Friday, November 13, 2015

ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!

November 13,11 2015
“ህይወት ለማትረፍ በቅድሚያ መተማመን”
drought and hope

* ከአገዛዝ ለውጥ በፊት ችጋር ይቀድማል?
* “በአሁኑ ጊዜ ችጋሩ እንደ 1977 ሆኗል!”
በኢትዮጵያ ላለፉት ፴ ዓመታት ያለታየ ችጋር ተከስቷል። ድርቁና ረሃቡ ከዚህም በላይ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ኢህአዴግን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይፋ እያደረጉ ነው። “የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ” በማለት ሲወተውት የኖረው ህወሃት ተገዶ ያመነው ችጋር ከ፩፱፯፯ ድርቅ በላይ የከፋ እንደሚሆን ስጋት አይሏል። ከዚህ በፊት እንደተከሰቱት ለውጦች ይህኛውም የአገዛዝ ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ተነገረ። በአስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
ህወሃት ከድርቅ እና ድርቅን ተከትሎ ከሚገኝ ዕርዳታ ጋር በተያያዘ ካለው አስጸያፊ ተሞክሮ በመነሳት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ከድርቁ ጋር በተያያዘ ፍትሐዊነት ያሳስባቸዋል፡፡ ሲያብራሩም በከፍተኛ የሙስና እና የአድልዖ ወጥመድ ውስጥ መዘፈቁን ራሱ ያመነው ህወሃት የሚመራው አገዛዝ ችጋር በመታቸው ወገኖች ስም የሚመጣውን የውጭ ምንዛሪ በአግባቡ ሥራ ላይ የማዋል አቅምም ሆነ ተዓማኒነትም በጭራሽ የለውም ይላሉ፡፡ መለስ “እስከ እንጥላችን ገምተናል” ያሉትንና በቅርቡ ደግሞ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ሕዝብ ያውቀናል፤ አያምነንም፤ ቀበሌ እንኳን ስብሰባ መጥራት አንችልም” በማለት የተናገሩትን ለአብነት ይጠቅሳሉ፡፡ ራሱ “አልታመንም፤ ሌባ ነኝ” እያለ የሚለፍፍ አገዛዝ እንዴት በረሃብ ለተጠቁ በፍትሐዊነት ዕርዳታ ያደርሳል በማለት ይጠይቃሉ?
እነዚሁ ክፍሎች የሚሉትን በመደገፍ ስማቸውን ያልገለጹ የኢህአዴግ ዲፕሎማት እንዳሉት ከሆነ አንድ ከፍተኛ ብሔራዊ መነቃቃት ካልተፈጠረ ኢህአዴግና ካድሬዎቹ ሕዝብን በማነቃነቅ ችግሩን በፍትሐዊ መንገድ ሊፈቱት እንደማይቻላቸው እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ዲፕሎማቱ የኢህአዴግ ሎሌ ቢሆኑም የህወሃት የበረሃ ውጤት ስላልሆኑ ህወሃት በበረሃው ተሞክሮ በዕርዳታ እህል ስም እያጭበረበረ ስለዘረፈው ገንዘብ ሲያስቡ አሁንም ይዘገንናቸዋል፡፡
ኢህአዴግ “ብሔራዊ” በሚል የሚጀምሩ ሕዝባዊ ንቅናቄዎችን የመውደድ ባህርይ ባይኖረውም፤ የተፈጠረውን ድርቅና ችጋር አስመልክቶ በጋራ ለመሥራት የግድ ይህንን ማድረግ እንደሚገባው የሚጠቁሙ ክፍሎች ህወሃትና ድርቅ ያላቸውን የጠነከረ መሳሳብና ግንኙነት መረጃ በማጣቀስ ያስታውሳሉ፡፡eTHIOPIA-worst-drought-of-africa-in-60-years
በተገንጣይ ስም ራሱን የሚጠራውና የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) የሚገዛት ኢትዮጵያ “በልማት ተጥለቅልቃለች፣ ልማት ላይ ነን” እየተባለ ቢዘመረላትም በውል የታየው ግን ሌላ ነው። ለዝርፊያው ሽፋን የሚለፈፈው የልማት ቀረርቶ ችጋር የሚያቃጥላቸውን ህጻናትና አረጋዊያን አንድ ወር እንኳን መታደግ የሚችል አቅም አልፈጠረም። ለምርጫ ዘመቻ ሲባል ተደብቆ የነበረው ችጋር ይፋ ሲሆን የታየው እውነት የመሰከረው ሃቅ ቢኖር አገሪቱ በባዶ ቀረርቶ እየደነቆረች መሆኑን ነው።
ህወሃት ሥልጣን ላይ በቆየበት ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ ችጋር ከመከሰቱ አንጻር ጉዳዩን የሚመለከቱ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ እንደታየው አስከፊው ችጋር የአገዛዝ ለውጥ ለማምጣት የራሱን የሆነ ከፍተኛ ሚና ተጫውቶ አልፏል፡፡ ይኸኛውንም ከዚሁ ጋር በመዳመር የለውጥ ማዕበል ሊያመጣ ይችል ይሆን የሚለው የመነጋገሪያ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ችጋሩን በግምባር የተጋፈጡ ነዋሪዎች አሁን ያለው የጠኔ ደረጃ እንደ 1977ቱ ዓይነት ነው ይላሉ፡፡ ከዚያም የሚያስበልጡት አሉ።
ህወሃት/ኢህአዴግ ለማድበስበስና ለመሸፋፈን የሚጥረው ችጋር ዓይኑን አፍጥጦ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እየተሰማ ነው፡፡ በመሆኑም በመጪው የአውሮጳውያን አዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ በችጋር የተመታው ሕዝብ ቁጥር 15 ሚሊዮን እንደሚደርስ የመንግሥታቱ ድርጅት አስታውቋል፡፡ ከዚህ ቁጥር ውስጥ ግማሽ የሚያህሉት ህጻናት እንደሆኑም ይገመታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ 8.2 ሚሊዮን ሕዝብ የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ እንደሚስፈልገው ይኸው የተባበሩት መንግሥታት ዘገባ ያስረዳል፡፡ ይህ አኻዝ ከስድስት ወር በፊት በችጋር ከተጠቃው በዕጥፍ እንዳደገ መረጃው ይጠቁማል፡፡ ይህም ህወሃት/ኢህአዴግ “ልማት፣ ውዳሴ፣ ህዳሴ፣ …” በማለት እንደ ጎበዝ ተማሪ መቶ በመቶ ያመጣበት “ምርጫ” ከመደረጉበፊት ነበር፡፡ በወቅቱ የችጋርና የድርቅ ጉዳይ አልተነሳም፤ የተፎካካሪ ፓርቲዎችም እንደሌላው ጉዳይ በቂ ሽፋን ሲሰጡበት አልታየም፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ “የጎበዝ ተማሪ” ሰርቲፊኬቱን ከተቀበለ፣ ከበሮውን ከደለቀ፣ ድግሱን ከደገሰ፣ መሸከም እስኪያቅተው ከበላና ከጠጣ በኋላ ከሰከረበት በቅርሻትና በግሳት ሲነቃ የመልካም አስተዳደር መጓደል፣ የድርቅና ረሃብ፣ የሙስና፣ … ጉዳዮችን ከዚህ በፊት እንዳልነበሩ አድርጎ ሕዝብ ሊያሳምን መሞከሩ ተቀባይነት እንደሌለው ለዝግጅት ክፍላችን አስተያየታቸውን የላኩ በአጽዕኖት የሚያስረዱት ነው፡፡
ሰሞኑን ከቪኦኤ ጋር በተደረገ ቃለ ምልልስ ቴድሮስ አድሃኖም “የህዝብ ቁጥር እጥፍ በመጨመሩ ፰ ሚሊዮን ህዝብ ቢራብ ፹ ሚሊዮኑ በአስተማማኝ ደረጃ በምግብ ራሱን ችሏል” በማለት መሳለቃቸው ይታወሳል። ከእንደ ቴድሮስ ዓይነቱ ችጋርን በቴሌቪዥን መስኮት ከመመልከት ያለፈ ዕውቀትና ርኅራኄ የሌለው ይህ መሰሉ የድንቁርና አነጋገር መሰማቱ የሚያስደንቅ እንዳልሆነ የሚናገሩ ወገኖች ቴድሮስ ለቪኦኤ የተናገሩትን ሃሳብ ሞት ካስፈነጠራቸው መለስ እንደኮረጁት ይናገራሉ፡፡ ሕዝብ በተራበ ቁጥር መለስ ዜናዊ ምክንያቱን ሲጠየቁ የሕዝብ ቁጥር በመጨመሩ እንደሆነ የመሃይም መልስ በመስጠት ተደናቁረው ሲያደናቁሩና ሎሌዎቻቸውን ሲያስጨበጭቡ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ መለስ የሥልጣኑን ኮርቻ መጋለብ እንደጀመሩም አምላካዊነት ተሰምቷቸው የኢትዮጵያን ሕዝብ በቀን ሦስት ጊዜ እንመግባለን ብለው የተነበዩት ወደ ዜሮ ወርዶ በሞት መቀደማቸው የአስተሳሰብ ብቻ ሳይሆን የምኞትም ደሃ መሆናቸውን ያረጋገጡበት እንደሆነ በርካታዎች የሚመሰክሩት ነው፡፡
ህወሃት ቃላት በማሳመርና ቁጥሩን በመቀነስ “የምግብ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው፣ የምግብ ዕጥረት የደረሰባቸው፣ …” በማለት ንብረቱ ባደረገው ሚዲያ ጉዳዩን አቃልሎ ቢያስወራም እውነታው ግን ሕዝብና እንስሳት በችጋር እየሞቱ መሆናቸው ነው በማለት በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ የግብርና ባለሙያ ተናግረዋል፡፡ ምናልባትም በጠኔ እየተቃጠለ ያለው ሕዝብ ብዛት ከተገመተው በላይ ሊሆን እንደሚችልና ጉዳቱም እጅግ አስከፊ እንደሚሆን እኚሁ ባለሙያ አስረድተዋል፡፡ በመንግሥታቱ ድርጅት ዘገባ መሠረት በቀን ቢያንስ ሁለት ህጻናት ይሞታሉ፡፡
አበራ ወልዱ የተባሉ የ60 ዓመት አዛውንት የግብርናው ባለሙያ የተናገሩትን ሃሳብ የሚያጠናክር አስተያየት መስጠታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ “ችጋሩ ገና ጅማሮ ቢሆንም እየከፋ ነው የሄደው፤ ገና ካሁኑ በጣም አስከፊ ሆኗል፤ ሰዎች እየሞቱ ነው፤ ሌሎች ሰዎችም (በችጋር ምክንያት) ታምመው አልጋ ላይ ወድቀዋል” በማለት አዛውንቱ ተናግረዋል፡፡ አክለውም “እንዲያውም አሁን ልክ እንደ 1977ቱ ችጋር ሆኗል” በማለት የሰጡትን ምስክርነት ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አገዛዝ ዘመን የተከሰተውን የወሎ ችጋር (የወሎ ድርቅ የሚባለውን) ለመደበቅ የተደረገው ሁኔታ ለንጉሣዊው አገዛዝ መውደቅ ክብሪት ከጫሩ ምክንያቶች እንደ ዋንኛው ይጠቀሳል፡፡ በወቅቱ ንጉሣውያን ቤተሰቦች ለንጉሡ ልደት በርካታ ገንዘብ በከንቱ እንዳባከኑ ደርግ የአጼ ኃይሥላሴን አገዛዝ ሲያማበትና ሲኮንንበት የነበረ ፕሮፓጋንዳ ነበር፡፡
Gebremedhin Araya (L) says he posed as a merchant, but was in fact a rebel
ከውጭ ዜጋው በስተቀኝ አቶ ገብረመድኅን አርአያ “ለሸጡት እህል” ገንዘብ ቆጥረው ሲቀበሉ::
ከላይ አቶ አበራ ወልዱ ያወሱት የ1977ቱ ረሃብ በተከሰተበት ወቅት ደርግ ለ10ኛው ዓመት የአገዛዝ ዘመኑን አገር ምድሩን በሰሜን ኮሪያ ብልጭልጭ ማድመቂያዎች “አስውቦ” ነበር፡፡ ይኸው ችጋር ለደርግ መውደቂያ ምክንያት ሲሆን በሌላ በኩል ለህወሃት ደግሞ ከፍተኛ የፖለቲካ እና የፋይናንስ “ዕድል” ከፍቶለት ነበር፡፡ በወቅቱ ለበዓሉ ድግስ የወጣው ወጪ ለተረጂ ወገኖች መዋል ነበረበት በማለት ህወሃት ከበረሃ ሲጮህ በተመሳሳይ መልኩ ለትግራይ ሕዝብ እህል መግዣነት የመጣውን ገንዘብ ህወሃት ለራሱ ማድረጉን የአሜሪካ የስለላ ድርጅት (ሲአይኤ) ማረጋገጡን ቢቢሲ ሲዘግብ የቀድሞ አባላቱም የድርጊቱን ትክክለኛነት አረጋግጠው ነበር፡፡
የዛሬ አምስት ዓመት አካባቢ በቢቢሲ ይፋ የተደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው በ1977 በተከሰተው አስከፊ ችጋር ምዕራባውያን ድርጅቶች እና ለጋሾች ወደ ኢትዮጵያ ለእህል መግዣነት እንዲውል የላኩት ገንዘብ የህወሃት ሹሞች ራሳቸውን በመደበቅ እህል ሻጭ መስለው በመቅረብ ከላዩ እህል ከሥሩ በአሸዋ የተሞላ ጆኒያዎችን እንዳረካከቡ በወቅቱ በሽያጩ ላይ የነበሩት የቀድሞው ከፍተኛ አመራር አባል አሁን በአውስትራሊያ የሚገኙት አቶ ገብረመድህን አርአያ አረጋግጠዋል፡፡ ቢቢሲ ባሰራጨው ፎቶግራፍ ላይ እንደሚታየው ሻጭ ሆነው የቀረቡት ገብረመድኅን ለሸጡበጥ ገንዘብ ቆጥረው ሲረከቡ የሚታዩት ራሳቸው መሆናችን ከመመስከር በተጨማሪ ሙስሊም መስለው በመቅረብ ጉዳዩን እንደፈጸሙም ተናግረዋል፡፡ የሸጡበትንም ገንዘብ ለመለስ ዜናዊና ለሌሎቹ የህወሃት አመራሮች ማስረከባቸውን ጨምረው አስረድተዋል፡፡ ቢቢሲ በጉዳዩ ላይ መለስን ቢጠይቅም እርሳቸው ግን ምንም ዓይነት አስተያየት ሳይሰጡ ጥቂት ቆይተው በዚያው አልፈዋል፡፡
በወቅቱ Christian Aid ከተባለው የዕርዳታ ድርጅት 500ሺህ ዶላር በብር ይዞ እህል ለመግዛት የመጣው ማክስ ፐበርዲ እንደሚለው ገንዘቡን ለእህል መግዣ እንዳዋለውና አንዳችም የዕርዳታ ገንዘብ ለሌላ ነገር እንዳልዋለ ቢናገርም ግብይይቱን የፈጸመው ግን ከከፍተኛ የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) አመራር ጋር እንደሆነ መናገሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ይህንን ተግባር አሁን በኔዘርላንድስ በስደት የሚገኙት የቀድሞ የህወሃት አመራር አረጋዊ በርሄም ያረጋገጡ መሆናቸው በወቅቱ የተዘገበ ጉዳይ ነበር፡፡ “የዕርዳታ ሠራተኞቹ ተሞኝተው ነበር” ያሉት አረጋዊ በርሄ እስከ 100 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ መገኘቱንና ከዚህ ውስጥ 95በመቶ የሚያክለው የጦር መሣሪያ ለመግዛትና ማርክሲስት ሌኒንስት ሊግ ትግራይ (ማሌሊትን) ለመገንባት ወጪ እንደተደረገ መስክረዋል፡፡
“ነጻ አወጣዋለሁ” ያለውን ሕዝብ የዕርዳታ እህል እንዳይደርሰው በማድረግ አሰቃቂ ግፍን የፈጸመው ህወሃት አሁንም ተመሳሳይ ተግባር ከማድረግ የሚቆጥበው ምንድነው በማለት የሚጠይቁ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በተለይ ችጋሩ ከበረታባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ በሆነው ትግራይ የሚገኙ ነዋሪዎች በከፍተኛ ሰቆቃ ውስጥ እንዳሉና ይህንኑ ችግራቸውን ከህወሃት ይልቅ ለአረና ሰዎች እና ለሌሎች ሊሰሟቸው ለሚችሉ እየተናገሩ እንደሆነ ከማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
eprdf homesየችጋር ሰቆቃ በአገሪቱ መከሰቱ እየታወቀ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት አገር ለማፍረስ የተመሠረተበትን 40ኛ የልደት ዓመት በዓል ሲያከብር 2 ቢሊዮን ብር ማውጣቱን እንዲሁም በትግራይ የዳያስፖራ ቀን ሲያከብር 200 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉን፤ “እጅግ ቅንጡ የሆኑ ዘመናዊ ቪላዎች ለስድስት የቀድሞ የኢህአዴግ ባለሥልጣናት በ154 ሚሊዮን ብር ተሰርተው” እየተጠናቀቁ መሆናቸውን፣ እንዲሁም “የህወሃት የአማርኛ ክፍል” የሆነው ብአዴን በህወሃት እንደ ጭቃ ተጠፍጥፎ የተሰራበትን 35ኛ ዓመት ለማክበር 300 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚሆን (ትክክለኛው ከዚህ ሊበልጥም ይችላል) በተሰማበት ሰሞን 15 ሚሊዮን ሕዝብ ለአስከፊ ችጋር መጋለጡን የዓለም ሚዲያ መዘገቡ “ችጋር ውድቀትን ይቀድማል” የሚለውን አባባል እያጠናከረው መጥቷል፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚለው ከሆነ የኢትዮጵያን ችጋር ለጊዜው ለመታደግ ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልጋል ብሏል፡፡ ችጋሩ በአገሪቱ የተወሰነ ብቻ ሳይሆን ከምስራቅ እስከ ሰሜን ዘልቋል፡፡ ሰሞኑን ከሚከሰተው ዝናብ ጋር በተያያዘ በጥቂቱም ቢሆን እየበቀለ ያለው ሰብል እንደሚወድም ይጠበቃል፡፡ ስለዚህ አሁን የሚታየው ሁኔታ “የምጥ ጣዕር መጀመሪያ” የሚባለው ሆኖ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ችጋሩ እየዘለቀና እየከረረ እንደሚሄድ በግልጽ የሚታየው ሁኔታና ሌሎች በርካታ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የመጨረሻውን የጠኔ ሳል ስለው ህይወታቸው የሚጠፋው ህጻናት ቁጥር በቀን ሁለት ብቻ ተወስኖ የሚቀር እንዳልሆነ በስፋት ይገመታል፡፡
ለተረጂው ወገን በዕርዳታ ስም የሚገባ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ዕጥረት ለሚንፏቀቀው ኢህአዴግ ታላቅ ገጸበረከት እንደሚሆን የብዙዎች ግምት ነው፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ የማይታመን ድርጅት የሆነው በሕዝብ ዘንድ ብቻ ሳይሆን ከከፍተኛ አመራሮቹ አንስቶ እስከ ቀበሌ ያለው እርስበርሱ አንዳች አመኔታ የለውም፡፡ በሙስና “መበስበሳቸውን” ደጋግመው በአደባባይ ይናገራሉ፤ ይደሰኩራሉ፤ ይመሰክራሉ፡፡ ስለዚህ “በመንግሥት ሌቦች” የተሞላው ኢህአዴግ የተረጂዎችን ገንዘብ የግሉ ከማድረጉ በፊት የዕርዳታውን አሰባሰብና ፍትሐዊ አሰረጫጨት የሚቆጣጠር፣ የሚመራና የሚያስተዳድር ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንዳለበት በአጽዕኖት የሚያምኑ ወገኖች ሃሳባቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ለግሰዋል፡፡ ይህ ግብረኃይል ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ፤ ህወሃት ባዋረደው “ሽምግልና” ያልቀለሉ፤ በዕድሜ ብቻ ሳይሆን በተግባራቸው “አንቱ” የተባሉ አገር ውስጥና ውጭ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መሆን እንደሚገባው አበክረው ይማጸናሉ፡፡ የአምስት ለአንድና መሰል የህወሃት አደረጃጀቶችን ለጊዜው ወደ ጎን ተደርገው ለሕዝብ ሲባል አስቸኳይ ውሳኔ ላይ ካልተደረሰ የችጋሩ ጉዳይ በትንሹም ቢሆን የቀረውን ክብራችንን አሟጥጦ በየሄድንበት ዕድሜ ልካችንን አንገታችንን የምንደፋበት እንደሚሆን በየዕለቱ በችጋር በሚሞቱት ህጻናት ስም ተማጽነዋል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ስለ “ውዳሴ፣ ህዳሴ፣ ባቡር፣ መንገድ፣ ፎቅ፣ ትልቅነትና ትልቅ መሆን፣ …” ሲደሰኮር ቢዋል መቀመጫን ገልቦ ፊት ከመከናነብ የማያልፍ ግብዝነት እንደሚሆንና ይህም ጊዜውን ጠብቆ ዋጋ እንደሚያስከፍል በእርግጠኝነት ይናገራሉ፡፡

Monday, November 9, 2015

ከትናንት በፊት የተቀሰቀሰው ጦርነት ሮቢት፣ ጎንደሮች ማሪያምና ጋባ በተባሉ አካባቢዎችም ጭምር ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ቀጥሎ ውሏል፡፡

November 9,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
ከጎንደር 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ከምትገኘው ማውራ መንደር በገበሬው ህዝብና በህወሓት ልዩ ኃይል መካከል ከትናንት በፊት የተቀሰቀሰው ጦርነት አድማሱን አስፍቶ ሮቢት፣ ጎንደሮች ማሪያምና ጋባ በተባሉ አካባቢዎችም ጭምር ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ቀጥሎ ውሏል፡፡
ቅዳሜ ዕለት ጥቅምት 27 2008 ዓ.ም ከ200 በላይ የህወሓት ልዩ ኃይል አባላት በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተደማጭነት ያላቸውንና እንደ መሪ የሚታዩትን የአገር ሽማግሌዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል ወደ ማውራ ለመግባት ሞክረው የአካባቢው ገበሬ በጠቅላላ በአንድነት ሆ ብሎ ታጥቆ በመውጣት ወደ ቀዬው አላስደርስም በማለቱ ሲሆን ግጭቱ የተቀሰቀሰው ወደ ማውራ ከሄዱት 200 የህወሓት ልዩ ኃይል አባላት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ከገበሬዎቹ በተተኮሰባቸው ጥይት ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል፡፡ 
ማውራ ላይ የተቀሰቀሰው ጦርነት ወደ ሌሎች አጎራባች መንደሮችም በመቀጣጠል ተስፋፍቶ በጎንደሮች ማርያም፣ ሮቢትና ጋባ በጎንደር ገበሬዎችና በህወሓት ልዩ ኃይሎች መካከል ደም ባፋሰሰ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በተለይም ደግሞ የጎንደሮች ማርያም ገበሬ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የህወሓት ልዩ ኃይል ጦር በመክበብ መውጫ ቀዳዳ አሳጥቶ ጭፍጭፎ አስቀርቶታል፡፡
በማውራ የተከፈተው ጦርነት ትናንት ቀኑን ሙሉ ውሎ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰዓት ያለምንም ፋታ መቀጠሉን ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ ዛሬ ከማለዳ ጀምሮ እስከ ረፋዱ አራት ሰዓት ድረስ በማውራ ገበሬዎችና በህወሓት ልዩ ኃይሎች መካከል ከባድ ውጊያ ተካሂዷል፡፡ 
በአሁኑ ሰዓት የማውራና ሌሎች መንደሮች ነዋሪ የሆኑ ወንዶች በጠቅላላ ታጥቀው ባቅራቢያቸው ወደሚገኝ ጫካ የገቡ ሲሆን መንደሮቹ ከፍተኛ ቁጥር ባለው የህወሓት ፌደራል ፖሊስ ጦር ተወረዋል፡፡ በመንደሮቹ ውስጥ የቀሩት ህፃናትና ሴቶች ብቻ ናቸው፡፡ አስገድዶ መድፈር፣ ግድያ፣ ግርፋትና እስር በፖሊሶቹ እየተፈፀመባቸው ይገኛሉ፡፡ መፈናቀልም ተፈጥሮ ብዙ ጎጆዎች ውስጣቸው ኦና ሆኖ በሮቻቸው ተዘግተዋል፡፡
በውጊያ ከገበሬዎች በኩል 1 ተዋጊ ብቻ እስካሁን ተሰውቷል ሌሎችም የቆሰሉ አሉ እየተባለ ነው፡፡ በተጨማሪም ቁጥራቸው ያልታወቁ ህፃናትና ሴቶች ተገድለዋል፡፡ 
የህወሓት አገልጋይ የሆነው ብአዴን አባል የሆኑት የጎንደር ሹሞች ነፍጥ አንስተው እየተፋለሙ ከሚገኙት ገበሬዎች ጋር በስልክ ለመደራደር ሞክረው "እንኳን ለእናንተ ልንሸነፍ እነ ገዛኸኝ ወርቄንም አርበድብደናቸዋል፡፡" የሚል ምላሽ እንዳገኙ ታውቋል፡

ኢህዴን/ብአዴን የአማራን ሕዝብ አይወክልም ሞራሉም ብቃቱም የለውም!!

November 9,2011
አንተነህ ገብርየ
መብርሓቱ ገብረእግዚአብሔር ወይም በረከት ስምኦን በበርሃ ስሙ (አንበርብር) እየተባለ የሚታወቀው ጎንደር የተወለደው ኤርትራዊ የአማራ ሕዝብ ጠላት ከኢህአፓ እስከ ብአዴን የፈፀማቸው ፀረ-ሕዝብ ተግባሮቹ ።Bereket Simon/Mebratu
ይህን ሰው በሚመለከት ከዚህ ቀደም ትውልዱና የዘር ሀረጉን የቤተሰቡን ሁኔታ መጻፌና ጹሁፉ ለአንባቢያን መቅረቡን አስታውሳለሁ። ሌሎች ለሕዝብ ይፋ ያልተደረጉ ኅልቆ መስፈርያ የሌላቸውን ጉዳዮች ጊዜ ወስዶ ለማጋለጥ ይህ ባካናም ዘመን እድል ሊሰጠኝ አልቻለም እንጅ በውስጥ ከመቃጠል አላረፍኩም። ያም ሆነ ይህ በዚህ በያዝነው ወር 35ኛውን ዓመት የአማራውን ሕዝብ የገደሉበትን፤እስር ቤት ያጎሩበትን፤አካሉን ያጎደሉበትን፤ንብረቱን የዘረፉበትን፤አገር ጥሎ እንዲሰደድ ያደረጉበትን፤የዘር ፍሬውን ያመከኑበትን፤ጦርነት ውስጥ ማግደው ያስፈጁበትን፤እንደከብት ቆዳውን ገፈው በሕይወቱ ገደል የጨመሩበትን፤እቤት ውስጥ አስገብተው በሳት ያቃጠሉበትን፤ደሙን የመጠጡበትን፤የሰውነት ክፍሉን አውጥተው የሸጡበትን፤ተወልዶ ካደገበት ቀየው አፈናቅለው መሬቱን የሸጡበትን ልደት ለማክበር የቀረህን አራግፈህ ወዲህ በል እያሉ አማራውን እያመሱ ያሉበት ወቅት ላይ ስለምንገኝ እንደ አንድ የአማራ ነገድ ተወላጅ በአለሁበት ሆኜም አንደበቱ የታፈነውን አማራ ሕዝብ ድምጽ ማሰማት ኃላፊነትና ግዴታየ በመሆኑ ለዛሬ ይህን መጣጥፌን አቀርባለሁ።
በረከት ከላይ እንደተገለጸው ትውልዱ በእናት በአባቱ ኤርትራዊ መሆኑ ግልጽ ነው ተወልዶ ያደገው ጎንደር ሲሆን በረከት ያችን የጎንደሬነት ካርድ እየመዘዘ የጎንደርን ተወላጆች ከሌላው ነጥሎ ለማስመታት የሄደባቸው መንገዶች በጣም አደገኛ እንደነበሩና አሁንም ስልታቸውን እየቀያየረ እየተጠቀመባቸው እንደሆነ በግልጽ ሊታወቅበት ይገባል።ይህን ጉዳይ ነባር የኢህዴን ታጋዮችም ሆነ የአሁኖቹ የብአዴን ታጋዮች ያውቁታል።አዲሱ ለገሰ የአማራ ክልል ገዥ በነበረበት ወቅት በረከት በቀጥታ ወደ ጎንደር እየሄደ ጎንደርን አትንኩ አይነት ቃላትን እየተጠቀመ ጎንደሬ የሆኑ ካድሬዎችን ይቀጣ ነበር።ካድሬዎችን ለምን ቀጣ ሳይሆን ወደ ጎንደር መመላለስ ሲያበዛ አንድ የፈለገው ነገር እንዳለ አውቅ ነበር። 1ኛው ጉዳይ አንዳንድ አስተሳሰበ ደካማ የሆኑ ቅማንቶችን አስተባብሮ በአማራው ላይ አመጽ እንዲያነሱ ለማድረግ መሆኑ ግልጽ ነበር ይህም አሁን እየተደረገ ያለ ጉዳይ ነው። 2ኛው ጉዳይ የህወሃትን ወደ ጎንደር መስፋፋት ለማጠናከር እንደሆነም ይታወቃል። ጎንደሬ ነኝ እያለ ግን የጎንደር ሕዝብ ሥራ የማይወድና ሰነፍ ሕዝብ ስለሆነ መሬቱ ጦሙን ከሚያድር ቢለማ ምን አለበት? የምትለዋን ቃላት በስፋት ይጠቀማል።ስለጎንደር ሲነሳ ትግሬዎችም ሆኑ ትግርኛ ተናጋሪዎች አስቀድመው የሚወረውሯት ቃል ይህችው ናት።በረከት እንደ የብአዴን አመራር ከብአዴን ማ/ኮ ጋር ሳይሆን የሚማከረውና ትእዛዝ የሚቀበለው መለስ በነበረበት ወቅት ከመለስ ሲሆን አሁን ደግሞ የመለስ ራእይ አራማጅ ከሆኑ የህወሃት መሪዎች ጋር ነው። ይህን የብአዴን ማ/ኮ ሳያውቀው በስሎ የሚቀርብን ሃሳብ በተግባር ለማዋል በተናጠል እያሳመኑ እጅ እንዲሰጡ በማድረግ መሄድ የተለመደ ነበር።ዋናው ግብ በአማራ ክልል የሚገኙ የተለያዩ ጎሳዎችን ውስጥ ለውስጥ በማደራጀት በአማራው ላይ አምጸው እንዲቆሙ ማድረግና በተለመደው የአማራ ጥላቻ ከአናሳዎቹ ጎን በመሆን አማራውን ለመምታት የሚጠቀሙበት መሣርያ ነበር አሁንም በዚሁ መንገድ እንደሚሄዱ ሥራዎቹ ወይም የሚፈጽሟቸው ተግባሮች በግልጽ ያሳያሉ።
የዚህን መሰሪ ሰው ተንኮል ለመመልከት ወደ ኋላ ሄጀ አንድ ምሳሌ ልጥቀስ፦በደርግ አገዛዝ ወቅት ህወሃት ጎንደርን በተለይም የሰሜኑን ክፍል ይዞ ነበር በ1977 ዓ/ም የተወሰነውን ቦታ ለኢህዴን አስረክቦ ሲንቀሳቀስ በመጀመርያዎቹ አካባቢ ህዝቡ ከደርግ ጋር በነበረው ጥላቻ ብቻ ተቀብሎ ማስተናገዱ አልቀረም ይህ በዚህ እንዳለ በ1978 እና በ1979 ዓ/ም ኢህዴን በሁለት ተከፍሎ የመበተን አደጋ ላይ ወድቆ ነበር።ምክንያቱ ያሬድ ጥበቡ ወይም ጌታቸው ጀቤሳ እየተባለ የሚጠራው የኢህዴን ሊቀመንበር የነበረ በኋላ ታምራትና መለስ በፈጠሩት ሴራ ጌታቸው በውጭ ሄዶ የማደራጀትና ኢህዴንን የማጠናከር ሥራ እንዲሰራ ተብሎ ወደ ውጭ ወጣ የሱን ቦታ ታምራት ተካ።በዚህ ወቅት አብዛኛው ታጋይ በታምራት ላይ ቅሬታ ያሳደረና በጌታቸው መነሳት ቅሬታ የተሰማው ነበር። ጌታቸው ሳያኮርፍና ተስፋ ሳይቆርጥ ኢህዴንን የማጠናከር ተግባሩን ቀጥሎ ተጓዘ በየጊዜው የሚፈጽመውን ተግባርም አገር ቤት ላለው የኢህዴን ማ/ኮ ሪፖርት ያደርግ ነበር።መልእክቱ ከአሜሪካ ወደ ሱዳን በህወሃት መስመር ይላካል የራዲዮ መልእክት የጹሑፍ ይላካሉ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የህወሃትን በጎ ፈቃድ ማግኘት ነበረበት።ከእለታት አንድ ቀን ህወሃት የኢህዴንን የጹሑፍ መልእክት ይጠልፍና ፖስታው ተከፍቶ ይነበባል የሰው ስም ዝርዝር ያለበት ነበር ጌታቸው የላከው ለኢህዴን አባልነት፤ደጋፊና ተባባሪ ይሆናሉ የተባሉትን ስም የያዘ ደብዳቤ።
ኋላስ ምን ሆነ? አጅሬ ህወሃት ይህን ደብዳቤ አፍኖ ከቆየ በኋላ በውጭ ያለውና በአገር ቤት ያለውን የኢህዴን አመራር በጥርጣሬ ላይ አክርመው ደብዳቤው እጃቸው መግባቱንና ጌታቸው የመለመላቸው ሰዎች ለኢህዴን አደገኛ ስለሚሆኑ ኢህዴንን ከአደጋ ለመከላከል ስንል ያደረግነው ነው ተብሎ በበጎነት እንዲታይና የኢህዴን አመራር እምነት እንዲጥሉበት ተደረገ።አደጋው ግን ለኢህዴን ሳይሆን ለህወሃት እንደነበር ግልጽ ነበር ይህ ይፋ ሲሆን የኢህዴን አባላትና አመራር በጌታቸውና ታምራት ቲፎዞነት ሲጦዝ ከረመ ህወሃትና ኢህዴን በጹሑፍ መባጠስ የጀመሩበት ወቅትም ነበር ዋናው ነጥብ አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘርዓ ጽዮንን በገዳሪፍና ካርቱም የኢህዴን ጽ/ቤት በማስተናገዱ ህወሃትን ደፍሯል የሚል ሲሆን ኢህዴን ደግሞ ምሥጢሬን አይታችኋል በሚለው ዙርያ ነበር።በዚህ ወቅት አያ በረከት ያዙኝ ልቀቁኝ በማለት ሲሸመገል የነበረው ከጌታቸው ወገን በመሆን ሲሆን እስከ መቼ የህወሃት ሸሚዝ ሆነን ልንኖር ነው በማለት አኩራፊ ነበር ይህች ግን በነመለስ ቅንብር ከጌታቸው ጎን ገፍተው የሚወጡትን የአማራ ተወላጆች ለማጥመድና ጊዜ ገዝቶ(ጠብቆ)ፀጥ ለማድረግ ያለመ ነበር ተሳካ። የበረከት ወንድም ካሣሁን የተገደለው በህወሃትና በኢህአፓ በተደረገ ጦርነት ከህወሃት በተተኮሰ ጥይት ነው ይህ ግን ለበረከት ምኑም አልነበረም በሬ ካራጁ ብንልም የበረከት ዓላማ ሌላ ነበርና ዛሬ ላይ ሆነን በረከት የመጣበትን መንገድ ስንመለከት ዘለቀ፤ሙሉዓለም፤ጌጡ(ኡስማን)፤አውጃኖ፤አገኘሁ፤ንጉሤ…ወዘተ የተገደሉበትን ሁኔታ በገሃድ ያስያል።
ሌላው በረከት በአማራ ህዝብ ደም ምን ያህል እንደቀለደ የሚያሳየው በ1984 ዓ/ም ደቡብ አካባቢ ምክንያቱ ኦነግን ያደረገ ነገር ግን ኢህአዴግ በዋናነት የመራው በሐረር፤በአርባ ጉጉ፤ወተርና እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች የአማራ ነገድ ባላቸው ምስኪን ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመው እልቂትን አስመልክቶ እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ በማለት ማስረጃዎች ተቀብረው የሚቀሩ ይመስል ነገርን ከራስ አውርዶ ለመጣል በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አማራዎችን ሆድ ለማባበል ሲባል የጎንደር 21 ቀበሌዎች ያዘጋጁት እንዲባልና ኢህዴን ወደ ብአዴንነት ሽግግርን በሚያደርግበት ወቅት ለደቡብ አማራዎች ትርንስፖርት ተዘጋጅቶ ጎንደር ከተማ ድረስ እንዲሄዱ ተደርጎ ሰፊ ድግስ ተደርጎ የደቡብ አማራ ወገኖቼ አይዟችሁን ተችረው እንዲመለሱ የተደረገው ትራጀዲ ወደ ኋላ ተመልሸ ሳስበው ያመኛል።በድርጅት ገንዘብ ወጭ ተመድቦ ነገር ግን ገንዘቡ ደብዛው ጠፍቶ ዝግጅቱ በ21ዱ ቀበሌዎች በጀት ተሸፈነ። ያ ዝግጅት በጎንደር አማራዎችና ከደቡብ ወገኖቹ በመጡ አማራዎች መካከል ልብ ለልብ ያገናኘ ከበረት የጠነከረ አንድነትን ፈጥሮ ነበር የሚያሳዝነው ነገር ያኔ የተወረወረች የውሸት አይዟችሁ ለምን ከክልሌ መጣችሁብኝ በማለት በሽፈራው ሽጉጤ ፊታውራሪነት በጉራ ፈርዳና በቬንሻንጉል በጋምቤላ እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች አማራን አያሳየኝ በማለት ምስኪን ወገኖቻችን ሲያልቁ የደረሰላቸው አልተገኘም በራሳቸው የአማራ ክልል በሚባለው እንኳን የሚተባበራቸው ጠፍቶ የአማራው ገዥዎች ጀርባቸውን ሲሰጡ ተመልክተናል።
ዛሬ የ35ኛ ዓመታችን ልደት ልናከብር ስለሆነ ገንዘብህን አምጣ የሚሉት ደሙን መጥምጠው የጠቡትን አጥንቱን የጋጡትን አማራ ምን አለውና ነው ገንዘብ የሚጠየቀው? ለነ ህላዊ ታደሰና ዓለምነው መኮንን ፈንጠዝያ ወይስ የአማራው ህዝብ እንባ አባሽና ድምጽ ለሆነ ድርጅት? መንደር ለመንደር የእያንዳንዱን አርሶ አደርና አባወራ ቤት በማሰስ አስገድዶ ገንዘብ መሰብሰብ ሊቆም ይገባዋል። ማን አለብኝነት ለደርግ አልበጀም ይህ ሕዝብ ሆ!! ብሎ ሲነሳ የሚከፈለው ዋጋ እጥፍ ድርብ እንደሚሆን መዘንጋት አይገባም ዛሬ ሆድህን ወደህ አንድነትን ከሚንዱ የውጭ ጌቶቻቸውን ለማስደሰት ታሪክ ከሚያጠፉ፤አገር ከሚሸጡ የሀገር ሀብት ከሚዘርፉና ትውልድን እየበሉ ከሚገኙ ፀረ-ሕዝቦች ወግነህ ዜጐችህን እያጫረስክ ያለህ ካድሬ፤የደህንነትና የፖሊስ ኃይል፤የመከላከያ ሰራዊት የአማራውን ሕዝብ ክንድ ጠምዝዘህ እያሳረድክ ያለህን እያንዳንድህን ታሪክ ስለሚፋረድህ ነገ ይህ የአማራ ነገድ ሕዝብ አንገቱን ቀና አድርጎ መሄድ ሲጀምር መሬት ከምትጠብህ አሁን ታሪክ ለመስራትና ከወገንህ ጐን ቆመህ አይዞሽ እማየ!! አይዞህ አባየ!! አይዞህ ወንድም ዓለም!! ይዞሽ እህት ዓለም!!ማለት ብትሞክር ትናንት ለግል ጥቅም ስትል የፈጸምክበትን በደል ሁሉ ይቅር ሊልህ እንደሚችል እርግጠኛ ነኝ።
የአማራ ህዝብ አማራ ባልሆኑ መሪዎች አይገዛም!

Saturday, November 7, 2015

እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቁስለኛ ወታደሮች ዳሽ-6 በተባለ አውሮፕላንና ኤም.አይ-17 ሄሊኮፕተር ከሶማሊያ አየተጫኑ ድሬ ደዋ ላይ በመራገፍ ላይ ናቸው፡፡

November 7,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
የህወሓት አገዛዝ የሚቆጣጠረው መከላከያ ሰራዊት አባላት የሆኑ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቁስለኛ ወታደሮች ዳሽ-6 በተባለ አውሮፕላንና ኤም.አይ-17 ሄሊኮፕተር ከሶማሊያ አየተጫኑ ድሬ ደዋ ላይ በመራገፍ ላይ ናቸው፡፡

ራሱን በመንግስትነት ስም የሚጠራው የማፍያው ቡድን ህወሓት የምዕራባዊያንን ቁሳዊና ፖለቲካዊ ድጋፍ በማግኘት ስልጣኑን ለማደላደል ሲል ብቻ ከ10 ዓመታት በፊት ማለትም ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የድሃው የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅ የሆኑ ዕልፍ አዕላፍ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያለማቋረጥ ወደ ሶማሊያ በረሃማ ምድር እያስገባ እጅግ በጣም አሰቃቂ ለሆነ እልቂት እየዳረጋቸው ይገኛል፡፡ ...

የህወሓት አመራሮች የእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረትን ከሁለት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በመደምሰስ አፈራርሰውት ለቀው እንደሚወጡ ለህዝቡ ገልፀው ወደ ምድራዊ ሲኦል ወደሆነችው ሶማሊያ ጦር ጭነው ያስገቡ ሲሆን ነገር ግን አልሸባብ የተባለ ሌላ ፅንፈኛ ቡድን ፈጥረው ምስኪን ኢትዮጵያዊያን ወጣቶችን ከማይወጡበት የጦርነት አዙሪት ውስጥ ከተዋቸው ለድፍን 10 ዓመታት ሰቅጣጭ የሞት ገፈትን ሲግቷቸው ቆይተዋል፡፡ ቀጠናውንም የባሰ አለመረጋጋት እንዲሰፍንበት አድርገውታል፡፡


በዶላር ፍቅር ዓይኑ የታወረው የህወሓት አገዛዝ ከ10 ዓመታት በፊት ጦሩን ወደ ሶማሊያ ሲያስገባ እሱ እንደሚነግረን መጀመሪያ ላይ ጦርነት የገጠመው ከእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት ሽምቅ ተዋጊዎች ጋር ብቻ ሳይሆን በዋነኝነት ከሶማሊያ ጎሳዎች መካከል በጠንካራነቱና በታላቅነቱ ከሚታወቀው የሃውዬ ጎሳ ጋር ነበር፡፡ በመሆኑም በገብረ ዲላ እና በሌሎች ህወሓታዊ ድኩማን የጦር አዛዦች የሚመሩት 43ኛ እና 44ኛ ክፍለ ጦር ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል፤ መሪዎቹ ጭነዋቸው የሄዱትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ወታደሮች ለሶማሊያ በረሃ ገብረው አምስትና ስድስት ወታደሮችን ብቻ አስከትለው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል፡፡ ሞቃዲሹ ውስጥ አንድ የሃውዬ ጎሳ አባል በአንድ ህንፃ ውስጥ መትረየስ ጠምዶ ቢያንስ አንድ ሻምበል ጦር ብቻውን ጨርሷል፡፡ የድሃ ልጆች ለኢትዮጵያ ምንም አይነት ጠቀሜታ በሌለው ጦርነት በክንቱ ደማቸው ፈሶ ረግፈው ያለቀባሪ ቀርተዋል፡፡ አሁንም በዘግናኝ ሁኔታ መገደላቸው ቀጥሏል፡፡ ሬሳቸውም እንዳያርፍ ተፈርዶበት በየጎዳናው በገመድ ታስሮ ሲጎተት ታይቷል፡፡ 


ምንም እንኳን አሮጌዎቹ የአየር ኃይል አውሮፕላኖችና ሄሊኮፕተሮች የወታደር ሬሳና ቁስለኛ ወደ ድሬ ደዋ ያለማቋረጥ ማመላለስ የጀመሩት ካለፈው 2007 ዓ.ም ጀምሮ ቢሆንም አሁን አሁን ደግሞ የባሰውኑ ስራ በዝቶባቸዋል፡፡ ዳሽ-6 አውሮፕላንና ኤም.አይ-17 ሄሊኮፕተር በቁስለኛ ወታደሮች ጥቅጥቅ ብለው ተሞልተው ከወደ ሶማሊያ እየመጡ ድሬ ደዋ ላይ በማራገፍ ላይ ናቸው፡፡
ከሶማሊያ በአውሮፕላንና በሄሊኮፕተር ተጭነው ድሬ ደዋ ላይ የተራገፉት ቁስለኛ የሰራዊቱ አባላት ወደ ሐረር ወታደራዊ ሆስፒታል እየተወሰዱ በመግባት ላይ ናቸው፡፡ በመሆኑም የሐረሩ የመከላከያ ሆስፒታል ከአቅሙ በላይ በቆስለኞች መሞላቱን የሆስፒታሉ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡
ሆኖም ለቁስለኞች የሚደረገው ህክምና እና እንክብካቤ በራሱ ከአድሏዊነት የፀዳ እንዳልሆነ ተጎጅዎች ቅሬታቸውን እየተናገሩ ነው፡፡ የህወሓት ታጋዮች የነበሩ የሰራዊቱ አባላት ሆዳቸውን በቆረጣቸው ቁጥር ደቡብ አፍሪካና ሳዑዲ አረቢያ ድረስ እየሄዱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እየታከሙ ተገደው የሶማሊያው ጦርነት ውስጥ ተማግደው ስጋቸው በእሳት ተጠብሶ የተመለሱት ወታደሮች ግን ጦር ኃይሎች ሆስፒታልን እንኳን በዓይኖቻቸው የማየት እድላቸው የጠበበ እንደሆነ እና አካላቸውን ላጡትም ምንም አይነት የሞራልም ሆነ የቁሳቁስ ድጋፍ እንደማይደረግላቸው ብሶታቸውን ዘርዝረዋል፡፡
በተጨማሪም ሶማሊያ ውስጥ የሚገኙ የአየር ኃይል አባላት በአውሮፕላኖችና ሄሊኮፕተሮች ብልሽትና እንዲሁም የመለዋወጫ እጥረት ምክንያት ስራ ፈትተው ለረጂም ጊዜ በመቀመጣቸው በአገዛዙ ላይ ከፍተኛ ቅሬታ ያዘለ ጥያቄ በአንድነት አንስተዋል፡፡ የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ጀነራል ማዕሾ ሐጎስ ወደ ቦታው አምርቶ ጥያቄ ያነሱ አባላትን የማረጋጋት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ለተነሳው ጥያቄ ተገቢ መፍትሄ ባለመሰጠቱ አሁንም ቅሬታው ባለበት ቀጠለ እንጂ ሊቀረፍ አልቻለም፡፡
የእነዚህን ሶማሊያ ዘማቾች የአየር ኃይል አባላት ሚስቶች የምስራቅ አየር ምድብ አዛዥ የሆነው ኮሎኔል አበበ ተካ በየተራ እያማገጠ እንደሚገኝም ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ገልፀውልናል፡፡
በአጠቃላይ ሰሞኑን በኢትዮጵያና በሶማሊያ አዋሳኝ ድንበር ላይ በህወሓት መራሹ መከላከያ ሰራዊትና በአልሸባብ ተዋጊዎች መካከል ከባድ ጦርነት እንደተካሄደ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡


Thursday, November 5, 2015

የኢትዮጵያ ወጣቶች ክልል፣ ቋንቋም ሆነ ሀይማኖት ሳይገድባቸው በጋራ ይቁሙ!

November 5, 2015
def-thumbከ1950ዎቹ ጀምሮ የተደረጉ ሕዝባዊ ንቅናቄዎች በሙሉ የተጠነሰሱትና የተመሩት እድሜያቸው ከሠላሳ አምስት ዓመት በታች በሆኑ ወጣቶች ነው። የ1997 ምርጫ ታሪካዊ እንዲሆን ያደረጉ፤ የሚያዝያ 30 ቀን 1997ን ታላቅ ሰልፍ ያደራጁ፤ ሕዝብን አደፈፍረው ለምርጫ በማሰለፍ ግንቦት 7 ቀን 1997 ታሪካዊ ዕለት እንድትሆን ያደረጉ፤ በኋላም “ድምፃችንን አናስነጥቅም” በማለት የአግዓዚ ፋሽስቶችን በድንጋይና ዱላ የገጠሙ የኢትዮጵያ ወጣቶች ናቸው። በዚህ ትግል ሽብሬ ደሳለኝን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች ሕይወታቸውን ሰውተዋል፤ በቁጥር የበዙት ደግሞ አካሎቻቸውን አጥተዋል፤ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች አሁንም በአገዛዙ እስር ቤቶች ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው ነው። ጥቃቱ ቢበዛም ትግሉ ደግሞ የዚያኑ ያህል ተጠናክሮ ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ወጣት ጥቃትን አሜን ብሎ አይቀበልም።
ህወሓትና ህወሓት የፈጠራቸው አድርባይ ድርጅቶች የዛሬው ወጣት ወኔው የላሸቀ፤ ኑሮው የተጎሳቆለ፤ የነገ ተስፋውም የጨለመ እንዲሆን ፓሊሲ ነድፈው እየተንቀሳቀሱ ነው። ህወሓት “መብት ተነፈግን” ብለው ብረት ባነሱ ወጣቶች መቋቋሙን ረስቶ የዛሬ ወጣቶች መብቶቻቸውን ተጠቅመው ሕይወታቸውን መምራት ቀርቶ መብቶቻቸው ምን እንደሆኑ እንዲጠይቁ እንኳን አይፈቅድላቸውም። በህወሓት አገዛዝ የትምህርት ተቋማት የሚሰጡት ትምህርት ጥራት እጅግ የወረደ በመሆኑ ወጣቶች የሕይወትን ፈተና ለመቋቋም የሚያስችል ክህሎት ሳይዙ እንዲመረቁ እየተደረገ የተመራቂ ሥራ አጦች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር ተደርጓል። ለወጣቱ የሥራ እድሎችን የመክፈት ጉዳይ አገዛዙን የሚያስጨንቀው አይደለም። ለም መሬታችን ለባዕዳን በመሸጡ የገጠሩ ወጣት የሚያርሰው ቁራሽ መሬት እያጣ መሰደድ ከጀመረ ውሎ አድሯል። በሀገር ውስጥ ተስፋ በመታጣቱ በገጠርም በከተማም የሚገኙ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ወደ ደቡብ አፍሪቃና አረብ አገራት ለመሄድ በረሃ ማቋረጥ፤ ባህርን በታንኳ መሻገር የጀመሩት በዚሁ የግፍ አገዛዝ ዘመን ነው። ዘመናዊ ትምህርት ያገኘው ወጣትም በተማረው ትምህርት አገሩንና ወገኑን የማገልገል ህልሙ ተጨናግፎ ስደት እጣ ፈንታው የሆነው በዚሁ በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ነው። በጫትና ሌሎች ሱሶች አዕምሮው የደነዘዘው ወጣት ቁጥርም አስደንጋጭ ነው።
ከዚህ ሁሉ የከፋው ደግሞ ወጣቱን በዘር በማደራጀት እርስ በርሱ እንዲጣላ መደረጉ ነው። በየጊዜው በሚፈለፈሉ “የወጣቶች ፎረሞች” አማካይነት የወጣቱ ወኔ ተሰልቦ አድርባይነትን እንዲለማመድ ተደርጓል። የጎንደሩ ወጣት ለአሰላው፣ የመቀሌው ለባህርዳሩ፣ የጅማው ለአዋሳው ባዕድ እንዲሆን፤ በጥርጣሬም እንዲጠባበቅ፤ በሰበብ አስባቡም እንዲቆራቆስ ተደርጓል። ህወሓት ወጣቶችን በወጣቶች ላይ የሚያዘምት እርኩስ ኃይል ነው።
አገዛዙ ይኸ ሁሉ ቢያደርግም ዛሬም የኢትዮጵያ ወጣት፣ የነብር ጣት መሆኑን እያስመሰከረ ነው። አገሩን ከህወሓት ፋሽስቶች ለማዳን ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር በመቀላቀል ላይ ያለው የወጣት ቁጥር በከፍተኛ መጠን እየጨመረ ነው፤ በያለበት ከተማና መንደር ሆኖ በመደራጀት ላይ ያለው ወጣት ቁጥር ደግሞ በጣም አበረታች ነው። ከዚህም በላይ የቴፒ፣ አርባምንጭ፣ ባህርዳርና ጎንደር ወጣቶች እያደረጉት እንዳለው በተደራጀ መንገድ አምባገነኑን ሥርዓት መጋፈጥ ጀምሯል። ጊዜው የአርበኖች ግንቦት 7ቱ አርበኛ አምሳሉ ተሾመን የመሰሉ ለጠላት እጅ ከመስጠት በራስ ላይ እርምጃ መውሰድን የሚመርጡ ቆራጦችን ፈጥሯል።
በእንዲህ ዓይነት ወቅት ክልልን፣ ቋንቋን፣ ዘርንና ሀይማኖትን የተሻገረ የወጣቶች ኅብረት መኖሩ እጅግ አስፈላጊ ጉዳይ ነው። በቴፒ ወጣቶች ላይ በሚደርሰው ጥቃት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ወጣት ሊቆጭና ድጋፍ ሊሰጣቸው ይገባል። የአርባምንጭ ወጣቶች ሲሳደዱ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ በመላ ኢትዮጵያ ያሉ ወጣቶች ሊንቀሳቀሱ ይገባል። በለቀምት ወጣቶች በደል ሲደርስ በመላው የኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ የደረሰ ጥቃት ነውና ሁሉም ሊያመውና ከጎናቸው ሊቆም ይገባል። በባህርዳርና ጎንደር ወጣቶች ላይ በደል ሲደርስ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ወጣቶች ከጎናቸው ሊቆሙ ይገባል።
የህወወሓት “ወጣቱን ከፋፍለህ፣ አዳክመህ ግዛ” ፓሊሲ በራሱ በወጣቱ ቁርጠኝነትና የጋራ ስሜት ሊከሽፍ ይገባል። ህወሓትን ወደ መቃብሩ የሚገፋው በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ተወልዶ ያደገ ወጣት መሆኑ የአገዛዙ ኋላቀርነትና የመጪው ጊዜ ብሩህነት ማረጋገጫ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7 የወደፊቷ ኢትዮጵያ ለወጣቱ ምቹ አገር መሆን አለባት፤ መገንባት የሚኖርባትም በወጣቱ ትውልድ ነው ብሎ ያምናል። በዚህም የኢትዮጵያ ወጣቶች ክልል፣ ዘር፣ ቋንቋም ሆነ ሀይማኖት ሳይገድባቸው ለጋራ መብቶቻቸው በጋራ እንዲቆሙ፤ በአንድ አካባቢ ወጣቶች ለሚደርስ ጥቃት የሌላ አካባቢ ወጣቶች አፀፋዊ ምላሽ እንዲሰጡ ያበረታታል። ኢትዮጵያ በወጣቶቿ ያላሰለሰ ትግል ከወያኔ አምባገናዊ አገዛዝ ነፃ ትወጣለች።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

መንግስት በርሃብ ለተጠቁት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ታወቀ

November
• በርሃብ የተጠቁት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው እየተሰደዱ ነው
• ‹‹ሰው በርሃብ እያለቀ ነው››
• ‹‹የሚላስ የሚቀመስ የለም፡፡ ቤተሰባችን ፈርሷል››
• ‹‹እርዳታ ቢሰጥማ ከዚህ ድረስ አንመጣም ነበር፡፡››
መንግስት በርሃብ ለተጎዱት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ቀያቸውን ለቀው አዲስ አበባ የገቡት የርሃቡ ሰለባዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ከወሎ የተለያዩ አካባቢዎች በርሃብ የተጠቁ ዜጎች ህይወታቸውን ለማትረፍ ወሎ ውስጥ ከሚገኙት ከተሞች አልፈው ወደ ጎጃም፣ ጎንደርን እንዲሁም አዲስ አበባ እየተሰደዱ ሲሆን አዲስ አበባ በርካታ ተጎጅዎች ህፃናትን አዝለው እየለመኑ ይገኛሉ፡፡ የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ካነጋገራቸው መካከል ሁሉም መንግስት ለርሃቡ ተጎጅዎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ገልፀዋል፡፡ ቤተሰቦቻቸውና ጎረቤቶቻቸውም እንደነሱ ቀያቸውን ጥለው ወደ መተማ፣ ሁመራ፣ ባህርዳር፣ ደሴ፣ እንዲሁም ወደ አዲስ አበባ መሰደዳቸውን በሀዘን ገልፀዋል፡፡
ወሎ ውስጥ ጮሬ ሶዶማ ከተባለ ቦታ ተነስታ እንደመጣች፣ አዲስ አበባ ከገባች ሶስት ሳምንት እንደሆናት የገለፀችውና ሁለት ህፃናትን ይዛ ስትለምን ያገኘናት፤ በግምት በ30ዎቹ መጨረሻ ዕድሜ የምትገኝ እናት ‹‹የመጣነው የሚላስ የሚቀመስ ስለሌለ ነው፡፡ ከብቶቻችን አልቀዋል፡፡ አዝመራ የሚባል የለም፡፡ ሰው በርሃብ እያለቀ ነው፡፡ እኛ ሴቶቹ ወደ ከተማው ስንመጣ ወንዶቹ ደግሞ ወደ ሁመራና መተማ ሄደዋል፡፡ እኛም ከዚህ የመጣነው ጉልበት ስላለን ነው፡፡ አብዛኛዎቹ ደካሞች በዛው አካባቢ ቀርተዋል፡፡›› ስትል በሀዘን ገልፃልናለች፡፡ መንግስት እርዳታ አይሰጥም ወይ ብለን ላነሳንላት ጥያቄም ‹‹ምንም እርዳታ አልተሰጠንም፡፡ እርዳታ ቢሰጥ ኖሮ ቤታችን ጥለን አንመጣም ነበር፡፡ ባያበቅልም መሬት አለን፡፡ የከተማው ሰው ይሻላል ብለን ነው ወደዚህ የመጣነው›› ስትል ስለ ርሃቡ አስከፊነትና መንግስትም እርዳታ እየተሰጠ እንዳልሆነ ገልፃልናለች፡፡
ባለቤቷ ወደ መታማ ሲሄድ እሷም ቤቷን ጥላ ወደማታውቀው አዲስ አበባ እየጠየቀች እንደመጣች የገለፀችልን ወጣት በበኩሏ ‹‹ቤቴ ተፈትቷል፡፡ ባለፈው አመት ከብቶችም እህልም ነበረን፡፡ ዘንድሮ ግን ምንም ነገር የለም፡፡ ጊዜው ከፍቷል፡፡ ባሌ ወደ መተማ ሄዷል፡፡ እኔም ልጄን አዝዬ እስከ ደሴ በእግሬ መጣሁ፡፡ ከዛ በኋላ እየለምንኩ ከዚህ ደርሻለሁ፡፡ ማንም እርዳታ አልሰጠንም፡፡›› ስትል ስለሁኔታው ገለፃልናለች፡፡
ከመርሳ ወረዳ እንደመጡ የገለፁልንና ከልጃቸው ልጅ ጋር እየለመኑ ያገኘናቸው የ65 አመት አዛውንት በበኩላቸው ‹‹ዝናቡ ሲቀር ከብቶቻችንም ሞቱ፡፡ አዝመራ የሚባልም ነገር የለም፡፡ ከመርሳ ደሴ እየለመንኩ መጣሁ፡፡ ደሴም እንደኛ ብዙ ሰው አለ፡፡ አገኝ ብሎ በየከተማው ተሰራጭቷል፡፡ ወደዚህ ይሻላል ብዬ በለመንኳት ተሳፍሬ መጣሁ፡፡ ርሃቡ ሲብስብን ወደማናውቀው አገር መጣን፡፡›› ሲሉ የርሃቡን አስከፉነት ገልፀውልናል፡፡
‹‹እርዱኝ!›› እያሉ እየለመኑ ያገኘናቸው ከኬሚሴ አካባቢ እንደመጡና ከ8 ቀን በፊት አዲስ አበባ እንደደረሱ የገለፁልን ሌላኛዋ እናትም ቤታቸውን ጥለው እንደመጡና፣ ሌሎች ቤተሰቦቻቸው ወደ የት እንደሄዱ እንኳን እንደማያውቁ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ መንግስት እርዳታ እየሰጠሁ ነው እንደሚል ስንገልፅላቸው ‹‹ለእኔ አልደረሰኝም፡፡ እርዳታ ተሰጠኝ ያለም አልሰማሁም፡፡ እርዳታ ቢሰጥማ ከዚህ ድረስ አልመጣም ነበር፡፡ አሁን ነው ከከተማው ሰው ትንሽ ትንሽ እያገኘን ያለነው፡፡ በየ ከተማው ስንደርስ ሰው አይነፍገንም›› ሲሉ ከህዝብ እንጅ ከመንግስት እርዳታ እንዳላገኙ ገልፀዋል፡፡
ካሳንቺስ አካባቢ ልጅ አዝለው ታክሲ ተሳፋሪዎችን ምንም አይነት ቃል ሳያሰሙ ልጃቸውን በመዘርጋት ብቻ እንዲረዷቸው እየጠየቁ ያገኘናቸው እናትም የራሳቸውንና የታዘለውን ልጅ ነፍስ ለማዳን ቀያቸውን ጥለው ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡
የርሃቡ ተጎጅዎች አዲስ አበባ ውስጥም ነፍሳቸውን ለማቆየት በጠራራ ፀሀይ ሲለምኑ እንደሚውሉና ምቹ ያልሆነ ቦታ አንድ ላይ የሚያድሩ በመሆኑ ልጆቻቸው ለበሽታ እየተጋለጡ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ተማሪ የነበሩና በርሃቡ ምክንያት ለማቋረጥ የተገደዱት ልጆቻቸው ከእነሱ ጋር ወይንም ወደ ሌላ አካባቢ ነፍሳቸውን ለመዳን መሰደዳቸውን፣ በያለፉበት ከተማም በርካታ ስደተኛ እንዳለም ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

Tuesday, November 3, 2015

Ethiopia: Can TPLF Survive Its Own War on Terror?

November 3,2015
by Christina Goldbaum | OZY
Can Ethiopia Survive Its Own War on Terror?
On April 2, as I waited in a doctor’s office near Nairobi, the anchor of Kenya’s morning news broadcast began reporting what would prove to be a horrific attack on Garissa University by the Somali terrorist group al-Shabab. As the early news trickled in, some people around me looked at the television screen, and others just checked their phones. Most, however, just stared impatiently at the doctor’s door.
In Kenya, another terror attack wasn’t shocking news. Indeed, the number of attacks in Kenya has more than doubled since 2013, and the assault on Garissa, which killed 148, was just the latest in a growing list of al-Shabab outside Somalia. In 2010, a suicide bombing in Uganda killed 74 people; last year, militants carried out the first suicide bombing in Djibouti’s history; and in April, Tanzanian authorities arrested 10 people carrying explosives, bomb detonators and an al-Shabab flag. Meanwhile, in Ethiopia, a country with a longer history of military involvement in Somalia and a much longer border with the country than Kenya, the number of al-Shabab attacks in recent years is … well, zero. The last attempted attack in the country happened two years ago and ended when two would-be suicide bombers blew themselves up in their safe house in the capital of Addis Ababa.

My big concern with Ethiopia is the way they are behaving … is actually going to push people into the arms of extremists.

Bronwyn Bruton, deputy director, Atlantic Council’s Africa Center
Ethiopia’s success at evading attacks might not seem so remarkable, except that even the most developed countries, including the United States, have generally floundered in their counterterrorism efforts. Yet the blueprint Ethiopia is following to thwart al-Shabab attacks — and ultimately to help stall the Islamic State’s inroads into Africa — has its own set of civil rights issues. Indeed, the country sparked its own form of an ends-justify-the-means debate, with critics saying it relies on security and intelligence gathering that is too heavy-handed.
In its defense, the country of 94 million has been focused on the jihadi threat much longer than the rest of the region. Antagonism began in the 1990s, when al-Shabab’s precursor, al-Ittihad al-Islami, or AIAI, launched a number of border region attacks. In 2006, Ethiopia invaded Somalia to oust Islamists who had seized control of large swaths of the country; rights groups accused Ethiopian forces of killing civilians and other atrocities. Ethiopia withdrew its troops in 2009, but last year it joined AMISOM, the African Union’s peacekeeping force in Somalia.
In the years since, Ethiopia has set up a buffer zone along its 1,010-mile border with Somalia. On the Somali side, it has trained local militias; on the Ethiopian side, it has created a militarized zone off-limits to American military or humanitarian aid. Meanwhile, the country’s grassroots “five-to-one” security program provides a safety net: For every five households, one person is designated to report on new faces and any other changes in the status quo.
And despite having one of the world’s lowest rates of mobile phone and Internet penetration, Ethiopia has some of the world’s most high-tech surveillance capabilities. The government has a monopoly on the telecommunications sector, and in 2012 it invested roughly $1 million in hacking software, allowing it to record Skype calls, listen in on phone conversations, and access emails, files and passwords.
Were it monitoring only legitimate terrorist threats, its intelligence system could be a model. But like the U.S., Kenya and so many others, Ethiopia hasn’t escaped the great irony of counterterrorism: undermining human rights as it tries to protect them. According to recent Human Rights Watch reports, the government has monitored journalists, opposition party members and anyone else perceived to be a threat to its grip on power. Recordings of phone calls have been used during abusive interrogations of people whom, under Ethiopia’s vaguely worded 2009 anti-terrorism law, the government labels terrorists, a 2014 HRW report says. “Ethiopia is a police state,” says Bronwyn Bruton, deputy director of the Atlantic Council’s Africa Center, terming it “almost North Korea–esque.”
So far, Ethiopia’s authoritarian regime has been given a relatively free pass by the international community. The U.S., which is Ethiopia’s largest provider of foreign aid, considers it a strategic partner in counterterrorism efforts. In July, President Barack Obama visited Addis Ababa to address the African Union. Some worry the West’s acquiescence sets a dangerous precedent. “The rest of the sub-Saharan countries see this and see that they can pass this kind of legislation,” says Felix Horne, a researcher at Human Rights Watch. The government seems unfazed by criticism. Din Mufti Sid, ambassador to Kenya, laughed off the label “police state.” “If protecting [your people] gives you a bad name,” he tells OZY, “who the hell cares?”
Critics suggest the country’s repressive measures could breed homegrown terrorism. “My big concern with Ethiopia is the way they are behaving … is actually going to push people into the arms of extremists,” Bruton says. For the past several years, thousands of Muslims have marched in protests over government treatment of the Islamic community. Many protests have been violently disrupted.
But with al-Shabab calling for fresh attacks inside the country, even its strict security may not be enough going forward. “If there’s one thing we’ve learned about al-Shabab it’s that it’s highly adaptive and creative,” says Matt Bryden, chairman of Sahan Research, a Nairobi-based think tank. “The measures Ethiopia has in place today may well not be sufficient tomorrow.”

Monday, November 2, 2015

የፓርላማው ድራማ

November 2,2015
ይገረም ዓለሙ
ሙሉ በሙሉ በአብዮታዊ ዴሞክራቶች በመያዙ የተለየ ሀሳብ የማይሰማበት ሙት የሆነውን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተዘጋጀው ድራማ ማክሰኞ ጥቅምት 16/2008 መታየት ጀምሯል፡፡ ይህ የፓርላማ ድራማ ቤቴሌቭዥን እንደምናያቸው ድራማዎች ሰሞነኛውን ትኩሳት እየተከተለ በየሳምንቱ የሚጻፍና የሚዘጋጅ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ቀን ትዕይንት መሪ ተዋናይ ሆነው የቀረቡት ጠቅላይ ምኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከፓርላማው አባላት መካከል በተመረጡት ተዋንያን እየተጠየቁ በመመለስ ሲተውኑ ታይተዋል፡፡Hailemariam Desalegn in the TPLF parliament
ከቀደሙት ጠቅላይ ምኒስትር ጀምሮ ሲነገር እንጂ ሲተገበር የማይታየው ከተቀዋሚዎች ጋር አብሮ የመስራት ጉዳይ ለመጀመሪያው ቀን ድራማ ማድመቂያነት ከተመረጡት ጉዳዮች አንዱ ነበር፡፡ ተባብሮ መስራት ማለት እንደ ተቀዋሚዎች በመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመነጋገር ሀገራዊ መግባባት ከመፍጠር የሚጀምር እንደ ወያኔ ደግሞ እሱ በሚፈልገው ጉዳይ ሲፈልጋቸው ብቻ በመጥራት የሚገለጽ ነው፡፡ እንዲ ሆነናም በአምስት ዓመቱ ዕቅድ ላይ ለማወያየት ምርጫ ቦርድ መዝግቦ ለሚያውቃቸው ፓርቲዎች በሙሉ መንግጨሥታቸው ሰነድና ደብዳቤ መላኩን የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም ብዙዎቹ በስብሰባው ላይ ሲገኙ ጥቂቶች ውኃ የማይቋጥር ምክንያት በመስጠት አልተገኙም አሉ፡፡ ያልተገኙት ፓርቲዎች ያቀረቡት ምክንያት ውኃ የማይቋጥር ነው ያሉበትን ምክንያትም ሲያረዱ በሕጋዊ መንግድ የተመረጠ መንግሥት ስላልሆነ ከእርሱ ጋር አንነጋርም ማለታቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ለመሆኑ ጥሪያችንን ተቀብለው ብዙዎቹ ተገኝተዋል የተባሉት ፓርቲዎች የትኞቹና እነማን ናቸው፡፡ዝቅ ብለን እናያቸዋለን፡፡
የመሳሪያ ትግል የሚያካሂዱትን ድርጅቶች አስመልክቶም ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ለራሱም መሆን ካልቻለው ሻዕቢያ ጋር ሆነው የሚያመጡት ውጤት ስለማይኖር ጊዜያቸውን በከንቱ ባያባክኑ በማለት ምክር ለመስጠት የዳዳቸው አቶ ኃይለማሪያም አንዳንዶቹ እኮ ጭራሽ የሌሉ ናቸው በማለት ኦነግን ኦብነግንና የጋምቤላ ህዝቦች ንቅናቄን ጠቀሱ፡፡ ይቺ ገለጻ የቀረበችው በደራሲውና አዘጋጁ ስህተት ይሁን ወይንም በርሳቸው የጥናት ጉደለት ባይታወቅም ሁለት መልእክት ታስተላልፋለች፡፡ አንደኛ እነዚህ የተጠቀሱት ድርጅቶች ሰሞኑን ተባብረው ለመስራት የደረሱበት ስምምነት እነ አቶ ኃይለማያም ሰፈር የፈጠረው ነገር መኖሩን እንድንጠረጥር ያሚያደርግ ፣ ሁለተኛ ደግሞ በሰሜን በኩል ድምጻቸው የሚሰማው ድርጅቶች እነዚህ ብቻ አይደሉምና ለሌሎቹ መኖሮና ጠንካራ መሆን በዘወርዋራ እውቅና የሰጠ ነው፡፡
አቶ ኃይለማሪያም የአቶ መለስ ሌጋስ አስቀጣይ እንደመሆናቸው ስለ ድርጅቶቹ የተናገሩት ከርሳቸው የወሰዱትን ነው፡፡ አቶ መለስ ብረት አንስተው መንግሥታቸውን የሚታገሉ ድርጅቶችን አስመልክቶ ሲላቸው አጥፍተናቸዋል የሉም ሲሉ ሌላ ግዜ ደግሞ በግላቸው ብዙ ርቀት ሄደው ከድርጅቶቹ መሪዎች ጋር ለመገናኘትና ለመደራደር እንደጣሩ ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ ሌላ ግዜ ደግሞ ወድመዋል ተደምስሰዋል የተባሉት ደርጅቶች በዚህ ቦታ እንዲህ አደረጉ ጥፋት አደረሱ የሚል ዜና ስንሰማ ኖረናል፡፡ የሉም በተባሉ ድርጅቶች ስምም ዜጎች እየተወነጀሉ ታስረዋል እየታሰሩም ነው፡፡ አቶ መለስ አይደለም የሀገር ውስጥ ተፋላሚዎችን ሶማሌ ተሻግረው አልሻባብን ድምጥማጡን አጥፍተነዋል ብለውንም ነበር፡፡
አቶ ኃይለማሪያም ባያስታውሱም እኛ አንረሳውም፡፡ አቶ መለስ ከርሳቸው ፍላጎት ውጪ ስንዝር መሄድ የማይችለውን ፓርላማ አስፍቅደው(ነግረው) እንዲህ አስታዋሽ አጥቶ የቀረውን ሰራዊት ሶማሊያ በላኩበት ወቅት የገጠማቸውን ተቃውሞ ዝም ለማሰኘት ሰራዊታችን አልሻባብን ደምስሶ አሁን የቀረው ቃርሚያ ብቻ ነው፣ ያንን አጠናቆ በቅርብ ቀን ይመለሳል ብለውን ነበር፡፡ ነገር ግን ይኸው እስካሁን አልሻባብም አልጠፋ ሰራዊቱም አልተመለሰ፡፡ እንደውም በተቃራኒው ወንድሞቻችን የአልሻባብ ጥቃት ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡ አቶ ኃለማሪያም እኔም አንደ መለስ ብለው በንቀት ስሜት የሉም ጠፍተዋል ስላሉዋቸው ድርጅቶች መረጃ ስለሌለኝ የምለው አይኖርም፤ የላችሁም የተባላችሁ መኖራችሁን አሳይዋቸውና አቶ ኃይለማሪም በዚህ አፋቸው ምን እንደሚሉ ለመስማት አብቁን የሚለው ግን መልእክቴ ነው፡፡
አቶ መለስ የሻዕቢያና ወያኔ ጸብና ፍቅር ለወላይታው ምኑ ነው ብለው ለአቶ ኃይለማሪያም አለነገሯቸው እንደሁ እንጂ ወያኔን አዲስ አበባ ያደረሰው ለራሱም የማይሆን ያሉት ሻዕቢያ ነው፡፡ ይህም ብቻ አይደለም ሌላው ኢትዮጵያዊ (የወያኔ ታጋይ ጭምር ) የማይታመን ሆኖ እስከ ተጣሉበት ግዜ ድረስ ቤተ መንግሥቱ ይጠበቅ የነበረው በሻዕቢያ ሰራዊት እንደነበረ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ስለሆነም አቶ ኃይለማሪያም ወያኔዎች ስለ ሻዕቢያ ዛሬ የሚሉትን ብቻ እየተቀበሉ መናገር ሳይሆን ትናንት ምን ይሉ ምንስ ያደርጉ እንደነበር የተጻፈ አንብበው የነበረ ጠይቀው ቢናገሩ ቢያንስ ጠቅላይ ምኒስትር ለሚለው ማዕረጋቸው( ይስሙላም ቢሆን) የሚመጥን ይሆናል፡፡
ከላይ እንደተገለጸው አቶ ኃይለማሪያም ስለ አብሮ መስራት ሲናገሩ ምርጫ ቦርድ የመዘገባቸውን ፓርቲዎች በሙሉ ጠርተን አብዛኛዎቹ ተገኝተዋል ነው ያሉት፡፡ አብዛኛው የሚለው የጥቅል መጠሪያ ለወያኔም ለፓርቲዎቹም ለምርጫ ቦርድም እያገለገለ ነው፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በቁጥር ሲገለጹ እንጂ በስም ሲጠሩ አይሰማም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ምርጫ ቦርድ መዝገብ ላይ ሰፍረው የሚገኙት አንዳንዶቹ የሌሉ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ምርጫ ሲመጣ ብቻ ብቅ የሚሉና ለምርጫ የሚሰጣቸውን ገንዘብ ተቀብለው የአጃቢነት ሚናቸውን ተወጥተው ለአራት ዓመት የሚጠፉ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹም ፓርቲ ለመባል የሚያበቃ ቁመና የሌላቸው አቶ በረከት የፓርቲዎቹ ጥቅማቸው አልታይ ብሉአቸው ይሁን ስሜት ገፋፍቶአቸው ወይንም እውነት ተናንቆአቸው ባይታወቅም በመጽሀፋቸው የቤተሰብ ፓርቲ ሲሉ የገለጹዋቸው ናቸው ፡፡ በርግጥ ለመናገር አንዳንዶቹ ሊቀመንበር ተብሎ ከሚጠራው ሰው ቀጥሎ የሚጠራ ሶስትና አራት ሰው የሌላቸው በመሆኑ የቤተሰብ ፓርቲ የሚለውንም አያሟሉም፡፡ ብዙዎቹ ከተባሉት ከእነዚህ ስመ ፓርቲዎች ውስጥ ብዙዎቹን እንኳን ህብረተሰቡ ምርጫ ቦርድም አያውቃቸው፡፡ ድረ ገጹን ብትጎበኙ ቦርዱ ስለማያውቃቸው የተመዘገቡበትን ቀን መሙላት አቅቶት ቦታው ክፍት ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ፤ብቻ ብዙዎች እየተባሉ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ይውላሉ፡፡እነዚህን በስም እየጠቀሱ መሪ የሚባሉትን ሰዎች ምንነትና ማንነት እያሳዩ መግለጽ የሚቻል ቢሆንም የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ የምርጫ ቦርድን ድረ ገጽ ከጎበኙ ሌላም ነገር ይታዘባሉ፣ ምርጫ የማስፈጸም ብቃት አለው ተብሎ ምስጋና የተዥጎደጎደለት ይህ ተቋም ድረ- ገጹን ወቅታዊ ማድረግ ተስኖት ከአስር ዓመት በፊት የነበረ መረጃ ነው የሚያገኙት፡፡
ፓርቲ ማለት በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የህጋዊነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የተሰጠው ነው ካልተባለ በስተቀር ብዙዎች የሚባሉት ከወያኔ ዳረጎት እየተቀበሉ፤ በምርጫ ቦርድ መልካም ፈቃድ ፓርቲ እየተባሉ፤ በአዳማቂነትና በአጃቢነት የሚያገለግሉ፣ እንኳን አባል የተሟላ አመራር የሌላቸው ናቸውና ፓርቲ ሊባሉ የሚበቁ አይደሉም፡፡ መሪ ለሚባሉት ሰዎች ግን የእለት እንጀራም የሕይወት መንገድም ሆኖ እየጠቀማቸው ነው፡፡ በአንጻሩ ብዙም ባይሆን ለወያኔ ዕድሜ መርዘምም እየረዱ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ኖሩም አልኖሩ “ተለበሰ ቀረ የደበሎ ቅዳጅ ”እንደሚባለው ናቸውና ምንም ፋይዳ የላቸውም፡፡ እንደውም የማይቻል ሆኖ እንጂ አለመኖራቸው ይሻል ነበር፡፡
ሙቱን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተጀመረው ድራማ ደራሲና አዘጋጁ ሰልችቶአቸው እስካላቆሙት ድረስ በጀመረው መልኩ ወቅታዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን እየተከተለ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የእኛም ማየትና መስማት ብሎም ከምናይ ከምንሰማው ተነስተን ብዕር ከወረቀት ማገናኘት እንዲሁ ይቀጥላል፡፡እስካላቆሙት ድረስ ያልኩት አቅጣጫ ለማስቀየሻ እየተባሉ በዚህ መልኩ የሚጀመሩ ጉዳዮች ሲዘልቁ ስለማይታይ ነው፡፡ደግሞስ የማስመሰል ስራ መች ብዙ መንገድ ያስኬዳል፡፡ይህ የፓርላማ ድራማ ቀልቡን የሚስበው ሰው ኖር ይሆን!!

Berhanu Nega: Ethiopia’s Most Dangerous Professor

November 2,2015
by Laura Secorun Palet | OZY
It was the spring of 2001 and 43-year-old Berhanu Nega was optimistic. His homeland, Ethiopia, was recovering from decades of conflict, he had just given a speech to university students about academic freedom, and now he had landed at Charles de Gaulle Airport for a business conference in Paris.
Professor Berhanu Nega, Chairman of Patriotic Ginbot7
Professor Berhanu Nega, Chairman of Patriotic Ginbot7
Then he turned on his phone. The students he’d spoken to hours earlier had staged a peaceful protest that the police answered with brute force and live ammunition, leaving 40 people dead. A week later, Nega was back in Ethiopia, behind bars.
So began a 14-year-long ordeal that has seen Nega, one of Ethiopia’s leading activists, arrested and jailed twice — once for almost two years — exiled to the United States and finally, condemned to death, in absentia. These days, the would-be mayor of Addis Ababa (he was detained right after he won the election) is an associate professor of economics at Bucknell University. But Nega remains a prominent opposition leader: He is the co-founder of Ginbot 7, an outlawed political party that he leads from the sleepy Pennsylvania campus town of Lewisburg.
Of late, Ethiopia has been a darling of Western powers. The landlocked country is considered an island of stability in the otherwise turbulent Horn of Africa. Yes, its name was once synonymous with starving children and charity concerts, but today, Ethiopia posts GDP growth numbers in the double digits. In the past year, foreign investment has skyrocketed. The country is also a valuable partner against the threat of Islamist terrorism — here, in the incarnation of al-Shabab in Somalia, which killed 148 students in April at a Kenyan university.
In Nega’s view, that’s why the the U.S. donated $340 million to a country with such a horrible human rights record. Under Meles Zenawi, who ruled from 1991 until his death in 2012, the government ostracized the opposition and imposed a system of ethnic-based federalism, which enhanced divisions and was useful for repressing certain ethnic groups. Zenawi’s successor, Hailemariam Desalegn, has carried on his legacy of media muffling, extrajudicial executions and torturing dissidents. Nega says protecting a regime that most citizens resent will backfire in the long run: “Ethiopia is ready to explode, it just needs a little match to light it up,” he says. “The West is not going to give Africans democracy, Africans have to fight for it.”
The U.S. State Department did not comment on Nega’s criticisms of U.S. policy in the Horn of Africa. Via email, a representative described U.S relations with the Ethiopian government as “robust” and said it partners “with Ethiopia and its people, as we do with people and governments across Africa, to pursue shared goals of democracy, peace and prosperity.”
I have completely given up on the possibility of a democratic change.
Nega doesn’t look as pugnacious as he sounds. He wears small glasses and, on the day we speak over Skype, a professorial gray cardigan. Surrounded by walls of thick books in his university office Nega, now 57, looks much like any other professor. He talks like one too, explaining concepts with patience and detail. “But that’s his strength,” says Messay Kebede, an Ethiopian professor of social philosophy at the University of Dayton. Kebede says Nega’s deportment makes him seem more charismatic educator than politician. “And the crueler the regime becomes, the more people listen to him.”
The son of a prominent businessman, Nega first got involved in politics in school, in the ’70s, during the final days of Emperor Haile Selassie. He then had to flee to Sudan, where he spent two years reading philosophy in Khartoum’s public library, before making his way to the U.S. There he went straight back to the books, obtaining a Ph.D. in economics and becoming a teacher. In 1991, when the communist government was overthrown, Nega returned home only to find his country “hadn’t learned its lessons yet.” After his short stay in prison in 2001, he left his job as a lecturer and his fertilizer producing company for politics. It was a reluctant decision, he says: “The reality became so terrible that we had to do something to try to change it.”
His party, the Coalition for Unity and Democracy, rocked votes in the 2005 elections — Nega won the mayoralty of Addis Ababa — but the joy gave way to a crackdown. Nega was in jail for 21 months; when he got out, he headed almost straight to the United States. Last year, his friend and Ginbot 7 colleague Andargachew Tsige was detained in Yemen and presumably handed over to the Ethiopian authorities. Nega says Tsige’s disappearance and the detention of others has made the struggle personal. “We owe it to them to do everything we can,” he says.
Leaders like Nega are gone and, in the eyes of some, discredited. Without fair elections or international pressure, Nega says only one option remains: force. “I have completely given up on the possibility of a democratic change,” he says. So Ginbot is calling to dethrone Desalegn “by all means necessary.” This is a dangerous route for a country with such recent conflict and so many ethnic feuds, and, opposition leaders inside Ethiopia argue, an easy call for a man at a university 7,000 miles from Addis Ababa. As Merera Gudina, founder of local opposition party Oromo People’s Congress, says, “If there’s a coup, people will die.”
Nega says unnecessary violence would be avoided by educating those with weapons about democracy and the separation of powers; he regularly talks with members of armed groups and other dissidents about blueprints for the future. It will be based on strong institutions, an independent judiciary and economic policies that aim to serve Ethiopia’s poor majority.
Still, despite his best efforts to teach and mobilize, what’s to stop the country from falling into chaos after the last two changes in government? Nega is not sure. “History repeating itself,” he says, “that is what keeps me up at night.”
Source: OZY

Saturday, October 31, 2015

አይኔ አያየ እዚህ ዉስጥ አልገባም – መሠረት ሙሌ (ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር)

October 31, 2015
ኤፍሬም ማዴቦ ከአርበኞች መንደር
መብራቱን አጥፍቼዉ አልጋዬ ላይ የወጣሁት በግዜ ነዉ። አለወትሮዬ እንቅልፍ የሚባል ነገር በአይኔ አልዞር ብሎኝ ከጨለማዉ ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠናል። የነፋስ ሸዉታ እንኳን የማይሰማበት ደረቅ ሌሊት ነዉ። ጨላማዉ አይን ይበሳል። እቤቱ ዉስጥ ያለዉ ሰዉ ሁሉ ተኝቷል። ቀኑን በሠላም ላዋለኝ አምላክ ምስጋና ሰጥቼ ሌሊቱንም አደራ ብዬዉ ፀሎቴን ጨረስኩ። ያ ምቀኛ እንቅልፍ ግን አሁንም እንደከዳኝ ነዉ። ትንሿ አልጋዬ ላይ ግራ ቀኝ እያልኩ ተገለባበጥኩ። እንቅልፍ ተጎትቶ የሚመጣ ይመስል አሁንም አሁንም ላይ ታች እያልኩ አልጋዉ ላይ እራሴን ጎተትኩት . . . እንኳን እንቅልፍ ሊወስደኝ ጭራሽ አይኖቼ መርገብገባቸዉን ያቆሙ ይመስል ቀጥ ብለዉ ቀሩ። ከተጋደምኩበት ብድግ ብዬ መብራቱን አበራሁና ለመንገድ ከያዝኳቸዉ ሁለት መጻህፍት አንዱን አዉጥቼ ማንበብ ጀመርኩ። እኔ ላንብበዉ ወይ መጽሀፉ ያንብበኝ አላዉቅም። ጧት ስነሳ ግን “The Architecture of Democracy” የሚል መጽሐፍ ደረቴ ላይ ተለጥፎ ነበር። ሰዐቴን ሳየዉ ከሌሊቱ ስምንት ሰዐት ተኩል ይላል። ከአልጋዬ ላይ ዘልዬ ወረድኩና ሰዉነቴን ታጥቤ ልብሴን ከለበስኩ በኋላ መኪናዉ ዉስጥ ገብቼ “I’m ready” አልኩ። የመኪናችን መብራት ጨለማዉን እየገላለጠዉ የአስመራ ከረንን መንገድ ተያያዝነዉ። መኪናዉ ዉስጥ ከገባሁ በኋላ እንደገና አፌን የከፈትኩት ባሬንቱ ደርሰን ቁርስ ሳዝ ነዉ። ባሬንቱ በግዜ መድረሳችን ደስ ቢለኝም የቀረን መንገድ ርዝመት ታየኝና ቁርስ መብላቴን ትቼ . . . በሰዐት ይህን ያክል ብንጓዝ እያልኩ ዋናዉ ጉዳያችን ቦታ የምንደርስበትን ሰዐት ማስላት ጀመርኩ። የስሌቱ ዉጤት ከሦስት ሰዐት ሲበልጥብኝ ተናደድኩ። ቀሪዉ መንገድ ገና ሳልጀምረዉ ሰለቸኝ። በተፈጥሮዬ መንገድና መኃላ ሲረዝም አልወድም።Patriotic Ginbot7 fighters
ተሰነይ ስንደርስ መኪናዉ ዉስጥ የነበረዉ ሰዉ ሁሉ ቡና ካልጠጣሁ አለ። መኪናችንን አቁመን በቁማችን ቡናችንን ፉት አድርገን መንገዳችንን ተያያዝነዉ። እሁድ ጥቅምት 7 ቀን 2008 ዓም አርበኞች ግንቦት ሰባትን የፈጠሩት ሁለት ድርጅቶች ከተዋሃዱ በኋላ ለሁለተኛ ግዜ የሰለጠኑ ታጋይ አርበኞች የሚመረቁበት ቀን ነበር። ከዚህ ቀደም እንደዚህ አይነቱን የምርቃት ዜና የምሰማዉ በኢሳት ሬዲዮና ቴሌቭዥን ብቻ ስለነበር እቦታዉ ደርሼ የምረቃዉን ስነስርዐት ለማየት የነበረኝ ጉጉት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነበር። የምሳ ሰዐት ከመድረሱ በፊት በቀኝ በኩል ዋናዉን መንገድ ለቅቀን ዉስጥ ዉስጡን ወደ ምርቃቱ ቦታ የሚወስደዉን ኮረኮንች መንገድ ተያያዝነዉ።
ግቢዉ ዉስጥ ያለዉ ጥድፊያና ግርግር አንድ ትልቅ ዝግጅት መኖሩን በግልጽ ይናገራል። የተለያየ ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱና መሳሪያ የተሸከሙ አርበኞች ግቢዉን ሞልተዉታል። ያነገቱትን ጠመንጃ ስመለከት ቆራጥነታቸዉ ታየኝ። በቀጭኑ ተጎንጉኖ ማጅራታቸዉ ላይ የወደቀዉን ፀጉራቸዉን ሳይ ቴዎድሮስና ዮሐንስ ትዝ አሉኝ። ፈገግታ በፈገግታ የሆነዉን ፊታቸዉን ስመለከት ደግሞ የእናት አገሬ ኢትዮጵያ ትንሳኤ ደጃፍ ላይ መሆኑ ታየኝና የኔም ፊት እንደነሱ በፈገግታ ተሞላ። ተራ በተራ እየመጡ “ጋሼ አፍሬም” እንደኳን ደህና መጣህ ብለዉ ሲጠመጠሙብኝ በአንዱ ትከሻዬ ፍቅራቸዉ በሌላዉ ጀግንነታቸዉ ዘልቆ ሰዉነቴ ዉስጥ ገባ። ጥንካሬያቸዉ በጅማቴ ፍቅራቸዉ በደም ስሬ ዘለቀ። እኔነቴ ሲታደስና በአገሬ ላይ ያለኝ ተስፋ ሲለመልም ተሰማኝና ደስ አለኝ። አዎ ደስ አለኝ . . . እየመጣ የሚሄድ ግዜያዊ ደስታ ሳይሆን የዉስጥ አካላቴን የዳሰሰ ዘላቂ የመንፈስ ደስታ ተሰማኝ። በጣም ደስ የሚልና በአሁኖቹ ቋንቋ “የሚመች” ቀን ነበር። የዕለቱን ዝግጅት ለማየት መቸኮሌን ያወቁት እግሮቼ የምረቃዉ በዐል ወደሚከበርበት ዳስ- ፍትህ፤ ነጻነትና እኩልነት የናፈቀዉ ልቤ ደግሞ ወደ ወደፊቷ ኢትዮጵያ ይዘዉኝ ጭልጥ አሉ፡ . . . ለካስ የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሩቅ አይደለችም።
“ማነዉ ሚለየዉ . . .ሚለየዉ፤ ይህም ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” የሚለዉን የጃሉድ ዘፈን በርቀት ሲሰማ በቀኑና በዘፈኑ መግጠም ተገረምኩ። “እዉነትም ይህ ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” እያልኩ በለሆሳስ ለራሴ እየነገርኩት ዳሱ ዉስጥ ገብቼ ቁጭ አልኩ። እርግጠኛ ነኝ ይህንን ጽሁፍ የሚያነብ ሰዉ ዳሱ ዉስጥ የነበረዉን ፍጹም ኢትዮጵያዊ የሆነ የጀግንነት፤ የቆራጥነት፤ የእልህና የመተማመን ልዩ ስሜት መረዳት የሚችለዉ እኔ በዚህ ባልተባ ብዕሬ ስገልጸዉ ሳይሆን እንዳዉ በደፈናዉ ዳሱ እራሱ ኢትዮጵያዊ ነበር ብዬ ባልፈዉ ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያ ከራሱ ምቾትና የተደላደለ ኑሮ ይልቅ የወገኖቹ መብትና ነጻነት የሚያንገበግበዉና እራሱን ለፍትህ፤ ለአንድነትና ለነጻነት ለመሰዋት ዝግጁ የሆነ የየዘመኑ ምርጥ ትዉልድ አላት። ይህንን የኛን ዘመን ምርጥ ትዉልድ ነዉ አርቲስት ጃሉድ “ይህም ትዉልድ ፍም እሳት ነዉ” ብሎ በጣፋጭ ዜማዉ ያወደሰዉ። እኔ ጥርጥርም የለኝ ይህ ትዉልድ አንድና ሁለት ብቻ ሳይሆን ለቁጥር የሚታክቱ ብዙ ፍም እሳቶች አሉት። ችግሩ የእሳት ነገር አዚህ ቤት ነደዳ እዚያም ቤት ነደደ ስራዉ ማቃጠል ነዉና አንዱን እሳት ከሌላዉ እሳት መለየት አስቸጋሪ ነዉ። እኔም ችግሬ እዚህ ላይ ነዉ። ፊት ለፊቴ ላይ ቁጭ ብለዉ ስለማያቸዉ ፍም እሳቶች (ጀግኖች) ላወራችሁ እየፈለኩ ምርጫዉ አዋጅ ሆነብኝ. . . የራሱ ጉዳይ ብዬ አንዱን ጀግና መረጥኩ። ይህንን ዛሬ የምተርክላችሁን ጀግና ስመርጥ ግን እንዳዉ በደፈና አልነበረም። ጉዳይ አለኝ . . . . ጉዳዩ አንዲህ ነዉ።
በዕለቱ በተመራቂ አርበኞች ተዘጋጅተዉ ከቀሩቡት የተለያዩ የኪነት ስራዎች ዉስጥ አንዱ የድራማ ዝግጅት ነበር። ሦስት የተለያዩ ድራማዎች መታየታቸዉ ትዝ ይለኛል። ዳሱ ዉስጥ የተሰበሰበዉን በብዙ መቶዎች የሚቆጠር ሰዉ ስሜት የኮረኮረዉና የእያንዳንዱን ሰዉ የልብ ትርታ ሰቅዞ የያዘዉ ግን በእዉነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተከወነዉ የመጨረሻዉ ድራማ ነበር። ድራማዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለይ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ የአርበኞች ግንቦት 7 አባላት ናችሁ እየተባለ በየቀኑ በህወሃት የደህንነት ሠራተኞች እጃቸዉ እየታሰረ በየወንዙና በየፈፋዉ በግፍ እየተገደሉ ስለሚጣሉ ኢትዮጵያዉያን የሚተርክ ድራማ ነበር።
ድራማዉ “ኮሜዲ” የሚባል ክፍል የለዉም። ተጀምሮ እስኪያልቅ “ትራጄዲ” ብቻ ነዉ። ያሳዝናል፤ ያስቆጣል፤ ያስቆጫል፤ያንገበግባል፤ አንጀት ያቆስላል፤ ልብ ያነድዳል . . . ወይ ነዶ ያሰኛል ። እኔማ እንኳን ትራጄዲ አይቼ በተፈጥሮዬ ሆደ ቡቡ ነኝና በደል ስመለከት ማዘን ልማዴ ሆኖ አምባዬ መፍሰስ የጀመረዉ ገና ድራማዉ ሲጀምር ነበር። በተለይ አናታቸዉ እየተደበደበ የሚቀበሩበትን ጉድጓድ በግድ እንዲቆፍሩ የተደረጉትን ሁለት ወጣት ወገኖቼን ሳይ ሆዴ ባባ፤ አንጀቴም ቆሰለ። ልቤ ዉሰጥ የነደደዉ እሳት ትንታጉ እየተንቦገቦገ ወጥቶ የዉጭ ሰዉነቴን ጭምር ለበለበዉ። ለወትሮዉ ነገር ማመዛዘን የሚቀድመዉ አዕምሮዬ በቀል በቀል አሰኘዉ። የነደደዉ ልቤም ለበቀል አደባ። ጉድጓዱ ተቆፍሮ ካለቀ በኋላ የደህንነት ሠራተኛዉ AK ጠመንጃዉን አንደኛዉ ወጣት አገጭ ላይ ቀስሮ በአፈሙዙ አንገቱን ቀና እንዲያደርግ እያስገደደዉ . . . “አየኸዉ የምትገባበትን ጉድጓድ” እያለ ወጣቱ ወገኔ ላይ ሲሳልቅበት ሰማሁና በሀይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ ኢትዮጵያዊነቴን ጠላሁት። አጠገቡ የቆመዉና በቁሙ ሞቱን የሚጠባበቀዉ ሌላዉ ወጣት ወገኔ ደግሞ . . . ግደለኝ . . . ግደለኝ. . . ግደለኝ እንጂ! . . . ምን ትጠብቃለህ እያለ የጓደኛዉን ሞት በአይኑ ከሚያይ የራሱን ሞት የሚለምነዉን ቆራጥ ኢትዮጵያዊ ድምጽ ስሰማ ደግሞ 360 ዲግሪ ተገለበጥኩና ከደቂቃዎች በፊት የጠላሁትን ኢትዮጵያዊነት መልሼ ወድድ አደረኩት። የወያኔዉ ጨካኝ ነብሰ ገዳይ ፉከራና ቆራጡ ኢትዮጵያዊ ያደረጉት የቃላት ምልልስ እምባዬን ጎትቶ አመጣዉና ፊቴ እምባ በእምባ ሆነ። ያ ከግማሽ ሰዐት በፊት ሲጨፈርበትና ሲደነስበት የነበረዉ ዳስ ሰዉ የሌለበት ባዶ ቤት ይመስል ጭጭ አለ። እኔ ኤፍሬም ሰዉ አልገድልም፤ በእኔ እጅ የሰዉ ህይወት ይጠፋል ብዬ አስቤም አልሜም አላዉቅም። ያንን የህወሃት ቅጥረኛ በዚያች ሰዐት ባገኘዉ ኖሮ ግን ለመበቀል ሳይሆን ለሰዉ ልጅ ህይወት ክብር ስል እገድለዉ ነበር።
ድራማዉ እንዳለቀ ወደ ዉጭ ወጣሁና ድቅድቅ ጨለማ ዉስጥ ብቻዬን ቁጭ አልኩ። ሀሳብ. . . የትናንት ሀሳብ፤ የዛሬ ሃሳብ፤ የነገ ሀሳብ፤ የከረመ ሀሳብና ሁሉም ሀሳብ አንድ ላይ ተሰባስበዉ ወረሩኝ። ግራ ሲገባኝና መላቅጡ ሲጠፋኝ ግዜ ትንፋሼን ዋጥ አደረኩና አንቺ እማማ ብዬ አገሬን ተጣራሁ . . . አሁንም አሁንም ደግሜ ተጣራሁ። ህመሟ ብርቱ ነበርና አልሰማችኝም። አይዞሽ ይህ ቀን ያልፍና አንቺም ከህመምሽ እኔም ከማያባራዉ የሀሳብ በሽታ ድነን አዲስ ታሪክ እንጽፋለን ብዬ ከአገሬ ጋር ቃል ኪዳን ገባሁና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ዳሱ ዉስጥ ከነበሩት አርበኞች ጋር ተቀላቀልኩ። እለቱን ሲያስጨፍረን የዋለዉ አደራ ባንድ “ነይ ደኑን ጥሰሺ” የሚለዉን ቆየት ያለ የመሀሙድ አህመድ ዘፈን ሲጫወት ልጅነቴ ትዝ አለኝና ከፍም እሳቶች ጋር መደነስ ጀመርኩ።
ጭልጋን ይዞ፤ጋይንትን ይዞ፤ የጎበዞቹን ጎራ ጃናሞራን ይዞ፤ ደምቢያን ይዞ፤ ወልቃይት ጠገዴን ይዞ፤ ላይ አርማጭሆንና ታች አርማጭሆን ይዞ ወዘተ . . .ድፍን ጎንደር የጀግኖች አገር ነዉ። አዎ! ወልቃይት ጠገዴ ከጀግናም የጀግና አገር ነዉ።ወልቃይት ጠገዴ ጎንደሬ አይደለህም ተብሎ ከተነገረዉ ከሃያ አራት አመታት በኋላ ዛሬም ህልዉናዉን ለወያኔ ፋሺስቶች አላስረክብም ብሎ ጎንደሬነቱን ለማረጋገጥ ሽንጡን ገትሮ የሚዋጋ የጀግኖች አገር ነዉ። ጎንደር የአፄ ቴዎድሮስ፤ የእቴጌ ምንትዋብ፤ የፊትአዉራሪ ገብርዬ፤ የአየለ አባ ጓዴና የጄኔራል ነጋ ተገኝ አገር ናት። ጎንደር ኢትዮጵያ ከሌለች እኛ የለንም ብለዉ ሙሉ ህይወታቸዉን ለትግል የሰጡ እነ ታማኝ በየነንና እነ አርቲስት ሻምበል በላይነህን ያበቀለች አገር ናት። ወላድ በድባብ ትሂድ. . . የጎንደር ማህፀን ዛሬም አልነጠፈም።
ዛሬ ይዤላችሁ የመጣሁት ጀግና ተወልዶ ያደገዉ አማራ ክልል ጭልጋ ወረዳ ልዩ ስሟ ጫኮ በምትባል ቦታ ነዉ። የገበሬ ልጅ ነዉ፤ እሱም ምኞቱ ገበሬ መሆን ነዉ። የሚኖረዉ መተማ ከተማ ዉስጥ ነዉ። ስሙ መሠረት ሙሌ ይባላል። ፈገግታ የማይለየዉ ፊቱ የዋህነቱንና ገራገርነቱን አፍ አዉጥቶ ይናገራል። ሲናገር ረጋ ብሎ ነዉ። አተኩሮ ላየዉ ሰዉ አይነ አፋር ይመስላል፤ የቁርጥ ቀን ሲመጣ ግን እንደ መሠረት ሙሌ ደፋር ሰዉ የለም። አይኑ እፊቱ ላይ ቆሞ ከሚያናግረዉ ሰዉ አይን ጋር ሲጋጭ አንገቱን ይሰብራል። እቺ የሰዉ አይን የመሸሽ በሽታ ደግሞ አበሾች ስንባል የሁላችንም በሽታ ናት። ጠይም ፊቱ ላይ እንደ ችቦ የተተከሉት የመሠረት ሙሌ አይኖች የሰዉን ዉስጥ ዘልቀዉ የሚያዩ ይመስላሉ። ሰዉነቱ ደንዳና ቁመቱ መካከለኛ ነዉ። ልቡ ግን ትልቅ ነዉ። አዎ መሠረት ሙሌ ልቡ ትልቅ ነዉ።
ዕለቱ ሰኞ ነዉ – ሰኞ ሚያዝያ 26 ቀን 2007 ዓም። የህወሃት የደህንነት ሰዎች አንድ ኮሎኔልና ሌሎች አራት ሰዎች ተገድለዋል በሚል ድፍን መተማን እያመሷት ነዉ። እያንዳንዱ የመተማ ነዋሪ በግድያዉ የተሳተፈ ይመስል በአጠገባቸዉ ያለፈዉን ሁሉ ወንድ፤ ሴት፤ ወጣትና ሽማግሌ ሳይለዩ ሁሉንም እያስቆሙ አጥንት ዉስጥ ዘልቆ የሚገባ ስድብ ይሰድባሉ፤ ይደበድባሉ ያስራሉ። በሠላም አዉለኝ ብሎ በጧት የተነሳዉ መሠረት ሙሌ የእህል ወፍጮዉን አስነስቶ የዕለት ስራዉን ለመጀመር ጉድ ጉድ ማለት ጀምሯል። ሴቶች እህላቸዉን ያስመዝናሉ። ሸክም የተራገፈለት አህያ ያናፋል። ነጋዴዉ፤ ደላላዉ፤ ገበሬዉና ሸማቹ ዋጋ ቀንስ ዋጋ ጨምር እያሉ ይንጫጫሉ። መተማ መደበኛ ስራዋ ላይ ናት።
“ቁም . . . እጅ ወደ ላይ . . . እንዳትነቃነቅ” የሚል ድምጽ የደራዉን የመተማ ገበያ በአንድ ግዜ ጭጭ አሰኘዉ። መሳሪያ ያነገቡ ፖሊሶችና ሲቪል የለበሱ የደህንነት ሰራተኞች ከመኪና እየዘለሉ ወርደዉ መሠረትን የፊጥኝ አስረዉ መኪናዉ ላይ ወረወሩት። ምነዉ? ምን አጠፋሁ . . . ዬት ነዉ የምትወስዱኝ? አለ መሠረት በሁኔታዉ እጅግ በጣም ተደናግጦ። አንድ አጠገቡ የነበረዉ የህወሃት ነብሰ ገዳይ . . . ዝም በል ብሎ በጥፊ አጮለዉና ለአርበኞች ግንቦት 7 የመለመልካቸዉን ሰዎች አድራሻና ስም ዝርዝር ካላመጣህ ዕድሜህ ከአንድ ጀምበር አያልፍም አለዉ።
መኪናዉ ዉስጥ ከተቀመጡት ሁለት ሰዎች አንደኛዉ አንሂድ ብሎ በእጁ ምልክት ሲያሳይ መሬት ላይ የነበሩት ፖሊሶች እየዘለሉ መኪናዉ ላይ ወጡና መሠረትንና ሌሎች ሦስት እስረኞችን የያዘችዉ ቶዮታ ሂሉክስ መኪና ፍጥነት እየጨመረች የመተማ ሁመራን መንገድ ተያያዘቸዉ። በሚቀጥለዉ ቀን ጧት ሲነጋጋ ሁመራ ደረሱና አራቱ እስረኞች እጃቸዉ እንደታሰረ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ ተደረገ። ከምሽቱ ሦስት ሰዐት ሲሆን መሠረትና ጓደኞቹ እጅ ለእጅ እንደተሳሰሩ ጉዞ ወደ ተከዜ ወንዝ ሆነ። የዚህች ከንቱ አለም የመጨረሻ ጉዟቸዉ ነበር።
ዶማና አካፋ ያዙ እንጂ . . . ደግሞም ፈጠን በሉ ግዜ የለንም. . . አለ የነብሰ ገዳዮቹ አለቃ። ከሁመራ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ተከዜ ወንዝ የሚያደርገዉ ጉዞ በህይወቱ የመጨረሻዉ ጉዞ እንደሆነ የተረዳዉ መሠረት . . . አንተዬ ልትገድሉን ነዉ እንዴ ብሎ ጠየቀ። ፊት ለፊቱ የነበረዉ ፖሊስ ከተቀመጠበት ዘልሎ ተነሳና . . .ዝም በል . . . አንተ የሴት ልጅ . . . ምን አስቸኮለህ ይልቅ የተጠየከዉን ጥያቄ መልስ አለዉና የያዘዉን የእጅ መከርቸሚያ ካቴና ፊቱ ላይ ወረወረበት። ካቴናዉ ሳይሆን ከዚያ ባለጌ አፍ የወጡት ቃላት ጅማቶቹ ድረስ ዘልቀዉ ገብተዉ መንፈሱን ጎዱትና መሠረት ለመጀመሪያ ግዜ ተስፋ ቆረጦ . . . ምንም የምሰጥህ መልስ የለኝም አለና አንገቱን ደፋ። . . . አንቺ ወላዲት አምላክ ምነዉ . . . ምን አደረኩሽ ብሎ ቀና ሲል እሱንና ሦስት ጓደኞቹን ለመዋጥ አፋቸዉን ከፍተዉ የሚጠባበቁትን አራት ጉድጓዶች ተመለከተ። አይኔ እያየ እዚህ ወስጥ አልገባም ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ተከታታይ የጥይት ድምጽ ሰማ። ዞር ሲል ፖሊሶች አብረዉት ከታሰሩት ሦስት እስረኞች ዉስጥ አንዱን በእግራቸዉ እየገፉ የተቆፈረዉ ጉድጓድ ዉስጥ ሲጨምሩት አየ። ደቂቃዎች የቀሩት የሱ የራሱ ህይወት ሳይሆን በህወሃት ነብሰ ገዳዮች በግፍ የተገደለዉ የጓደኛዉ ህይወት አንገበገበዉ። አዘነ – በአይኑም በሆደም አነባ። “አይኔ እያየ እዚህ ወስጥ አልገባም” ብሎ የተናገረዉ የራሱ ድምጽ ጆሮዉ ላይ አቃጨለበት። መሠረት ሞት ፈርቶ አያዉቅም፤ ግን ህይወቱ የህይወትን ክቡርነት በማይረዱ ባለጌዎች እጅ እንድታልፍ አልፈለገም። ያ የንጹሃን ኢትዮጵያዉያንን ሰዉነት ማፍረስ የለመደዉ የህወሃት ጠመንጃ ወደሱ ከመዞሩ በፊት አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ ብሎ ወሰነ። እጁ ከጓደኛዉ ጋር የታሰረበትን ገመድ በጥርሱ በጣጠሰዉና ከቀለሁ እንደተላቀቀ ጥይት ተወርዉሮ እግሬ አዉጭኝ ብሎ ጫካ ዉስጥ ዘልሎ ገባ። የህወሃት ነብሰ ገዳዮች የጥይት ናዳ ለቀቁበት፤ እሱ ግን ጫካ ጫካዉን ይዞ ወደማያዉቀዉ ቦታ ሩጫዉን ተያያዘዉ።
መሠረት- ቆራጥነቱና የልቡ ትልቅነት ጉልበት እየሆኑት ነዉ እንጂ ያ የሚጠላዉ የህወሃት ጥይት አካሉን በሳስቶ ወንፊት አድርጎታል። ሰዉነቱ ቁስል በቁስል ሆኗል። ከራሱ ሰዉነት እንደ ጎርፍ የሚፈስሰዉ ደም ጠልፎ የሚጥለዉ እስኪመስለዉ ድረስ አካሉ ደምቷል። ሩጫዉን ግን አላቆመም። ደም እንዳይፈሰዉ ጥይት የበሳዉን ቦታ ሁሉ በሁለት እጆቹ ሸፈነ። እንደኛዉ ቁስል ጋብ ሲልለት እጁን ከሱ ላይ እያነሳ ሌላዉን ቁስል ሸፈነ። ደሙ መፍሰሱን ግን አላቆመም። መሠረትም ሩጫዉን አላቆመም። መሠረት ሙሌ ህይወቱን ለማዳን ወደ ፊት የህወሃት ነብሰ ገዳዮች ደግሞ ወንጀላቸዉን ለመደበቅ ወደኋላ በተለያየ አቅጣጫ ሩጫቸዉን ተያያዙት። ሁለቱም አግሬ አዉጭኝ አሉ።
መሠረት ሞትን እየሸሸ መሆኑን ነዉ እንጂ ከሞት ለመራቁ ምንም ዋስትና አልነበረዉም። ደግሞም መሮጡን ብቻ ነዉ እንጂ ወዴት እንደሚሮጥ አያዉቅም ነበር። ከኋላዉ የሚከተለዉ ማንም ሰዉ እንደሌለ ቢረዳም ከፊት ለፊቱ ህይወቱን የሚታደግለት ሰዉ እስኪያገኝ ድረስ ሩጫዉን ቀጠለ። ጧት ጎህ ከመቅደዱ በፊት “ጠጠዉ በል” የሚል ድምጽ ሲሰማ ያ ሁሉ ሩጫዉ መልሶ ሞት ዉስጥ የከተተዉ መሰለዉና ደነገጠ። ሩጫዉን እንዳይቀጥል ቁም ያሉት ሰዎች ከበዉታል። እሺ ብሎ እንዳይቆም ሞትን አልቀበልም ያለዉ ልቡ አሁንም እንደደነደነ ነዉ። ትንፋሹን ሰበሰበና. . . ማናችሁ እናንተ ብሎ ያቆሙትን ሰዎች ጥያቄ ጠይቆ መልሱን ሳይሰማ ተዝልፍለፎ መሬቱ ላይ በግንባሩ ተደፋ።
የኤርትራ ድንበር ጠባቂ ወታደሮች መሠረትን አንድ ወር ሙሉ በህክምና ሲንከባከቡት ቆዩና እሱ እራሱ በጠየቃቸዉ መሠረት ሃሬና ወስደዉ ለአርበኞች ግንቦት 7 አስረከቡት። መሠረት ሙሌ ጥቅምት 7 ቀን ከተመረቁት አርበኞች ዉስጥ አንዱ ነዉ። ለዚህ ጀግና ያቀረብኩለት የመጨረሻ ጥያቄ . . . ሊገድሉህ የነበሩትን የህወሃት ሰዎች አሁን ብታገኛቸዉ ምን ታደርጋቸዋለህ የሚል ጥያቄ ነበር። ነጻ አወጣቸዋለኋ! አለኝና ጭፈራዉ ዉስጥ ዘልሎ ገባ። አርግጠኛ ነኝ መሠረት ሙሌ አንድ ቀን ሁላችንንም ሸገር ላይ ያስጨፍረናል። ቸር ይግጠመን።
ኤፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር
ebini23@yahoo.com

የህወሓት አገዛዝ የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት የነበሩትን እየለቀመ እያባረረ ነው

October 31,2015
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ እንደዘገበው) ህወሓት በ1983 ዓ.ም መላ አገሪቱን በነፍጥ እንደተቆጣጠረ በሁለት ያለፉ የኢትዮጵያ መንግስታት ከፍተኛ የህዝብ ሀብት፣ ዕውቀትና ጉልበት ፈሶበት ለዘመናት በስንት ልፋትና ጥረት የተገነባውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ባደረበት ጭፍን ጥላቻና ቂም ብቻ ተመስርቶ “የደርግ ነው” በሚል ሰበብ ባንድ ጀምበር ንዶ ማፈራረሱን አገር ያወቀው ፀሃይ የሞቀው ሀቅ ነው፡፡
(ፎቶ ፋይል መፍቻ) የሕወሓት መንግስት በስማቸ እየነገደ ገንዘቡን የሚበላባቸው የኢትዮጵያ መከላከያ ወታደሮች በሱማሊያ ሬሳቸው ሲጎተት::

(ፎቶ ፋይል መፍቻ) የሕወሓት መንግስት በስማቸ እየነገደ ገንዘቡን የሚበላባቸው የኢትዮጵያ መከላከያ ወታደሮች በሱማሊያ ሬሳቸው ሲጎተት::



ከበረሃ የመጡ ድኩማን ታጋዮቹን ለሙያው የሚመጥን ምንም አይነት ዘመናዊ ዕውቀት ሳይኖራቸው የጀነራልነት ማዕረግ በማሸከም በአየር ኃይሉና በምድር ኃይሉ ውስጥ በሚገኙ የአዛዥነት ቦታዎች ላይ እነሱን ብቻ አስቀምጦ ስልጣኑን ለመጠበቅ ብቻ እንዲተጉለት በማድረግ የአገራችንን ብሄራዊ ደህንነት አደጋ ላይ ጥሎት ይገኛል፡፡

ህወሓት የተባለው ዘረኛ ቡድን ውስጡ በቂምና በጥላቻ ብቻ ተሞልቶ ያፈራረሰውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት አደጋ ባንዣበበበት ጊዜ ጥሪ በማድረግ መልሶ ለመሰብሰብ የሞከረ ሲሆን ከጦርነቱ በኋላ ደግሞ አብዛኞቹን ከተጠቀመባቸው በኋላ እንደገና አባሯቸዋል፡፡

አሁን ደግሞ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ እያፋፋመው ከሚገኘው የአርበኝነት ትግል ጋር በተያያዘ ከትግራይ ተወላጅ የህወሓት ተጋዮች ውጭ በሆኑ ወታደራዊ አዛዦች ላይ ዕምነት በማጣቱ የመከላከያ ኃይሉን የማጥራት የወቅቱ አንገብጋቢ ውሳኔውን የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላትን በማባረር ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል፡፡

ቂምና በቀሉ መቸም የማይበርድለት ህወሓት በተደጋጋሚ የደም ቁማር ሲቆምርባቸው ከኖሩት የተባረሩ የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት አብዛኞቹ የአርበኝነት ትግሉን በመቀላቀል ላይ ናቸው፡፡

Wednesday, October 28, 2015

Andargachew Tsege ‘fears he will die in Ethiopia’

October 27,2015
A British man locked up for more than a year in Ethiopia fears he could die in prison.
Andargachew “Andy” Tsege, a father-of-three, has been detained in the country since he was removed from an airport in Yemen in June 2014.UK “stands shoulder to shoulder” with Ethiopia
Legal charity Reprieve said the 60-year-old asked the British Government to ensure that he is buried in England and told his children to “be brave” during a recent visit by the UK ambassador.
Mr Tsege, a prominent critic of Ethiopia’s ruling party, was sentenced to death in his absence in 2009 for allegedly plotting a coup – charges he and others deny.
The trial has been described as “lacking in basic elements of due process”.
He fled Ethiopia in the 1970s, seeking asylum in the UK in 1979.
Maya Foa, head of the death penalty team at Reprieve, said: “It is tragic that he now feels the only way he will return home to Britain is in a coffin.
“The Foreign Office must urgently push for his release, so he can return to his partner and children in London before it’s too late.”
Last week, Foreign Secretary Philip Hammond discussed the case with the Ethiopian Foreign minister.
Mr Hammond said: “I raised the case of Andargachew Tsege with the Ethiopian Foreign Minister during our meeting on October 21, and made it clear that the way he has been treated is unacceptable.
“I welcome the improvement in access to him, following the British Government’s intervention, but it must be more regular and it must include access to a lawyer.
“I am still not satisfied that Mr Tsege has been given an ability to challenge his detention through a legal process, and this is something we are continuing to pursue.
“The Foreign Office will continue to provide consular support to Mr Tsege and his family.”
Source: BT.com