Friday, August 7, 2015

የፕሬዚዳንት ኦባማ የአፍሪካ ኅብረት ንግግርና እንደምታው

August 7, 2015
def-thumbየዩ ኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባ ውስጥ በአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ያደረጉት ንግግር በርካታ ቁምነገሮችን የያዘ በመሆኑ አንጽዖት ሊሰጠው እንደሚገባ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው የአፍሪቃን በተለይም ደግሞ የአገራችንን ችግሮች ነቅሰው አሳይተዋል። ሰብዓዊ መብቶች ሰው በመሆናችን ያገኘናቸው በመሆኑ በቆዳችን ቀለም፣ በተወለድንበት አካባቢ፣ በምንናገረው ቋንቋ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያቶች ሊሸራረፉ የማይገቡ መሆኑን በመግለጽ “ሁላችንም እኩል ተወልደናል” በማለት ዘረኞችን አፍ የሚያዘጋ ኃይለቃል ተናግረዋል። “ሁላችንም ከአንድ ግንድ የበቀልን ነን፤ ሁላችንም አንድ ቤተሰብ ነን፤ ሁላችንም አንድ ጎሳ ነን” ካሉ በኋላ በዓለም ያለው አብዛኛው ችግር ይህንን መረዳት አለመቻላችን፤ ራሳችንን በእያንዳንዳችን ውስጥ ማየት አለመቻላችን ነው ብለዋል።
ይሁን እንጂ በብዙ የአፍሪቃ አገሮች፣ ዜጎች ነፃነታቸው የተገፈፈ መሆኑን፤ ምርጫ መኖሩ ብቻ ዲሞክራሲ ሰፈነ ማለት አለመሆኑ አብራርተዋል። ጋዜጠኞች፣ የተቃውሞ ፓለቲካ መሪዎችና ግንባር ቀደም ተሳታፊዎች፣ የሲቪክ እንቅስቃሴዎች መሪዎችን በእስር ቤት እያጎሩ ወይም በነፃነት እንዳይቀሳቀሱ እያደረጉ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አደረግን የሚሉ አገሮች መኖራቸው ለመግለጽ ኢትዮጵያን በዋቢነት ጠርተዋል።
ፕሬዚዳንት ኦባማ የሰላምና የደህንነት ጉዳይ ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን በሰፊው ከገለጹ በኋላ ለሰላም ሲባል ነፃነትን መንፈግ ሁለቱንም ሊያሳጣ የሚችል መሆኑም አስገንዝበዋል።
እድገትን በማፋጠን ዜጎችን ከድህነት ለማውጣት አዲስ አስተሳብ ያሻል፤ ለአዲስ አስተሳሰብ ደግሞ በነፃነት ማሰብ፤ ድምፃቸው የሚሰማ ዜጎች መኖር እና የሰብዓዊ መብቶች መከበር ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል። የአፍሪቃ መሪዎች ሥልጣን ላለመልቀቅ የሚሄዱትን ርቀት በማንሳት ተሳልቀውበታል፤ ሙስናም የልማትና የመልካም አስተዳደር ፀር መሆኑን አስምረውበታል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ፕሬዚዳንት ኦባማ ይኸ ቀራቸው በማይባል ሁኔታ በአህጉራችን በአፍሪቃ በተለይ በኢትዮጵያ የሰፈነው ክፉ አገዛዝ መተቸታቸው፤ ይህንን እዚያው የአፍሪቃ መዲና በሆነችሁ አዲስ አበባ ተገኝተው መናገራቸው በበጎ ይመለከተዋል። እሳቸው ያነሷቸውን ቁም ነገሮችን አድምጠው ማስተካከያዎችን የሚያደርጉ ገዢዎች ኑረውን ቢሆን ኖሮ የኛ ትግል ባላስፈለገ ነበር። ችግሩ መስማት እንጂ ማዳመጥና መተግበር የማያውቁ ገዢዎች የሰፈኑብን መሆኑን ነው።
ስለሆነም፣ አርበኞች ግንቦት 7: ፕሬዚዳንት ኦባማ በአፍሪቃ ኅብረት ንግግራቸው ሀቁን አብጠርጥረው በመናገራቸው የተሰማውን አድናቆት ይገልፃል፤ በዚሁ አጋጣሚ ደግሞ በንግግራቸው ያነሷቸው ቁምነገሮችን መደመጣቸውና በተግባር መተረጎማቸውን እንዲከታተሉ አበክሮ ይጠይቃል።
የፕሬዚዳንት ኦባማ ንግግር በሀቅ ላይ የተመረኮዘ በመሆኑ የህወሓት ሽማምንት የተከፉ ቢሆንም የኢትዮጵያን ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እውነታ የመቀየር ኃላፊነት የእኛው የኢትዮጵያዊያን ኃላፊነት መሆኑን በመረዳት፤ ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያለን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ተባብረን አገራችን ከዘረኛውና ፋሽስታዊ ህወሓት አገዛዝ ነፃ የማውጣት ተጋድሎዓችን አጠናክረን እንድንቀጥል አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Tuesday, August 4, 2015

በሙስሊም እንቅስቃሴ መሪዎች ላይ የተሰጠውን ፍርደገምድል ፍርድን እናወግዛለን!

August 4, 2015
def-thumbየህወሓት አገዛዝ የሚዘውረው የይስሙላ ፍርድ ቤት ዛሬ ሀምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. በሙስሊም ወገኖቻችን መሪዎች ላይ ፍርደገምድል ውሳኔ ሰጥቷል። በዚህ ውሳኔ መሠረትም የእምነት መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው በሰላማዊ በሆነ መንገድ የጠየቁ ወገኖቻችን መሪዎች እስከ 22 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።
ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸው ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። ሥርዓቱ ያደረገውን ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን ተቋቁመው “ድምፃችን ይሰማ!” የሚል አቤቱታ ከማቅረብ የዘለለ አንዳችም የኃይል እርምጃ ወስደው አያውቁም። ሆኖም “በደል ደርሶብኛልና ልሰማ” ብሎ አቤቱታ ያቀረበ ሕዝብ መሪዎችን እስከ ሃያ ሁለት ዓመታት በእስር መቅጣት የአገዛዙ እብሪትና ማናለብኝነት አጉልቶ የሚያሳይ ተግባር ነው።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህን ፍርደገምድል ውሳኔ አጥብቆ ያወግዛል።ይህ ፍርደገምድል ውሳኔ የተሰጠው ፕሬዚዳንት ኦባማ በአገራችን መዲና ተገኝተው “ለሰላም ሲባል ነፃነትን ማፈን ሁለቱንም ያሳጣል” ባሉ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ መሆኑ አገዛዙ የሚሰማ ጆሮ የሌለው መሆኑ የሚያረጋግጥ ሆኗል።
የሙስሊም መሪዎች በእስር ላይ በነበሩት ጊዜ በምርመራ ስም ተደብድበዋል፤ ክብራቸው ተደፍሯል፤ የተለያዩ ዘግናኝ ሰቆቃዎች ተፈጽሞባቸዋል፤ የሀሰት ዶክመንታሪ ፊልሞች እንዲሰራጩ ተደርገው ስማቸውን ለማጥፋት ሙከራ ተደርጓል።
በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል ሃይማኖት ሳይለይ በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰ በደል ነው፤ መፍትሄ የምናገኘውም በጋራ በምናደርገው ትግል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና የአገር አንድነት የሚጠብቅ የመንግሥት ሥርዓት ስናቆም ነው። ከዚህ በመለስ የሚገኝ መፍትሄ የለም። የእምነት መብቶች የሚከበሩት ሰብዓዊ መብቶች ሁሉ ሲከበሩ እንደሆኑ “በድምፃችን ይሰማ” ሥር የተሰባሰቡ ወገኖቻችን ይረዳሉ ብለን እናምናለን።
አርበኞች ግንቦት 7 ሙስሊም ወገኖቻችን ለዓመታት ያለመታከት ያካሄዱትን ትግል ያደንቃል። ከእንግዲህ ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዘን፤ ተደጋግፈን በመታገል ህወሓትን አስወግደን በምትኩ ለሁላችንም የምትመች አገር እንድንገነባ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

Ethiopia hands lengthy prison terms to Muslim activists

August 4, 2015
(Reuters) – Aug 3 An Ethiopian court sentenced 17 Muslim activists on Monday to prison sentences ranging from seven to 22 years on charges they plotted to create an Islamic state in the majority Christian country.Ethiopian Muslims Arbitration Committee
A journalist for a Muslim newspaper was also sentenced for conspiring with the activists, the court in Addis Ababa said.
The defendants, who all denied the charges, were arrested in 2012 on charges of plotting to stage attacks to create an Islamic state in Ethiopia, which has a sizable Muslim minority.
The sentencing comes as Ethiopia faces increasing scrutiny from human rights groups that have regularly accused it of arresting activists, journalists and bloggers to stamp out dissent. The government dismisses the allegations.
The activists were arrested during protests between 2011 and 2013 by Muslims – a rare event in this tightly-controlled country – who accused the government of interference in their affairs. Officials have denied this.
The protesters accused the government of trying to impose a little-known Islamic sect called Al Ahbash on the country’s Muslim population as a moderate bulwark against the hardline Islam it believes is being spread by extremist preachers.
Ethiopian Muslim leaders say their community follows traditional Sufi-inspired Islam and not any radical movement.
The court sentenced four of the activists to 22 years in jail, five to 18 years, another five to 15 years and four defendants to seven years behind bars. One in the last group was the journalist working for the Muslim newspaper.

Saturday, August 1, 2015

የናትናኤል ፈለቀ ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

August 1, 2015
ናትናኤል ፈለቀ (ከቂሊንጦ እስር ቤት) – ምንጭ ዞን9 ፌስቡክ ገጽ
An economist by training and a human right activist by interest.
ናትናኤል ፈለቀ
ይህንን ጽሁፍ ስጽፍ ዓላማዬ ማዕከላዊ ያሉ ሥራቸውን አክብረው የኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ፖሊሶችን (ምናልባትም በአንድ እጅ ጣቶች ተቆጥረው የሚያልቁ መርማሪዎችን) ለማበረታታት አይደለም፡፡ ይህን ዓላማ በሌላ ጽሁፍ እመለስበት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ሥራቸውን አክብረው የሚሰሩ ባለሙያ ፖሊሶች የኔ ማበረታታትን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ ያሉበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በኃላፊነት ማሰብ የቻሉ ስለሆኑ፡፡
ስለዚህ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በተቋሙ ውስጥ ኢትዮጵያ የምትተዳደርባቸውን ሕጎች ለማክበር (የተላለፉትን ለይቶ ለማስቀመጥና በስህተት የተጠረጠሩትን ነጻ ለማውጣት) ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማርዘም የሚሰሩትን አብዛኞቹን ሙያቸውን የማያከብሩ ፖሊሶች ‹‹ምርመራ›› ሴራቸውን እንዴት እንደሚፈትሉ ለማሳየት፣ ቢያንስ ሌላ ስልት እስኪፈጥሩ ድረስ በሀገሪቷ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ኢትዮጵያውያን አንዴ በተቋሙ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችለውን የተንኮል መረብ ለማስረዳት እና ቀድሞ ለማዘጋጀት ያሰበ ነው፡፡
እውነት ለመናገር እነዚህ የስርዓቱ ጠባቂ ሎሌዎች የህዝብን ደህንነት ለአደጋ የሚያጋልጥ ወንጀልን እና ወንጀለኞችን ለይተው አውቀው ፍትህ እንዲያገኙ አድርገው ጭራሹንም አያውቁም ማለት አልችልም፡፡ ስለዚህ አሁን የማብራራው ጉዳይ ለወንጀለኞችም መዘጋጃ ሊሆን እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ነገር ግን ወንጀለኞች ከፍትህ እንዲያመልጡ ጠብታ ውሃ ማቀበል አልፈልግም፡፡ አንድ ነጻ ሰው ባልሰራው ወንጀል ከሚቀጣ መቶ ወንጀለኞች ቢያመልጡ ይሻላል የሚለው የህግ መርህ የበለጠ አቋሜን ያስረዳል፡፡
ሁለት ማሳሰቢያዎች አሉኝ፤ አንደኛ፡-እኔ ተይዤ ማዕከላዊ እስክገባ ድረስ ልታሰር እንደምችል አስቀድሜ ባውቅም ሊጠብቀኝ የሚችለውን የ‹‹ምርመራ›› ሂደት (የሴራ መረብ የበለጠ ይገልጸዋል) አጽንዖት ሰጥቼ አላሰብኩበትም፡፡ የምርመራው ሂደትን ተንተርሼ የማነሳቸውን ሀሳቦች የተረዳሁት በምርመራ ውስጥ ካለፍኩ በኋላ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ይህንን ጽሁፍ የሚያነቡ ሰዎች እኔ በፍርሃት ያላደረኳቸውን ነገሮች እንዲያደርጉ (በምርመራ ሂደት) የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ሁለተኛ ይህንን ጽሁፍ በሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል እና ሀሳቡን ሕገ-መንግስታዊ ድንጋጌዎች በሚፈቅዱት መሰረት በነጻነት የሚገልጽ ሁሉ ጊዜ ሳይሰጥ ቢያነበው እመክራለሁ፡፡
ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሀሳብ የአቃቤ ህግ ምስክር ከተሰማ በኋላ በብይን የተለቀቁ ሙስሊም ወንድሞች መጻፋቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ያ ጽሁፍ የተሻለ የተደራጀ ነው ብየ ስለማስብ እንዲነበብ እጋብዛለሁ፡፡ በተጨማሪም ስርዓቱን የሚደግፉ ሰዎች ይህንን ጽሁፍ በማንበብ ወንጀለኞች ከሚጠቀሙበት ለተሻለ አላማ ያውሉታል ብዬ ስለማስብ ሁለቱም ባያነቡት ይሻላቸዋል፡፡
ወደ ዋናው ሀሳብ ልግባ፤ ከተያዝኩ በኋላ በነበሩ የመጀመሪዎቹ ቀናት ውስጥ የነበሩት‹‹ምርመራዎች›› እውነቱን እና የማውቀውን ብቻ በመናገር እራሴን ነጻ ማውጣት እንደምችል መተማመኛ መስጠትን ያለሙ ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ሚያዝያ 18/2006 (በተያዝኩኝ በማግስቱ ቅዳሜ) የነበረውን ምርመራ ም/ሳጅን መኮንን በተረጋጋ ሁኔታ የምርመራው ሂደት በመከባበር እንደሚቀጥል፣ ልክ እኔ የዕለት ስራየን ለማከናወን ሙያ እንደሚጠይቀው ያክል የፖሊስ ምርመራም ተመሳሳይ እንደሆነ፣ በቁጥጥር ስር የዋልኩት ተጠርጥሬ ብቻ እንደሆነ እና በምርመራው ሂደት ወንጀል አለመፈጸሜ ከተረጋገጠ በነጻ ወደቤቴ እንደምሄድ ነበር ያስረዳኝ፡፡ ይንቁናል የሚል ስሜት አስቀድሞ ስለሚያድርባቸው ተቋሙን እና እራሳቸውንም ከፍ የሚያደርግ ነገር በነዚህ የመጀመሪያ ‹‹የምርመራ››ቀናት ይናገራሉ፡፡
‹‹ይህ የወረዳ ጣቢያ አይደለም፡፡ የክልልም አይደለም፡፡ ይህ የፌደራል ወንጀል ምርመራነው፡፡ ሚኒስትር ደረጃ የደረሱ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር እዚህ ተመርምረዋል›› ነበር ያለኝ ም/ሳጅን መኮንን በአጽንኦት፡፡ ከዚህ ገለጻ በኋላ ነበር ስለህይወት ታሪኬ በመጠየቅ ቃል የመስጠት ሂደቱን የጀመርኩት፡፡
ማስታወሻ- 1. ቃል ያለመስጠት መብት
ቃሌን ያለመስጠት መብት ስላለኝ ቃሌን አልሰጥም ለማለት መጀመሪያ መብቱ እንዳለ ማወቅ ይጠይቃል፡፡ በወቅቱ ይህ መብት እንዳለኝ ማወቄን እጠራጠራለሁ፡፡ አውቅ ከነበረም ግን በፍጹም ትዝ አላለኝም፡፡ ቃል አለመስጠት አንድ ለምርመራ ሂደቱ ተባባሪ አለመሆንን ማሳያ ነው፡፡ ለተቋሙ የጭቆና መሳሪያ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ እንዳለ አምነን ተጨማሪ ማረጋገጫ ዕድል (benefit of the doubt) መስጠት የማንፈልግ ከሆነ ይህ ትክክለኛው አማራጭ ይመስለኛል፡፡ ከግምት መግባት ያለበት ቃል በመስጠቱ ሂደት ውስጥ ፖሊስ በእርግጠኝነት ስህተት መስራቱ አይቀርም፡፡ ይህም የማይቀረው ክስ ሲመጣ ተቋሙን ማጋለጥ እንደ ስልት የሚወሰድ ከሆነ እንደማስረጃ ሊቀርብ ይችላል፡፡ ለምሳሌ በኛ ጉዳይ የቀረበብን ክስ የሽብር ቡድን በኅቡዕ አደራጅተዋል በሚል ሲሆን ሁላችንም ቃል ስንሰጥ የተጠየቅነው እና ስናብራራ የነበረው ግን በይፋ ስንጽፍበት እና ዘመቻዎቻችንን ስናካሂድበት ስለነበረው ዞን 9 ነው፡፡
አቃቤ ህግ በክሱ እያለ ያለው የከሰስኳችሁ በመጻፋችሁ እና መብትን የሚጠይቁ ዘመቻዎችን በማድረጋችሁ (በአጠቃላይ ከዞን-9 ጋር በተያያዘ) ሳይሆን ሌላ የህቡዕ ቡድን መስርታችሁ ለሽብር ዓላማ ስትንቀሳቀሱ ስለነበር ነው፡፡ የሰጠነው ቃል እና ክሱን ለመደገፍ የቀረቡት ማስረጃዎች ግን ስለ ዞን-9 አውርተው አይጠግቡም፡፡ በመጀመሪያዎቹ ቀናት የሚነግረውን ‹‹ተቋሙ ገለልተኛ ነው፣ ሰዎችን ወንጀለኛ ለማድረግ ሳይሆን እውነትን ፈልፍሎ አግኝቶ ነጻ ሰውን ወደቤቱ ይሸኛል›› የሚለውን ዕምነት በቀላሉ ማስረጽ ከቻሉ የሚቀጥሉት ጥርጣሬ ወደመዝራት ይመስለኛል፡፡ በቀላሉ ያሉትን የማያምኑ ከሆነ ግን የተጠርጣሪውን በራስ መተማመን ለመሸርሸር ህገ-ወጥ ተግባራቸውን ይቀጥላሉ፡፡
‹‹ምርመራ›› በጀመርኩ በአራተኛው ቀን የተከሰተው ይሄው ነው፡፡ ሚያዝያ 21/2006 ዓ.ም ምሽት ድረስ ‹‹በምርመራው›› ሂደት ውስጥ ስሳተፍ የነበረው በሙሉ የራስ መተማመን ነበር፡፡ ለምሳሌ ም/ሳጅን መኮንን፣ ም/ሳጅን እቴነሽ፣ እና ሳጅን ፈይሳ በነበሩበት ታስሬ ‹‹እየተመረመርኩ›› ያለሁት ሀሳቤን በነጻነት ለመግለጽ ባለመፍራት ነው፡፡ ያኔ ‹‹ፖሊስ ለህዝብ የሚሰራ ተቋም ነው የምትሉትንም አላምንም፡፡ በአሁኑ ሰዓት ፖሊስ እንደ ተቋም እየሰራ ያለው አገዛዙን ስልጣን ላይ ለማቆየት ነው›› ብያቸዋለሁ፡፡
ከላይ በጠቀስኩት ቀን ማታ ግን ሌላ ሊከሰት እንደሚችል የማውቀው፣ ግን ከምር ያልተዘጋጀሁበት ነገር ተከሰተ፡፡ ምሽት 1፡00 አካባቢ የተጀመረው ‹‹ምርመራ›› ቶሎ ኃይለ ቃል ወደመሰንዘር እና ዛቻ ተለወጠ፡፡ በወቅቱ ም/ሳጅን መኮንን፣ የመጀመሪያ ቀን ፍርድ ቤት የወሰደን እና በየመተላለፊያው ሳገኘው ጭምር ቤተሰብ እንዲያገኘን መብት አለን፣ ፍርድ ቤት አዝዞልን ሳለ ለምንድነው የማታገናኙን እያልኩ ስጠይቀው የቆየሁት ሳጅን ምንላርግልህ እና ማዕረጉን የማላስታውሰው ፀጋየ (በቅጽል ስሙ ጥጋቡ) የሚባል መርማሪ ነበሩ፡፡ የ‹‹ምርመራ››ውም ዋነኛ አጀንዳ የዞን 9 ድብቅ ግብ እና የውስጥ የስራ ክፍፍል (መዋቅር)በተመለከተ ነበር፡፡ በሁለቱ ጉዳይ ላይ እውነተኛው የማውቀው መልስ ‹‹መዋቅር የለውም›› የሚለው ነበር፡፡ ዞን 9 ድብቅ ግብም መዋቅርም ኖሮት አያውቅም፡፡ ሳጅን ምንላርግልህ መልሴ አላጠገበውም፡፡ ‹‹እኔ እንደሱ እንዳልመስልህ (የእኔን ጉዳይ በዋነኛነት ወደያዘው ም/ሳጅን መኮንን እየጠቆመ) አለቅህም! ሽባ ነው ማደርግህ! ልብስህን አስወልቄ ሳልለጠልጥህ እውነቱን ብትነግረኝ ይሻልሃል!›› የሚሉ ዛቻዎች ደረደረ፡፡ እኔ ግን መዋቅሩን በተመለከተ ስራ ለማቅናት ሲባል ምክረ ሀሳብ ቀርቦ እንደተወያየንበት፣ ነገር ግን ሀሳቡ ውድቅ እንደተደረገ ከማስረዳት በቀር የምጨምረው የማውቀው እውነት አልነበረም፡፡ ም/ሳጅን መኮንን እና ፀጋየ (ጥጋቡ) በየተራ ክፍሉን ለቀው ከወጡ በኋላ ሳጅን ምንላርግልህ ከወንበሩ በመነሳት ምቾት በሚነሳ ሁኔታ ከተቀመጥኩበት ፊት ተጠግቶኝ ቆሞ ጥያቄዎችን ይደረድር ጀመር፡፡
ጥያቄ፡- ‹‹ለምንድነው እነ ርዕዮትን ብቻ የምትጠይቁት?››
መልስ፡- ‹‹ኢትዮጵያውያን ስለሆኑ እና የታሰሩት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ነው ብለን ስለምናምን፡፡››
ጥያቄ፡- ‹‹(በቁጣ) ባንክ የዘረፈውስ ኢትዮጵያዊ አይደለም? ለምንድነው ሌላውን ወንጀለኛ የማትጠይቁት?››
በእውነት እዚህ ጋ ሳቄ መጥቶ ነበር፡፡ በርግጥ የታሰረን ሁሉ ከተቻለ መጠየቅ ለህሊና የሚያስደስት ስራ ነው፡፡ እግዜርም ይወደዋል፡፡ ግን ርዕዮትን ስጠይቅ እንዲሰማት የምፈልገው፣ ትግሏ ዋጋ እንዳላጣ እና እንዳልተረሳች ነው፡፡ ይህም ትንሽም ቢሆን ብርታት ይጨምርላታል ከሚል ተስፋም ጭምር ነው፡፡ ተመሳሳይ ነገር የባንክ ዘራፊ እንዲሰማው በፍጹም አልፈልግም፡፡ ጥያቄው ቀጠለ፣
‹‹ዝዋይ ለምን ሄዳችሁ?››
‹‹እነ ውብሸትን ለመጠየቅ››
‹‹አትዋሽ! በቀለ ገርባን ለመጠየቅ ነበር?››
‹‹አዎ በቀለንም ለመጠየቅ ነበር፡፡››
‹‹በቀለ ምን እንደሚል ታውቃለህ? ለምን እንደታሰረ ታውቃለህ? ኦሮምኛ ትችላለህ?››
‹‹አልችልም››
‹‹በቀለ እኮ የሚለው ኦሮምኛ የማይችሉ ሰዎች በሙሉ ይታረዱ ነው፡፡››
ስለ በቀለ ገርባ የማውቀው ጥቂት ነገር ከሚለኝ ጋር ፍጹም የሚጣጣም ስላልነበር የፊቴን መለዋወጥ መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡ ፊት ለፊቴ ተደንቅሮ የጥያቄ ዝናብ ሲያወርድ የነበረው ሳጅን ምንላርግልህ አሁን ማድረግ የሚፈልገውን ለማድረግ በቂ ምክንያት አገኘ፡፡ የመጀመሪያዋን ጥፊ ሰነዘራት፡፡ መብቴን እየነካ እንደሆነ ስነግረው ‹‹ይህንን ነው አይደል ፈረንጆቹ ወስደው የሚያሰለጥኗችሁ?›› በማለት ስራውን ቀጠለ፡፡ ድብደባው እዚያ ቤት ከሚፈጽሙት ሰቆቃዎች (torture) አንጻር ትንሽ ቢሆንም አሸነፈኝ፡፡ አሁን የሚጸጽቱኝንም ቃላት ተናገረኝ፡፡ ከውጭ የነበሩት ሁለቱ መርማሪዎች ድብደባ ሲፈጸምብኝ በነበረበት ወቅት በመሐል መጥተው ገላጋይ ሆነው ነበር፡፡ ምንላርግልህ ግን ለያዥ ለገናዥ አስቸገረ፡፡
ማስታወሻ፡-2. መርማሪዎች አንድ አላማ ነው ያላቸው
ሁለትና ከዚያ በላይ ሆነው ሲመረምሩ የትኛውንም ማመን አያስፈልግም፡፡ በኋላ ላይ ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ጋር ሳወራ የተረዳሁት ይህ የተለመደ አሰራር መሆኑን ነው፡፡
ሌላ ተጠርጣሪ ሲመረመር ሳጅን ምንላርግልህ ገላጋይ ሌላኛው ደግሞ እምቡር እምቡር ይላል፡፡ ከዚያም ፀጋየ (ጥጋቡ) እኔ ላይ ሲያደርግ እንደነበረው ገላጋይ የሚሆነው መርማሪ ‹‹እኔ ችግር ውስጥ እንድትገባ አልፈልግም፤ ለምን እውነቱን አትነግረንምና ራስህን አትጠብቅም? ደግሞ ዘጠኝ ሆናችሁ ለሰራችሁት ስራ አንተ ብቻህን ለምን ትጎዳለህ? ሌሎቹ እኮ እየተናገሩ ነው፤ አይደለም ዘጠኝ ሰው የሚያውቀው ነገር ይቅርና ለሌላ አንድ ሰው የነገርከው ነገር እኮ ሚስጥር መሆኑ ያበቃል›› የሚሉ ማግባቢያዎች በመደርደር ምስኪን ምስኪን ሊጫወት ይሞክራል፡፡
የዛን ምሽት ምርመራ ሲጠናቀቅ የሁለት ሰዓት ማሰቢያ ጊዜ ተሰጥቶኝ የዞን 9 ግብ ምን እንደሆነ እና የመዋቅራችንን እያንዳንዱን የስራ ዘርፍ እንዳስታውስ የቤት ስራ ተሰጥቶኝ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ተመልሼ እንደምጠራ ተነግሮኝ ነበር ወደ ማረፊያ ቤት ውስጥ የተመለስኩት፡፡
በተለምዶ ሳይቤሪያ የሚባለው ማረፊያ ቤት ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ሲሆን የታችኛው ወለል በኮሪደር ተከፍሎ በግራና በቀኝ አምስት አምስት ክፍሎች አሉት፡፡ ኮሪደሩ መሀል ላይ አንድ የግድግዳ ሰዓት ተሰቅሏል፡፡ የመጀመሪያ ሰሞን ልብ ስላልኩት ሰዓት የማውቀው ምርመራ ክፍል ካሉት ሰዓቶች በመነሳት በግምት ነበር፡፡ ከሳጅን ምንላርግልህ በተሰጠኝ የቤት ስራ መሰረት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሲል ተመልሼ ወደ ምርመራ እጠራለሁ፡፡ ከምርመራ ከተመለስኩ ጀምሮ በአዕምሮዬ ሲመላለስ የነበረው ነገር ተጨማሪ መልስ ልሰጣቸው እንደማልችል እና በዚህ ምክንያት ተመልሼ ከሄድኩ በኋላ የሚደርስብኝ ሰቆቃ ማብቂያ ምን እንደሚሆን ማሰብ ነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ በምርመራ በማሳለፌ ድካም የነበረብኝ ቢሆንም እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ራሴን አረጋግቼ በተሰጠኝ ሁለት ሰዓት እረፍት መውሰድ ብፈልግም ምንም ዓይነት ድምጽ በሰማሁ ቁጥር አምስት ሰዓት የሆነ እየመሰለኝ እባንን ነበር፡፡ እነምንላርግልህ ግን አልፈለጉኝም፡፡ አይነጋ የለም ሌሊቱም ነጋ፡፡ ጠርተው ቢደበድቡኝ ይሻል ይሆን እንደነበር እንጃ!
ማስታወሻ፡- 3. እራስን አረጋግቶ በቂ እረፍት መውሰድ
መርማሪዎቹ መቼም ቢሆን ምርመራ ጨርሰናል ደህና እደሩ ብለው አይሸኙም፡፡ ሁል ጊዜ‹‹በኋላ እንገናኛለን፤ አስብበት›› ብለው ነው የሚጨርሱት፡፡ አንዳንድ ጊዜ በቀጠሮ መሰረት ምርመራው ይቀጥላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የውሃ ሽታ ይሆናሉ፡፡ በቀጠሮ መሰረት ብጠራም ባልጠራም ያለችውን ጊዜ በቂ እረፍት ለማድረግ መጠቀሚያ ማድረግ የሚያዋጣው አማራጭ ነው፡፡ ከድብደባው በባሰ የሚጎዳው የማያቋርጥ ጭንቀት እና የእረፍት እጦት ነው፡፡ ከአሁን አሁን ወደምርመራ ተጠራሁ ብሎ መጨነቅ ጥሪውን የማዘግየትም የማስቀረትም አቅም የለውም፡፡ ‹በኋላ እንገናኝ› የምትለዋ ቀጠሮ እረፍት መንሻ ዘዴ ናት፡፡
በመቀጠል የምርመራው ዓላማ የነበረው ከጓደኞቼ ያገኟቸውን መረጃዎች በመጠቀም ብዙ እንደሚያውቁ ጥያቄ የሚጠይቁትም ከኔ ይምጣ ብለው እንጂ ሁሉ ነገር ላይ መረጃ እነዳላቸው ለማሳመን መጣር ነበር፡፡ በወቅቱ የእኔ ምላሽ የነበረው ሁሉንም የሚያውቁ ከሆነ ለኔ ጥሩ እንደሆነ እና ምንም ጥፋት እንደሌለብኝ ከዛ በላይ ማስረጃ እንደሌለ የሚያስረዳ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-4. አብረው የሚሰሩ ጓደኛሞች ወጥ መልስ ለመስጠት አስቀድመው ስምምነት ላይ መድረስ
ስለ አንድ ጉዳይ ሁለት ጓደኛሞች የተለያየ መልስ ከሰጡ ሰቆቃው ሁለቱም ላይ የጠና ነው፡፡ አንደኛው ወደ ሌላኛው መልስ የሚጠጋ ነገር እስካልተናገረ ድረስ ሁለቱም ይሰቃያሉ፡፡ በኛ ምርመራ ወቅት አስቀድመን ምንም የምንደብቀው ወይንም የምንዋሸው ነገር እንዳይኖር ስንነጋገር ስለከረምን በተነጋገርነው መሰረት የአንዳችን ቃል ከሌላችን የጎላ ልዩነት አልነበረውም፡፡
በጓደኞች መሀከል ክፍተት ለመፍጠር ሙከራ ያደርጋሉ፡፡ ለምሳሌ ለበፍቄ ‹‹ናትናኤል እኮ እውነቱን ነግሮናል፡፡ በፍቃዱ ነው አብዮት እና አመጽ እንድንጠራ የሚገፋፋን ብሏል፡፡ አንተ ለምንድነው እንዲህ የምትደብቅላቸው እነሱ እውነቱን እየተናገሩ›› ብለውታል፡፡ ቀዳዳ ካገኙ ቅያሜ በመፍጠር ከጓደኛሞች መሀል አንዱን መስካሪ ለማድረግ ይጥራሉ፡፡ ማስፈራሪያዎች በታጨቁበት ምርመራ መሀል እራሴን ነጻ ማውጣት ቀላሉ አማራጭ እንደሆነ ደጋግመው ይነግሩኝ ነበር፡፡ ፀጋዬ (ጥጋቡ)፣ ም/ሳጅን መኮንን እና ኢንስፔክተር አሰፋ እየመረመሩኝ በነበሩበት ወቅት ፀጋዬ ተራ ስድቦችን እና ዛቻዎችን ከሰነዘረ በኋላ በዛው አፉ እኔን ማቆየት እንደማይፈልጉ እና የሚፈልጉትን ካልኩላቸው ወዲያውኑ ወደቤቴ እንደሚሸኙኝ አባቴንም መንከባከብ እንደሚሻለኝ ሲነግረኝ ነበር፡፡ የአባቴ ጤንነት እንዳሳሰበኝ ስለገባቸው ባገኙት አጋጣሚ ለምርመራው ግብአትነት ይጠቀሙበት ነበር፡፡
አብዛኛው የምርመራ ጊዜ በተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና ተደጋጋሚ መልሶች የሚያልፍ ነው፡፡ ይህም ምርመራዎችን እጅግ አድካሚ እና አሰልቺ ያደርጋቸዋል፡፡ ዝርዝር ጉዳዮችን በተደጋጋሚ በመጠየቅ ከምሰጠው መልስ ላይ ልዩነት ለማግኘት ይህንንም ተጠቅሞ ሌላ አዲስ ነገር ለማውጣጣት ይጥሩ ነበር፡፡ የተሳካላቸው ግን አይመስለኝም፡፡ በተቻለኝ አቅም ቀዳዳ ሳገኝ የማምንበትን አቋም ከመናገር ወደኋላ አላልኩም፡፡ የማውቀውን ለማካፈልም እንደዚያው፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 39ን የሚቃወም መርማሪ አግኝቼ ለምን ልክ ነው ብዬ እንደማምን አስረዳኋቸው፡፡ በተለያየ ጊዜ የወሰድኳቸው የበይነ መረብ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችንም በተመለከተ ያብራራሁለትም መርማሪ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-5. በተገኘው አጋጣሚ አቋምን ማስረዳት
መርማሪዎቹ በተደጋጋሚ ስለተነገራቸው ብቻ የሚያምኑት ብዙ ነገር አለ፡፡ ኢህአዴግ ትግል ላይ በነበረበት ወቅት ጭራቅ ተደርጎ ይሳል እንደነበረው አሁንም የነጻነት ትግል እያደረጉ ያሉትን ሰዎች እንደ ሰው በላዎች የሚቆጥሯቸው መርማሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ በነዚህ መርማሪዎች ይህን ከተማ (አ.አ) ተወልዶ ያደገ ሰው ፖለቲካ ውስጥ ቦታ የለውም፡፡ ተደጋግሞ ሲነሱልኝ ከነበሩት ጥያቄዎች መሀል ይህ መንግስት ምን በድሎሃል (በግል) እንዴት እንደዚህ አይነት አቋም ልትይዝ ቻልክ? የሚለው እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ መልሴ ግን አጭር ነበር፡፡ ነጻነቴን ዋጋ እሰጠዋለሁ!!
ከምክትል ሳጅን መኮንን ጋር በነበረን ጊዜ የተረዳሁት ስለ አቋሞቼ በጥልቀት ማወቅ ቢፈልግም እንደ ጦር እንደሚፈራቸው ነው፡፡ ገና ማስረዳት ስጀምር ቶሎ ብሎ ‹ወደ ጉዳያችን እንመለስ፣ ዳግም ወደ አንተ ልትስበኝ ነው?› ይለኝ ነበር፡፡ ሌሎችም መርማሪዎች ተመሳሳይ ፍላጎት አይቸባቸዋለሁ፡፡ አንድ የማይረሳኝ ምሳሌ ከኢሜሌ ላይ የተገኘውን የዜና መጽሔት በተመስጦ ሲያነብ የነበር አንድ መርማሪ አለቃቸው ድንገት ቢሮውን ከፍቶ ሲገባ ወረቀቱን በድንጋጤ ወርውሮታል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የቻልኩት እነዚህን በአንድ በኩል መረጃ የተደፈኑ ሰዎች ሌላኛውን ጎን ማሳየት በሌላ አማራጭ የማያገኙት መረጃ ምንጭ መሆን ስለሆነ በምርመራ ወቅት እንደ አንድ ዓላማ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው፡፡
አልፎ አልፎ ከሌላ ቦታ የሚመጡ (ከደህንነት መስሪያ ቤት) መርማሪዎች ለመመለስ አደጋች የሆኑ ውስብስብ ጥያቄዎችን ከመጠየቃቸው ውጭ የሚጠየቁት ጥያቄዎች እዚህ ግባ የሚባሉ አይደሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ መርማሪዎች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎች ለራሳቸውም ግልጽ አይደሉም፡፡ ጥያቄዎችን የሚያበጁት ከጀርባ ሆነው ምርመራውን የሚመሩት አለቆቻቸው ናቸው፡፡ አልፎ አልፎ ለመመለስ አደጋች የሚመስሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ፡፡ ለምሳሌ ሚያዝያ 27 ቀን (የአርበኞች ድል ቀን) ኢንስፔክተር አሰፋ እና አንድ የደህንነት ባልደረባ ሆነው ባካሄዱብኝ ምርመራ ወቅት አንድ አስቸጋሪ ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡-
የደህንነት ባልደረባው፡- ‹‹ዞን 9 ምን ማለት ነው?››
መልስ ፡- ‹‹ዞን 9 ማለት ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ታሳሪ ነው ለማለት የተጠቀምንበት ስም ነው፡፡››
‹‹እኔም የዞን 9 አባል (ነዋሪ) ነኝ ማለት ነው?››
‹‹አዎ!››
‹‹ጥሩ! ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ከሆነ መቼ እና እንዴት ነው ዞን9 ነጻ የሚወጣው?››
ይህ ጥያቄ ትንሽ ለመመለስ አስቸጋሪ ነበር፡፡ በርግጥ እንደማነኛውም ግለሰብ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን መቼ ያገኛል ለሚለው ጥያቄ የራሴ አስተያየት ቢኖረኝም በዚህ ምርመራ ወቅት ሀሳቤን በነጻነት ብናገር የሚያመዝነው አደጋው ነበር፡፡ ስለዚህ ማለት የቻልኩት ዞን 9 የሚለውን ተምሳሌታዊ ስያሜ አምነንበት ብንጠቀምም የዞን 9 ነዋሪዎችን ነጻ ማውጣት ግን እንደ ግብ ያስቀመጥነው እና እንዲሳካም ኃላፊነት ወስደን የሰራንበት ጉዳይ እንዳልነበር ነው፡፡
አጠቃላይ የእስር ቤቱ የአያያዝ ሁኔታና የምርመራው አሰልቺነት በየዕለቱ መርማሪዎቹ ከሚነግሩኝ የራሳቸው እውነት ጋር ተደማምሮ ሊያሸንፈኝ ዳር ዳር ብሎ ነበር፡፡ ነገር ግን በተባራሪ የምንሰማቸው ጓደኞቻችን እና መታሰራችን የሚቆረቁራቸው ሰዎች የሚያደርጉት ሰላማዊ ሰልፍ እና የበይነ መረብ ዘመቻ ተጨማሪ የጥንካሬ ምንጭ ሆነውኛል፡፡ የማታዎቹ ምርመራዎች ለዚህ ምቹ ናቸው፡፡ ካስተዋልኩት የተረዳሁት የማታውን (የሌሊቱን) የምርመራ ጊዜ መርማሪዎቹ ለሚከፈላቸው ተጨማሪ ገንዘብ እና ስላመሹ መ/ቤቱ ለሚያቀርብላቸው ቆሎ እና ውሃ ካልሆነ በስተቀር አይፈልጉትም፡፡
በማታው ምርመራ ወቅት ቶሎ የመሰላቸት እና የኃይል እርምጃ ወደ መውሰድ ይሄዳሉ፡፡ ብዙ ማውራት አይፈልጉም፡፡ ስለዚህ አለቆቻቸው የሰጧቸው ጥያቄዎች ሲያልቁባቸው የተለያዩ ስፖርታዊ ቅጣቶች በማዘዝ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው አማካኝነት ጨዋታ (game) ይይዛሉ፡፡ ወይንም ሌላ ክፍል ምርመራ ላይ ካለ ጓደኛቸው ጋር በኢንተር ኮም ወግ ይይዛሉ፡፡ በተመርማሪዎች ላይ ያላግጣሉ፡፡ በማታዎቹ ምርመራዎች ወቅት ለሚነሱ ጥያቄዎች ረዘም ያሉ መልሶችን መምረጥ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ መልሶችንም በህገ-መንግስቱ ስለተፈቀዱ መብቶች፣ ስለ ተቋማት ነጻነት አስፈላጊነት፣ እና መሰል ፖለቲካዊ ጉዳዮች ወደ ማብራራት ማጠጋጋት፣ ከተቻለ የመርማሪዎቹን ቀልብ ለመሳብ እና ከሚወስዷቸው አላስፈላጊ የኃይል እርምጃዎች መከላከል ይቻላል፡፡
ማስታወሻ፡-6. አቤቱታ ማሰማት
የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ፍርድ ቤት በሚወሰዱበት ጊዜ ያለውን አጋጣሚ በሚገባ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በተለምዶ ፍርድቤት በፖሊስ የአያያዝ በደል ተፈጽሞብኛል ብሎ የሚያመለክት ሰው ከፍርድ ቤቱ መልስ ተመልሶ ማዕከላዊ እንደሚገባ ስለሚያውቅ የባሰአደጋ ለመቀነስ በሚል አቤቱታ ከማቅረብ ሊቆጠብ ይችላል፡፡ ነገር ግን አቤቱታውን አቀረበም አላቀረበም ሰብዓዊ መብቱን ከመረገጥ አይድንም፡፡ ልዩነቱ የሚሆነው የፍርድ ቤቱ መዝገብ ላይ የመብት ጥሰቱ ተመዝግቧል ወይስ አልተመዘገበም የሚለው ነው፡፡
እዚህ ላይ የምመክራቸውን ነገሮች ያለማድረግ ቁጭት በእኔ ብቻ ሳይሆን ብዙ ታሳሪዎች ላይ ያስተዋልኩት ነው፡፡ ያላደረግሁትን አድርጉ ብሎ የመጠየቅ ይሉኝታም ጽሁፉን ልጻፍ ወይስ ይቅርብኝ ብዬ እንዳንገራግር አድርጎኝ ነበር፡፡ ውስጤ ከሚብላላ ግን ጽፌው አንብቦ ቢያንስ አንድ ሰው የተለየ መንገድ ተከትሎ ጉዳት ቢቀንስ የተሻለ ነው የሚለው ሀሳብ የተሻለ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ሌሎቹም ጓደኞቼ ተመሳሳይ መንገድ አልፈዋል፡፡ የነሱንም የምርመራ ሂደት ይጽፉታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እስከዛው ድረስ መታገስ ያልቻለ የሀገር ውስጥ ነዋሪ ግን ወደ ቂሊንጦ ጎራ ብሎ ከራሳቸው አፍ ጠይቆ መረዳት ይችላል፡፡ እኔ ቀረኝ የምለው ነገር ካለኝ በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ፡፡
ማስታወሻ፡-7. የማዕከላዊ ቤቶችን (ክፍሎች) ይተዋወቁ
ማዕከላዊ
በግቢው ውስጥ ሶስት የእስረኛ ማቆያ ቦታዎች አሉ፡፡ በተለምዶ ጣውላ ቤት፣ ሳይቤሪያ እና ሸራተን በመባል ይታወቃሉ፡፡ጣውላ ቤት አምስት ክፍሎችን በተርታ የያዘ ሲሆን የምርመራ ቢሮዎች ያሉበት ህንጻ ጀርባ ምድር ላይ ያሉ ክፍሎች ናቸው፡፡ እኛ ማዕከላዊታስረን በነበርንበት ወቅት ሶስቱ ክፍሎች ለሴት ተጠርጣሪዎች ማቆያ ሲሆኑ ቆርቆሮ መከለያ ተደርጎለት፣ ደግሞ የተቀሩት ሁለቱ ምስክርለመሆን የተስማሙ ወንድ ተመርማሪዎች ማቆያ ነው፡፡ ማሂ እና ኤዶም ከሶስቱ ክፍሎች በአንደኛው ከሌላ ሴት ታሳሪዎች ጋር እንዳይገናኙሁለቱ ብቻ ተለይተው ነበር፡፡ ጣውላ ቤት ፊት ለፊት የክፍሎቹ ወለል ጣውላ መሆኑ ነው ጣውላ ቤት የሚል ስያሜ ያሰጠው፡፡ ይህንንማቆያ ቤት አልፎ አልፎ ሂልተን በማለት የሚጠሩት ሰዎች ገጥመውኛል፡፡
ሳይቤሪያ የሚባለው የእስረኛ ማቆያ በቅዝቃዜው ምክንያት ነው ስሙን ያገኘው፡፡ ይህ ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ምድር ላይየሚገኘው ማቆያ ቦታ በረጅም ኮሪደር የተከፈለ ሲሆን በግራና በቀኝ ከ2 ቁጥር እስከ 10 ቁጥር የተለጠፈባቸው አምስት አምስት ክፍሎች አሉት፡፡ 8 ቁጥር ከተለጠፈበት ውጭ ሌሎቹ ወጥ ክፍሎች ሲሆኑ 8 ቁጥር የተለጠፈበትን በር ተከፍቶ ሲገባ ግን ሌሎች ራሳቸውን የቻሉ አራት ክፍሎች አሉት፡፡ የበለጠ ቅጣት እንዲቀጣ የሚፈልጉት ተመርማሪ እነዚህ ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር የሆነ ጨለማ ክፍል ውስጥ ያስሯቸዋል፡፡ ሳይቤሪያ የምርመራ ግለቱ እስኪሰክን ድረስ ተመርማሪዎች የሚቆዩበት ቦታ ሲሆን ሁሉም ክፍሎች ከኤሌክትሪክ መብራት ውጭ ምንም አይነት ብርሃን አይደርሳቸውም፡፡ የክፍሎቹ ግድግዳዎች ወለሉና ጣራው ከኮንክሪት የተሰራ ነው፡፡ ቀኑን ሙሉ ከውጭ ተዘግቶ የሚውለው ክፍል በቀን ለሶስት ጊዜ ያክል ይከፈታል፡፡
ሳይቤሪያ ውስጥ ያሉ ክፍሎች ጠዋትና ማታ በተራ በተራ እየተከፈቱ ተመርማሪዎች በጋራ ወደሚጠቀሙት ባለስድስት ክፍል ሽንት ቤት እና መታጠቢያ ቤት እንዲሄዱና ተጠቅመው እንዲመለሱ ለደቂቃዎች ፈቃድ ያገኛሉ፡፡ ለሌሎች ጥቂት ደቂቃዎች ደግሞ የፀሐይ ብርሃን ለማግኘት ይፈቀድልን ነበር፡፡ ፀሐይ የምናገኘው በጣውላ ቤት እና በህክምና ክሊኒኩ መሐከል ባለ ክፍት ቦታ ላይ ነበር፡፡ጣውላ ቤት ያሉት ክፍሎች በር ክፍት ስለሚሆን ከማሂ እና ኤዶም ጋር በዓይን እና በምልክት ብቻ እናወራ ነበር፡፡ የሳይቤሪያ ክፍሎች በየተራ በሳምንት አንድ ቀን የሚጸዱ ሲሆን ባለችን መታጠቢያ ጊዜም የምናገኘው በነዚህ ቀናት ብቻ በሳምንት አንዴ ነው፡፡
ሸራተን ለ12 ሰዓት ፀሐይ የሚገኝበት፣ ቲቪ የሚታይበት እና የሽንት ቤት እና የመታጠብ ፍላጎት ያለው ሰው የፈለገውን ማድረግ የሚችልበት ቦታ ነው፡፡ የምርመራው ሂደት ሲጠናቀቅ ቀለል ባለ ጉዳይ የሚመረመር ሰው ወይንም ደህና ባለስልጣን ዘመድ ያለው ሰው ሸራተን ሆኖ የማዕከላዊ ቆይታውን ያጠናቅቃል፡፡
በመጨረሻም አንድ እብሪተኛ መርማሪ በተናገረኝ ንግግር ማስታወሻየን ላጠናቅቅ፡፡ እንዲህ ነበር ያለኝ፣ ‹‹መንግስት ብዙ ዓይኖች እና ጆሮዎች አሉት፡፡ እናንተ ደግሞ ስታወሩ የነበረው በእኛው ስልክ፣ ከሀገር ስትወጡ የነበረው በእኛው በሀገራችን አየር መንገድ እና በቦሌ በኩል ነበር፡፡ እያንዳንዱ እንቅስቃሴያችሁን መረጃ አለን፡፡ አንተ አሁን እየደበቅህን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለአንተ አይጠቅምም፡፡ እኛ ምርጫ እንሰጥሃለን፡፡ ሕይወትህን ወደብርሃን መውሰድ የምትፈልግ ከሆነ ወደዚያው እንመራሃለን፡፡ አይ አልፈልግም የምትል ከሆነ ደግሞ መውጣት ወደማትችለው ድቅድቅ ጨለማ እንከትሃለን፡፡ ምርጫው የአንተ ነው፡፡››

Friday, July 31, 2015

ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ለምን ያስጨንቃቸዋል?

July 31, 2015
ሽብሬ ደሳለኝ
Andargachew Tsige is Ethiopianባለፉት 24 ዓመታት ወያኔዎች በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) ለውጥ ለማምጣት የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካ ድርጅቶች እና ፖለቲከኞች ከማዳከም አልፈው በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት ተጽኖ መፍጠር እንዳይችሉ አድርገዋቸዋል።

አብዛኛዎቹ ፖለቲከኞች የወያኔ አፈና ሲበረታ ከማምረር ይልቅ ፖለቲካውን እርግፍ አድርገው ይተውታል ወይንም ደግሞ ስደት ይወጡና ቀደም ሲል የተሰደደውን የኢትዮጵያ ስደተኛ ተቀላቅለው እንደ አብዛኛው ስደተኛ ቤተሰቦቻቸውን እና እራሳቸውን በኢኮኖሚ የማሻሻል ተግባር ላይ አተኩረው ይቀራሉ። ይህ እየተለመደ የመጣ አካሄድ ወያኔዎቹን ተመችቷቸው ኖረዋል፣ እነ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የጨዋታውን ህግ እስከቀየሩት ድረስ።

በርግጥም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ ወደ ፖለቲካው ሜዳ ያመጡት አዲስ የጫወታ ህግ ሰርቷል!
ወያኔ አዲሱን የጨዋታ ህግ ከጅምሩ አልወደደውም፣ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ኋይት ሃውስ ፊት ለፊት ሻማ ከማብራት ያለፉ እንዳይሆኑ ምኞቱ ነበር። ይህ አልሆነም።

አቶ አንዳርጋቸው እና ጓዶቹ ኢትዮጵያውያን የአሜሪካን ወይንም የእንግሊዝን መንግስት በመለመን ነጻነታቸውን እንደማይቀናጁ ይልቁንም ብረት አንስተው ወያኔን በሚገባው ቋንቋ የማነጋገር አስፈላጊነትን አስተማሩ፣ ወተወቱ፣ የመውጪያ መግቢያ ቀዳዳዎችንም አመላከቱ… ኤርትራ!

ወያኔ በሃገር ውስጥ (በሰላማዊ መንገድ) የሚደረጉ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን ሲያዳፍን፣ ለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን እንደሚያማትር አልጠፋውም፣ ወያኔዎች የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የሃይል አማራጮችን በስራ ላይ ለማዋል ተባባሪ/ፈቃደኛ የጎረቤት ሃገሮች እንደሚያስፈልጉት ቀደም ብሎ መተንበዩ አልቀረም (ወያኔ ከደርግ መንግስት ጋር ባደረገው የሃይል ትግል ወቅት ሱዳን እና ሶማሊያ ዋንኞቹ መጠለያው ነበሩ)። ከሃገር ጥቅም ይልቅ ለመንበረ ስልጣኑ ቅድሚያ የሚሰጠው ወያኔ ለኢትዮጵያ አጎራባች ሃገሮች ሁሉ የሚጠይቁትን እየሰጠ (ለምሳሌ ሱዳን ከሃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ ይገባኛል የምትለውን የኢትዮጵያ መሬት ከወያኔ ተቀብላለች) በምላሹም ተቃዋሚዎቹን እንዳያስጠልሉ፣ አልፎ ተርፎም ተቃዋሚዎቹን እያደኑ እንዲያስተላልፉለት አግባባቸው። ይሁንና ይህ አካሄድ በጎረቤት ኤርትራ ሊሰራለት አልቻለም።

አንዳርጋቸው ጽጌ እና ጓዶቹ አውርተው አልቀሩም፣ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተሳካ ግንኙነት ፈጠሩ፣ ጦርም ማደራጀት ቻሉ፣ ቀደም ሲል ጀምሮ በኤርትራ መሬት ይንቀሳቀሱ በነበሩት ሃይሎች መካከልም መልካም እና መተማመን የሰፈነበት ግንኙነት እንዲኖር አስቻሉ።

ወያኔ ከሚቆጣጠረው ግዛት ውጪ የሚደረገው የለውጥ እንቅስቃሴ እየበረታ መሄዱን በመገንዘብ እንቅስቃሴውን በእንጭጩ ለማስቀረት መንቀሳቀሱ አልቀረም፣ ይህንን ወያኔን እንቅልፍ የነሳ እንቅስቃሴ ወደ ተግባራዊነት እየቀየሩ ባሉት የግንቦት 7 አመራሮች ላይ አነጣጥሮ በተገዙና የተቃዋሚ ካባ በደረቡ ግለሰቦች አማካኝነት አመራሮቹን ከህዝብ ለመነጠል ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም ውጤቱ አመርቂ አልሆነም። ወያኔ ከዚህ በኋላ ነበር አማተር ሰላዮቹን ወደ ኤርትራ በመላክ አርበኛውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመግደል ሙከራ ያደረገው ይህም አልተሳካም እንደውም ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ደረሰበት (ብዙዎች አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጠንቅቀው የማያውቁት ሳይቀሩ የአንዳርጋቸውን ማንነት ለመገንዘብ ቻሉ)።

ወያኔ በመጨረሻ ያደረገው ሙከራ ተሳክቶለት አቶ አንዳርጋቸውን ከየመን አፍኖ ወደ አዲስ አበባ መውሰድ ቻለ።
ለጊዜው ወያኔዎች ከፍተኛ የድል አድራጊነት ሰሜት ተሰምቷቸው ጮቤ ረገጡ ይሁንና ብዙም ሳይቆይ ደስታቸው እንደጉም በኖ እስካሁን በሚያቃዣቸው ስጋት ውስጥ እንዲዘፈቁ ሆነ። ጀግናቸው (አንዳርጋቸው ጽጌ) በወያኔ እጅ መውደቁን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከጫፍ ተነቃነቁ፣ አንዳርጋቸው የጀመረውን የትግል ጉዞ ከግብ ለማድረስም ቁርጠኝነትቸውን አሳዩ፣ የአንዳርጋቸው ቤተሰቦች ሴት ከወንድ ሳይባል በአንዳርጋቸው ጽጌ እግር ተተክተው አንዳርጋቸው ያቀጣጠለውን ችቦ ተረከቡ።
የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራሮችና የአንዳርጋቸው የትግል ጓዶች ዙሩን አከረሩት፣ በተደጋጋሚ ከወያኔ ጋር ባካሄዳቸው የሽምቅ ውጊያዎች ልምድ ካካበተውና የሰሜኑን የኢትዮጵያ ግዛቶች መግቢያ መውጫ ጠንቅቆ ከሚያውቀው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጋር ውህደትን ፈጠሩ፣ በውጤቱም አርበኞች ግንቦት 7 ተወለደ።

በለስ ቀንቷቸው አቶ አንዳርጋቸውን በእጃቸው ያስገቡት ወያኔዎች ከሚቆጣጠሩት ግዛት ውጪ እየተካሄ ያለው እንቅስቃሴ በአንዳርጋቸው መያዝ ምክንያት መባባሱን ተረድተዋል። የእንቅስቃሴውን ፍጥነት ለመግታት በቁጥጥራቸው ስር ያለውን አንዳርጋቸው ጽጌን ለመጠቀም በማሰብ እየቆረጡ እና እየቀጠሉ የሚለቋቸው የአዳርጋቸው ጽጌ ቪዲዮዎች ምንም ውጤት አላመጡም፣ ይልቁንም በኢትዮጵያውያኑ ዘንድ ከፍተኛ ቁጭትን እየጫሩ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ ቃላቸውን እንዲያድሱ አድርጓቸዋል።

ለዚህም ይመስላል አንዳርጋቸው ጽጌን የስፖርት ቱታ በማልበስ ሰው በሌለበት ጎዳና ላይ ፎቶ አንስተው “ተመልከቱ እባካችሁ አንዳርጋቸው ሰላም ነው” በማለት ኢትዮጵያውያኑን ለማረጋጋት የሞከሩት።
አርበኞች ግንቦት 7 ጥቃት መፈጸም ከጀመረና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኤርትራ ገብቶ በአንዳርጋቸው እግር መተካቱ ከተሰማ በኋላ ደግሞ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጉዳይ ፍም እሳት ሆኖባቸው የሚያደርጉትን አሳጥቷቸዋል፣ ለዚህም ምልክቱ ቴድሮስ አድሃኖም በቪኦኤ ላይ የተናገረው ነው “አንዳርጋቸው ላፕ ቶፕ ተሰጥቶት መጽሃፍ ጽፎ ጨርሷል፣ አንዳርጋቸው የሃገሪቱን ልማት ማየት ፈልጎ እያዟዟርን አሳይተነዋል ወዘተ…”

እውነታው ግን አንዳርጋቸው ጽጌን የት እንዳሰሩት አይናገሩም፣ አንዳርጋቸውን ቤተሰብም ሆነ ማንኛውም ሰው አይጎበኘውም። በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ወያኔዎች በአንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሚያውቁትን የማሰቃያ መንገዶች ሁሉ በመጠቀም አንዳርጋቸው እነርሱ የሚፈልጉትን አይነት መልእት እንዲያስተላልፍ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። ይሁንና ጀግናው አንዳርጋቸው ጽጌ እስካሁን የሚፈልጉትን አልሰጣቸውም (ይህንንም ለማረጋገጥ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ስቃይ እየፈጸሙ ቀርጸው የሚያሰራጯቸውን ቪዲዮዎችን መመልከት ይበቃል)።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በአካል ተገኝቶ ትግሉን መምራት ባይችልም መንፈሱ ግን ትግሉን በማቀጣጠል ላይ ይገኛል። እንግዲህ ወያኔዎች የአንዳርጋቸው ጽጌን ለመቆጣጠር ነው ቁጭ ብድግ በመስራት ላይ ያሉት፣ ይሳካላቸው ይሆን? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል።

ሁሉም በያለበት የነፃነት ትግሉን ይቀላቀል!!!

July 31, 2015
def-thumbእኛ ኢትዮጵያውያን ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ የሰውነት መብታችን ተገፎ የዜግነት ነፃነታችን ተረግጦና ተዋርደን የምንገኝበት ጊዜ ቢኖር ዛሬ ነው፡፡ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ እስርና የጅምላ ስደት እንደ ዘመነ ወያኔ የታየበት ዘመን የለም፡፡ ህፃናት በረሀብ ከሚማሩበት ክፍል ውስጥ የሚወድቁበት ፤ ወንድ ልጅ በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ የሚደፈርበት፤ ሴት ልጅ በገመድ የታሰረ የባልዋነወ ብልት መንገድ ለመንገድ እንድትጎትት የተደረገበት ዘመን ቢኖር ያሳለፍነው የወያኔ ዘመናት ብቻ ነው፡፡ ባጠቃላይ የሰው ልጅ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ መከራና ሰቆቃ እንድንሸከም የተገደድንበት ዘመን ላይ እንገኛለን፡
በአንፃሩም ስለ ለፃነት ስለ ፍትህና እኩልነት ሲሉ የተሰዉ ዋጋም የከፈሉ፤ አሁንም እየከፈሉ የሚገኙ ጥቂት አይደ ሉ ም፡፡ ከነዚህም አንዱ አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህ ለነፃነት ለፍትህና ለ ዲሞክራሲ የሚደረገው ተጋድሎ ውሎ አድሮ ዛሬ ከዋናውና ወሳኝ ከሆነው ምእራፍ ላይ መድረሱ ደግሞ የሁላችንንም ተስ ፋ ያለመለመና የተደፋው አንገታችን ቀና ያደረገ መሆኑና በተቃራኒው የወያኔን ካንፕ ያሸበረ መሆኑ በገሀድ እየታየ የሚገኝ እውነት ነው፡፡
እንግዲህ ይህን ወራዳ ስርአት አስወግዶ በምትኩ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመተካት የሚደረገው ትግል ዛሬ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የተደረገው ርብርብ ቀላል ባይሆንም ቀሪውን አጠናቆ ከዳር ለመድረስ ከመቼውም ጊዜ በላይ የእያንዳዱን ኢትዮጵያዊ የተግባር ተሳትፎ የሚጠይቅ፤ ሁሉም ከያለበት ስለ ነፃነት የሚደረገውን የአርነኝነት ትግል በመቀላቀል የድርሻ ውን ሀላፊነት መወጣት ከሚጠይቅበት ወሳኝ ምእራፍ ላይ መድረሳችንን መረዳት ግድ ይላል፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን ያለ ማንም እርዳታና ድጋፍ ዋጋ ከፍሎ ለፃነትን የማሰከበር እንግዳ ሳንሆን በታሪክ የምንታወቅበት መለያችን መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ እንኳን ዛሬ አለም አለም በጠበበችበት ዘመን ቀርቶ ትናንት በጨለማው ዘመን እንኳ እነ ዶ/ር መላኩ በያን ከአኛ አልፎ ለአፍሪካ ነፃነት ፈር ቀዳጅ ሆነው የተገኙበትን ታሪክ ማስታወስ ይገባል፡፡
እናም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኟውም ስፍራ የሚገኝ ሁሉ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል እውቀት ያለው በእውቀቱ፤ ጉልበት  ያለው በጉልበቱ፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ ለመደገፍ ዛሬ ነገ ሳይል አሁኑኑ ከአርበኝነቱ ትግል መቀላቀል ይጠበቅበታል፡፡ ኢትዮጵያዊነታችንን ብቻ ሳይሆን ሰው መሆናችን የሚረጋገጠው ነፃነታችንን አስጠብቀን በነፃነት መኖር ስንችል ብቻ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡
ስለዚህ ዛሬ አርበኞች ግንቦት ሰባት የለኮሰው የነፃነት ቀንዲል ከነጻነት አደባባይ ለመትከል የጀመረውን ጉዞ በሰው ሀይል፤ በገንዘብና በቁሳቁስ በማገዝ ሁላችንም የድርሻችንን እንድንወጣ ጥሪ ስናደርግ ለእኛ ኢትዮጵያውያን ከእኛ ኢትዮጵ ያውያን ውጭ ማንም እንደሌለ በማስገንዘብ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Wednesday, July 29, 2015

ከአምስት በላይ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና የሸዋሮቢት ነዋሪዎች በእስር ላይ መሆናቸው ተገለጸ

July 29,2015
በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ሸዋሮቢት ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች እና ወጣት የለውጥ አራማጅ የፓርቲው አቀንቃኞች በመንግስት ሃይል ታፍነው ወደ እስር ቤት ከተወረወሩ ከወር በላይ መሆናቸውን ከክልል ሶስት ሰሜን ሸዋ ዞን የሸዋሮቢት ከተማ አስተደር ነዋሪዎች የሆኑ እና የፓርቲው አባሎች እና አመራሮች ለማለዳ ታይምስ የአባሎቻቸውን መታሰር ጠቁመዋል ።
እነዚህ የሰማያዊ ፓርቲ አባሎች በየትኛው ቦታ እና እንዴት እንደታሰሩ ለመጠየቅ ቢሄዱም የመንግስት ሃይሎች ምንም አይነት መረጃም ሊሰጧቸው እና ያሉበትንም ሁኔታዎች ሊያሳውቋቸው ባለመቻላቸው በከፍተኛ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ የሚገኘውን የሰማያዊ ፓርቲ ዋና መስሪያ ቤት ለማግኘት እና ስለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው መግለጫ እንዲያወጡ ለመጠየቅ በደጋግሚ ቢጥሩም ምንም ምላሽ ሊሰጧቸው አለመቻሉ እራሱ አሳሳቢ ከመሆኑም በልይ በክልሉ ለሚገኙት አባሎች እራስ ምታት መሆኑን ገልጸዋል ።
የፓርቲው አመራር ምላሽ መስጠት ሲገባቸው እንደ ወያኔ መንግስት ለአባሎቻቸው ዝምታን መፍጠሩ ለለውጥ የተዘጋጁ ሳይሆኑ ለጥቅሞቻቸው የተነሱ ሃይሎች መስለው ነው የታዩን ብለው የተናገሩት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት እና የቀወት ወረዳ የሰማያዊ ፓርቲ የወጣት መልማዮች ዋና ሃላፊ በዛሬው እለት ይህንን መግለጭ ወደ ግል መገናኛ ብዙሃን ልናመጣው የቻልነው ሰሚ አካል ብናገኝ ጥሩ ነው በሚል ምክንያት ነው ሲሉም አክለው ገልጸዋል ። ከአንድ ወር በፊት የታሰረውን ወጣት ቴዎድሮስ ሃብቴ እስካሁን ያለበትንም ሁኔ ካለማወቃችን የተነሳም ለፍርድ እንኳን አቅርበው ጥፋተኝነቱንም ህነ የተከሰሰበትን ሁኔታ ለመረዳት አልቻልንም የሌሎችንም ወጣት የዘርፍ ክፍሎቹንም ለመከታተል አልቻልንም ሲሎ ገልጸዋል ።

Monday, July 27, 2015

ፕ/ት ኦባማ «ኤርትራ ያለ ተቃዋሚ ድርጅትን በአሸባሪነት ለመፈረጅ» የሚያስችል በቂ መረጃ የለንም አሉ፤

July 27,2015
ኢሳት ዜና ፦ የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ ዌዲ ሸርማን አርበኞች ግንቦት7ትን በአሸባሪነት እንዲፈረጅ ያቀረቡትን ጥያቄ፣ ለፕ/ት ኦባማም ማቅረባቸውን የሚያመለክት ነው። ፕ/ት ኦባማ በመልሳቸው «ፖሊሲያችን መንግስትን በሃይል ከስልጣን ማውረድን አይደግፍም፣ ይህ ፖሊሲያችን በዲሞክራሲያዊ ሁኔታ የተመረጠውን የኢትዮጵያን መንግስትንም ያካትታል» ካሉ በኋላ፣ «በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ከፍተኛ ችግር እየፈጠሩብኝ ነው በማለት የሚፈርጃቸው ድርጅቶች እንዳሉ እናውቃለን፣ ይሁን እንጅ በመንግስት ላይ ተቃውሞ ቢያሰሙም የሽብር ዝንባሌ እንደሌላቸው የእኛ የመረጃና የደህንነት መረጃዎች ያሳዩናአል» በማለት በኢህአዴግ መንግስት በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበሉት መቅረታቸውን ተናግረዋል። «ይህንን በመገምገም በኩል ግልጽ የሆነ መስፈርት አለን ያሉት ኦባማ፣ ለወደፊቱ እነዚህ ድርጅቶች የሽብር ጥቃት ይፈጽማሉ አይፈጽሙም የሚለውን ለወደፊቱ የምናየው ይሆናል ብለዋል።
.
«አንድ ድርጅት የፖለቲካ ተቃውሞውን ቢገልጽ ፣ ከአስተሳሰቡ ጋር ባንስማማም እንኳ ከለላ እንሰጠዋለን፣ ይሄ በአሜሪካ በሌላም ቦታ የሚሰራበት እውነታ ነው፤ ይህን ማድረግ ለዲሞክራሲ እድገት አስፈላጊ ነገር ነው» ያሉት ኦባማ ፣ ድርጅቶቹ ወደ ሃይል ሲያዘነብሉና በህገመንግስት የተቋቋመን መንግስት ለመገልበጥ ሲሞክሩ፣ ድርጊቱ ያሳስበናል።» በማለት መልሰዋል። የውጭ አገር ጋዜጠኞች ፣ በእስር ላይ ስለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እንዲሁም ስለኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ጉዳይ ለፕ/ት ኦባማና ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጥበቃ እና በዲሞክራሲ ዙሪያ ከአቶ ሃይለማርያም ጋር ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን፣ አሜሪካ በቅርብ ሁና እገዛ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልጸዋል። የኢህአዴግ መንግስት ከፕ/ቱ ጉብኝት በዋናነት የሚጠብቀው ለስልጣኑ ስጋት የሚፈጥሩ ድርጅቶች በሽብረተኝነት እንዲፈረጁለት ቢሆንም፣ ይህንን ሳያገኝ ቀርቷል። ይሁን እንጅ ባራክ ኦባማ የኢህአዴግን መንግስት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው በርካታ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶችን ሳያስቆጣ አይቀርም። ኦባማ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየጠበበ ስለመጣው የፖለቲካ ምህዳር ሲናገሩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫውን ዲሞክራሲያዊ የሚል ካባ ማልበሳቸው፣ የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲን ተቃርኖ የሚያሳይ ነው።
.
በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል ለፕሬዝደንት ኦባማ በተዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታውቀዋል። የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት መንግስት ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገውን የእራት ግብዣ ያልተቀበሉት፣ «አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ፣ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም» ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም «የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ» ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸውም ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ «ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው» ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ኢ/ር ይልቃል

July 27,2015
ኢ/ር ይልቃል መንግስት ለፕሬዝደንት ኦባማ ያዘጋጀው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ
• ‹‹ኦባማ ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ውሃ የሚቸልስ ነው››
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ ለነገረ ኢትየጵያ ገልጸዋል፡፡ የራት ግብዣው ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥሪ የተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ‹‹ አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም›› ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ›› ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ኢህአዴግ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለታቸው ቅር እንዳሰኛቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ማለት የሰላማዊ ታጋዮችን ስቃይ የሚክድና ለአምባገነኖች ይሁንታ የሚሰጥ ነው›› ሲሉ የፕሬዝደንት ኦባማን ንግግር ነቅፈውታል፡፡ ፕሬዝደንት ኦባማ የጠበንጃ ትግልን አለመደገፍን ለመግለፅ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንትን ጨምሮ ሌሎች የአሜሪካ ተቋማት ኢ-ዴሞክራሲያዊ መሆኑን አረጋግጠውት፣ መቶ ፐርሰንት ምርጫ አሸንፌያለሁ የሚልን ፓርቲ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደተመረጠ መግለፃቸው እንዳሳዘናቸው ኢ/ር ይልቃል ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል ኢ/ር ይልቃል በነገው ዕለት የአሜሪካ ኤምባሲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የወያኔ ታጣቂዎች በታህታይ አድያቦ ወረዳ እርስ በራሳቸው ተዋጉ

July 27,2015
በታህታይ አድያቦ ወረዳ አካባቢ የሚገኙ የገዢው የኢህአዴግ ስርዓት ወታደሮች እርሰ በራሳቸው እየተገዳደሉ እንደሚገኙ ተገለፀ። በትግራይ ሰሜናዊ ምእራብ ዞንEthiopian dictatorial regime troopsታህታይ አድያቦ ወረዳ ተሰማርተው የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት በመካከላቸው አንድነትና ፍቅር እንደሌላቸው የገለፀው መረጃው በተለይ ደግሞ በአባላትና በአዛዦች መሃል በተከሰተው ያለመስማማት ምክንያት ወታደር ታዘዘ ደበበ የተባለ ግለሰብ መቶ አለቃ አስራት ባዩና አምሳ አለቃ ካሳ አለሙ የተባሉን በጥይት ገድሎ ለራሱም ህይወቱን እንዳጠፋ የተገኘው መረጃ አስረድቷል።
በተመሳሳይ- በአዲ ሃገራይ አካባቢ የሚገኙ የኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት አንድ ወታደር 3ት ኮነሬሎችን ከነ አጃቢዎቻቸው ገድሎ ራሱን ህይወቱን እንዳጠፋ ባላፈው የዜና ዘገባችን መግለፃችን ይታወሳል።
ምንጭ – ትህዴን

የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት ነው

July27,2015

(ወለላዬ ከስዊድን)


አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል።
“ወደ ሰፈር፣ ወደ ሰፈር እየወረድኩ ነው ንጉሥ ሆይ!”
“ምነው ደህናም እማይደለህ?”
“ጣቴን ድንጋይ ቀርጥፎኝ ነው ንጉሥ ሆይ!”፤ ትንሽዋን ጣቱን በጨርቅ ነገር ጠቅሎ አንከርፏል።
“ና እስቲ! ቀረብ በልና የተጎዳኸውን አሳየኝ”፤ ሰውየው ንጉሡ ጋ ቀርቦ የቋጠራትን ጨርቅ ፈቶ ጣቱን ሲያሳይ ንጉሡ ትንሽ ጭረት ቢጤ ብቻ ያያሉ።
“ሌላ ቦታም ተጎተሃል እንዴ?”
“የለም! ይሄው ብቻ ነው።”
“እና! ይቺን ቁስል ናት! ብለህ ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ?”
“ይችኑስ ቢሆን በማን ልላካት ጌታዬ?” ብሎ ንጉሡን እንዳሳቃቸው ይነገራል። እኔም ለሌላ ሰው የሚላከክ ቢሆን የአቶ መለስን ሙት መንፈስ እዚህ ጋ ባልሸነጎርኩ ነበር። ሆኖም የሳቸው ቁስል ምንም እንኳን አነስተኛ ባይሆንም በማንም ልላክከው ስለማልችል ማንሳት ሊኖርብኝ ነው። አንድ ጊዜ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሁራንን ሰብስበው ንግግር አደረጉ። ምሁራኑ በአንክሮ ሰሟችው። የአነጋገራቸውን አካሄድ ተንኮልና ክፋት እንዳዘለ ቢያውቁም ብዙዎቹ ሊናገሩ አልፈለጉም። በኋላ ግን አንድ እጅ ከመሃል ተቀሰረች። አቶ መለስ ምሁሩ እንዲናገሩ ዕድል ሰጡ። ሰውዬው ከማንም ይበልጥ የአቶ መለስ ንግግር አንገብግቦአቸዋል። ማንገብገብ ብቻ አይደለም በእንዲህ አይነቱ መሪ አገሪቷና ህዝቡ ወደፊት የሚደርስበት ውርጅብኝ የበዛ እንደሚሆን በደልና ስቃዩም አስከፊ ደረጃ እንደሚደርስ ተሰምቷቸዋል።
ምሁሩ ዕድሉን ተጠቀሙበት፤ ማለት የሚገባቸውን አጠቃለው እስኪጨርሱ አንዳችም ፍርሃትና መደናገር ሳይታይባቸው “… አሁን ለሁሉ ነገር ጊዜው አልፏል። እርስዎ እያሉ ገበሬው ውስጥ ገብቶ አደራጅቶ ፋይዳ የሚያመጣ ፓርቲ ይኖራል ተብሎ አይገመትም። ስለዚህ ኳሷ በርስዎ ቁጥጥር ስር እስከዋለች ድረስ ከምንም ነገር በላይ ቅንነትዎን ብቻ እንፈልጋለን። ቅንነትዎ አይለየን ቅን ሆነው ይምሩን ይሄን ብቻ ነው የምንጠይቅዎ …” ነበር ያሉት።
ምሁሩ አቶ መለስ እስከወዲያኛው ቀና እንደማይሆኑና በቀናነት ሊመሩ እንደማይችሉ አላጡትም። ነገር ግን ቀና ማድረግ ባይቻል እንኳን ቀና እንዳልሆኑ ለማሳወቅ ፈልገዋል። ሆኖም አቶ መለስ ቀና ባይሆኑ አይገርምም ከሚሰሩት ተንኮል አንጻር ቀናነት ኪሳራ እንጂ ትርፍ ሊያስገኝላቸው አይችልም። ተፈጥሮአቸውም ቢሆን በቀናነት ተቃኝቶ በሥነ ምግባር ጎልብቶ የቀናነትን ጎዳና የተከተለ ስላልሆነ ቀና ልሁን ቢሉ እንኳን አይችሉም። ይህ ብቻ አይደለም ከአመራራቸው ግብና ዓላማም ጋር ቀናነት አብሮ አይሄድም።
ገና ከትምህርት ቤት ጀምሮ የመሰሪነት ባህሪ እንደነበራቸው የሚመሰክሩ ብዙዎች ናቸው። ስንት ታጋይ ጓደኞቻቸውን ወደ እማይመለሱበት እየላኩ ለሥልጣን የበቁም ናቸው። ከሥልጣን በኋላም ሞት እጃቸውን እስከሰበሰበው ድረስ አለ እረፍት ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያን ያዋረዱ፤ ህዝብ የናቁ፣ የከፋፈሉ፣ ያሰሩ፣ የገደሉ፣ ባንዲራን ያቃለሉ፣ ያገር ክብር የደፈሩን ሰው በምንም አይነት ቅንነት ልንመኝላቸው አንችልም።
እንግዲህ ስለአቶ መለስ ቀና አለመሆን ከተፈጥሮቸውና ከዓላማቸው አንጻር ነው ብለናል። ነገር ግን አቶ መለስን የሚያወግዝ፣ ለዲሞክራሲ ለሠላምና ለእኩልነት መከበር የቆመ፣ የተጣመመን ፍትህ አቃናለሁ የሚል፣ በሰው ልጅ እኩልነት የሚያምንና ይህንንም ለማስከበር የተነሳ ለአገሩ ብልጽግናና ነጻ መውጣት የሚያስብ ቅንነት ከጎደለው ከዓላማና ግቡ ጋር የተቃረነ መሆኑ አያጠራጥርም። አቶ መለስ የጣሏትን ቅንነት አንስቶ በጉያው ካልያዘ ልዩነታቸው ብዙም የተራራቀ አይሆንም። ለሳቸው ቅንነት ይጎዳቸዋል እሱ ደግሞ አለቅንነት ምንም አይነት የነጻነት ጉዞ ሊጓዝ አይችልም።
እንደውም ቀና ልቦና የሌለው ታጋይ ጊዜውና ሁኔታው ሲገጥመው አንዳንዴ ብልጭ እያለች የምታሳጣውን መጥፎ ባህሪ ሰው ጥላቻና ክፋት እፊት ለፊት አውጥቶ እማይጠቀምበት ምንም ምክንያት የለውም። ያንን እስከሚጠብቅና ድብቅ ፍላጎቱን እስኪያሟላ ድረስ ተፈጥሮው እያወከው ለትግል ጓዶቹ የማይመች የትግል እንቅፋት ሆኖ መቆየቱ አይቀሬ ነው።
ጎኑ ያለውን የትግል ጓዱን ያልወደደ ለዲሞክራሲ ቆሜያለሁ፣ ለነጻነት እፋለማለሁ፣ ለነፍትህ እዋደቃለሁ፣ … ቢለኝ አላምነውም፤ ባህሪው የገባበትን ዓላማ እንዳያሳካ አንቆ ስለያዘው የሱን ታጋይነት እጠራጠራለሁ። እውነቴን ነው ይህ ሰው ጫፍ ድረስ አይዘልቅም ይሰናከላል። ተሰናክሎም ያሰናክላል።
እናም የኢትዮጵያ ህዝብ ከገባበት የእጅ አዙር የባርነት አገዛዝ፣ ከነፃነት እጦት፣ ከእስር፣ ከንግልት፣ ከስደትና ከረሃብ ለማላቀቅ የተነሳህ፤ ፍትህ እንዲከበር፣ ዲሞክራሲና ሰላም፣ እድገትና ብልጽግና እንዲገኝ የምትፈልግ ሁሉ የትግልህ መጀመሪያ የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆንን በማመን በቀናነት ከትግሉና ከታጋዩ ጋር ተቀላቀል። ቀና ልቦና ያለው መንገዱ ሁሉ ክፍት ይሆንለታል፣ በቀላሉ አይሰናከልም፣ ልቡ አያውከውም፣ አቀራረቡ ግልጽ ነው። አይፈራም፣ አይዋሽም፣ አያታልልም፣ አይጠራጠርም፣ ለቂም አያደባም፣ ለዝና አይናውዝም፣ ለሥልጣን አይዳክርም …
ይህ ካልሆነ ግን፤ እታገልልሃለሁ በምትለው ህዝብ ፊት ለመቆም ጉልበትህ አይጠናም። ህዝብ የምታደርገውን የትግል እንቅስቃሴ ቢያይም የአስተሳሰብህን ሸካራነት፣ የልቦናህን ክፋት ለመረዳት ብዙ ስለማይፈጅበት ክብርና ፍቅር ሊሰጥህ ይቸገራል፣ አይከተልህም። አይዞህ ልጃችን በማለት አያበረታታህም። እንደውም ልታታልለው እንደተነሳህ፣ ልታሞኘው እንዳደባህ ስለሚቆጥርህ ልቡን ከፍቶ አያሳይህም፤ ስለዚህ ቀና ሁን።
የፖለቲካን ትርጉም ከክፋት ጋር አትቀላቅል። ሌላም የምመክርህ አለኝ፣ የትግል ጓዶችህን አክብር፣ ጓደኛህ ስህተት ካለበት በድብቅ ከማማት ይልቅ ስህተቱን ፊት ለፊት ነግረህ እንዲመለስ አድርግ። ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ አሲረህ አሳድመህ አጥቂ አትሁን፤ ቂመኛ ሀሚተኛ አትሁን፤ መልካምነትን አሳንሰህ ስህተትን አታጉላ፤ የኔ ሃሳብ ይበልጣል፣ የምናገረውና የምሠራው ሁሉ የኔ ልክ ነው አትበል። ለቡዙሃን ድምጽና ሃሳብ ተገዛ፤ ሌላውን ደካማ አድርገህ አትይ፤ ለመወንጀል አትፍጠን፤ ልብህን ለንጹህ ወንድምነት ክፍት አድርግ። መቻቻልን፣ በጋራ መሥራትን አዳብር፤ የትግል ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን ለሥልጣንና ለሀብት አትጓጓ፤ ድርሻና ኃላፊነትን ከፍ አድረገህ በመመልከት ሌሎችን አትጫን፤ መልካም ሥነምግባር በማሳየት ሌሎችም አንተን እንዲከተሉ አድርግ። አትወላውል! ለተነሳህበት ዓላማ እስከመጨረሻው ተጓዝ። ወዳጄ ሆይ! ምክር ቢበዛ ባህያ አይጫንምና ይበቃኛል። ለማንኛውም የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት መሆኑን አትዘንጋ።

የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት ባደረጉት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸውን የኢህአዴግ ሰራዊት ደመሰሱ

July27,2015
arbegnoch g7 በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ማይ-ሰገን በተባለው አካባቢ የሚገኙትን የኢህአዴግ የሰራዊት አባላት በግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በደረሰባቸው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ምክንያት ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውን ተገለፀ።
ባለፈው ቀናት በሑመራ አካባቢ ማይ ሰገን በተባለው ቦታ ላይ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በኢህአዴግ ሰራዊት ላይ ባደረሱት ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ ብዛት ያላቸው ታጣቂዎች ከጥቅም ውጭ ማድረጋቸውን የገለጸው መረጃው በውጊያው ከተገደሉት ታጣቂ አመራሮችም።….
ኮማንደር ወልደሚካኤል ገብረእዝጊአብሄር የሃይል አዛዥ የነበረ፤ ካሕሳይ ነጋሽ በባዕኸር የሚልሻ አዛዥ የነበረ፤ ለግዜው ስሙ ያልታወቀው የሻምበል ማእርግ ያለው በ24 ክፍለጦር የሓይል አዛዥ የሆነውና ሌሎች የሚገኙባቸው እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
እነዚህ የስርዓቱ ታጣቂዎች- በአካባቢው ሰላማዊ ህዝብ የተለያዩ ግፍ ሲፈፅሙ የቆዩ በመሆናቸው የተነሳ የግንቦት 7 አርበኞች ግንባር ሰራዊት በላያቸው ላይ እርምጃ መውሰዱን የተገኘው መረጃው አስረድቷል።

Saturday, July 25, 2015

Ethiopian Opposition Group Threatens Armed Resistance

July 25, 2015
(VOA News) Ethiopia’s opposition Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has decided to use armed resistance in addition to peaceful resistance against the government in Addis Ababa. This follows the move of the group’s leader from the United States to Eritrea.Dr. Berhanu Nega
Berhanu Nega travelled to Ethiopia’s northern neighbor following the merger of his Ginbot 7 with the Ethiopian People’s Patriotic Front. “It’s true he travelled to Eritrea, he went on July 17, 2015,” said the spokesman for the group, Dr. Tadesse Biru.
“He is the leader of an organization that strives to bring about democratic order in Ethiopia, and he went to fulfil his leadership role,” he explained in reference to Dr. Berhanu, who was sentenced to death in absentia while living in the US.
Ethiopia’s government classes Ginbot 7 as a terrorist group. It comprises former members of the Coalition for Unity and Democracy, an opposition grouping that made unprecedented gains against the ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front in 2005 elections.
Tadesse confirmed the merger of Ginbot 7 with the Ethiopian People’s Patriotic Front this year. On armed resistance, he said: “We do have a kind of blended strategy to challenge the government in Addis Ababa. We have been trying to stage civic disobedience; we tried peaceful resistance starting in 2005.”
But, a non-violent solution, he said, has been closed by the government in Ethiopia, and the group has been forced to consider all possible avenues including civic disobedience and armed resistance.
Tadesse emphasized, however, that the group is still open to a non-violent settlement. “We are always open to possibilities of a peaceful resolution. The group emerged from a peaceful movement but now we are forced to consider armed resistance. It’s not our choice but there is no other feasible option to challenge the government in Addis Ababa.”
He said civil disobedience will continue, but will be complemented by ‘non-peaceful resistance, like it was done in South Africa’.
Some observers say the move of the group to Eritrea could renew tensions between the Horn of Africa nations, which fought a two-year war that ended in 2000.
The spokesperson dispelled such fears, saying nothing will happen since the two countries had no friendly relationship anyway. “Eritrea has provided us an opportunity to organize our movement there, that’s all. I don’t think it will in any way affect the relationship – it has not been good.”
As to the strength of the group’s armed force, Tadesse said: “yes, there is a small group that has been training in Eritrea, and there is a movement developing.”
Officials in Addis Ababa have dismissed the group’s move. A special adviser to the Prime Minister was reported saying Ginbot 7 is militarily weak and Berhanu’s move to Eritrea is a “publicity stunt.”

TPLF Security Forces Terrorist Plot in Addis Ababa Leaked

July 25, 2015
def-thumbPatriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has received credible reports that the fascist regime in Ethiopia has made intricate plans to detonate explosives and blame Patriotic Ginbot 7 for its own terrorist acts.
While we had received the leaked information of the sinister plans being hatched by the TPLF politburo members a few weeks ago, the pending visit of the U.S. President to Ethiopia have made it imperative for the TPLF regime to carry out the heinous crimes in the next few days.
We would like to inform the Ethiopian people and the international community that TPLF has finalized plans to carry on terrorist acts at Bole International Airport, along the major highway leading to the airport, at the headquarters of the African Union and the U.S. Embassy.
The TPLF minority regime is, of course, no stranger to planting bombs in Ethiopia’s capital Addis Ababa in a bid to frame its real and perceived political enemies and brutally murder innocent Ethiopians.
Massive leaks of secret files by WikiLeaks has exposed the late Prime Minister Meles Zenawi as the terrorist-in-chief. In a report from 2006 marked “Secret; Subject: Ethiopia: Recent Bombings Blamed on Oromos Possibly the Work of Government of Ethiopia” “Classified By: Charge [d’Affairs] Vicki Huddleston”, “An embassy source, as well as clandestine reporting, suggests that the bombing may have in fact been the work of the Government of Ethiopia security forces.” (Cable reference id:#06ADDISABABA2708.)
Patriotic Ginbot 7 strongly condemns the senseless brutality and the unconscionable use of terror by the rogue regime in Ethiopia to garner international support. Its utter disregard for the sanctity of human life and the Ethiopian people’s well known reputation as a peaceful and cultured people who abhor violence is truly horrifying.
The very fact that this dying regime is willing to kill, maim and cause mayhem in Addis Ababa to maintain power at any cost and in the face of a shrinking political base is a clear indication that it has lost any legitimacy to rule Ethiopia.
Patriotic Ginbot 7 would like to remind the deeply traumatized people of Ethiopia who are knowledgeable of the sinister motives of the fascist regime to be ever so vigilant and take every precaution for their individual and collective safety.
It is also time for the United States and the international community to realize that a terrorist regime willing to use violence to cling to power will never be a credible partner in the “war against terror.”

ኦባማ፡ “በንግግር (ወሬ) A፣ በተግባር D” ኦባንግ ሜቶ

July 25,2015
“በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን”
obang voa4

ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ውጤት ቢሰጥ በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው በንግግር (በወሬ) ደረጃ A በተግባር ግን D እንደሚሰጧቸው ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ፡፡ አፍሪካውያንም ሆኑ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት በሚያደርጉት ትግል ምዕራባውያን ዕንቅፋት ከመሆን እንዲቆጠቡ አስረዱ፡፡
በአሜሪካ ድምጽ የStraight Talk Africa አዘጋጅ ሻካ ሳሊ የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን የአፍሪካ ጉብኝት በተመለከተ ከሁለት ቀናት በፊት ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ሦስት አፍሪካውያንን ተጋብዘው ነበር፡፡ ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ የሴራሊዮኑ ፕሮፌሰር አብዱል ካሪም ባንጉራ፣ የአፍሪካ ስደተኞች ስብስብ ኃላፊ ጋናዊው ኒ አኩቴ እና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር ኢትዮጵያዊው ኦባንግ ሜቶ ነበሩ፡፡
በእስካሁኑ የአፍሪካ ፖሊሲያቸው ለፕሬዚዳንቱ ምን ውጤት ትሰጣላችሁ በማለት ሻካ ላቀረበው ጥያቄ ዶ/ር አብዱል D እሰጣቸዋለሁ፡፡ ይህም በተለይ ከአፍሪካ ጋር ስላለላቸው ግንኙነትና እንዴት የአፍሪካ ፖሊሲያቸው ውጤት አልባ እንደሆነ በመመልከት ነው ብለዋል፡፡ ይህንን ያሉበትም ምክንያት በርካታ ሰዎችን በመጠየቅ ባደረጉት ጥናትና ምርምር እንደሆነ ሆኖም አሜሪካ ከኩባ ጋር ያላትን የሻከረ ግንኙነት በማለዘብደረጃ የተጫወቱ ሚና ከዚህ የወረደ ነጥብ እንዳያገኙ እንደረዳቸው ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል፡፡
ጋናዊው  አኩቴ ግን ለኦባማ A እንደማይሰጡ ከተናገሩ በኋላ በዝርዝር ሳይጠቅሱ ፕሬዚዳንቱ ላከናወኑት ተግባራት ግን ተመጣጣኝ ነጥብ ሊሰጣቸው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን የትኛውም ነጥብ ይህ ነጥብ ወይም ደረጃ ለምንድነው የሚሰጣቸው ብሎ መጠየቅ ተገቢና አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡obang voa2
ኢትዮጵያዊው ኦባንግ ሜቶ በበኩላቸው ለፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ውጤት ስጡ ቢባሉ “በንግግር (በወሬ) A በተግባር ግን D” እንደሚሰጧቸው ተናግረዋል፡፡ ይህንንም ሲያስረዱ ከዓመታት በፊት ጋናን በጎበኙ ወቅት “አፍሪካ የሚያስፈልጋት ጠንካራ መሪዎች ሳይሆን ጠንካራ ተቋማት” ነው ማለታቸውን ከጠቀሱ በኋላ “በአሁኑ ወቅት በአገሬ ያለው አገዛዝ በምርጫ መቶ በመቶ አሸንፌአለሁ” የሚል መሆኑን አውስተዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቋማት መቀጨጭ ወይም መምከን ምን ደረጃ እንደደረሰ ሲያስረዱም “በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብት፣ ለሴቶች መብት፣ ለህጻናት መብት፣ ለዕርቅ፣  መሥራት ሕግን እንደ መጣስ ተቆጥሮ” ለእስር እንደሚዳርግ አስረድተዋል፡፡ አሜሪካ የተመሠረተችባቸው እነዚህ እሴቶች በኢትዮጵያ ዋጋ የሌላቸው መሆኑን ሲገልጹ ዋንኛው ምክንያት ጠንካራ ተቋማት በኢትዮጵያ እንዳይኖሩ አገዛዙ የመያዶች ሕግ በመባል የሚታወቀውን በማወጅ ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖርና ሊቃወሙት የሚችሉትን ሁሉ በሕገወጥነት በመፈረጁ መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከዚህ ሌላ በአገራቸው ጠንካራ ተቋም እንዳይመሠረት ዕንቅፋት የሚሆን የጸረ አሸባሪነት ሕግ በሥራ ላይ መዋሉን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ የፕሬዚዳንቱን ጉብኝት በተመለከተ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን እንደተናገሩት ዋናው ዓላማ የአሸባሪነት ጉዳይ ተብሎ መጠቀሱ ኦባማ ለአፍሪካ ያላቸውን አመለካከት ያሳያል ብለዋል፡፡ ይህም ማለት ማንኛውም የአፍሪካ መሪ ሕዝቡን እያሸበረ የአሜሪካንን ጥቅም እስካስከበረ ድረስ የዜጎች መብት መረገጥ ነገር ለአሜሪካም ሆነ ለምዕራባውያን ከጉዳይ እንደማይቆጥሩት የጋራ ንቅናቄው መሪ ኦባንግ አስረድተዋል፡፡ “ለዚህም ነው በአሁኑ ጊዜ ጠንካራ ተቋማት መመሥረት የሚችሉ ብሩህ ኅሊና ያላቸው ጦማሪያንና ጋዜጠኞችና የነጻነት ድምጾች በአሸባሪነት ተፈርጀው በእስር የሚማቅቁት” በማለት ኦባማ በንግግር ደረጃ ለጠንካራ “ተቋማት መመሥረት ቢያወሩም በተግባር ግን የከሰሩ ናቸው፤ (የአፍሪካ ኅብረትን ሰብስበው ሲያናግሩም) የሚናገሩት ከጠንካራ መሪዎች ጋር ነው” ብለዋል፡፡
ኦባንግ ቀጠሉ “ዛሬ ኢትዮጵያ የምትተዳደረው በአፓርታይድ ዓይነት ዘረኛ አገዛዝ ነው፤ (ወደ አዘጋጁ ሻካ ሳሊ በመጠቆም) ለምሳሌ እኔና አንተ እዚህ አሜሪካ አገር በመጀመሪያ ሰዎች ነን፤ ወንድማማች ነን እንጂ ኢትዮጵያዊ ወይም ዑጋንዳዊ ተባብለን በዘርና በአካባቢ የተለያየን አይደለም፤ በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ግን ይህ አይደለም፤ አንዲያውም በቅርቡ ከአሜሪካ የኔብራስካ ጠቅላይ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ የሄደች አንዲት እህት መታወቂያ ካርድ ለማውጣት ስታመለክት ዘርሽ (ብሔርሽ) ምንድነው ተብላ ስትጠየቅ የሁለት ቅልቅል በመሆኗ ይህ ነው ብላ መናገር እንደማትችል፤ ኢትዮጵያዊ መሆኗን ብታስረዳም የግድ እንደሆነ ከኃላፊዎች ሲነገራት በማመልከቻው ቅጽ ላይ አማራ + ኦሮሞ = ______ በማለት እናንተው ሙሉት በሚል ክፍት አድርጋ ትታዋለች፤ (በኢትዮጵያ ሰው ከመሆንህ በፊት ዘርህ ይቀድማል) የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት የሚባለው ከደርግ ለመታገል በረሃ ወረደ፤ ደርግ ከተወገደ በኋላ ኢህአዴግ በማለት ራሱን የቀየረ በመምሰል አሁንም (ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም) እየገዛ ይገኛል፤ ዛሬ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት በህወሃት ቁጥጥር ሥር ውሎ ዜጎች ይበረበራሉ፤ ሚሊታሪው፣ ኢኮኖሚው፣ ደኅንነቱ፣ በሙሉ በህወሃት ቁጥጥር ሥር ነው፤ በመሆኑም ኦማባ እስካሁን በኢትዮጵያ ላይ የተከተሉት ፖሊሲ ይህንኑ የሚደግፍና ከሕዝቡ ያልወገነ ነው” በማለት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አስረድተዋል፡፡
ጠያቂው ሻካ ሳሊ “እርስዎ ከበርካታ የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎችና ከፍተኛ የፖለቲካ ኃላፊዎች ጋር በየጊዜው ይገናኛሉ፤ ከእነዚህ ሰዎች ጋር በሚያደርጉት ንግግር ወቅት እነዚህ ባለሥልጣናት አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ስላላት አቋም በተመለከተ ምንድነው የሚሉት” በማለት ለኦባንግ ላቀረቡላቸው ጥያቄ ሲመልሱ “በየጊዜው የሚሉት በኢትዮጵያ ጠንካራ ተቃዋሚ የለም ነው፤ እኔ የማስረዳቸው ደግሞ አገዛዙ ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖር በስልት እንዴት እንዳደረገ ነው፤ ኢንተርኔቱን ተቆጣጥረውታል፤ ከሃያ ዓመታት በላይ መንግሥት የሌላት ሶማሊያ በኢትንተርኔት አጠቃቀም ኢትዮጵያን ትበልጣለች፤ በየጊዜው የሚነሱ የነጻነት ድምጾች ታፍነዋል፤ ታስረዋል፤ ኢትዮጵያውያን በውጪ መደራጀት ይችላሉ ሆኖም በአገር ውስጥ (ህወሃት) ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖር አድርጓል” በማለት በየጊዜው ለሚያገኟቸው የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንደሚያስረዱ ጠቁመዋል፡፡
ፕ/ር አብዱል በተራቸው በሙያቸው ባደረጉት ጥናት ኦባማ ለአፍሪካ እጅግም የበጀ ወይም በዋንኘነት የሚጠቀስ ተግባር አለመፈጸማቸው ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር አብዱል ማመጣጠን እንዳለባቸው አዘጋጁ ሻካ ሳሊ በመጥቀስ ለአብነት ያህል በራሳቸው በፕ/ሩ የትውልድ አገር ሴራሊዮን የተከሰተውን የኢቦላ ቫይረስ በመከላከል ኦባማ ያደረጉት አስተዋጽዖ ታላቅ እንደሆነ የሴራሊዮኑ ፕሬዚዳንት መናገራቸውን፣ እንዲሁም በላይቤሪያ ኦባማ የፈጸሙት ተግባር ተጠቃሽ እንደሆነ ፕሬዚዳንት ሰርሊፍ የመሰከሩ መሆኑን ከዚህም ባሻገር ወጣት አፍሪካውያንን ወደ አሜሪካ እየመጡ እንዲማሩ በማድረግ ለአህጉሪቱ የወደፊት ራዕይ የሚበጅ Young Africans Leadership Initiative (YALI) ፕሮግራም መመሥረታቸው ሊጠቀስ እንደሚገባው በቃለምልልሱ ወቅት አውስቷል፡፡
ፕ/ር አብዱል ከበፊቱ ጠንከር ባለ ሁኔታ እንዲያውም ፕሬዚዳንት ኦባማ በኬኒያም ሆነ በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ጉብኝት የደመቀ አከባበርም ሆነ ዳንስና ጭፈራ እንደማያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ምክንያቱም ፕሬዚዳንቱ ለሥራ የመጡ ከሆነ ያላቸውን ጊዜ ሁሉ ምን መደረግ እንዳለበት በዝርዝርና ነጥብ በነጥብ ከአፍሪካውያን ጋር ጊዜያቸውን በሙሉ ማዋል ይገባቸዋል፡፡ ጊዜው የጭፈራና የዳንስ ሳይሆን የሥራና ተግባራዊ ለውጥ የሚታቀድበት ሊሆን እንደሚገባ ፕ/ር አብዱል አስረድተዋል፡፡
obang voa5“ፕሬዚዳንት ኦባማ ይህንን ፕሮግራም ቢመለከቱ ለእርሳቸው የሚነግሩት መልዕክት ምንድነው? ካሜራውን እየተመለከቱ መልዕክት አስተላልፉ” በማለት ሻካ ለኦባንግ ሜቶ ላቀረበላቸው ጥያቄ ጥቁሩ ሰው “ከሥልጣን ከለቀቁ በኋላ ስለሚቀጥለው ሌጋሲዎ የሚያስቡ ከሆነ እና መታወስ፣ መታሰብ የሚፈልጉ ከሆነ ሲታወሱ ሊኖሩበት የሚችልበት አንዱ መንገድ ለአምባገነኖች በሠሩት ተግባር ሳይሆን ለሕዝብ በሚያከናውኑት ሥራ ነው፤ የአፍሪካ ኀብረት 50ዓመታት እለፎታል በአኅጉሪቷ (ፖለቲካ) ላይ ያመጣው ይህ ነው የሚባል ለውጥ የለም፤ ስለዚህ በሕዝብ ላይ ኢንቨስት ያድርጉ፤ (ከሕዝብ ጋር ይቁሙ)፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማነቆ የሆኑት የጸረ አሸባሪነት ሕግ እና የመያዶች ሕግ እንዲሻሻሉ ወይም እንዲሻሩ ማድረግ ይችላሉና በዚህ ላይ ይሥሩ፤ በቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት አሜሪካ እንዳደረገችው በኢትዮጵያም የሲቪክ ማኅበረሰቦች (መያዶች) በነጻነት እንዲንቀሳቀሱና ሕዝብን በማንቃት ረገድ ተግባራቸውን እንዲወጡ እርስዎም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ይቁሙ” በማለት በቀጥታ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ሲቀጥሉም “የኢኮኖሚ ዕድገት አለ ይባላል፤ የሚታይ እንቅስቃሴ አለ፤ መንገድ ይሠራል፤ ፎቅም ይገነባል፤ ሆኖም የኢኮኖሚን ዕድገት በፎቅና መንገድ ሥራ መለካት አይቻልም፤ ኢኮኖሚው በእርግጥ እያደገ እየተመደገ የሄደ ከሆነ ለምንድነው ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን መስዋዕት በማድረግ ቀይባህርን አቋርጠው የተሻለ ኑሮ ፍለጋ የሚሰደዱት፤ ከአጠቃላዩ ሕዝብ 6 በመቶ በማይበልጥ አናሳ ብሔረተኞች ቁጥጥር ስር ስለሆነ አድጓል የሚባለው ኦኮኖሚ ይህ ነው የሚባል ለውጥ በሕዝቡ ኑሮ ላይ ሊያመጣ አልቻለም” በማለት ኦባንግ ሜቶ በመላው ዓለም ፕሮግራሙን ለሚከታተሉ የአገራቸውን ሁኔታ አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም የጋራ ንቅናቄው ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ “አፍሪካውያንም ሆነ ኢትዮጵያውያን ኦባማን ወይም አሜሪካንን ወይም ምዕራባውያንን ነጻ እንዲያወጡን እየለመንን አይደለም፤ ራሳችንን እንዴት ነጻ እንደምናወጣ እናውቃለን፤ ነገር ግን (ከአምባገነኖች ጋር በማበር) በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን” በማለት ግልጽ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Friday, July 24, 2015

ዝዋይ እስር ቤት

July 24,2015
ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም
temeprison

ሐምሌ 16/2007 ዓ.ም. ለአሥር ወራት በእስር ላይ የቆየውን ጋዜጠኛ፣ ተመስገን ደሳለኝን (ከኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ዝምድና የለውም፤) ለመጠየቅ ወደዝዋይ ወህኔ ቤት ሄጄ ነበር፤ የወሕኒ ቤቱ ባለቤቶች ማረሚያ ቤት ይሉታል፤ ማረሚያ ቤት ማለት ሀሳቡን በነጻነት የሚገልጽና በሀሳቡም ከወያኔ ጋር በሎሌነት ለመተዳደር የማያመች ሲሆን የቀናውን በጉልበት የሚያጎብጡበት ማለታቸው ነው፤ ማረም ማለት ቀጥታውን ማጉበጥ ነው፤ እንዴት እንደሚያጎብጡት ላሳያችሁ፤–
1. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች ሰዎች በመሆናቸው ሰብአዊ ደኅንነታቸውና ክብራቸው ሁልጊዜም እንዲጠበቅላቸው ያስፈልጋል፡፡
2. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች ሁሉ ከመሰቃየትና ከመጉላላት በጸዳ አያያዝ እንዲጠበቁ ይደነግጋል፤
3. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ አንድ እስረኛ ዘመዶቹና ወዳጆቹ ከሚኖሩበት በጣም ርቆ አይታሰርም፤
4. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ የታመመ እስረኛ ሙሉ ህክምናና አስፈላጊውን መድኃኒት ሁሉ ማግኘት አለበት፤
5. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ እስረኞች በአእምሮና በመንፈስ የሚያድጉበት ትምህርትን የማግኘት፣ መጻሕፍትን የማግኘት መብቶች አሏቸው፤
6. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ማንኛውም እስረኛ በእምነቱ መሠረት አምልኮቱን የመፈጸምና የሃይማኖቱን መጻሕፍት የማንበብ መብት አለው፤
7. የኛን እንተወውና በተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ማንኛውም እስረኛ ዘመዶቹና ወዳጆቹ እንዲጎበኙት መብት አለው፤
8. እስረኞች የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ከወህኒ ቤት ሲወጡ ትክክለኛ የማኅበረሰቡ አባሎች ሆነው እየሠሩ ለማኅበረሰቡ እድገት ድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ማሰናዳት ያስፈልጋል፤
በዝዋይ እንዳየነውና እንደተነገርነው የእስረኞች ሁኔታ በጣም የሚያሳዝንና ከላይ የተዘረዘሩትን የሰብአዊ መብቶች የሚጥስ ነው፤ ጤንነት ዋና ነገር ነውና በሱ እንጀምር፤ ተመስገን ደሳለኝ ወንጀል የተባለበት የፖሊቲካም ሆነ የማኅበረሰብ እምነቱን እያፍረጠረጠ በመጻፉ ነው፤ (በ1992 ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባደረግሁት ንግግር ‹‹አትፍሩ›› ብለሃል ተብዬ ተከስሼ ነበር!) እንዲያውም ክሱን አስቂኝ የሚያደርገው መንግሥትን ነቅፈሃል የሚል መሆኑ ነው፤ ሦስት ዓመት እስራት ተፈረደበት፤ ይግባኝ ተከለከለ፤ አሁን ከታሰረ አሥር ወራት ሆኑት፤ ተመስገን በጣም ከታመመ ጥቂት ቆየ፤ አንደኛ አንዱ ጆሮው በጭራሽ አይሰማም፤ ሁለተኛ ከባድ የወገብ ሕመም ስላለበት መተኛትና መቀጥም በጭንቅ ሆኖበታል፤ ሆኖም አሳሪዎቹ ወደሀኪም ቤት ሊወስዱት ፈቃደኛ አይደሉም፤ ከዚያም በላይ መድኃኒት ከውጭ ሲመጣለት ይከለክላሉ፤ እኔም የወገብ ሕመም ስላለብኝ የወገብ ሕመሙን የሚያቀልለትን መድኃኒት ወስጄለት ነበር፤ አንድ አሥር አለቃ መድኃኒቱን አየና ከለከለ፤ መልሼ ይዤው መጣሁ፤ እንዲህ ያለውን ውሳኔ የሚያደርጉ ሁሉ ወያኔዎች ናቸው፡፡
ከተመስገን ጋር ትንሽ ጊዜ ቆይተን በዚያው በዝዋይ የታሰሩ ሌሎች ጋዜጠኞችን ለመጠየቅ መጀመሪያ ተፈቅዶልን ስለነበረ ወደዚያ ስናመራ አንድ ሹም መሳይ መጥቶ ወታደሮቹን ለብቻ ለብቻ በስም እየጠራ በመንሾካሾክ ትእዛዝ ይሰጣል፤ እየተንሾካሾከ ለአንዱ ትእዛዝ ሰጥቶ ሌሎቹን እንዳናይ ከለከለንና ተመለስን፤ ምክንያቱን ብንጠይቅ በአንድ ጊዜ መጠየቅ የሚቻለው አንድ እስረኛ ብቻ ነው ተባልን፤ ቅን መንፈስ ለጎደለውና ለሙስና ለተጋለጠ አሠራር ጥሩ ምሳሌ ነው፤ በመንሾካሾክ የሚሰጠውም ትእዛዝ ዓላማው ያው ይመስላል፤ ወያኔ በሰዎች ላይ እንዲህ ያለ ጭካኔ ማሳየት የሚፈልገው ለምንድን ነው?
በዝዋይ እስር ቤት ትምህርትም እንደመድኃኒት የተጠላ ነገር ነው፤ ለተመስገንም ሆነ ለሌሎች መጻሕፍት አይገቡላቸውም፤ ለምን? ብዬ ስጠይቅ አንዱ ጠባቂ ‹‹ለእውቀት የሚሆን መጽሐፍ ይገባል፤›› አለኝ፤ የእውቀትን ፍቺ ለመጠየቅ ስሞክር ቶሎ ግራ መጋባቱን አየሁና ተውሁት፤ እሱም እንዳያውቅ ስለሚፈልጉ፣ አለቆቹ የእውቀትን ፍቺ ጠበብና ቀለል አድርገው አስተምረውታል፤ ሎሌ ትእዛዝን በሹክሹክታ እየተቀበለ ማስፈጸም እንጂ፣ እውቀት አያስፈልገውም፤ እዚህ ላይ ምናልባት በደርግ ጊዜ በእስር ቤቶች የነበረውን የትምህርት መስፋፋት ማንሣት ይጠቅም ይሆናል፤ በደርግ ዘመን ብዙ የተማሩ ሰዎች ታስረው ስለነበረ እረስበርሳቸው እየተማማሩ አንዳንድ ሰዎች ጀርመንኛና ፈረንሳይና ቋንቋዎች፣ ግእዝና ታሪክ እየተማሩ ወጥተዋል፤ በተለይ በሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ወህኒ ቤቶች አንደኛ ሲወጡ እንደነበረ አስታውሳለሁ፤ ዛሬ በወህኒ ቤቶች ትምህርት ክልክል ነው፤ በቃሊቲ ሁለት የትምህርት ሙከራዎች ከሽፈውብናል፤ አንድ ጊዜ ኦሮምኛ ለመማር የፈለግን ሰዎች ተሰባስበን ተከልክለናል፤ ሕግ ለመማርም ጀምረን ታግደናል፤ እንዲሁም ጂምናስቲክ በቡድን መሥራት ክልክል ነበር፤ ማናቸውም እውቀት አደገኛ ነው! ታዲያ ማረሚያ ቤት የሚሉት ማንን ለማታለል ነው? ማረሚያ ቤት እንዲሆን በመጀመሪያ አሳሪዎቹ መታረም አለባቸው!
እንደተመስገን ደሳለኝ፣ እንደአብርሃ ደስታ፣ እንደእስክንድር ነጋ፣ ከዞን ዘጠኝም በፈቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ወበላ፣ አጥናፉ ብርሃኔ ገና አልተለቀቁም፤ በተጨማሪም ከእስልምና በኩል የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባሎች ዛሬም እንደታሰሩ ነው፤ የመፍትሔ አፈላላጊዎችን ማሰር ነገሩም ግራ ነው፡፡
በመጨረሻም መነሣት ያለበት አንድ አደገኛ አዝማሚያ አለ፤ ፖሊስ የሚባለው ፍርድ ቤት ከሚባለው ጋር ያለው ግንኙነት ሕግ የሚባለውን ከጨዋታ ውጭ አድርጎታል፤ ፍርድ ቤት የሚባለው እስረኛ እንዲፈታ ፖሊስ የሚባለውን ሲያዝ እንደማይፈጸም በተደጋጋሚ ታየ፤ ይህ የመጨረሻው የውድቀት ምልክትይመስለኛል፤ቆም ብሎ ማሰብና አስፈላጊውን የለውጥ እርምጃ መውሰድ የሚያስፈልገው አሁን ነው፡፡
ሐምሌ 17/2007

Thursday, July 23, 2015

AG7, TPDM, and ADFM to form a coalition; OLF and ONLF excluded

July 23,2015
Image
Arbegnoch Ginbot 7 (AG7), Tigray People's Democratic Movement (TPDM), and Amhara Democratic Force Movement (ADFM) have been directed by the Eritrean regime to form a coalition, according to ER sources in Eritrea.

Two senior leaders of AG7, Dr Berhanu Nega and Ato Neamin Zeleke, are currently in Asmara.

The AG7-TPDM-ADFM coalition's political wing will be headed by Dr Berhanu while the military wing will be headed by Ato Molla Asgedom, ER sources report.

AG7 and ADFM combined have less than 100 members on the ground, while TPDM has over 40,000 armed and well-trained members.

AG7 has been pushing for Oromo Liberation Front (OLF) and Ogaden National Liberation Front (ONLF) to be included in the coalition, but the Eritrean regime (Shabia) has refused.

ER sources added that Shabia is preparing to launch a guerrilla-style and asymmetrical warfare with TPDM and its own forces before the rainy season is over. Shabia believes that it can cripple Woyanne's military during the next few months when it is able to respond only by air. Woyanne tanks and artillery will be useless during the rainy season, according to military analysts. Targets will include lightly protected factories, bridges, and key supply routes. More details later...

Q&A: Professor Berhanu Nega – Bucknell University

July 23, 2015
dr-berhanu-NegaIn December, an Ethiopian court sentenced Professor of Economics Berhanu Nega to death in absentia for terrorism.
Q: Your colleagues and friends understand that this charge is bogus, but do you hear from others who don’t?
A: I haven’t heard from any one who takes this as a serious judicial decision. Only the Ethiopian government and its blind supporters take this decision seriously. Even the government knows that the decision of the court is nothing but a reflection of the regime’s desires rather than based on any reasonable evidence. It sends a message to the public — there is no court to save you, you live by our rules, if you question our rules, we will do what we want, and no one will stop us.
Q: The death sentence is real, and you were jailed under the Zenawi government. Are you afraid?
A. One of the reasons that you struggle for freedom and liberty is because you feel that life isn’t meaningful without liberty. I don’t want to think about this in a way that would affect my day-to-day existence. I am not worried not because the government would not try to harm me, but I now live in a society of laws that will protect me. You can’t live in fear. If you allow this kind of fear to determine your actions, dictatorships will exist forever.
Q: What sustained you when you were imprisoned?
A: First, the Ethiopian people and their yearning for freedom. While I was incredibly disappointed by U.S. and European policy makers and diplomats at the time, while I was in prison, I also was hearing about Bucknell, my colleagues, students and people at other universities supporting freedom. People who love liberty and stand by your side — that’s the more endearing attachment. This connection at the human level, that people love and support freedom everywhere, recognizing that freedom is a human condition, is the hope for humanity that keeps you going. It was a source of hope for me when I was in prison, and I suspect for all people fighting for liberty around the world.
Q: What is your hope for Ethiopia?
A. Unless the international community takes the position of outrage as it did in Guinea, the government will not change. The brutality of this regime is mind boggling. This is a government that is known for committing genocide against its people. This is a most hated government because it is not only undemocratic, it is ethnocentric. Its basic strategy is to stay in power by terrorizing people and by dividing them on primordial grounds. There are several groups fighting against the government. Unless there is a serious intervention, the whole region will blow up. I encourage Western policymakers to recognize what is happening and adjust their policy before it is too late to make a difference. The only credible and durable solution for the region, in my view, is the democratization of Ethiopia.