Wednesday, September 30, 2015

የትጥቅ ትግልና ግራ የሚያጋባ አስተያየት – ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

September 30,2015
getachew
በኢትዮጵያ ትከሻ ላይ የተቆለፈውን ቀምበር ለማላቀቅ ቍልፉ የትጥቅ ትግል መሆኑ በተነሣ ቍጥር ከአንዳንድ ሰዎች የሚሰጠው አስተያየት ግራ የሚያገባ ነው። ገዢዎቹና ደጋፊዎቻቸው ቢቃወሙ ይገባኛል። የሚሰጡት አስተያየት ግን ሕፃንን ሳይቀር የሚያሥቅ ነው። “ጦርነት በቃን” ይላሉ። “አትንኩን” ማለታቸውን የማናውቅ ይመስላቸዋል። ጦርነት ካላስፈለገ፥ ለምን ከንጉሣዊው አስተዳደር ጋር ተዋጉ? ለምን ከደርግ ጋር ተዋጉ? ጨቋኝ ገዢ የት አገር ነው በሌላ መንገድ ሥልጣን ለሕዝብ ሲለቅ የታየው? የምሥራቁ ዓለም ጨቋኞች የወደቁት በሕዝብ ዐመፅ ነው ማለት፥ የምዕራቡን ዓለም ከባድ እጅ ሚና መርሳት ይሆናል።
የኛዎቹ ጦርነት ከመረራቸው፥ ሕዝብን ወደጦርነት የሚመራ በደል አይሥሩበት። ምን ጊዜም ቢሆን የትጥቅ ትግል የመጨረሻው አማራጭ ነው። የትጥቅ ትግል የሚያደርሰው ጉዳት በአንዱ ወገን ላይ ብቻ አይደለም። መሣሪያ የሚያነሣ መሣሪያ ማንሣት የሚያመጣበትን ጉዳት ሳያውቅ አይነሣም። ሰው ሆኖ እንደከብት መገዛት ያልቻለ ሰው በቃኝ ሲል፥ ክብሩን በመጠበቁ ከተቀመጡበት ተነሥቶ “ነወር” የሚባል እንጂ፥ በባርነት ጥላ ሥር ተቀምጦ የሚተች አይደለም። “ጦርነት መርሮናል” የሚለውን ምክር መገዛት ለመረረው አይመክሩም።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ግራ አጋቢ አስተያየት “ጦርነትስ አስፈላጊ ነው፥ ግን . . .” የሚለው ነው። ይህ አስተያየት በቅን አሳብ፥ የተሰጠ ሊሆን ይችላል። ግን አዛኝ መስሎ፥ ቀምበረኛውን ለመደገፍ የተሰጠ አስተያየት አለመሆኑ በምን ይታወቃል? እውነተኛ አሳቢና ሠጊ ሰው አስተያየቱን የሚሰጠው ሲጠየቅ፥ ካልተጠየቀም በግሉ ትጥቅ ያነሡትን ፈልጎ በጨዋ ደምብ መንገር ነው። ሳይጠየቁ ተነሥቶ በይፋ ምክር መስጠት ግን ሰሚው ሕዝብ ትግሉን እንዳይደግፍ መገፋፋት ነው። የትጥቅ ትግል ከታመነበት እንዲፋፋም የማይፈለግበት ምክንያት ምንድን ነው?
ትጥቅ ትግል የራስን ሕይወት ለወገን ነፃነት መሠዋት ማድረግ ነው። ሌላ ዓለማ የሌለው ሰው መሣሪያ ሲያነሣ፥ እንዴት ይኸንን የሚሰነዘርበትንና የሚሰነዘርለትን ምክር ሳያስብበት ራሱን ለመሥዋዕትነት ያቀርባል? የሚካኼደው የትጥቅ ትግል የሚያዋጣ የመሰለው እርዳታውን ያቅርብ፤ የማያዋጣ የመሰለው ለምንድን ነው የሚቃወመው? ተቃውሞው ማንን ለመጥቀም ነው? ለታጋዮቹ አስቦ ከሆነ፥ ከባለቤት ያወቀ ቡዳ ነው። “የኔን ያህል የማሰብ ችሎታ የላችሁም” ማለት ነው። እንዴት ነው ለታጋዮቹ ያልተገለጠ ሥጋት ለምክር ሰጪዎቹ የተገለጠው?

አንዳንዱ ደግሞ፥ “ይኸው እንታገላለን ሲሉ ዓመታት አሳለፉ፥ ግን አንዳች ውጤት አላሳዩም” ይላል፤ ውጤት እንዲያሳዩ የቀጠራቸውና ካልሆነላቸው የሚያሰናብታቸው ሹም ይመስል። አርፎ መቀመጥ ስንት ውጤት አሳየ? ሌሎችን ሙከራዎችም “አንዳች ውጤት አላሳዩም” ብለን እንንቀፋቸዋ!ውይስ ውጤት አሳይተዋል?
“በመካሄድ ላይ ያለው የትጥቅ ትግል ኢትዮጵያን የሚጎዳ ነው” ከተባለ፥ እርግጥ ሊታሰብበት ይገባል። ግን አሳሳቢው ምክንያት ሊቀበሉት በሚገባ መልኩ አልተሰጠንም። ይህ ትግል የሚያመጣው ጉዳት ከተሸከምነው ቀምበር ይበልጥ ሊከብድ እንደሚችል አሳዩን።
የወያኔ ቀምበር መሰበር አለበት የምንል ሁሉ በመሰለንና በተቻለን መንገድ እንታገል። ካልተቻለን፥ ካልመሰለን፥ አርፈን እንቀመጥ፤ ታጋዮችን አለማደናቀፍ፥ እንደ ትግል እንዲቈጠርልን።

Tuesday, September 29, 2015

አርባ‬ ምንጭ የነበረው የአሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን አካባቢውን ለቆ እየወጣ ነው

September 29,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)


‪አርባ‬ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡ ‪‎ህወሓት‬ በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡
አርባ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡

በአርባ ምንጭ እና አካባቢው ሲንቀሳቀስ እና ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ከዚያ እያስነሳ ወደ ሚፈልገው አቅጣጫ ለጥቃት ሲያሰማራ ለረጅም ጊዜ የቆየው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን ከአገሪቱ መንግስት በተሰጠው መመሪያ የቆይታ ጊዜ ኮንትራቱን አቋርጦ ሀሙስ ዕለት አካባቢውን ለቆ መውጣት መጀመሩን በቦታው የሚገኙ ምንጮቻችን ገልፅዋል፡፡ ድሮን የታጠቀው የአሜሪካ የመከላከያ ኃይል ቡድን የአርባ ምንጭን መሬት ለቆ መንቀሳቀስ የጀመረበት ምክንያት ለጊዜው በውል ተለይቶ ባይታወቅም መንግስት ነኝ በሚለው በህወሓት አገዛዝ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል አለመግባባት ተከስቶ ቅራኔ ሳይፈጠር እንዳልቀረ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ ከአሁን በፊት ከአርባ ምንጭ በተጨማሪ በድሬ ደዋ ላይ ተቀምጦ በሰው አልባ አውሮፕላኖች በሶማሊያ በሚንቀሳቀሱ የአልሸባብ ተዋጊዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት መክፈቱ ይታወቃል፡፡ ህወሓት በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ገና ከሽፍትነቱ ጀምሮ በህዝብ ላይ ሴራ በማቀነባበር የሚታወቀው ህወሓት ራሱ ግንብቶ ለግለሰቦች ያከራየውን የንግድ ማዕከል ነው በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ድርጊቱን እንደፈፀሙት በማስመሰል ከህዝብ ለመነጠል ሲል ነው በተቀነባበረ ሂደት በእሳት የለቀቀው ፡፡

በህወሓት የተቀነባበረ ሴራ የተከሰተው ከባድ የእሳት አደጋ የደረሰው መስከረም 14 ቀን 2008 ዓ.ም ሲሆን ከ40 በላይ ሱቆች ተበልተው ወደ አመድነት ተቀይረዋል፤ በሚሊዮኖች ገንዘብ የሚገመት ንብረትም ወድሟል፡፡ ህወሓት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ጊዜያት በተከሰቱት የቦንብ ፍንዳታዎች ትግራይ ሆቴልን ጨምሮ እጁ እንዳለበት የአሜሪካ ኤምባሲ ለስቴት ዲፓርትመንት የላከውን ደብዳቤ በዋቢነት ጠቅሶ ዊክሊክስ የተባለው ድረ-ገፅ ማጋለጡ የሚታውስ ነው፡፡

Saturday, September 26, 2015

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia

September 26, 2015

logo-timeret
United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy

Launching an Effective Resistance against TPLF Tyranny – a tyranny which is the Real Driver of Instability and Civil Strife in Ethiopia, (pdf)

Ethiopia is one of the oldest nation-states in the world. Both written and oral history and recent archeological discoveries, despite regional rivalries, suggest the historical continuity of the nation. It was a Monarchy until 1974. From 1974 to 1991 the country was declared to be ‘Peoples Democratic Republic’ by the military junta, Derg, and went through a traumatic experience. Tigrai Peoples Liberation Front (TPLF), a guerrilla force from a minority ethnic group that led the rebellion against the military junta and captured the institutions of the State, has been in power for the past 24 years. The country is ruled as a one-party state under a façade of multi-party system since 1991.
The state is characterized by an intensifying political repression, rampant economic corruption, denial of basic human and political rights and repeated sham elections. The top brass of the army and security organs of the state, including key diplomatic positions, are effectively mono-ethnic despite the claim of the regime to stand for the equality of all ethnic groups. The people have completely lost confidence in the government after the regime shamelessly declared itself to have won 100% of the parliamentary seats in the 2015 election. Ethiopians, with no other choice available to them for democratic transition, have now risen up in arms. And this is a credible threat of force to the regime. History has time and again proven that no government that denies freedom, justice and democracy to its people will not survive their wrath.
Against this background, Ethiopian democratic forces, reflecting the broad diversity of the Ethiopian society, have recently formed the United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED) as an umbrella organization. UMSED is committed to coordinate the people’s struggle for effective resistance against TPLF’s tyranny and to ensure the transition to true democracy and stable political order in Ethiopia. No one relishes the idea of armed conflict; but, there are times when armed self-defense becomes the only choice to resist the unbearable violence by minority against majorities and to bring about an enduring peace and stability in a society.
Ethiopians have given up on elections as they have become meaningless rituals:There have been five national elections under the TPLF. The first election in 1995 resulted in 3 opposition members being elected to the parliament that has a total of 548 MPs. In the second election of 2000, the number for the opposition members rose to 27. In the 2005 general election, which was monitored by the Carter Center, European Union and other observers, Ethiopians turned out in record numbers and voted for the opposition, mainly CUD and UEDF. The results were rigged; and the election was blatantly stolen. Furthermore, many unarmed and defenseless peaceful protesters demanding the respect for the vote of the people were indiscriminately gunned down in a broad daylight. Leaders of opposition political parties, civic societies, journalists and dignified and well-meaning Ethiopian citizens were jailed for two years. Members of the fact finding commission appointed by the government itself published the evidence that the government has cold-bloodedly massacred 197 Ethiopians on this day of infamy. Today, these fact finders are themselves in exile fleeing for their lives. Only one opposition member was able to win a seat in the parliament during the 2010 fourth national election. In the most recent election of May 2015, in which the regime claimed 100% landslide victory of all parliamentary seats, no credible outside/international observers, excepting those from the corrupt African Union, were allowed to monitor the election.
The Ethiopian government owns all land in the country, including most residential and commercial real estate in towns and cities like all other communist totalitarian regimes in the world. The industrial and service sector of the economy is also heavily controlled by Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFFORT), an endowed conglomerate parastatal serving as a front for the ruling TPLF party. Until recently it was managed by the wife of the late Prime Minister. Both were members of the TPLF/EPRDF politbureau and the legislative assembly, making their work similar to the work of the late Romanian dictators, Nicolae Ceaușescu and his wife Elena Ceaușescu. The total grip on land and the economy is a source of much power to the regime and the accompanying oppression of the people in a country where eighty five percent of the population is engaged in farming and most city dwellers rely on the government for employment and housing. All land in the country was declared government property by the old communist military regime and the current regime has continued the practice. The monopolization of land by the TPLF and its surrogate administrators has been the source of wealth for some, but continued to stifle the production of food as in the communist era. Thanks to this land policy, today lives particularly that of children and cattle in the Afar, Amara, Gambella, Somali and Southern regions of the country are perishing due to a single season rainfall failure.
Ethiopians are tired of their voices being totally muffled: Independent media is not tolerated. The International Federation of Journalists has declared the regime to be one of the worst offenders of press freedom. Television, Internet, and major print media is owned and operated by the government. The state is the only Internet Service Provider and uses Chinese, Italian and British Internet hacking and intercepting technology vendors to spy, trap and intimidate its critics and opponents. The regime also spends precious resources on signal jamming technology to stop the free flow of information from the outside. Foreign based and independently operated radio and TV broadcasts by the Ethiopian Diaspora are jammed on regular basis as are broadcasts in Ethiopian languages by Voice of America and Deutsche Welle Radio.
Ethiopians can no longer tolerate an entrenched ethnic minority rule: The TPLF, the dominant party in the coalition known as Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), controls all aspects of life in the country, similar to apartheid South Africa, by installing its ethnic rulers as heads of major institutions across the entire state apparatus. Ethiopians and international observers including those who bend backwards to “apologize” for the regime know very well that ethnic Tigrayans control the army, security services, telecoms , foreign affairs, and other nerve centers of the Ethiopian state machinery. The TPLF party pits different ethnic and religious groups against one another simply to perpetuate its minority rule and monopoly on resources. The regime has no respect for religious freedom. It has created chaos in both the Ethiopia Orthodox Tewahido Church and the Muslim mosques by interfering in the administration of their purely religious institutions through its political cadres. It has similar surrogates in Pentecostal Churches. Religious leaders who resist this interference are exiled (as the Orthodox Christian leaders) and imprisoned (as the Muslim community leaders). Ethnic minority domination has become a source of stress on the harmony of the people that is essential for peaceful coexistence in a diverse mutli-ethnic and multi-religious country like Ethiopia.
Ethiopians have said enough to the regime’s oppression with impunity: In the last twenty four years, the people have been appealing to the regime to respect the fundamental political and civil liberties of the citizenry. Peaceful protests are disallowed. Countless petitions and protest demonstrations that were held in the major capitals of the world have ended in deaf ears. The response by the government has been more repression and more violence. Today there is no independent media in the country due to the wide spread practice of jailing and forcing publishers and reporters in to exile. Today there are no functioning independent political parties due to the practice of systematic disruption of their normal day-to-day activities, jailing of opposition leaders or forcing them out of their country. Currently, prisons are filled with thousands of well-known political, civic organization and religious leaders as well as journalists under trumped-up “terrorism” charges. Certain ethnic groups are targeted. These prisoners are tortured to confess and to corroborate the charges against themselves and their colleagues. In spite of this massive oppression, victims of the regime have no recourse to justice since the judiciary is made subservient to the political manipulation of the ruling party.
As presented above, Ethiopians are once again faced with a regime that is led by a group of people who oppress them in multiple ways; deny them basic human rights and are hell-bent on blocking the democratic process for self-rule. We are also aware that though the regime comes from Tigrai, a thousands of Ethiopians that come from this ethnic group are victimized and have already started armed insurrection well over one decade ago. The predicament the Ethiopian people find themselves in currently is not unique. Under similar conditions, the founding fathers of one of the earliest democracies in the world have said it best in the Declaration of Independence by the Colonies from the Great Britain: ‘We hold these truths to be self-evident, that all men are created equal, that they are endowed by their Creator with certain unalienable Rights, that among these are Life, Liberty and the pursuit of Happiness. — That to secure these rights, Governments are instituted among Men, deriving their just powers from the consent of the governed, — That whenever any Form of Government becomes destructive of these ends, it is the Right of the People to alter or to abolish it, and to institute new Government, laying its foundation on such principles and organizing its powers in such form, as to them shall seem most likely to affect their Safety and Happiness’ A similar spirited paragraph is found in the preamble of African National Congress’s Freedom Charter. These words ring true today for the people of Ethiopia.
At this critical juncture, to facilitate the Ethiopian people’s struggle with able leadership, the democratic forces in the country are coalescing under the newly formed UMSED as a “broad church”.. It is not lost on the part of these democratic forces that one of the potential obstacles on the road to the Ethiopian people’s struggle for freedom and democracy is the international community’s multifaceted collaboration with the TPLF dominated government with seeming indifference to the prevailing repressive political conditions in the country.
Following their new goal of making inroads into Africa, some countries have become major financiers of the TPLF repressive regime. This may be an expected behavior from these governments, given the nature of their systems. However, the West’s support for the rogue dictatorial regime is inconsistent with the values of freedom, justice, and democracy the West practices at home and espouses for the stable world order. The West led by the US has correctly and understandably declared terrorism as the number one menace to global peace while in a typical short-term calculus have also decided to consider dictatorial regimes like that of Ethiopia to be “allies” in its anti-terrorism effort and the disorder in the Greater Horn of Africa region. As a result, the West has made the Ethiopian regime a beneficiary of its substantial financial, political, diplomatic and even military support indirectly emboldening it to continue with impunity in its human rights abuse and repression of its own people. This policy on the part of the Western countries is not only short sighted and immoral but is more than likely to lead to greater instability especially when minority regimes collapse.
It is obvious that the repressive nature of the regime and its extensive human rights abuses are among the main causes of instability in the region. For all those who are willing to see the writing on the wall, the regime is internally in continuous conflict with its citizens; it uses scorch-earth military expeditions in the Ogaden region to the east and makes occasional incursions into Kenyan territory pursuing armed resisters. The regime is also locked in constant conflict with Eritrea in the north. This is the reason why the regime has one of the biggest standing army in Sub-Saharan Africa thus spending large portion of the poor country’s budget on the military while the danger of famine and lack of resources for basic needs of its population is always lurking around.
While this is the true reason for the TPLF regime to build an army that is beyond the country’s legitimate external security threat need, it cynically uses a fraction of this army in international peace keeping missions in order to get acquiescence from the West for its nefarious repression at home as well as use these missions as a source of hard currency income for its corrupt highest military brass. Recently, the Ethiopian government is even seen scheming to leverage its security cooperation with the West, hopefully in vain, for extending its repressive hand abroad by invoking the legitimate rebellion and resistance of Ethiopians as a terrorist act. The truth is that the Ethiopian people’s resistance is a very disciplined and well organized struggle that is focused only on a political goal of making Ethiopia a democratic country either by forcing the minority regime to come to table or removing it if it continues to persist on blocking Ethiopians’ right for self-government. The people’s resistance movement is also very much aware of its responsibilities for the Ethiopian people, the people of the region and the international community. It is a resistance movement which is informed from the rich tradition of Ethiopian history. It is not a group of bandits and terrorists. It includes several members of the opposition who contested the ill-fated 2005 election. In deed it is a democratic force and represents a cross section of Ethiopians.
In their long history of existence, Ethiopians have shown no affinity for internalizing any sort of extremist ideology let alone to terrorist practice despite the persistent attempt to impose communism during the military regime and ethno-centric politics by the current regime on them. The history of Ethiopia is replete with building good relationship with its neighbors, peaceful coexistence and social stability. Ethiopian history also shows the courage and willingness of the people to lay their lives and honor to resist and prevail over colonialism and minority rule.. Witness the Ethiopian people’s glorious victory in the battle of Adwa and their resistance against fascist Italy even when the world turned its face and gave them its cold shoulders.
To stay true to our forefathers’ tradition saying no to oppression and its own commitment for democracy, UMSED pledges to work hard and to pay the necessary sacrifice to put an end to the tyranny of TPLF dominated regime and to assure that the TPLF regime becomes the last dictatorship in Ethiopian history. The UMSED appeals to the peace loving people of the world and the international community to stand in solidarity with the Ethiopian people; for it is only by democratizing Ethiopia that a lasting stability can be achieved and the specter of terrorism can be dealt with effectively in one of the most volatile regions of the world. Anything else will further destabilize Ethiopia and turns the Horn of Africa into a hot bed of terrorism.
From the Foreign Relations Office of United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy (UMSED)
September 25, 2015

Thursday, September 24, 2015

የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ እየተባባሰ መጥቶአል፣ መንግስትም ችልተኝነትን አብዝቶአል

September 24,2015
በሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣውን አረንጓዴው ድርቅ እየተባለ የሚጠራው ከፍተኛ ረሃብ በመላው ሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣ ሲሆን በአሁን ሰአት በሰሜኑ ክልል ምስራቅ እና ደቡቡን በከፊል ከማጥቃቱም በላይ ከፍተኛውን ህዝብ ወደ ስደት ሲዳርግ ብዙሃኑን ደግሞ በተለያዩ የሃገሪቱ ትልልቅ ከተሞች ለልመና እንዲሰደዱ አድርጎአል ። በተለይም የገበሪው የዚህ አመት የምርት ሁኔት ማሽቆልቆል እና መንግስት በገበሬው ህዝብ ላይ የሚያሳርፈው ጫና ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ፣ምርቱን ማምረት ያልቻለው እና ያሉትን የቀንድ ከብቶችንም ለመሸጥ ወደ ከተማ የሚያጓጉዘው ገበሬ በፖሊሶች እየተነጠቀ ለጨረታ ሲቀርብበት ገበሬውን ለረሃብ እና ለከፍተኛ ችግር እንዲሁም ቤተሰቡን በየሜዳው ትቶ እንዲሄድ እያእረገው ነው ሲሉ ከአዲስ አበባ የተሰራጨው ሪፖርት ያመለክታል ።

ባሳለፍነው ሁለት ወራት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ምንስቴር የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን ገበሬው ክብቶቹን በወቅቱ ስላላጠጣ ነው ብለው በአደባባይ ዋሽተውት የነበረውን ዘገባ እንደገና መልስ ብለው እርዳታ ያሽናል ብለው የአለም መንግስታትን መማጸን የቻሉበት አጋጣሚ እንደነበር ቢታወስም የጉዳዩ ተያያዥነት የመጣው የኢትዮጵያ መንግስት ኦባማን እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎችን ለመቀበል ያቀረበውን በጀት እንዳይቆረጥበት ያዘጋጀው እቅድ ነሲሉ ይሄውም ከ8፣ሚሊዮን ኣሜሪካን ዶላር በላይ ለዚኢያ ስብሰባ የታቀደ አላማ ላይ እንዲውል ሃገሪቱ ለስብሰባው መበጀቷን ሪፖርቱ ያመለክታል ፤ ይህ በእንዲህ እንዳለ ፕረዚዳንት ኦባማ ለሶስት ቀን ጉብኝቱ ብቻ 2.4 ሚሊዮን ዶላር ብቻ የከፈለ ሲሆን ይህም ከሁለት መቶ አባል ሰራተኞቹ እና የአየር ሃይል አባላቶቹ ጭምር እና ፣የበረራ ቁጥጥር ክፍል የሚያደርጉትንም የሚጨምር እንደሆነ ገለጸዋ አብራርቶአል ሆኖም  ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ግን በአፍሪካ የኢኮኖሚ ደረጃ ብች ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ ሲሆን ይህን ያህል ወጭ የሚሸፍኑ ኣልሆኑ ይታወቃል በዚህ ጉዳይ ላይ ሃገሪቱ ከትርፍ ይልቅ በኪሳራ ልትንቀሳቀስ ትችላለች የሚለው ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ከመሆኑም በላይ መንግስት ለሃገሩ እና ለህዝቡ እንዲሁም  ለህልውናው ቸልተኛ በመሆኑ አስጊ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

Zone9 Bloggers Are Not Alone: More Ethiopian Citizens Face Terrorism Charges

September 24, 2015
by Tedla D. Tekle | GlobalVoices
Alongside the now-famous case of the Zone9 bloggers, there are so many detained Ethiopian bloggers, online activists and politicians, whose names are not yet on the map.
Zelalem, Yonatan, Bahiru and Abraham
Zelalem, Yonatan, Bahiru and Abraham. Photo used with permission from debirhan.com
Last year on July 8, 2014, Ethiopia detained a number of local opposition leaders, bloggers, online activists and concerned citizens. Some were released after four months of interrogation. However, ten were charged on October 31, 2014 under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation with having links to diaspora-based Ethiopian opposition groups such as Ginbot 7, applying to attend an online security training, and engaging in online activism. Three of the 10 defendants are not members of any political party but ordinary citizens who were arrested for applying to attend a course. These are Zelalem Workagenegu, Yonatan Wolde and  Bahiru Degu.
The controversial Anti-Terrorism Proclamation was adopted in July 2009. Ethiopian officials tend to defend the law by arguing that its controversial provisions were copied from the existing laws of countries such as the United Kingdom. Article 6 of the Proclamation, which has been used to curtail freedom of expression, provides that:
[w]hosoever publishes or causes the publication of a statement that is likely to be understood by some or all of the members of the public to whom it is published as a direct or indirect encouragement or other inducement to them to the commission or preparation or instigation of an act of terrorism [is subject to between 10 and 20 years in prison].
Zelalem, the first defendant, is a human rights activist who blogs at DeBirhan. Yonatan and Bahiru, who are best described as concerned citizens, had applied along with Zelalem for a social media and Internet security training that was brought to their knowledge by a US-based Ethiopian journalist. After an email from the Ethiopian journalist in the US was found in their possession, these young men were also arrested and later charged with applying for “a terror training” when in fact the training was about Internet safety and security.
Ethiopian court last month acquitted Abraham Solomon, detained for having connections with the first defendant Zelalem, along with four other opposition politicians namely Abraha Desta, an official of the opposition Arena Tigray Party and social media activist, Yeshiwas Assefa, council member of the Blue (Semayawi) Party, Daniel Shibeshi, official of the now defunct Unity for Democracy and Justice (UDJ) party and Habtamu Ayalew, former Public Relations Head of the defunct UDJ. However, until today they have not been released because the Prosecutor has reportedly appealed the decision.
An article by the Electronic Frontier Foundation shows the increasing attempts of silencing online activists and netizens in Ethiopia. The organisation called Ethiopia to:
Immediately free all journalists in prison, including the remaining Zone 9 bloggers, and relieve them of all charges for the “crime” of reporting the news.
End the prosecution of individuals for pursuing security training and using encryption technologies, and free Zelalem Workagegnehu, Yonatan Wolde, Abraham Solomon, and Bahiru Degu.
Cease and desist from using invasive surveillance technologies like FinFisher and Hacking Team’s Remote Control System to spy” on Ethiopian journalists, Diaspora, and opposition groups.
While Zone9 remains among Ethiopia’s best-known case of its kind, stories like that of Zelalem demonstrate that the issues these bloggers face extend far beyond a few individuals. The next court appearance of Zelalem, Yonatan and Bahiru is between November 7-9, 2015.

በወያኔ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የሰራዊት አመራሮችና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬ ተስፋፍቶል

September 24,2014
በወያኔ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የሰራዊት አመራሮችና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬ መስፋፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች አስረድተዋል:: የሕዝብን መብት እና በልማት ስም በፕሮፓጋንዳ በመደለል በስልጣን ላይ ያለው በወያኔው አመራሮችና እና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አለመተማመን እና ጥርጣሬው እየሰፋ መምጣቱን ለምድር ጦር ክፍል ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልፀው። ባለፉት አመታት በሰራዊት ውስጥ ወታደራዊ ደህንነቶች መሰግሰጋቸው ከሰራዊቱ ጥያቄዎች ጋር ተደምሮ በተለይ በምስራቅ ደቡብ እዝ እና በሰሜን እዝ ከፍተኛ የሆነ የውስጥ ውጥረት እንዳለና እንዲሁም በሰራዊቱ ውስጥ በየስብሰባው ሶማሊያ ስለዘመቱ ወታደሮች ማብራሪያ መጠየቁን ታውቋል::
በሰራዊት ውስጥ በወታደራዊ ደህንነት ቦታ የሚያገለግሉ ምንጮች እንዳሉት ሰራዊቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና ጥርጣሬ እየጨመረ የመጣው አሁንም በየእዙ የሚጠረጠሩ መኮንኖች እስራት እንደቀጠለ ተናግረዋል::ለሆዳቸው ያደሩ የሰራዊት አባላት ቢኖሩም ይህን ያህል አይደሉም የሚሉት ምንጮቹ ሰራዊቱ ግን በመፈራራት እና እርስ በርስ ጥርጣሬ ውስጥ እየተጓዘ እንደሆነ ገልጸዋል::በተለያዩ ግምገማዎች ከ10 የሰራዊቱ አባላት ሰባቱ በማስጠንቀቂያ መታለፋቸውን በራሱ በሰራዊት ውስጥ ያለው ችግር አንደኛው ገጽታ መሆኑም አውስተዋል::

Wednesday, September 23, 2015

የተናገሩት ከሚጠፋ… (በኤፍሬም ማዴቦ – ከአርበኞች መንደር)

September 23, 2015
በኤፍሬም ማዴቦ
ባለፈዉ መጣጥፌ “ቃል የእምነት ዕዳ ነዉ” ብዬ ጀምሬ “ቃላችን አይለወጥ” ብዬ ነበር የተለየኋችሁ። አለምክንያት አልነበረም እንዲህ ያልኳችሁ፤ በአንድ በኩለ ቃል መከበርም መከፈልም ያለበት ዕዳ ስለሆነ በሌላ በኩል ደግሞ ቀትር ላይ የገባዉን ቃል ሳይመሽ እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ የሚክድ ብዙ ቃላ አባይ ሰላለ ነዉ። አገሬን ከወያኔ አጸዳለሁ ብሎ ቃል የሚገባ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዕዳ አለበት። ዕዳዉ ደግሞ ገንዘብ ወይም ንብረት አይደለም። ቃሉን መጠበቅ ወይም ቃሉን ማክበር ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ደግሞም አንድ ሰዉ የተናገርዉን ቃል ሰብሮ የእምነት ባለዕዳ ከሚሆን ዕድሜ ልኩን የገንዘብ ባለዕዳ ቢሆን ይሻለዋል። የገንዘብ ዕዳ ቆይቶም ቢሆን ይከፈላል ወይም አበዳሪዉ ሊምረን ይችላል፤ የዕምነት ዕዳ ግን የማይሽር ጠባሳዉ እየቆረቆረን አብሮን ይኖራል እንጂ አይጠፋም። ማንም ሰዉ ለአገሬ ህይወቴን እሰጣለሁ ብሎ ቃል ሲገባ መሃላዉ ከህዝብና ከአገር ጋር ብቻ አይደለም፤ እንዳዉም የሰዉ ልጅ ቃል የሚገባዉ መጀመሪያ ከራሱ ጋር ነዉ። ለራሱ የገባዉን ቃል የማያከብርና ቃሌ ቃል ነዉ ብሎ የገዛ ራሱን የእምነት ዕዳ ያልከፈለ ሰዉ ለህዝብና ለአገር ቃል መግባት አይችልም። ዛሬ ወያኔን እናጥፋ ብሎ ካራ ጨብጦ አብሮኝ የቆመ ሰዉ ነገ ከወያኔ ጋር ሆኖ ካራዉን እኔዉ ላይ አዙሮ ባየዉ እሱ ቀድሞዉንም ካራ የጨበጠዉ ወያኔን ለማጥፋት ሳይሆን ስጋ ሊቆርጥብት ነዉና ብዙ አይገርመኝም። እንዲህ አይነቱን ለቁም ነገር ሲፈልጉት አልሰማ ብሎ ሆዱ ሲሞላለት ግን ሳይጠሩት አቤት የሚል ስጋ ወዳድ ሆዳም ደግሞ ኢትዮጵያ በየዘመኑ አፍርታለችና ብዙ ሊገርመን አይገባም። ከሰሞኑ ከምድረ ኤርትራ የነፈሰዉ ነፋስ ያስተማረን አንድ ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር እንዲህ አይነቱን ሞላ ጎደለ የሚባል የካራና የስጋ ጨዋታ ነዉ። አዎ! የካራ ጨወታ – ወዲህ ማዶ ስጋ ሊቆርጡበት ወዲያ ማዶም ስጋ ሊቆርጡበት።
“የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ” . . . ገዢዎቻችን በተለይ የዛሬዎቹ ቃል አባዮች እንደቆሻሻ ዕቃ መሬት ላይ ጣሉት እንጂ ቃል የዕምነት ዕዳ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ዘመን አይሽሬ የአገራችን አባባል ነዉ። አባቶቻችን የተናገሩትን ወይም ቃል ገብተዉ የተማማሉትን ነገር ከሚያጥፉ የወለዱትን ማጣት ይቀላቸዋል። እኛ ልጆቻቸዉ ግን ከዬት የመጣን ጉዶች አንደሆንን አላዉቅም ቃል አባይነታችን እኛን፤ ልጆቻቸንና አገራችንን ሲያጠፋ በአይናችን እያየን ቅር እንኳን አይለንም። “እመጣለሁ ብሎ ሰዉ እንዴት ይዋሻል፤ ማበል እንኳን አንቺን ምድር ያበላሻል” መሬት ላይ ጠብ የማይል ትክክለኛ አባባል ነዉ። አገራችን ኢትዮጵያ ትናንት እንሞትልሻለን ብለዉ ዛሬ በሚገድሏት ቃል አባይ ልጆቿ እየተበላሸች ነዉ። እነዚህ ቃልአባዮች የኢትዮጵያን የምድር ላይና የምድር ዉስጥ ኋብቷን አንጂ የገረጣዉን ፊቷን ማየት አይፈልጉም- አዎ ወያኔ የሚያየዉ ኃብትሽን፤ የሳዑዲዉ ሰዉ ወርቅሽን፤ ባዕድ ከበርቴዉ ለምለም መሬትሽን . . . ወይኔ ኢትዮጵያ ማን ይሆን የሚያየዉ የጠቆረዉ ፊትሽን፤ ማን ይሆን የሚያብሰዉ እምባሽን፤ እኮ ማን ይሆን የሚያቆመዉ መከራሺን . . . ማን ይሆን?. . . ማን ይሆን?
የዛሬዋ ኢትዮጵያ አንድ ትዉልድ ዉሸት ብቻ እየሰማ ያደገባት የዉሸት መዲና ሆናለች። ጳጳሱ፤ ቄሱና ፓስተሩ “እኔ መንገድ፤ አዉነትና ህይወትና ነኝ” ያለዉን የሰማዩን አምላካቸዉን ረስተዉ ለምድር ዉሸታሞች አደሩ። ሂዱና ዋሹ ሲባሉ ሄደዉ ዋሹ፤ እዉነትን በዉሸት አስተባብሉ ሲባሉ አስተባበሉ፤ በሀሰት መስክሩ ሲባሉ አፋቸዉን ሞልተዉ በሀሰት መሰከሩ። “ታላቁ መሪ” እየዋሸን ኖሮ እየዋሸን ሞተ። መታወቂያዉ ዉሸት ነዉና ሞቶም አልሞተም ተብሎ ተዋሸለት። ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር ምን ለምዳ ትመጣለች እንዲሉ ሌላ ሁሉ ቢቀር ዉሸትን ይፀየፋል ተብሎ የተነገረለት የዛሬዉ ጠ/ሚኒስቴር ጭራሽ “ታላቁን መሪ” እንደዋቢ እየጠቀሰ ስራዉ ሁሉ ዉሸት፤ ዉሸት፤ ዉሸት ብቻ ሆኖ ቀረ። የኢትዮጵያ ሬድዮ ሲከፈት ዉሸት ይናገራል፤ ሲዘጋ ደግሞ ነገ ስለሚዋሸዉ ዉሸት ያስባል። ጋዜጦች በስህተት አንኳን እዉነት አይጻፍባቸዉም። የኢቲቪ ዜና አንባቢ ተመስገን በየነ ግማሽ ሰዐት የዋሸዉን ዉሸት ለማካካስ ዜናዉን አንብቦ ሲጨርስ ለ15 ደቂቃ ጎንበስ ብሎ ይሰግዳል።
ለረጂም ግዜ ተማምነን ጀርባችንን የሰጠነዉ ሰዉ ለጠላት እጁን ሰጥቶ ጦርነት ሲያዉጅብን አንዳንዴ በትግሉ ዉስጥ ማንን አምነን ጀርባችንን እንደምንሰጠዉ ግራ ሊገባን ይችላል። ከሰሞኑ የሰማነዉ ዜና እንዲህ ግራ የሚያጋባ ዜና ነዉ። ሆኖም ሳንተማመን ትግል ብሎ ነገር የለምና የትግል ጓዶቻችንን ማመን ብርታት እንጂ ደካሞች እንደሚሉት ሞኝነት ወይም የዋህነት አይደለም። በጓዶቻችን ላይ ክህደት ፈጽመን ከምናሰቃያቸዉ እኛ ብንሰቃይ ይሻላል፤ ደግሞም ጓዶቻችንን ማመን አቅቶን በጥርጣሬ ተፋጥጠን ባለንበት ከምንረግጥ አንዳንዴ አዉቀንም ቢሆን ብንታለል ብዙ መንገድ መጓዝ እንችላለን። ትግል በተለይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ከሚያስተምረን ትምህርቶች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ሌሎች በኛ ላይ እምነት እንዲኖራቸዉ ከፈለግን እኛ አስቀድመን ልናምናቸዉ አንደሚገባን ነዉ። አለዚያ ሁለታችንም አንተማመንም። አለመተማመን ደግሞ ያጠፋፋናል እንጂ አንድ ቤት ዉስጥ አብሮ አያኖረንም። እንደኔ እንደኔ የወያኔን ስርዐት ደምስሰን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር የምናደርጋት እያንዳንዳችን ለትግል ጓዶቻችን የገባነዉን ቃል ሰብረን ረጂም ህይወት ከመኖር ቃላችንን አክብረን ዛሬዉኑ መሞትን ስንመርጥ ብቻ ነዉ። ወያኔ አንደ እሳት የሚፈራዉና በፍጹም የማያሸንፈዉ አንዲህ አይነቱን ከብረት የጠነከረ ጽኑ አቋማችንን ብቻ ነዉ። ለዚህ ነዉ እንዲህ አይነት ጽናት የሌላቸዉን ደካማ ግለሰቦች ፈልጎ እያማለለ ጽናታችንን የሚፈታተነዉ። ከሰሞኑ ለህዝብ ከመታገል ህዝብን መታገል መርጦ ከለየላቸዉ የህዝብ ጠላቶች ጋር የተቀላቀለዉ ሞላ አስገዶም ለዚህ ዉሳኔ የበቃዉ ህዝባዊዉ ትግል የሚፈልገዉ የአለማ ጽናት የሌለዉ ደካማ ግለሰብ ስለሆነ ብቻ ነዉ። ዉድ ኢትዮጵያዉያን ክህደት ትናንት ነበር፤ ዛሬ አለ፤ ነገም ይኖራል። ስለዚህ ክህደት ሊያስተምረን እንጂ በፍጹም ሊያስበረግገንና አንገታችንን ሊያሰደፋን አይገባም። ክህደትና ከሀዲዎችን እያሰላሰልን የምንኖር ከሆነ የበለጠ እንዲጎዱን ተጨማሪ ዕድል እንሰጣቸዋለን እንጂ ሌላ ምንም የምንፈይደዉ ፋይዳ የለም።
ሞላ አስገዶም እሱን የመሰሉ ደካማ ጓደኞቹን ከተቀላቀለ በኋላ መቀሌ፤ አዲስ አበባና አዳማ ዉስጥ ክህደቱን አስመልክቶ እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ሦስት ጋዜጣዊ መግለጫዎችን ሰጥቷል። እርግጠኛ ነኝ ይህ ቁርስ ላይ የተናገረዉን ምሳ ላይ የማያስታዉስ ግለሰብ በተያዘለት የጉብኝት ሰሌዳ መሠረት ዘጠኙን ክልሎች የሚዞር ከሆነ ዘጠኝ የተለያዩና እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ምክንያቶችን መደርደሩ አይቀርም። የወያኔ የመረጃና የደህንነት መ/ቤት ተብዬዉም ቢሆን ምን ያህል የዉሸትና የጉራ ቤት ለመሆኑ መረጃ ብሎ የለቀቃቸዉን ዉሸቶችና ቱልቱላዎች መጥቀሱ ይበቃል። ለምሳሌ የመረጃና ስለላ ድርጅቱ ከአንድ አመት በላይ ከሞላ አስገዶም ጋር በሚስጢር ይሰራ እንደነበር ተናግሯል። ይህ እዉነት ከሆነ የደምህት ታጋዮች በዚህ አንድ አመት ግዜ ዉስጥ በወያኔ ታጣቂዎችና ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ ለወሰዷቸዉ እርምጃዎች በተለይ እግር ኳስ ጨዋታ በመከታተል ላይ እንዳሉ ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር እንዳለ ለተደመሰሱት የኢትዮጵያ ወታደሮች ተጠያቂዉ ከሞላ አስገዶም ጋር ይሰራ የነበረዉ የወያኔ የመረጃና የስለላ ድርጅት ነዉ ማለት ነዉ።
ሞላ አስገዶም ትናንት ከኛ ጋር ሆኖ እኛ ሲል ነበር፤ ዛሬ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጠለቶች ጋር ሆኖ እኛ ይላል። ይህ ሰዉ “እኛ” ሲል የሱ እኛ እነማንን እንደሚያጠቃልል አይታወቅም፤ እሱ እራሱም የሚያዉቀዉ አይመስለኝም። ሞላ አስገዶም ወያኔን እንደተቀላቀለ አፉን ሞልቶ ጥምረቱን የፈጠርነዉ “እኛ” ነን ብሎ ሲናገር በተደጋጋሚ ተደምጧል። ጥምረቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎትና ህዝባዊ ትግሉ የደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዉጤት ነዉ እንጂ ሞላ አስገዶም ስለፈለገዉ የሚፈጠር አለዚያ የሚቀር የሞላ አስገዶም የቤት ዉስጥ ዕቃ አይደለም። ደግሞም እንደ ሞላ አስገዶም ፍላጎት ቢሆን ኖሮ የደምህት ጥምረቱ ዉስጥ መግባት ለግዜዉም ቢሆን ሊዘገይ ይችል ነበር። ደምህት ጥምረቱ ዉስጥ ገብቶ አገር አድን የጋራ ንቅናቄዉ የተፈጠረዉ የደምህት ሠራዊትና ከሞላ አስገዶም ዉጭ ሁሉም የደምህት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከሌሎች ኢትዮጳያዉያን ወገኖቻቸዉ ጋር ሆነዉ በጋራ ለመታገል በመወሰናቸዉ ነዉ። የሞላ አስገዶም ፈርጥጦ ወያኔ ጉያ ዉስጥ የመሸጎጡ ዋነኛዉ ምክንያትም የዚህ ዉሳኔ ዉጤት ነዉ እንጂ የወያኔ መረጃና ስለላ ድርጀት ሚስጥራዊ ግንኙነት ዉጤት አይደለም። ሌላዉ እርስ በርሱ የሚጋጭ የወያኔ ዉሸት – በአንድ በኩል ሞላ አስገዶምና የደምህት ሠራዊት ሙሉ ትጥቃቸዉን እንደታጠቁ ጠቅልለዉ ወደ አገራቸዉ ተመለሱ የሚለዉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቁጥሩ ወደ 700 የሚጠጋ የደምህት ሠራዊት ወደ አገሩ ተመለሰ የሚለዉ የተምታታ ዘገባ ነዉ። እዚህ ላይ የደምህትን ሠራዊት ብዛት መናገሩ አስፈላጊ ባይሆንም ግንዛቤ ማግኘት የፈለገ ሰዉ ግን ተመድ ያወጣቸዉን ሪፖርቶች መመልከቱ የሚበቃ ይመስለኛል። ደግሞም ሞላ አስገዶም አታልሎ መንገድ ካስጀመረዉ ሠራዊት ዉስጥ ገሚሱ ወደ ትግሉ ሜዳ ተመልሷል፤ የተቀረዉ ደግሞ ወደ ትግሉ ሜዳ ካልተመለስኩ እያለ ከሱዳን ባልስልጣኖች ጋር እየተደራደረ ነዉ። በነገራችን ላይ የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ ሞላ አስገዶም አታልሎ ሀምዳይት ከወሰዳቸዉ በኋላ ትግል ወይም ሞት ብለዉ ተመልሰዉ ከትግል ጓዶቻቸዉ ጋር ከተቀላቀሉ ጀግኖች ኢትዮጵያዉያን ጋር አብሮ ቡና ጠጥቷል።
ጓዜን ጠቅልዬ ትግሎ ሜዳ ከመግባቴ በፊትም ሆነ ከገባሁ በኋላ የደምህት ስም በተነሳ ቁጥር አብረዉ የሚነሱ ሁለት መላምቶች አሉ። አንደኛዉ መላምት ደምህት የኤርትራ መንግስት ሆን ብሎ የፈጠረዉና ጭራሽ ኤርትራ ዉስጥ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎችን ተክቶ በመንግስታዊ ተቋሞች ጥበቃና ደህንነት ስራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነዉ የሚል መላምት ሲሆን ሁለተኛዉ መላምት ደግሞ ሞላ አስገዶም በኤርትራ መንግስት ድጋፍ ሁለተኛዉ መለስ ዜናዊ ሆኖ ህወሃትን ተክቶ አትዮጵያን ይመራል የሚለዉ መላምት ነዉ። ደግነቱ የነዚህ መላምቶች የማዕዝን ራስ የሆነዉ ሞላ አስገዶም ኮብልሎ ወያኔን መቀላቀሉና ከተቀላቀለ በኋላ የሰጣቸዉ ጋዜጣዊ መግለጫዎች ሁለቱንም መላምቶች እንዳልነበሩ አድርጓቸዋል። እኔን አልገባ ያለኝና በጣም የሚገርመኝ ግን በአንድ በኩል የኤርትራ መንግስት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች ትብብር እንዲፈጥሩ አይፈልግም ይባላል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ጥምረቱ የተፈጠረዉ በሻዕቢያ ግፊት ነዉ ይባላል። መቼም ገና በልጅነቴ ካልጃጀሁ በቀር ሻዕቢያና የኤርትራ መንግስት መሃል ልዩነት ያለ አይመስለኝም። ሌላዉ የሰሞኑ አስቂኝ ድራማ ደግሞ ሞላ አስገዶም ጥምረቱን የፈጠርነዉ እኛ ነን ሲል የሱን መኮብለል አስመልክቶ የሚሰጠዉ አስተያያት ደግሞ ሞላ አስገዶም ጨርቁን ጠቅልሎ ወያኔን የተቀላቀለዉ ብርሀኑ ነጋ በኤርትራ መንግስት ግፊት የጥምረቱ ሊ/መንበር መሆኑ አልዋጥ ብሎት ነዉ ይባላል።
ሌላዉ አሁን በቅርቡ ወይም ከሞላ አስገዶም መኮብለል በኋላ የተጠነሰሰዉ መላምት ደግሞ ደምህቶች እራሳቸዉ ኤርትራ ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ድርጅቶች በወያኔ ስርዐት ላይ ወታደራዊ እርምጃ መዉሰድ እንዳይችሉ ሆን ተብለዉ በወያኔ የተፈጠሩ እንቅፋቶች ናቸዉ የሚለዉ መላምት ነዉ። በኔ ግምት ይህኛዉ መላምት ከሁሉም መላምቶች የከፋና እጅግ በጣም አደገኛ የሆነ ጽንፈኛ መላምት ነዉ። እንደዚህ መላምት ፈጣሪዎች አባባል የትግራይ ህዝብ በህወሃት አመራር በደል አይደርስበትም ወይም የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር ሆኖ የህወሃትን ግፈኛ ስርዐት አይታገልም ማለት ነዉ። እንዲህ አይነቱ ጭፍንነትና ጠባብነት የሚመነጨዉ ደግሞ ሞላ አስገዶምንና ደምህትን ወይም ህወሃትንና የትግራይን ህዝብ ለያይቶ ማየት ካለመቻል አባዜ ነዉ። በደርግ ስርዐት ዉስጥ ጭቆናዉና በደሉ በዛብኝ ብሎ ጠመንጃ ያነሳዉ ጀግናዉ የትግራይ ህዝብ ህወሃት ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ተነጥሎ እንዲታይ ለማድርግ የሚሸርብበትን ሤራና የሚያደርስበትን ግፍና መከራ አፉን ዘግቶ የሚቀበልበት ምንም ምክንያት የለም። ስለዚህ ደምህት የትግራይ ህዝብ ብሶትና ምሬት አምጦ የወለደዉ ፀረ ህወሃት ንቅናቄ ነዉ እንጂ ወያኔ የፈጠረዉ ድርጅት አይደለም፤ሊሆንም አይችልም። ሞላ አስገዶምም ቢሆን የራሱ የተጠረቃቀመ ድክመት ከንቅናቄዉ ሊ/መንበርነቱ እንደሚያስነሳዉ ሲያዉቅ የፈረጠጠ ፈርጣጭ እንጂ እሱና ወያኔ እንደሚሉት የአንድ አመት ቀርቶ የአንድ ወርም ተከታታይ ግንኙነት አልነበራቸዉም።
ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረከ ብቅ ብለዉ የጠፉትንም ሆነ ዛሬም ድረስ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች ባህልና ድርጅታዊ አሰራር ስንመለከት የድርጅቶች ህልዉና መመዘኛና የማንነታቸዉ መለኪያ ቆምንለት የሚሉት አላማ ሳይሆን የመሪዎቻቸዉ በተለይ የዋናዉ መሪ ተክለሰዉነት ነበር። የድርጅት ወይም የፓርቲ ሊ/መንበር ከድርጅቱ ባለይ ነዉ፤ እሱ ይሁን ያለዉ ይሆናል፤አይሁን ያለዉ አይሆንም። ብዙ ግዜ የድርጅት/ፓርቲ ሊ/መንበር ድርጅቱን የማፍረስ አቅም ጭምር አለዉ። ይህንን ደግሞ በቅርብ ግዜ ታሪካችን በተደጋጋሚ አይተናል። አንድን ድርጅት ወይም ፓርቲ አባላት ሲቀላቀሉ የሚመለከቱት የፓርቲዉን ሊ/መንበር እንጂ የፓርቲዉን የፖለቲካና የኤኮኖሚ ፕሮግራም አይደለም። የፓርቲ ሊ/መንበርም ቢሆን የኔ የሚላቸዉን ሰዎች ነበር እየመረጠ የሚያሰባስበዉ። እንደዚህ አይነቱ የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር አሁን እየተቀየረ የመጣ ቢሆንም ለረጂም ግዜ የፖለቲካ ትግላችን ችግር ሆኖ ቆይቷል። ሞላ አስገዶም በቅርቡ የደምህትን ሠራዊት ከነሙሉ ትጥቁ ይዤ ኢትዮጵያ ገባሁ ብሎ በድፍረት የተናገረዉ ንግግር ይሄዉ የድርጅት ሊ/መንበር ያሰኘዉን ሁሉ ማድረግ ይችላል የሚለዉ የቆየ የፖለቲካ ባህላችን በሽታ ተጠናዉቶት ነዉ። “ዝንጀሮዉን ከጫካ ያዉጡታል እንጂ ጫካዉን ከዝንጀሮዉ ዉስጥ አያወጡትም” የሚል ብህል አለ፤ ትክክለኛ ብህል ነዉ። ሞላ አስገዶም ህወሃት/ወያኔ የኢትዮጵን ህዝብ በአጥር እየለያየ በትናናንሽ ጎጆዎች ዉስጥ ማኖሩ አልዋጥ ብሎት ሁሉንም የሚያቅፍ ሰፊ ቤት ሰርተን ኢትዮጵያን የዲሞክራሲ አገር እናደርጋለን ብሎ ለብዙ አመታት የታገለ ሰዉ ነዉ። ችግሩ ሞላ አስገዶም ነዉ ከነዚያ ትናንሽ የወያኔ ጎጆዎች የወጣዉ እንጂ ትናንሽ ጎጆዎቹ ከሞላ አስገዶም ዉስጥ ስላልወጡ እንደ ማግኔት እየሳቡት ወደነበረበት ቦታ መልሰዉታል። ለሁሉም የሞላ አስገዶም ታሪክ ሲጻፍ – መጣና ሄደ ከሚሉ አምስት ሆሄያት የዘለለ ምንም ቁም ነገር የለዉም። እየመጡ መሄድና እየሄዱ መምጣት ደግሞ ትናንሽ ቤት የሚናፍቃቸዉ ትናንሽ ሰዎች እስካሉ ድረስ ይቀጥላል።
ሁለት ሺ ሰባት ሊጠናቀቅ ሦስት ቀን ሲቀረዉ አንድ የብዙ ኢትዮጵያዉያንን ጆሮ የሳበ ዜና ቴሌቪዥኑን፤ ሬድዮኑን፤ ጋዜጣዉንና ድረገጹን ተቆጣጠረዉ። ዜናዉ የወያኔ/ህወሃትን ስርዐት በመሳሪያ ኃይል የሚታገሉ አራት ድርጅቶች አገር አድን የጋራ ንቅናቄ ፈጠሩ የሚል የአዲስ አመት የምስራች ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብ ለረጂም ዘመን የናፈቀዉ የምስራች ነበር። ግን ምን ያደርጋል – በጥባጭ እያለ ንጹህ ዉኃ አይጠጣምና ይሀንን የአዲስ አመት የምስራች ሰምተን ሳናጣጥም ነበር የሞላ አስገዶምን ዜና ክህደት የሰማነዉ። አስደንጋጭ ዜና ነበር። በእርግጥም የአራት ድርጅቶች ጥምረት ተፈጠረ የሚል ዜና በተሰማ ማግስት የጥምረቱ ምክትል ሊ/መንበር ሠራዊት እየመራ ሄዶ ወያኔን ተቀላቀለ የሚል ዜና መስማት የሚያስደነግጥና በመጀመሪያዉ ዜና ላይ ቀዝቃዛ ዉኃ የቸለሰ ልብ ሰባሪ ዜና ነዉ። ደግነቱ ሁሉም ነገር ለበጎ ነዉ። የሞላ አስገዶም መክዳት ተራ ዜና ነዉ ማለቴ አይደለም። ግን ሞላ አስገዶምና የወያኔ መረጃ ድርጅት በትብብር ሠራነዉ ያሉት አዲስ ድራማ ተዉኔቱ ሳይጻፍ አየር በአየር የተከወነ ምናቡ ያልተባ ድራማ በመሆኑ ድራማዉ ከያኒዉን ሳይሆን የኢትዮጵያን ህዝብና ለአንድነቱና ለነጻነቱ የሚታገሉ ልጆቹን በከፍተኛ ደረጃ የጠቀመ መሆኑን ማሳዉቁ አስፈላጊ ይመስለኛል።
ደምህት በዚህ የወያኔ ድራማ ዉስጥ በእሳት ተፈትኖ ወርቅነቱን አረጋግጧል። ሞላ አስገዶም የደምህትን ሠራዊት ለወያኔ አስረከብኩ ብሎ በተናገረ ማግስት የደምህት መሪዎች የሰጡት አርቆ አስተዋይነት የታየበት አመራርና ያሳዩት ቆራጥነት የፖለቲካ ድርጅቶቻችን የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ በግልጽ አሳይቷል። ደምህት እራሱም እንደ አንድ የትግል ድርጅት የተደቀነበትን አደጋና ፈተና በጣጥሶ በመዉጣት በትናንሾችና በደካሞች ሴራ በፍጹም የማይናጋ ጠንካራ ድርጅት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። የዛሬዉ ደምህት ዉስጡን ከአድርባዮች ያፀዳ ሁለትና ሦስት እርምጃዎች ወደፊት የተራመደ ጠንካራ ድርጅት ነዉ። እርግጠኛ ነኝ ይህ የደምህት መሪዎች ያሳዩት አስተዋይነት፤ ጽናትና ቆራጥነት እኔ የምፈልገዉ ነገር ካልሆነ ድርጅቱን በአፍጢሙ እደፋዋለሁ ብለዉ ለሚያስቡ ዕብሪተኛ መሪዎች ጥሩ ትምህርት ነዉ። ሌላዉ የሞላ አስገዶም ክህደት በግልጽ ያሳየን ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረክ የሀዝብ መብትና ነጻነት ይከበር በሚሉ የነጻነት ሀይሎችና ህዝብን ረግጠን እንገዛለን በሚሉ ፀረ ህዘብ ሀይሎች ለሁለት መከፈሉን ነዉ። ወደድንም ጣላን ካሁን በኋላ ያለን አማራጭ ሁለት ብቻ ነዉ፤ ወይ ወያኔ ሆኖ ከህዝብ ጋራ መዋጋት ወይም ከህዘብ ጋር ሆኖ ወያኔንና ስርዐቱን መዋጋት። ሞላ አስገዶም ጎራዉን ለይቷል፤ እኛም ጎራችንን እንለይ። መኃል ቆሞ መመልከት አብቅቷል።
ጠላቴን አግዝፌ መመልከት አልወድም፤ ትንሽ ነዉ ብዬም ጠላቴን በፍጹም አልንቅም። በቅርቡ የወያኔ የመረጃና ደህንነት መ/ቤትና ሞላ አስገዶም ከአንድ አመት በላይ አብረን ሠራን ያሉትን የጀማሪዎች ስራ ስምለከት ግን ወያኔ/ህወሃት “የምትሰሩትን ብቻ ሳይሆን የምታስቡትን ጭምር የሚያይ አይን አለኝ” እያለ የኢትዮጵያን ህዝብ ከማስፈራራት ዉጭ የረቀቀ የመረጃ ስራ መስራት ቀርቶ አረፍተነገሮችን አገጣጥሞ ለጆሮ የሚጥም ንግግር ማድረግ የሚችል አዋቂ የሌለበት የባዶዎች ድርጅት መሆኑን ነዉ የተረዳሁት። ሞላ አስገዶምም በወዶገባነት ሄዶ የተቀላቀለዉ ይህንኑ አዋቂ የሌለበትን እሱን የመሰለ ድርጅት ነዉ። ይህንን ደግሞ እስከዛሬ በሰጣቸዉ ቃለመጠይቆች በግልጽ አይተናል። ህወሃት/ወያኔን እስከዛሬ በሥልጣን ላይ ያቆዩት ሁለት ነገሮች ቢኖሩ አንዱ ጠመንጃ ሁለተኛዉ የኛ የነጻነት ኃይሎች መበታተን ብቻ ነዉ።
ነገ የምንፈልጋት ኢትዮጵያ እንደ መኪና ተገጣጥማ አትጠብቀንም – የዛሬዉ ጥረታችንና ድካማችን ዉጤት ናት። ኢትዮጵያና ህዝቧ ከወያኔ ሲፀዱ የሚነፍሰዉ የነጻነት አየር ሁላችንንም ቢያስደስትም ደስታዉ የሚገለጸዉ በግለሰብ ደረጃ ነዉ። ዛሬ ከጠላት ጋር ተፋልመን የተቀማነዉን ነፃነት ማስመለስና እንደገና እንዳንቀማ ነቅቶ መጠበቅ ግን የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት ነዉ። እንግዲህ ወገን ወገባችንን ጠበቅ የምናደርግበት ግዜ አሁን ነዉና ሁላችንም በየተሰለፍንበት መስክ እንበርታ። ጠላታችን ጠንካራ መስሎ የሚታየዉና ያለ የሌለ ጡንቻዉን የሚያሳርፍብን የማይቀረዉን ድል ማሽተት ስንጀምር ነዉ። የድል መአዛችንን የምናሸትበት ግዜ ደግሞ ሩቅ እንዳይመስለን ነገና ከነገ ወዲያ ነዉ። ከወላዋይና እዚህም እዚያም እየዘለለ ከሚያዘናጋን አጉል ጓደኛ አንዱኑ የለየለት ጠላት ይሻላልና የሞላ አስገዶም ክህደት ትግላችንን ሊያጠራዉና መንገዳችንንም ሊያሳጥረዉ ይገባል እንጂ በፍጹም ግራ ሊያጋባን አይገባም። አይዞን. . . ሞኝ ከዘመዱ ከሚያገኝዉ ጥቅም አዋቂ ከጠላቱ የሚያገኘዉ ጥቅም ይበልጣልና ጠላቶቻችን የፈጠሩልንን አጋጣሚዎች ሁሉ በሚገባ እንጠቀምባቸዉ እንጂ ለጠላት አንመቻች። ጠላታችን እየተሳሳተልን ነዉ፤ ጠላት ሲሳሳት ማቋረጥ ነዉር ነዉ። ቸር ይግጠመን!!!
አፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር ebini23@yahoo.com

በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል የሕወሃት/ብአዴን ታጣቂዎች 2 ነዋሪዎችን ገደሉ፣ ከ50 በላይ አቆሰሉ

September 23,2015

picture

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ሕወሃት) የፈጠረው የብአዴን ታጣቂዎች በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል ሁለት ነዋሪዎችን መግደላቸው፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው እንዲሁም ከሃምሳ በላይ ማቁሰላቸው ተሰማ።
የብአዴን አባላት እና መሪዎች የዐማራን ሕዝብ እያሰቃዩ እና እያስፈጁ የሚያካብቱት ማንኛውም ሃብት በክህደትና በግፍ የተሰበሰበ በመሆኑ ለህዝብ የሚያስረክቡበት ግዜ ሩቅ አይደለም።
pictureለዚህ የክህደት ተግባራችው ተገቢውን ቅጣት ያገኛሉ፣ በባህርዳር እና በጎንደር በሰፊው እየተሳሳቡ አገር እየዘረፋ መሆኑን እያንዳንዷንም ተግባራቸውንም እየተከታተልን ዝርዝር ይፋ እናደርጋለን።
እነኝህ ስግብግቦች በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ ምክንያት በተፈጠረው ግጭት፣ የሕወሃት ብአዴን ታጣቂዎች ሁለት ነዋሪዎችን ሲገድሉ፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ከአምሳ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል። (ምንጭ፦ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት Dr.Getachew Reda ጠቅሶ መስከረም ፱ ቀን ፪ሺህ፰ ዓም የላከው መረጃ)

Tuesday, September 22, 2015

Ethiopia: Activists Heading for Food Workshop Charged With Terrorism

September 22, 2015

World Bank Translator, Activists Face Trial

Human Rights Watch
(Nairobi) – Ethiopian authorities should immediately drop all charges and release a former World Bank translator and two other local activists charged under Ethiopia’s repressive counterterrorism law after trying to attend a workshop on food security in Nairobi, six international development and human rights groups said today.
Pastor Omot Agwa was charged by Ethiopian authorities
Pastor Omot Agwa was charged by Ethiopian authorities under the anti-terrorism law after being detained for nearly six months.
© Dead Donkeys Fear No Hyenas / WG Film
On September 7, 2015, the authorities charged Pastor Omot Agwa, Ashinie Astin, and Jamal Oumar Hojele under the counterterrorism law after detaining them for nearly six months. The charge sheet refers to the food security workshop, which was organized by an indigenous rights group and two international organizations, as a “terrorist group meeting.” The three were arrested on March 15 with four others while en route to the workshop in Nairobi, Kenya. Three were released without charge on April 24, and a fourth on June 26.
“Ethiopia should be encouraging debate about its development and food security challenges, not charging people with terrorism for attending a workshop organized by respected international organizations,” said Miges Baumann, deputy director at Bread for All. “These absurd charges should be dropped immediately.”
Omot, of the evangelical Mekane Yesus church in Ethiopia’s Gambella region, was an interpreter for the World Bank Inspection Panel’s 2014 investigation of a complaint by the Anuak indigenous people alleging widespread forced displacement and other serious human rights violations in relation to a World Bank project in Gambella. He had raised concerns with workshop organizers about increasing threats from Ethiopian security officials in the weeks before his arrest.
The food security workshop in Nairobi was organized by Bread for All, with the support of the Anywaa Survival Organisation (ASO) and GRAIN. Bread for All is the Development Service of the Protestant Churches in Switzerland. ASO is a London-based registered charity that seeks to support the rights of indigenous peoples in southwest Ethiopia. GRAIN is a small international nonprofit organization based in Barcelona, Spain that received the 2011 Right Livelihood Award at the Swedish Parliament for its “worldwide work to protect the livelihoods and rights of farming communities.”
The objective of the Nairobi workshop was to exchange “experience and information among different indigenous communities from Ethiopia and experts from international groups around food security challenges.” Participants from Ethiopia were selected by ASO based on their experience in supporting local communities to ensure their food security and access to land.
The charge sheet accuses Omot of being the co-founder and leader of the Gambella People’s Liberation Movement (GPLM) and communicating with its leaders abroad, including ASO Director Nyikaw Ochalla, who is described in the charge sheet as GPLM’s London-based “senior group terrorist leader.” Omot faces between 20 years and life in prison. Ashinie is accused of participating in the GPLM, including communicating with Nyikaw and preparing a research document entitled “Deforestation, dispossession and displacement of Gambela in general and Majang people in particular.” Jamal Oumar is accused of being a participant of a “terrorist group” and of organizing recruits to attend the Nairobi workshop.
The GPLM is not among the five organizations that the Ethiopian parliament has designated terrorist groups. It is an ethnic Anuak organization that fought alongside the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) to oust the repressive Derg regime in the 1990s, and was folded into the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) power structure in 1998. Currently the GPLM has no public profile, no known leadership structure, and has not made any public statement of its goals.
“For the government to make criminal allegations against me because I assisted in coordinating a workshop about land and food issues in Ethiopia is simply incredible,” said Nyikaw Ochalla, ASO executive director. “Trying to give indigenous people a voice about their most precious resources – their land and their food – is not terrorism, it’s a critical part of any sustainable development strategy.”
All three detainees were recently moved to Kalinto prison, on the outskirts of the capital, Addis Ababa, after spending more than five months in Maekelawi, the Federal Police Crime Investigation Sector in the city. Human Rights Watch and other organizations have documented torture and other ill-treatment at Maekelawi. Omot, and possibly the other two, were held in solitary confinement for three weeks upon their arrest, and all have had limited access to family members. Jamal and Omot have reportedly been in poor health.
The detainees were held 161 days without charge, well beyond the four months allowed under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation, a period in violation of international human rights standards and among the longest permitted by law in the world. The next hearing in the case is scheduled for October 22, 2015.
Since 2011, Ethiopia’s counterterrorism law has been used to prosecute journalists, bloggers, opposition politicians, and peaceful protesters. Many have been accused without compelling evidence of association with banned opposition groups.
In August 2015, 18 leaders of protests by the country’s Muslim community were convicted and sentenced to between 7 and 22 years in prison. The ongoing trial of the members of a group called Zone 9 bloggers has been adjourned 36 times.
Human Rights Watch and other organizations have documented numerous incidents in which individuals critical of Ethiopia’s development programs have been detained and harassed, and often mistreated in detention. Journalists have been harassed for writing articles critical of the country’s development policy.
“These three men are the latest victims of the Ethiopian government’s crackdown on independent activists,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The arrests, lengthy detentions, and spurious terrorism charges bear all the hallmarks of Ethiopia’s effort to silence critical voices.”
The organizations seeking the release of Omot, Ashine, and Jamal are:
Human Rights Watch
Bread for All
GRAIN
Anywaa Survival Organization
Oakland Institute
Inclusive Development International
Case of Pastor Omot Agwa
In February 2014, Omot acted as interpreter and facilitator for the World Bank Inspection Panel during its visit to Gambella to investigate a complaint brought by former Gambella residents concerning the bank’s Protection of Basic Services (PBS) program. The program funded block grants to regional governments, including paying salaries of government officials.
The former residents alleged that the program was harming them by contributing to the government’s abusive “villagization” program. The program forcibly evicted indigenous and other marginalized peoples from their traditional lands and relocated them to new villages. In its report to the World Bank board of directors, which was leaked to the media in December 2014, the Inspection Panel concluded that the bank had violated some of its own policies in Ethiopia.
In February 2015, the World Bank board considered the Inspection Panel’s recommendations. Shortly thereafter, Omot reported that he was under increasing pressure from Ethiopian security personnel. While the Inspection Panel had not disclosed Omot’s identity in its report, it included a photograph of him with other community members, which was removed from subsequent versions. The week before his arrest, several people told Omot that a well-known federal security official from Gambella was looking for him.
On March 15, Omot texted an emergency contact that security officials at Addis Ababa’s international airport had detained him and the six others as they were heading for the workshop in Nairobi. Several days later, a witness saw four armed federal police officers and four plainclothes security officials take Omot, in chains, to his house in Addis Ababa, where they removed computers, cameras, and other documents.
The seizure of Omot’s computers and other materials raises concerns about the security of other Gambella community members the Inspection Panel interviewed. Given the severe restrictions on human rights investigation and reporting in Ethiopia, it is virtually impossible for rights groups to learn about reprisals in the villages the Inspection Panel visited.
Within days of Omot’s arrest, Human Rights Watch and other organizations alerted the World Bank Group president, Jim Yong Kim, and the European Union, United States, and Swiss missions in Addis Ababa. But on March 31, the World Bank board approved a new US$350 million agriculture project in Ethiopia. On September 15, the World Bank approved a $600 million Enhancing Shared Prosperity through Equitable Services project, which is replacing one of the subprograms of the PBS program.
World Bank staff assert that they have privately raised the case with Ethiopian government officials, but the nature of any communications is unclear. In a May meeting with nongovernmental organizations in Washington, DC, World Bank staff said that the government had informed them that Omot’s arrest was in accordance with Ethiopian law and unrelated to the bank’s accountability process.

Monday, September 21, 2015

የወያኔን ስርዓት በመቃወም በርካታ ወጣቶች የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ድርጅትን ተቀላቀሉ።

Sebtember 21,2015

hadesti
በዚህ ሳምንት ውስጥ የህወሃት ኢ.ህ.አ.ዴ.ግን ስርዓት በመቃወም በርካታ ወጣቶች ወደ ትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ድርጂት መቀላቀላቸውን ከማሰልጠኛ ማዕከል የደረሰን መረጃ አመለከተ።በደረሰን መረጃ መሰረት የወያኔን ከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በመቃወም በርካታ ወጣቶች ወደ ማሰልጠኛ ማዕከል መቀላቀላቸውን የገለፀ ሲሆን የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያህል
1 ተክላይ ታፈረ ገብረዋሂድ ከትግራይ ማዕከላዊ ዞን ናዴር አዴት ወረዳ አዲ ላኪያን ቀበሌ አዲ በዛ አካባቢ
2 በሪሁ ገብረየሱስ ሃድጉ ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ጉሎ መከዳ ቀበሌ አዲስ ተስፋ ሰፈር ደንጎሎ ከተባለው መንደር
3 ነፀረ-አብ አባዲ ፍስሃ ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ታህዳይ አድያቦ ወረዳ ገመሃሎ ቀበሌ ሁመር ከተባለው ሰፈር
4 ፍስሃ ገብረስላሴ ገብረ መድህን ከማዕከላዊ ዞን አህፈሮም ወረዳ ቤተ ገበዝ ቀበሌ ዝባን እንዳቦይ ገብራት ከተባለው አካባቢ
5 ጉዑሽ ሃይለ ገብረስላሴ ከስሜን ምዕራብ ዞን ታህታይ ቆራሮ ወረዳ ማይ አድራሻ ከተባለው ቀበሌ
6 አወት ገዛኢ ፈዳይ ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ጉሎመከዳ ወረዳ ዛላንበሳ ከተማ
7 ክብሮም ገብረ ፃድቅ ረዳ ከማዕከላዊ ዞን መረብ ለኸ ወረዳ አድፍታው ቀበሌ አዲ ቀረዲሂም ከተባለ መንደር
8 በሪሁ አብረሃ ተላ ከትግራይ ደቡባዊ ዞን አምባላጀ ወረዳ ስስት ቀበሌ ከታረ ከተባለው ሰፈር
9 በረከት ገብረ ኪዳን ወልደማሪያም ከትግራይ ማኦከላዊ ዞን ናአዴር አዴት ወረዳ አዲ ለኪያን ከተባለው ቀበሌ
10 ሚኪኤሌ ካህሳይ በርኸ ከትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ታህታይ አድያቦ ወረዳ አዲ ፀፀር ከተባለው ቀበሌ
11 ፀጋይ ሃፍታይ ከምስራቃዊ ዞን ክልተ አውላሎ ወረዳ ፅጌረዳ ቀበሌ
12 ከድር ወህበይ አብራር ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ታህታይ ቆራሮ ወረዳ አድ ብዘት ከተባለው ቀበሌ ብዘት አካባቢ እምቢሉ ከተባለው መንደር
13 ሃጎስ ገብረ ዮሃንስ ንጉሴ ከማዕከላዊ ዞን መረብ ለኸ ወረዳ አወት ቀበሌ
14 ግደይ ወልደሚካኤል ወልደማሪያም ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ሽረ ወረዳ ሰመማ ቀበሌ
15 አሸናፊ ገብረየሱስ ወልዱ ከምስራቃዊ ዞን ጉሎ መከዳ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ አዲ ገናህ ከተባለው አካባቢ
16 ዘነበ አለም ገብረ ሚካኤል ከሰሜን ምዕራብ ታህታይ አድያቦ ወረዳ ባድመ ቀበሌ
17 ገብረ ሂወት ጉዕሽ ገብረ መስቀል ከማዕከላዊ ዞን መረብ ለኸ ወረዳ ራማ ቀበሌ ሰፈር 03
18 መብርሃቶም ሃዲሽ ተክለ ከሰሜን ምዕራብ ዞን ላእላይ አድያቦ ወረዳ አድክልተ ቀበሌ ገዛ ስቃ ከተባለው መንደር
19 ክብሮም ተሾመ ክንፈ ከማዕከላዊ ዞን መረብ ለኸ ወረዳ ማይ ወዳምበራይ ቀበሌ አዲገባ እና ሌሎችም ሲሆኑ በተለይ ፍስሃ ገብረ ስላሴ ስርዓቱን እንዲቃወም ያስገደደውን ምክንያት ሲናገር ስርዓቱ አገዛዙን ለማስረዘም ሲል ብድር በመስጠት ሞዴል ተሸላሚ ናችሁ ብሎ ሲያበቃ እንደገና ተገልብጦ በተላላኪዎቹ ተጠቅሞ አቶ ገብረእግዜር ጋዕሲ የተባለውን ንፁህ ዜጋ የቀፎ ንቡን በማላታይን ሲያጠፉ በማየቱ መሆኑን ገልፀዋል።
ሰልጣኝ ጉዕሽ ሃይሉ ገብረስላሴ በበኩሉ ባለፈው ምርጫ አረና የተባለውን ድርጂት የመረጡ ዜጎች ከመሬት እደላ እንደተከለከሉ ከገለፀ በኋላ ቀደም ሲልም በብድር የተሰጡ ወገኖችን ጊዜው ሳይደርስ መልሱ እያሉ እያሰሩ ያሰቃዩአቸው እንደነብር ገልፀዋል።

Sunday, September 20, 2015

Anyway you shake-it-or-bake it; the struggle is between criminals and the innocent

September 20, 2015
“A lie gets halfway around the world before the truth has a chance to get its pants on”
by Teshome Debalke
Let’s not lose sight and be diverted. Anyway we shake-it-or-bake it, the struggle for justice, freedom and democracy remains between criminals and the innocent.
If the rule of law is not supreme as it is a mob rule in Ethiopia there is no government but a criminal syndicate posed as a government with smalltime assassins that sworn to uphold the mob rule against the innocent people of Ethiopia.
Therefore, you can put a lipstick on it or cross-dress it to look whatever you want to make it look like and clip and paste pictures and videos of wherever your criminal imagination would take you, Woyane is still a criminal syndicate that sooth the unlimited appetite of those that eat their own roots to fulfill someone else’s wishes.
Do we need a PhD to figure out these simple ABC facts to run around making so much background noise to agree who is criminal and who is the innocent?
That question was answered over-and-over again and no need to dwell on it. Even the criminal syndicate- and apologists accept that reality and agonizing over not innocence but by arguing others are as equally criminal if not more as the reason to sustain the mobs in Arat Kilo. How convenient.
The phrase ‘Little knowledge is dangerous’ often associated with 18th-century English poet Alexander Pope once again came to bit us in the latest episode of video clipping-pasting regime of Woyane.
It reminds me Winston Churchill saying; “A lie gets halfway around the world before the truth has a chance to get its pants on” and it did. I believe liars are better organized than truth-tellers and you can quote me on it. That is what happen in the latest lies that broke the speed of light with one Woyane defecator named Molla greatest escape story in three separate countries
Look my people; most of us travel by plane in different cities with the hassle of modern life and often takes too much time, overnight stay; stranded in strange places with all the hassle that comes with it. But, to see a man crisscrossing nations — shooting his way out at ease makes ISIS’s advance in North Iraq and Syria a child play, to use the infamous mouthpiece Minster Berket Simon’s word.
There is no question we are under organized criminal syndicate regime. Not even Woyanes deny that reality from their hiding. We are distracted with so many liars associated with The Mob in Arat Kilo we lost sight of who-is-who and where to begin to catch them. Instead, we rely on those that sacrifice to round them up and seat and wait to react when they are badgering Ethiopians like members of Patriotic-Ginbot 7 Movement for justice, freedom and Democracy.
We don’t have to support or like Patriotic-Ginbot 7 or anyone group or another to bring about Justice, Freedom and Democracy to our people. Unless we are against justice, freedom and democracy I don’t see why we oppose those that try. For instance, the justice system under the Mob regime is what makes and breaks freedom and democracy. Without freeing it we will never see freedom and democracy. Instead of waiting for someone to do it for us; we can help the struggle by helping identify who-is-who depriving our people justice and go after them.
It reminds me an African Proverb that says ‘Corn can’t expect justice from a court composed of chickens.’
Why are we waiting for others to find out who are the ‘Chickens’ eating our corn faster than a rabbit eats a salad to do something about it?
President as Tigne Getaneh You will be surprise to find out the ‘Chickens’ eating our ‘corn’ are playing hide-and-seek like gorillas in the jungle to ambush us where ever you look. Wikipedia has an empty page with only Birtukan Mideksa listed as the only judge under Ethiopian judges. You would think the Mob Regime by will tell us who the judges running the justice system — from the Supreme Court to lower courts. Good luck; the Ministry of Justice doesn’t name them. We might as well call it the Ministry of Chickens-gorillas eating our corn faster than we can grow them. The Federal Court website identifies the President as Tigne Getaneh (pictured) leave all the Supreme Court, The High Court and First Instance Courts’ judges blank-hiding in their chambers.
As far as the President of the Federal Court that is responsible for running the court system concerned the judges are on an under cover mission to fight Ethiopian terrorist as the Medias are in reporting on Ethiopian terrorist. By the way there is money to make Ethiopians terrorist. If you see the Woyane record if money is to be gained it will find unborn terrorist in the womb.
Here is the message of the President that wouldn’t provide the names and the background of the seating Federal Judges (chickens) of Ethiopia.
“ህብረተሰቡ መረጃን ከፍርድ ቤቶቻችን በተለያዩ መንገዶች ሊያገኝ የሚችል ሲሆን በድረ ገጽና በሰው አልባ የስልክ አገልግሎት መረጃን ለማስተላለፍ በተደረገ ጥረት ጥሩ ጅምሮች እየታዩ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት አገልግሎቶች ላለፉት 3 ዓመታት በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሙከራ ላይ የቆዩ ሲሆን አሁን የማስፋፊያ ሥራዎች ተካሂደው ሦስቱም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አገልግሎቶቹን እየሠጡ ነው፡፡ በዚህ ድረ ገጽ የተሟላ መረጃ ማግኘት የሚቻል በመሆኑ ህብረተሰቡ በአገልግሎቱ እንዲጠቀም እየጠየቅሁ ሊታረሙ የሚገባቸውንም ሆነ ሌሎች በማሻሻያ ሥራዎቹ ላይ ያሉ አስተያየቶችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናችንን በአክብሮት እገልጻለሁ፡፡ “
The website has more blank pages than pages with content and only in Amharic; so much for justice. Should we call it the Federal Gorilla Court?
The Gorilla judges are not there to dispense justice but, to cover up for the Mob in Arat Kilo. We can identify them and go after them wherever they may be hiding one by one. Isn’t that what the struggle for justice is all about?
The same goes with the Gorilla Media establishments infested with the regime syndicates clipping-pasting picture and video to make the Mob in Arat Kilo look good.
We saw what the rapid deployment Media Ethiopia First did to undermine the struggle this week. To many surprise; we also saw how veteran Medias like EthioMedia and Ethiopian Review scramble for the piece of the action of the cooked video — clipping and pasting to spin their own imagination to undermine the struggle in their own way.
Couldn’t at least shame them as few did in writing to restrain their behavior? I think they should be invited on ESAT to face Ethiopians.
But, there is more to the Medias than what you think. The Mob regime not only runs the entire Media establishment in Ethiopia but it outsource its video and film production to an outfit by the called Akirma Media Inc, a Toronto, based ‘multimedia and film production’ company established in 2001, according to its website with unidentified individuals with Addis Ababa phone: 251-91-2004594..
The outfit says it “works with the Government of Ethiopia to improve the production quality of ERTA’s (Ethiopian Radio and Television Agency) training journalists in various Ethiopian public media entities including: Tigray Mass Media Agency, Amhara Mass Media Agency, Oromiya Radio and Television Agency, Southern Nations and Nationalities Mass Media Agency, Ethiopian News Agency, Addis Ababa Mass Media Agency and the Federal Police and Defense media departments”, according to its website. It reviles the extent the Mob regime in Arat Kilo and associates in Toronto control the nation Media. Talk about multinational Media of corruption. Why do I have a feeling Ben of Ethiopia First and his gorilla associates run this outfit that clip-and-paste propaganda video undermining the struggle?
Well let’s find out. The servers (bluenile.com http://www.bluenilehost.com) that host Ethiopia First also host Aend Ethiopia (http://aend-ethiopia.com), the infamous radio in the Washington DC area along the host of others including Admas TV run by Akirma Media Inc, go figure.
Akirma Media training government journalists
Akirma Media training government journalists in Ethiopia Photo: Akirma website (who is unidentified person?
No wonder Ben the Gorilla reporter is running from his Toronto to his Addis Ababa office to make sure to report for us terrorist activities sponsored by Shabia. We have to be grateful for Woyane for making ‘terrorist’ surrender with their full gear. The world can learn from Woyane how to fight terrorist as one Woyane expert by the name Mehari declared on Aljazeera.
The damage the fragmented Diaspora Media that are causing havoc in our community is not helping to identify Woyane’s gorilla Medias with no one setting the standard. But, the Gorilla Medias directly associated with the Mob in Arat Kilo regime like Ben of Ethiopia First and their hosts Akirma are by far dragging the struggle from achieving its goal.
Why are the people running Akrima Media hiding like gorillas in Manila explains why our community in Diaspora and the people at home are confused with elaborate propaganda concocted by the mob in Arat Kilio and their Media and Film Production outfit of Toronto and elsewhere.
Isn’t about time the struggle open multiple fronts to free the justice, the Media… while the ground front clean out the Mob in Arat Kilo?
Let’s face it, if you are in the Media and hiding, what are you; a gorilla or a journalist? I don’t even have a fake diploma I can tell the difference. You mean all these PhDs preaching growth and transformation bull couldn’t figure out we got gorilla judges, journalists…depriving the people of Ethiopia justice, freedom, and democracy and they blame Patriotic-Ginbot 7 ? What is this; a Mob assassin free ride.
My people; there is dumb and dumb but, I never heard of the dumbest excuses coming out of Woyanes since TPLF said it is not Ethiopia to come back and say it is more Ethiopian than the Ethiopians.
As I said; any way you shake it or bake or paste ethnicity, religion, terrorism or Shabia on it; the struggle is between criminals and the innocent. Do I have to tell you who-is-who?
Wouldn’t it be smart if Woyane surrender and ask forgiveness from Ethiopians instead of hiding behind Shaibia and killing Ethiopians again?
Face it, Woyane can‘t shoot, steals and lies its way out of the problem. I am 100% sure of that. Therefore, those that participate in one or more of its crimes on the expenses of our people are better off to good bye my beloved Woyane and get over it. The must accept the reality with a grain-of-salt now than later.
By the way, where is ‘General’ Siye Abraha when we need him most? Is the Woyane’s version of the rank of General only good to kill Ethiopians not to save us? Go figure, no one want to take responsibility but hide. What is up with that?
If history is a lesson; when Ethiopians say no, it means no.
This article is dedicated to Brother Andargachew Tsege. Your sacrifices assured you are the true son of Ethiopia. No one let alone Woyane will take that away from you.

Friday, September 18, 2015

ህወሃት ጦርነት ጀመረ፣ ቁስለኞች ታይተዋል

September 18,2015

“ሕዝብ አስፈቅደን ውጊያ እንጀምራለን” ሃይለማርያም
omhajer

በነጻ አውጪ ስም አገር እየገዛ ያለውን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃትን) ለመውጋት ብረት ያነሳው ሌላ የትግራይ ነጻ አውጪ ሃይል /ትህዴን ወይም በትግሪኛ ዴምህት/ መሪ የነበረው “ተጋዳላይ” ሞላ አስገዶም ህወሃትን ከተቀላቀለ ጥቂት ቀናት በኋላ ጦርነት መጀመሩ ተሰማ። የህወሃት ወኪል ሃይለማርያም ደሳለኝ ውጊያው የሚጀመረው የህዝብ ፈቃድ ተጠይቆ እንደሚሆን ተናግረው ነበር።
የጎልጉል መረጃ አቀባዮች ከአዲስ አበባ እንደገለጹት ጦር ኃይሎች ሆስፒታል ቁስለኞች እየገቡ መሆኑንን እማኞች ነግረዋቸዋል። ጦርነቱ በየትኛው መንደርና ወረዳ እንደተጀመረ ለይተው ያላስረዱት የዜናው ባለቤቶች፣ ውጊያ እየተካሄደ ያለው ኤርትራ ምድር ላይ እንደሆነ ግንአልሸሸጉም።
አንድ የሆስፒታል ሰራተኛ ዘመድ ደውሎላቸው “ቁሰለኞች አሉ ሥራ በዝቶብኛል” ማለታቸውን የጎልጉል መረጃ ሰጪዎች ከአዲሰ አበባ ገልጸዋል። ባለፈው ሳምንት በሁመራ አቅጣጫ የከባድ መሳሪያ ተኩስና ድብደባ መሰማቱን የተለያዩ ድረገጾች ዘግበው ነበር። ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት ሻእቢያ “ህወሃት ሊወረኝ ነው” ሲል ክስ ማሰማቱ አይዘነጋም።
ኦምሃጀር በሚባለው ስፍራ የከረረ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን እንደሰሙ የገለጹ በውጊያው የትኛው ወገን ድል እንደተቀዳጀ ለጊዜው መናገር እንደማይቻል አመልክተዋል። ውጊያው ጠርዙን አስፍቶ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
four front mapከህወሃት በኩል ውጊያው ከሻዕቢያ ጋር እንደሆነ ቢገለጽም ከሌላ ወገን “ህወሃትን የወጋሁት እኔ ነኝ” ባይ ይህ ዜና እስከታተመ ድረስ አልተሰማም። የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ህወሃትን በነፍጥ አንበረክካለሁ በማለት ማወጁና አመራሮቹም ወደ ውጊያው አውድ ማምራታቸው ይታወቃል። ህወሃት ኤርትራን በአራት አቅጣጫ የመውጋት እቅድ እንዳለው ጎልጉል መዘገቡ የሚታወስ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በርካታ የሰራዊቱ አባላት ከሰራዊቱ እየሸሹና እየተሰወሩ መሆናቸው ህወሃትን እንዳሳሰበው፣ ጦሩ የመዋጋት ፍላጎት ያጣል የሚል ሥጋት እንዳለ የሚጠቁሙ ክፍሎች “የአሁኑ የውጊያ አቅጣጫ በዚህ መልኩ እንዲሆን መደረጉ ይህንኑ ለመፈተንም ጭምር ነው” ብለዋል።
በሌላ ዜና በሶማሌ ያለው ሰራዊት የመመለስ ጥያቄ ማንሳቱና ሁለት ጄኔራሎች ጦሩን ለማወያየት ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ስፍራው አቅንተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ጦሩ መስዋዕትነት እየከፈለ በተደጋጋሚ የተቆጣጠረውን ቦታ እንዲለቅ ትዕዛዝ ሲቀበል መቆየቱ ሌላው የቅሬታው መነሻ ሲሆን በሶማሌ ያለው የሰላም አስከባሪ ሃይል ይህንኑ ነቅፎ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል። በህወሃት የሚመሩት የኢህአዴግ ባለስልጣናት በሶማሌ ስለተገደሉት ወገኖች መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ይህንን አክርረው አለመጠየቃቸው፣ ላለፉት አምስት ዓመታት 99.6 በመቶ ህወሃት የነገሰበት ማኅበርም (ፓርላማ) ለይስሙላ እንኳን ጥያቄ አቅርቦ እንደማያውቅ በርካቶች የሚተቹበት አገራዊ ጉዳይ ነው።

ከጎልጉል የተወሰደ