አቶ አክሉ ግርግሬ፣ አቶ ሙላት ጣሰው፣ አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን፣ አቶ ተክሌ በቀለ፣ አቶ ትዕግስቱ አወሉ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራና ሌሎችም የፓርቲው አመራሮችና አባላት እንደተገኙ የህዝብ ግንኙነት ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
 
የማረሚያ ቤቱ የወቅቱ ተረኞች የስም ዝርዝራቸውን መታወቂያቸውን እያዩ ከተመዘገቡ በኋላ ከአቅማቸው በላይ እንደሆነ ገልጠው ወደ ዋናው የአስተዳደሩ የመግቢያ በር በመግባት ሃላፊዎችን እንዲያነጋግሩ ነግረዋቸው ወደዚያው በማምራት ቢጠይቁም እንዲጠብቁ ከነገሯቸው በኋላ የተሰጣቸው ምላሽ መጠየቅ አትችሉም የሚል ነው፡፡ ከዚህ በፊት በተለይ አንዷለም አራጌን ከጥቂት ቤተሰቦቹ በስተቀር ማንም እንዳይጠይቀው የተደረገ ሲሆን በተደጋጋሚ ቢያመለክትም ምንም ምላሽ ማግኘት አለመቻሉ ይታወቃል፡፡ ከዚህ በፊት ግን የበዓል ቀናት ብቻ የፓርቲው አመራሮችና የስራ ባልደረቦቹ ለተወሰኑ ደቂቃዎች በጅምላ እንዲጠይቁት ቢደረግም በዘንድሮው የትንሳዔ በዓል ግን የገጠማቸው በልዩ የታጠቁ ሃይሎች መባረር ሆኗል፡፡ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ አካባቢውን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታጣቂዎች ወረውታል፡፡ ለመጠየቅ የመጡት መጠየቅ መብታቸው እንደሆነ ለማስረዳት ቢሞክሩም እነዚህ ሃይሎች መሳሪያቸውን በተጠንቀቅ በመያዝ ፀብ ለማስነሳት ሙከራ አድርገዋል በማለት የህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልፆልናል፡፡ (በፍኖተ ነጻነት የተላከ)

ጎልጉል

Sunday, May 5, 2013

ኦባንግ የኢህአዴግ ደጋፊ ስደተኞችን አስጠነቀቁ

“በአስመሳይ ስደተኞች ላይ በቂ መረጃ አለ”
obang
“ክፉን በክፉ መመከት ባያስደስትም ወቅቱ ያስገድደናል” ሲሉ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል ተናገሩ። አገዛዙን ሸሽተው በተለያዩ አገራት ከለላ አግኝተው በስደት የሚኖሩም ሆኑ ጉዳያቸው እየታየ ያሉ ወገኖች አካሄዳቸውን እንዲያስተካክሉ አስጠንቅቀዋል።
 
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ህግ አውጪዎች፣ የጀርመን የኢሚግሬሽን ሃላፊዎችና ከፍተኛ የፖለቲካ ሰዎች፣ ከኖርዌይ የኢሚግሬሽን ጉዳይ ሃላፊዎችና ተዛማጅ ሃላፊነት ካላቸው የህግ ክፍሎች፣ በካናዳ በተለያዩ ደረጃ ካሉ ባለስልጣናትና ወትዋቾች (አክቲቪስቶች)፣ በስዊድን አንዲሁም በእንግሊዝ በተመሳሳይ ግንኙነት ፈጥረው እየሰሩ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አገራቱ የስደት ፈቃድ ካገኙ በኋላ ለስደት ዳረገን ከሚሉት መንግሥት ጋር በቅርብ እየሰሩ ስላሉ አስመሳይ ስደተኞች አስገራሚ መረጃዎች መሰብሰባቸውን አውቃለሁ” ብለዋል።
 
አቶ መለስ በሞቱ በወር ጊዜ ውስጥ ብቻ በካናዳ ቫንኮቨር 27 አንድ አይነት ቋንቋ ብቻ የሚናገሩ ወጣቶች ጥገኛነት መጠየቃቸውን ጉዳዩን በጥብቅ እየመረመሩት ካሉ ክፍሎች ማረጋገጣቸውንና የምርመራውን ውጤት በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ “ወጣቶቹ ካናዳ የገቡት ለእያንዳንዳቸው 75 ሺህ ዶላር በማውጣት ነው። ይህን ገንዘብ ማን ሰጣቸው? እንዴት አገኙት? እንዴት ከአንድ አካባቢ (ክልል) ብቻ ሊሆኑ ቻሉ? የሚሉት ጉዳዮች ምርመራውን በያዙት ወገኖች ላይ ግራሞት የፈጠረ ትልቅ ጉዳይ ነው” በማለት የጉዳዩን አሳሳቢነት ከገንዘብ ማሸሽ ጋር በማያያዝ አመላክተዋል። ለምሳሌ አንድ ጉዳይ አነሱ እንጂ በመላው ካናዳ በተመሳሳይ የምርመራ ስራ እየተሰራ መሆኑንን ተናግረዋል።
 
የካናዳው አንድ ማሳያ ሲሆን በአሜሪካ ግዙፍ ቪላዎችን እየገዙ ያሉት ክፍሎች ጉዳይ ከገንዘብ ማሸሽ ጋር ተያይዞ እየተመረመረ እንደሆነ አቶ ኦባንግ አስረድተዋል። ጥገኝነት ካገኙ በኋላ “ሊገለን ሲል አመለጥነው” ያሉትን ኢህአዴግን የሚደግፉ ክፍሎች ላይም ለሚመለከታቸው ባለስልጣናትና ተቋማት ከሚቀርበው መረጃ በተጨማሪ ከፍትህ ወዳድ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ድርጅታቸው በጥምረት እየሰራ መሆኑን አቶ ኦባንግ አልሸሸጉም፡፡
በጀርመን ኑረንበርግ በኢሚግሬሽን ጉዳዮች ዙሪያ የሚሰሩ ባለስልጣናት በተመሳሳይ የምርመራ ስራ እያከናወኑ እንደሆነ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ በግል በጉዳዩ ዙሪያ መነጋገራቸውን አስታውቀዋል። የጥገኝነት ፈቃድ ካገኙ በኋላ ዲያስፖራውን በመከታተልና አገር ቤት የሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለችግር እንዲዳረጉ የሚያደርጉትን ክፍሎች ማንነት ነቅሰው እንደሚያውቋቸው ባለሥልጣናቱ በግንኙነታቸው ወቅት እንዳረጋገጡላቸው አመልክተዋል።
“ኢህአዴግ ለጊዜው የጠመንጃ ሃይል አለው። የገንዘብ አቅም አለው። ወዳጆችም አሉት። እኛ ደግሞ በየአቅጣጫው ፍትህ ወዳድ አጋሮች አሉን። ከነሱ ጋር እየሰራን ነው” በማለት አስረግጠው የተናገሩት ኦባንግ በማንኛውም መስፈርት ስደት ላይ ያሉ ወገኖችን መከታተልና መሰለል ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
 
“አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ፣ እንግሊዝ፣ ስዊድንና ጀርመን አገር ባለስልጣናቱ ከበቂ በላይ መረጃ አግኝተዋል። እኛም እየሰራንበት ያለ ተከታታይ ስራ አለ። በየአቅጣጫው የሚደረገው ትግል በቅርቡ ፍሬው መታየት ይጀምራል” የሚሉት ኦባንግ ርምጃው መወሰድ ሲጀምር ከስድስት እስከ አስራ ሁለት ዓመት እስር እንደሚያስከትል፣ ከዚያም የከፋ አደጋ እንዳለው ጠቁመዋል።
በትምህርትና በተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ተለያዩ ዓለማት የሚሰማሩ የአገዛዙ አገልጋዮችም ቢሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው የሚያሳስቡት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር “አገዛዙ መድቧቸው በየኤምባሲው ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፣ የስለላ ሰዎች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናት ምስላቸውንና ማንነታቸውን ባደባባይ አይገልጹም። በኤምባሲዎች ድረ ገጽ ላይ እንኳ ስለማንነታቸው በቂ መረጃ ለመስጠት ድፍረት የላቸውም። የስርዓቱ ባህሪና የወንጀለኛነቱ መጠን ራሳቸውን እንዲገልጹ አይፈቅድላቸውም” በማለት በተራ መደለያና ጥቅማ ጥቅም ደረታቸውን እየሰጡ ያሉ ወገኖች አካሄዳቸውን በመመርመርና የሚያስከብራቸውን ተግባር እንዲፈጽሙ ጥሪ አስተላልፈዋል።
 
“ምክር በመለገስ ሰፊ ጊዜ የወሰድነው ክፉን በክፉ የመመለስ እምነት፣ ክፉ እንድናደርግ የሚገፋን ድርጅታዊ አቋም ስለሌለንና የሚጠሉንን ጭምር ነጻ የሚያወጣ ግዙፍ ራዕይ ስላለን ነው” የሚል ጥልቅ አስተያየት የሰነዘሩት አቶ ኦባንግ፣ በአገራቸው መኖር ያልቻሉ ወገኖች ተሰደውም ሰላም ሲያጡ መመልከት ግን የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን አመልክተዋል። ከዚህም በተጨማሪ እሳቸው በግል፣ ድርጅታቸው በመርህ የሚታገሉለት የሰዎች መብት መከበር ብሩህ አጀንዳ በዝምታ እንዲቀመጡ እንደማይፈቅድላቸው ተናግረዋል።
 
ከኖርዌይ የኢሚግሬሽን ባለስልጣናት ጋር በተገናኙባቸው ወቅቶች ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ በግልጽ እንደነገሯቸው ያመለከቱት ኦባንግ ሜቶ፣ አሁን ስሙንና ዝርዝር ጉዳዩን ለመናገር ፈቃደኛ ካልሆኑት ክፍል ጋር በጋራ እየሰሩ መሆኑንን ጠቁመዋል። አኢጋን ያቋቋመው የግልጽነትና የተጠያቂነት ግብረ ሃይል አንዱና ትልቁ ስራው እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን መርምሮና አጣርቶ ለሚመለከታቸው በማቅረብ ፍትህን መጠየቅ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ዝርዝሩን መናገር ቢከብድም ብዙ ስራ እየሰራንበት ያለው የስደተኞች ጉዳይ የሌሎችንም ተሳትፎና ትብብር ይጠይቃል” ብለዋል።
 
“በስሜት መታገል አያዋጣም” የሚል የትግል ማስተካከያ ሃሳብ ፈንጠቅ ያደረጉት አቶ ኦባንግ የስደት ማመልከቻቸው ተቀባይነት አግኝቶ የመኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ አገር ቤት በመመላለስ፣ ህግ በመተላለፍ ለአገዛዙ የሚሰሩ በሙሉ “ብልጥና አዋቂ ነን፣ ባለጊዜዎች ነን” በሚል አስተሳሰብ የሚንቀሰቀሱ አንደማያዋጣቸው ሲያሳስቡ “ለእንደዚህ አይነቶች ሁሉም ዓይነት መንገድ አይሰራላቸውም። ግለሰቦችንና ባለስልጣናትን ሳይሆን አሰራርን በማጭበርበር ይጠየቃሉ። አገራቱ እንደ ኢትዮጵያ ሳይሆን ስራ ላይ የሚውል ህግ አላቸውና ይተገብሩባቸዋል። አሰራራቸው ሲጭበረበር ዝም የማይሉት ለማንም ሲሉ ሳይሆን ለራሳቸው ሲሉ ነው። አሰራር / ሲስተም/ ሲበረዝ የሚያስከትለውን አደጋ ስለሚረዱ የሚታገሱ ካልሆነ በቀር በዝምታ አያልፉም። በኖርዌይም ሊሆን የታሰበው ይህ ነው። አሁንም ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እቸገራለሁ” በማለት ነው። አቶ መለስ ህይወታቸው ባለፈ ወቅት በስደት ካምፕ የሚኖሩ ጭምር ለቅሶ መቀመጣቸው በኖርዌይ ሚዲያዎች አስገራሚ ተብሎ መዘገቡ፣ በህዝቡና በፖለቲከኞች ዘንድ መነጋገሪያ አጀንዳ እንደነበር አይዘነጋም።
 
በርካታ አሳዛኝና ህሊናን የሚፈታተኑ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሆነ ያወሱት ኦባንግ ሜቶ፣ ህጻናትን በጉዲፈቻ ስም በመቸብቸብ፣ ሴት እህቶቻችንን አረብ አገራት ያለ ዋስትና በመላክ ከፍተኛ ገበያ እየሰሩ ያሉት የህወሃት ሰዎች እንደሆኑ በበርካታ ማስረጃዎች መረጋገጡን ያስታውሳሉ። አያይዘውም አገራቸውን ለቀው ለስደት የሚወጡትን ወደ ኬኒያ፣ ታንዛኒያና ደቡብ አፍሪካ ብሎም በጅቡቲና በሶማሌ በኩል ገንዘብ እያስከፈሉ የሚያሻግሩት አሁንም እነሱ ናቸው ሲሉ አስቀድመው ስለ ጠየቁት ትብብር ማሳሰቢያቸውን ያጠናክራሉ።
 
“በማስተዋል እንስራ” የሚሉት ኦባንግ በየአቅጣጫው መረጃ ላይ የተኙና፣ በምን አገባኝ ስሜት ዝምታን የመረጡ ወገኖች ያላቸውን መረጃ በመስጠት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከተለያዩ አካላት ጋር እየሰራ ያለውን ስራ እንዲያግዙ አሳስበዋል። ይህንን ማድረግ አቶ ኦባንግንና እርሳቸው የሚመሩትን ድርጅት መርዳት ሳይሆን ራስንና አገርን መርዳት እንደሆነም አጽንዖት ሰጥተው
ተናግረዋል።

 aba
 
ከተቋቋመ 135ዓመታትን ያስቆጠረው የአሜሪካ ሕግ ባለሙያዎች ማኅበር (ABA) እየተባለ በሚጠራውና 400 ሺህ በላይ አባላት ባሉት የህግ ባለሙያዎች ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት ንግግር እንዲያደርጉ በተጋበዙበት ወቅት አቶ ኦባንግ ሜቶ በርካታ ጉዳዮችን በማንሳት ድጋፍ ጠይቀው አዎንታዊ ምላሽ እንዳገኙ ጠቅሰዋል፡፡ በርካታ የህግ ባለሙያዎች በተገኙበት ስብሰባ ላይ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ኢህአዴግ ህግን ከለላ በማድረግ በዜጎች ላይ የሚፈጽመውን ወንጀል፣ ለእንደዚህ ዓይነት ተግባሩ ማስፈጸሚያም የጸረ ሽብርተኝነትን፣ የመያዶችን፣ ወዘተ ህጎች በማውጣት ዜጎችን ለእስር፣ ለስደት፣ ለስቃይ መዳረጉን፣ የፍትህ አካላቱን ህግን በሚያከብሩና ፍትህ በሚያስፈጽሙ ሳይሆን ራሱ በመሠረተው ተቋም እያመረተ ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን፣ ከዚህ አልፎ ደግሞ በስደተኛነት ስም ደጋፊዎቹን ወደ ውጪ በመላክ በሃሰት የኢህአዴግ ሰለባ በማስመሰል በየምዕራቡ ዓለም የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያገኙ በማስደረግ መልሶ ስደተኛውን እዲሰልሉና ለሥርዓቱ እንዲሰሩ እያደረገ መሆኑን፣ ወዘተ በስፋት አብራርተዋል፡፡ የባለሙያዎቹ ማኅበር ጉዳዩን በጥልቀት እንደሚያየውና ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል በመጠቀም ከአኢጋን ጋር እንደሚሰራ ከሌሎች ማኀበራት ጋር በመሆንም በተለይ በምዕራቡ ዓለም የተሰገሰጉትን አስመሳይ ስደተኞች ወደ ፍትህ የማምጣቱ ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ለአቶ ኦባንግና ለድርጅታቸው አረጋግጠዋል፡፡

ምንጭ ጎልጉል
 

Saturday, May 4, 2013

ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ የሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ የ2013 ሽልማት አሸናፊ ሆነ

 ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በስዊድን በስደት ላይ የሚገኘው የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ሽልማቱን ያገኘው በኢትዮጵያ በሽብረተኝነትና በህገወጥ መንገድ ወደ አገር በመግባት ተከሰው ከአንድ አመት በላይ ታስረው ከተፈቱት የስዊድን ጋዜጠኞች ከሆኑት ማርቲን ሽብየ እና ጆሀን ፒርሰን ጋር በጋራ በመሆን ነው።

ጋዜጠኛ መስፍን በውጭ አገር ሆኖ ለፕሬስ ነጻነት በመታገሉ ለሽልማት እንደበቃ ድርጅቱ አስታውቋል። ጋዜጠኛ መስፍን “ሽልማቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ስራ በመስራት ላይ ላሉ እንዲሁም በእስር ቤት ውስጥ ላሉ የሙያ ባልደረቦቼ እውቅና የሚሰጥ ነው” በማለት ተናግሯል።
ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ የሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ የ2013 ሽልማት አሸናፊ ሆነ
ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በስዊድን በስደት ላይ የሚገኘው የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ሽልማቱን ያገኘው በኢትዮጵያ በሽብረተኝነትና በህገወጥ መንገድ ወደ አገር በመግባት ተከሰው ከአንድ አመት በላይ ታስረው ከተፈቱት የስዊድን ጋዜጠኞች ከሆኑት ማርቲን ሽብየ እና ጆሀን ፒርሰን ጋር በጋራ በመሆን ነው።

ጋዜጠኛ መስፍን በውጭ አገር ሆኖ ለፕሬስ ነጻነት በመታገሉ ለሽልማት እንደበቃ ድርጅቱ አስታውቋል። ጋዜጠኛ መስፍን “ሽልማቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ስራ በመስራት ላይ ላሉ እንዲሁም በእስር ቤት ውስጥ ላሉ የሙያ ባልደረቦቼ እውቅና የሚሰጥ ነው” በማለት ተናግሯል።

Friday, May 3, 2013

የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም


ሀገራችንን አንቆ የሚገዛው ወያኔ ራሱን የልማት መንግስት ነኝ በሚል ራሱን በሚጠፋ ስእል ላይ አስቀምጦል። በየአመቱ የተጋነነ እና የሌለ ነጠላ የስታቲስቲክ ዜማ እየለቀቀ ያቀርባል። በዴሞክራሲያዊ መንገድ ህጋዊ መሰረት ማግኘት ስለተሳነው በልማታዊ መዝገብ ስም ለመገኘት አይን የአወጣ ሙከራ ያደርጋል።

የወያኔ ልማት ሰዋዊ ሽታ የለውም። ለዘረኛው መንግስት ልማት ማለት ብልጭልጫዊ ነገር ማሳየት እንጂ የሰውን፣ የህዝቡን ጉስቁል ኑሮ መቀየር ማሻሻል መሆኑን አያውቅም። አንድ ሺ አፈናቅሎ አንድ የስርአቱን አገልጋይ ቱጃር ያከብርና አገር ለማ ይለናል። የጋምቤላን አኙዋኮች ከአያት ቅድመ አያት መሬት አፈናቅሎ በርሃብ እየቆላ፣ የአረብና ህንድ የሩዝ ሁዳድ ስላደረገው ብቻ አገር ለማ ከበሮ ደልቁ ይለናል።

ወያኔ ልማት ለሰው መሆኑን ወይ አያውቀውም አሊያም ረስቶታል። በአዲስ አበባና በብዙ አካባቢዎች መንደርን እያፈረሰ የሚበትናቸው ዜጎች፤ ከእነሱ ጋር እድራቸው፣ ሰንበቴያቸው፣ ማህበራቸው፣ ማህበራዊ ህይወታቸው አብሮ እንደሚፈርስ ቢያውቅም ግድ የለውም። የወያኔ ልማት ሰውን ወደተራ እንስሳነት የሚያወርድ የወሮበላ ስራ ነው።

ህወሃት እንደ መንግስት ሱፍ ለብሶ፣ በሌላ በኩል እንደ ኢፈርት ባለቤትነቱ ወዛደር መስሎ ውል ይፈራረማል። ኢፈርት የሚገጣጥመውን መኪና ለመከላከያ ሚኒስተር ይሸጣል፤ እንደ መንግስት በህዝብ ስም እርዳታ ይቀበላል፣ እንደ ወሮበላ ዘራፊ ስማቸውን ቀይረው ወዲያውኑ ዘረፋውን ይጀምራል። ይህን የመሰለ የዘቀጠ ውንብድና በህዝብ ንብረት ላይ እየሰሩ ሌሎችን የወያኔ ግልገሎች ደግሞ ሌቦች፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች እያሉ ሲሳደቡ አይናቸውን አያሹም።

የወያኔ አለቆች ድሃ ገበሬዎችን ከመኖሪያቸው ሲያፈናቅሉ ደን ስለጨፈጨፉ ነው የሚል የፈጠራ ክስ ይፈጥሩና የኤፈርት ኩባንያዎች ኢሉ አባቦር ውስጥ የያዩን ደን እየጨፈጨፉና እያጋዩ የሚሰሩትን የዝርፊያ ማእድን ቁፈራ ልማት ነው ይሉናል።

ወያኔ በሚገዛት ኢትዮጵያ ባለሀብት መሆንና ሀገር አልምቶ ራስን መጥቀም ገደብና መስመር አለው። ብዙ ኢንቨስተሮች የወያኔ ባለስልጣንን በአጋርነት፣ በሸሪክነት እንዲያስገቡ ይገደዳሉ። አሊያም ሀብቱን ላለመነጠቅ የፈለገ ሀብታም ልሁን ባይ የዳጎሰ ገንዘብ ለባለስልጣናቱ እጅ መንሻ ለኪስ ተጠይቀው ይሰጣሉ። በአንጻሩ የወያኔን የሀብታምነትን ቀይ መስመር ዘለው እምቢ ያሉ እስር ቤት የተጣሉ፣ የተሰደዱ በተለይ ወያኔ ከሚጠላው የጎሳ ወገን የሆኑ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ፣ የልማት ተስፈኞቹ በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች ተጨናንቀዋል።

ዛሬ ዛሬ ጤፍ ጠፋ ተወደደ፣ ስኳር ጠፋ ምን እንሁን፣ መብራትና ውሃ ጠፋ ፈረቃው በዛብን ሲባሉ፤ መልሳቸው አስገራሚ እና አሳዛኝ ነው፡፡ ይህ ሁሉ የጠፋው፣ የምትራቡት አገሪቱ እያደገች ስለሆነ ነው የሚል የማላገጥ መልስ ይሰጣሉ። የሚሉት እድገት ቁልቁል እንደካሮት እየጨመረ ያለውን ድህነት መሆኑን ማለታቸው ነው።

በኢትዮጵያ የነገሰው ደህነት፣ ከድህነቱ ጋር የተያያዘው መጠነ ሰፊ ተስፋ መቁረጥና ስደት ለወያኔ ምኑም አይደለም። ምናልባትም የአገሪቱን እድገት ያመጣው ነገር ነው በሚል መላምት የሆነ፣ የይሆናል ግምታቸውን ይሰጡናል።

የአደገችና የበለጸገችን ኢትዮጵያ ከመፍጠር ይልቅ በልማት ስም የግል ምቾታቸውንና ድሎቶቻቸውን ለማስጠበቅ፣ ብሎም የስልጣን ጊዚያቸውን ለማራዘም ሲሉ፤ ህዝብን ከቀዪው በማፈናቀል ለርሃብና ለስቃይ ለስደት እየዳረጉት ይገኛሉ።

ህወሃቶች የሀብት ክፍፍል በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በሚል የአካባቢውን ነዋሪ በማንነቱ ምክንያት አፈናቅለው የህወሃት አባላትንና ደጋፊዎችን የመጥቀም ስትራቴጂዎችን ቀርጸው ሰፊውን የህዝብ ጉልበት እንደ መዥገር መጠው፣ በቀዪው ያፈራውን ንብረትና ገንዘብ እንኳ ሳይሰበስብ ያፈናቅሉታል። ታዲያ የትኛው የልማት ስትራቴጂ ይሆን ህዝብን ማእከል ያደረገው?

የተማሩ ዜጎች በተማሩበት ሙያ ሰርተው በልማቱ ሂደት ራሳቸውንና ሀገራቸውን እንዳይጠቅሙ አድረገው ራእያቸው በማጨለም በጨፍን የስርአቱ ባሪያ አገልጋይ አሊያም አጨብጫቢ እንዲሆኑ ሆነው ይቀረጻሉ፤ አሊያ ግን መጽዋት ጠባቂ ወይም ከሀገር እንዲሰደዱ ይደረጋሉ።

የወያኔ ልማት ህዝብ ህዝብም፣ ሰው ሰውም አይሸትም! ስለዚህም በአገር አልሚነት ስም ማንንም ማታለል አይችልም። ይህ የዝርፊያና የፈንጋይ የወያኔ ኢኮኖሚ ከራሳቸውና ከጉጅሌዎች ባለፈ ውጭ የሚጠቅመው ኢትዮጵያዊ አይኖርም።
ኢትዮጵያ ለሁሉም ልጆቿ የሚሆን የተፈጥሮ ጸጋ አላት። ምቹ የአየር ንብረት፣ ለም አፍርና በተስተካከለ መልከዓ ምድር የተቸረች ሀገር ነች። ልጆቿ ሁሉ የዚህ ጸጋ ባለቤት እንዳይሆኑ እና ዜጎቿ በእኩልነት ተጠቃሚ ሳይሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሆነው እንዲሰደዱ እያደረገ ያለው ወያኔ ነው። ወያኔ አልሚ ሳይሆን የልማት ፀርና የአንድነት ቀበኛ ነው።

በኢትዮጵያ ልማትም፣ እድገትም፣ እኩልነትም፣ ሰብአዊ ክብርም፣ ተስፋም፣ በሀገር መኩራትም እንዲኖር ወያኔ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መወገድ አለበት። ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ለነዚህና ለእውነተኛ የሰበአዊ መብት መከበር፣ ሁሉም ዜጎች በሀገራቸው የትኛውም ቦታ በእኩልነት ሰርቶ የማደግ መሰረታዊ መብቶች፤ ህዝብን ማእከል ላደረገ እውነተኛ ልማት እና ሀገራችንን ከመፈራረስ አደጋ ለመታደግ ረጅሙን የትግል ጉዞ በአንድ ርምጃ ጀምሮአል፡፡ እርሰዎስ? ኑ! ተቀላቀሉን፡፡ ድህነት፣ ውርደት፣ ስደት እስከመቼ?

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Thursday, May 2, 2013

አቶ ሃይለማርያም ለአውሮፓ ህብረት የገባውን ቃል አፈረሰ::የወያኔ የፖለቲካ ፍርድ ቤቱ በእነ እስክንድር ነጋ ላይ ፍርዱን አጸና::



አዲስ አበባ ያሉ ዲፕሎማቶች መታገስ ነው ይላሉ:;
ምንሊክ ሳልሳዊ

ባለፈው የአውሮፓን ህብረት ለመጎብኘት ወደ ብራስልስ ያመሩት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በህብረቱ በቆዩበት ጊዜ ተደጋግሞ ሲነሳላቸው የነበረው ጉዳይ የእስረኞች ጉዳይ እንደነበር ይታወቃል ::በዚህም መሰረት በሕወሓት መራሽነት የሚተሙት አቶ ሃይለማርያም እጅግ ጥብቅ የሆነ ቃል ገብተው ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸውን የትላንት ዜናችን ነበር :; እንዲሁም ከዚህ ቀደም በተለያዩ ወቅቶች ሟቹ ጠ/ሚ የተለያዩ ገንዘቦችን እና መደለያዎችን ከህብረት በልማት ስም በመውሰድ ቃል እየገቡ ነገሩ ጎትተውት አልፈዋል:: ህብረቱ የልማት እርዳት ሲያደርግ የነበረ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ያለውን የተካረረ ነገር ላማላልት እና ወደ ስብኣዊ መብቶች ላይ ለማተኮር መሆኑን በተደጋጋሚ ገልጿል::

ከወደ አዲስ አበባ ዛሬ በፍርድ ቤቱ አሳዛኝ ፖለቲካዊ ውሳኔን ተከትሎ በሃገር ውስጥ ያሉ የተለያዩ ዲፕሎማቶች ሁኔታው ከማስገረምም አልፎ አስደንግጦናል ሲሉ ተደምተዋል:: ሆኖም የመንግስታቹህን ጭራ ለመያዝ ይከብዳል የሚሉ ዲፕሎማቶች ነገሮችን በትእግስት መመልከት እና መጠበቅ ነው ሁኔታዎች ሊቀየሩ ይችላሉ የውስጥ አጣብቂኞች የፈጠሩት ውሳኔ ይሆናል ምናልባት......የጀመርነውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንቀጥላልን ብለዋል::

ዛሬ በጠቅላይ ፍርድቤት የዋለው የፍርድ ሂደት በእስንድር ነጋ የ18 አመት እና አንዷለም ላይ የእድሜልክ እስራት ያጸና ሲሆን ዳኛው የወያኔ ጀሌው ዻኜ መላኩ ክሱም ሆነ ውሳኔው ትክክል እና ምንም አስተያየት ሊደረግለት የማይችል ሲል ከታሪክ ተጠያቂነት የማይድንበትን አስተያየት የሰጠ ሲሆን ሌሎች የጠቅላይ ፍ/ቤ ዳኞች አናየውም ብለው እስከ በላይ አካል ክርክር የተኬደበትን ጉዳይ ከምን ሞራል እንዲህ ሊደመድምበት እንደቻል ጊዜ ይጠይቀዋል::
እንደዚህ አይነት በፍትህ ላይ ጠባብ አመለካከታቸውን እና ጸረ ህዝብ አቋማቸውን የሚያራምዱ ዳኞችን መከታተል እና ከየተደበቁበት ጊዜ ጠብቆ መጋለጥ የዜግነት ግዴታ ነው:: ይህ መንግስት ሲወድቅ በተለያዩ የአውሮፓ እና የአሜሪካ ከተሞች ለመመሸግ እያለሙ የሚገኙት የፍትህ አካላትን መከታተል ግዴታችን ነው::

ከፍርዱ በኋላ "እውነት ነጻ ታወጣናለች!!!" ያለው እስክንድር ነጋ "የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እውነት በራሱ ጊዜ እንደሚወጣ ለኢትዮጵያውያን ማሳወቅ እንፈልጋለን "ብሏል:የተከሰሱበት ጉዳይ በአሸባሪነት እና አሸባሪ ተብሎ በተፈረጀው ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላቹህ ተብለው ቢሆንም ከዚህ በፊት ጉዳዩን እንዲያዩት ይግባኙ የቀረበላቸው ዳጛ አማረ አሞኘ ይህን ክስ ለማየት የሚያስችል በቂ ማስረጃ ስላሌለ በነጻ እለቃቸዋለሁ በማለታቸው ጉዳዩ ከሳቸው እጅ ተነጥቆ ፖለቲካዊ ዉሳኔ እንዲሰጥበት ተደርጓል::
በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ያለው የፍርድ ቤት ስርኣት እና ውሳኔዎች በአለም አቀፍ ደረጃ አነጋጋሪ ከሆነ ረዥም አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን የወያኔ ካንጋሮ ፍርድቤት እና ያልሰለጠኑ በፖለቲካ ታማኝነት ዳኛ የሆኑ ያልበሰሉ ካድሬዎች እየወሰዱ ያለው ህገወጥ እርምጃ እና ውሳኔ ነገ እንደማያስጠይቃቸው ሆነው መታየታቸው ሃገር ምን ያህል በፍትህ እጦት ቀውስ ውስጥ እንደሆነች ያሳያል:; ለግል የወያኔ ጥቅማጥቅሞች እና የኑሮ ምጮት እየተገዙ ያሉት የህግን ከለላ እንኳን ምን ያህል ስሜቶችን መረዳት ያልቻሉ ፍርደገምድል ዳኞችን መፋረድ ግዴታችን ነው::
እስክንድር ነጋም ሆኑ ሌሎች እስረኞች ቀን ሳይረዝም በቅርብ ጊዜ እንደሚለቀቁ ባለሙሉ ተስፋ ስሆን ይህ ደሞ ወያኔ እየደረሰ ያለበትን ኪሳራ እያሳየን ነው :: በተለያዩ የአውሮፓ እና የሰሜን አሜሪካ ከተሞች ወያኔ እየደረሰበት ያለውን ውርደት ለማካካስ እየተጠቀመበት ያለው ስልት እንደማያዋጣው ልንነግረው ይገባል::
ዲያስፖራው ትግሉን ያቆማል ብሎ የሚያስብ ከሆነ ዘላለሙን በጫካ ሞኝነት ራሱን የሚነዳው ወያኔ ልክ እያስገባነው መሆኑን አልተረዳውም:; በተከታይነት ደሞ በቀሪ የህሊና እስረኞች ላይ ሊወስን የተዘጋጀውን እየጠበቅን ትግሉ ግን ወያኔ አፈር እስኪገባ እንደሚቀጥል ለመናገር እወዳለሁ :: ትግሉ ይቀጥላል!!!

ምንጭ ምኒልክ ሳልሳዊ

የሕዳሴው” ግድብና ደሞዜ

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ

ከስድሰት ወር በፊት እሠራበት የነበረው የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ለግድቡ መዋጮ የፈለግነውን ያክል ገንዘብ የምናዋጣበት ባዶ ቅጽ ላከልን። ብዙዎቻችን የወሩን ሦስት አራተኛ በጥልፍልፍ ብድር የምናሳልፍ በመሆኑ ገሚሶቻችን በትሕትና ማዋጣት እንደማንችል ስንገልጽ ቀሪዎቹ ደግሞ “መቶም፣ ሁለት መቶም በዓመት ክፍያ ይቆረጥብን” ብለው ፈረሙ። ይህ ያላስደሰታቸው አለቆች ከቆይታ በኋላ 50% ደሞዛችንን በዓመት ክፍያ እንድናዋጣ የተጻፈበት ቅጽ ሊያስፈርሙን ሲያመጡ የፈቃደኝነታችን ሥርዓተ ቀብር ተከናወነ። እኔ አልፈርምም አልኩኝ። የድኅረ ምረቃው ት/ቤት ም/ፕሬዚደንት ቢሮዬ ድረስ መጥቶ ተማፀነኝ – “የተቋማችን ስም ይጎድፋል” በማለት። እኔም አልኩት “ወር በገባ በ10ኛው ቀን ከሚያልቀው ደሞዜ ላይ የማዋጣው ገንዘብ የለኝም፣ ከቻሉ የገቢ ግብሬን ይጠቀሙበት – ለማይወክለኝ ግንቦት 20 ድግስ ርችት የሚተኩሱበትንና ከአፌ ነጥለው የወሰዱትን ታክስ መጀመሪያ ባግባቡ ይጠቀሙበት። አሁን ግን አዋጣ ከምትሉኝ ልቀቅ ብትሉኝ እመርጣለሁ። በእኔ ገንዘብ እየተሠራ ኢሕአዴግ ራሱን በኢቴቪ ሲያሞግስ ማየት አልችልም” ብዬ ተንጣጣሁ። አስብበት ብሎ ቅጹን አስቀምጦልኝ ሄደ።

የሕዳሴው" ግድብና ደሞዜ

30 ደቂቃ ቆይቼ ሄድኩና “አሰብኩበት ግን አላዋጣም” አልኩት።

ነገሩ በዚህ ያበቃ መስሎኝ ሳለ የዛሬ ስድስት ወር ገደማ በግል ጉዳዬ ተቋሙን ልለቅ ሳመለክት እና ‘ክሊራንስ‘ ሳዞር የሕዳሴው መዋጮ ቀሪ አምስት መቶ ምናምን ብር አለብህ ተባልኩ። “I was like ‘what?!’” ይሉ ነበት ፈረንጆቹ ቢሆኑ። ድንግጥ አልኩ።

 “ያ አሲዳም ደሞዜ ወትሮም ከብድር ከፋይነት የትም አላደረሰኝ። ለካስ በየወሩ እየተቀነጠበ ነበር የባሰ መቅኖ ያጣብኝ” አልኩና ባሳቤ “በማን ፈቃድ ቆረጣችሁት?” አልኳት ሒሳብ ሠራተኛዋን። የሆነ ዶሴ ፈልፍላ አወጣችና “አቶ በፍቃዱ …. እስካሁን ስላልተቆረጠባቸው … ከዚህ ወር ጀምሮ …” ደብዳቤው እንደቃለጉባኤ ያለ ሲሆን ከግርጌው ፊርማዎች ሰፍረውበታል።

ም/ፕሬዚደንቱ ቢሮ ብስጭቴን ይዤ ሄድኩ። “እኔ የለሁበትም” ተባልኩ። የፋይናንስ ኃላፊውጋ ሄድኩ “ተቋሞች በሙሉ የሠራተኞቻቸውን ደሞዝ አምሳ በመቶ ለማዋጣት ስለተስማሙ ሁሉም ሠራተኛ ግዴታ ማዋጣት አለበት ተብሎ ተወስኗል” አለኝ። “በገዛ ደሞዜ ማን የመወሰን ሥልጣን አለው? የኔ ደሞዝ የመንግሥት ፓሊሲ ለማውጣት የማይተገበረው የድምፅ ብልጫ ለምን ይተገበርበታል?” በማለት አማረርኩ። በጩኸት “እከሳችሀኋለሁ” እያልኩ ዛትኩ።

ከዚያ በኋላ ግን አንደኛ “አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ” መሆኑን እያወቅኩ ለማን እከሳለሁ? ሁለተኛ መቼም ጉዳዩ የአገር ጉዳይ ነው፣ እስኪ ከፕሮፓጋንዳ ተርፏቸው ከሠሩት ይሥሩበት በማለት ቀሪውን ከ‘ፕሮቪደንት ፈንዴ‘ ላይ ከፍዬ ለቀቅኩ። ምናልባትም ከከሰስኩ ተቋሜን ሳይሆን መከሰስ የሚገባውን የምከስበት ቀን ይመጣል!
ይህ ከሆነ ጀምሮ ያተረፍኩት ነገር ብስጭት ነው። ከጉሮሮዬ ነጥዬ ያዋጣሁት እኔ እያለሁ፣ “አባይን የደፈረ ጀግና” ሌላ ነው። እኔ ካሁን አሁን ግድቡ አለቀ ብዬ በጉጉት እጠብቃለሁ፣ የግድቡ ፅንሰት እየተባባሉ በገንዘቤ ደግሰው ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ይጨፍራሉ። ይህንንም በኢቴቪ ያስተላልፋሉ።