Tuesday, March 3, 2015

ግልጽ ደብዳቤ፣ በምርጫ ቦርድ ድረ ገጽ ለወጣው የአመክንዮ ክሽፈት ጽሁፍ ባለቤት

March 3, 2015
ከግርማ በቀለ ( የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት ሊቀመንበር)1.መግቢያ፡-
በምርጫ ቦርድ ኦፊሺያል ዌብ ሳይት ላይ ስለ ኢ/ር ይልቃል ‹‹የአመክንዮ ክሽፈት›› የተለጠፈ አንድ መግለጫ ይሁን ማብራሪያ ፣ ማስፈራሪያ ይሁን ማስተማሪያ መሆኑ ያለየለት/ወይም ለመለየት የሚስቸግር እንዲያው በጥቅሉ ቦርዱ ራሱን ከኢ/ር ይልቃል ጋር እያወዳደረ ወይም እልህ የገባ ወይም በፈጠራ ወንጀል ለመጥለፍ እየተዘጋጀ መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ጽሁፍ ይነበባል፡፡ የጽሁፉን ይዘት በሚመለከት አጭር አስተያየት የምንሰጥበት ሆኖ አንባቢ ሲያነብ እነዚህን ጥያቄዎች በአዕምሮው ይዞ ቢሆን የዚህን አስተያየት መነሻ ምክንያትና አመክንዮ የመረዳት መንገዱን ያቀልለታል፡፡ እነዚህም– በይዘቱ ላይ የሚነሱ ሌሎች መከራከሪያዎች ቀርተው ጽሁፉ በምርጫ ቦርድ ኦፊሺያል ዌብ ሳይት ላይ በመውጣቱ ብቻ ፡- ለቦርዱ ይህን ግለሰብን/ያውም የፓርቲ መሪን/ በስም መስደብና መወንጀል የሀገሪቱ ህግ ይፈቅድለታልን/የሚፈቅድለት ህግ አለን ወይስ ቦርዱ ከህግ በላይ/ ‹‹የባለሥልጣን ዶሮ›› ስለሆነ ጠያቂ የለኝም በሚል ያደረገው ነው? በተሻሻለው የምርጫ ህግ አንቀጽ 5 ላይ ለቦርድ ከተቀመጠው ዓላማ /ገለልተኝነት፣ ኢ-አድሎኣዊነት…./ አይጋጭምን? አንቀጽ 7 ላይ ለቦርድ ከተቀመጠው ተግባርና ኃላፊነት የወጣ አይደለምን?Girman Bekele Ethiopian politician
ጽሁፉ በመነሻው ላይ የቦርዱን ያላሰለሰ ጥረትና የሚጠበቀውን ውጤት ሲገልጽ ‹‹…ከእንከን የፀዳ ሆኖ እንዲጠናቀቅ…››ይላል፡፡ ጸሃፊው የቦርዱ ሰብሳቢ በአደባባይ/ሸራተን/ ‹‹እንከንየለሽ/ከእንከን የጸዳ/ ምርጫ በዓለማችን የለም ›› ያሉትንና ሁሉንም/ቢያንስ ከእኔ ኃሳብ የሚስማማ/ የሚያስማማ ንግግር አልሰማም ወይስ ምርጫ 2007 በዓለም ታይቶ የማይታወቅና በ‹‹ ጊነስ ቡክ››የሚመዘገብ ታሪክ ለማስመዝገብ ግብ ማስቀመጡን የቦርዱ ሰብሳቢ አልሰሙም ማለት ነው?
እዚህ ላይ አንድ ጉዳይ ጠቅሶ ማለፍ የጽሁፌን ዓላማ ግልጽ ያደርገዋል፡፡ ይህም ይህን የምጽፈው ለኢ/ር ይልቃል ጥብቅና ለመቆም (በራሳቸው አይደለም በአገራቸውና በዜጎች የሚፈጸመውን ህገወጥ ተግባር ለመመከት ያላቸውን ብቃት አስመስክረዋልና የእኔ ድጋፍ አያስፈልጋቸውም በሚል) አይደለም፤ ይልቁንም በአመክንዮ ስም የሚደረገውን ከአመክንዮ የወጣ ጽሁፍ ዝም ብሎ ማለፍ ተገቢ ሆኖ ስላላገኘሁበትና ከጽሁፉ በተቃራኒ በቦርዱ የተደረገውንና በቀጣይም ‹‹ሠይጣን ለማሳቻ ከመጽኃፍ ቅዱስ ይጠቅሳል›› እንዲሉ መሆኑን ለማሳየት/ለማጋለጥ ነው፤ ምን ያልተጋለጠ አለና በከንቱ ትደክማለህ ካልተባልኩ በቀር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሳይሆን ባልተናነሰ በጽሁፉ የተነሳው ጉዳይ በግልና እንደ ድርጅት መሪ በቀጥታ የሚመለከተኝ በመሆኑና በተነሳው ጉዳይ ሂደትና ውጤት በቀጥታና በተዘዋዋሪ የተጎዳሁ በመሆኑ ነው፡፡
የጥያቄዎችን መልስና ስለ ጽሁፉ ዓላማ ያነሳሁትን በዚሁ ልግታና በ‹‹ምርጫ ቦርድ›› ጽሁፍ ላይ ወደ ተነሱት የአመክንዮ ክሽፈት ነጥቦች እናምራ፡፡
2. የተነሱ የአመክንዮ ክሽፈት ነጥቦች፤
2.1. ክሹፍ አመክንዮ 1 ላይ–
ይህ ላይ የቀረበውን የጽሁፉን ይዘት ስናጠቃል ‹‹ህግ መቃወም አይችልም›› የሚል አንድምታ እንዳለው እንመለከታለን፡፡ የተደራጁ ዜጎቸ ቀርቶ አንድ ዜጋ እንኳ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ አንድን አዋጅና ህግ አይደለም፣ህገ መንግስቱን መቃወም፣ የሚቃወመውንም ለመቀየር/እንዲቀየር መታገል ይችላል፤ ይህ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ህገ መንግስቱም ሆነ አዋጆች/ህጎች የፈጣሪ ቃል አይደሉምና ሊተቹ አይደለም ሊቀየሩ እንደሚችሉ ስለሚታወቅ ህገ መንግስቱን የማሻሻያ ስርዓት በህገ መንግስቱ በግልጽ ሰፍሯል፡፡ የኢትዮጵያ የምርጫ ህግና የፓርቲዎች ምዝገባ አዋጆች መሻሻላቸው ወደፊትም ሊሻሻሉ የሚችሉ መሆናቸው የሚያረጋግጠው ይህንኑ ነው፤ በመሆኑም ጉድለትን መተቸት፣መቃወም፣ የማይቻልም ወንጀልም አይደለምና ባለ አመክንዮው ጸሃፊ/ቦርዱ ይህንን ከየት እንዳመጣው አልገለጸምና አመክንዮኣዊነቱን ባዶ ያስቀረዋል፡፡
ሌላው በጽሁፉ የተነሳው ጉዳይ የኢ/ር ይልቃልን ኃሳብ ‹‹…የፖለቲካ ፓርቲዎቹን ህጋዊ ሰውነት የሚገዳደር…›› በማለት የቀረበው ነው፡፡ ይህ ኢንጂነሩ ‹‹ህጋዊ ሰውነታቸውን ለተገዳደሩኣቸው›› ፓርቲዎች በመቆርቆር የተነሳ ኃሳብ ከሆነ በአንድ በኩል እውነትም ቦርዱ ለፓርቲዎች ዋስ ጠበቃ እየሆነ ነውና መጪው ጊዜ ከቦርዱ ጋር ለፓርቲዎች ‹‹ብሩህ›› መሆኑን ያሳያልና እሰዬው እንበል፤ በሌላ በኩል እንዲያውም በተቃራኒው ህጋዊ ሰውነታቸውን ኢንጂነሩ ለተገዳደሩባቸውና ቦርዱ ዋስ ጠበቃ ለሚሆንላቸው ፓርቲዎች ‹‹መብታቸውን የማያውቁ፣የራሳቸውን መብት ማስጠበቅ የማይችሉ፣ ደካሞች፣…›› የሚል መልዕክት የሚያስተላልፍና ለመብታችሁ እድንቆምላችሁና መጪው ጊዜ ከእኔ ጋር ብሩህ እንዲሆንላችሁ ከጎኔ ተሰለፉ ጥሪ ነው ማለት ይቻላል፡፡ አመክንዮውን የበለጠ ባዶ የሚያስቀረው ጸሃፊው/ቦርዱ ስለፓርቲዎች ህጋዊ ሰውነት የተቆረቆረው በምርጫ አዋጁ የተቀመጠለትን ተግባር ተከትሎ ከኦሕዲኅና 9 ፓርቲዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች መልስ ባልሰጠበት መሆኑ ነው፡፡
ግልጽ ላድርገው–ከቦርዱ ዓላማ፣አሰራርና እየፈጸመ ያለውን ከታች በ2.1.3. ስር በተጠቀሰው የምርጫ ህግ አንቀጽ 12 የቦርድ አባላት ስነ ምግባር ቁጥር 1፣2፣5፣እና አንቀጽ 38 መሰረት እንመልከተው፡- ከላይ ጸሃፊው/ቦርዱ ለፓርቲዎች ህጋዊ ሰውነት ተቆርቋሪነቱን የገለጸው በምን ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ነው ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ የሚከተለው ነው፡፡
2.1.1. ቦርዱ ኦሕዲኅ አመራሩና አባላቱ በምርጫ 2007 በ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ምልክት›› እንዲወዳደሩ የፈቀደበትን ምክንያትና መነሻ የሚያብራራና ይህም በቦርዱ የጸደቀ መሆኑን የሚያሳይ ደብዳቤ (በቁጥር-ኦህዲኅ/0017/07፣በቀን ጥር 30/07 ) በቦርዱ ሳይታይ በጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ ተጽፎ ሲሰራጭ ለኦህዲኅ ያልደረሰ ህገወጥ የጓሮ በር መልስ በሰጡበት፣ ይህንንም በመቃወም ለቦርዱ በድጋሚ ለቀረበው ይህ የም/ኃላፊው ደብዳቤ እንዲሻር በኦሕዲኀ የተጻፈ ደብዳቤ (በቁጥር-ኦህዲኅ/0017/07፣በቀን የካቲት 10/07 ) የውኃ ሽታ ሆኖ በቀረበትና በዚህም ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸው የኦሕዲኅ አመራርና አባላት አቤቱታ ሳይቀርብባቸው በምርጫ የጊዜ ሰሌዳው መሰረት የዕጩ ምዝገባው በ04/06/07 ከተጠናቀቀ ሳምንት በኋላ በ11/04/07 በስልክ ትዕዛዝሙሉ በሙሉ ከዕጩነት በተሰረዙበት፤
2.1.2. በተመሳሳይ የቦርዱ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ የ9ኙ ፓርቲዎችን ህጋዊ ሰውነት በመካድ በ‹‹ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ/ትብብር›› በቅንጅት ለመስራት ያቀረቡትን ጥያቄ (በመንገድ ቁጥር በቀን 21/02/ 2007 ዓ.ም. ወጪ የሆነ ደብዳቤ) ከህግ አግባብ ውጪ አፍነው ለማስቀረት በተደጋጋሚ የሄዱበትን አሰራር በመቃወም ለቦርዱ ሰብሳቢ ላቀረቡት ደብዳቤ መልስ ባለመስጠቱ የ‹‹ትብብሩ››አባላት የጋራ እንቅስቃሴኣቸውን ለማቆም በተገደደቡት፤
2.1.3. በተቃራኒው ሌሎች 9ኙ ፓርቲዎች (አሁን በጋራ በመስራት ላይ ያሉት- የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር) ደግሞ የጋራ ተግባራትን በጋራ ለመስራት ‹‹የስነ ምግባር ህጉ አንቀጽ 3 (የተፈጻሚነት ወሰን) ቁጥር 1 ( ይህ አዋጅ- በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ፣የግል ዕጩ ተወዳዳሪ፣እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅንጅት፣ ግንባር፣ ጥምረት፣ ወይም ንቅናቄ…ተፈጻሚ ይሆናል)፣አንቀጽ 38 ላይ (‹‹ማንኛውም ህግ ወይም አሰራር በዚህ አዋጅ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚ አይሆንም፡፡››) በሚልበት በህጋዊ ሰውነታቸው በሚመነጨው መብታቸው ላይ ቆመው በጋራ ለመስራት (ጥምረት ይሁን ንቅናቄ ዕውቅና/ሰርቲፊኬት ቦርዱን የሚጠየቁበት ህግ በሌለበት) የተስማሙ፣ ነገር ግን ለዚህ የቦርዱን ዕውቅና ያልጠየቁ (ቦርዱ ዕውቅና/ሰርቲፊኬት የሚጠየቀው በቅንጅት፣ በግንባር ለመስራት ወይም ለመዋሃድ ብቻ ሆኖ ባለበት) ለ9ኙ ፓርቲዎች ዕውቅና/ ሰርቲፊኬት አልሰጠሁም በሚል ‹‹…ሰማያዊ አስተባብራለሁ…›› እያለ… በሚወነጅልበትና የድርጅቶችን ህልውና ከተቋቋመበት ዓላማ በተቃራኒ ራሱ እየካደ፣ ይህ ኃላፊነትና ተግባር ከማይጠበቅበት እንዲያውም የራሱን ዓላማና ፓርቲ ከሌላው የሚሻልበትን/የሚበልጥበትን ማሳየት የማያስጠይቀው ወገን /ሰማያዊ/ ላይ ጣት መጠንቆል፤ አመክንያኣዊ ነውን?
ከላይ እንዳልነው መልሶቹንና ፍርዱን ለአንባቢ፣ ለኢትዮጵያዊያን በመተው፣ይህንንም መዝግበን ወደ ቀጣዩ የጸሃፊው/ቦርዱ ‹‹የአመክንዮ ክሽፈት›› ትንታኔ እንለፍ፡፡
2.2. ክሹፍ አመክንዮ 2 ላይ –
ይህም ከላይ ከተጠቀሰው ብዙም የተለየ አይደለም፤ ህጉን ‹‹አይነኬና አይጠየቄ›› ከማድረግ ባለፈ በዓላማ ደረጃም አነሳሱ ባዶ ውንጀላ በማቅረብ የማስፈራሪያ ፣ሲያልፍም በመሰረተ ቢስ ክስ ለመጥለፍ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አብሪ ጥይት ነው ማለት ይቻላል፡፡ እስቲ ማሳያዎቹን ጠቅለል አድርገን እንመልከት፡፡
በዚህ ክፍል የቀረበውን የጽሁፉን ይዘት የ‹‹ከስነ ምግባር ደንቡ ጋር የሚያላትማቸዉ ስለመሆኑ ልብ ያሉት አይመስሉም ወይም የህግ ጥሰቱን የስራቸዉ አንድ አካል አድርገዉታል ማለት ነዉ፡፡›› በማለት የተገለጸው ያጠቃልለዋል ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ደግሞ ጸሃፊው/ቦርዱ ‹‹አይነኬና አይጠየቄ›› ባደረጓቸው ህጎች (የመተቸትና መጠየቅ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ተቀብለናቸው) አንጻር እንመልከት፡፡
ይህን እስኪ የምርጫ ህግ አንቀጽ 12 (የቦርድ አባላት ስነ ምግባር) ቁጥር 1.(በነጻነት፣ ገለልተኝነትና ቅን ልቡና ማገልገል)፣ ቁ.2 (በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የቱንም ወገን ያለመቃወም ወይም ያለመደገፍ)፣ቁ.5 (በማንኛውም ሁኔታ የቦርዱን ወይም የአባሉን ተኣማኒነት፣ገለልተኝነትና ነጻነት ከሚጎዳ ወይም ከሚያጎድፍ ማንኛውም ተግባር መቆጠብ)፣ አለበት ከሚለው አንጻር እንዳሰው ፡፡
2.2.1. ከዚህ አንጻር የሥነ ምግባር ደንቡ ዝግጅት የቀረቡት (በሂደት/አዘገጃጀት/ እና ይዘት/) ጥያቄዎች ሳይመለሱ የጸደቀን የስነ ምግባር ህግን፣ያውም በዝግጅቱ ወቅት ያልነበረ ፓርቲን መቃወም አይችልም የሚል ክስ ማቅረብ አመክንዮ መነሻ ከየት የመጣ ነው/ወይም አመክንዮኣዊ ነውን?
2.2.2. የምርጫ ህጉስ ቢሆን በፓርቲዎች ዕጣ አወጣጥስ የዕጩዎች በፓርቲ አመራር ያላቸውን ደረጃ፣ የፓርቲው አደረጃጀት/ብሄራዊ ወይም ክልላዊ/፣ ዕጩዎችን ያቀረቡ ፓርቲዎች በምርጫው ያላቸው ተሳትፎ/ያቀረቡት ዕጩዎች ብዛት/፣ የፓርቲዎች በአገራዊ ፖለቲካው ያላቸው እንቅስቃሴ/ተሳትፎ-የቢሮ ብዛት፣ለህዝብ ተደራሽነት/… ባለማካተቱ ጉድለት አለበት ማለት አይቻልም የሚል አመክንዮስ ከየት የመጣ ነው/ወይም አመክንዮኣዊ ነውን?
2.2.3. ለመሆኑ ቦርዱ ራሱ የሥነ ምግባር ህጉን፣ያውቀዋል፣ እየተገበረ ነውን? ለዚህ ጥቄ መነሻ ማሳያዎች -
የምርጫ ህጉ አንቀጽ 8 (የቦርዱ ሰብሳቢ ስልጣንና ተግባር) ቁጥር 4 ላይ ‹‹የፖለቲካ ድርጅቶችን የጋራ መድረክ በሰብሳቢነት ይመራል›› ይላል፡፡ የሥነ ምግባር ህጉ ደግሞ የጋራ መድረክ ሰብሳቢ ማን እንደሆነ አንድም ቦታ አይገልጽም፣ይህን በሁለት አዋጆች መካከል መናበብ በሌለበት ሁኔታ ባልተጻፈ ህግ በዘፈቀደ የሚከወነውን አፈጻጸም አይነኬ ማድረግ ነውን አመክንያዊነት?
ቦርዱስ በምርጫ ህጉ በአንቀጽ 7 ቁጥር 9 ላይ (‹‹የፖለቲካ ድርጅቶችን የጋራ መድረክ የማደራጀትና ማስተባበር) የተጣለበትን ኃላፊነት እየተወጣ ነውን?
2.2.4. የስነ ምግባር ደንቡን ከኢህአዴግ ጋር ያረቀቀው/ያዘጋጀው…መኢአድ በጋራ ምክር ቤት ተሳትፎ ማድረግ ባቆመበት/እምነት ባጣበት/ ህጉ ሲወጣ ላልነበረው ለሰማያዊ ፓርቲ መሪ አይነኬ ማድረግ ነውን አመክንያዊነት?
የሚሉትን ስንመለከት ጸሃፊው/ቦርዱ ከላይ በምርጫ ህጉ ቀ 12 በቦርዱ ላይ የተጣለበትን ሥነ ምግባር የተከተለ አሰራር ባልተከተለበት፣ነጻነቱ፣ገለልተኝነቱ… ተኣማኒነቱ ከጥያቄ ውስጥ ወድቆ ባለበት፣በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር ባላከናወነበት…በሌላው ያውም በግለሰብ ላይ ይህን ዓይነት ጽሁፍ መጻፍና በዌብሳይቱ ላይ መለጠፍ እንደምን ህጋዊና ምክንያታዊ ያደርገዋል፣በምን የሞራል መሰረት በአመክንዮ ለመከራከር ያስችለዋል? መልሱንና ፍርዱን ለአንባቢና ለባለቤቱ መራጭ ህዝብ እንተወውና ወደ ቀጣዩ እንሸጋገር፡፡
2.3. ክሹፍ አመክንዮ 3 ላይ፡-
በዚህ ክፍል ውስጥ በጽኁፉ ‹‹…. 23 ተጠቋሚ እጩዎችን አቅርበዋል፡፡ይሁንና ከእነዚህ መካከል ሁለቱ የአንድነትና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኀብረት አመራሮች በመሆናቸዉና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በሰማያዊ ፓርቲ ጥላ ስር (በ9 ኙ ፓርቲዎች ትብብር ስም )ለመወዳደር የተመዘገቡ በመሆናቸዉ እንዲሰረዙ ሆኗል፡፡ ›› የሚለውን እናገኛለን፡፡
ይህ ደግሞ የባሰበትና ጆሮ ደፍኖ/ይዞ በህግ አምላክ እያሉ የሚያስጮህ በቅጥፈትና ክህደት የተሞላ ነው፣ እንዴት የሚለውን አብረን እንመልከት፤
2.3.1. ጽሁፉ ‹‹….(በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ስም) በመመዝገባቸው እንዲሰረዙ ሆኗል›› ያለው በ9ኙ ትብብር ስም የቀረበ ዕጩ በመላ አገሪቱ ባሉት ምርጫ ክልሎች ቢታሰስ በማይገኝበት በመሆኑ ትዝብት ላይ የሚጥል ነው፤/በዚህ ላይ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ኢትዮምህዳር የካቲት 18/07 ቅጽ2 ቁጥር 96 እትም እና Fortune Vol 15 No 773, Feb 22/15/ ይመልከቱ፤
2.3.2. ቦርዱ ‹‹…አመራሮች በመሆናቸዉና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በሰማያዊ ፓርቲ ጥላ ስር…›› ይላል በሌላ በኩል የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አባል የሆነው መኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ የፋይናንስ ኃላፊ አቶ ኑሪ ሙዲስር ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ ሆነው ተመዝግበዋል፡፡ ይህ የዕጩ ምዝገባው በህግ ሳይሆን በዘፈቀደና በምርጫ ቦርድ በጎ ፈቃድ ወይም በድርብ መመዘኛ/Double Standard/ የተመራ መሆኑን በግልጽ ያሳያል፡፡
2.3.3. ይህን በሚመለከት ኦህዲኅ ከላይ በ2.1.1. ሥር የተገለጹትን ሁለት ደብዳቤዎች አቅርቦ መልስ ባላገኘበት በጓሮ በር ትዕዛዝ አመራሩና አባላቱ ከዕጩ ምዝገባ ቀን በኋላ በስልክ በተሰጠ ትዕዛዝ በተሰረዙበት፤ እውነት ውስጥ የሆነው ነው አመክኒዮኣዊነት?
እንግዲህ በዚህ መልክ የተሰራውን/ጸሃፊው/ ወይም የሰራውን /ቦርዱ/ ነው ክሹፍ አመክንዮ እና ህገወጥ እየተባለ የተፈረጀው፡፡ ፍርዱን ለአንባቢ ትተን የያዝነውን ጉዳይ እናጠቃለው፡፡
3. ማጠቃለያ፡-
3.1. ውሉ የጠፋበት/ የቦርድ መግለጫ ይሁን የቦርድ ሠራተኛ አስተያየት/ የክስ ማቀበያና ፈሪ ከተገኘም ማስፈራሪያ ጽሁፍ መሆኑ፤ ይህን አቶ ወንድሙ በአየር ሰዓት ድልደላ ላይ ሰማያዊ ላቀረበውን ጥያቄና ተቃውሞ ምላሽ ከዚህ ቀደም የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ አስታውሰው ‹‹በቀጣይ ከእንዲህ ዓይነቱ ተግባር የማይቆጠብ ከሆነ ቦርዱ እርምጃ ለመውሰድ ይገደዳል›› ካሉት ጋር ሲታይ፤
3.2. በጽሁፉ ማብቂያ ላይ ‹‹እንደ አጠቃላይ ኢ/ር ይልቃል በምርጫዉ ሂደት ላይ ጭቃ ይለጥፉ ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ መድረኮችን ረግጦ መዉጣት፣ በኢ-ተገቢ ዘለፋ መጀገን እና የሀገሪቱን የምርጫና የስነምግባር ደንቡን የሚገዳደር ተግባር በመፈጸም መጀገን የሚያስከፍለዉን ዋጋ ካለማወቅ ወይም ለማወቅ ካለመሻት መነሾ ባደረገ መልኩ እየገፉበት ነዉ፡፡›› የሚለውን ስንመለከት፤
3.3. ከላይ የቀረቡትን ጥያቄዎችና በተጨባጭ መረጃዎች የተደገፉ ማሳያዎችን እና የተጠቀሱትን የህግ አንቀጾች ከጽሁፉ ይዘት ጋር ስናገናዝብ፤
የጽሁፉ መልዕክትና ይዘት ወገናዊነት ግልጽ መሆኑ ቀርቶ ይህ ዓይነቱ በአንድ የፖለቲካ አመራር ላይ ያነጣጠረ ጽሁፍ በቦርዱ ዌብሳይት መውጣቱ በራሱ የቦርዱን ገለልተኝነት አጠያያቂ ከማድረግ አልፎ ህገወጥና የሚስጠይቅ ያደርገዋል ወይም ያስጠይቀው ‹‹ነበር›› ብሎ ማጠቃለል ይቻላል፡፡
ሆኖም ምርጫ ቦርድ የሚመካበት አለውና ድርጊቱም ‹‹እስመ አልቦ ነገር ዘይሳነው ለምርጫ ቦርድ›› እየሆነ ነውና አይደለም ኢ/ር ይልቃልን፣ ፓርቲንም ከሁለት ወንጀለኞች በህግበተሰጠው መብትና ኃላፊነት መሰረት በመዳኘት ሳይሆን በራሱ መንገድ የተሻለውን በመምረጥ የፈለገውን ማድረግ እንደሚችል አሳይቶናልና በአመክኒዮኣዊ ክርክር ከመድከም ወደ አቋሙ ቢገባ መልካም ይሆናል ፣ያሊያ ጽሁፉ ጠረን ‹‹ አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ›› የሚያስብል ነው፡፡
እንዲያው በማብቂያው ላይ ቢሆንም ለጽሁፌ ማዋዣ እንዲሆን ጠርጥረን ብናበቃስ–ይሄው ጽሁፍ በፋና ብሮድካስት ዌብሳይትም መለጠፉን፣እና ከዚህ በፊት በፋና ም/ሥራአስኪያጅና ኢ/ር ይልቃል ‹‹ሞጋች›› ፕሮግራም ላይ የነበረውንና ከፋና ‹፣ጠፍቶበት/በስህተት ሳይቀዳ ቀርቶ›› በኢሳት በሰማነው ክርክር ያስመዘገቡትን ‹‹ማርክ/ነጥብ›› ለመዘኑ ሰዎች ምርጫ ቦርድና ፋና ሬዲዮ እንደማይጠየቀው የኢህአዴግና አጋሮቹ ግንኙነት የ ‹‹አጋርነት›› ውል ተፈራረሙ ብሎ መጠርጠር በምርጫ ህጉም ሆነ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ያስጠይቅ ይሆን?
በመጨረሻም ማሳሰቢያ
የቦርዱ ሰብሳቢ እንዳሉት እንከን የለሽ ምርጫ ለማድረግ እንኳን እኛ እነርሱም አልደረሱምና በእኛ አገርም እየሆነ ያለውን ሁላችንም- እኛም፣ ቦርዱም፣ መንግስትም/ገዢው ፓርቲም፣ ህዝቡም ያውቀዋልና በመስተዋት ቤት ውስጥ ያለ ድንጋይ ለመወርወር ቀዳሚ መሆን ተገቢ አይደለም፤ ከነዚህ ሁሉ በላይ ህዝብ ያውቃል፣ይታዘባል፤ በጊዜውም ይፈርዳል፡፡ ማንም ምን ይበልም ለማድረግ ይፈልግም፣ያድርግም– የእኛ የማይናወጥ አቋም – ትግላችን ህገ መንግስታዊ መብታችን ላይ የተመሰረተ፣በሰላማዊና ህጋዊና ህጋዊ መንገድ ብቻ የሚጓዝ በመሆኑ ማንም ዜጋ ከህግ ባሻገር የኅሊና ፣ከሥልጣን በላይ የዜግነት ግዴታና የታሪክ ተጠያቂነት አለበት፤ ይህን የዘላቂ ሰላምና ልማት ወደ ዲሞክራሲ ሥርዓት የሚያደርስ የትብብሩን አካታችና ባለው ላይ መገንባት ምርጫው ያደረገ አካሄድ የመጥለፍ ሳይሆን የማበረታታት የሞራል ግዴታ እንዳለበት ማስተዋል ለሁላችንም- ለዜጎችም ለአገራችንም- ጠቃሚ መሆኑን በማሳሰብ አበቃለሁ፡፡
አንድ ሙስሊም ወዳጄ የነገረኝን ውስጤ የቀረ የታላቅ ኃይማኖት መሪ አስተምህሮ ለመዝጊያ ልጠቀመው ‹‹መልካምነት የተወደደ/በጣም ጥሩ/ ነው፤ መልካም ሆኖ መልካም ማድረግ ደግሞ የበለጠ የተወደደ/እጅግ በጣም ጥሩ/ ነው››፡፡ ለዚህ እንድበቃ ማስተዋሉን ተችረን በቸር አሰንብቶን በቸር ያገናኘን በሚል መልካም ምኞት መለያየት መልካም ነው፡፡ እስከዚያው መልካም ሆነን መልካም መልካሙን እያሰብንና እየሰራን እንድንቆይ ፈቃዱ ይሁን፡፡

Monday, March 2, 2015

አሁንም ደግመን እንነግራችኋለን

March2,2015
pg7-logoኢትዮጵያችን እግዚአብሔርንና ሰውን በማይፈሩ ጨካኞች እጅ ወድቃ የመከራ አገር ከሆነች ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ ተቆጥረዋል። በህዝባችን ላይ የተመዘዘው የመከራ ሰይፍም ወደ ሰገባው የሚመለስ አልሆነም። እንዲያውም በህዝባችን ላይ ሲዘንብ የቆየው የመከራ መንፈስ እንደገና ታድሶ ገና “ልክ እናስገባችኋለን” የሚል የጣዕረ ሞት ድምፅ ከህወሃት መንደር እየተሰማ ነው።
አባይ ፀሃይ የሚባለው ወላዋይና አደር ባይ ግለሰብ በህዝቡ ላይ ሲፈፅመው በኖረው ወንጀል ገና የረካ አይመስልም። ሌላ ግዲያ፤ ሌላ ስደት፤ ሌላ የላቀ መከራ ለኢትዮጵያዊያን ደግሶላቸዋል። አባይ ፀሃይ ለአዲስ አበባ ከተማ ልቀት እርሱ ብቻ አሳቢ፤ እርሱ ብቻ ተቆርቋሪ ሁኖ ራሱን ሹሟል።የአዲስ አበባም ሆነ በአካባቢው የሚኖረው ኗሪ ህዝብ ግን አባይ ፀሃይን የሚያውቁት በእኩይ ተግባሩ እንጂ በደግ ተግባሩ እንዳለሆነ እኛ ልናስታውሰው እንወዳለን። በዚህ ግለሰብ አማካሪነት የተጀመረው ኗሪውን ህዝብ የማፈናቀል፤ ቤተሰብን የመበተን፤ የህዝቡን አብሮነት የማፍረስ ተግባር ገና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል “ገና ልክ እናስገባችኋለን” በሚል መፈክር ሥር እንደሚቀጥል ታቅዷል። አዲስ አበባን በማስፋፋት ሰበብ ብዙ ገበሬዎች ከኖሩበት መንደር ያለምንም ካሳ ተፈናቅለው የሌላ ሎሌ እንዲሆኑ መደረጉ የሚረሳ አይደለም። ይሄን የአንድን ህዝብ ማንነት የማጥፋት ድርጊትን የተቃወሙ ብዙ ወጣቶች በሞት እና በእሥራት እንደተቀጡም አረሳነውም። ትላንት የፈሰሰው ደም ሳይደርቅ፤ የፈሰሰው እንባ ሳይታበስ፤የተበተነው ሳይሰበሰብ፤ የተሰበረው ሳይጠገን እንደገና ለሌላ ዙር ጥፋት እየተዘጋጁ እንደሆነ ነግረውናል።
አባይ ፀሃይ “ልክ እናስገባችኋለን” ሲል የተማመነው ጠመንጃ ያነገተውን ኢትዮጵያዊ ወታደር እንጂ ህዝብን እንዳልሆነ እናውቃለን። ወታደር አገሩን መጠበቅ፤ ህዝቡንም ከጥፋት መታደግ፤ አጠቃላይ የአገሪቷን ህግም ማስከበር ዋናው ተልዕኮው ነበር። የአገራችን ወታደሮች ግን ዋናውን ተልእኳቸውን ትተው ኢትዮጵያን እንደ አገር እንዳትቀጥል የሚያደርጉ ቡድኖችን እድሜያቸውን ለማራዘም እየሰሩ እንደሆነ እያየን ነው።በአገራችን ጠመንጃ የታጠቁ ኃይሎች መከላከያ ኃይል አባላት፤ የፖሊስ አባላት፤ የፌዴራል ፖሊስ አባላት እና በአገራችን ታሪክ በነፍሰ ገዳይነቱ የሚታወቀው አግዓዚ የተባለው ክፍለ ጦር አባላት እና የአገር ውስጥ ደህንነት አባላት የህወሃትን ዕድሜ ለማራዘም ከልብ የመነጨ ፍላጎት አላቸው ብለን አናምንም። እነዚህ ኃይሎች የወጡበትን ጎጆ፤ ነገ ዞሮ መግቢያ የሚሆናቸውን ማህበረሰብ ወደውና ፈቅደው ያፈርሳሉ ብለን ለማሰብ ይቸግረናል።በሌላ በኩል ደግሞ ድርጊታቸው ብዙዎችን እያስከፋ እንደሆነም እናውቃለን።
አሁንም ደግመን ደጋግመን በኢትዮጵያችን ጠመንጃ ላነገቱ ኃይሎች መልዕክት መላካችንን አናቋርጥም። ጠመንጃውን ያነገቱ ኃይሎች ካነገቱት ጠመንጃ የተለዩ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ስሜት አሏቸው፤ ፍላጎት አሏቸው፤ ማሰብ የሚችል አዕምሮም እንዳሏቸውም የሚካድ አይደለም።የሚያዝንና የሚደሰት ስሜት፤ ለመኖር ፍላጎት፤ በጎውን ከክፉ ለመለየት የሚያስችል አዕምሮ ያሏቸው ስለሆነ ፈፅሞ እስከ ሚመሽ ድረስ መልዕክታችንን ከመስደድ አናቆምም። መልዕክታችንም አጭርና ግልፅ ነው። በዚያች አገር ውስጥ ጠመንጃ የታጠቀው ኃይል ጋር ጠላትነት የለንም።በእኛ እምነት መከላከያ ኃይል፤ ፖሊስ እና የደህንነት ሠራተኞች ጠላቶቻችን አይደሉም። እኛ ጠላት የምንለው ጠመንጃ የታጠቀውን ድሃ እና ከርታታ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ይህን ኃይል በገዛ ወገኑ ላይ ሰይፉን እንዲመዝ እና የንፁሃንን ደም እንዲያፈስ የሚያደርገውን ኃይል ነው።የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አሁን ባለበት ሁኔታ ለተሻለ ውጤት የሚያበቃው አማራጭ ስለሌለው ሂሊናው እየወቀሰውም ቢሆን የገዛ ወገኑን ደም እያፈሰሰ ለመቆየት የተገደደ ይመስላል። ይህን ማለታችን የድርጊቱን መፈፀም ትክክል ነው እያልን አይደለም። በማንኛውም መለኪያ የንፁህ ሰውን ደም ማፍሰስ ትክክል አይደለም። በሰማይ በእግዚአብሄር ፊት የሚያስጠይቅ፤ በምድር በሰው ዘንድም የሚያስወቅስ ክፉ ተግባር መሆኑን ሳንናገር አናልፍም።
እስከ ዛሬ የተሻለ መረጃ ስለሌለኝ፤ የተሻለ አማራጭ ስላጣሁ፤ የተሻለን መንገድ ለመፈለግ ሁኔታው ስላልፈቀደልኝ ከሂሊናየ ውጪ ሁኜ ለመኖር ተገድጄአለሁ የሚለው ምክንያት አሁን አብቅቷል። አሁን መረጃ አለ፤ ኢትዮጵያን እንደ አገር እንድትቀጥል ለማስቻል የተሻለ አማራጭም አሁን ተዘጋጅቷል። መረጃና አማራጭ መንገድ ካለ ደግሞ ከሂሊና ጋር ታርቆ እንደ ሰው ለመኖር ሁኔታው የተመቸ ሁኗል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል፤ የፖሊስ ሠራዊት አባላት፤የአገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎች ሆይ ስሙን !
ህወሃቶች እናንተን ተገን አድርገው የገዛ ወገኖቻችሁን “ልክ እናስገባለን” ማለታቸውን ሰምታችኋል የሚል ግምት አለን። ልክ ማስገባት ማለት-ከሥራ ማባረር፤ከትውልድ ሥፍራ ማፈናቀል፤ እስር ቤት መጨመር፤ ለስደት መዳረግ እና መግደል ማለት ነው። የአባይ ፀሃይ ልክ ማስገባት ይሄን ይመስላል።ይሄን የምትፈፅሙት ደግሞ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች ትሆናላችሁ። ወገኖቻችሁ በህወሃቶች እጅ እንባቸውን በመዳፋቸው ሲያፍሱ ኑረዋል።በህወሃት አገዛዝ ሥር ያለች አገራችሁ ከውዳቂ አገራት ተርታ ገብታለች፤ ከዓለም አስር ፍፁም ድሃ አገሮች መካከል አንዷ ሁናለች።የአገራችሁ ወጣቶች ሞትን ፊት ለፊታቸው እያዩ ተሰደው የዓዞና የበርሃ ዕራት ሁነው ቀርተዋል። ከዚህ የተረፉትም የዓረብ መጫወቻ ሁነዋል። ይህ ሁሉ መከራ ህወሃት በተባለው ክፉ ዘረኛና ቂመኛ ቡድን ይፈፀማል። አሁን ይሄን በቃ ለማለት ግዜው ነው። ከእንግዲህ ወዲያ ታዝዤ ነው፤ ለእንጀራ ብየ ነው፤ ልጆቼን ላሳድግ ብየ ነው፤ አማራጭ አጥቼ ነው፤ የሚሉ ምክንያቶች ሚዛን የሚያነሱ ባለመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም።
አሁን አስተማማኝ አማራጭ አለ። የኢትዮጵያ ውረደት ያንገበገበን፤ የህዝባችን ጉስቁልና ያስቆጨን ወገኖች የአያቶቻችንን ጋሻና ጦር አንስተን ለግዳጅ ተዘጋጅተናል። ከመቸውም ግዜ በተሻለ ህዝባዊ መሠረት ላይ የቆመ ድርጅት መሥርተን ንቅናቄ ጀምረናል። ትግላችን ኢትዮጵያዊያን ከተዘፈቁበት ጭለማ ወደ ብርሃን የሚያሻግር ነው። ትግላችን ህወሃት የጫነውን የዘረኝነት ቀንበር የሚሰብር ነው። ትግላችን ህወሃት የዘረጋውን የዝርፊያ መረብ የሚበጣጥስ ነው። ትግላችን ህዝቡን በሙሉ የተጫኑ ጥቂት መንደርተኞች ሥፍራቸውን እንዲይዙ ማድረግ ነው።ትግላችን ጎጠኛ አስተሳሰብን አምክኖ ብሄራዊ ስሜትንና ውህደትን የሚፈጥር ነው። ትግላችን ዜጎች በዜግነታቸው ብቻ በኢትዮጵያ ውስጥ በማንኛውም ሥፍራ ያለ ፍርሃት የሚኖሩበትን ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን አብዛኛው ህዝብ በመረጠው መንግስት የሚተዳደርበት፤ ይህም መንግስት ህዝቡን ፈርቶና አክብሮ የሚሠራበት ሁኔታ የሚፈጥር ነው። ትግላችን የአገሪቷ መከላከያ ኃይል አገሩንና ህዝቡን የሚጠብቅ እንጂ የገዛ ወገኑን ደም በከንቱ የሚያፈስበት ሁኔታ እንዲያበቃ የሚያደርግ ነው።ጠመንጃውን ያንገትከው ኃይል የቀረበልህ አማራጭ መሥመር ይሄ ነው።
ደግመን እንነግርሃለን አሁን አማራጭ መንገድ አለህ። በገዛ ወገኖችህ ላይ ስይፍህን ለመምዘዝ እምቢ የማትል ከሆነና አሁንም በዚያው በጭለማ መንገድ መሄድን ከመርጥክ መጨረሻህ መልካም አይሆንም። እኛ እንድሆንን ተነስተናል። ከመንገዳችን የሚያቆመን ምዳራዊ ኃይል አይኖርም።የቃየል ልጆች ሲያጠፉን እንዲያው ዝም ብለን የምንጠፋ አይደለንም።ከእኛ ዘንድ እውነት አለ፤ ከእኛ ዘንድ የነፃነት ብርሃን አለ፤ ከእኛ ዘንድ የፍትህ ዘንግ አለ፤ከእኛ ዘንድ የእኩልነት ሚዛን አለ፤ ከእኛ ዘንድ እግዚአብሄር አለ።ይሄን ሁሉ ይዘን እናሸንፋለን እንጂ አንሸነፍም።የምናሸንፈው ለበቀል እንዳይደለ አሁንም እንነግራችኋለን። የምናሸንፈው በክፉው ላይ መልካሙን ዘር በመዝራት ነው።በጭቆና ላይ ነፃነትን፤ በአድልዎ ላይ ፍትህን፤ በህግ አልባነት ላይ የህግ የበላይነትን፤ በጎጠኛ አስተሳሰብ ላይ ብሄራዊ አስተሳሰብን ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። የጎሰኛነትን አጥር አፍርሰን የኢትዮጵያዊነት ስሜት ማስረፅ ስንችል ነው አሸንፈናል የምንለው። እኛ ስናሸነፍ የሚሆነው ይሄው ነው። ከእኛ ዘንድ የበቀል ስሜት የለም። ከእኛ ዘንድ ያለው ሁሉም ከህግ በታች ሁኖ ህግና ፍትህ እንዲነግሱ የሚያስችል ብርቱ ፍላጎት ነው።
ስለዚህ ጠመንጃ ያነገታችሁ ኃይሎች እኛ ከቆምንለት ቅዱስ ዓላማ ጋር እንድትተባበሩ እንጠራችኋለን።ኑና የጭለማ ኃይሎችን ምሽግ አፍርሰን የብርሃን ልጆችን አምባ አብረን እንሥራ። ኑና አብረን የወገኖቻችንን እምባ እናብስ። ኑና በግፍ ያለፍርድ የታሠሩትን እናስፈታ ።ኑና የጭቆናን ቀንበር አብረን እንስበር። ኑና አብረን አገራችንን ከፍ ከፍ እናድርጋት።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Saturday, February 28, 2015

ሰበር ዜና: የወያኔ ሰላይ ከሆላንድ ተባረረ!

February 28,2015

ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ'ኢንቨስትመንት" አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ
ከመሃል ያለው ኢዛና (እስራኤል ገደቡ) ለ’ኢንቨስትመንት” አዲስ አበበ ያለፈው ወር በሄደ ጊዜ
ሂሩት መለሰ – ከሮተርዳም
ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማየሁ ስንታየው በመባል የሚታወቀው የህወሃት ሰላይ ከኔዘርላንድስ ተባረረ። አለማየሁ ስንታየሁ ቋሚ ነዋሪ ከነበረበት ከኔዘርላንድስ እንዲባረር የተደረገው በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በከፈቱበት የስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።


የሮተርዳም ከተማ ፍርድ ቤት በአለማየሁ ላይ የተመሰረተውን የስለላ ክስና ማስራጃ ለረጅም ጊዜ ሲመረምር ከቆየ በኋላ የግለሰቡ የመኖርያ ፈቃድ እና ቤት እንዲነጠቅ፣ የሆላንድን ምድርም በአስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ከሆላንድ የምመራ ቡድን እንደተረዳነው ከሆነ – የግለሰቡ ቤት ሲፈተሽ ወያኔ የሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ የስለላ ሰነዶች ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም የተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሾ ማስረጃዎች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።
alemayehu-sentayehu
ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለረጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጦር ቅጥር ግቢ ተላከ። በተሃድሶ በነበረበት ጊዜ ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ የሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር የዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። የበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማየሁ ከተሃድሶው ከወጣ በኋላ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ከተባለ ወታደር ጋር በመሆን የሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማየሁ እና ኢዛና በየሃገሩ እየዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ከረሙ። ከዚያም አስመራ ድረስ ተልከው የሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።

አለማየሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደረገ። ይህም የተደረገበት ምክንያት በአውሮፓ የሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በረቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው። በሆላንድ ሃገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን የስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማየሁ የሆላንድ ዜግነት ቢኖረው ኖሮ ቅጣቱ የከፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እየተከታተሉ ያሉ የህግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።

የአለማየሁ መባረር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ የህወሃት ደጋፊዎች የአቤቱታ ደብዳቤ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላቸው አልቻለም። የአቤቱታ ደብዳቤው ግለሰቡ እዚህ የተወለዱ ሁለት ለጆቹን እየመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት የሚል ነበር።
አለማየሁ ስንታየሁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሆላንድ ተባረረ። ኢዛና ግን አሁን የተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጽ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል። ኢዛና የሆላንድ ዜግነት ቢኖረውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። የቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ የተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮችን እየመራ በቴሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት የወያኔ ኢንቨስተሮች በጨበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳየናል።

British support for Ethiopia scheme withdrawn amid abuse allegations

February 27, 2015

Department for International Development will no longer back $4.9bn project that critics claim has funded a brutal resettlement programme

(The Guardian) The UK has ended its financial support for a controversial development project alleged to have helped the Ethiopian government fund a brutal resettlement programme. Hundreds of people have been forced from their land as a result of the scheme, while there have also been reports of torture, rape and beatings.
An Anuak woman at work in Abobo, a village in Ethiopia’s Gambella region.
An Anuak woman at work in Abobo, a village in Ethiopia’s Gambella region. It has been claimed that UK money has funded abuses against Anuak people in the area. Photograph: Alamy
Until last month, Britain’s Department for International Development (DfID) was the primary funder of the promotion of basic services (PBS) programme, a $4.9bn (£3.2bn) project run by the World Bank and designed to boost education, health and water services in Ethiopia.
On Thursday, DfID said it had ended its PBS contributions because of Ethiopia’s “growing success”, adding that financial decisions of this nature were routinely made after considering a recipient country’s “commitment to partnership principles”.
It has been alleged that programme funds have been used to bankroll the Ethiopian government’s push to move 1.5 million rural families from their land to new “model” villages across the country.
Opponents of the commune development programme (CDP) say it has been characterised by violence. One Ethiopian farmer is taking legal action against the British government, claiming UK money has funded abuses against Anuak peoplein the Gambella region. The man, an Anuak known as Mr O, says he was beaten and witnessed rapes and assaults as government soldiers cleared people off their land. DfID has always insisted it does not fund Ethiopia’s commune development programme.
scathing draft report from the World Bank’s internal watchdog recently concluded that inadequate oversight, bad audit practices, and a failure to follow the bank’s own rules had allowed operational links to form between the PBS programme and the Ethiopian government’s resettlement scheme.
Although the bank’s inspection panel found that funds could have been diverted to implement villagisation, it did not look into whether the resettlement programme had involved human rights abuses, claiming such questions were outside its remit.
DfID, which has contributed nearly £745m of UK taxpayer money to the PBS programme, said the decision to withdraw financial support was prompted in part by Ethiopia’s “impressive progress” towards the millennium development goals.
“The UK will now evolve its approach by transitioning support towards economic development to help generate jobs, income and growth that will enable self-sufficiency and ultimately end poverty,” it said.
“This will go alongside additional funding for specific health, education and water programmes – where impressive results are already being delivered – resourced by ending support for the promotion of basic Services programme.”
A DfID spokesman said the move had nothing to do with Mr O’s ongoing legal action or the World Bank’s internal report, but added: “Changes to programmes are based on a number of factors including, but not limited to, country context, progress to date and commitment to partnership principles.”
The department said its overall financial commitment to Ethiopia, one of the largest recipients of UK aid, would remain unchanged, with almost £256m due to be spent between 2015 and 2016.
The Ethiopian government said DfID’s decision was not a matter of concern.
“They have been discussing it with pertinent government bodies,” said the communications minister, Redwan Hussien.
“What they said is that the aid that they’re giving will not be refused or stopped, it will be reorganised.”
The World Bank’s executive board met on Thursday to discuss the internal report on the PBS programme and the management response.
In a statement released on Friday, the bank said that although its inspection panel had concluded that the seizing of land and use of violence and intimidation were not consequences of PBS, it had determined that the programme “did not fully assess and mitigate the risks arising from the government’s implementation of CDP, particularly in the delivery of agricultural services to the Anuaks”.
The World Bank Group president, Jim Yong Kim, said that one of the institution’s core principles was to do no harm to the poor, adding: “In this case, while the inspection panel found no violations, it did point out areas where we could have done more to help the Anuak people. We draw important lessons from this case to better anticipate ways to protect the poor and be more effective in fighting poverty.”
Opponents of the villagisation process have been vocal in their criticisms of the bank’s role.Jessica Evans, senior international financial institutions researcher at Human Rights Watch, said the inspection panel’s report showed the bank had “largely ignored human rights risks evident in its projects in Ethiopia” and highlighted “the perils of unaccountable budget support” in the country.

በአዋሳ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ ነው ሲሉ የቃጠለው ሰለባ የሆኑ ሰዎች ገለጹ

February 27,2015
Awasaየካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል ዋና ከተማ በአዋሳ የካቲት 14 ቀን 2007 ዓም በደረሰው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር በመንግስት እንደተገለጸው አንድ ሳይሆን ከ20 በላይ መሆኑን ተገጂዎች ለኢሳት ገልጸዋል።
ከፍተኛ ንብረት ከወደመባቸውና እሳቱ ሲነሳ በስፍራው ከነበሩት መካከል አንዱ ለኢሳት ሲናገር፣ እርሱ የ6 ሰዎችን የተቃጠለ አስከሬን ማየቱን፣ በስፍራው የሚገኙ ጓደኞቹ ደግሞ በአጠቃላይ እስካሁን 27 አስከሬን ተፈልጎ መቀበሩን ተናገሩዋል።
አንድ ህጻነት እና አንዲት እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሞታ መመልከቱን፣ በማግስቱ ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ሞተው ማየቱን የሚናገረው ግለሰቡ፣ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች አካባቢውን ከነዋሪው በመከለል ማታ ማታ የተቃጠለ አስከሬን እየፈለጉ በመቅበር ላይ ናቸው ብሎአል። እናቶች አሁንም ድረስ ልጆቻቸውን እየጠየቁ ቢሆንም፣ በከንቲባው በኩል የሚሰጠው ምላሽ አሳዛኝ መሆኑን ግለሰቡ ገልጿል። ነዋሪዎቹ በመንግስት በኩል በቂ እርዳታ እንዳልተደረገላቸው በምሬት ተናግረዋል።
መንግስት የእሳቱን መነሻ እስካሁን ይፋ አላደረገም። ነዋሪዎች እንደሚሉት ግን መስተዳድሩ ቦታውን ለመሸጥ እሳቱን ሆን ብሎ አስነስቶታል። በጉዳዩ ዙሪያ የአዋሳን ከንቲባ ለማግኘት ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

Thursday, February 26, 2015

ምርጫ ለኢትዮጵያ ወታደርና ፓሊስ: – ለህወሓት ባርነት ወይስ ለኢትዮጵያ ነፃነት

February 26,2015
pg7-logoየኢትዮጵያ ሕዝብ ለውትድርና ከፍተኛ ክብር አለው። ውትድርና ከሙያና ሥራ በላይ የነፃነትና የክብር መገለጫ፤ ሀገርን ከባዕድ ወረራ መከላከያ ጋሻ ነው ብሎ ያምናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ህግና ሥርዓት አክባሪ በመሆኑ ለፓሊስም ከፍተኛ አክብሮት አለው። የፓሊስ ሥራ ወንጀልን መከላከልና ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ ማቅረብ መሆኑ በኢትዮጵያ ባህል የተከበረ ቦታና እውቅና አለው።
በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ግን ይህ እየተቀየረ ነው። የህወሓት አዛዦች እየመሩት ያለው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ሀገርን ከባዕድ ጠላት ከመከላከል ጋር ምንም ዝምድና በሌላቸው ሁለት አበይት ተግባራት ላይ ተጠምዷል። በህወሓት አዛዦች የሚመራው ሠራዊት ዋነኛ ተግባር ለሰብዓዊ መብቶቻቸው መከበር እና ለፍትህ መስፈን የሚታገሉ ዜጎችን ማጥቃት ሆኗል። የጦሩ ሁለተኛው አቢይ ተግባር ደግሞ ለአዛዦች የግል ጥቅም ማካበቻ ገቢዎችን በሚያስገኙ ሥራ ላይ መሠማራት ነው።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያዊያንን ማጥቂያ ሠራዊት መሆኑ ሲቪሉን ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የሠራዊቱንም አባላትን ጭምር ለህሊና ወቀሳ የዳረገ ጉዳይ ነው። ሆኖም ግን ይህ በህሊና ወቀሳ ብቻ ሊታለፍ የማይችል ወንጀል ነው። ሠራዊቱ በህወሓት እየታዘዘ የሚዘምተው በገዛ ራሱ ልጆች፣ እህቶች፣ ወንድሞችና ወላጆች፤ በገዛ ራሱ ጥቅሞች እና በገዛ ራሱ ላይ መሆኑ መገንዘብ ይኖርበታል። በገዛ ራሱ ጥቅሞች ላይ የሚዘምት አንድም ህሊና የሌለው አሊያም ነፃነት የተነፈገው ሰው ብቻ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ሠራዊቱ እየተራበና እየታረዘ አለቆቹ የታላላቅ ህንፃዎች ባለቤቶች፣ ባለፋብሪካዎች፣ የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባለአክሲኖች የሚሆኑበት ሥርዓት ከዳር ሆኖ የሚመለከት መሆኑ የሚገርም ነው። ሠራዊቱ ቤተሰቦቹን መመገብ አቅቶት እያለ የአዛዦቹ ልጆች ለሽርሽር ዓለምን ይዞራሉ። እንዴት ነው ሠራዊቱ እየደኸየና እየሞተ አዛዦቹ እየከበሩ የሚሄዱት? ይህ አዋራጅ ሁኔታ እንዲያበቃ መታገል የሠራዊቱ ግንባር ቀደም ኃላፊነት ነው። ሠራዊቱ ወይ ባርነትን አሜን ብሎ መቀበል አለበት አለበዚያም እሱም እንደነሱ ሰው መሆኑን ማሳየት መቻል አለበት። በኢትዮጵያ ውስጥ የህወሓት አገዛዝ ወድቆ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረቱ በከፍተኛ ሁኔታ ከሚጠቅማቸው የኅብረተብ ክፍሎች ግንባር ቀደሙ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ናቸው። በዚህም ምክንያት የሠራዊቱ አባላት ለሥርዓቱ መውደቅ በግልጽም በስውርም መታገል የዜግነት ብቻ ሳይሆን አዕምሮ ያለው ሰው ሆነው በመፈጠራቸው የተቀበሉት ግዴታ ነው።
ፓሊስን በተመለከተም ሁኔታው ተመሳሳይ ነው። ህወሓት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ ለመግዛት የቻለው በዋኛነት የፓሊስን ኃይል ለአፈናው ተግባር የሚጠቀም በመሆኑ ነው። የተቃውሞ ድምጾች በተሰሙ ቁጥር የኢትዮጵያ ፓሊስ በወገኖቹ ላይ የሚያወርደው ዱላ የሚዘገንን ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት መግደልና ማቁሰል፤ አረጋዊያንን፣ ሴቶችንና ሕፃናትን መግደል፣ ማቁሰል፣ መደብደብ በዚህ ተግባር የተሠማሩ ፓሊሶችን በቡድንም በግልም በህግ የሚያስጠይቅ ከባድ ወንጀል ነው። በህወሃት እየተመራ ያለው የኢትዮጵያ ፓሊስ ተግባራት ተበዳዮችን ብቻ ሳይሆን ራሱ ፓሊስንም ጭምር አንገት የሚያስደፋ ተግባር ነው። ለመሆኑ አንድ ተራ የኢትዮጵያ ፓሊስ ባልደረባ ከህወሓት አገዛዝ ምን ተጠቀመ? መልሱ “ምንም” የሚል ነው። ይልቁንስ በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ፓሊስ የተናቀና የተዋረደ ሥራ ሆነ። በህወሓት አገዛዝ ፓሊስ እንደሰለጠነ አዳኝ ውሻ “ያዝ” ሲሉት የሚነክስ፣ የሚያደማ፣ የሚቦጭቅ ሆኗል። ይህ ለፓሊስ፣ ወንጀልም ውርደትም ነው። በህወሓት አገዛዝ መገርሰስ እና በምትኩ የህግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት መስፈን ፓሊስ ከሁሉ በላይ ተጠቃሚ ነው፤ ሰብዓዊ ክብሩን ያረጋግጥለታልና።
ዛሬ በኢትዮጵያችን ውስጥ የታዘዙትን የሚፈጽሙ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ስላሉ ነው የህወሓት ሹማምንት ልባቸው ያበጠው። ለማስረጃ ያህል ሰሞኑን የህወሓቱ ሹም አባይ ፀሐዬ የአዲስ አበባ ዙሪያ ገበሬዎች በግዴታ መነሳታቸው የሚቃወሙትን ዜጎችን ሁሉ ”ልክ እናስገባቸዋለን” ብሎ በሸንጎ የዛተው የታዘዘውን የሚፈጽም የጦርና የፓሊስ ሠራዊት መኖሩን ተማምኖ ነው። እስከ መቼ የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊትና ፓሊስ ሕዝብን ማስፈራሪያ መሣሪያ ይሆናል?
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የኢትዮጵያ የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ለራሳቸው እና ለወገናቸው የሚበጀው ሥርዓት የቱ እንደሆነ ያውቃሉ ብሎ ያምናል። በዚህም ምክንያት ስብዕናቸውን እያዋረደ እና እያደኸያቸው ያለውን የህወሓት አገዛዝን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመሆን ይፋለሙታል ብሎ ያምናል። ይህ ውሳኔ ግን ሠራዊቱ በጅምላ ሳይሆን እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግሉ የሚወስደው ውሳኔ እንደሆነ አርበኞች ግንቦት 7 ይገነዘባል።
በዚህም መሠረት ተደጋጋሚ ጥሪ እየተደረገለት፤ ጥሪውንም እየሰማ ከህወሓት ጋር ወግኖ ሕዝብን መውጋት የቀጠለ የሠራዊቱ አባል ላደረሰው ጥፋት በግል መጠየቁ የማይቀር መሆኑ ሊገነዘብ ይገባል። በእያንዳንዳንዱ የጦርና ፓሊስ ሠራዊት ባልደረባ ፊት የቀረበው ምርጫ “ለህወሓት ባርነት ታድራለህ ወይስ ራስህንና ሀገርን ነፃ ታወጣለህ” የሚል ነው።
ራስህንና ሀገርህን ነፃ ለማውጣት የመረጥክ የሠራዊቱና የፓሊስ ባልደረባ አሁኑኑ ሕዝባዊ ትግሉን ተቀላቀል። እስከዛሬ የበደልከውን ሕዝብ ለመካስ ምቹ ሁኔታ አለህ። በግልጽ የነፃነት ኃይሎችን እንድትቀላቀል፤ አሊያም አለህበት ሆነህ በውስጥ አርበኝነት እንድትደራጅና ተግባራዊ ሥራ እንድትጀምር መንገዱ ተመቻችቶልሃል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Wednesday, February 25, 2015

አዋራጅ ሰልፎችና ድግሶች እንዲያበቁ ህወሓት ይወገድ!

February 25,2015
pg7-logoድግሶችን፣ ወታደራዊ ሰልፎችንና ሀውልቶችን ማብዛት የአባገነኖች ሁሉ የጋራ ባህርይ ነው። ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝም በሕዝብ እየተጠላ፣ እያረጀና እየወላለቀ በሄደ መጠን በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግሶ መብላት፤ ወታደራዊ ሰልፍና የመሣሪያ ጋጋታ ማሳየት እና በየመንደሩ ሀውልት መመረቅ ሙያው አድርጎት ቆይቷል።
የህወሓት ድግሶችና ፌሽታዎች የአገራችን ሀብት ከማሟጠጣቸውም በላይ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ የአርሶ አደሮችንና የአነስተኛ ነጋዴዎችን ኪስ እያራቆቱ ናቸው። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች በእስር ቤቶች እየማቀቁ በሚገኙበት ሁኔታ፤ በመቶ ሺዎች የሚገመቱ የአማራ አርሶአደሮች ተፈናቅለው እያለ፤ በጋምቤላና በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እየተደረጉ፤ በአፋር፣ በሲዳማ፣ በቦረና፣ በወልቃይት እና በመላው ኢትዮጵያ ግጭቶች በበዙበት፤ ሕዝብ እያለቀሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት “የብሔር፣ ብሔረሰቦች መብት ተከበረ” እያሉ እነዚህኑ በደል እየደረሰባቸው ያሉ ዜጎችን ማስጨፈር እና ለእነዚህ ጭፈራዎች በርካታ ሚሊዮኖች ብር ማውጣት በእጅጉ ያስቆጫል። እነዚህ ጭፈራዎች ለህወሓት ሰዎች የገቢ ምንጮች መሆናቸው ጥርጥር የለውም፤ ለድሀው ኢትዮጵያዊ ግን መራቆቻዎች ናቸው። ከዚህም አልፎ በዘረኝነት እየተበደለ ያለ ሕዝብ ስለእኩልነት ዝፈን ማለት ክብረ ነክ ተግባር ነው። ዘንድሮ በአሶሳ የተደረገው አገር አቀፍ ድግስ ካለቀ ጥቂት ወራት በኋላ አገራችን በሌላ ዙር የህወሓቶች ድግስ ተወጥራለች።
ሰሞኑን በባህር ዳር በተደረገው የጦር ሠራዊት ሰልፍ እና ሰልፉን ተከትሎ በነበረው የድግሶች ግርግር ከሁሉም በላይ የተሰደበውና የተዋረደው የሠራዊቱ አባል ነው። አዛዦቹ መቶ በመቶ የህወሓት አባላት የሆኑበትን ሠራዊት “የኢትዮጵያ መከላከያ” ተብሎ መጠራቱ ራሱ የሚያሳፍረው ኢትዮጵያዊ ወኔ በልባቸው ውስጥ እየተንቀለቀለና እልህ እየተናነቃቸው ያሉ የሠራዊቱን አባላት ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንዴት የኢትዮጵያ ጠላቶች በሆኑ የህወሓት ካድሬዎች ይመራል? እንዴት የአስር አለቃ እንኳን ሊሆን የማይገባው የህወሓት ካድሬ “ጄኔራል” ተብሎ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮችን እንደ ሎሌው ያዛል? እንዴት አንድ የህወሓት ሎሌ ሹመት ተሰጥቶት እየፏለለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት የሚበልጠውን ኢትዮጵያዊ ተንቆ ይዋረዳል? ይህ ቁጭትና እልህ ሠራዊቱ የዘረኛውን ህወሓት ሰልፍ አድማቂ መሆኑ የሚያከትምበት ጊዜ ይበልጥ እንዲናፍቅ የሚደረገው ነው። አልያማ ሰልፍ ያሳመረ ሠራዊት ሁሉ አሸናፊ እንዳልሆነ የታወቀ ነው። በሰልፍ ብዛትና በመሣሪያ ትዕይንት ማሸነፍ ቢቻል ኖሮ የትም አገር አምባገነኖች ባልወደቁም፤ ህወሓት ራሱን ስልጣን ላይ ባልወጣም ነበር።
የህወሓት ምሥረታ 40ኛ ዓመት ድግስም ሌላው የታሪክና የሀብት ውድመት የሚያስከትል ክስተት ነው። የካቲት 11 ቀን 1967፣ ጥቂት ኢትዮጵያዊያን እናታቸውን ኢትዮጵያን ለመግደል ያሴሩበት እና ልጆች በእናታቸው ላይ ቢላዋ የሳሉበት ዕለት በመሆኑ በሀዘንና በሱባኤ እንጂ በድግስና በጭፈራ የሚታሰብ ዕለት አይደለም። ሲነሳ ምንም ይሁን ምን ዛሬ በደረስንበት ሁኔታ ሲገመገም፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ ህወሓትን የመሰለ መሠሪና አድርባይ ድርጅት ገጥሟት አያውቅም። እነሆ ዘንድሮም ይኸው አድርባይ ድርጅት የመሪዎቹን የሀብትና ዝና ረሀብ ለማስታገስ ሲል ያልነበረ ታሪክ እየፈጠረ በድግስ ስም ከድሀው ገንዘብ እየሰበሰበ ለሀብታም የህወሓት አባላትና ደጋፊዎች ያሸጋግራል። የድግሶቹ ሁሉ አዘጋጆች፣ እቃ አቅራቢዎችና ተጠቃሚዎች ራሳቸው የህወሓት መሪዎችና አሽቃባጮቻቸው ሲሆኑ ከፋዩ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። በህወሓት ድግስ የሚባክነው የሕዝብ ሀብት ስንት ሆስፒታል ይገነባ እንደነበር ስናስብ እና ይህ ሀብት በተገቢው ቦታ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ስም ብቻ የያዙ ዩንቨርስቲዎቻችንን ትምህርት መቅሰሚያ ማድረግ እንችል እንደነበር ስናሰላ ሀዘናችን ጥልቅ ነው። ህወሓት ለልጅ ልጆቻችን የሚተርፍ ዕዳ እየቆለለ ዳንኪራ ሲረግጥና ሲያስረግጥ ማየትና መስማት ህሊና ሊሸከመው ከሚችል በላይ ነው።
አርበኞች ግንቦት 7፡ የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት ወታደራዊ ሰልፍ እና የመሣሪያዎች ትዕይንት የሚረበሽ ድርጅት አይደለም። ይልቁንም በሰልፉ ጨኸት የታፈነው የኢትዮጵያዊ ወታደር ጩኸት ይሰማዋል። ኢትዮጵያዊ ወታደር በአዛዦቹ ላይ ጥርሱን ነክሶ፣ ቂም አርግዞ ሰልፋቸውን እንደሚሰለፍ አርበኞች ግንቦት 7 ያውቃል። አርበኞች ግንቦት 7፣ የሠራዊቱ አባላት ውስጥ ውስጡን እየተሰቃዩ የታዘዙትን መፈፀማቸው መብቃት አለበት ይላል፤ ወይ ተቀላቀሉን፣ አሊያም እውስጡ ሆናችሁ ሥርዓቱን የማዳከም ሥራዎችን ሥሩ። በእናንተ ውርደት የዘራፊዎች፣ ሙሰኖች፣ ጎጠኞችና ዘረኞች ደረት አብጦ መታየት የለበትም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ የዘንድሮው የህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል የጨረሻው በዓል እንዲሆን፤ ከርሞም ተመሳሳይ አዋራጅ በዓል እንዳናከብር፤ ሠራዊቱ በዘራፊዎች ታዞ የሚሰለፍበት ውርደት እንዲያበቃ ተባብረን ህወሓትን እንቅበር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ድል የአላማ ጽናት እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት አይደለም

February 25,2015

pg7-logoጣሊያን ዋና ከተማ ሮም ዉስጥ ዋና ከተማዋን ከተለያዩ የጣሊያን ከተሞችና ጣሊያንን ከፓሪስ፤ከሙኒክ፤ከጄኔቫና ከቪዬና ጋር የሚያገናዉና በአመት ከ 150 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን የሚያስተናግድ አንድ ትልቅ የባቡር መስመር አለ። ይህ የባቡር መስመር የሚጠራዉ ሮማ ተርሚኒ እየተባለ ሲሆን የባቡር መስመሩ አድራሻ ደግሞ የአምስት መቶዎቹ አደባባይ በመባል ይታወቃል። ወደዘህ ትልቅ ባቡር መስመር ሲገባ አንድ እጅግ በጣም ትልቅ ሀዉልት ወለል ብሎ ይታያል፤ ይህም ሀዉልት የአምስት መቶዎቹ አደባባይ ወይም ፒያዛ ዴ ቺንኮቼንቶ በመባል የታወቃል። የፒያሳ ዴ ቺንኮቼንቶ መታሰቢያ ሀዉልት የተሰራዉ ወራሪዉ የጣሊያን ጦር አገራችንን ለመወረር ሲመጣ ዶጋሌ ላይ በራስ አሉላ ጦር የተገደሉትን አምስት መቶ የጣሊያን ወታደሮች ለማስታወስ ነዉ። በ1877 ዓም ዘመናዊ መሳሪያ ታጥቆ ጦርና ጎራዴ በታጠቀዉ የራስ አሉላ ጦር ዉርደት የተከናነበዉ የጣሊያን ወራሪ ሠራዊት ብድሩን ለመመለስ በ1888 ዓ.ም ብዛት ያለዉ ካባድ መሳሪያ፤ መድፍና መትረየስ ታጥቆ አድዋ ድረስ ቢመጣም በዳግማዊ ሚኒሊክ የተመራዉ ጀግናዉ የኢትዮጵያ ሠራዊት እንደገና ዉርደት አከናንቦት በጥቁር ህዝብ ታሪክ ዉስጥ ትዝታዉ ምንግዜም የማይደበዝዝ ድል አስመዝግቧል። የኢትዮጵያ ሠራዊት ዶጋሌና አድዋ ላይ እስካፍንጫዉ የታጠቀዉን የጣሊያን ወራሪ ጦር ደጋግሞ ያሸነፈዉ በመሳሪያ በልጦ ወይም የተሻለ የዉትድርና ችሎታ ስለነበረዉ ሳይሆን ከወራሪዉ ጦር የበለጠ ቆራጥነትና የአለማ ጽናት ሰለነበረዉ ነዉ።
በሃያኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን የተደረጉ ሌሎች የነጻነት ትግሎችን ስንመለከት በወቅቱ የአየር ኃይል ያልነበራት ትንሿ አገር ቬትናም በባህር፤ በአየርና በየብስ ጦርነት የገጠማትን ትልቁን የአለማችን ሀይል አሜሪካንን አሸንፋ ነፃነቷን ያስከበረችዉ በመሳሪያ ጋጋታ ሳይሆን የዛፍ ላይ ቅጠልና የተቦጫጨቀ ጨርቅ በለበሱ ነገር ግን ከፍተኛ የአላማ ጽናት በነበራቸዉ ጀግኖች ልጆቿ አማካይነት ነዉ።
አለማችን ትልቅ የጦርነት አዉድማ ናት ቢባል አባባሉ እምብዛም ከእዉነት የራቀ አባባል አይደለም። በእርግጥም አለም የጦርነት መድረክ ናት። ወደድንም ጠላን ወይም ብናምንም ባናምንም ጦርነቶች ሁሉ የተካሄዱት የህዝብን ነፃነት በሚደፍሩ ኃይሎችና መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች መካከል ነዉ። የአለማችን ታሪክ ወለል አድርጎ እንደሚያሳየን ደግሞ ይዋል ይደር እንጂ ሁሉም ዘለቄታዊ ድሎች የተመዘገቡት የአላማ ጽናት ባላቸዉ መብቴንና ነጻነቴን አትንኩ በሚሉ ኃይሎች ነዉ እንጂ የመሳሪያ ጋጋታ በተሸከሙ ኃይሎች አይደለም። የመሳሪያ ጋጋታ የተሸከመና ብዛት ያለዉ ወታደር ያሰለፈ ነገር ግን ለምን እንደሚዋጋ የማያዉቅና የአላማ ጽናት የሌለዉ ሠራዊት ግዜያዊ የጦር የጦር ሜዳ ድል ለያገኝ ይችላል፤ ሆኖም ጦርነቱን አሸንፎና የህዝብን ነጻነት ቀምቶ መዝለቅ በፍጹም አይችልም።
የአለም ታሪክ በነጭ ወረቀት ላይ በጥቁር ቀለም ቁልጭ አድርጎ የጻፈዉ አንድ ግዙፍ ሀቅ ቢኖር እልፍ ታንክና እልፍ አዕላፋት መድፎች ቢታጠቁም አምባገነኖች ለግዜዉ እንደተቆጣ ነብር ያስፈራሉ እንጂ ህዝባዊ አለማና ጽናት ያለዉ ጦር ፊት ሲቆሙ ፀሐይ እንደገላመጠዉ በረዶ ሟሽሸዉ የሚጠፉ ደንባራ ፈረሶች ናቸዉ። ለዚህም ነዉ ህዝብ አምባገነኖችን የወረቀት ላይ ነብር እያለ የሚጠራቸዉ።
ዛሬ ዕድሜዉ 35 እና ከዚያም በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚኒልክን ቤ/መንግስት ተቆጣጥረዉ የረገጡትን፤ የገደሉትንና መብቱንና ነጻነቱን ገፍፈዉ ያዋረዱትን ሁለት የወረቀት ላይ ነብሮች ያስታዉሳል የሚል ሙሉ እምነት አለን። ደርግ በ1967 ዓም “ያለ ምንም ደም እንከኗ ይዉደም” እያለ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በፊዉዳሉ ስርዐት ጀርባዉ የጎበጠዉን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ደስ አሸኝቶ ነበር። እየቆየ ሲሄድና የተደበቀ ትክክለኛ መልኩ አደባባይ ሲወጣ ግን ያንን “ያለ ምንም ደም” የሚለዉን መፈክሩን ረስቶ ኢትዮጵያን የደም ገንዳ ሲያደርጋት በኢትዮጵያ ህዝብ ተጠልቶ አይንህን ለአፈር ተባለ። በሩሲያ ሰራሽ ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች አስካፍንጫዉ የታጠቀዉና በቁጥሩና በወታደራዊ ብቃቱ አፍሪካ ዉስጥ ትልቁን ሠራዊት የገነባዉ ደርግ “እንደ ዉኃ የሚያጥለቀልቅ ኃይል አለኝ” እያለ ቢፎክርም እሱ እራሱ ተጥለቅልቆና በያለበት ተሸንፎ አገራችን ኢትዮጵያን ለዘረኛ አምባገነኖች ያስረከበዉ ለእግሩ ጫማ ለወገቡ መታጠቂያ በሌለዉ የገበሬ ጦር ተሸንፎ ነዉ። ደርግ እንደታጠቀዉ መሳሪያ ብዛት፤ እንዳደራጀዉ ወታደራዊ ብቃትና እንደ ወታደራዊ መሪዎቹ ችሎታ ቢሆን ኖሮ ደርግን እንኳን ተዋግቶ ለማሸነፍ በዉግያ ለመግጠምም የሚያስብ ኃይል በፍጹም አይነሳም ነበር፤ ነገር ግን ድል ምን ግዜም ቢሆን የመሳሪያ ጋጋታ ዉጤት ሳይሆን የራዕይ ጥራትና የአላማ ጽናት ዉጤት በመሆኑ በወቅቱ ይህንን የተገነዘቡ ኃይሎች ህብረትና አገር ዉስጥ የተቀሰቀሰዉ ህዝባዊ ቁጣ አንድ ላይ ሆነዉ ደርግን ጠራርገዉ የታሪክ ቆሻሻ ዉስጥ ሊጨምሩት ችለዋል።
ዛሬ ደርግን አሸንፈዉ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ የተቀመጡት ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የአገርን ኃብት ከመዝረፍ፤ የተቃወማቸዉን ከመግደልና የኢትዮጵያን አንድነት ከማፍረስ ዉጭ እንዴትና ለምን ደርግን የመሰለ ሠራዊት እንዳሸፉ የተገነዘቡ አይመስልም። ወያኔዎች ደርግ ከወደቀ ከ24 አመት በኋላ ዛሬም በየቀኑ ደርግን ቢኮንኑም ተቀምጠዉ አገር የሚገዙት ልበቢሱ ደርግ የተቀመጠበት ወንበር ላይ ነዉና የደርግ በሽታ ተጋብቶባቸዉ እነሱም እንደደርግ ልበቢሶች ሆነዋል።
ኢትዮጵያ በየዘመኑ እያደገና እየዘመነ የመጣ፤ ከተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የተዉጣጣና ሞያን፤ ችሎታንና ወታደራዊ ሳይንስን አዳብሎ የታጠቀ ዘመናዊ የአገር መከላከያ ተቋም የነበራት አገር ነበረች። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ ይህንን ዘመናዊ የአገርና የወገን መመኪያ የሆነ ሠራዊት አፍርሰዉና በየበረሃዉ ለእናት አገሩ የተዋደቀዉን ሰራዊት ለማኝ አድርገዉት ነዉ እነሱ ወርቃማዉ ዘር ብለዉ በሚጠሩት ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ተቋም የገነቡት። ወያኔ የገነባዉ የመከላከያ ተቋም ባለፉት ሃያ አራት አመታት ዉስጥ አዲስ አበባ፤ ኦጋዴን፤ ጋምቤላ፤ ደቡብ ኦሞና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የወሰዳቸዉን ፀረ ህዝብና ፀረ አገር እርምጃዎች ስንመለከት ተቋሙ እዉነትም ለአገር ጥበቃ ሳይሆን የወያኔን የበላይነት ለማረጋገጥ የተቋቋመ ኃይል መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይችላል።
ይህ ሙሉ በሙሉ በትግርኛ ተናጋሪዎች የሚታዘዘዉ መከላከያ ሠራዊት ጋምቤላና ኦሞ ሸለቆ ዉስጥ ገበሬዉ ከቀዬዉ ተፈናቅሎ መሬቱ ባዕዳን ሲቸበቸብ አፉን ዘግቶ እንዲመለከት አድርጓል። ይሄዉ ሠራዊት በ1997 ዓም በአግአዚ ነብሰ ገዳዮች እየተመራ የህዘብ ድምጽ ይከበር ያሉ ከ200 በላይ ሠላማዊ ዜጎችን በግፍ ጨፍጭፏል፤ ከዚህ በተጨማሪ የወያኔ መከላከያ ሠራዊት አጋዴንና ጋምቤላ ዉስጥ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽሟል አሁንም እየፈጸመ ነዉ። እዚህ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ትኩረት ሰጥቶ ሊመለከተዉ የሚገባዉ ነገር አለ፤ እሱም ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ልማታዊ ሠራዊት ብለዉ እያሞካሹና “የመከላከያ ኃይሎች ቀን” የሚል ስያሜ ሰጥተዉ በየአመቱ ማክበር የጀመሩት በዐል የሚያወድሰዉ ይህንኑ አንድነቱንና ነፃነቱን እጠብቃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን የገባለትን ህዝብ ያለ ርህራሄ የሚጨፈጭፈዉን የወያኔ ሠራዊት ነዉ። በተለይ ወያኔ ባለፈዉ ሳምንት ባህር ዳር ዉስጥ ያለ የለሌ የመሳሪያ ጋጋታዉን አደባባይ አዉጥቶ ለህዝብ እያሳየ ባከበረዉ የመከላከያ ቀን በዐል ለህዝብ ማስተላለፍ የፈለገዉ መልዕክት ቢኖር “ይህንን እያያችሁ ከወያኔ ጋር በእሳት አትጫወቱ “ የሚል የሞኝ መልዕክት ነዉ።
ይህ ባህር ዳር ላይ የተላለፈዉ መልዕክት ለማን እንደሆነና በተለይ ባህር ዳር የመልዕክቱ ማስተላለፊያ ቦታ ሆና የተመረጠችበት ምክንያት ለማንም ኢትዮጵያዊ ግልፅ ይመስለናል። የዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች መሰባሰቢያ የሆነዉ ህወሓት የተወለደዉም ሞቶ የሚቀበረዉም ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ መሆኑን እሱም ደጋፊዎቹም ካወቁ ቆይቷል። ዉቧና የጀግኖች መፍለቂያ የሆነችዉ ባህር ዳር ደግሞ ይህንን የወያኔን የቀብር ጉዞ ከጀመረች አመታት አስቆጥራለች። እንገዲህ ወያኔ በየቀኑ ከባድ መሳሪያና ስፍር ቁጥር የሌለዉ ወታደር ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ከዚሁ ከማይቀርለት ዉድቀቱ የሚያድኑት እየመሰለዉ ነዉ። እዚህ ላይ አንድ ወያኔ በፍጹም ያልተረዳዉ ነገር ቢኖር ህወሓትን ከኢትዮጵያ ምድር ጠራርጎ የሚያጠፋዉና ግብዐተ መሬቱን የሚፈጽመዉ ይሄዉ ወያኔ በነጋ በጠባ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚያጓጉዘዉ ሠራዊት መሆኑን አለመረዳቱ ነዉ። የወያኔ አይን ያወጣ ዘረኝነት በከፍተኛ ደረጃ ከተንጸባረቀባቸዉና በየቀኑ በዘረኝነት እሳት ከሚለበለቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የመከላከያ ሠራዊት ነዉ። ይህ ሰራዊት እንደ መሬት የሚረግጡትን የወያኔን አለቆቹን ትዕዛዝ ተቀብሎ ከታሰረበት የዘረኝነት እስር ቤት ነፃ ሊያወጡት በሚታገሉ የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ኃይሎች ላይ መሳሪያዉን ያዞራል ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ያለ አይስለንም፤ በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔን የመሳሪያ ጋጋታ አይቶ ለእናት አገሩ አንድነትና ለኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ነጻነት ህይወቱን ከመስጠት ወደ ኋላ የሚል ኢትዮጵያዊ ቢኖር እሱ ከወያኔ ጋር በጥቅም የተጋባ ከሃዲ መሆን አለበት። የኢትዮጵያ ህዝብ ምንግዜም ቢሆን በወሬ ቱማታና በመሳሪያ ጋጋታ ትጥቁን ፈትቶ አያዉቅም። በ1930ዎቹ ፋሺስት ጣሊያኖችንና በ1970ዎቹ ወታደራዊዉን ደርግ ተዋግቶ ያሸነፈዉ እነዚህ ኃይሎች የታጠቁትን መሳሪያ እየቀማ በተዋጋቸዉ ነጻነት የጠማዉ ኃይል ነዉ። የዛሬዎቹ የወያኔ ፋሺስቶች እጣም ጣሊያንና ደርግ ከገጠማቸዉ ሽንፈት የተለየ አይሆንም።
የአገራቸዉን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ከጠላት ለመከላከል የመከላከያ ሠራዊትን የተቀላቀሉ የኢትዮጵያ ልጆች “ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት” የሚለዉን የአባቶቻቸዉ ምሳሌያዊ አባባል ምንነት በሚገባ የሚረዱ ይመስለናል። ስለሆነም ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ በዘር ለይቶ እየረገጣቸዉ፤ እያዋረዳቸዉና ከሰዉ በታች አድርጎ እየተመለከታቸዉ ይህንን ቅጥ ያጣ በደል ለማረሳሳት የመከላከያ ቀን እያለ በሚያከብረዉን የይስሙላ በዐል እንድም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባል ሊታለል አይገባም። ከአግአዚ ነብሰ ገዳዮች ዉጭ ያለዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እንደማንኛዉም የወያኔ እስረኛ እንደሆነ የህብረተሰብ ክፍል ነፃ መዉጣት የሚገባዉ ክፍል ነዉ። ይህ የህዝብ ወገን የሆነዉ የመከላከያ ሠራዊት እራሱን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹንና እህቶቹን ጭምር ከወያኔ ዘረኝነት ነጻ ሚያወጣት አለበት። እስከቅርብ ግዜ ድረስ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ብዙም አማራጭ ስላልነበራቸዉ አንገታቸዉን ደፍተዉ የጠላታቸዉን የወያኔን ትዕዛዝ እየተቀበሉ ሲፈጽሙ ቆይተዋል፤ አሁን ግን አንገታቸዉን ቀና አድርገዉ የወያኔን አንገት የሚያሰደፉበት አመቺ ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል። ዛሬ ለእናት አገራቸዉ ነጻነት በህይወታቸዉ ቆርጠዉ ብረት ያነሱ የነጻነት አርበኞች የመከላከያ ሠራዊት የወያኔ አለቆቼን ትዕዛዝ ላለመቀበልም ሆነ ወይም የታጠቀዉን መሳሪያ ወደ ጠላቱ ወደ ወያኔ ማዞር የሚችልበትን አመቺ ሁኔታ ፈጥረዉለታል።
ዉድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት ሆይ ጨለማዉ ሊጠራ ሲል ይበልጥ ይጨልማልና ወያኔ ወደ ሰሜናዊዉ የአገራችን ክፍል የሚያጓጉዘዉ የመሳሪያ ጋጋታና የሠራዊት ብዛት በፍጹም ልትደናገጥ አይገባም። ወያኔን ካንተ በላይ በቅርብ የሚያዉቀዉ የለም፤ የወያኔ ኃይለኝነትና ትልቅ መስሎ መታየት አንተ በዉስጡ ስላለህበት ብቻ ነዉ። ስለዚህ ይህንን ፀረ ኢትዮጵያ ኃይል ለቅቀህ በያለህበት ላንተ፤ ለወገኖችህና ለእናት አገርህ ነፃነት መከበር ከቆረጡ ወገኖችህ ጋር በፍጥነት ተቀላቀል። ይህንን ማድረግ የማትችለዉ ደግሞ ወያኔ ከገዛ ወገኖችህ ጋር እንድትዋጋ ትዕዛዝ ሲሰጥህ የታጠከዉን መሳሪያ ወደ ወገኖችህ ሳይሆን ወደ ራሱ ወደ ወያኔ አዙር። ወያኔ ለትንሽ ግዜ የማይበገር መስሎ ሊታይ ይችል ይሆናል የማይቀረዉ የዘለቄታ ድል ግን ምን ግዜም የህዝብ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ደግሞ ትናንት አንደነበረ ሁሉ ዛሬም የኢትዮጵያ ህዝብ አለኝታ ነዉ።
ድል የህዝብ ነዉ!

የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በጨለማ ቤት መታሰራቸውን አስታወቁ

February 25,2015

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡
ዛሬ የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች ‹‹መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ›› እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡
ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና ጎጃም አካባቢዎች የዛሬ አራት ወር ገደማ በፖሊስ ታስረው ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ እንዲዛወሩ የተደረጉ ሲሆን፣ ጠበቃቸው በተደረገባቸው ክልከላ ምክንያት ተጠርጣሪዎቹን ካገኟቸው 2 ወር እንደሞላቸው ተናግረዋል፡፡ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አቶ አግባው ሰጠኝ እየተፈጸመበት ያለውን የመብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ ላይ መሆኑ የታወቀ ሲሆን አድማውን ከጀመረ ሁለተኛ ቀኑ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፍርድ ቤቱ በሰጠው የጊዜ ቀጠሮ መሰረት አመራሮቹ የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Tuesday, February 24, 2015

የጦፈ ሙስና ከመንገድ ሥራ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና ከቤቶች ልማት

February 24,2015
በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ ነው - ሚኒስትሩ

lightrail road

* ከ30 እስከ 40% የግንባታ ወጭ ይዘረፋል!!

የኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ፣ ከባቡር መስመር ዝርጋታና፣ ከቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየተዘረፈ መሆኑን አምነዋል።

 የፀረ ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው ጥናት በባቡር መስመር ግንባታ 2.3 ኪሜ የባቡር ሃዲድ መስመር በሙስና ምክንያት ከደረጃ ውጭ እንዲሆን በመደረጉ የ124 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ደርሷል። የአደጋ መከላከያ ብረቶች የተሰሩት ከወጣላቸው የጥራት ደረጃ በሶስት እጅ ያነሱ ሆነው በመገኘታቸው ጉዳዩ ለቦርድ ሰብሳቢው አርከበ እቁባይ ቢቀርብም ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረቱ በቢሊዮየኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪ ልማት ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ሃይሌ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን አጣሪ ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ከመንገድ ስራ፣ን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገባ ማወቅ አለመቻሉን ገልጿል።
የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ምላሽ የሰጡት ሚኒስትር መኩሪያ ሃይሌ፣ ችግሩ የተፈጠረው ለምርጫው ሲባል የባቡሩ ግንባታ እንደ ትልቅ የምርጫ ማሳመኛ በመያዙ ነው ።
የግንባታ ኢንዱስትሪው ከሚያወጣው ወጪ ከ30 እስከ 60 በመቶ የሚሆነው በሙስና ይባክናል ሲሉም ሚኒስትሩ አክለዋል።
እንደዚያም ሆኖ በቅርቡ የተመረቀ የአዲስ አበባ መለስተኛ የባቡር ግንባታ፣ አገልግሎት ከመጀመሩ ከወዲሁ በርካታ የመፈራረስ ችግሮች እያጋጠሙት ነው። ለፖለቲካ ፍጆታና ለፕሮፓጋንዳ ሲባል ቶሎ ቶሎ እንዲሰራ ከማድረግ ዉጭ እነ አቶ አርከበ እቁባይ የሕዝቡን ፍላጎት ከግምት ያላስገቡ ሲሆን፣ አስፈላጊ የጥንቃቄ እርምጃዎች አልተወሰዱም። በዋናነት የባቡ ሃዲዱ ከተማዋን ለሁለት የከፈለ ሲሆን ከሃዲዱ በስተቀኝ እና በስተግራ ያሉ ነዋሪዎች ለመገናኘት እጅግ በጣም ብዙ ርቀት ለመጓዝ ተገደዋል።

Monday, February 23, 2015

World Bank: Address Ethiopia Findings (Human Rights Watch)

February 23, 2015

Response to Inquiry Dismissive of Abuses

(Washington, DC) – The World Bank should fully address serious human rights issues raised by the bank’s internal investigation into a project in Ethiopia, Human Rights Watch said in a letter to the bank’s vice president for Africa. The bank’s response to the investigation findings attempts to distance the bank from the many problems confirmed by the investigation and should be revised. The World Bank board of directors is to consider the investigation report and management’s response, which includes an Action Plan, on February 26, 2015.Response to Inquiry Dismissive of Abuses
The Inspection Panel, the World Bank’s independent accountability mechanism, found that the bank violated its own policies in Ethiopia. The investigation was prompted by a formal complaint brought by refugees from Ethiopia’s Gambella region concerning the Promoting Basic Services (PBS) projects funded by the World Bank, the United Kingdom’s Department for International Development (DFID), the African Development Bank, and several other donors.
“The Inspection Panel’s report shows that the World Bank has largely ignored human rights risks evident in its projects in Ethiopia,” said Jessica Evans, senior international financial institutions researcher at Human Rights Watch. “The bank has the opportunity and responsibility to adjust course on its Ethiopia programming and provide redress to those who were harmed. But management’s Action Plan achieves neither of these goals.”
The report, leaked to the media in January, determined that “there is an operational link” between the World Bank projects in Ethiopia and a government relocation program known as “villagization.” It concluded that the bank had violated its policy that is intended to protect indigenous peoples’ rights. It also found that the bank “did not carry out the required full risk analysis, nor were its mitigation measures adequate to manage the concurrent rollout of the villagisation programme.” These findings should prompt the World Bank and other donors to take all necessary measures to prevent and address links between its programs and abusive government initiatives, Human Rights Watch said.
Rather than taking on these important findings and applying lessons learned, World Bank management has drafted an Action Plan that merely reinforces its problematic current course, Human Rights Watch said. The Action Plan emphasizes the role of programs designed to mobilize communities to engage in local government’s decisions without addressing the significant risks people take in speaking critically.
The Inspection Panel also found that the bank did not take the necessary steps to mitigate the risk presented by Ethiopia’s 2009 law on civil society organizations. The law prohibits human rights organizations in Ethiopia from receiving more than 10 percent of their funding from foreign sources. As a result of the law, most independent Ethiopian civil society organizations working on human rights issues have had to discontinue their work.
The plan also pledges to enhance the capacity of local government staff to comply with the bank’s policies and to provide complaint resolution mechanisms without addressing the role of the local government in human rights abuses. This continues an approach of seeing the officials implicated in human rights abuses as a source of potential resolution, Human Rights Watch said. Management has also concluded, contrary to the Inspection Panel, that the World Bank is adequately complying with the bank’s policy to protect the rights of indigenous peoples.
Human Rights Watch research into the first year of the villagization program in the western Gambella region found that people were forced to move into the government’s new villages. Human Rights Watch found that the relocation was accompanied by serious abuses, including intimidation, assaults, and arbitrary arrests by security officials, and contributed to the loss of livelihoods for the people forced to move. While the Ethiopian government has officially finished its villagization program in Gambella, it is forcibly evicting communities in other regions, including indigenous people, ostensibly for development projects such as large-scale agriculture projects.
Donors to the Ethiopia Promoting Basic Services Program, including the World Bank and the UK, have repeatedly denied any link between their programs and problematic government programs like villagization.
Human Rights Watch has long raised concerns over inadequate monitoring and the risks of misuse of development assistance in Ethiopia. In 2010 Human Rights Watch documentedthe government’s use of donor-supported resources and aid to consolidate the power of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF). Government officials discriminated on the basis of real and perceived political opinion in distributing resources, including access to donor-supported programs, salaries, and training opportunities. Donors have never systematically investigated these risks to their programming, much less addressed them.
The Inspection Panel report is the first donor mechanism that has investigated the donor’s approach to risk assessment in Ethiopia. Although the Inspection Panel adopted a narrow view of its mandate and decided explicitly to exclude human rights violations, its findings underscore the need for donors to considerably enhance and broaden their risk assessment processes in Ethiopia. These processes are crucial for ensuring that their programs advance the social and economic rights of the people they are intended to benefit, without violating their human rights. Management’s response misrepresents the panel’s view of its mandate, erroneously concurring “with the panel’s conclusion that the harm alleged in the Request cannot be attributed to the Project” – the Inspection Panel report makes no such sweeping conclusion.
“The bank directors should send management’s response and Action Plan back and insist on a plan that addresses the Inspection Panel’s findings and the concerns of the people who sought the inquiry,” Evans said. “A meaningful Action Plan should address the program in question, bank-lending in Ethiopia more broadly, and how to apply lessons from these mistakes to all bank programing in high-risk, repressive environments around the world.”
The Action Plan should include provisions for high-level dialogue between the bank and the Ethiopian government to address key human rights issues that are obstacles to effective development, Human Rights Watch said. These issues include forced evictions and development-related displacement, restrictions on civil society, including attacks on independent groups and journalistsdiscriminatory practices, and violations of indigenous peoples’ rights.
The plan should include provisions for identifying and mitigating all human rights risks and adverse impacts at the project level, and for independent monitoring to make sure these concerns are fully addressed. The plan should also include provisions for people affected by projects to be involved in projects from their conception and remedies for people negatively affected by bank projects.
Given the climate of fear and repression in Ethiopia, Gambella residents who brought the complaint to the bank and have taken refuge in South Sudan and Kenya are unlikely to feel safe returning home. In light of this, the Action Plan should address their most urgent needs abroad, including education and livelihood opportunities, Human Rights Watch said.
The Inspection Panel’s findings also have wider implications for donor programming in Ethiopia. Donors’ current appraisal methods do not consider human rights and other risks from their programs. The panel highlighted particular problems with budget support or block grants that cannot be tracked at the local level.
“The Inspection Panel report illustrates the perils of unaccountable budget support in Ethiopia,” Evans said. “Donors should implement programs that ensure that Ethiopia’s neediest participate in and have access to the benefits of donor aid.”

Thursday, February 19, 2015

እውን ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚደነቅ የሚከበር ነገር አለውን?

February 19,2015
(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
tplf addis
በእስካሁኑ ግፍ ያልጠፋኸው ነገር ግን ለማይቀርልህ ወገኔ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እንኳን ለአጥፊህ ለወያኔ ሐርነት ትግራይ 40ኛ ዓመት የልደት በዓል አደረሰህ! የዚህች ሀገር ነቀርሳ በውስጧ የበቀለበት 40ኛ ዓመት እነሆ ከነገ ወዲያ እሮብ የካቲት 11 2007ዓ.ም. ይከበራል፡፡
ግን ወያኔ ማን ነው? እውን የሚከበር የሚያኮራ ማንነት አለው? ነው ወይስ የሚረገምና የሚያሳፍር? ከዚህ ቡድን ውስጣዊ ታሪክ እንደምንረዳው ይህ ቡድን በርዕዮተ ዓለምና በአስተሳሰብ ልዩነት በግል ጥቅምና በሥልጣን ሽኩቻ አንዱ ሌላውን እየበላ አንዱ በሌላው እየተበላ እርስ በእርስ እንደ አውሬ እየተባላ እየተጠፋፋ በመጨረሻ በአውሬነቱ የበረታው የበረታው አስከፊው አስከፊው ቀርቶና ተቧድኖ ለዚህ የደረሰ እኩይ ሰይጣናዊ ቡድን ነው፡፡
የወያኔን የትግል ታሪክ ስናይ ከቀደምቶቹ የሕወሀት አባላት ጥለው ከወጡትም ካሉትም ከተገለሉትም በተለያየ ጊዜ በሰጡት ቃለ መጠይቆቻቸውና በጻፉት መጻሕፍቶቻቸው ላይ እንደተረዳነው ወያኔ እዚህ ለመድረስ ተጀምሮ እስኪጨረስ ድረስ አብዛኛውን ጊዜ ከዓረብ ሀገራት ከሸአቢያ በተለይም ከሱዳን ለሚያደርገው የትጥቅ ትግል ምድሯን እንደፈለገ እንዲጠቀምበት ፈቅዳ ለወያኔ መሸሻ መሸሸጊያ መሠልጠኛና መደራጃ የተለያዩ ዓይነት ድጋፍ እርዳታዎችን ያገኝ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ደርግ በበቀል 800ኪ.ሜ. ድረስ ወደ ሱዳን ዘልቆ እየገባ በጦር አውሮፕላን የሚደበድብበት ሁኔታ ነበር፡፡ ሱዳን ከወያኔ የምትፈልገው ብዙ ነገር ነበርና በወያኔ ትግል ወቅት ለወያኔ ብዙ ዋጋ ከፍላለች፡፡ ወደ ኋላ አካባቢ ደግሞ ወያኔ ድጋፍ እርዳታን ከአውሮፓና ከአሜሪካ ያገኝ ነበር፡፡
እነኝህ አካላት ሁሉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍና እርዳታ ለወያኔ ሲሰጡ እንዲሁ በነጻ ያለ ጥቅም ከሱ የሚፈልጉት ነገር ሳይኖር አልነበረም፡፡ ሁሉም ከወያኔ እንዲሰጣቸው ወይም እንዲደረግላቸው የሚፈልጉትና ወያኔም ሊያደርግላቸው ቃል የገባላቸው የየራሳቸው ጥቅሞች አላቸው፡፡ የሚያሳዝነው ሁሉም እንዲደረግላቸው የሚፈልጉት ነገር ሁሉ የሀገራችንንና የሕዝቧን ብሔራዊ ጥቅሞችና ሉዓላዊነት በእጅጉ የሚጎዱ መሆናቸው ነው፡፡ እነኝህ አካላት የፈለጉት ምንም ከባባድ ነገር ቢሆንም ቅሉ ከራሱ ጥቅም የሚበልጥበት ምንም ነገር ለሌለው ለወያኔ የወንበዴ ቡድን ግን ኢምንት ነውና እንደየፍላጎቶቻቸው ተቀብሎ አስተናግዷቸዋል፡፡ ለምሳሌ የሱዳንን ብናይ ወያኔ የገባላትን ከጎንደር እስከ ጋንቤላ በ1600 ኪ.ሜ. እርዝመት ከ40 እስከ 60 ኪ.ሜ. ስፋት የሚያህልን ከአንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት በእጅጉ የሚልቅ መሬት ከሀገራችን ቆርሶ በሰነድ ደረጃ አስረክቧታል፡፡ ይህ በሰነድ አረጋግጦ የሰጣትን መሬት ግን መሬት ላይ ተፈጻሚ አድርጎ ወደ ሱዳን ለመቀላቀል በተደጋጋሚ ተሞክሮ ከሀገሬው በተነሣ የቆረጠ ቁጣ ሌላ መዘዝ እንደሚያመጣበት ስለሠጋ የራሱን ምቹ ጊዜ እየጠበቁለት ይገኛሉ፡፡ ሸአቢያም ከሚፈልገው በላይ አሰብን ያህል ወደብ ከነምርቃቱ አግኝቷል፡፡ ቢዘረዘር ሐተታው ብዙ ነው ብቻ ሁሉም የየድርሻቸውን አግኝተዋል እያገኙም ይገኛሉ፡፡
እንግዲህ የታሪክ አተላዎቹ፣ የወራዶቹ፣ የደናቁርቱ፣ የባንዳ ውላጁ ሁሉና የደዳብቱ ኩራት ወያኔ “አይ! ይሄማ እንዴት ይሆናል? እናንተስ እንዴት ደፋሮች ብትሆኑና እንዴትስ ብትንቁን ነው ኢትዮጵያዊያን መሆናችንን እያወቃቹህ እንደዚህ ዓይነት ጥያቄ የምትጠይቁን?” የሚልበት ጉዳይ አንዲት እንኳን ሳይኖረው የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅሞች አሳልፎ በመስጠትና ለመስጠትም ቃል በመግባት በሀገር ክህደት ወንጀሎች እስከ አፍንጫው ተነክሮበት ነው ለዚህ ስኬቱ የበቃው፡፡ እኔን የሚገርመኝ በእነኝህ ሁሉ አካላት ሁሉን አቀፍ ድጋፍና ምቹ ሁኔታዎች ተደግፎ 17ዓመታትን ያህል ዘመን መፍጀቱ ነው፡፡ ይህ የሚያሳየው ሕወሀት ምን ያህል ደካማ እንደነበረ ነው፡፡ ወያኔ ከጠላት ያገኝ የነበረውን ድጋፍና እርዳታ እርም ስለሆነ እሱን ተውትና እንዲያው ተገን ብቻ የሚሰጥ አንድ ጎረቤት ሀገር ቢኖርና በኢትዮጵያ አንድ ሌላ የከፋው ኃይል እንበል ለምሳሌ በወያኔ እስከ የዘር ማጥፋት ወንጀል ድረስ እየተፈጸመበት ያለው የአማራ ሕዝብ ይሄንን ዕድል ቢያገኝ 17 ዓመታት አይደለም መንፈቅ እንኳን የሚፈጅበት መሆኑ በጣም ያጠራጥረኛል፡፡ ወያኔ ይሄንንም ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ነው የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ እየሰጠ ሉዓላዊነቷን እያስደፈረ ጎረቤት ሀገራትን በሙሉ በጥቅም ይዞ መሸሻ መሸፈቻ እንዳይኖር ዙሪያውን ያጠረብን፡፡
ሌላ እንደ ወያኔ ያለ የጥፋትና የክህደት ኃይል ኢትዮጵያ ውስጥ ቢኖርና ወያኔ በመጣበት የረከሰ የጎደፈ ነውረኛና ወራዳ መንገድ ለመምጣት ቢሞክር ላይሳካለት የሚችልበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ምክንያቱም ይህ ወያኔ የመጣበት መንገድ የመጨረሻ ደካማ የተባለ ኃይል ሁሉ ሊመጣበት የሚችልበትና ለስኬትም ሊበቃበት የሚችልበት የመጨረሻው መንገድ በመሆኑ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን የትግል ተጋድሎና ስኬት ሊያደንቅና ክብር ሊሰጥ እችል የነበረው ወያኔ ለግል ቡድናዊ ጥቅሙ ሲል የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም፣ ክብር፣ ሉዓላዊነት ለድርድር ሳያቀርብና እየቸረቸረ አሳልፎ ሳይሰጥ ውድ መሥዋዕትነትን ከፍሎ በጀግኖች በቆራጦች በአርበኞች በፋኖዎች መንገድ የመጣ ቢሆን ነበር፡፡ ነገር ግን ወያኔ በተፈጥሮው ጠባብ፣ እራስ ወዳድ፣ ወራዳ፣ ነውረኛ፣ ደንቆሮ፣ ርካሽ፣ ከሀዲ፣ የእፉኝት ልጅ፣ በፀረ ኢትዮጵያ ዓላማ የተመረዘ እኩይ የእርግማን ልጅ የአጋንንት ውላጅ ስለሆነ ማንም ያስገደደው ሳይኖር ከፊሎቹን ከያሉበት ድረስ እየሔደ ያላሰቡትን እያሳሰበ “እንዲህ ብታደርጉልኝ እንዲህ አደርግላቹሀለው” እያለ እየዞረ እየለመነ እየተማጸነ ይሄንን ዓይነት በአሳፋሪነቱ ተወዳዳሪ የማይገኝለትን ኢትዮጵያዊ ደም ካለው ፈጽሞ የማይጠበቅ በእጅጉ የራቀና ባዕድ የሆነ ወራዳና ነውረኛ መንገድ ፈጥሮ ሊመጣበትና ለስኬት ሊበቃበት ቻለ፡፡ በዚህ የወያኔ ነውረኛና ወራዳ ማንነት ሊኮራ የሚቃጣው ማንም ዜጋ ካለ ለበሽተኛነቱ ፈጽሞ አትጠራጠሩ፡፡ ለሀገር ለወገንም ቅንጣትም እንኳን የማይጠቅም ይልቁንም የሚያጠፋ ነውና አደራቹህን ሲያጋጥማቹህ እንደ እባብ እራስ እራሱን ቀጥቅጣቹህ አጥፉት፡፡
ወያኔ ከራስ ወዳድነቱ፣ ከጠባብነቱ፣ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” የአሕያ አስተሳሰቡ የተነሣ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሀገራችንን እንደ ግል ንብረቱ በመቁጠር ስንትና ስንት ሊያገለግሏት የሚሹ የተማሩ የበቁ የነቁ የጠነቀቁ ምሁራን እያሏት “እኛን እስካልመሰለ ጊዜ ድረስ ሽ ጊዜ አዋቂ ምሁር ቢሆን አንፈልገውም፡፡ መርሖዋችንን እስከተቀበለ ጊዜ ድረስ ደግሞ መሀይምም ቢሆን በሚንስትር ደረጃ እንሾመዋለን” በሚለው በብዙኃን መገናኛ በአቶ መለስ በተገለጸው የአገዛዙ አቋም መሠረት ሥልጣንና ኃላፊነት የተባለን ቦታ ሁሉ በደናቁርት ልጆቹና አጋር ደጋፊዎቹ ጠቅጥቆ ሞልቶ ሀገሪቱ በሌላት አቅም ብዙ ነገር እየተበላሸባት እየባከነባት እየጠፋባት እየተበላባት ተምረው ላይማሩ ነገር መማሪያ መለማመጃ መቀለጃ መጫወቻ አድርገዋት ይገኛሉ፡፡ ይህ ሁሌም ሳስበው ድንቅ የሚለኝ የአገዛዙ አቋም ወያኔ ሳያፍር ሊያራምደው ሊሠራበት የቻለበት ምክንያቶች አንደኛ ሊደብቀው ባልቻለው ባለው ፈላጭ ቆራጭ ፀረ ዲሞክራሲ (በይነ ሕዝብ) እና ፀረ ሕዝብ ማንነቱ የተነሣ፣ ሁለተኛ ሊከውነው ሊፈጽመው የሚፈልገውን በየ ፈርጁ ያለውን ያሰበውን ፀረ ሕዝብና ፀረ ኢትዮጵያ የጥፋት ዓላማ ሊያስፈጽሙት ስለማይችሉ፣ ሦስተኛ ምሁራን ከጎናቸው ቢሆኑ በአላዋቂነታቸው መሸማቀቅ ሊሰማቸው የሚችለውን መሳቀቅና ሀፍረት በመፍራት ናቸው፡፡
tplf12በእነዚህ ምክንያቶች የተነሣ እያየነው እንዳለነው ሁሉ ሀገራችን የ4ኛ ክፍልና የ5ኛ ክፍል የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪ ጄኔራሎች ሚንስትሮችና የሥራ ኃላፊዎች ያሉባት በ21ኛው መቶ ክ/ን ተገዳ በመሀይማን የምትመራ የዓለማችን ብቸኛ ሀገር ለመሆን በቅታለች፡፡ በዚህም የወያኔ የደነቆረና አንባገነናዊ አሠራር ምክንያት በገንዘብ ሊሰላ የማይችለው ቀርቶ በገንዘብ ሊሰላ የሚችለው በዚህች ሀገር የደረሰባት ኪሳራና ጉዳት ይሰላ ቢባል በትሪሊዬን (በብልፊት) ደረጃ የሚጠቀስ የገንዘብ መጠን ሊገልጸው መቻሉን እጠራጠራለሁ፡፡ ከዚህ የሚከፋው ጉዳትና ኪሳራ ግን በገንዘብ ሊገለጹ የማይችሉ የደረሱብን ጉዳትና ኪሳራዎች ናቸው፡፡ እንግዲህ ወያኔ ማለት ይሄ ነው እና ታዲያ ወያኔን በየትኛው ኢትዮጵያዊ ተፈጥሮውና ብቃቱ፣ ማንነቱ፣ ድንቅ ሥራው፣ ጽናቱ፣ ቁርጠኝነቱ መልካም ምግባሩ ነው ላደንቀው የምችለው? መች ጭንቅላቴ ላሸቀና? መች ታመምኩና? መች ማሰብ ተሳነኝና? መች ደነቆርኩና? መች ሆዴን አመለኩና? እነዚህ የወያኔ ርካሽና ወራዳ ማንነቶች እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ሊገለጽ በሚከብድ በማይቻል ስሜት እንድጠየፈው እንድንቀው ያደርጉኛል እንጅ ከቶ እንዴት ሆኖ በምን ተአምር ነው እንዳደንቀው እንዳከብረው የሚያደርጉኝ? ወያኔን ባሰብኩ ቁጥር ሀገሬን እንዴት ተሸማቃ ተጨንቃ ተሸብራ ተመሰቃቅላ እንደማያት ማን በነገረልኝ?
ወያኔ ሀገር አያውቅም ወያኔ ሕዝብ አያውቅም ለወያኔ ሀገሩ ትግራይ ናት ለወያኔ ሕዝቡ የትግራይ ሕዝብ ነው፡፡ ምንም እንኳን ወያኔ እየለፋ እየደከመ እየጣረ ያለው ለትግራይና ለትግራይ ሕዝብ ነው ይበል እንጅ ነገሩን ልብ ብለን ካየነው ግን የትግራይን ሕዝብ መቃብር ነው ተግቶ እየቆፈረ ያለው፡፡ የትግራይ ሕዝብ አልገባውም እንጅ ወያኔ እሱ በሥልጣን እስካለ ጊዜ ብቻ እንዲኖር አድርጎ ነው ሰይጣናዊ ሸር እያሴረበት ያለው፡፡ ወያኔ ሆን ብሎ በትግራይ ሕዝብ ስም በሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ግፍ በደልና ክህደት እየፈጸመ ፍጹም ኃላፊነት በጎደለው ተግባርና ጠላትነት ሕዝቤ በሚለው የትግራይ ሕዝብ ላይ ተግቶ በነፍሱ እየቀለደበት እየቆመረበትና ሴራ እየተበተበበት ይገኛል፡፡ ወያኔ “በእኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አስተሳሰቡ ምክንያት እሱ የማይኖርባት ኢትዮጵያ ከመጣች ሊያፈራርሳት ቆርጦ ከጠዋቱ አስቦበት የጥፋት ሴራውን ሕገ መንግሥቴ በሚለው የፀረ ኢትዮጵያ ሰነዱ አስቀምጧል፡፡ ከዚህ ቀደምም እንዳልኩት ወያኔ ፀረ ኢትዮጵያና ሕዝቧ መሆኑን ከሚያጋልጡበት ድርጊቶቹ አንዱ ይሄንን አንቀጽ ሕገ ምንግሥቴ በሚለው ሰነዱ ማካተቱና በዚህም አጥፊ አስተሳሰቡ መሠረት ባሕረ ምድርን ማስገንጠሉ ነው፡፡ ይሄንን ጸረ ኢትዮጵያ ሰነዱን ለማጽደቅ የተደፋፈረው ለዚህች ሀገርና ሕዝብ ካለው የባዕድነትና የጠላትነትና የቅጥረኛነት ስሜቱ የነተሣ ነው፡፡ ይህ ወያኔ ኢትዮጵያን ለመበታተን ያሴረበት አንቀጽ በየትኛውም ሀገር ሕገ መንግሥት ወያኔ ባሰፈረው መልኩ ተቀርጾ አያውቅም፡፡ በገዛ ሀገሩ ላይ የሚያሴር ሕገ መንግሥት ተብየ የወያኔው የጥፋት ሰነድ ለዓለማችን ብቸኛውና የመጀመሪያው ነው፡፡
ወያኔ ልማት የሚባል ነገር አያውቅም ጥፋት እንጅ፡፡ ብዙ የዋሀን አሉ ወያኔ ልማት እየሠራ የሚመስላቸው፡፡ ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ እያለ በሀገሪቱ ስም ዓለማቀፋዊ ደረጃውን የጠበቀ ሥራ ሊያሠራ የሚችል ብድርና እርዳታን ይወስድና አብዛኛውን መዝብሮ ይወስዳል ከአበዳሪዎቹ “የታለ የተሠራው?” መባሉ አይቀርምና ካልሠራም ሌላ ብድርና እርዳታ ማግኘት ስለማይችል ተመዝብሮ በቀረው በጥቂቱ የማይረባ ተመርቆ ለአገልግሎት ከመብቃቱ በፊት ውኃ ውስጥ እንደገባ ካርቶን የሚፍረከረክ መንገድ፣ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የማይችል የቴሌኮምና የመብራት ኃይል አገልግሎት ወዘተ. እየገነባ በብዙ ቢሊዮን (ብልፍ) የሚቆጠር ብድርና ዕርዳታ በማምጣት ሀገሪቱን ላልተገባና እጅግ ከአቅም በላይ ለሆነ በትውልደ ትውልድ ተከፍሎ ለማያልቅ ባለዕዳነት ዳርጓታል፡፡ ይሄም ወደፊት ብዙ ብዙ ብዙ መከራና ችግር ይዞ ይጠብቃታል፡፡
አሁን ወያኔ 40ኛ ዓመቱን እያከበረ ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ምን ታዘብኩ መሰላቹህ?  ከሦስት ወራት በፊት ወያኔ ቅሊንጦ አስሮኝ እያለ እዚያ ካሉ ከተለያየ የአስተሳሰብ ጫፍ ካሉ ወገኖች ጋር በሀገራችን ችግሮች ላይ ያተኮረ ያደረግነውን ውይይትና ክርክር ከቅሊንጦ ከወጣሁ በኋላ ኅዳር ወር ላይ “የሀገራችን ፖለቲካና ስሉጣን (አክቲቪስቶች) በቅሊንጦ” በሚል ርእስ በጻፍኩት ሦስት ተከታታይ ጽሑፍ ላይ ገልጨው ነበር፡፡ እዚያ ያደረግነውን ውይይትና ክርክር ባሰፈርኩበት ጽሑፍ ላይ ታዲያ እነዚህ ተወያይ ተከራካሪ ወገኖች ወያኔና ሌሎቹ የጥፋት ኃይሎች እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ለእርኩሳዊ የጥፋት ዓላማቸው ሲሉ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚያወሩትን ስም ማጥፋትና የፈጠራ ወሬ ይዘው ያነሡትን ስም ማጥፋት እያንዳንዷን ነቅሸ በማውጣት ሐሰት ስለመሆኑም በመረጃ አስደግፌ ካስተባበልኩ ካረጋገጥኩ በኋላ የአማራ ሕዝብ ለዚህች ሀገር ነጻነት ህልውና ሥልጣኔና ደኅንነት ዕድሜ ልኩን ምን ያህል መራራ መሥዋዕትነት ሲከፍል እንደኖረ፣ በዚህም ሳቢያ ዛሬ ድረስ ስር ለሰደደ ድህነትና መሰል ችግሮች መዳረጉን ዘርዝሬ በውይይቱ ላይ ያልኩትን የሚከተለውን ቃል አስፍሬ ነበር፡-
“እናም የወያኔ መርዘኛ የጥፋትና የፈጠራ ፕሮፖጋንዳ (ልፈፋ) እና ስብከት ሰለባ ስለሆንን እንጅ ጭንቅላት ቢኖረን፣ ወደ ኋላም ወደ ፊትም ደወ ግራም ወደ ቀኝም መመልከት ብንችል፣ አርቀን አስፍተን ጠልቀን ማሰብ ብንችል፣ ኢትዮጵያዊነቱ ቢሰማን፣ የሀገራችንንና የሕዝቧንም ህልውና የምንፈልግ የምንመኝ የምንወድ ብንሆን በምንም ተአምር ያውም በሐሰተኛ ወሬ ለአማራ ጥላቻ ሊያድርብን አይችልም ነበር፡፡ ለዚህች ሀገርና ሕዝብ ህልውናና ነጻነት አማራ ለከፈለው ገደብ የለሽ መራራ ዋጋና መሥዋዕትነት እናመስግነው ብንል ለምስጋናችን ተስተካካይ ቃል ፈጽሞ ልናገኝለት አለመቻላችንን በሚገባ በተረዳን ነበር፡፡ ከፍለን ልንጨርሰው የማንችለው ዕዳ እንዳለብን በተረዳን ነበር፡፡ አማራን ልንጸየፍ ልንጠላ አይደለም ወደነውም ለፍቅራችን የልባችን ባልደረሰ ነበር፡፡ ውግዘትና ጥላቻውን ትተን ክብር በሰጠነው በኮራንበትም ነበር፡፡ ለዚህ ነው ለአማራ ያለው የጥላቻ መንፈስ መሠረቱ ድንቁርና፣ ጠባብነት፣ የሀገር ጣላትነትም ነው ያልኩት” ብየ፡፡
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ታዲያ እላቹህ ወያኔ ይህችን እንዳለች ቀዳላቹህና አማራ የምትለዋን አውጥቶ የትግራይ ሕዝብ የምትለዋን ተካላቹህና በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሕወሀት 40ኛ ዓመት የእንኳን አደረሳቹህ መልእክት ላይ አስገብቶ እንዲያነቧት አደረገ፡፡ አይገርማቹህም? አየ ወያኔ! በዚህ እንቋጭ አውቃለሁ ወያኔ በርካታ ለጆሮ የሚከብድ ጉድ እንዳለበት የሙስናውን የተለያየ ዓይነቱን ግፉና በደሉን ሁሉ እንዘክዝክ ካልን በዓመትም የሚያልቅ አይመስለኝም፡፡
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!