Saturday, July 18, 2015

ኢትዮጵያ ከ184 አገራት 171ኛዋ ደሃ አገር!

July 18,2015

“ኢኮኖሚ በመንገድና ፎቅ ሥራ አይለካም”
women carrying

ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የአምስት ዓመታት አኻዝ ያካተተ የዓለማችንን ሃብታምና ደሃ አገራት ዝርዝር ሰሞኑን አውጥቷል፡፡ የዓለም የፋይናንስ መጽሔት ላይ የታተመው ይኸው ዘገባ እንደሚያሳየው በሃብታምና ደሃ አገራት መካከል ያለው ልዩነት በእጅጉ እየጨመረ እንደመጣ ነው፡፡ በዚህ የአምስት ዓመት አኻዛዊ ዘገባ መሠረት ከ184 አገራት መካከል ኢትዮጵያ 171ኛ ተራ ላይ የምትገኝ ስትሆን ይህም በድህነት ከሚጠቀሱት ቀዳሚ አገራት ቁጥር ውስጥ አስገብቷታል፡፡ ዘገባውን የተመለከቱ የኢኮኖሚ ባለሙያ የአንድ አገር ኢኮኖሚ በከተሞች ውስጥ በሚሰራ ፎቅ ብዛት እና የመንገድ ሥራ አይለካም ይላሉ፡፡ ሌላ የኢኮኖሚ ባለሙያ ደግሞ “ኢኮኖሚ ከቁጥር ሌላ ሥነ ልቦናዊ ጉዳይም ነው፡፡ የኑሮ ጉዳይም ነው፡፡ የጉሮሮ ጉዳይም ነው፡፡ በቁጥር ብቻ አይለካም፡፡ … የሕንፃ መሐንዲስ ቢሳሳት ሕንፃ ይደረመሳል፡፡ የሰው ኑሮ መሐንዲስ ሲሳሳት ግን ሕይወት ይጠፋል፣ ሕዝብ ያልቃል፣ ትውልድ ይረግፋል፣ አገር ይበጠበጣል፡፡ በዓይናችን እያየነው ነው” ይላሉ፡፡
ይፋ በሆነው ጥናት እንደተገለጸው ደረጃው የወጣው በተለይ ሁለት የኢኮኖሚ መለኪያዎችን በማቆራኘት ነው፡፡ እነዚህም የአገር ውስጥ ምርት (GDP) በካፒታል የሚባለውንና የመግዛት ኃይል ንጽጽር (purchasing-power-parity (PPP) በማጣመር ነው፡፡ በቀላል አገላለጽ PPP ማለት ኅብረተሰቡ የሚጠቀምባቸውን የተወሰኑ የተለመዱ ሸቀጦችን (ለምሳሌ ዳቦ፣ እርሳስ፣ የብርቱካን ጭማቂ፣ ወዘተ) ሰብስቦ በአንድ ቅርጫት ውስጥ በማድረግ ዋጋቸውን መተመን ነው፡፡ እነዚህ በአንድ ቅርጫት ውስጥ የተካተቱት ሸቀጦች አጠቃላይ ዋጋ ኢትዮጵያ ውስጥ 50 ዶላር ቢሆን ኬኒያ ደግሞ 100 ዶላር ቢሆን በኢትዮጵያና በኬኒያ መካከል ያለው የመግዛት ኃይል ንጽጽር 1፡2 (አንድ ለሁለት) ነው ማለት ነው፡፡ ይህንን ቀመር ከአጠቃላይ የዓለም አገራት ጋር በማነጻጸር የአንድን አገር ሕዝብ የመግዛት አቅም ከመላው ዓለም አገራት ጋር ማነጻጸር ይቻላል፡፡ ጥናቱ ያደረገውም ይህንኑ ነው፡፡
በኢኮኖሚክስ ጥናት መሠረት የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒን) መለኪያዎች በርካታ ናቸው፡፡ አንዱ ምርቱን ለማምረት በወጣው የመለካት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከዋጋ ንረት ጋር በማገናዘብ የመለካት ስልት ነው፡፡ ይህ ጥናት የተጠቀመበት መለኪያ ደግሞ ጂዲፒን በካፒታል መለካት ሲሆን ይህም የአንድ አገር ገቢ በነዋሪው ሕዝብ ተካፍሎ የሚመጣው ነው፡፡ የጥናቱ አቅራቢዎች ይህንን የጂዲፒ ውጤት ከመግዛት ኃይል ንጽጽር ጋር በማካፈል ነው መረጃውን ይፋ ያደረጉት፡፡ ይህ ዓይነቱ የመግዛት ኃይል ንጽጽርን ግምት ውስጥ ያስገባ የጂዲፒ አለካክ በኅብረተሰቡ ውስጥ የሚታየውን የኑሮ ውድነት በስሌቱ ውስጥ የሚያካትት በመሆኑ ከሁሉም የጂዲፒ መለኪያዎች የተሻለ ነው የሚል አስተያየት ይሰጥበታል፡፡
economic map
Darkest red: highest GDP per capita (PPP) Medium red: medium-high GDP per capita (PPP) Light red: medium-low GDP per capita (PPP) Lightest red: lowest GDP per capita (PPP)
በእነዚህ የኢኮኖሚ ስሌቶች መሠረት የተደረገው የአምስት ዓመታት ጥናት (እኤአ 2009-2013) እንዳመለከተው በዝርዝሩ ከተካተቱት አገራት ኢትዮጵያ 171ኛ ተራ ላይ ነው የምትገኘው፡፡ ኳታር በአንደኛነት ስትገኝ ሉግዘምበርግ ሁለተኛ፣ ኖርዌይ ሦስተኛ፣ ብሩናይ አራተኛ፣ ሲንጋፖር አምስተኛ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ስድስተኛ፣ አሜሪካ ሰባተኛ፣ ሆንግ ኮንግ ስምንተኛ፣ ስዊትዘርላንድ ዘጠነኛ፣ ኔዘርላንድስ አስረኛ ተራ ላይ ሰፍረዋል፡፡ በዘገባው ላይ እንደተጠቀሰው የእነዚህ አገራት በካፒታል ላይ የተሰላው የ2013 ዓም ጂዲፒ ከመግዛት ኃይል ንጽጽር ጋር ተካፍሎ የተገኘው ውጤት በአሜሪካ ዶላር የሚከተለው ነው፡፡ ኳታር $105,091.42፣ ሉግዘምበርግ $79,593.91፣ ኖርዌይ $56,663.47፣ ብሩናይ $55,111.20፣ ሲንጋፖር $61,567.28፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ $49,883.58፣ አሜሪካ $51,248.21፣ ሆንግ ኮንግ $53,432.23፣ ስዊትዘርላንድ $46,474.95፣ ኔዘርላንድስ $42,493.49፡፡ ይህ ማለት አንድ አገር የምታመርተውን አምርታ፣ የኑሮው ውድነት ተሰልቶ እና በዚያች አገር ውስጥ ያሉት ሸቀጦች የሚያወጡት ዋጋ ከሌሎች የዓለም አገራት ጋር ተነጻጽሮ አንድ ሰው ሊኖረው የሚችለው የገንዘብ መጠን ተብሎ በግርድፉ ሊወሰድ ይችላል፡፡ (ማሳሰቢያ፡ እዚህ ላይ ለማሳያነት የ2013 ዓም ብቻ በማውጣታችን የቁጥርና የደረጃ ልዩነት ይታያል፡፡ ይህም የሆነው የአንዳንዶቹ አገራት ዘገባ የተወሰደበት ዓመት ከሌሎቹ ጋር ተመሳሳይ ባለመሆኑ ነው፡፡ ሙሉውን ዘገባ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል)
በድህነት ከሰፈሩት አገራት ተራ የምትመደበው ኢትዮጵያ (171ኛ $1,258.60) በበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቀድማለች፡፡ ሴራሊዮን 170ኛ ($1,559.95)፣ ማሊ 168ኛ ($1,136.77)፣ ጊኒ ቢሳው 166ኛ ($1,268.46)፣ ኮሞሮስ 164ኛ ($1,296.77)፣ ሩዋንዳ 162ኛ ($1,591.71)፣ ዑጋንዳ 160ኛ ($1,459.62)፣ ታንዛኒያ 159ኛ ($1,670.21)፣ ዛምቢያ 158ኛ ($1,841.64)፣ ኬኒያ 156ኛ ($1,884.57)፣ ቻድ 155ኛ ($2,061.63)፣ ሱዳን 144ኛ ($2,550.10)፣ ናይጄሪያ 141ኛ ($2,883.44)፣ ጂቡቲ 139ኛ ($2,778.25)፣ ጋና 137ኛ ($3,501.53)፡፡
ኮከቡ ያልሰመረለት ትሪሊየን ጂዲፒ በሚል ርዕስ (June 14, 2015) በታተመው ሪፖርተር ላይ ጽሁፍ ያቀረቡት የኢኮኖሚ ባለሙያ ጌታቸው አሰፋ በኢትዮጵያ ያለውን የኢኮኖሚ ሁኔታና መጪውን እንደሚከተለው ይገልጹታል፡፡
“ገንዘቡ ዋጋ ያጣው ገቢ አሁንም ቢሆን ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ቢሆንም፣ የገቢ ዕድገት ከምርታማነት ዕድገት በላይ ስለሆነ ነው፡፡ ምርታማነት የቀነሰው የመንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ዕድገት፣ የሥልጠና ዕድል፣ ሙያዊ ክህሎትን መገንባት፣ ወዘተ የሚቻለው አለቃን በማምለክ እንጂ ችሎታን አዳብሮ ውድድር ውስጥ በመግባት ስላልሆነ ነው፡፡ … ሥራ ፈጠራ በብሎኬት ምርት፣ መስኮትና በር መግጠም፣ አልባሳት፣ ቦርሳና ቀበቶን የመሳሰሉ የግል መጠቀሚያዎችን ማምረት ጀምሮ አሁን ወደ ጀበና ቡና፣ ቦርዴ (ሻሜታ) ጠመቃ፣ የዓረብ ሱቅ፣ በቆርቆሮ ግድግዳ ደሳሳ ጎጆ የሆቴል ኪዮስክ ወርዷል፡፡ ከዚህ በታች ወዴት እንደሚወርድ አይታወቅም፡፡ …
“ምርታማ ሆኖ ገንዘብ ማግኘት ካልተቻለ አጭበርብሮም፣ ቀምቶም፣ ሰርቆም፣ የሰው አካልንም ቢሆን ደልሎ ገንዘብ ለማግኘት ይሞከራል፡፡ ውድድር ሳይሆን ሽሚያ ይፈጠራል፡፡ በኢትዮጵያ እያደገ የመጣው ይህ አጉል የመስገብገብ፣ የመሻማት፣ የመሻሻጥ ባህሪይ ነው፡፡ ሁላችንም በባህሪይ፣ በአስተሳሰብና መስሎ በመታየት ደላላ እየሆን ነው፡፡ በመንግሥት ድጋፍ በሦስት ሺሕ ብር የፈጠራ ሥራ ጀምሮ በዓመቱ ሦስት ሚሊዮን ብር ካፒታል ማስመዝገብ፣ መቶ ሺሕ ብር ለደላላ ከፍሎ ወደ ሞት ለመሄድ መደራደር፣ ለጥቂት ደቂቃዎች መዝናኛ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ማውጣት፣ ቅጥ ላጣ የውጭ አገር ጉዞ የቅንጦት ወጪ ማድረግ፣ ምልክት የጥሬ ገንዘብ ከጓሮ የሚሸመጠጥ ቅጠል መምሰል ነው፡፡ …
“አምና በመቶ ሺሕ ብር መነሻ ካፒታል የከተማ ሥራ ጀምሬ ዘንድሮ ሦስት ሚሊዮን ብር ካፒታል አለኝ፣ በግማሽ ሔክታር መሬት የግብርና ሥራ አሥር ሚሊዮን ብር ካፒታል አለኝ፣ የሬድዮና የቴሌቪዥን ፕሮፓጋንዳ የወጣቱን ሥነ ልቦና ሰለበ፡፡ የሥራ ባህል ጠፋ፡፡ ገንዘብ ተሠርቶ የሚገኝ ሳይሆን ከሜዳ የሚታፈስ ወይም ጓሮ ከበቀለ ዛፍ የሚሸመጠጥ መሰለ፡፡ መቶ ሺሕ በትኖ ሚሊዮን ለማፈስ የተሰናዳ ትውልድ ተፈጠረ፡፡ ከሠርቶ በሌው አውርቶ በሌውና ዘሎ በሌው በዛ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ትምህርትን አቋርጦ ጊታር ማንሳት ተለመደ፡፡ …
“የጋራ በሆነ መሬት ላይ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና እንክብካቤ መሥራት የሚቻለው በጋራ ብቻ ነው፡፡ የጋራ የሆነም የግል አይደለም፡፡ የግል ያልሆነም ገበያ አይወጣም፡፡ ገበያ ያልወጣም የገበያ ዋጋ የለውም፡፡ የገበያ ዋጋ የሌለውም በገበያ ዋጋ በገንዘብ አይተመንም፡፡ ስለዚህም በሪፖርት ከምናየውና ከሚነገረን የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) መጠን ገሚሱ የገበያ ዋጋ የሌለው ምናባዊ ስሌት ነው፡፡ የኑሮ መሐንዲሱ ኢኮኖሚያዊ ኑሮን ወደ ምናባዊ ሥሌት ከወሰደው የሕዝብ ገቢ መጠንና ኑሮም በገበያ ተለክቶ እውነቱ የሚታወቅ ሳይሆን ምናባዊ ይሆናል፡፡ አመለካከቱና አስተሳሰቡም የኑሮው ነፀብራቅ ነውና ኑሮውን ተከትሎ ምናባዊ ይሆናል፡፡ ሲያገኝም ሲያወጣም በምናባዊ ሥሌት ነው፡፡ ሳይበላ የበላ መስሎ፣ ሳይጠጣ የጠጣ መስሎ፣ ሳይደላው የደላው መስሎ፣ ያላመነውን ያመነ መስሎ፣ ያልተቀበለውን የተቀበለ መስሎ፣ የናቀውን ያከበረ መስሎ፣ የጠላውን የወደደ መስሎ በመታየት በምናባዊ ዓለም ውስጥ ይኖራል፡፡…poor
“ሕዝቡ ከምናባዊ ዓለም ወጥቶ ገሃዱን ዓለም እንዲቀላቀል የኑሮ መሐንዲሱ ኢኮኖሚስት አለ ብሎ በወረቀት ላይ የሚጽፈውን የምርት መጠን ለሽያጭ ወደ ገበያ አውጥቶ፣ በበያ ዋጋ አስተምኖ እውነተኛውን በገበያ ዋጋ የተለካ የምርት መጠን ያሳየን፡፡ ያለበለዚያም የገንዘብ አቅርቦቱ ለገበያ በቀረበው ምርት መጠን ልክ ሆኖ በዋጋ ግሽበት ስቃይ እንዳን፡፡ እኔ እንኳ በሩቁ ከማውቀው ወደ ገበያ ከማይቀርቡና ማገበያያ ገንዘብ ከማያስፈልጋቸው ምርቶች ውስጥ ከጠቅላላ ጂዲፒው አንድ ሦስተኛው የሚሆነው፣ ገበሬው ከራሱ እንደገዛ ተቆጥሮ በምናባዊ ሥሌት በገንዘብ የሚለካው የግብርና ምርት ይገኝበታል፡፡ በወረቀት ላይ የሚመለከቱ የአገር ውስጥ ምርት መጠን ቁጥርና ለፕሮፓጋንዳ የሚያገለግሉ ጥንስስ ፕሮጀክቶች ስም ጋጋታ ሳይሆን፣ የአጠቃላዩ ሕዝብ ምርታማነት ብቻ የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ወሳኝ ነው፡፡…
“አንጀት ላይ ጠብ የሚለው ሺዎች ለሚሊዮኖች አስበውና ተደራጅተው ሲሠሩ ሳይሆን፣ የአጠቃላዩ ሕዝብ ሚሊዮኖች ለራሳቸው አስበው በገበያ ውስጥ ተወዳድረው እንዲሠሩ የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሁኔታዎች ሲመቻችላቸው ነው፡፡ ‹‹ጧት ጧት ዳቦአችንን ጠረጴዛችን ላይ የምናገኘው በዳቦ ጋጋሪው የፅድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ለራሱ ገንዘብ ለማግኘት ሲል በሚሠራው ሥራ ነው›› አዳም ስሚዝ፡- ነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት ጠንሳሽ፡፡ ‹‹ልማት ማለት አንድ ሰው ሊሆንና ሊያደርግ የሚፈልገውን ሕጋዊ ነገሮች የመሆንና የማድረግ ነፃነትና አቅም ሲያገኝ ነው›› አማርተያ ሴን፡- በ1998 በልማት ኢኮኖሚክስ የኖቤል ተሸላሚ፡፡”
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በፋይናንስ መጽሔት ላይ ያወጣውን ይህንን መረጃ የተመለከቱ በኢትዮጵያ የግል ትምህርት ተቋም የኢኮኖሚክስ ባለሙያ የሆኑ ለጎልጉል እንዳሉት የዴሞክራሲን መንገድ የተከተለችው ጋና ከሌሎቹ የሰሃራ በታች አገራት በከፍተኛ ፍጥነት የማደጓ ምክንያት ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደሚጠቀስ ጠቁመዋል፡፡ የዕድገቷ መጠንም ዘገባው በተጠናቀረበት ባለፉት አምስት ውስጥ ያልተዛባ ነገር ግን ሥርዓት ያለው ዕድገት እያሳየች መሆኗን ጨምረው ተናግረዋል፡፡ አክለውም ሲናገሩ “አንድ የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ያልሆነ ሰው ይህንን ዘገባ በመመልከትና የኢትዮጵያን ደረጃ ከሌሎቹ የአፍሪካ አገራት ጋር በማነጻጸር ብቻ ለምን ኢትዮጵያውያን ለተሻለ ኑሮ ወደሌሎች አገራት እንደሚኮበልሉ መናገር ይችላል፤ የአገራችን ሕዝብ ያለው አቅም እጅግ የወደቀ በመሆኑ በአቅም ከምትበልጠን ጂቡቲ መሰደድ እንደ አማራጭ ሊወሰድ ይችላል” ብለዋል፡፡ በመጨረሻም “እንደ ባለሙያ ለመንግሥት አካላት የኢኮኖሚውን ጉዳይ ስናስረዳ የሚሰማን የለም፤ ከዚያ ይልቅ እንደ ካድሬ ፕሮፓጋንዳ እንድንናገር፣ ኢኮኖሚው በድርብ አኃዝ እንዳደገ እንድንደሰኩር፣ ወዘተ ነው የሚፈለግብን፡፡ ሃቁ ግን ይኸው በገሃድ የሚታይ ነው፤ የአንድ አገር ዕድገት በበርካታ የኢኮኖሚ መመዘኛዎች በሳይንሳዊ መንገድ የሚለካ ነው እንጂ በዘጋቢ ፊልም በታጀበ የመንገድ ሥራና የፎቅ ብዛት ጨርሶውኑ ሊሆን አይችልም፤ ምናልባትም ካልተሳሳትኩ በዓለም ላይ ኢኮኖሚዋን በመንገድ ሥራና በፎቅ ብዛት የምትለካ አገር ኢህአዴግየሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አትቀርም” ብለዋል፡፡ethio poor
የኢኮኖሚ ባለሙያው ጌታቸው አሰፋ ሪፖርተር ላይ ያወጡትን ጽሁፍ ሲያጠናቅቁ እንዲህ ይላሉ፤ “የአገር ውስጥ ምርት በግሳንግስ ምርቶች ማበጡ የምርታማነት ማደግ አይደለም፡፡ ያበጠ ነገርም ይፈርጣል፡፡ ኢኮኖሚ ሲፈርጥ ደግሞ ማኅበራዊ ቀውስ ያመጣል፡፡ ‹ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል› ተረት እንዳይተረትብን፡፡ የብሔራዊ ገቢ ሒሳብ ባለሙያው በተቀመጠለት የማዕከላዊ ዕቅድ የጊዜ ገደብ አገሪቱን በእጁም በእግሩም ገፍቶ መካከለኛ ገቢ ደረጃ ለማድረስ አስቦ፣ በነፃና በጋራ የሚሠራውን የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሥራ በምናባዊ ሒሳብ የአገር ውስጥ ምርት ሥሌት ውስጥ አካቶ ሊሆንም ይችላል ምርቱን ያሳበጠው፡፡ ኢኮኖሚ ከቁጥር ሌላ ሥነ ልቦናዊ ጉዳይም ነው፡፡ የኑሮ ጉዳይም ነው፡፡ የጉሮሮ ጉዳይም ነው፡፡ በቁጥር ብቻ አይለካም፡፡ እንደ ዶሚኖ ጨዋታ ቁጥር በመገጣጠም ብቻም የሚገነባ አይደለም፡፡ የሕንፃ መሐንዲስ ቢሳሳት ሕንፃ ይደረመሳል፡፡ የሰው ኑሮ መሐንዲስ ሲሳሳት ግን ሕይወት ይጠፋል፣ ሕዝብ ያልቃል፣ ትውልድ ይረግፋል፣ አገር ይበጠበጣል፡፡ በዓይናችን እያየነው ነው፡፡”
ይህንን ዓለምአቀፍ የደረጃ ዘገባ በመመርኮዝ እኤአ እስከ 2020 ድረስ ይህ የደረጃ ስሌት እምብዛም ለውጥ ሳያሳይ እንደሚቀጥል በርካታ ትንበያዎች አሉ፡፡ በሌሎች ደግሞ ምናልባትም በዝቅተኛው ተራ ላይ የሚገኙት አገራት እጅግ እየደኸዩ በሃብታምና በደሃ መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ ለከፍተኛ የማኅበራዊ ቀውስ እየተጋለጡ ይሄዳሉ የሚል ሙያዊ ስሌትም ይሰጣል፡፡ (ፎቶ: ከኢንተርኔት የተገኙ በጎልጉል የተገጣጠሙ)
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, July 16, 2015

አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጠ (የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ይዘናል)

July 16,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
andargachew new picture
የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር በአካል ተገናኝታችኋል›› የሚል ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሾቹ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችኋል ከተባለ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ታስረው የሚገኙ በመሆናቸው መከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ይታዘዝልን›› የሚል ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
የፌደራል አቃቤ ህግ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ አይችሉም ብሎ ተቃውሟል፡፡ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህዝባዊ መብት በመሻሩ ለፍርድ ስራ ልዩ አዋቂ ወይንም ነባሪ ሆነው መስራት አይችሉም ያለው የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በተጨማሪ ምስክርነት ቀርበው መመስከር አይገባቸውም ሲል የተከሳሾቹ ጥያቄ ውድቅ እንዲሆን ለፍርድ ቤቱ አመልክቶ ነበር፡፡
ሆኖም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር ለምስክርነት በመሆኑ፣ ምስክርነትም ግዴታ እንጅ መብት በመሆኑ ሰኞ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ለተከሰሱት ተከሳሾች ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲመሰክሩ ወስኗል፡፡ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው የት እንደሚገኙና ማዘዢያው የት ተብሎ ሊፃፍላቸው እንደሚገባ ተጠይቀው ለቃሊቲ ማረሚያ ወይንም ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ሊጻፍላቸው እንደሚገባ፣ ካልቀረቡላቸውም ክሳቸው ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር የተገናኘ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ አቤቱታ እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል፡፡


ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው በጠየቁበት ወቅት በዳኞችና በአቃቤ ህጎች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ መፈጠሩንና ከአቶ አንዳርጋቸው ይልቅ ሌሎች መከላከያ ምስክሮችን ማቅረብ እንደሚችሉ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት ለማቅረብ መሞከር እንደሌለባቸው እንደገለፁላቸው ታውቋል፡፡ ዳኛው በድንጋጤ ‹‹እኛ እዚህ ጉዳይ ላይ የለንበትም›› ማለታቸውን ተከሳሾቹ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ ላነጋገራቸው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ገልጸውለታል፡፡
andargachew

Tuesday, July 14, 2015

Ethiopian journalist on fear of returning to prison

July 14, 2015
by Andrew Harding | BBC News

It’s never an easy decision: Should I interview someone who wants to talk in public, but who knows that a word out of line could mean arrest and imprisonment?

Ethiopian journalist Tesfalem Waldyes
“I’m still scared that I might go back to prison” says journalist Tesfalem Waldyes
I’ve wrestled with the issue before in Myanmar, also known as Burma, Zimbabwe, Iraq and elsewhere.
Ethiopian journalist Tesfalem Waldyes sat in a hotel in Addis Ababa last weekend, and decided it was necessary to speak out.
“I’m afraid. I’m still scared that I might go back to prison… Maybe today, maybe this afternoon.
“[Journalism here] is a very dangerous job, because there’s this red line that was marked by the government, and we don’t know when we crossed that red line,” he said.
‘Totally absurd’
Last week Mr Tesfalem was unexpectedly released from a remand prison outside the capital, along with four colleagues.
He and eight other bloggers and journalists had been imprisoned for well over a year, facing trial under Ethiopian anti-terrorism legislation – accused of working with forces seeking to overthrow the state.
“It’s totally absurd…. Our work has appeared in newspapers, magazines.
“We are only doing our jobs,” he said, declining to speculate on whether the timing of his release was linked to a big UN development summit being hosted in Ethiopia this week, or President Barack Obama’s visit later in the month.
Mr Tesfalem said he did not want to talk about prison conditions, for fear of provoking Ethiopia’s government, but he was motivated to speak out on behalf of the four journalists still in detention.
“I beg all the international community, all concerned people… to push, to keep pushing… for the release of our friends.
“The charges are very similar. There is no difference between me and those guys who are still languishing in prison,” he said.
Ethiopia is a de facto one party state, after the governing EPRDF won every parliamentary seat in May’s election.
Although it has presided over extraordinary economic growth, and a rapid reduction in extreme poverty and child mortality in the past decade, it is regularly criticised for human rights abuses, and is often ranked as one the world’s “most censored” countries.

አንዱዋለም አራጌ ለልጁ የጻፈው – የሚሊዮኖች ድምጽ

July14,2015
Andualem f
ሁለት ሕጻናት  አሉት። የመጀመሪያ ወንድ ልጁ ሩህ ይባላል። ከአራት አመታት በፊት፣ ልጁን ከትምህርት ቤት ሊያወጣ ወደዚያ ሲያመራ ታጣቂዎች ከበቡት። እየሰደቡ፣ እየደበደቡ ወደ ወህኒ ወሰዱት። አንድ ፖሊስ ይበቃ ነበር። ግን የለየለት ነፈሰ ገዳይ የሚይዙ ይመስል፣  ይሄን አንድ ሰላማዊ የልጅ አባት ለመያዝ ተረባረቡ። አይ ጭካኔ !

ይህ ሰው አንዱዋለም አራጌ ነው። የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳነት የነበረ፣ አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኛ። ባላጠፋው ጥፋት፣ ለሰላም በቆመ፣ በዉሸት ክስ፣ ሽብርተኛ ተብሎ የእድሜ ልክ  እስራት የተፈረደበት።
ልጅ ሩህ ከዚያ ቀን ጀምሮ ከአባቱ ጋር አላደረም። አባቱ ለአገርና ለሕዝብ ሲል ወህኒ ወረደ። አገር ትጠቀም ተብሎ ልጅ ሩህ አባት ተነፈገ።  አገር ልጥቀም ብሎ እንዱዋለም አራጌ፣ እንደ  ሌሎች አባቶች ልጆቹን የማሳደግ እድል ተነፈገ። ለአገርና ለሕዝብ በመቆሙ፣ የአገርን የሕዝብ ጥቅምን በማስቀደሙ የጨካኞ በትር አረፈበት። ይህ የኢትዮጵያ ኔልሰን  ማንዴላ የሆነው  አንዱዋለም አራጌ !!!!!
አንዱዋለም አራጌ፣  አልጋ ዳር ሆኖ ከልጆቹ ጋር መጫወት፣ ለነርሱ ተረት ማውራት፣ የልጆች መጽሃፍ ማንበብ አልቻለም። ግን በመንፈስ ከነርሱ ጋር ነው የሚያድረው። ያለዉን ፍቅርና ናፍቆት ከቃሊቲ በጽሁፍ ይገልጻል። ለወንድ ልጁ ሩህ  አንድዋለም ሲጽፍ “ከዘላለም በፊት የተቸርከኝ  …እንኳን ወለድኩህ” ይላል። “የአምባብገነኖች ግፍ ሰለባ” ይለዋል፤ አገዛዙ በዉሸት ክስና  በግፍ ዜጎችን በሚያስረበት  ጊዜ የሚጎዱት ልጆች፣ ቤተሰብም እንደሆነ ለማሣየት።
አንዱዋለም አራጌ ከሚወዳቸው ልጆቹ መለየቱ ትልቅ ሕመም እንደሆነበት ደብዳቤው ያሳያል። ሆኖም አንዱዋለም እርሱ የኖረባት በግፍ የተሞላች፣ በዘረኝነት የተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለልጆቹ ማስረከብ አልፈለገም። እርሱ መስዋትነት ከፍሎ ልጆቹና የየልጅ ልጆቹ በነጻነት እንዲኖሩ ይህ ወያኔዎች “ሽብርተኛ”  የሚሉት ምመላአው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንደ ጀግና የሚያየው ወጣት የአንድነት መሪ በጨካኖች በትር ስቃይ እየደረሰበት ነው።
ከዋክብትና ብርሃናት ሰማያትና አለማት
በፈጣሪ ቃል ከመፌጥራቸው በፊት
በዚያ በፈጣሪ እቅፍ በዚያ በኔ ጉልበት ዉስጥ
ከስጋና ደሜ ተዋህደህ
ከነፍሴ ደም ስሮች ጋር ተገምደህ
በልቤ ጓዳ ዉስጥ ተኝተህ ሳለህ የማውቅህ
ከዘላለም ዘመናት በፊት የተቸርከኝ
ከዘላለም ዘመናት በፊት የወለድኩህ
በድቅድቅ ዉስጥ ያገኝሁህ
የነፍስያዬ ሃቅል ሩህ
የሕይወቴ የብርሃን ጎርፍ
የሕይወቴ ምገስ ካባ
የፌሽታዬ ምንም ቀዘባ
የአምባገነኖችን ግፍ ሰለባ
የአብይተነታቸው ማሳያ ጫማ
በውል የማታወቀው እስረኛ አባት ጠያቂ
ያለተመለሱ ጥያቄዎች ማህደር አማቂ
የነፍስዬ ሃቅል ሩህ በድቅድቅ ዉስጥ ያገኘሁህ
የሕይወቴ የብርሃን ጎርፍ
እንኳን ወደዚህ አለም መጣህ
እንኳን በድጋሚ ወለድኩህ

Saturday, July 11, 2015

አካባቢውን የምታተራምሰው ኢትዮጵያ ነች - ኤርትራ

July 11,2015
የኢትዮጵያና የኤርትራ ካርታዎች ከየባንዲራዎቻቸው ጋርየኢትዮጵያና የኤርትራ ካርታዎች ከየባንዲራዎቻቸው ጋር
አካባቢውን እያተራመሰች ያለችው ኢትዮጵያ እንጂ ኤርትራ አይደለችም” ሲሉ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ዳይሬክተር አስታወቁ፡፡


የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ዳይሬክተር  አቶ ፀሐዬ ፋሲል ዛሬ ከአሜሪካ ድምፅ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ችግር ለመሸፈን ስትል የምታሰማው የተለመደ ፉከራ ነው፤ ኤርትራ ለአካባቢው መረጋጋት እየጣረች ያለች ሃገር ነች ብለዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም ሰላም ቢሉም የሰው ግዛት በኃይል ይዘው ሰላም እንፈልጋለን ማለታቸው አስቂኝ ነው” ብለዋል አቶ ፀሐዬ፡፡

አቶ ኃይለማርያም ያስተላለፉትንን ዛቻ አዘል መልዕክት አስመልክቶም “ኤርትራ ከልማቷ አታፈገፍግም፤ ለፉከራውም ትኩረት አትሰጥም” ሲሉ አክለዋል፡፡የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃን አስመልክቶ የተናገሩት አቶ ፀሐዬ “በማንኛውም የሦስተኛው ዓለም ሃገር ውስጥ የሰብዓዊ መብቶች ችግር ሁልጊዜ ያለ ቢሆንም ኤርትራ ግን በተሻለ ሁኔታ ሰብዓዊ መብቶችን ታከብራለች” ብለዋል፡፡

የኤርትራን ወጣቶች መሰደድ አስመልክቶ ለተነሣላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ኢትዮጵያና ሌሎችም የውጭ ኃይሎች በቪዛና በመሣሰሉ አማላይ ጥሪያዎች ወጣቶቹ ሃገራቸውን እየጣሉ እንዲወጡ፤ ብዙ ገንዘብ መድበው የሚያካሂዱት ዘመቻ ውጤት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ስለ እውነት፣ ስለፍትሕ እናት ኢትዮጵያ አሁንም ትጮኻለች!!

July 11, 2015
በዲ/ን ተረፈ ወርቁ
Few bloggers and journalists freed in Ethiopia
የኢሕአዴግ መንግሥት አሸባሪዎች ናቸው፣ በዜጎች ክቡር ደም የቆመውን ሕገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ የተደራጁ ናቸው፣ በውጭ አገር ካሉ ሰላማችን፣ ዕድገታችን በቅናት ብግን እያደረጋቸው ካሉና አገራችንን ለማተራመስ ቆርጠው ከተነሡ ከፈረደበት ሻቢያ፣ ሽብርተኛ ድርጅቶችና ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር አብረው ይሠራሉ፣ የአገርንና የሕዝብን ደኅንነትና ፀጥታ አደጋ ላይ ጥለዋል፣ በኢትዮጵያ ሰላምና በሕዝቦቿ ልዑላዊነትም ላይ በመደራደር ይቅር የማይባል ክህደት ፈጽመዋል ያላቸውን የዞን ፱ ጦማርያንና ሌሎች ጋዜጠኞችን ከአንድ ዓመት በላይ ፍርድ ቤት ሲያመላልሳቸው ቆይቷል፡፡
ማብቂያ የሌለው በሚመስል ቀጠሮ በነጋ ጠባ ወደ ፍርድ ቤት ሲመላለሱ የቆዩ ወገኖቻችንም ያን አምኖ ለመቀበል ቀርቶ ለመስማት እንኳን የሚከብድ ክስና የወንጀል ማስረጃ አቅርቤባችኋለኹ ያላቸውንና ፍርዳቸውን ከእውነት፣ ከፍትሕ አምላክ ሲጠብቁ የነበሩ ወገኖቻችንን መንግሥት በነጻ ተሰናብታችኋል ሲል የመለቀቃቸውን ዜና እንደ ዋዛ አበሰረን፡፡ መንግሥት እነዚህን ወገኖቻችንን በነጻ ያሰናበተበትን ምክንያቱን አልነገረንም፡፡ ቅሉ እንዲነግረንም የምንጠብቀው ሰዎችም ያለን አይመስለኝም፡፡
ኢሕአዴግ እንደቀደመው ጊዜም መንግሥት መሐሪ ነውና በአገርና በሕዝብ ላይ ላደረሳችሁት ክህደትና ወንጀል ይቅርታ ጠይቁና ነጻ ውጡ የሚለውን የተለመደች ብልጣብልጥነቱንም አልተጠቀመም፡፡ በዚህ ሰበብም ሽማግሌዎችንም እነዚህን ሰዎች እባካችሁ ማልዱኝ፣ አማልዱኝ በሚል አላደከመም፡፡ እንደው ብቻ ደርሶ ነጻ እኮ ናችሁ ሲል በአንድ ሺ አንድ መረጃና ሰነድ ወንጀላቸውን፣ ኃጢአታቸውን ሰማይ የሰቀለውን እነዚህን ሰዎች በአንዲት ማዘዣ ቃል ብቻ ነጻ ናችሁ ሲል አሰናበታቸው፡፡
መቼም ዘንድሮ ኢሕአዴግ እፍረትና ይሉኝታ ይሉትን ባህላችንን አሸቀንጥሮ የጣለ ነው የሚመስለው፡፡ ምርጫውን መቶ በመቶ አሸንፌያለኹ ብሎ ባወጀ መሬት አንቀጥቅጥ ድሉ ማግሥት ደግሞ እነዚህን በአገር ልዑላዊነት በሕዝብ ጥቅም ላይ የተደራደሩ ሰዎችን ማን ወንድ ነው ፍርዳቸውን ሳያገኙ፣ የእጃቸውን ሳይከፈሉ ከእጄ የሚያወጣቸው ሲል እንዳልነበር፣ እንዳልተገዘተ ኹላ ‹‹ሾላ በድፍኑ›› እንዲሉ አበው ከአንድ ዓመት በላይ በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን እነዚህን ወገኖች በነጻ አሰናብቼቸዋለኹ እንግዲህ ደስ ይበላችሁ ሲል ዜናውን፣ የምስራቹን አበሰረን፡፡
እኛም መንግሥትን እንደው እነዚህን ወገኖች ስታስርም ሆነ ስትፈታ ምክንያትህ ምንድን ነበር በሚል ጥያቄ ራሳችንን ስናሞኝ አንገኝም፡፡ መንግሥት ምክንያቱ ምንም ይሁን ምንም እነዚህ ወገኖቻችን በነጻ በመለቀቃቸው የሁላችንም ደስታ፣ ሐሤትና እረፍት ነው፡፡ ሌሎችም ያለ ፍርድ የታሰሩ፣ ፍትሕን የተነፈጉ ወገኖቻችንም ነጻ ይወጡ ዘንድም ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ከዚህ ግማሽ ደስታ ባሻገር ግን አሁንም ሌላ ጥያቄ፣ ሌላ ብሶት፣ ሌላ ቁጭት አሁንም በብዙዎች ልብ ውስጥ ተከድኖ አለ፡፡
‹‹በፍርድ ከኼደች በቅሎዬ፣ ያለ ፍርድ የኼደች ቆሎዬ›› እንዲሉ አበው እንዲህ በእናት ኢትዮጵያ ምድር ስለተረገጠው እውነት፣ ስለዘመመው ፍትሕ፣ ስለተዛነፈው ፍርድ የብዙዎች ቁጭት፣ ብሶትና ምሬት ከትናንትና ይልቅ ዛሬ ተባብሶ ይቀጥላል፡፡ እናም መንግሥት ሆይ ‹‹የፍትሕ ያለ፣ የእውነት ያለኽ፣ የፍርድ ያለኽ!›› የሚለው የሕዝብ፣ የኢትዮጵያ እናቶች እንባና ጩኸት ሰማይን እንዳናወጠ፣ ምድሪቱን እንዳጨቀየ ወደ ሰማይ መፍሰሱን ቀጥሏል፡፡ ግና መንግሥት አሁንም ድረስ በዚሁ ኹሉ በሕዝብ ብሶት፣ እዬዬና እሮሮ ውስጥ የሚሰማ ጆሮን፣ የሚያይ ዓይንን የታደለ አይመስልም፡፡
ግና የራሄሎች እንባ ወደ ጸባኦት አምላክ ጆሮ በደረሰ ጊዜ፣ ያ የፍርድ ጽዋ የሞላ ጊዜ ግን… ወየው ፍርድን ለሚያጣምሙ፣ ፍትሕን ለሚያዛቡ የእውነት ጠላቶች!! እነዚህ ልባቸውን እንደ ግብጻዊው ፈርኦን ልብ ፈጽመው ያደነደኑ፣ በኢትዮጵያ አምላክ ላይ ልባቸውን ያኮሩ፣ በሕዝባቸው ላይ የጭቆናን ቀንበር ያጠበቁ፣ ፍርድንና ፍትሕን ያዛቡ፣ መበለቲቱንና ባልቴቶችን ያስለቀሱ፣ የሽማግሌዎችንም ፊት ያላፈሩ ዓመፀኞች፣ የአምላክን ወሰን የሌለውን ትዕግሥቱንና ምሕረቱን እንደ ከንቱ ነገር የቆጠሩና ያጣጣሉ አምባገነኖች ኹሉ ራሳቸውን ለመቅሠፍት፣ ለውርደት ሞት የጠበቁ፣ አጥፊው የሞት መልአክ በቤታቸው ደጃፍ አድብቶ፣ ቆሞ ያለ መሆኑን ያውቁት ዘንድ በእርግጥም የግድ ይላቸዋል፡፡
ከትናንትና መሰሎቻቸው አሳዛኝ የውርደት ታሪክና የአምላክ እውነተኛ ፍርድና ፍትሕ ለመማር እምቢ ያሉ ኹሉ የውርድት፣ የጥፋት ታሪክን በራሳቸው ላይ ለመድገም ዛሬም በተጠንቀቅ ላይ እንዳሉ እየታዘብን ነው፡፡ ግና ቢሆንልንና ቢሰምርልን ምኞታችን፣ ጸሎታችን ግን አበው እንደሚመርቁት፡- ‹‹ዕድሜ ለንስሓ ዘመን ለፍሥሐ!›› እንዲሰጣቸው፣ እንዲያድላቸው ነው፣ ጥፋታቸውንና ክፋታቸው፣ ዓመፃቸውና በደላቸው ሌላውም እንዳይተርፍ ሲባል፡፡
ታላቁ መጽሐፍ፡- ‹‹እግዚአብሔር በቅዱስ ቦታው ለድሀ አደጎች አባት፣ ለባልቴቶች ዳኛ ነው፡፡ እግዚአብሔር እስረኞችን በኃይሉ ያወጣቸዋል፡፡›› እንዲል በግፍ ስለተጋዙባቸው፣ ፍትሕ ስለተነፈጋቸው፣ ፍርድ ስለተጓደለባቸው ልጆቻቸው ወደ ሰማይ የተረጨ የኢትዮጵያውያን ምሰኪን እናቶች እንባ እንዴት በከንቱ ይቀራል?! እርጅና ባደከመው ጉልበታቸው፣ ችግርና ጉስቁልና ከሰው መልክ ባወጣቸው እናቶች የተጎሳቆለ ፊት ላይ የፈሰሰው ያ እንባ፣ በልጆቻቸው ናፍቆትና ስስት ነፍሳቸው ዝላና ደክማ በነጋ ጠባ የቃሊትንና የቅሊንጦን ወኅኒ ቤቶች እንደ መቅደስ ሲሳለሙ የነበሩ የእነዚህ እናቶች ድካምና ልፋት፣ ሰቀቀንና ናፍቆት በአምላክ ፊት በእውነትም ይዘከራል፣ ይታሰባል፡፡
መቼም ለሚያስተዳድረው ሕዝብ የሚገባውን ፍቅርንና ክብርን ለመስጠት ዳገትን የመውጣት ያህል ለከበደው መንግሥታችን ይህን ደግመን ደጋግመን እንላለን፡፡ ፍቅር በሌለበት እውነት የለም፤ እውነትም በሌለበት ፍትሕ የለም፣ ፍትሕ በሌለበትም ምሕረት ተብሎ ነገርም አይታሰብም፡፡ እናም ገና በምድሪቱ ላይ ፍቅር እስክትነግሥ፣ ፍትሕ እንደ ወንዝ ውኃ ሞልቶ እስኪፈስ፣ ፍርድ ድል ነሥቶ እስኪወጣ፣ እውነት እስኪያሸንፍ፣ ዓመፀኞችና በደለኞች የእጃቸውን እስኪያገኙ ድረስ የምድራችን ግፉአን ጩኸት፣ እንባና ደም የፍርድ ያለኽ ማስተጋባቱን አያቆምም፡፡
ስለፍቅር፣ ስለእውነት፣ ስለፍትሕ የእናት ኢትዮጵያ ለቅሶና እንባዋ አሁንም በጉንጮቿ ላይ ነው፡፡ መጽሐፍ እንደሚልም፡- ‹‹የሰማይ አምላክ ስለችግረኞች ጩኸት አሁን እነሣለሁ፣ እገለጣለኹ፣ ፍርድንም አደርጋለኹ!›› እንዲል ኢትዮጵያ የአምላኳን ቅን ፍርድ፣ እውነተኛ ፍትሕ በምድሯ እስኪገለጥ ድረስ ዛሬም እጇን ዘርግታ በትዕግሥት፣ በጽናት ትጠብቃለች!! ‹‹ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሐ ሀበ እግዚአብሔር!›› እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት፡፡

Friday, July 10, 2015

Ethiopia politicizes courts to strangle dissent

July 10, 2015

The crackdown on Muslim activists is part of Addis Ababa’s crusade against independent voices and opposition leaders

The crackdown on Muslim
by Awol Allo | Al Jazeera
On July 6, Ethiopia’s Federal High Court convicted leaders of the Ethiopian Muslims protest movement on charges of terrorism and conspiracy to create an Islamic state in Ethiopia. The verdict — against two Muslim journalists, 10 activists and six members of the Ethiopian Muslims Arbitration Committee — came after three years of a politically motivated trial whose outcome was long ago determined. Sentencing is scheduled for Aug. 3.
The trial and the verdict against the Muslim leaders is a political spectacle designed to conceal the regime’s reindoctrination campaign and silence long-standing grievances of the Muslim population. The crackdown on Muslim activists is part of the ruling party’s larger crusade against journalists, bloggers, activists and opposition leaders and supporters.
A peaceful movement
The Ethiopian Muslims movement was organized around the community’s three core demands: ending the government’s continued control of the Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council, the official Islamic authority in Ethiopia; terminating the controversial reindoctrination of Ethiopian Muslims launched by the government in July 2011; and reopening the Awoliya College, the country’s only Muslim college. Authorities closed the institution in 2011, alleging it had become a breeding ground for radicals.
While the government has always controlled the council, it was Awoliya’s closure and the coercive reindoctrination campaign that triggered the confrontation. The government denies allegations of interference and control of religious institutions, but a leaked audio from the initial indoctrination sessions shows that it has invited preachers from Lebanon to introduce Al-Ahbash, a supposedly moderate sect of Sunni Islam, to Ethiopia.
Authorities arrested members of the Arbitration Committee in July 2012 after negotiations with the government failed, and they were charged with “intending to advance a political, religious or ideological cause” by force, signaling the impending criminalization of the peaceful movement.
Repressive political ends
Since the disputed 2005 elections and the mass arrests of opposition leaders and journalists, the use of court proceedings for repressive political ends has become one of the signature traits of the Ethiopian government. The primary purpose of these administrative acts disguised as criminal proceedings is the elimination of political opposition and critical voices. These trials function not to adjudicate legal disputes but to remove actors from the democratic sphere. The judicial machinery is set in motion not to determine guilt or innocence but to sustain and consolidate the government’s authoritarian stranglehold on its people.
In order to build a coherent narrative, the government often recasts genuine grievances as a national security threat and reconfigures activism as criminal offenses. For example, it accused the jailed Muslim leaders of working in tandem with foreign terrorist groups to destabilize Ethiopia and undo its economic progress. By dramatizing the impending danger and alleged links to regional militant groups such as Somalia’s Al-Shabab and Nigeria’s Boko Haram, the defendants’ prolonged trial was used to create an alternative reality manufactured by the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF).
The government presented various forms of evidence — including documents, audio and video of sermons and speeches by the defendants, witness testimonies and material obtained through surveillance. However, most of the evidence was presented in closed sessions, and the accused were not given adequate opportunities for cross-examination. The government has deployed stealth propaganda to incriminate the defendants. Since the committee members’ arrests, authorities have produced two fake documentaries intended to generate images and narratives of terrorism to scare Christian Ethiopians and Western observers, in flagrant violation of the presumption of defendants’ innocence until proven guilty.
The verdict of history
The accused Muslim leaders see their actions as a defense of the constitution and their trial as persecution — a dubious plot to delegitimize their peaceful protests against the injustices of the state. The government misrepresented their cause in a desperate attempt to suppress their aspiration and consolidate its control over religious institutions and doctrines.
As the judge read out the verdict, one of the committee members accused the judge of being complicit in the perversion of justice and reading a judgment “written by the security establishment,” according to defense lawyers. “We appear before this court not because we thought that this court is an institution of truth and justice that judges without fear of favor but to clarify the historical record,” another defendant said.
The trial has been an occasion for the defendants to mount their objection to the government’s oppressive narratives and expose its abuse of institutions of truth and justice. As part of their struggle over the historical record, the committee members petitioned Africa’s top human rights watchdog, the African Commission on Human and Peoples’ Rights, to intervene in the matter. Given the justice system’s lack of independence, the defendants are seeking to present their version of events before an independent international institution, contesting the allegations and images the government created in a trial in which it is both prosecutor and judge. In February 2015 the commission granted a provisional measure, asking Prime Minister Hailemariam Desalegn to undertake a full investigation into allegations of torture and other violations of due process rights.
The EPRDF is using counterterrorism as carte blanche to consolidate its authoritarian control over the country. Meanwhile, the United States, Ethiopia’s close ally in the global war on terrorism, has turned a blind eye to the misuse and abuse of its counterterrorism funding. President Barack Obama’s upcoming trip to Addis Ababa would be seen as yet another seal of approval for the regime’s repressive practices and the ruling party’s landslide victory in the recent elections. Ethiopia’s sudden and unexplained release of journalists and bloggers ahead of Obama’s visit later this month is a strategic move meant to assuage Washington’s concerns and to minimize the bad publicity around their continued incarceration.
Regardless of the outcome of these trials, history’s judgment will be different. In the verdict of history and the archives and repertoires of the oppressed, these individuals, like many who came before them, will be seen as victims of a grotesque system of justice.
Awol Allo is a fellow in human rights at the London School of Economics and Political Science.

ጋዜጠኛ ኤዶም፣ርዮትና ማህሌት-ከተፈቱ በሁዋላ ሀብታሙ ምናለ ታፍኖ ተወሰደ

July 10,2015
የጋዜጣው ስራ አስኪያጅ በአዲስ አበባ በደህነቶች ታፍኖ ተወሰደ
፣ከእነ ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ በተጨማሪ ሌሎችም የታሰሩ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ ሲፒጄ ጠየቀ
የጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ እና ከዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ሶስቱ ጋዜጠኞችና ሁለቱ ጦማሪያን መፈታት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሰፊ መነጋገሪአ በሆነበት በአሁኑ ወቅት እንደ ሌሎች ሁሉ እንካን ከጠባቡ እስር ቤት ተፈታችሁ ያለውን የቀዳሚ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሀብታሙ ምናለን የአገዛዙ ደህንነቶች ዛሬ ማምሻውን ከቤቱ አፍነው መውሰዳቸውን ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
Habtamu Minale
የሀብታሙ ምናለን ከቤቱ ዛሬ ዕኩለ ሌሊት ላይ ታፍኖ መወሰድ ይፋ ያደረገው ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ ማንነታቸው ባልታወቀ የደህነት አባላት ታፍኖ ት እንደወሰዱት እንደማያውቁና ከዚህ በፊት ለአንድ ሙሉ ቀን ጥብቅ ምርመራ ሲደረግበት ውሎ አሻራ ሰጥቶ መውጣቱን አስታውሷል።
የቀዳሚ ገጽ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ የነበረው ሀብታሙ ምናለ ዛሬ ማለዳ ከአራት ዓመት እስር በሁዋላ የአመክሮዋ ጊዜ አልፎ በአመክሮ ከእስር ወጣች የተባለችውን ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙን አስመልክቶ በፌስ ቡክ ገጹ የርዮትን መፈታት የፈጠረበትን ስሜት በመግለጹ አይዘነጋም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ መፈታትን አስመልክቶ ዓለም አቀፉ ጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ድርጅት ሲ.ፒ.ጄ ባወጣው መግለጫ አስቀድሞም መታሰር የሌለባት ርዮት በመፈታቱዋ ደስተኛ መሆኗንና የጤናዋን ጉዳይ ተጠይቃም የህመም ማስታገሻ እየወሰደች መሆኑን መግለጿን ጠቅሷል። መጀመሪያውኑ መታሰር እንደሌለባትና ከአራት ዓመት በላይ በእስር በልዩ ልዩ ክልከላዎች ጭምር መቆቷን፣ከእስር በሁዋላ የጡቷ ህመምን ጠቅሷል። ሁሉም ጋዜጠኞች ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቋል።
በአሁኑ ወቅት የእነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ውብሸት ታዬ፣ተመስገን ደሳለኝ፣ የሱፍ ጌታቸው እና የሌሎቹም ፖለቲካና የህሊና እስረኞች የፕ/ት ኦባማን የኢትዮጵአ ጉዞ ዕቅድ ተከትሎ ከእስር ይፈቱ ወይም አይፈቱ ታወቀ ነገር የለም በሚባልበት በዚህ ወቅት የቀዳሚ ገጽ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ የነበረው ሀብታሙ ምናለ በደህነቶች ታፍኖ መወሰድ አንዱን ፈቶ ሌላ ማሰር እንቅስቃሴ አስመስሎታል።
ትላንት ተፈቱትን ከዞን ዘጠኝ አባላት አምስቱ በስተቀር በቀሪዎቹ ላይ ክሱ ይቀጥላል ከመባል አልፎ የፖለቲካው ውሳኔ ምን እንደሆነ አልታወቀም። በትላንቱ ዘገባችን ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ፣ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ፣ ጦማሪ ዘላለም ክብረት፣ማህሌት ፋንታሁንና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ ዛሬ ማምሳውን በፍትሕ ሚኒስቴር ውሳኔ መፈታታቸው የታወቀ ሲሆን ከቤተሰብ መቀላቀላቸው ከአዲስ አበባ የወጡ መረጃዎች ገለጹ።የቀሩት በእስርና በስደት ያሉ አምስት ጦማሪያን ጉዳኢ በተጀመረው የክስ ሂደት ይቀጥላል ቢባልም ቁርጥ አለ ውሳኔ አለመሰጠቱ ታውቋል። በክሱ ላይ ብኢን ለመስጠት ከመጪው ቀጠሮ ሐምሌ 13 ቀን 2007 በፊት ይፈቱ ወይ እንደተባለው ክሱ ቀጥሎ ብይን ይሰጥ አልታወቀም።
ከአስሩ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች መካከል የክስ ሂደታቸው ይቀጥላል የተባለው የክሱ መዝገብ በስሟ የተከፈተውን ሶሊያና ሽመልስ ፣ አቤል ዋበላ ሱጌቦ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ሃይሉ እና አጥናፉ ብርሃኔ ጉዳይ መታየቱ እንደሚቀጥል ከፍርድ ቤቱ የተገኘ መረጃ ጠቅሰን መዘገባችን አይዘነጋም።

የሰሜን ግንባር እየታመሰ ነው!

July 10,2015
(ኢ.ኤም.ኤፍ) የግንቦት ሰባት አርበኛ ጦር በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ የጦር እንቅስቃሴ ማድረግ ከጀመረ በህላ፤ በሰሜን ግንባር የትርምስ ዜናዎች ደርሰውናል። ከዚህ በታች አርበኞች ግንቦት 7 ህዝብ ግንኙነት ያገኘውን መረጃ ዋና ዋናዎቹን እናቀርብላችኋለን።
የአርበኞች ግስጋሴ
የአርበኞች ግስጋሴ
የዳባት ፖሊሶች ታስረዋል
በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት ውስጥ የከረረ ተቃውሞ በፖሊስ አባላቱ በመነሳቱ በርካታ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶች መታሰራቸው ተሰማ፡፡
ቅዳሜ ዕለት ሰኔ 27 2007 ዓ.ም ዳባት ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የከረረ ተቃውሞ የተነሳ ሲሆን ተቃውሞውን ተከትሎ የበርካታ ፖሊስ አባላት እስር እና ከአካባቢው መሰወር ተከስቷል፡፡
በስብሰባው ላይ የተነሳው ተቃውሞ ዋነኛ ምክንያትና ሰበብ የፖሊስ ፅ/ቤቱ ዋና ኃላፊ ሆኖ የተሾመው ሰው ከትግራይ ክልል የመጣ የህወሓት አባል መሆኑ ነው፡፡
በስብሰባው ላይ ጠንካራ የተቃውሞ ድምፃቸውን ካሰሙት የዳባት ፖሊስ አባላት መካከል ካሳው ማሞ እና ሰጡ እጥናፉ የተባሉት ይገኙበታል፡፡ ካሳው ማሞ እና ሰጡ አጥናፉ “ተጠሪነታችን ለአማራ ህዝብ ሆኖ እያለ ለምን በህወሓት አባል እንመራለን? ተጠሪነታችን ለትግራይ ክልል ፖሊስ ሆኖ ከሆነ የተቋሙን ስም ቀይሩት፤ አለበለዚያ ከስራ አሰናብቱን… ዘረኝነት ይቁም…” በማለት ተናግረዋል፡፡
ከስብሰባው በኋላ ካሳው ማሞንና ሰጡ አጥናፉን ጨምሮ በስብሰባው ላይ የዘረኝነት አገዛዝ ተቃውሞ ድምፃቸውን ያሰሙ በርካታ የዳባት ፖሊስ አባላት እግረ ሙቅ እያጠለቁ ወደ ዘብጥያ ወርደዋል፡፡ ሦስት ፖሊሶች ደግሞ ድንገት ከአካባቢው የተሰወሩ ሲሆን በህወሓት ይታፈኑ ወይንም አምፀው ወደጫካ ይውጡ እስካሁን ምንም የታወቀ ነገር የለም፡
በህወሓቶች ቤት ውስጥ ታላቅ ሽብር ነግሷል
ከወልቃይቱ /ቃፍታ መሲን፣ ኮርጃሙስ፣ ማይ ሰገን፣ በዋል፣ ንኳል ሳግላ እና ማይ እምቧ…/ የአርበኞች ግንቦት 7 ወታደራዊ እርምጃ በኋላ ማለስልጣናቱ እንደተነፈሰ ፊኛ በመልፈስፈስ ኩምትርትር ጭምትርትር ብለዋል፡፡
የጦርነት ደመና ካጠላበት የኢትዮጵያ ጠቁር ሰማይ ስር በፍርሃት ተሸብበው የሚገኙት የህወሃት ባለስልጣናት እና ጀነራሎች የጨነቃቸውን ያክል ሰራዊቱን ወዲያ ወዲህ በማተራመስና በማንጓለል በድሃ ልጅ ዥዋዥዌ በመጫዎት ላይ ናቸው፡፡ ኤታማጆር ሹሙ “ጀነራል” ሳሞራ የኑስ ሰራዊቱ ኋላቀር እንደሆነ ህወሓቶች ባደረጉት ምስጢራዊ ስብሰባ ላይ አምኗል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ ከመጀመሩ ከወራት በፊት ግን አገሪቱ በወታደራዊ አቅሟ ከዓለም አገሮች ጋር ተወዳድራ ከዓለም በ46ኛ ከአፍሪካ ደግሞ በ4ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች ብለው ያን የተለመደ የፕሮፖካንዳ ቱልቱላቸውን ነፍተው ነበር፡፡
አሁን ኋላቀር በማለት ያጣጣሉትን ለእርድ የተዘጋጀ ሰራዊት በአራቱም የአገሪቱ ማዕዘናት እየበተኑት ይገኛሉ፡፡ የሰሞኑ ወደ ሰሜን የሚደረገው እንቅስቃሴ እንዳለ ሆኖ ትናንት ጠዋት ከአዋሳ በሀገረ ማርያም በኩል ወደ ሞያሌ እና ሌሎች ጠረፎች አካባቢ በርካታ ሜካናይዝድና እና እግረኛ ጦር እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ፌደራል ፖሊስ ተጭኖ ተልኳል፡፡
የኦነግ ጎሬላ ተዋጊዎች፡
የሀገረ ማርያም ዓይን እማኞች 26 አሮጌ ታንኮች በሚንገራገጭ ድምፃቸው አካባቢውን በማወክ እንደ ኤሊ እያዘገሙ ሲያልፉ መቁጠራቸውን ለዜና ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ ወደ ዚህ አካባቢ ጦር በገፍ እየተጫነ የሚገኘው የኦነግ ጎሬላ ተዋጊዎች ጥቃት ለመክፈት እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ የሚያረጋግጥ መረጃ ስለደረሳቸው መሆኑ ታውቋል፡፡
ከአፋር ነፃ አውጭዎቹ አርዱፍና ጋዲሌ ጋር በመቀናጀት ኦብነግ በአፋር ክልል ሰርጎ እንደገባ የሚያመላክት መረጃም ጭምር ስለደረሳቸው ወደ አፋር ክልልም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጦር እያጓጓዙ ይገኛሉ፡፡
ከዚህ መተራመስና መታመስ ጋር ተያይዞ ጦር እየመሩ በየማዕዘናቱ በሚላኩት ወታደራዊ አዛዦችና የበላይ አለቆቻቸው መካከል የተካረረ ፀብ እየተፈጠረ መሆኑን ከመከላከያ ምንጮቻችን የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል፡፡ የፀቡ መንስኤ እያንዳንዱ አዝማች “የተመደበልኝ የሰው ሃይል እንዲሁም ትጥቅና ስንቅ ያንሰኛል…” የሚል ሰበብ ማንሳቱ መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህም የሚያመላክተው የህወሓት ወታደራዊ አዛዦች ወኔያቸውን መሽናታቸውን ነው፡፡
አፈናው ቀጥሏል
በሌላ በኩል ደግሞ የህወሓት ዘረኛ ቡድን ሰራዊት ከማተራመሱ ጎን ለጎን ህዝብ በገፍ እያፈነ ወዳልታወቀ ቦታ ይዞ መሰወሩን በርትቶበታል፡፡ በተለይም አዲስ አበባ፣ ባህር ዳር ጎንደር… በርካታ ሰዎች በታጠቁ ኃይሎች እየታፈኑ ወዳልታወቀ ቦታ በመወሰድ ላይ ናቸው፡፡
የሰሜን ጎንደር ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ የነበረውና ጎንደር መምህራን ኮሌጅ ውስጥ የሚያስተምረው መምህር አለላቸው አታለለ ትናንት ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ የህወሓት የታጠቁ ቡድኖች ወደ መኖሪያ ቤቱ ገብተው አፍነው ወስደውታል፡፡ መምህሩ እስካሁን ድረስ የት እንዳለ አይታወቅም፡፡
በተጨማሪም የጎንደር እና አካባቢውን ገበሬዎች የህወሓት ካድሬዎች ዋጋውን መቶ በመቶ ቅድሚያ ካልከፈላችሁ በማለት ማዳበሪያ እንዳይወስዱ ከልክለዋቸዋል፡፡ ገበሬው የባሰውኑ በህወሃት ልቡ ሻክሯል…

Wednesday, July 8, 2015

Hacking Team & The Woyane regime email exchange: EXPOSED!

July 8, 2015

Leaked internal emails show Hacking Team dropped support for Ethiopia after CitizenLab and Human Rights Watch reports.

Hacking Team internal email exchange:
Dear all,
I’m receiving ongoing pressure from the Ethiopian client to resume the relationship that came to an halt after the CitizenLab/HRW reports.
I think that we all agree that we should interrupt any business with them due to the recurring media exposure and resulting technical issues.
Their reckless and clumsy usage of our solution caused us enough damage. What’s worst is that we can be sure that if we allow them to continue, more will come.
I would like to have your opinion on this and eventually on how to communicate this decision both with the customer and the media, if appropriate.
Thanks,
Daniele
Hacking Team internal email exchange:
Hello David,
The meeting with Biniam is over.
Despite the way we are used to know him, let me say this time was very collaborative.
He understood the consequences of the actual situation and why we had to react the way we did.
We explained him that we are facing issues with all our customers.
With reference to its specific case, we agreed the following:
– Wait of the input from our government
– If feedback is positive, he “promised” to comply to any security features/requests we may require.
– We’ll quote some additional training and certifications related to the security measures and practices that have to be followed in order to reduce the future risk of new issues.
Massimiliano
The Woyane agent Biniam Tewolde’s email message to the Hacking Team:
Dear HT,
It has been almost two months since we lost our control of more than 30 agents.
These agents are very critical for our operation. So far we could not restore control of those agents.
Before some days, Danielle has told my colleague that restoration is not possible.
We once again ask HT to do all their best to restore the control of agents.
Besides we want all the information about the hosting company, and contact persons of the company.
Waiting.

Tuesday, July 7, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የሰነዘረውን ድንገተኛ ማጥቃት ተከትሎ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብን አስፈቅደን ከሻብያ ጋር እንዋጋለን” አሉ

July 7, 2015
አርበኞች ግንቦት 7 በተለያዩ ግንባሮች በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት ተከትሎ ከወያኔ ጎራ የተምታቱ ዜናዎች እየተደመጡ ነው።Ethiopian PM Hailemariam Desalegn on Al Jazeera
ቀደም ሲል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት “ምንም ነገር የለም” ብለው ለማድበስበስ የሞከሩት የወያኔ ሹማምንትና ካድሬዎች ዜናው በኢሳት ቴሌቪዥን፣ ሬድዮ፣ በተለያዩ ድረ-ገጾች እና በዋንኛነት ደግሞ በማህበራዊ መገናኛ ገጾች በስፋት በመዘገቡ “ምንም ነገር የለም” ከሚለው ወደ ተምታታ ዜና ማሰራጨት ተሸጋግረዋል።
የወያኔዎቹ ቃል-አቀባይ ጌታቸው ረዳ በሚሚ ስብሃቱ ኤፍ ኤም ራድዮ ላይ ቀርቦ “በአካባቢው በመሬት የተነሳ መጠነኛ ግጭት ነበር” በማለት ሁኔታውን ከገለጸ በኋላ ወድያውም “በሻብያ ላይ የማያዳግም ቅጣት” ሊሰነዝሩ እንደሚችሉ ተናግሯል።
አይጋ ፎረም የሚባለውና በአፍቃሪ ወያኔነቱ የሚታወቀው ድረገጽ ደግሞ የመከላከያ ሰራዊቱ በሻብያ ተላኩ ያላቸውን ታጣቂዎች መማረኩን ዘግቧል።
አነጋጋሪ የሆነውና ምናልባትም አብዛኞችን ፈገግ ያደረገው ዜና ደግሞ ኣሻንጉሊቱ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለአሻንጉሊቱ የተወካዮች ምክር ቤት ያደረጉት ንግግር ነው፣ “ህዝብን አስፈቅደን ከሻብያ ጋር ጦርነት እንገጥማለን” ነበር ያሉት ኃይለማርያም ደሳለኝ።
የወያኔ ሹማምንት ጥቃት እየሰነዘረባቸው ያለውን “አርበኞች ግንቦት 7ን” በስም ለመጥቀስ እጅግ የፈሩ ይመስላሉ።
አርበኞች ግንቦት 7ን በስም መጥቀስ ለምን ፈሩ? ብሎ ለሚጠይቅ መልሱ ቀላል ነው።
ህዝብ የአርበኞች ግንቦት 7 የነጻነት ታጋዮች ከአብራኩ የወጡ የቁርጥ ቀን ልጆቹ እንደሆኑ ያውቃል። ስለዚህም ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ጦርነት ልንገጥም ነው ቢሉ ማንም እንደማይተባበራቸው ይረዳሉ። ያላቸው እድል “ሻብያ” እያሉ መለፈፍ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ይገነዘባል ይሁንና የወያኔ አስከፊ ዘረኛ ስርዓት እያደረሰበት ካለው የመረረ ጭቆና ጋር በማነጻጸር ይመስላል አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የሰነዘረውን ጥቃት በደስታ ነው የተቀበለው።
በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ኢሳት ቴሌቭዥን በመደወል ደስታቸውን ሲገልጹና ለአርበኞቹም መልካሙን ሁሉ ሲመኙ ተደምጠዋል።

Sunday, July 5, 2015

UN demands release of British activist jailed in Ethiopia amid torture fears – The Guardian

July 5, 2015
The Foreign Office has pushed for consular access to Andargachew Tsige with no tangible results, since the British citizen was abducted in Ethiopia a year ago
The UN has demanded the immediate release of a Briton held on death row in Ethiopia for more than a year, an intervention that campaigners say exposes Britain’s poor diplomacy towards the case.
Experts from the UN Human Rights Council have advised Ethiopia to pay Andargachew Tsige “adequate compensation” before sending him home to London, an abrupt hardening of its position on the case at a time when Britain pursues a softly, softly approach with no tangible reward.
Yemi Hailemariam campaigns in London to demand the immediate release of her partner, British citizen Andargachew Tsege, who has been held in Ethiopia since June 2014. Photograph: Alamy
Internal Foreign Office emails, disclosed for the first time, reveal that even before Tsige was kidnapped and jailed in an unknown location in June 2014, British officials had voiced fears at “the real risk of torture if [Tsige is] returned to Ethiopia”, along with “fair trial concerns”.
An eight-page judgment from the UNHRC’s working group on arbitrary detention handed to Ethiopia suggests such fears have been realised, saying that there is “reliable evidence on a possible situation of physical abuse and mistreatment which could amount to cruel, inhuman and degrading treatment.”
Tsige, 60, a father of three from London, and known to friends as Andy, was arrested in Yemen’s main airport while in transit and forcibly removed to the Ethiopian capital, Addis Ababa.
He is prominent in Ethiopian politics, having been leader of opposition party Ginbot 7, which has called for democracy, free elections and civil rights. The government has accused him of being a terrorist and in 2009 he was tried in his absence and sentenced to death.
Foreign secretary Philip Hammond has refused to demand his urgent release, preferring to push for consular access, a request rejected by Ethiopia. Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, who lives in London with their children, has spoken to him just once by telephone since his abduction.
Advertisement
Another internal government email from the UK ambassador to Ethiopia to Laurence Robertson MP, who heads the all-party parliamentary group on Ethiopia, describes the Ethiopians as “obdurate”.
Hammond recently attempted to harden up the UK’s position on Tsige, calling for rapid progress in the case, but campaigners say this remains significantly short of what is required. Another recent Foreign Office statement made no mention of Tsige, but welcomed the “generally peaceful environment” of the recent Ethiopian elections, which saw the government locking up political opponents and journalists.
Maya Foa, head of the death penalty team at legal charity Reprieve, said: “Despite the injustices that have been – and continue to be – committed against this British national, the foreign secretary refuses to ask for Andy’s release and his return back home to his family in Britain.
“The UN is right to be taking action and demanding Andy’s immediate release from his unlawful detention. The UK’s refusal to do the same is an unacceptable abdication of responsibility to one of its citizens.”
Kevin Laue of the human rights organisation Redress, which helps torture survivors, said: “The UK government should be outraged by this behaviour and should be responding in the strongest possible terms.” A Foreign Office spokesman said: “The foreign secretary has raised this case with the Ethiopian foreign minister on 13 separate occasions, most recently on 29 April 2015. The minister for Africa raised this again on 11 June. We will continue to lobby at all levels, conveying our concern over Andargachew Tsige being detained without regular consular visits and access to a lawyer.”

Saturday, July 4, 2015

አይቀሬዉ የድል ፊሽካ ተነፋ!! አርበኞች ግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል በወያኔ ሰራዊት የኃይል ጥቃት ሰነዘረ

July 4,2015

 ሀሙስ ዕለት ሰኔ 25 2007 ዓ.ም የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሰራዊት በትግራይ ክልል ቀፍታ መሲል፣ ሆርጃሞ እና ማይሰገል ላይ ህወሓት ከሚቆጣጠረው የ24ኛ ክፍለ ጦር፣ ፌደራል ፖሊስና ልዩ ኃይል ጋር ባደረገው ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ከባድ ጦርት ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ፡፡

የአርበኞች ግንቦት 7 አርበኛ ተጋዮች በትግራይ ቀፍታ መሲልና ሆርጃሞ ላይ መሽጎ ያገኙትን ከሶስት ክፍሎች ማለትም ከ24ኛ ክፍለ ጦር፣ ከፌደራል ፖሊስና ከልዩ ኃይል የተውጣጣና እስከ አፍንጫው የታጣቀ ቁጥር ስፍር የሌለው ጦር ከቀኑ ሰባት ሰዓት እስከ አስር ሰዓት ለተከታታይ ሦስት ሰዓታት በጥይት ቆልተውታል፡፡

በተጨማሪም እዚያው ትግራይ ውስጥ ማይሰገል በተባለው ቦታ ምሽት ከአስራ ሁለት ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት በተደረገው ፍልሚያ በጠላት ጦር ሰራዊት ላይ ከፍተኛ እልቂት ደርሷል፡፡ 

ትግራይ ውስጥ በሚገኙ በሦስቱ ቦታዎች በተደረው አራት ሰዓታትን የፈጀ መራራ ውጊያ ከተለያዩ ሶስት ክፍሎች የተደራጀው የጠላት ጦር በአርበኞች ግንቦት ሰባት የነፃነት ፋኖዎች ፈርጣማ ክንድ ክፉኛ ተደቁሶ የተበታተነ ሲሆን በትንሹ ከ50 በላይ ወታደሮች ሲሞቱ ከ60 በላይ ደግሞ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል፡፡ ህወሓት በሚቆጣጠረው ሰራዊት ላይ የደረሰው ጉዳት አሁን ገና በመጣራት ላይ የሚገኝ ሲሆን ውሎ አድሮ ትክክለኛው መረጃ ሲገኝ የሞቱትና የቆሰሉት ወታደሮቹ ቁጥር አሁን ከተገለፀው ከሁለትና ሦስት እጥፍ ሊያሻቅብ እንደሚችል ይገመታል፡፡ 


ስለዚህም በአሁኑ ሰዓት አርበኞች ግንቦት 7 ጦርነት አውጇል በሚል ከሁመራ-ዳንሻ፣ ከሁመራ-ሽሬ እና እንዲሁም በተጨማሪ ከሁመራ-ጎንደር የሚገኙት አውራ ጎዳናዎች ጥርቅም ብለው በጦር ሰራዊት ተዘግተው ምንም አይነት የመኪና እንቅስቃሴ የለም፡፡


እስከ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ በጉጉት ሲጠብቀው የኖረው ህወሓትን በጠብመንጃ የማስወገዱ ጦርነት ፍልሚያ አብሳሪ የሆነው ፊሽካ በአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ እነሆ ተነፍቷል፡፡ በመሆኑም ነፃነት ፈላጊ የሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ/ወጣት ሁሉ በያለበት ትጥቅ ያለው ትጥቁን አንስቶ፣ ድንጋይና ዱላ የጨበጠም በእጁ በሚገኝ ማናቸውም መሳሪያ የዘረኛውን አገዛዝ የህወሓትን ቡድን ራስ ራሱን በመቀጥቀጥ በረሃ ወርደው በመፋለም ውድ ህይወታቸውን እየከፈሉ ከሚገኙት ልጆቹ፣ ወንድሞቹ እና እህቶቹ የሆኑ አርበኛ ታጋዮች ጎን አንዲሰለፍ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

Friday, July 3, 2015

በህወሓት አገዛዝ እየተሰቃዩ ላሉ ወገኖቻችን ደህንነት የሚደረገው ዓለም አቀፍ ጫና ይቀጥል!

July 3, 2015
def-thumbከሣምንት በፊት የብሪታኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን የሚመለከት አንድ መግለጫ አውጥቷል። በዚህ መግለጫው፣ አንዳርጋቸው ጽጌ ለአንድ ዓመት ሙሉ መሠረታዊ የሆኑ የታሳሪዎች መብት እንኳን ተነፍጎት ባልታወቀ እስር ቤት የሚገኝ መሆኑ እና በእንግሊዝ ባለሥልጣናትና በቤተሰቦቻቸው እንዲጠየቅ፣ ቋሚ የቆንስላና የህግ ምክር እንዲያገኝ በተደጋጋሚ የቀረበው ጥያቄ በወያኔ አገዛዝ ውድቅ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል ያለው መልካም ግንኙነት የሚያሻክር መሆኑ ከወትሮው ጠንከር ባሉ ቃላት ገልጿል። አዲስ አበባ የሚገኘው የብሪታኒያ አምባሳደርም እንደዚሁ ከተለመደው ዲፕሎማሲያዊ ለስላሳነት ወጣ ያለ ያለ መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ለሚታተመው ሪፓርተር ጋዜጣ ሰጥቷል። እነዚህ የሰሞኑ የእንግሊዝ መንግሥት መግለጫዎች በቀና የሚታዩ ቢሆንም የብሪታኒያ መንግሥት ማድረግ ይገባው ከነበረው እና ማድረግ ከሚችለው አንፃር ሲታይ ብዙ ይቀረዋል። የአውሮፓ ኅብረት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በተደጋጋሚ አንስቷል። የተባበሩት መንግሥታትም የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝ ጉዳይ ምርመራ እንዲደረግበት እንቅስቃሴ ጀምሯል። ከላይ የተዘረዘሩት ኩነቶች፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለሟቋረጥ የሚያደርጉት ውትወታ ውጤት እያመጣ መሆኑ ያሳያል። ይህ ጥረት ለወደፊቱም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።
በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አስልጥኖ አሰማርቷችኋል” ተብለው እንደተለመደው በሀሰት የተከሰሱ ወገኖቻችን “አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ መከላከያ ምስክር እንዲሆኑን ይታዘዝልን“ ብለው ሲጠይቁ ዳኛ ተብየው “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ ሰውን በመከላከያ ምስክርነት ማቅረብ ይከብዳል” ብሎ ሲናገር ተደምጧል። አቶ አንዳርጋቸው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ ብይን ሊሰጥበት ቀጠሮ ተይዟል።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የነፃነት አርበኛው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የእስር አያያዝ ሁኔታ ዓለም ዓቀፍ የዲፕሎማሲ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ወቅት በህወሓት አገዛዝ በተሾመ ዳኛ “የት እንደሚገኙ የማይታወቁ” መባሉ አሳሳቢ ጉዳይ አድርጎ ይመለከተዋል። አርበኞች ግንቦት 7፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የተከሳሾች፣ የአቃቤ ህጉና የዳኛው ምልልስ ለተባበሩት መንግሥታት፣ ለአውሮፓ ኅብረትና ለእንግሊዝ መንግሥት እንዲደርስ እንዲያደርጉም ያሳስባል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ብቻ ሳይሆን በህወሓት እስርቤቶችና ከእስር ቤቶች ውጭ ባልታውቁ ቦታዎች ታስረው እየተሰቃዩ የሚገኙ ወገኖቻችን ሁሉ እና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃ የሚወጣው፣ ኢትዮጵያዊያን በሚያደርጉት ሁለገብ ትግል ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል። ስለሆነም ራሳችንን፣ ወገኖቻችንና አገራችን ነፃ ለማውጣት የምናደርገው ትግል ማጠናከር ግዴታችን ነው። እኛ ራሳችን እንጂ ማንም ነፃነታችንን አያጎናጽፈልንም።
ይህ እንዳለ ሆኖ ግን የህወሓትን እኩይ ተግባራት በዓለም አደባባዮች ማጋለጥ፤ የህወሓት አገዛዝን ወዳጅ ማሳጣት እና በእስር ላይ የሚገኙ ወገኖቻችንን ደህነት የሚያሻሽሉ ተጽዕኖዎችን መፍጠር እጅግ አስፈላጊ ተግባር በመሆኑ፣ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፣ በህወሓት እጅ ለወደቁ ወገኖቻችን ድጋፍ የሚያሰሙትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Thursday, July 2, 2015

Ethiopia: Respect court rulings and release opposition members

July2, 2015
Amnesty International
Semayawi party members have been rearrested repeatedly
Woyneshet Molla (left), Ermias Tsegaye, Daniel Tesfaye(right) and Betelehem Akalework( not in the picture) have been rearrested repeatedly on the same charges.
Ethiopian authorities must stop harassing two men and two women linked to the opposition Semayawi (Blue) Party, and immediately release them from detention, Amnesty International said as they were expected to face fresh charges in court today in the capital Addis Ababa.
“On five separate occasions over the course of the last 10 days, three different courts have ordered the police to release these four people,” said Michelle Kagari, Deputy Regional Director for East Africa, the Horn and Great Lakes. “Their continued detention is blatantly unlawful and in clear violation of their rights to liberty and a fair trial.”
Woyneshet Molla, Ermias Tsegaye, Daniel Tesfaye and Betelehem Akalework were arrested in April this year and charged with inciting violence during a rally in the capital. They remained in custody awaiting trial. The four were convicted at the Federal First Instance Criminal Court at Kirkos on 22 June 2015 and sentenced to two months in prison. The judge however ordered their immediate release on the basis that they had already served their time, but the police ignored court orders and returned them to Kality and Kilinto prisons.
They were released the following morning, but police and security officials immediately re-arrested the four without a warrant and brought them to Kasanchiz 6th police station. On 25 June, they were presented on the same charges before the same judge that had ordered their release. He dismissed the case and again ordered their immediate release but the police did not comply and instead unsuccessfully sought to have another judge in the same court accept the case.
The following day the police brought the four before a new judge at Keraa Federal First Instance Court, on new charges of threatening witnesses to their original case. In a hearing on 30 June the court accepted the case, but ordered that the accused be released on bail pending the case’s resumption today. Again, the police disregarded court orders and the four remain in custody.
Separately, the Federal High Court Lideta Branch on 29 June accepted to hear the public prosecutor’s appeal against the original verdict, but refused their request to keep the four in custody. The appeal has been adjourned until 3 July.
“This charade must come to a halt. These four men and women have already served their jail term. This blatant disregard for judicial orders, and attempts to press fresh charges amounts to persecution, and takes harassment and intimidation to new heights,” said Michelle Kagari.
“By keeping Woyneshet Molla, Ermias Tsegaye, Daniel Tesfaye and Betelehem Akalework in detention, the Ethiopian authorities are undermining the credibility and authority of the court process and eroding the rule of law. They must stop harassing opposition members and ensure that the right to a fair trial is upheld.”