Friday, February 6, 2015

ጠቅላይ ሚነስትራችን ከእውነት ጋር ከሚጋጩ ስልጣን ቢለቁስ?

February 6,2015
ግርማ ሰ ይፉ
My Photo
የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ ቢሆኑ የሚሰሙት እና የሚያምኑት በኢቲቪ ወይም በሌላ የመንግሰት መገናኛ ብዙዓን የተላለፈ ነገር ነው፡፡ ሌላው እውነተኛ የመረጃ ምንጫቸው ደግሞ እንደ ትላንቱ (ጥር 28/2007) ጠቅለይ ሚኒሰትሩ ቀርበው እውነት ነው ብለው የሚነግሯቸውን ነው፡፡ ከዚህ ፍንክች ማለት ቢፈልጉም አይፈቀድም፡፡ ይህ እውነት ሊሆን የሚችልበት እድል የሚኖረው በሚዲያ በኩል ከፖለቲካ ነፃ የሆነ የመረጃ ምንጭ መሆን ሲችል እና ጠቅላይ ሚኒስትሩም የሚቀርብላቸውን መረጃ ከሰሩ የሚያጣሩ ቢሆን ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተነገራቸው ደረጃ እውነት ነው ያሉትን ለምክር ቤት አቅርበው፤ የራሳቸውን ፉከራ ጨምረው አስፈራርተውን ተሰናብተውናል፡፡ በዚያን ዕለት እውነት አለኝ ብዬ በምክር ቤት የነበርኩ አንድ ሰው ግን የተረዳሁት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የሚመሩን እንዲያውቁ በተፈቀደላቸው መረጃ ልክ መሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከእውነት ጋር ያጋጫል፤ እኔ እርሳቸውን ብሆን በዚህ ደረጃ ጠቅላይ ሚኒስትር ከምባል ስልጣን መልቀቅ እመርጣለሁ፡፡ ነጥቦቼን ላስቀምጥ፤

በሁለት ቦታ ሁለት መቶና ሶስት መቶ ሰው ተሰብሰቦ ጉባዔ አካሄደ የሚሉት ማብራሪያ ውሽት ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የአንድነት ጠቅላላ ጉበዔ አባላት ቁጥር 320 ከሆኑ ሁለት ቦታ ላይ ሁለት መቶና ሶሰት መቶ ሰው ሊሰበሰብ አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ የፖለቲካ እውቀት ሳይሆን መደበኛ የሂሳብ እውቀት ነው የሚጠይቀው፡፡ ለዚህ ደግሞ መሀንዲሱ ጠቅላይ ሚኒሰትር የሚቸገሩ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ ጠቅላላ ጉባዔ ያካሄደው ማን እንደሆነ መርምሮ ውሳኔ መስጠት ያልፈለገው ምርጫ ቦርድ ነው፡፡ ምክንያቱም ከጀርባ ሆኖ ለሳቸው መረጃ ለምርጫ ቦርድ ደግሞ መመሪያ የሚሰጥ አንድ አካል አለ፡፡ ስለዚህ ምርጫ ቦርድ ገለልተኛ አይደለም ስንል ህንፃውን ሳይሆን በህግ ከተሰጣቸው መተዳደሪያ ይልቅ በሌላ አካል መመሪያ የሚሰሩትን ሰዎች ነው፡፡ ይህን ማለት የሚያሰከስስ ከሆነ ለመከሰስ ዝግጁ ነኝ፡፡ አሁን እንደገባኝ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ቢሆኑ መረጃ ለማጣራት ፈቃደኛ ያለመሆኑ ሚስጥር እርሶም ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብት ያሎት አይመስለኝም፡፡

ሌላው የሚያሳዝነው የተሳሳተ መረጃ ደግሞ የአንድነት አባላት ክፍፍል በውጭ እና በውስጥ የሚመራ የተባለው ነው፡፡ በውጭ የሚመራው ቡድን ውስጥ ደግሞ እኔም አለሁበት፡፡ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን አንድነትን መደገፋቸው ምንም ክፋት ባይታየንም እኔ ያለሁበት አመራር ምርጫ መግባት ስንወስን በውጭ ያሉ የፈጠሩትን ጫጫታ፤ በተለይ ደግሞ የምናቀርባቸው እጩዎች ለምርጫ ውድድር የሚያስፈልጋቸውን ወጭ ለመሸፈን የሚያስችል የግል የፋይናንስ ቁመና እና በሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመሰብሰብ ያላቸው አቅም እንደ አንድ መሰፈርት ያሰቀመጥን መሆኑ ያለመረዳት አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም የሚለውን ብሂል ከማስታወስ ባለፈ ምንም ማለት አይቻልም፡፡ ይልቁንም በፓርቲው ውስጥ የምንከሰሰው እና ምርጫ ቦርድ ደጅ የሚጠኑት የአንድነት አባላት በኢኮኖሚም ሆነ በትምህርት ለዚህ መሰፈርት ስለማይመጥኑ ከዕጩነት ተገለልን የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ዘወትር የሚቀርብብኝ ክስ ፓርቲውን የተማረና የሀብትም ሊያደርገው ነው የሚለው ነው፡፡ ይኼ ደግሞ በምንም የውጭ ጥገኝነትን የሚያሳይ አልነበረም፡፡

ለማነኛውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጥር 28 መልዕክታቸው ግልፅ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድን እና ፍርድ ቤትን በተግባር በሚያሳዩት ሰማቸው ብንጠራቸው ለፍርድ እንደምንቀርብ ማስጠንቀቅ ነው፡፡ ደስ የሚለው የግል አስተያየቴ በሚል ነው የነገሩን፡፡ ይህን የግል አስተሳሰባቸውን እንደ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የምር የሚወስድላቸው ከተገኘ ሰሞኑን ፍትህ ሚኒስትር ክስ መመስረት ይኖርበታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተሰጣቸው መረጃ ትክክል የሚመስለው የፍርድ ቤት ጉዳይ በሚመለከት ላነሳሁት ጥያቄ የሰጡት መልስ ነው፡፡ ነገር ግን የፍርድ ቤቱ ም/ፕሬዝደንት ምርጫ ቦርድ አስተዳደራዊ ውሳኔ ባልሰጠበት ሁኔታ ክስ መመስረት አይቻልም ሲሉን፣ ምርጫ ቦርድ በፓርቲያችን ላይ የተለያየ ህገወጥ ውሳኔ እየወሰነ የነበረ ሲሆን ከዚህም አንዱ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት አልሰጥም፤ የጠቅላላ ጉባዔ ሪፖርት መርምሮ ውሳኔ በወቅቱ አልሰጥም እያለ የነበረ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ የፍርድ ቤት ውሳኔ የተረዳነው ቁም ነገር ፍርድ ቤት ምርጫ ቦርድ የሚሰጠውን የመጨረሻ ፖለቲካ ውሳኔ ያውቅ እንደነበረ ነው፡፡ የፖለቲካውን ውሳኔ የሚቃረን መረጃ መሰረት ያደረገ ውሳኔ እንዳይሰጥ ከለላ እየተደረገ መሆኑ ግልፅ ሆኖዋል አሁን ባለንበት ሁኔታ፡፡ የሚገርመው አሁን ፍርድ ቤት ሲኬድ በአስተዳደራዊ ውሳኔ በፖሊስ ሰራዊት የተቀማነውን አንድነት አትወክሉም ልንባል እንደምንችል ነው፡፡ ይህ ነው እንግዲ ነፃ ፍርድ ቤት ካላላችሁ ለፍርድ ትቀርባላችሁ የምንባልበት ስርዓት፡፡
ጠቅላይ ሚኒሰትር ሀይለማሪያም ከመረጃ እጥረት ይሁን አውቀው በድፍረት ሊመልሱት ያልቻሉት “የምርጫ ቦርድ ህገ ወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔ ለማሰፈፀም የፖሊስ ሀይል ማስማራትና ቢሮ የመዝረፍ መብት ማን ነው የሰጠው?” የሚለውን ጥያቄ ነው፡፡ የአንድነት አባላት የሆኑ በበሩ እንዳያልፉ በፖሊሰና ደህንነት ኃይሎች ጥበቃ የሚደረግለት አዲሱ ሹም “የአንድነት ፕሬዝደንት” አቶ ትዕግሰቱ አጉሉ በሚዲያ ቀርቦ ምርጫ ቦረድ ለእኔ ስጥቶኛል ብሎ የመሰከረውን ሀቅ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ምርጫ ቦርድ ምን ያድርግ ሊሉን አይችሉም፡፡ ምርጫ ቦረድ ኢህአዴግ እንዲያሸንፍ የታዘዘውን ሁሉ መፈፀም ነው፡፡ በምክር ቤት መቋቋም ነፃነትን የሚያረጋግጥ ቢሆን ኖሮ…… ሌላ ጊዜ በዝርዝር እንመለስበታለን፡፡
ለማነኛውም ጠቅላይ ሚኒስትራችን እውነት ነው ተብሎ በተነገራቸው መረጃ ልክ ለምክር ቤት አባላት እና ለኢትዮጵያ ህዝብ እውነት ነው ያሉትን አስተላልፈዋል፡፡ ከዚህ ውሳኔ የተረዳሁት እርሳቸው የሚመሩት ካቢኔ በዚህ ጉዳይ ውስጥ ከስረ-መሰረቱ እንዳልተሳተፈ ነው፡፡ በመጨረሻ በግንባር የተገናኘን እለት የተረዳሁት ይህን ነበር፡፡ ነገር ግን ለማስተካከል አቅም ይኖራቸዋል ብዬ እምነት ነበረኝ፡፡ መረጃ በተሳሳተ ተሰጥቷቸው እንዳይሳሳቱም መረጃ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር በገቡልኝ ቃል መሰረት እንድንገናኝ ያደረኩት ሙከራም ያልተሳካው  የተለየ መረጃ ማግኘት ስለማይፈልጉ ሳይሆን ስለአልተፈቀደላቸው ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሻለሁ፡፡ ለዚህ ነው “ከእውነት ጋር ከሚጋጩ ስልጣን ቢለቁስ?” የሚል ሃሳብ መሰንዘር የፈለኩት፡፡

ቸር ይግጠመን!!!!!! 

ETHIOPIA : DICTATORSHIP WRESTLED BEFORE DEATH,OPPOSITION PARTY HOPES TO WIN IN THE NEXT ELECTION

February 6,2015
Addis Ababa ( DIPLOMAT.SO) – According to some Ethiopian and Eritrean websites , A Week ago, the opposition party Unity for Justice and Democracy (UDJ)- widely known by its Ethiopian name ‘Andenet‘ – was brimming with confidence that it will contend for power in the national elections in May 2015. Of course, there was an uphill battle, and that was to make sure the elections would be free and fair.
The-Unity-for-Democracy-and-Justice-Party-said-the-country-is-heading-toward-“absolute-dictatorship”-under-the-ruling-party
The Unity for Democracy and Justice Party said the country is heading toward “absolute dictatorship” under the ruling party

What Andenet’s young and charismatic leaders may not have anticipated was that the ruling party and its arm, the ‘Election Board’, would cut Andenet in two, then discard the real, authentic Andenet group off the precipice, while preparing the puppet for the election.
Andenet was not only popular but also an organization that transcended the politics of ethnicity and had drawn members from all corners of the country. And this was a threat to the ruling TPLF, a pioneer of the politics of ethnicity and hate with stand-by program for the disintegration of the country in the event TPLF loses power.
Now Andenet is history. If there is any group that claims to be ‘Andenet,’ it is the puppet hatched by the ruling party.
On Tuesday, former leaders and members of Andenet Party announced at the Semayawi Party HQs that they have officially joined Semayawi because there was little or no difference in their political programs.
TPLF committed a crime but every dark cloud has a silver lining, and that is TPLF unintentionally brought two same-minded organizations into a ‘merger.’ The struggle against tyranny continues.
For more news and stories, join us on Facebook,Twitter and Subcripe ourYoutube Channel,Or contact us through our Emails : info@diplomat.so,adv@diplomat.so,diplomatnewsdesk@gmail.com
Source- diplomat.so

The Upcoming May 2015 Ethiopian General Election and Ethiopian-American Action

February 6, 2015
by Dallol Kiros
Two years ago I participated in the “Ethiopian American Convention” that was held in Washington Middle School in Alexandria, Virginia. Throughout the 2012 November election, Loudon County which is not far from where most Ethiopia American reside in northern Virginia was a battle ground. More than any time Ethiopia-American voters in swing states like Virginia has mattered and candidates should put into consideration the demand Ethiopian American constituents are making.The Upcoming May 2015 Ethiopian General Election
On 2014 mid-term election, the democratic candidate Senator Mark Warner won by small margin 49 percent versus 48 percent for the republican candidate Ed Gillespie. Historically there is a low voters turnout in mid-term election and let’s assume that most Ethiopian American did not cast their vote. But that would not be the case in upcoming 2016 presidential elections.
Therefore, Ethiopian American should follow suit on what they have started two years ago in November. The ‘Ethiopian American Convention’ that was held on Sunday October 14, 2012 “Vote Free Ethiopia’ and other civic organizations was the beginning of that process. Ethiopian community need to articulate.
When it comes to human right in Ethiopia, the Obama administration have not made a strong condemnation let alone take serious action. To our surprise in the dawn of the November mid-term election in November 2014, the US State Department has made a press releases concerned about the recent sentencing of journalist Mr. Temsegen Desalegne, which is was a little late in getting Ethiopia Americans to cast their votes for a democrat. http://www.state.gov/r/pa/prs/ps/2014/10/233556.htm
The Ethiopian government is tirelessly working with Washington lobbyist and spending millions. Hiring firms such as DLA Piper and Good Works International , chaired by Andrew Young former UN ambassador under President Jimmy Charter. According to Corporate watch dog few of the favourite African government lobbyists are Herman Cohen, former State Department official under president George Bush.http://www.corpwatch.org/article.php?id=98
On the flip side the Ethiopian-Americans have put at the bay the TPLF operatives in most major United State cities and Western Europe. One group that works tirelessly is the DC task force, is a group that consists of human right activist such First Hijarh Foundation and opposition political members from EPRP, Ginbot Seven and other human right activists.
Because of effective group such as DC task force, the TPLF regime has not been able to rally the Ethiopian Diaspora for any public meeting and fund raising events. No government official can freely mingle among the Diaspora community without being confronted by DC area task force,
All over the Western Europe, including Norway, Sweden, Canada and Australia, Ethiopian government official are confronted by protestor. Video of egg throwing on Ethiopia Ambassador in Sweden have surfaced all over the social media.
But this time around the “ the DC task force” has made a very bold move, removing Ethiopian national flag with TPLF/EPRDF rebel group emblem with the true Ethiopian flag at Ethiopia Embassy in Washington DC. This has been a big blow for Ethiopian government and regime supporters. The Prime minster of Ethiopia was so aggravated had to address the rubber stamp parliament about the group naming the participants Eritrean government agents.
A video has surfaced all over the media outlets. Showing the Ethiopian embassy security attaché Mr. Solomon Tadesse Gebre Sellasie, a former TPLF guerrilla fighter was caught on camera shooting point blank at unarmed protesters and activists Mr. Mekonnen Getachew inside the embassy grounds.
The resistance against the regime is at all time high, especially in the Washington DC metro area where large Ethiopian-Americans population reside in the North America. The Ethiopia bond purchase program is a total failure. The Ethiopian government TV channel is off the cable channels in DC metro area. Whereas more than any time in past 23 years, the Ethiopia population in Ethiopia and overseas with access to radio and TV are getting their news from the Diaspora financed TV and radio program called Ethiopian Satellite Television (ESAT).
VOA-Amharic, on time popular outlet has been accused by civic and oppositions forces for making favourable reporting for the Ethiopia regime and has lost its creditability among its listeners. In which the chief of horn African program Peter Peter Heinlein as Chief of the Horn of Africa was demoted for deliberate distortions and professional misconduct. The allegation of misinforming by his subordinate Henok Semaegzer on Ethiopia prime minster cancel award by Azusa Pacific university was first aired by ESAT radio.
The TPLF regime is also trying very hard to silence dissent among Ethiopian-American with a total failure. After the Ethiopian communication minister Rewdan Hussien was confronted and humiliated at Arlington’s Marshal store on 08/07/14 by two Ethiopian activists, the regime took the case to Arlington court where the prosecutor decided not to prosecute the case” Nolle Prosequi” against Mekonnen Getachew, the same activity from the Ethiopian Embassy flag incidence. Similarly, a German court in Munich had dropped the charge made against Tibebu Assefa for protesting against bond purchase program held by TPLF operatives for the Grand Renaissance Dam building.
Few months ago Ethiopian Americans have launched a task force to bring to justice 70 TPLF high ranking and Ethiopia government official that are accused of war crimes, crimes against humanities, genocide, extrajudicial killing, torture, illegal imprisonment, rape, corruption, extortion and embezzlement. The spoke person for the task force activist Mr. Tamagene Beyene have announced there is an effort with U.S law enforcement agencies and human right organizations.
On its official website http://www.masreja.com/ the task force have listed Ethiopian officials and security officers and army officers according to their crimes committed, at the top of the list Mr. Abay Teshaye Minster of Federal Affairs, Dr. Debrestsion Gebre-Michael Deputy prime mister and in charge of Ethiopian National Intelligence and Security Service, Mr. Tesgay Berhe National Security Affairs Adviser Minister , Mr Abay Woldu president of the TPLF and the Tigray Regional State, Mr Arkebe Oqubay the prime minster policy advisor and former Addis Ababa mayor followed by the current prime minster of Ethiopia Mr. Hailemariam Desalegn, accused of crime when he was a President of the Southern Nations, Nationalities, and People’s Region (SNNPR) from November 2001 to March 2006.
Ethiopian in Sweden has also submitted a charge against 13 Ethiopian government and Defense Force officials that are also on the list above to the Swedish International Criminal Tribunal and Courts.
More than any time the Diaspora opposition forces are organized, coordinated, committed and above all aggressive. But with all this success stories, the Ethiopia- Americans have been unable to influence the US policy toward Ethiopia.
The US together with has its strong board of directors presentence at the World Bank, has continued to write a blank check.
As recently as September 2012, the World Bank Group have mobilized US$600 million in development financing for the third phase of the Promoting Basic Services (PBS III). These are the type of programs they need to be identified. Ethiopian- American should chose a candidates for United State Senate and congress that understand their cause only vote for those candidates, preferably this time around republican candidates.
The World Bank loans are literally providing a budget support to the government of Ethiopia, which means the Ethiopian government is only accountable to donor governments, and not to the Ethiopian people.
Ethiopian-American should not be requesting that that the World Food Program’s US humanitarian assistance be stopped to Ethiopia either, but for US government to make sure food aid and humanitarian assistance are not diverted, or used to coerce the Ethiopian peasants for political gain.
Ethiopian-American that voted for Obama in good faith and had received in return a flat out insult by Ambassador Susan Rice, calling the Ethiopia American voters “Fools” in Addis Ababa on the late Prime Minister Meles Zenawi funeral in Addis Ababa. This is a strong indication that Ethiopian- American vote by Obama administration has been taken for granted.
In 2016 presidential election, the Democratic Party should not be getting the usual support it gets from Ethiopian American especially in Washington DC metro area.
Ethiopian-Americans should indentify a candidate that will serve the interest of the opposition Ethiopia American and endorse and vote for that candidate.
This time around the opposition Diaspora and the Ethiopian-American at large need to vote for a republican candidate. Ethiopian Americans should endorse and announce their choice on the local media and news outlets. The candidate should back its promise with strong actions.
Following the footsteps of African Americans that predominately votes for the Democratic Party, Ethiopian-American have been voting for the Democratic Party, this needs to change. For the upcoming 2016 presidential election, what Ethiopian-American should be demanding from both the Republican and the Democratic parties is for congress to stop writing a blank check to the government of Ethiopia. Specially, candidates in swing states like Virginia should realize Ethiopia- American vote matters.
Ethiopian-American should demand that the US government to pressures for the release of all political prisoners and journalists and give room for the Ethiopian opposition to organize freely to mobilize its supporter and raise funds, without being persecuted. They should request that the US administration make a strong statement backed by action. ESAT and Ethiopian opposition groups and civil organization coordinate their effort to mobilize and frame the agenda.
On September 25, president Obama meet prime minster Hailemariam Desalegn of Ethiopia who was also at New York to attend the 68th United Nations General Assembly. The Obama administration officials including Susan Rice and Secretary of State Kerry were present. In which, President Obama spoke in the interest of United States peacekeeping in Africa, Ethiopia being a hired gun. At least in front of the camera, good governance, democracy, corruption, the jailing and persecution of journalist and the Ethiopia oppositions were not part of his statement.
Going forward, candidate especially in swing states should not just award their votes to candidate just because they are running on the Democratic Party platform.
Ethiopian-Americans need to articulate there demand and most importantly educate voters in their community about make specific demands. Ethiopian Americans need to support only a candidate that can address their specific demand.
The 2016 elections would be the greatest one time opportunity for Ethiopian Americans to get the attention of the US legislative body.
There are groups that have no faith in the US policy maker and believe Ethiopia’s destiny should not be with the next US administration or the democratic or republic party, but Ethiopians democratic aspirations. That would flatly reject the above notion and suggestions, it does not matter who Ethiopian American should vote in the November 2016 and upcoming elections. Rehearse the famous quote from former American foreign secretary Henry Kissinger “America has no permanent friends or enemies, only interest”
By May 2015 Ethiopian general election if the Obama administration does not have a strong stance against the TPLF regime. http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2015/02/03/u-s-policy-ethiopia-a-failed-state-documentary/ The current Ethiopia- American policy must have an alternative plan toward the Ethiopia regime. The 2014, USAID and USADF foreign assistance program for Ethiopia excluding multinationals, military assistance and emergency food assistance disbursed $417 million.
The Ethiopia Diaspora have more financial leverage than the US foreign assistance program to Ethiopia. Especially for groups that believe in peaceful struggle this should be and encouraging sign. A simple action such as economic leverage by suspending remittance for 2-3 month, provided that Diaspora family members are willing to make sacrifices, is an effective method to bring the regime to its knees.
This will have one time impactful pressure on TPLF regime that is try hard to keep afloat. Ethiopian Ministry of Finance government annual Budget for 2014 is $8.92 billion of which $3 to $4 billion is financed by remittance. The Ethiopian economy is stretched beyond it means, there It is a strong indication that the National Bank Reserve is depleting with evidence that the government is cash strapped.
Group such as “DC task force” is effective but the struggle needs more commitment.

Thursday, February 5, 2015

የትግራይ ሕዝብንና የኢትዮጵያ ፓሊስን በኢትዮጵያዊያን ለማስጠላት የሚደረገው ጥረት ከሽፏል!

January 5,2015
ህወሓት ንፁሀንን ለመደብደብ የሚያበቃ በቂ ክፋት ያለው ልዩ ጦር ሲያሰለጥን ቆይቷል። ይህን ልዩ ጦር የፓሊስን መለያ እያለበሰ ነውረኛ ሥራዎችን እንዲሠራ በማድረግ በአንድ በኩል ንፁሀንን የመጉዳት በሌላ በኩል ደግሞ ፓሊስን በሕዝብ የማስጠላት መንታ ግቦችን ለማሳካት ተጠቅሞበታል። ይህ ልዩ ጦር በአለፉት ጥቂት ሳምንታት ባዶ እጃቸው ለተቃውሞ በወጡ ነብሰ ጡር ሴቶች ላይ ሳይቀር ባሳየው ጭካኔ፣ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ ባደረሰው ድብደባ መጠን እና ባካሄደው የግለሰብ ንብረቶች ዝርፊያ የሥርዓቱ ባህርይ ፈጽሞ ከሰውኛ ተፈጥሮ እየወጣ እንደሆነ አመላካች ነው። በእነዚህ ድብደባዎች ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስባቸው ተደርጓል። በትግራይ ተወላጆች ላይ የተለየ ትኩረት የተደረገው በደብዳቢዎቹ የግል ውሳኔ ሳይሆን ከበላዮቻቸው በተሰጠ ትዕዛዝ ነው ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
በአርበኞች ግንቦት 7: እምነት መሠረት የፓሊስ ከፍተኛ አዛዦች ህወሓቶች ቢሆኑም አብዛኛው የሠራዊቱ አባል በህወሓት ዘረኛና ፋሽስታዊ አገዛዝ የተማረረ፤ የሥርዓቱ መለወጥ የሚፈልግና ሥርዓቱን ለመለወጥ የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ኃይል ነው። ስለሆነም ህወሓት የተለየ ጦር አሰልጥኖ የፓሊስ ልብስ በማልበስ ነውረኛ ወንጀል በማሠራት ፓሊስን ለማስጠላት የሚያደርገው ሴራ ሊጋለጥ ይገባል ብሎ ያምናል። የፓሊስ ሠራዊት አባላትም በስማቸውና በደንብ ልብሳቸው የሚደረገውን ደባ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እንዲያጋልጡ አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ህወሓት እንደሚያስበው እና የኢትዮጵያም ሕዝብ እውነት አድርጎ እንዲቀበለው እንደሚፈልገው የትግራይ ሕዝብ በጅምላ የህወሓት አፍቃሪና ደጋፊ አይደለም። እንዲያውም በተፃፃሪው ህወሓት ከትግራይ ተወላጆች ልብ እየተነቀነ ነው። የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን/ደምህት) ከትግራይ የበቀለ፤ ህወሓትን በአመጽ ለመፋለም የቆረጠ ኃይል ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በትግራይ ውስጥ ብዙ ደጋፊዎች ያሉት መሆኑ የምናውቀው ሀቅ ነው። አረና ትግራይ ህወሓትን በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የተነሳ ተሰሚነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ የመጣ እና አቶ አብርሀ ደስታን የመሰለ ወጣት ኢትዮጵያዊ የፓለቲካ መሪ ያወጣ ድርጅት ነው። ህወሓት አንድነት ፓርቲ ላይ የመረረ አቋም ከወሰደባቸው ምክንያቶች አንዱ በትግራይ ውስጥ ያለው ተቀባይነት በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ነው። ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጅምላ ለማጣላት የሚያደርገው ጥረት ማክሸፍ ይኖርብናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 ያምናል፤ ለዚህም ተግቶ ይሠራል። አርበኞች ግንቦት 7 ከትግራይ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር ፀረ ህወሓት ትግል በትግራይ ውስጥ መቀጣጠል ይኖርበታል ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ትግራይ የህወሓት መቀበሪያ የመሆኗ ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በዘንድሮው የ2007 የሴራ ምርጫ አማካይነት ተድበስብሰው የመጡ እነዚህ ሁለት ክፋቶች ማለትም ፓሊስን በሕዝብ ማስጠላት እና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የዲሞክራሲ ወገንተኞችን ለይቶ ማጥቃት ከበስተጀርባቸው ያዘሉት እኩይ ዓላማ መጋለጡ መንገዳችን ያጠራልናል ብሎ አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። በአንድነትና በመኢአድ የተፈፀው የድርጅትና የንብረት ዘረፋም የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኝ ግልጽ ነው፤ ነገ ተመሳሳይ ነገር በሰማያዊ ፓርቲም ላይ ይፈጽም ይሆናል።
በመሆኑ ከ2007 የሴራ ምርጫ ትሩፋቶች በትግራይ ሕዝብና በፓሊስ ሠራዊት ጀርባ የሚደረገው ደባ መጋለጡ ነው። ይህ ድል ጽኑ መሠረት እንዲይዝ ህወሓትንና የትግራይን ሕዝብ የመነጠል እና ፓሊስ የሕዝብ አጋር መሆኑን የማረጋገጥ ሥራዎችን አጠናክረን መሥራት እንዳለብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

Wednesday, February 4, 2015

ፍትህ እና ርትዕ ለሁሉም ( ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ)

        

  በኢትዩጵያ ውስጥ ከሁለት አስርት አምታት ወዲህ በህዝብ ላይ በጣም  እየተንሰራፋ ስለሚገኘው የዘረኝነትን ተህዋስ ሳስብ በአንድ ወቅት በእስራኤል ያሉ አይሁዳውያን ያደረጉት አድሎ እና ወገናዊነት በአዕምሮዬ ይመጣል። ሁሉም ለፈለጉት ብቻ ነበር ጥብቅና የቆሙት።የሌላውን ሀዘን እና መከራ ከመጤፍ ሳይቆጥሩት በርባን!በርባን!በርባን! እያሉ በንጉሱ በር ላይ የራሳችው ወገን ብቻ እንዲፈታ አቤቱታቸው ታልቅ ነበር። ኢየሱስን አሳልፈው  ለፍርድ ሰጥተውት የራሳቸው ወገኔ የሚሉት እንዲፈታ በታላቅ አድማ ድምፃቸውን ያሰሙ ነበር።   በዚያን ጊዜ በርባን የሚባል ታወቂ እስረኛ ነበራቸውና  መፈክራችው ሁሉ እሱን የሚያወሳ ነበር።  በወቅቱ ፈራጅ ወደሆነው ቀርበው አድሎ የተሞላበት ጥያቄያቸውን አቀረቡ ገዥውም ጥያቄውን ከሰማ በኋላ እንዲህ አላቸው፥ ከሁለቱ ማንኛቸውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ አላቸው? እነርሱም በርባንን አሉ።   

       ይህ ነው አድሎ። ይህ ነው መለያየት።  ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? አሁን የደረስንበትም   ዘመን ይህንን መስሏል ። ሁሉም ቢጤዬ ለሚለው ለራሱ ፈርጆ ማድላቱ እና ለታሰረበት ሲጮህ የሌላውን ወገን አልባ መሆን ማታሰርና መንገላታት በስራህ ያውጣህ ጆሮ ዳባ ልበስ ካለው የአንድነት እና የመቀባበል ልብ ጠፍቷል ማለት ነው።           

  እንግዲያስ ትግሉ ለማን ነው?ለግለሰብ?ለፓርቲ?ለብሔራችን? ወይስ ለኢትዮጵያ ? ሚዛኑን ሳታዳሉ ምላሽ ስጡብት ። ተለያይቶ በየሰፈራው ለራስ ወግኖ እታገላለሁ ማለቱ የወያኔን እድሜ ቢያረዝም እንጂ ለኢትዮጵያ  ምንም  አይበጃትም።ወያኔ ለራሱ ብቻ ወግኗልና 23 አመታት አስቆጥሮ ሀገሪቷን ወደሚቀጥለው ረመጥ ይዞ 24 ለማለት የብቀላ አየሩን ወደውስጥ እየሳበ ነው። ሌላ የጨለማ ጉዞ።

                   እርስ በርሷ የምትለያይ መንግስት አትጸናም እንደተባለ ኢትዮጵያን በሁሉ አቅጣጫ ሸንሽኗት ይገኛል። ጎሳው፣ ክልሉ ፣ ብሔሩ፣ ፖለቲካው፣ የእምነት ተቋማቱ፣ ሚዲያው ወ.ዘ.ተ. . .  በሌላውም የኢትዮጵያ ጉዳይ ሁሉ ይህ አስከፊ የወያኔ የመለያየት መርዝ እንደ ተስቦ በሽታ በምድሪቷ ላይ ተረጭቷል። ማምከኛው ደግሞ አንድነት ብቻ ነው። የተባበረ ክንድ!           

        ወያኔ ኢትዮጵያን በአንድነቷ ሊገዛት ስለማይችል ከሰሜን አንስቶ ደቡብ ድረስ ከምስራቅ ጀምሮ እስከ ምእራብ ገንጥለህ እና ለያይተህ ግዛ በሚለው መርሁ ትውልዱ ቤተሰብ ሆኖ ሳለ እርስ በእርስ እንዳይቀባበል የጎጠኝነት እና የባይተዋርነት መንፈስ እየዘራበት ይገኛል። ውጤቱም ደግሞ እየተስተዋለ ነው። ይህን ለሚያህሉ አመታቶች በአንባገነንነት ምድሪቷን ሲመዘብር እና ወያኔ የራሱን ሆድ ሲያጠረቃ ከተጠቀመባቸው የውንብድና እና የማጭበርበርያ ስልቶቹ መሀል አንደኛው ኢትዮጵያውያንን እንደ ቅርጫ አጥንት መከትከት እና መቆራረጥ ነው። እናም ይህ የመለያየት መተት እና አዚም ብዙዎችን ለያይቶ ለኢትዮጵያዊነት ሳይሆን ለፓርቲ፣ ለግለሰብ፣ ለክልል፣ ለጎሳ ፣ ለእምነት ቤት፣ ወ.ዘ.ተ. . . ዘብ መቆም ብዙ ቦታ እየተስተዋለ የመጣ ጉዳይ ሆኗል ። ይህም በየስፍራው ያለው ልዩነት ወያኔን በግፍ አገዛዙ እስካሁን እንዲዘልቅ  አግዞታል።       

        በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የጭቆና አገዛዝ የነዳዳቸው ታጋዮች ጥቂቶች  አይደሉም ። በገዢው ቡድን የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ አማካይነት ደብዛቸው እና ስማቸው የጠፉት በብዙ ሺህ ይቆጠራሉ። ለአመታት ያህል በአሰቃቂ ሁኔታ ከታጎሩበት እስር በነጻ እንኳን ቢለቀቁ የአዕምሮ፣ የአካል፣ ህሙም ሆነው አሊያም ከተቀበሉት ሰቆቃ አንጻር በመሀላ ወያኔን አትድረስብኝ አልደርስብህም በማለት በአይነ ቁራኛ የሚጠበቁ ይሆናሉ።  

                ወያኔ ስላሰራቸው ሲናገር ወንጀልኞችን እና አሸባሪዎችን እንጂ ማንንም ጋዜጠኛም ሆነ የፖለቲካ እስረኛ የለኝም ማለቱን ከእውነታው ጋር ሲነጻጸር አንገት የሚያስደፋ ውሸት ሆኖ እናገኘዋለን።ፀሀይ ያሞቀው የውሸት ቋንጣ።ነገር ግን ስለታሰሩት ያለው እውነታ ሌላ ነው። በፀለምት፣ ወልቃይት ፀገዴ፣በቃሊቲ፣ ሸዋ ሮቢት፣ ዴዴሳ ፣ብርሸለቆ እና ዝዋይ የንፁህ ኢትዮጵያውያን ደም እምባ በምድሪቷ ላይ ድምፁን እያሰማ ይገኛል።  እስር ቤቶቹ ሁሉ በጋዜጠኞች እና ሀገር ሊቀና የሚችል እውቀት ባካበቱ ምሁራን ታጭቋል። ስለዚህ የታሰሩት ኢትዮጵያውያን ናቸው። የታሰሩት ሁሉም ናቸው! ከሁሉም ናቸው! ለሁሉም ናቸው። በሀገራችን ላይ ማንኛውንም ነገር በቀናነት ለማድረግ መብት ከሌለን ሀገር አልባ ነን ወይም ታስረናል ማለት ነው። በእስር ቤት ውስጥ አርፈህ ከተቀመጥህ ትበላለህ፣ ትተኛለህ ፣ትፀዳዳለህ ሌላ ትርፍ እርምጃ ለማድረግ ሀሳብ እንዳለህ ከተነቃብህ ፊደል ያልቆጠሩ የወያኔ ስልጡን ገራፊዎች ይገለብጡሀል። በከተማ ውስጥ ሰለተቀመጥህ ነፃ ነህ ማለት አይደለም አሊያም ነፃ መሆንህን ማረጋገጥ ካስፈለገህ እውነቱን በአደባባይ ቆመህ ተናገር ያን ጊዜ የት እንዳለህ ይገለፅልሀል። ለዚህ ነው ኢትዮጵያ ታስራለች ብለን የምንናገረው።  የእኛም  መለያየት  ወያኔ እየቆመረ እንዲቀጥል አስችሎታል።

          በወያኔ ግዞት ውስጥ በስቃይ ስላሉት ስናስብ ወደ አዕምሮአችን የሚመጡት ኢትዮጵያዊያን ናቸው ወይስ ግለሰቦች? ከታሰሩት ውስጥ የነማን ይፈቱ? የየትኞቹ የብሔር ነፃነት ታጋዮች አሊይስ የቱ ተቃዋሚ ፓርቲ? ቀደምት የነበረው ወይስ መጤው? ለማን አቤት እንበል? መልሱ ግራ የሚያጋባ አይደለም። ለኢትዮጵያውያን ነው መሆን ያለበት። በአንድነት፣ በመጣመር፣በመያያዝ ለኢትዮጵያ ሉአላዊነት ለአንድ አላማ መሰለፍ።

             ከቶውንም ኢትዮጵያዊ ባርያ ሆኖ አያውቅም። ሀገራችን በጄኔቫ የዓለም መንግሥታት ማህበር ጠቅላላ ስብሰባ ላይ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር መስከረም28 ቀን 1923 የመንግሥታቱ ማህበር ሃምሳ ሰባተኛዋ አባል ሆና መመዝገቧ በይፋ ታወጇል ።በዓለም መንግሥታት ማህበር መድረክ የክብር ቦታ ተሰጣት።ታዲያ ዛሬ ላይ ቆመን ይህንን የዚያን ዘመን ጀግንነት ስናስታውስ በፍፁም ቅንነትና የዋህነት የተሞላ ዕምነታቸውንና ተስፋቸውን ስናነብ የደማቸው ጩኽት እያስተጋባብን ማናችን የዚህ ዘመን ትውልድ ነን የዜግነት ግዴታን ቢያንስ ከእነሱ በተሻለ ለመወጣት  የሞራል ብቃት ያለን?           

    ዳር ድንበር የተጠበቀበት ከፋሺስቶች ጉልበት በላይ የተጎለበተበት ያንን  የመሰለ ለጥቁሩ ህዝብ ኩራት ሆኖ ወራሪው በተራው ያፈረበት እና ያጎነበሰበት ክንድ አሁንም በአንድነት አዲሱ ትውልድ ወያኔን ድባቅ ለመክተት ሊቀሰቀስ ይገባል።  ለፋሺስት ፀጉረ ልውጥ ወታደር ያልተበገረ ወኔ አሁንም በአንድነት በታላቅ እንቢተኝነትን እና አመፅ  የተሞላ ትግል  ያሻዋል። እንሔድብት ዘንድ ወያኔ አንጋዶ ያሰመረልን መስመር አሰናከለን፣በተነን፣ለየን እንጂ ለእድገት አላራመደንም።ስለዚህ በአንድነት በቁጣ እንነሳ ።

               ድምፃችን ይሰማ!!! ለአንዱ ብቻ አይደለም ለሁሉም ፍትህ እና ነፃነት  ይገባል። ሰሜኑ ፣ ደቡቡ፣ ምዕራቡ እና ምስራቁ በየክልሉ ያለው የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ሲደመር ነው ኢትዮጵያ የሚባለው።ስለዚህም ለሁሉም መጮህ አለበት። የታሰሩት የፖለቲካ እስረኞች ሁሉም ይፈቱ። በአንድነት ለአንድ ትግል ለአንዲት ኢትዮጵያ እንቁም።  

               ወያኔ ኢትዮጵያን ሊለቅ ይገባል።ሀገርን ቀምቶ በህዝብ ከርሰ ልብ ውስጥ ያለውን ሰላም ስርቆ ደስታን ወደ ሀዘን የለወጠውን የኢትዮጵያ ጠላት ለመፋለም  የጀግና ልጅ ሆይ ተነስ ከወያኔ ረገጣ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ያባቶችህ ወኔ እና አደራ ይጥራህ። 

ድል ለኢ ት ዮ ጵ ያ  ህዝብ !!!!                       
እናቸንፋለን!!!  Biniam Gizaw  Norway

Tuesday, February 3, 2015

ሰበር ዜና የአንድነት አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ

January 3,2015
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስታወቁ፡፡
በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር የፕሮግራምም ሆነ የስትራቴጂ ተመሳሳይነት ወዳለው ሰማያዊ ፓርቲ ተቀላቅለው ሰላማዊ ትግላቸውን ለመቀጠል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
መግለጫውን የ‹ቀድሞው አንድነት ፓርቲ› አፈ ጉባዔ የነበሩት አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔው አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እንዲሁም የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ሌሎችን በመወከል ሰጥተዋል፡፡
‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል በመግለጫው ላይ የተወከሉት አዲሶቹ የሰማያዊ አባላት፡፡ በዚህ መሰረትም በርከት ያሉ አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲ የአባልነት ፎርም ሞልተዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ወደ ሰማያዊ ቢሮ ባቀኑበት ወቅት ፖሊስ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ድረስ በመግባት ‹‹በሰማያዊ ስም መግለጫ የሚሰጡ አካላት እንዳሉ ሰለሰማን ነው›› በሚል ለፓርቲው አመራሮች ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡

Monday, February 2, 2015

ወያኔ የጋረደብንን የመበታተን አደጋ ለማክሸፍ ትግላችንን ማቀናጀትና በአንድ የአመራር ጥላ ሥር ማሰባሰብ ወቅቱ የሚጠይቀን እርምጃ ነው

February 2,2015
ትግራይን ከተቀረው የአገራችን ክፍል ለመገንጠልና የትግራይን ሪፑፕልክ ለማቋቋም ራዕይና ተልዕኮ ሰንቆ የዛሬ 40 አመት ደደቢት በረሃ ውስጥ የተፈጠረው ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ፡ በለስ ቀንቶት የመንግሥት ሥልጣን ከተቆጣጠረ ወዲህ፡ በስሙ የሚነግድበትን የትግራይን ህዝብ ጨምሮ በአገራችንና በመላው ህዝባችን ላይ የፈጸማቸው ወንጀሎችና ያደረሳቸው ሰቆቃዎች ተዘርዝረው የሚያልቁ አይደሉም::
ከነዚህ ወንጀሎች ሁሉ የከፋውና ምናልባትም የሚቀጥለውን ትውልድ ጭምር ዋጋ ያስከፍላል ተብሎ የሚፈራው ምዕራባዊያን ቅኝ ገዥዎች አህጉራችን አፍሪካን በተቀራመቱበት ወቅት የአገዛዝ ዘመናቸውን ለማራዘምና ቅኝ የገዙዋቸውን ህዝቦች ሃብትና ንብረት ለመዝረፍ እንዲመቻቸው የተጠቀሙበትን የከፋፍለህ ግዛ ፖሊስ በምድራችን ተግባራዊ በማድረግ ለዘመናት የተገነባውን የህዝብ አንድነትና የአገር ሉአላዊነት ሊያናጋ በሚችል መልኩ በዘር፤ በቋንቋና በሃይማኖት ተከፋፍለን የጎሪጥ እንድንተያይ የተፈጸመብን ደባ ነው::
በዚህ ደባ ምክንያት ዛሬ በአገራችን ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሆኔታ ኦሮሞነት፤ ሱማሌነት፤ ትግሬነት፤ አማራነት ፤ ስዳማነት፤ አፋርነት፤ ወላይታነት ፤ ከምባታነት ወዘተ ከዘግነት በላይ ገዝፎ የማንነት መለያና የፖለቲካ፤ የኢኮኖሚና ማህበራዊ መብቶች መሠረት ሆኖአል:: በዚህም የተነሳ የኦሮሞ ከብት አርቢ ለከብቶቹ ግጦሽ ፍለጋ ወደ ሱማሌ ድንበር ከተሻገረ እንደ ባዕድ ተቆጥሮ ተኩስ ይከፈትበታል፤ አፋር ወደ ኢሳ ከተሻገረ ይገደላል፤ ለቤነሻንጉል በተከለለ ክልል የሰፈረ የአማራ አርሶ አደር የደከመበትን አንጡራ ሃብት ተቀምቶ ይባረራል፤ አኝዋክ ለዘመናት ተከባብሮና ተቻችሎ ከኖረው ከኑዌር ወንድሙ ጋር እንዲጋጭ ተደርጎ በገላጋይነት ሥም የፈደራል ፖልስና የጸጥታ ሃይል በጅምላ እንዲጨፈጭፈው ይፈረድበታል :: በመልካም አስተዳደር እጦት የደረሰበትን መከራና ስቃይ አብሮ ሲጋፈጥ የኖረው የወልቃይት ጠገደ ህዝብ አንተ አማራ አንተ ትግሬ በሚል የዘር ክፍፍል ለመገዳደል ካራውን ስሎ ተቀምጦአል :: ይህ አልበቃ ብሎም የአንድ ብሄር አባላትን በጎሳ ሸንሽኖ የጉጂ ኦሮሞ ከአርስ ወንድሙ ጋር ደም እንዲቃባ ተደርጎአል:: የኦጋዴን የተለያዩ ጎሳዎችም ላይ እንዲሁ::
ወያኔ በጉልበት የጫነብን የመከፋፈልና የመለያየት አደጋ አንድ ቀን ሲያበቃ የነጻነት ብርሃን ፈንጥቆ በሠላምና በመቻቻል የምንኖርበት አገር እንኳ እንዳይኖረን በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች መጠነ ሰፊ የሆነ ድንግል መሬታችንን ለህንድ፤ ለቻይናና ለአረብ ከበርቴዎች በርካሽ ዋጋ በመቸብቸብ በገዛ አገራችን የባዕዳን አሽከሮች ሆነን እስከ ዘለአለሙ እንድንኖር መሠረት ተጥሎአል::
ይህ ሁሉ በደልና መከራ እንዲያበቃ በአገዛዙ ላይ የተቃውሞ ድምጹን ያሰማ ከሥራውና ከኑሮው ተፈናቅሎ በድህነት አረንቋ ውስጥ እንዲጣል አለያም እየታደነና የሽብርተኝነት ታፔላ እየተለጠፈበት ወደ የማጎሪያ ጥቢያዎች እንዲወረወር ተደርጎአል:: በዘርና በቋንቋ በተከለለልን ክልል በፈረቃ የሚደርስብንን አፈናና ሰቆቃ በህብረት ለመቃወም የሚደረጉ ጥረቶች በሙሉ “የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂ፤ ትምክህተኛ ፤ አክራሪ/ጽንፈኛ፤ ጸረ ልማት ወዘተ ” በሚሉ የማሸማቀቂያና የመወንጀያ ቃላቶች ጋጋታ እንዲደናቀፍ ለማድረግ ተሞክሮአል::
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጥር 2 ቀን 2007 አመተ ምህረት የፈጸሙት ውህደት ዋናው ምክንያት ከላይ የተዘረዘሩትን ግፎች ለማስቆም በተናጠል ከሚደረግ ትግል በህብረት የሚደረገው ትግል ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑ የፈጠረው ግንዛቤ ነው :: የወያኔ የጥቃት ክንዶች የፈረጠሙት በራሱ ጥንካሬ ወይም የሚተማመንበት ህዝባዊ ድጋፍ በደጀንነት ኖሮት ሳይሆን በኛ መከፋፈልና መለያየት ብቻ እንደሆነ ህዝባችን ከተረዳው ውሎ አድሮአል::
አርበኞች ግንቦት 7 በሚል መጠሪያ ሁለቱ ድርጅቶች በቅርቡ የፈጠሩት ውህደት ከድህረ ምርጫ 97 ጀምሮ ህዝባችን ከደረሰበት ስቆቃ ለመገላገል ተቃዋሚዎችን “ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” በማለት ሲያቀርብ ለኖረው የድረሱልኝ ጥሪ የተሰጠ የመጀመሪያው ተግባራዊ ምላሽ ነው:: ሁለቱም ድርጅቶች እስከ ዛሬ ምድር ላይ ያደራጁትን የሰው ሃይል ፤ እውቀትና ንብረት አዋህደው በአንድ አመራር ሥር ትግሉን ከዳር ለማድረስ መወሰናቸው በአላማና ግብ ለሚመሰሉዋቸው ሌሎች ተቃዋሚ ሃይሎች ብቻ ሳይሆን ወያኔን ከህዝብ ጫንቃ ላይ በማውረድ ፍትህና እኩልነት በአገራችን እንዲሰፍን እንታገላለን ለሚሉት ሃይሎች ሁሉ አርአያነት ያለው እርምጃ መሆኑ እየተነገረ ነው :: የአርበኞች ግንቦት 7 ውህደት በተፈጸመበት ሥነሥርዓት ላይ አገራቸውን ነጻ ለማውጣት ነፍጥ አንግበው ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ውስጥ የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ [ዴሚት] ሊቀመንበር አቶ ሞላ አስግዶም ፡ የአፋር ነጻነት ግንባር [አርዱፍ] ሊቀመንበር አቶ ኢብራሂም ሙሳ ፤የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ [ጋህነን] ሊቀመንበር አቶ ኦኬሎ አይዴድ ፡ የቤነሻንጉል ተወካይና የአድሃን ተወካዮች በየተራ የተናገሩት በአንድ የጋራ ግንባር ሥር ተሰባስቦ በገንዘብና በመሣሪያ ብዛት ተብቶ የህዝባችንን መከራና ስቃይ እድሜ እያራዘመ ያለውን የጥቂቶች አገዛዝ በሃይል የማንበርከክ አስፈላግነትና ወቅታዊነት ሁለቱ ድርጅቶች የፈጸሙት ውህደት ለትብብር ፈር ቀዳጅ መሆኑን አመላክቶአል :: አገራችንን ከመበታተን አደጋ ለመታደግ ወያኔ ባወጣቸው የአፈና ህጎች ተገዝተን ለውጥ ማምጣት አንችልም ያልን ሃይሎች እየተዋሃድንና እየተጣመርን በሄዱን ቁጥር አፈናና እንግልት ተቋቁመን እንታገላለን ያሉት ሃይሎችም በተናጠል ከሚደርስባቸው ጥቃት ለመገላገል ሲሉ ወደ ውህደትና ጥምረት ጎዳና ማቅናታቸው የማይቀር ነው::
ህዝባችን ላይ የደረሰው ግፍና መከራ ጻዋ ሞልቶ እየፈሰሰ ባለበት በዚህን ሰዓት የአገሩ ጉዳይ አሳስቦት በፖለቲካ ድርጅቶች ዙሪያ የተሰባሰበ ወገን ሁሉ ለመቀራረብና ለመተባበር እያደረገ ያለው ጥረት ተስፋ ሰጪና አበረታች ሆኖአል:: በዚህ አጋጣሚ ላለፉት 24 አመታት ወያኔ በወገኖቻችን ላይ ለፈጸማቸው ሰቆቃዎች በመሣሪያነት ያገለገሉና እያገለገሉ ያሉ ወገኖች በሙሉ ከውህዱ አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አንድ የተላለፈላቸው ወገናዊ ጥሪ አለ:: ይህም ጥሪ እስከ ዛሬ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወይም ለሥራ ዋስትና ብላችሁ የዚህ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ መሳሪያ በመሆን በወገኖቻችሁ ላይ ግዲያ ፤ እስርና ግርፋት ስትፈጽሙ የኖራችሁ ሁሉ የበደላችሁትን ህዝብ ለመካስ የአገዛዙን ዕድሜ ለማሳጠር በምናደርገው የሞት ሽረት ትግል ላይ እንቅፋት ከመሆን እራሳችሁን አግልሉ ! የሚል ነው:: ትግላችን ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ገና ከመድረሱ ከህዝብ በዘረፉት ሃብትና ገንዘብ ልጆቻቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ወደ ባህር ማዶ ማሸሽ ለጀመሩት ስግብግብ አለቆችህ ምቾትና ድሎት ብለህ ይህ የመከራ ዘመን ሲያልፍ በሃላፊነት የሚያስጠይቅህን ወንጀል ለነጻነት በሚታገሉ ወገኖችህ ላይ እንዳትፈጽም ለአገር የመከላኪያ ሠራዊት፤ ለፖልስና የጸጥታ ሃይል አባላት ሁሉ ጥሪ ቀርቦአል::
የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ድል ማድረጋችንን ፈጽሞ የማንጠራጠር የነጻነት ታጋዮች በሙሉልብ የምንናገረው ወያኔ አገራችንን ለመበታተን የቻለውን ሁሉ ድንጋይ ቢፈነቅልም በአንድ የአመራር ጥላ ሥር ተሰባስበን አገራችንን ከተጋረጠባት የመበታተን አደጋ ለመታደግና እያንዳንዱ ዜጋ የሚኮራባት የበለጸገችና ሉአላዊነቷ የተረጋገጠ አገር ባለቤት ለመሆን የጀመርነው ትግል ግቡን እንደሚመታ ነው:: ለዚህ ደግሞ በቅርቡ የፈጸምነው ውህደትና ከሌሎች ጋር በጥምረት ጠላትን ለመፋለም የጀመርነው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ወቅታዊነት ለወገን ተስፋ ለጠላት መርዶ ነው::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Sunday, February 1, 2015

ሬድዋን ሁሴንና የወደቀው ክሱ !

February 1,2015
በኢትዮጵያችን ህግ ትርጉሟን አጥታ፤ፍትህም ተዋርዳ ከተጣለች የህወሃትን እድሜ ብታስቆጥርም እነርሱ ግን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ስለ ህግ የበላይነት ማውራታቸውን አላቆሙም። እነዚህ ቡድኖች የህግ የበላይነት ሲሉ እነርሱ ከፍ ብለው ከህግ በላይ፤ ከእነርሱ መንደር ያለሆነው ደግሞ ዝቅ ብሎ ከሥር ከጫማቸው ሥር ሁኖ እነርሱን ተሸክሞ የሚኖርበትን ሥርዓት ማስጠበቅ የሚችለውን ህግ ነው። እናንተን መሸከም ከበደኝ፤ ቀንበራችሁ ሰበረኝ የሚል ሰው ከተገኘ የሚጠብቀው ፍርድ “አሸባሪነት” ነው። ይህ የክፉዎችና የልበ ደንዳኖች ፍርድ ፍትህ ተብሎ በህወህቶች መንደር ይወደሳል። መፅሃፍ እንዲህ ይላል “ክፍዎች ሰዎች ፍርድን አያስተውሉም”። ህወሃቶች ባወጧቸው ህጎች የስንት ንፁሃን ዜጎች ቤት እንደፈረሰ፤ ስንት ህፃናት አሳዳጊ አልባ እንደሆኑ፤ ስንቶች አገራችውን ትተው ተሰደው እንደጠፉ ቆጥረን አንዘልቀውም። በህወሃት መንደር ህግ ዜጎችን ማጥቂያ እና ማስጨነቂያ መሣሪያ እንጂ የፍትህ ማስከበሪያ መሳሪያ አይደለም። በህወሃት ህግ ብዙ ዜጎች ጠፍተዋል፤ ብዙዎች ደግሞ በብዙ ጭንቀት እና መከራ ውስጥ ይገኛሉ።

በህወሃት መንደር የተሰባሰቡ ግለሰቦች እንደምን ያለ ብርቱ ጭለማ እና ድንቁርና ውስጥ እንደሚገኙ በርካታ ምሳሌዎችን ማንሳት እንችላለን። ለአሁን ግን ማሰብ ካቆሙ ቅጥረኞች መካከል ሬድዋን ሁሴን የተባለው ግለሰብ የሆነውን እንመልከት። ሬድዋን ሁሴን፤ ጌቶቹ እና ሌሎች መሰሎቹ ያሉበትን ዘመን ረስተው ወይም መረዳት ተስኗቸው፤ ከስልጣኔ መንገድም ወጥተው እንዲሁ በጭለማ ዓለም እየተደናበሩ ይገኛሉ። ሬድዋን ሁሴን ያለበትን ዘመንና የያዘው የህዝብ ስልጣን የሚያስከትልበትን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ውጤት መገንዘብ ስለተሳነው ቀና ብሎ ተናገረኝ ባላው ወጣት ላይ በአሜሪካን አገር ክስ መመሥረቱን ስንሰማ በብርቱ ተደንቀናል። አገራችንም በእንደነዚህ ዓይነት ማስተዋል በጎደላቸው ግለሰቦች የምትመራ መሆኑም በእጅጉ ያሳዝነናል።

ሬድዋን ሁሴንን በቨርጂኒያ አገረ ግዛት ያገኘው ወጣት ህወሃቶች በወገኖቹ ላይ የጫኑባቸው ሸክም ያሳመመው፤ በዚህም ህመም የተቆጣ ቁጣውንም በሰላም የመግለፅ መብቱ ያለ ገደብ የተከበረባት አገር ውስጥ ኗሪ ነው። ሬዲዋን ሁሴንን የመሰለ ራሱን ለምናምንቴ ነገር አሳልፎ የሸጠ ትንሽ ግለሰብ ይቅርና የሃያሏ አገር አሜሪካን ፕሬዝዳንትም ብዙ ወቀሳና ስድብ ይደርስበታል።ፕሬዝዳንቱም የህዝብ ተቀጣሪ መሆኑን ስለሚያውቅ ተወቀስኩ ወይም አንድ ዜጋ ተናገረኝ ብሎ የበቀል ሰይፉን አይመዝም። ፕሬዝዳንቱ ተሰደብኩ ብሎ ክፉ ቢናገር የሚከተለው መዘዝ ከስድቡ የበለጠ ጉዳት ስለሚያደርስበት ስድቡን መቻል እና መሸከም የሥራው አንዱ አካል ይሆናል።ህግ ባለበት አገር የአገሩ መሪ ህዝቡን ፈርቶ ይኖራል እንጂ፤ ህዝብ መሪውን ፈርቶ አይኖርም። ሬዲዋንና መሰሎቹ ግን እንዲህ አይደሉም። ህዝብን ረግጠውና አስፈራርተው መኖር የጎበዝ ተግባር ነው ብለው አምነው ተቀብለዋል።

ህወሃት ትንሹንም ትልቁንም ፈርቶ፤ ፍርሃቱ በወለደው ጭካኔ ዜጎችን ሁሉ አስሮ መኖር ልማዱ ሁኗል። በኢትዮጵያ ዜጎች ህወሃቶችን ፈርተው፤ ህወሃቶችም ዜጎችን አስፈራርተው የሚኖሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ይሄ ሁኔታ ለማንም ወይም ለምንም እንደማይበጅ ለህወሃቶች ብንነግራቸውም ልቦናቸው በትዕቢት ታውሯልና አይሰሙንም። ሬድዋን ሁሴንም የዚህ መራራ ትዕቢት ትሩፋት ነው። እንደምን ሁኖ ቀና ብለው ያዩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ይናገሩኛል፤ እንደምንስ ሁኖ ስሜ በገበያ መሃል ይነሳል የሚል ትዕቢት ስለተፀናወተው ክስ መሠረተ፤ ክሱ ግን በህግ ፊት ሚዛን የማይደፋ በመሆኑ በአቃቤ ህጉ ውድቅ ተደረገ። ሬዲዋንም የፍትህን መራራ ፅዋ ተጎንጭቶ ሊውጣት ግድ ሆነበት። የህወሃት ቅጥረኞችና ህወሃቶች ውድቅ ከሆነው ከሬድዋን ህሴን ክስ ልትማሩ የሚገባችሁ የህግ የበላይነት በሰፈነበት አገር እናንተ ከተራው ዜጎች እኩል እንጂ የበላይ ልትሆኑ እንደማትችሉ፤ ከመጋረጃው ጀርባ ሁናችሁ ፍትህን የምትጠመዝዙበት እጃችሁ እንደሚታሰር እና ገና ወደፊት ደግሞ የእጃችሁን እንደምታገኙ ነው። እናንተን ከተራው ዜጋ እኩል የሚያደርግ ህግ ሲፈጠር የታጠቃችሁት ጠብመንጂያ የሸንበቆ ምርኩዝ፤ የመኖሪያ ድንኳን የሆናችሁ ማን አለብኝነታችሁ ደግሞ ፀሃይ እንዳየው ጤዛ እንደሚተን ልብ ልትሉ ይገባል። ሬዲዋንን የተናገረው ወጣት ኢትዮጵያ ውስጥ ሁኖ ቢሆን ኑሮ ዛሬ እነሬዳዋን ፈተው በሚለቋቸው ውሾች ሊደርስበት የሚችለውን ስቃይ ስናስበው ይዘገንነናል። ከባህር ማዶ መሆኑ ከሥጋዊ ስቃይ አድኖታል።

እንግዲህ ህወሃቶች የምትፈፅሟቸው ግፎች በየደረሳችሁበት እየተከታተሉ እረፍት ማሳጣታቸውን የሚያቆሙ አይሆንም። የምትሠሯቸው ግፎች የሚያሳድዱት እናንተን ብቻ አይደለም። ከእናንተ አብራክ የሚፈጠሩ ልጆቻችሁንም ጭምር የክፉ ሥራዎቻችሁ ሰለባዎች ከመሆን አያመልጡም። ልጆቻችሁ ተሳቀው ከህዝብ ዓይንና ጆሮ ተደብቀው መኖር ዕድል ፈንታቸው ይሆናል። እናንተ የምትፈፅሙት ወንጀል ለልጆቻችሁ ኩራት ሳይሆን እፍረት፤ ክብር ሳይሆን ውረደት ሁኖ ይቆያቸዋል። ቢያንስ ለልጆቻችሁ ሠላም ስትሉ ከእኩይ ድርጊታችሁ መታቀብ ይሻላችሁ ነበር። እናንተ ግን ለትውልዱ ሠላም የሚሻለውን ትታችሁ የጥፋቱንና የደም መፋሰሱን መንገድ መርጣችኋልና ወዮታ አለባችሁ።

እናንተን መታገል ከስጋና ከደም ጋር የሚደረግ ትግል ብቻ አይደለም። የምትፈፅሟቸው ግፎች ከሰው ልጅ አዕምሮ የሚፈልቁ ብቻ አይመስልም።ከእናንተ ጋር የሚሰራ ሌላ የማይታይ የክፋት አባት ያለ እስከሚመስለን ድረስ ግፋችሁ አንገፍግፎናል። ይህን ግፍ ዝም ብለን የምናይ አይመሰላችሁ። ሊከፈል የሚገባውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተናል። ወጣቶችም ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱባቸው ኮረብቶች ላይ ተሰማርተዋል። ክፉውን ለመቃወም፤ ደም አፍሳሹን ለማስቆም፤ ሌባውን ተው ለማለት፤ ትዕቢተኛውን አደብ ለማስያዝ፤ የነፃነት ቀበኛውን ለማስተማር ሰይፋቸው ከአፎቱ ተስማምቶ ተዘጋጅቷል።

የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች ሆይ !

ህወሃቶች በዜጎችቻን ላይ የሚፈፅሙትን ግፍ ለእናንተ መንገር ለቀባሪው እንደ ማርዳት ይሆንብናል።የእነዚህ ቡድኖች ግፍ ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰሰ ነው።የአገሪቷን ታሪክ አንድ በአንድ ለማጥፋት እየሠሩ ይገኛሉ-በየቦታው በእሳት የሚቃጠሉት ታሪካዊ አምባዎቻችን የአገሪቷን ታሪክ የማጥፋት ዘመቻ አካል ነው።ዜጎች አገር አልባ እንዲሆኑ ተደርገዋል፤ አብሮ በኖረው ህዝብ መካከል የሚዘራው የጥላቻ ዘር ለአገራችን አደጋ ሁኖ ተደንቅሯል። አገራችን ታሪኳ በሚመሰክርላት ሥፍራ ላይ እንዳትሆን፤ ለአፍሪካ ቀንድም ሆነ በአጠቃላይ ለዓለም ሠላም መጫወት የሚግባትን ሚና እንዳታከናውን ተደርጋለች። በተቃራኒው የግጭት አምባ፤ የችጋር ምሳሌ፤ የስደት ምልክት ሁና ከውዳቂ መንግስታት ተርታ ገብታለች። ይሄ ሁሉ እርግማን በህወሃት ምክንያት የመጣ ነው።

እኛ በአገራችን ላይ የተተከለውን ህወሃት የተባለውን እርግማን ነቅለን ለመጣል የምንችለውን ሁሉ እያደርገን ነው። ህወሃቶች የነፃነትን ዋጋ ተረድተው፤ ለፍትህ ክብር ሰጥተው፤ ዜጎችን አክብረው፤እኛም ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር እኩል ነን። ከማንም አንበልጥም፤ ሌላውም ከእኛ አያንስም ብለው በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመወያየት ፍርሃታቸው እና ድንቁርናቸው ቢፈቅድላቸው ለሁላችንም መልካም ነበር። ይህ መልካም ነገር ግን የእኛ ምኞት ብቻ ሁኖ ቀርቷል።ህወሃቶች የተፀናወታችው ትዕቢት የሰይጣን ትዕቢት ስለሆነ እንዲሁ በቀላሉ በጄ የሚሉ አይሆኑም። እኛ የቀረን አንድ መንገድ በማንኛውም መንገድ አገራችንን ከጥፋት ማዳን ብቻ ነው። ይህም ታሪካዊ ግዴታችን ሁኗል።

ይህን አገርን የማዳን ታሪካዊ ግዴታ የዚህ ቡድን ወይም ደግሞ የዚያ አካል ብቻ ተደርጎ መወሰድ ያለበት ተግባር አይደለም። እያንዳንዱ ማሰብ የሚችል እና ለራሱ ትንሽ ክብር ያለው ዜጋ ሁሉ ኢትዮጵያን ለመታደግ የሚችለውን ጠጠር መወረወር ይጠበቅበታል። ኢትዮጵያ ሬድዋን ሁሴንን በመሳሰሉ ምናምንቴዎች ስትዋረድ እጅን አጣምሮ ቁሞ መታዘብ ትክክለኛ ተግባር አይሆንም። የአገሪቷ ድሃ ዜጎች ስቃያቸው በዝቶ እና ጭንቀታቸው ልክ አጥቶ እያየን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ካሉ ዜጎች ጋር መተባበሪያ ግዜው አሁን ነው።

እኛ አርበኞች-ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለፍትህ ንቅናቄ አገራችን ከገባችበት የውርደት አዘቅት ውስጥ ለማውጣት የጀመርነውን ትግል እለት እለት እያደስነው፤ እለት እለት እያሰፋነው፤ እለት እለት እያሳደግነው ቀጥለናል። እኛ ዓይናችን እያየ ህዝባችን አይዋረድም፤ አገራችንም ከሥፍራዋ በታች ስትሆን ዝም አንልም።የሚከፈለውን ማንኛውንም መሥዋዕትነት ለመክፍለ አናቅማም። በአያት ቅደመ አያቶቻችን ደም ተከብራ የኖረች አገር ዳግም በእኛ ደም ተከብራ ትኖራለች። ቀጣዩ ትውልድም የተከበረች አገር ተርክቦ፤ እርሱም ተከብሮ ይኖር ዘንድ እኛ እንሰራለን እግዚአብሄርም ያከናውንልናል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Saturday, January 31, 2015

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

January 31,2015
የገዢውን ፓርቲና መንግስትን ሽፍትነት ያጋለጠው አንድነትን የማፍረስ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኢትዮጵያዊን ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም!!!
ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን፡፡ አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል፡፡
ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው፡፡ ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል፡፡ በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ  ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን፡፡
ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል፡፡ በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡
ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!!!
ጥር 22/ 2007 ዓ.ም
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)                                                      
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
UDJ




ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

January 31, 2015
‹‹ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ትወስዳላችሁ›› የቂ/ክ/ከ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ
የቤት ደላሎች ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳያከራዩ ከቀበሌ ባለስልጣናት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ተደራጅተው በመስራት ላይ የሚገኙት ደላሎች የቂ/ክ/ከ ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ከበደ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ አሸባሪ ፓርቲ ነው፡፡ ለአሸባሪ ፓርቲ ቢሮ ብታከራዩ ተጠያቂነቱን ራሳችሁ ትወስዳላችሁ›› ብለው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ እንደሰጧቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ለማከራየት ተስማምተው የነበሩ አንድ ግለሰብ በቀበሌ ካድሬዎች ትዕዛዝ ቤቱን እንዳያከራዩ ተደርገዋል፡፡ ማስጠንቀቂያ የደረሳቸው ደላሎች ግለሰቧን ‹‹መጀመሪያ ቀበሌ ሄደሽ ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ልታከራይ መሆኑን አሳውቂ›› ብለው በመከሯቸው መሰረት ቀበሌ ሄደው ‹‹ለሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ላከራይ ነበር፡፡ ምን ችግር ይኖረዋል?›› ብለው ሲጠይቁ የቀበሌ ካድሬዎች ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ህገ ወጥና አሸባሪ ፓርቲ ነው፡፡ ለእሱ ቢሮ ማከራየት በህግ ያስጠይቅሻል›› ብለው ስላስፈራሯቸው ለማራየት ሳይደፍሩ ቀርተዋል፡፡
የየካ ክፍለ ከተማና የቂርቆስ ክፍለ ከተማ በጋራ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ እንዳይከራይ ደላሎቹና አከራዮችን እያስጠነቀቁ ሲሆን ሰማያዊ ፓርቲ ካሳንቺስ የሚገኘው ጽ/ቤቱን እንዲለቅ በቤቱ ባለቤቶች ላይ ከፍተኛ ግፊት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ አከራዮቹ በቀበሌ ባለስልጣናትና በደህንነቶች በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ፓርቲው ቤታቸውን እንዲለቅላቸው፣ ካልለቀቀም አሁን ከሚከፍለው 3 እጥፍ ገንዘብ እንዲከፍላቸው ጠይቀዋል፡፡

አንድነት ታገደ፣ ጽ/ቤቱ ተወረረ ፣ ከዚህ በኋላስ

January 31,2015
ግርማ ካሳ
Girma Kassa's photo.
ይህ ሳምንታ በጣም አሳዛኝ ሳምንት !!!! በዚህ ምርጫ አንጻራዊ መረጋጋትና ብሄራዊ መግባባት መጥቶ ፣ የጋራ የልማት ኮሚሽን ተቋቁሞ በጋራ አባይን እንገነባላን፣ የባቡር መስመሮችን እንዘረጋለን፣ አገራችንን ከዉጭ ኃይሎች ከቻይናዎች ከመሳሰሉ ጥገኝነት እናወጣለን የሚል ተስፋ ነበረኝ።
ሆኖም በዚህ ሳምንት በኃይል፣ በጭካኔ የዚህን ፓርቲ ሕጋዊነት ሕወሃቶች ጨፍልቀዋል። በሐሳብ ማሸነፍ ሲያቅታቸው የኃይልና የጡንቻ እርምጃ ወስደዋል። በጠራራ ጸሃይና በአደባባይ ወንበዴዎችን ሽፎቶች መሆናቸውን አሳይተዋል። የ2007 ምርጫ በደምና በጭካኔ፣ ከመደረጉ ከአራት ወራት በፊት ተጠናቋል።
ፖለቲካዉን ከተቀላቀልኩ ከዘጠና ሰባት ጀምሮ በሰላም ለዉጥ ይመጣል ብዬ ስከራከር እንደነበረ ይታወቃል። ስለሰላማዊ ትግል ብዙ ጽፊያለሁ። አሁንም በሰላማዊ ትግል አምናለሁ። ወደ ጦርነት የሚሉ ወገኖቼ ስሜት ብረዳም፣ ዉሳኔያቸውን ባከብረም፣ የጦርነትን አስከፊነት ከግምት በማስገባት፣ አሁን የሰላማዊ ትግሉን ብቻ ነው የምደገፈው። (ይሄን ስል የትጥቅ ትግል እቃወማለሁ ማለት አይደለም። አለመቃወምና መደገፍ የተለያዩ ነገሮች ናቸው)
የሰላማዊ ትግልን እደግፋለሁ ስል፣ ህጋዊ የሰላማዊ ትግልን ማለቴ አይደለም። ሕጋዊ የሰላማዊ ትግል ከአሁን በኋላ በኢትዮጵያ ሞቷል። ተቀብሯል። የምርጫ ፓርቲ የሚባል ነገር ከአሁን በኋላ የለም። እርግጥ ነው እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ያሉ አሉ። እነርሱም ቢሆኑ በዚህ ሁኔት ይቀጥላሉ ብዬ አላስብም። ምናልባትም በአደባባይ የምርጫ ካርዶቻቸውን ቀዳደው ሊያቃጥሉም ይችላሉ። ምርጫዉን ከተሳተፉ የሚያመጡት ለውጥም አይኖርም። ለምን አንድ አስጊ ደረጃ ሲደርሱ በጉልበት መጨፍለቃቸው አይቀሬ ነው።
ትንሽ ላብራራ። ሕጋዊ ስል አገዛዙ ያወጣዉን ሕግ በመከተል የሚደረግ ትግልን ማለቴ ነው። በፈለጉ ጊዜ ሕጋዊነትን ሕግ ወጥ በሆነ መልኩ የሚረግጡ ከሆነ፣ ሕግን ተጠቅመው ዜጎችን የሚያፍኑ ከሆነ፣ እንዴት ተደርጎ ነው ሕጋዊ ትግል የሚደረገው ?
ለሕወሃት ሕግ አልገዛም የሚል የእምቢተንኘት ሰላማዊ ዘመቻና ትግል ነው የሚቀጥለው ምእራፍ። ሰላማዊ፣ የእምቢትኝነት ዘምቻ ስል፣ ጠመንጃ ከማንሳት ዉጭ የሚደረጉ ተግብራት ሁሉ ያጠቃልላል። ሕወሃትን ስናከብረው፣ እርሱ ባወጣው ሕግ ተገዝተን ስንቀሳቀስ፣ የሚጨፈልቀን ከሆነ፣ ታዲያ መብታችንን በራሳችን መንገድ ለምን አናስከበርም ?
ይህ አይነቱ ትግል አንደኛ ጥንቃቄ ይጠይቃል። ሁለተኛ ራስን አጋልጦ መሆን የለበትም። ሶስተኛ የምናደርገውን አስቀድመን እየነገርንና ወያኔዎች እንዲጠነቀቁ እያደረግን አይደለም። አራተኛ ዲሴንትራላይዝ መሆን አለበት። አምስተኛ ዲሲፕሊን እና ተጠያቂነት መኖር አለበት። በስሜት፣ ባልተጠና መልኩ አንድ ነገር አድርገን ብዙ ሰው እንዲጎዳ ማድረግ የለብንም። አንርሳ ለሕዝብ የሚያስብ "ኢትዮጵያው ነኝ" ቢልም ኢትዮጵያው ያልሆነ፣ ከግራዚያኒ የማይተናነስ አገዛዝ ነው ያለን። ስለዚህ በምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ለዜጎቻችን መጠንቀቅ አለብን።ስድስተኛ የምናደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች ከተደረጉ በኋላ ለሕዝብ እናሳወቅ። ሰባተኛ ገዢውን ፓርቲ ፍሊትሬት እናድረግና ሚስጥራቸውን እናወጣ። ስምንተኛ ሜዲያ በጣም አስፈላጊ ነው። በዚህ ረገድ እንደ ኢሳት ያሉ ትልቅ ሚና ሊጫወቱ ይገባል። ይጫወታሉምም።
አንድ ነገር ግን ግልጽ ላደርግ። ሕወሃት ይወድቃል። ይሄን እርግጠኛ እንሁን። በዚህ ሳምንት የወሰኑት ዉሳኔ እንደዉም የበለጠ እንድቆርጥና እንድንጨክን ነው ያደረጉን። አሁን አንዱን በር በኃይል ቢዘጉብንም፣ ሌሎች በሮች አሉ። ይህ ስርዓት ከሕዝቡ ጋር የተጣላ ስርዓት ነው። የበሰበሰ ስርዓት ነው።
ዉድ በገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ያላችሁ ወገኖቼ፡
ነጻነት ከሰማይ አይመጣም። ነጻነትን የምናመጠው እኛው ራሳችን ነን። ሕጋዊ ሆነው የሚንቀሳቀሱ የምርጫ ፓርቲዎች ፣ እግዚአብሄር ይባርካቸዉና፣ ተደብድበው፣ ታስረው ትልቅ ዋጋ ከፍለው መድረስ የሚችሉበት ጫፍ ላይ ደርሰዋል። ሕጋዊነታቸው ይኸው ተነጥቀዋል። ከአሁን በኋላ ተራው የእያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን ነው። በራሳችን ተደራጅተን፣ የምንቀሳቀስበት ሰዓት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት ወደፊት እመለስበታለሁ።

Friday, January 30, 2015

አንድነትን “እናኝከዋለን፤ እንገድለዋለን” – ምርጫ ቦርድ

January 30,2015
ትዕግስቱ አወሉ እንደ አየለ ጫሚሶ
tplfs election board

የዛሬ አስር ዓመት “የሕዝብ ሱናሚ” እያለ ሲምል ሲገዘት የነበረው ህወሃት ሱናሚው ወደ እርሱ እየጎረፈ ሲመጣ በረገገ፡፡ መፍትሔ በጠብመንጃ አፈሙዝና በብረት ብቻ እንደሆነ የሚያምነው ህወሃት በረሃ የለመደውን በትሩን አነሳ፤ ንጹሃንን ጨፈጨፈ፤ ደም አፈሰሰ፤ ኢትዮጵያን ወደ እስርቤትነት ቀየራት፡፡ ትዕዛዙን በቀጥታ የሰጡት “ባለራዕዩ” ለፍርድ ሳይቀርቡ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” ያሉትን ሰፊውን ሕዝብ ሳይጨርሱት እንደ ክዳን ቆርኪ ተስፈነጠሩት፤ ላይመለሱ ሄዱ፡፡
የዛሬ አስር ዓመት የቅንጅት አካሄድ ያስፈራው ህወሃት ጉዳዩን ለራሱ ለፓርቲውና ለሕዝብ ከመስጠት ይልቅ ደም መቃባት ውስጥ ገባ፡፡ ፓርቲው የነበረበት የውስጥ ችግር እንዳለ ሆኖ የፈሪ በትር የዘረጋው ህወሃት የገደለውን ገድሎ ከጨረሰ እና የኢትዮጵያን መሬት በደምና በእናቶች እምባ እንደገና ካጨቀየ በኋላ ቅንጅትን የማፍረስ ተግባሩን በዕቅድ ይዞ በይፋ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ግምባር ቀደም ተሰላፊው የተቋም ባንዳ “ምርጫ ቦርድን”፤ በግለሰብ ደረጃ ደግሞ በተለይ ሁለት ግለሰቦችን አሰለፈ፡፡ ዘመቻ “ቅንጅትን መግደል” ተጀመረ፡፡
በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ምንም በማያሻማ ሁኔታ በኢትዮጵያ የቀድሞ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ያማሞቶ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር (ስቴት ዲፓርትመንት) ለሚገኙት አለቆቻቸው THE ETHIOPIAN GOVERNMENT CHEWS THE CUD” (የኢትዮጵያ መንግሥት ቅንጅትን አኘከው) በሚል ርዕስ የጻፉት እንዲህ ይነበባል፤
Over the course of the week of January 7, the National Electoral Board of Ethiopia (NEB) hammered what appear to be the final nails in the coffin of the opposition Coalition for Unity and Democracy (CUD) party. Since their surprise showing in the 2005 elections, gaining enough seats to become the second largest political party in Ethiopia, the CUD has virtually disintegrated as a result of internal power struggles and interference from the Ethiopian Government (GoE). In the latest setback, the NEB awarded the famous victory sign — the CUD symbol widely recognized by voters — to former ally turned foe, Lidetu Ayalew of the United Ethiopian Democratic Party-Medhin (UEDP-Medhin).  The NEB followed this later in the week by finally awarding registration of the reformed Coalition for Unity and Democracy Party (CUDP) party name to yet another former CUD ally turned foe Addis Ababa city council member-elect Ayele Chamisso.  Though Ayele, who is broadly viewed as having been co-opt by the GoE, has invited all faction of the former CUD to join his party, few will likely take his offer.
In a meeting with Ambassador on January 11, NEB board chairman Dr. Merga Bekana and vice-chairman Dr. Addisu Gebre-Egziabhier said that the Board still had not decided on the CUDP’s registration and would continue to consider the matter in coming weeks. Almost immediately following the meeting, however, the NEB publicly announced that it had decided that morning to award the party license to Ayele. This followed their controversial decision earlier in the week to give the CUD’s famous victory symbol to the CUD’s despised adversary Lidetu Ayalew (another person believed to have been co-opted by the GoE during the CUD’s post-2005 election struggles), and his UEDP-Medhin party.
The opposition fiercely accused the NEB of being under the influence of the GoE and of delivering votes to the ruling Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Forces (EPRDF) party after the opposition’s surprisingly strong showing. Since then, a new Board has been put in place, but the opposition have not altered their criticism. The NEB’s recent decisions to award the CUD party symbol and name to politicians, who are at best undeserved and at worst proxies of the GoE, has done much to reignite lingering suspicions regarding the NEB’s independence. As if to prove these suspicions, NEB vice-chairman Dr. Addisu (a Tigrayan political scientist widely believed to be the “enforcer” at the NEB) recently commented to USAID’s Senior Democracy Advisor — a former Stanford University Political Science Professor ) (strictly protect) that the NEB had decided to “kill the CUD.” The NEB decisions of the last week have effectively done exactly that.
በጃኑዋሪ 7 ሳምንት ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ (ቅንጅት) ፓርቲ የሬሣ ሳጥን ላይ የመጨረሻ የሚባለውን ሚስማር መትቷል፡፡ በ2005 (1997) ምርጫ በአገሪቱ ሁለተኛው ትልቁ የተቃዋሚ ፓርቲ ለመሆን የሚያስችለውን አስደናቂ ድልና በቂ መቀመጫ ካገኘ በኋላ ቅንጅት በውስጡ በነበረው የኃይል (የሥልጣን) ሽኩቻና ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ይደርስበት በነበረው ጣልቃ ገብነት ምክንያት አለሁ ቢልም እየተፈረካከሰ ነበር፡፡ በቅርቡ በተደቀነበት ሌላ ደንቃራ ደግሞ ምርጫ ቦርድ ዝነኛውንና በብዙሃን መራጭ ዘንድ ዕውቅና የነበረውን የቅንጅትን (V) ምልክት ቀድሞ (የቅንጅት) ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ – ኢዴፓ-መድህን ልደቱ አያሌው ሸልሞታል፡፡ በመቀጠልም ምርጫ ቦርድ ይህንን ተከትሎ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የስም ምዝገባ ቀድሞ የቅንጅት ወዳጅ በኋላ ጠላት ለሆነው የአዲስ አበባ ምክርቤት እጩ ተመራጭ አየለ ጫሚሶ ሸልሞታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ቅጥረኛ እንደሆነ በሰፊው የሚታመነው አየለ ጫሚሶ ከቀድሞው ቅንጅት ተሸራርፈው ለወጡት ሁሉ የእርሱን ፓርቲ እንዲቀላቀሉ ጥሪ ቢደርግም ጥቂቶች ብቻ ጥሪውን ይቀበላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ . . .
addisu  g of neb
አዲሱ ገብረእግዚአብሔር
የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔርከአምባሳደሩ (ያማሞቶ) ጋር ጃኑዋሪ 11 ቀን ባደረጉት ስብሰባ የቅንጅትን ምዝገባ በተመለከተ ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሱ እና በመጪዎቹ ሳምንታት ጉዳዩን እንደሚመለከቱት ነበር የተናገሩት፡፡ ነገር ግን ወዲያውኑ ስብሰባው እንዳበቃ ማለት ይቻላል የዚያኑ ቀን ጠዋት የቅንጅትን የስም ምዝገባ ለአየለ ለመስጠት መወሰኑን ምርጫ ቦርድ ለሕዝብ ይፋ አደረገ፡፡ ይህ የቦርዱ ውሳኔ በሳምንቱ መጀመሪያ አካባቢ የቅንጅትን ዝነኛ (V) ምልክት በቅንጅቶች ለተናቀውና የፓርቲው ጠላት ለሆነው ልደቱ አያሌውና ለኢዴፓ-መድህን ፓርቲው ለመሸለም የተደረገውን አከራካሪ ውሳኔ ተከትሎ ነው፡፡ (ልደቱ አያሌው ከምርጫ 1997 በኋላ ቅንጅት ውስጥ በነበረው ትግል ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥት የተመደበ ሌላው ቅጥረኛ እንደሆነ ይታመናል)፡፡ . . .
ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ መንግሥት ሥር እንደሆነ እና ተቃዋሚዎች አስገራሚ ውጤት በምርጫው ላይ ካሳዩ በኋላ (የመራጮችን) ድምጽ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢህአዴግ) እንዳስረከበ ተቃዋሚ (ፓርቲዎች) አጥብቀው ይከስሳሉ፡፡ ከዚያ ወዲህ አዲስ ቦርድ የተሰየመ ቢሆንም ተቃዋሚዎች ግን አሁንም ትችታቸውን አላቆሙም፡፡ የቅንጅትን ስም እና ምልክት ፍጹም ለማይገባቸውና ለኢትዮጵያ መንግሥት የቅርብ ወዳጆች ለሆኑት ፖለቲከኞች ማስረከቡ ምርጫ ቦርድ ከአድልዎ የነጻ አለመሆኑ ላይ ያሉትን ጥርጣሬዎች እንደገና እንዲቀጣጠል አድርጓል፡፡ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር አዲሱ በቅርቡ ለዩኤስኤይድ ከፍተኛ የዴሞክራሲ አማካሪና የቀድሞ የስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ፕሮፌሰር (ስሙ እንዳይወጣ በጥብቅ የተከለከለ) ምርጫ ቦርድ “ቅንጅትን ለመግደል” ወስኖ እንደነበር መናገሩ እነዚህን ጥርጣሬዎች እርግጠኛ ያደርጋቸዋል፡፡ (የአዲግራት ተወላጅ የሆነው) (ዶ/ር አዲሱ የትግሬ የፖለቲካ ሳይቲስት ሲሆን የምርጫ ቦርድ “ፈጣሪና አድራጊ” እንደሆነ በሰፊው ይታመናል)፡፡ ባለፈው ሳምንት ምርጫ ቦርድ የወሰደው ውሳኔ (የቅንጅትን ስምና ምልክት ለቅጥረኞቹ መስጠቱ) ይህንኑ (ቅንጅትን የመግደሉን ዕቅድ) የሚያረጋግጥ ነው፡፡ . . . (ሹልክዓምድ (ዊኪሊክስ) ላይ የወጣውን ሙሉ መረጃ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
አሁንስ ማነው ባለሳምንት? በዚህኛው የምርጫ ድራማ አየለ ጫሚሶን የሚጫወተው ትዕግስቱ አወል እንደሆነ ይፋ ሆኗል፤ ልደቱንስ ማን ይተውነዋል?
ከዚህ በፊት በሰማያዊና በሌሎች ፓርቲዎች ላይ የደረሰውና አሁንም እየደረሰ ያለው እንዲሁም ሰሞኑን በአንድነት ፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ላይ የደረሰው ሰቆቃ የዘንድሮውን ሁኔታ የተለየ እያደረገው እንደሆነ ጎልጉል ከተለያዩ ምንጮች የሚደርሱት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ስለዚህም ነው “ምርጫ ቦርድ” ቅንጅትን በዕቅድ እንደገደለው አሁንም አንድነትንና ሌሎቹን ተቀናቃኞች “አኝኮ ለመግደል” ውሳኔው የሆነው፡፡
ከሕዝብ በኩል የሚሰማው የሰላማዊ ትግል ቁርጠኝነት ግን የህወሃትን የልመና ኮሮጆ በሚሞሉት ምዕራባውያንም ዘንድ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው እንደሆነ ጎልጉል የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ሰልፍ በተካሄደበት ወቅት በተለያዩ የማኅበራዊ ገጾች ላይ ተሰራጭቶ ያገኘነውን መረጃ መጥቀሱ የቁርጠኝነቱን መጠን በተወሰነ መልኩ የሚያመለክት ነው፡፡ “በዕለቱ የደረሰበትን ጉዳት አስመልክቶ ለቢቢኤን ሬዲዮ የተናገረው የአዲስ አበባ ወጣቶች ጉዳይ አንድነት ፓርቲ ኃላፊ ስንታየሁ ቁስሉ ሳይደርቅ በወኔ እንዲህ ነበር ያለው “ወያኔ ላጠፋው ጥፋት የሚያወራርደው ሒሳብ እንዳለ ማወቅ አለበት፡፡ ለትግላችን እንሰዋለን፤ በዋዛ አንላቀቅም”፡፡

Boycotting Ethiopian National Elections: Damn if You Do, Damn if You Don’t!

January 30, 2015
by Messay Kebede
I maintain that the upcoming elections will be a turning point for Ethiopia, not because they will result in a major change of policy subsequent to a renovation of the ruling elite but because the absence of change will compel opposition groups to reassess their strategies and the country as a whole will plunge further into the abyss of despair. While most reasonable people and opposition parties never contemplated the possibility of wining the elections and becoming the new ruling majority, nevertheless the expectation was—since the death of Meles Zenawi—for some opening, however narrow, to accommodate opposition groups. In light of the prevailing heightened repression and disqualification of some opposition parties from the competition by concocting bogus charges, the expectation proved utterly naïve. It is now patently clear that the EPRDF will use all available means to preserve the status quo indefinitely.
Opposition parties are already variously reacting to the perceived decision to exclude them once again. Some areBoycotting Ethiopian National Elections making their participation conditional on the change of policy of the National Election Board toward a neutral stand guaranteeing a level of playing field. Others have decided to participate regardless of the prevailing conditions because they believe that nothing can be achieved by shunning the elections. Still others seem undecided or are waiting for the development of the situation before taking a definitive stance. This article analyzes the cons and pros of participating in the upcoming elections with the view of showing the realistic alternative that emerges from taking part in the elections or boycotting them.
Let us state plainly the emerging quandary. Admittedly, the goal of participation is not to win, not because the regime is popular and has the allegiance of the majority of voters, but because it will use threat, harassment, deceit, and even violence to retain its present position, which is that only one parliament member is representing the opposition. The opposition may even lose this one seat or add some more, but the retention of an overwhelming majority will be the inevitable outcome of the elections. If so, why then participate when there is no the slightest opportunity to perform better?

Expected Gains from Participation

Those who opt for participation argue that winning has many forms. Indeed, elections, even if they are unwinnable, provide a good opportunity to denounce the regime. They supply a convenient platform to openly expose the failures and injustice of the regime at a time when popular attention and expectations are activated by the government’s own propaganda and its desire for renewed legitimacy. Exposing the regime is a vital component of nonviolent opposition. It is inconsistent to stay away from elections because the regime in place does not allow a fair playing field even as the purpose of peaceful struggle is, precisely, to mobilize voters to protest against the unfair conditions of political competition. Only such protests can bring about change, not boycott.
Parties that participate in elections find a good opportunity to promote themselves and make their program known to the public. Not only does participation help the recruitment of new members, but it also engages the party in the typical task of organizing and mobilizing the people. A party that is absent from the battle field on the pretext that conditions are highly unfavorable does not deserve to be called an opposition party, all the more so as it came into existence primarily to fight for the democratic opening of the political system.
To encourage people to oppose the regime, it is imperative to show the availability of an alternative program. If people are not exposed to the ideas of a viable organization and alternative policy, their legitimate fear of the unknown, including the possibility of a chaos, will prevail over their frustrations and make them stick to the status quo. Nothing extends more the life of unpopular governments than the lack of an alternative: such governments will always claim that the opposition is fearful to participate because it is too weak or has no viable rival program. And nothing shortens more their existence than the presence of a party that continues to fight against all odds. So that, in willingly participating in elections that are decided in advance, the opposition party demonstrates its full commitment, thereby changing its alleged weakness into the strength of steadfastness.
There is no telling in advance whether participation does not result in the gain of some seats. However limited, seats in the parliament offer the opportunity of voicing opposition from within the system, not so much to change the ongoing policy as to give more credibility to the availability of an alternative path. Parliamentary representation officializes opposition in the eyes of the people as well as of the government, forcing the latter to respond to criticisms instead of simply dismissing them as the views of outcasts.
To sum up, participation in elections, even when they are completely unfair, is not devoid of appreciable gains. In addition to being consistent with the choice of nonviolent opposition, it provides a much needed forum for opposition parties to convey their messages, mobilize voters, and strengthen their standing. By contrast, the rejection of elections until acceptable conditions emerges is defeatist and inconsistent with peaceful opposition, not to mention that it obtains and change nothing.

Expected Gains from Non-Participation

Naturally, those who favor boycotting the elections are not without some expectations of gains as well. To the extent that their decision is a political one, it must contain the possibility of advancing their cause in some way. So what do they expect to achieve in shining the elections?
Their main argument is that non-participation of opposition parties deprives the government of the legitimacy that it seeks by organizing these elections. Participating without the chance of winning even one seat is nothing but a free gift to the government. In advertising the pitiful result of the opposition, the government will have the easy game of declaring a crushing victory and portraying the opposition as irrelevant, nonexistent.
To take part under the existing conditions is to encourage the government to continue the same electoral policy. The only leverage that opposition parties have is that the government wants popular legitimacy by all means so that it is suicidal to give it up for what is nothing but a staged show to fool the Ethiopian people as well as the international community. Since opposition parties cannot expect anything unless existing conditions change, the kind of pressure liable to yield some results is precisely to make their participations conditional on some concessions on the part of the government. For this pressure to succeed, there is one and only one condition: the boycott must be unanimous and firm.
Experience teaches us that taking part in the elections under existing conditions will not result in any gain of parliamentary seat. Recall what happened to the All Ethiopian Unity Party in the 2010 elections: it broke away from the rest of the opposition by agreeing to participate without any tangible reforms of the electoral process only to find out that it was unable to secure even one seat despite its undeniable popularity in the Amhara region. What is more, opposition parties that already had some seats were completely wiped out. Obviously, the refusal of the government to make changes in the electoral process is motivated by a deliberate policy of expulsion of the opposition, and not by the precaution of having a sizeable majority.
As to exposing the anti-democratic nature of the regime, what else is more resoundingly revealing it than the refusal to participate in fake elections? By openly stating that participation depends on the creation of a level playing field, opposition parties do their primary job, namely, the presentation of reasonable and expected demands that normally go along with the very idea of holding elections. If elections do not have a minimum of fairness, they cease to be elections and turn into an exercise of canonization. The least that opposition parties can do is to put an end to this quinquennial farce.

Critical Assessment

What is striking about the above position is the belief that the refusal to participate puts pressure on the government. It would have been so if the opposition were united and the boycott unanimous. But to expect unity and a unanimous position is to assume solved the very problem that keeps the TPLF in power. Those who speaks of pressure put the cart before the horse by forgetting that the persistence of the hegemony of the TPLF is due to the success of its divide-and-rule policy, essentially manifested by the ethnicization of Ethiopia. Moreover, I do not remember a case where this government changed its opinion because of popular protests, let alone because of complaints from opposition parties. In other words, as hard as it may seem to accept, opposition parties have no leverage on this government.
True, the government wants legitimacy, but it can obtain it in various ways. For instance, it can force people to vote in great number so as to compensate the lack of opposition parties with a massive popular endorsement. Dictatorial regimes have practiced and refined this method for quite some time. If at all costs the presence of an opposition is required, the government can create fake opposition parties or divide existing parties by means of threats and bribes. This should not come as a surprise since the government has already given us the taste of such methods, just as it is presently doing it by prohibiting two major opposition parties, namely, Unity for Democracy and Justice Party and All Ethiopian Unity Party.
Given these available recourses, we can say that the government wants legitimacy, but not to the point of making concessions to the opposition. All the more reason for saying so is that legitimacy is essentially sought to shore up its international reputation, especially in the eyes of donor countries. Unfortunately, we have seen time and again that foreign countries, including democratic countries, are more interested in doing business than in denouncing and punishing undemocratic regimes.
To demand repeatedly for something and repeatedly obtain nothing, to the extent that it reveals the absence of leverage on the government, is easily construed as a demonstration of insurmountable weakness and inability to emerge as an alternative. What else can the people conclude from this constant failure to put pressure on the government but the utter weakness and irrelevance of the opposition? Since the opposition cannot extract the slightest concession from the government, there is no reason for the people to side with the opposition and become the target of government retaliation. Voting for the government may not bring change but at least it protects against retaliation.
As a matter of fact, neither participation nor boycott adds anything to the goal of denunciation for the simple reason that the anti-democratic nature of the regime has long ceased to be a mystery to foreigners or natives. If we still find Ethiopians who are not aware of its real nature, such people are better left alone since they are either irremediably apolitical or indifferent to what is going around them.
What about mobilization and organization? Does participation, as claimed by those opposing boycott, serve to strengthen opposition parties? It would have been so if the government would allow freedom of expression and organization. Such disposition would mean that the government is ready to face opposition in a level playing ground. But the very dilemma over participation stems from the knowledge that the government will not allow a condition of fair competition, that it will paralyzed the opposition by restrictions, harassments, and imprisonments, not to mention the silencing of the free press. To expect the strengthening of the opposition as a result of participation is just a wishful thinking.
The likely outcome being that participation will not bring any result, it removes the grounds for complaint about the lack of democracy. Your participation was a defiance intent on showing that you can pierce the barrier of exclusion. Your failure to do so only exposes your weakness and irrelevance. The aim of the government is not to show its strength by winning elections; rather, it is to display overtly that it has no real rivals worthy of that name. It does not want to win majority votes; it wants to ridicule the opposition by a crushing victory, thereby showing that there is no alternative to its rule. The proper analogy expressing Ethiopian elections is two soccer teams competing with the players of one of the teams being blindfolded.
In fact, a clear pattern emerges from the manner the government deals with opposition parties. Plainly, the government steps up its repressive power when it confronts unitary parties, such as the Unity for Democracy and Justice Party and All Ethiopian Unity Party, while being more tolerant of opposition parties with an ethnic banner. In ruthlessly repressing unitary parties, the government wants to bring about their final demise. The relative tolerance of the government to ethnicized opposition parties is, for sure, due to the perception of some affinity with its own policy; more importantly, however, it originates from the conviction that ethnic parties, fragmented as they are, can never become a threat to the hegemony of the TPLF. Add to this that it is simply easy to create hostility between these parties and reduce them to the permanent status of a negligible opposition.
The real threat, if fair elections were held, comes from unitary parties, as demonstrated by the success of Kinijit in 2005. In the eyes of the TPLF, Ethiopian nationalist parties cannot be allowed to grow, for the real enemy to its hegemony–which rests on the efficient implementation of divide-and-rule policy–is none other than Ethiopian nationalism. It is amazing that more than 20 years of uninterrupted attack and stifling have not succeeding in weakening Ethiopian nationalism. It has become the forbidden fruit: the more you want to muffle it, the more people want it.

Who Wins?

What springs from all is clear enough: opposition parties, whether they participate or not, lose in that none of the projected goals ascribed to participation or boycott is achievable. Neither participation nor boycott affects the standing of the government or the state of opposition parties in any meaningful way. Does this mean that the government win?
One thing is sure: after the elections, the government will not be better off. Not only will it face the same problems, but also its intransigence and repressive policy will heighten popular frustration and instill the sense of a political deadlock in the county. In other words, there is no winner, but only a huge loser, namely, nonviolent, peaceful opposition. Seeing the complete ineffectiveness of participation or boycott, people, especially the young, are increasingly bound to question the wisdom of peaceful opposition. The more repression continues, the more the deadlock over the possibility of change thickens, and the higher becomes the disposition toward uprising as the only alternative left. This is the iron law of all social blockage: Ethiopia will not be an exception.
When uprising becomes the only way out, young activists go underground or join armed struggle. Exciting nonviolent parties, too, to the extent that they are serious about the struggle for change, will be compelled to have a hard look at their strategy. Even if they continue to operate in a legal manner, it is no longer to win seats in the parliament. Instead, they anticipate uprising and hope to take its leadership when it erupts. Without doubt, the present attitude of the TPLF gives Ethiopians no other choice than revolution with, alas, the unpredictable but certainly severe and uncontrollable consequences that confrontation or civil war will have in present-day Ethiopia. Ethiopians, gear up for the worst!