Monday, November 24, 2014

“ምስጢር ካወጣህ ቤተሰቦችህን እንፈጃቸዋለን” “ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል”

November 24,2014


“የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል”
ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ በዝዋይ እስር ቤት ለወራት ስቃይ የተፈፀመበት

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ይባላል፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ አዳማ/ናዝሬት አድጎ፣ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት የመንግስት ደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ ከወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ጋር ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉን፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- ማን ነበር ያሰረህ?

ወጣት ተስፋዬ:- ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በማለዳ ቤቴ ተንኳኳ፤ ተነስቼ ከፈትኩኝ፡፡ የማላውቃቸው ሰዎች ናቸው፡፡ “ና ውጣ፤ ልብስህን ለብሰህ ውጣ” አሉኝ፡፡ እኔ እናቴ ሞታ ሊያረዱኝ የመጡ መስሎኝ “ምነው ቤተሰብ ደህና አደለም? የተፈጠረ ችግር አለ?” አልኳቸው “ዝም ብለህ ናውጣ” አሉኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩኝና ወጣሁ፤ አንቀው መኪና ውስጥ ከተው ወደ ማዕከላዊ ወሰዱኝና 3 ወር አሰሩኝ ከዛም አንድ አመት ከ8 ወር ዝዋይ ማረሚያ ቤት፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- መታሰርህን ለቤተሰብ ተናግረሀል?

ወጣት ተስፋዬ:- ለማንም ሰው እንድናገር አልፈቀዱልኝም፤ መስሪያ ቤቴ አልጠየቀኝም፣ ደሃዋ እናቴ ያለችው ናዝሬት ነው እሷም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ አባቴ አቶ ተካልኝ አስተማሪ ነበር አርባ ጉጉ ላይ ነው በ1985 ዓ.ም በነበረው ግጭት ነው የተገደለው፡፡ ማንም ሳይጠይቀኝ፣ፍ/ቤት ሳልቀርብ 23 ወር ታሰርኩ ልብስ ምግብም የሚያመጣልኝ ሰው አልነበረም፡፡ እናቴም መታሰሬን እንኳ አታውቅም መስሪያ ቤቴም ስኮላርሽፕ አግኝቷል፤ ወደ ውጪ ሃገር ሊማር ሊሄድ ነው የሚባል ነገር ስለነበረ አልጠየቁኝም፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የት ነበር ስኮላርሺፕ ያገኘኸው?

ወጣት ተስፋዬ:- የዛሬ 2 ዓመት አካባቢ የራስመስ ሙንደስን ስኮላርሽፕ አግኝቼ ነበር፡፡ ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ካሊፎርኒያና ከዩኒቨርስቲ ኦፍ ቶክዮ ባሉ ምሁራን ሪኮመንድ ተደርጌ በጣሊያኑ ፌራሪ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ተዘጋጅቼ ነበር፡፡ እንደተፈታሁ ሄጄ ስጠይቃቸው ብዙዎቹ ጓደኞቼ በጣም ደነገጡ፡፡ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ቅማል ተወርሬ … ባካችሁ ተውኝ … ምንም የሌለ ነገር የለም በጣም ተጎድቻለሁ፡፡ ከማረሚያ ቤት እንደወጣሁ እናቴ ጋ ስሄድ በጣም ደነገጠች፣ በሕይወት ያለሁ አልመሰላትም 23 ወር ሙሉ ከቤተሰብ ስለተለየሁ ግራተጋባች፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በእስር ወቅት የደረሰብህ ድብደባና ማሰቃየት ነበር?

ወጣት ተስፋዬ:- ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ በኤሌክትሪክ ጀርባዬ ላይ አቃጥለውኛል፣ በብልቴ ላይና በኩላሊቴ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ስላደረሱብኝ ሽንት ችዬ አልሸናም፣ ሽንቴን መቆጣጠርም አልችልም፡፡ ኩላሊቴንም በጣም ያመኛል፡፡ ውሃ ውስጥ እየነከሩ በጣም ደብድበውኛል፡፡ አሁን ስናገር ያመኛል ብዙ አይነት የድብደባና የስቃይ መአት ደርሶብኛል፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እንደው ስታስበው ለእስር ያበቃህ ወይም ከመንግስት ጋር ያጋጨህ አጋጣሚ ነበር?

ወጣት ተስፋዬ:- መስሪያ ቤቴ ውስጥ የኢህአዴግ አባላት ነበሩ፤ በጣም ይከታተሉኛል፡፡ በቢ.ፒ.አር ላይ ስብሰባ በተደጋጋሚ ይጠራ ነበር፡፡ እኔም ሠራተኛ ላይ ተፅእኖ የሚያደርሱ ነገሮች ሲመጡ እኔ አልቀበልም በግልፅ እናገር ነበር፤ ሠራተኛውም እኔን ይደግፋል፡፡ ከመታሰሬ ጥቂት ጊዜ በፊት ገነት ሆቴል ስብሰባ ነበረን፡፡ በዛ ስብሰባ ላይ በጣም ተከራከርኩ፤ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር አቶ ፀጋዬ ማሞ የሚባሉ አሰልጣኝ፣ ከውጭ ጉዳይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና ከንግድና ኢንዱስትሪም የመጡ ነበሩ ስማቸውን የማላስታውሳቸው ባለስልጣን ነበሩ፤ እዛ ላይ ሀሳብ አንስቼ ተከራክሬ ነበር፡፡ “የሠራተኛን ሀሳብ ዳይቨርት ያደርጋል” ይሉኝ ነበር፡፡ መቼም ግን ሀሳቤን በመናገሬ ይህን የመሰለ ስቃይ ይደርስብኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ “አሸባሪ፣ ግንቦት ሰባት” እያሉ እኔ በማላውቀው ነገር 23 ወር ሙሉ ፍርድ ቤት ሳልቀርብ ያለምንም ፍርድ በርሜል ውስጥ ውሃ ጨምረው እያስተኙ አሰቃዩኝ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እንደዚህ ያሰቃዩህ ምን አይነት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ ነው?

ወጣት ተስፋዬ:- እኔን ጥፋተኛ የሚያስደርግ ምንም መረጃ አላገኙም፣ እኔን አስረው ወደ መስሪያ ቤት በተደጋጋሚ ይደውሉ እንደነበር ይነግሩኝ ነበር፡፡ የኢሜይል አድሬሴንም ተቀብለው በርብረዋል ግን ምንም አላገኙም፡፡ እኔ ከማንም ጋር ሊንክ የለኝም ኢሜሌ ላይ የስኮላርሺፕ መልዕክት ካልሆነ በስተቀር ምንም የለውም፡፡ በመስሪያ ቤቴ ሪሰርቸር ነበርኩ፣ በሶሲዮሎጂ ነው የተመረኩት፡፡ ሉሲ የተገኘችበት ሣይት ላይ አፋር፣ ጋምቤላ ብዙ ሳይቶች ሰርቻለሁ፡፡ ከአለቆቼ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሰላማዊ ነው እነሱ ናቸው ስኮላርሽፕ ሪኮመንድ ያደረጉኝ፡፡ አንደኛው ፕሮፌሰር 25 ዓመት ሙሉ እዚህ አገር ሰርቷል፣ አርዲን ያገኘው እሱ ነው፡፡ ሄነሪ ጊልበርት ይባላል፤ እሱም ሪኮመንድ አድርጎኛል፡፡ እኔ በጣም የሚቆጨኝ ደሃዋ እናቴ አረቄና ጠላ ሸጣ ነው ያስተማረችኝ ምን ብዬ ልንገራት እንደዚህ አትጠብቀኝም ከበደኝ፣ አሁን እሷ የምትሰጠኝ ምግብ ራሱ ደምደም አለኝ… (ረጅም ለቅሶ)፡፡ ልጄ በደህናው አይደለም የጠፋው ሞቷል ወይም መኪና ገጭቶታል ብላ ነበር የምታስበው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- የከመታሰርህ በፊት ፖለቲካ ተሳትፎ ነበረህ?

ወጣት ተስፋዬ:- 1997 ዓ.ም የቅንጅት ደጋፊ ነበርኩ፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበርኩ በ97 የነበረው ሁኔታ ስንት ሰው አለቀ በጣም ተስፋ አስቆራጭ ነበር ታውቃላችሁ ምንም የምናደርገው ነገር አልነበረም ፡፡ በምርጫ አሸንፎ ሥልጣን መያዝ እንደማይቻል ተረዳሁኝ፡፡ ከ1997 ዓ.ም በኋላ የማንም የፖለቲካ ፓርቲ አባል አልሆንኩም፡፡ ከዚህ በኋላ ከምንም ነገር የተገለልኩ ሆኛለሁ፡፡ አንድ ብርጭቆ ሳትሰብር አሸባሪ ስትባል አስብ እንግዲህ አንድ ብርጭቆ እንኳን ሰብሬ አላውቅም ባለኝ እውቀት እንደውም ለእውቀት ነው የምጓጓው እውቀቴን አሳድጌ አገሬን ለመለወጥ ነው የማስበው እኔን ምንም የሚመለከተኝ ነገር የለም አሸባሪም ግንቦት ሰባትም አይደለሁም፡፡ስትደበደብ፣ ስትሰቃይ ያላደረከውን አድርጌያለሁ ትላለህ፤ በርሜል ውሃ ሞልተው ይከቱሃል ያሰቃዩሃል፡፡ አያሳዝንም ይሄ? እንዴት አድርጎ እዚህ አገር ይኖራል? 23 ወር ሙሉ አስረው ማሰቃየታቸው ሳያንስ የደረሰብኝን ስቃይ ለማንም ብናገር ቤተሰቦቼን በሙሉ እንደሚፈጁ አስጠንቅቀውኛል፡፡ እኔ ግን ከዚህ በላይ ሞት የለም ብዬ ነው የነገርኳችሁ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- አሁን የት ነው የምትኖረው?

ወጣት ተስፋዬ:- መኖሪያ የለኝም … (ረጅም ለቅሶ)

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝን ለመርዳት የምትፈልጉ አንባብያን ከፍኖተ ነፃነት መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ (ምንጭ ፍኖተ ነጻነት)

ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው

November 24,2014
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡

Photo: ለስብሰባ ሲቀሰቅሱ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ተጨማሪ 7 ቀናት ተቀጠረባቸው

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ጠርቶት ለነበረው የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ አርብ ህዳር 5/2007 ዓ.ም በቅስቀሳ ላይ እንደነበሩ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ 7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ ም/ሰብሳቢና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ማቲያስ መኩሪያ እና የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል ወጣት ሳምሶን ግዛቸው በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው አራዳ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ ሲሆን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ወጣቶቹ ‹‹ሽብር በማነሳሳት›› የሚል ‹ክስ› የተመሰረተባቸው ሲሆን ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ሌሊት ደህንነቶች በተደጋጋሚ በኃይልና በዛቻ እንደሚመረምሯቸው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

ባለፈው የፍርድ ውሎ ታሳሪዎቹ ህጋዊ እውቅና ለተሰጠው ስብሰባ የቀሰቀሱ መሆኑን ጠቅሰው መታሰራቸው ህገ ወጥ በመሆኑ እንዲፈለቀቁ ቢከራከሩም፤ ፖሊስ ‹‹ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ስላልተያዙ መያዝ አለብን፡፡ እነሱም ከተለቀቁ መረጃ ያጠፉብናል›› በሚል የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተቀባይት አግኝቷል ለዛሬ በቀጠሯቸው መሰረት ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ አንድ ሳምንት ጊዜ ለፖሊስ ፈቅዶለታል፡፡ በአንጻሩ ታሳዎቹ የቀረቧቸው ቅሬታዎችና መከራከሪያዎች ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡

Sunday, November 23, 2014

በሰሜን ጎንደር የሕወሓት አማሳኞች ሰርገው የበመግባት ወጣቱን እያጋደሉ መሆኑ ተሰማ

November 23,2014
-ከከተማው ለስራ የሄዱ ወጣቶች ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ አከባቢውን ለቀዋል
ሚኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው በኢትዮ ሱዳን ድንበር ላይ ለስራ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን መንደር እየለዩ በመቧደን በከፍተኛ ጭፍጭፍ ውስጥ እንደሚገኙ ከአከባቢው የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል::

ከሱዳን ጋር በተያያዘው እና የታች አርማጮ መሬት ከሆነው ሰቲቱ ሁመራ ማይካድራ ሉግዲ አብዲራፍ አብድራሃጀር መተማ ሸዲ የተወሰነውን ጠገዴ ያሉት የጎንደር መሬቶች ላይ በኢንቨስትመንት ስራ ላይ የተማሩ የሕወሓት አባላት የሆኑት የጊዜው ባለሃብቶች በቀተሯቸው እና ከአማራው ክልል ጎንደር ጎጃም እና ወሎ የመጡ ወጣት ገበሬዎችን እርሲ በራስ በመንደር እና በጎጥ በመከፋፈል እንዲተራረዱ እንዲጨራረሱ የሰሩበትን ገንዘብ ሳይሰበስቡ አከባቢውን በፍርሃት ለቀው እንዲሄዱ እያደረጉ መሆኑን መረጃዎቹ የሰሞኑን ከፍተኛ ግጭት አስመልክተው ጠቁመዋል::
በሉግዲ አከባቢ በዚህ ሰሞን ብቻ በጎንደር እና በጎጃም በወሎ እና በሸዋ በሚል የተቧደኑ ሰዎች በሕወሓት ኢንቨስተሮች ነገር አስፋፊነት ከፍተኛ ግጭት በመከሰቱ በርካታ ወጣቶች የተገደሉ ሲሆን ቀሪዎቹ ንብረታቸውን እና ገንዘባቸውን ሳይሰበስቡ ድንገት ግጭቱን ሸሽተው ወደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የሄዱ መሆናቸው ታውቋል::
የሕወሓት አማሳኞች እና ሰላዮች በወጣቶቹ መካከል ሰርገው በመግባት እሪስ በ እርስ ጎጥና መንደር እንዲለይ አድርገው በማቧደን እርስ በ እርስ ሕዝቡ እንዲተራረድ አድርገዋል ሲሉ ምንጮቹ በላኩት መረጃ ተናግረዋል::በዚህ ሳምንት ብቻ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ሬሳዎች ወደ ሉግዲ ከተማ የተጓጓዙ ሲሆን ይህ የሕወሓት ሰላዮች/አማሳኞች የሚቀሰቅሱት የሰርጎ ገብነት ዝሴራ እስከ ማይካድራ ድረስ ተስፋፍቶ ከፍተኛ የደም መፋሰስ እና የዘር መጠፋፋት እየተደረገ መሆኑን አክለው ገልጸዋል::

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

November 23,2014
በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። እነዚህን ነገሮች የወያኔ መሪዎችም ያደርጋሉ፤ ነገር ግን በወያኔና በሌሎቹ አምባገነን አገዛዞች መካክል እጅግ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ። ለምሳሌ ወያኔዎች ዘረኛ አምባገነኖች ናቸዉ፤ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥገት ላም አንጂ እንደ አገራቸዉ አይመለከቱም። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያን፤ ህዝቧንና ታሪኳን ይንቃሉ፤ ያንኳስሳሉ።
ባለፉት አምስትና ስድስት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፋናቅለዉ ለምለም መሬቱን ለባዕዳንና ለህወሓት የጦር መኮንኖች ሰጥተዋል። መሬቴንና ቤቴን አልለቅም ብሎ የተቀናቀናቸዉን ደግሞ በጅምላ ገድለዋል። በከተሞች ዉስጥም ከተሜዉን ምንም ካሳ ሳይከፍሉት ዕድሜ ልኩን ከኖረበት ቤቱ እያፈናቀሉ ከነቤተሰቡ ሜዳ ላይ ጥለዉት መሬቱን ባለኃብት ለሚሏቸዉ የወያኔ ባለሟሎች ሰጥተዋል። በአጠቃላይ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ አንድነት፤ በታሪኳና በህዝቧ ላይ እንዲህ ነዉ ተብሎ ለመናገር የሚዳግት ትልቅ በደል ፈጽመዋል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በእናት አገራችን ላይ ያደረሱት በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለምና ዛሬ ወደዚያ ዝርዝር ዉስጥ አንገባም፤ ዛሬ ትኩረት የምንሰጠዉ ወያኔ ደግሞ ደጋግሞ ከዘመተባቸዉና ሙሉ ኃይሉን ካሳረፈባቸዉ የአገራችን እሴቶች አንዱ ታሪካችን ነዉና የዛሬዉ ቆይታችን በዚሁ በታሪካችን አካባቢ ይሆናል።
ታሪክ በአንድ አገር ዉስጥ እያንዳንዱ ትዉልድ ከሱ የቀደመዉ ትዉልድ በግል፤ በቡድንና በማህበረሰብ ደረጃ የተጓዘበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ካለፈዉ የምንማርበትና የወደፊቱን ጉዟችንን ለመጀመር በመረጃነት የሚያገለግለንን እዉቀት የምናገኝበት የጥበብ ድርሳን ነዉ። የማንም አገር ታሪክ ዉብ ሆኖ የሚያምርና የማያምር ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ የማያምረንን የታሪክ ጠባሳ ወደ ኋላ ሄደን ማከም በፍጹም እንደማንችል ሁሉ የወደፊቱን ታሪካችንንም የብዙ ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ዉጤት ነዉና ያሰኘንን ቅርጽና ይዘት ልንሰጠዉ አንችልም። የታሪክ ዋናዉና ትልቁ ቁም ነገር የታሪኩ ባለቤት የሆነዉ ማህብረሰብ እራሱን ወደ ኋላም ወደ ፊትም የሚመለትበት መስኮት መሆኑ ነዉ። ምንም አይነት ታሪክ የሌለዉ ህብረተሰብ የለም፤ ካለም ከየት አንደመጣና ወዴት አንደሚሄድም አያዉቅም።
አገራችን ኢትዮጵያ ረጂምና ጥንታዊ ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት። ይህ ረጂም ታሪካችን ደግሞ አንገት ቀና የሚያስደርግ የድልና የገድል ታሪክ አንደሆነ ሁሉ አንገት የሚያስደፋ የግፍና የበደል ታሪክም አለበት። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ካለፈዉ ታሪኩ ከበደሉም ከገድሉም ተምሮ የወደፊት አካሄዱን ከሞላጎደል መቆጣጠር የሚችል እድለኛ ትዉልድ ነዉና አባቶቹ ባቆዩለት ታሪክ ሊኮራ ይገባል። አንድ ህዝብ በታሪኩ እንዲኮራ ደግሞ ታሪኩ በተደጋጋሚ ሊነገረዉ ሊተረክለትና በጽሁም መልክትም በገፍ ሊቀርብለት ይገባል። የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ለዚህ የታደለ አይደለም ፤ ምክንያቱም እንመራሀለን የሚሉት መሪዎቹ ታሪኩን የሚያንቋሽሹና የሚንቁ መሪዎች ናቸዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ካደረሱትና ዛሬም በማድረስ ላይ ካሉት በደሎች አንዱና ዋነኛዉ የኢትዮጳያን ታሪክ ለባዕዳንና የታሪኩ ባለቤት ለሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ አሳንሰዉና እንደ ተራ ዕቃ አቃልለዉ ማቅረባቸዉ ነዉ። የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ መጀመሪያ ከተናገሯቸዉ ንግግሮች አንዱ የኢትዮጵያን ህዝብ ታሪክ የመቶ አመት ታሪክ ነዉ ያሉት አስቀያሚ ንግግር ነዉ። በዚህ አባባል ላይ የጸና አቋም ካላቸዉ የወያኔ መሪዎች ዉስጥ ዛሬ በህይወት የማይገኘዉ መለስ ዜናዊና ጓደኛዉ ስብሐት ነጋ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ። የሚገርመዉ እነዚህ የኢትዮጵያን ታሪክ በአንድ መቶ አመት የወሰኑት ሁለት ግለሰቦች የተወለዱት የኢትዮጵያ ህዝብ የዛሬ 119 አመት በአፄ ሚኒልክ መሪነት ወራሪዉን የጣሊያን ጦር አይቀጡ ቅጣት በቀጡበት አድዋ ዉስጥ ነዉ።
ወያኔ ካለፈዉ መስከረም ወር ጀምሮ ባደበዘዘዉ ቁጥር እያሸበረቀ ያሰቸገረዉን የኢትዮጵያ ታሪክ ለማቆሸሽ ጠባሳዉ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ የክፋት ስራ እየሰራ ነዉ። ኢትዮጵያን የመሰለ ባለታሪክ አገር ገድሎ ለሞተዉ ዘረኛ ሰዉ ትልቅ ማዕከል በህዝብ ገንዘብ የሚያሰሩት የወያኔ መሪዎች ማስቀመጫ ቦታ ጠፋ እያሉ አያሌ ብርቅ የሆኑ የኢትዮጵያ ታሪክ መጽሀፍትን ከወመዘክር አይወጡ በችርቻሮ እየሸጡ ነዉ። እነዚህ ወያኔ የሚሸጣቸዉ መጽሐፍት የተጻፉት በተለያዪ ዘመናት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዉ በነበሩት የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይ፤ የጣሊያን፤ የስፔንና የጀርመን የታሪክ ጸሐፊዎች ነዉ። ከሰሞኑ ከአዲስ አበባ የሚመጡ ዜናዎች እንደሚያመለክቱት ወያኔ በዉጭ አገር የታሪክ ጸሐፊዎች የተጻፉትን የታሪክ መጽሐፍትና ተጠረዝዉ የተቀመጡ ቆየት ያሉ ጋዜጣዎችን በርካሽ ዋጋ እየቸበቸቡ የግሮሰሪ ዕቃ መጠቅለያ አድርጓቸዋል።
ይህንን አሳፋሪ የሆነ የወያኔ የመጽሐፍ ሽያጭ እንደ ተራ ወንጀል የምናልፍ ኢትዮጵያዉያን ካለን እጅግ በጣም ተሳስተናል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የሚሰሩትን ስራ አበክረዉ የሚያዉቁ ሰዎች ናቸዉ፤ እያሰሩ ያሉት ስራ ደግሞ ግልጽ ነዉ። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የተጻፈ ታሪካችንን ብቻ ሳይሆን እያወደሙ ያሉት ባህላችንን፤ ወጋችንንና ቅርሶቻችንን ጨምር ነዉ እንዳልነበረ ያደረጉት። ለምሳሌ በብዙ የአለም አገሮች ዉስጥ ረጂም ዕድሜ ያስቆጠሩ ህንፃዎች፤ የታሪካዊ ሰዎች መኖሪያ ቤቶችና የተለያዪ የአገር ቅርሳቅርሶች ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸዉ ከዘመን ወደ ዘመን እንዲተላለፉ የደረጋል። ኢትዮጵያ ወስጥ ግን ዕድሜ ለወያኔ ከፍተና ታሪካዊ እሴት ያላቸዉ ህንፃዎች በልማት ስም እንዲፈርሱ ይደረጋል። የጀግኖችን አጽም ያረፈበት የመቃብር ቦታም በግሬደር እየተደረመሰ የንግድና የችርቻሮ ቦታ ይሆናል።
ሌለዉ ወያኔ በታሪካችን ላይ የሚያደርሰዉ ጥፋት ታሪካችንን እንዳንማርና የታሪክ ተማራማሪዎቻችን በጥንታዊ ታሪካችን ላይ ምርምር እንዳያደርጉ እጅና እግራቸዉን ማሰሩ ነዉ። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ የሚገኛዉ የታሪክ ዲፓርትመንት የኢትዮጵያን ታሪክ ማስተማር ብቻ ሳይሆን ታሪካችንን ከተለያየ አቅጣጫ በማጥናትና ምርምር በማድረግ ለታሪካችን መበልጸግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ተቋም ነዉ። ሆኖም ይህ በተለያዪ መንግስታት ዉስጥ ለረጂም አመታት ትልቅ ስራ ሲሰራ የቆየዉ የታሪክ ዲፓርትመንት ዛሬ አለ ተብሎ መናገር በማይቻልበት አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ የቀድሞ ታሪካችንን እያወደመ የሚቀጥለዉን ታሪካችንን ደግሞ በራሱ አቅጣጫ እያጣመመ በመጻፍ ላይ መሆኑን ነዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ታሪክ አስመልክቶ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ የተጻፈዉ በተወሰኑ ሰዎች ከአንድ አቅጣጫ ብቻ ነዉ ሲሉ በሌላ በኩል ደግሞ የረጂሙን ዘመን የአገራችን የኢትዮጵያ ታሪክ ከአንድ ሞቶ አመታ የበለጠ ዕድሜ የለዉም እያሉ በተደጋጋሚ ተናግረዋል። ዛሬ በገፍ ለጨረታ ያቀረቧቸዉ የታሪክ መጽሐፍት ቁልጭ አድርገዉ የሚናገሩት ደግሞ ታሪካችን ከ3000 ሺ አመታት በላይ መሆኑንና የተጻፈዉም በተወሰኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆን በተለያዪ ኢትዮጵያዉያንና የዉጭ አገር ሰዎች ጭምር መሆኑንደ ነዉ። ዛሬ ወያኔ እንደ ርካሽ ዕቃ እያወጣ የሚቸበችባቸዉ መጽሀፍት ለዚህ አሳዛኝ ዕጣ የበቁት ይህንን የወያኔ አይን ያወጣ ዉሸት ስለሚያጋልጡ ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያን እንወዳለን የምንል ኢትዮጵያዉያን በሙሉ ይህ በአፋችን ሁሌም የምንለዉ ቃል በተግባር የምንተረጉምበት አጋጣሚ ፊት ለፊታችን ላይ ተደቅኗል። ኢትዮጵያ አንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች ወያኔ ባነደደዉ ረመጥ እሳት እየተለበለበች ነዉ። ይህንን እሳት ማጥፍትና አገራችንን ከወያኔ መታደግ ካለብን ግዜዉ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነዉ።
አያሌ ኢትዮጵያዉያን የወያኔን የመጽሐፍ ሽያጭ አስመልክቶ የወሰዱትን ቆራጥና ብልህ እርምጃ ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነጻነትና፤ የዲሞክራሲ ንቅናቄ እጅግ በጣም ያደንቃል። በአዲስ አበባና በአካባቢዋ የሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን የአገርና የወገን ሃላፊነት ተሰምቷቸዉ ወያኔ ለጨረታ ያቀረበዉን መጽሐፍ በመግዛት የአገራቸዉን ታሪክ ለመታደግ ያደረጉት ጥረት በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ አገራዊ ስራ ነዉ። አገራችን ዛሬ ባለችበት ሁኔታ ነገ አትገኝም የሚል እምነታችን የጸና ነዉና እነዚህን የገዛችኋቸዉን መጽሀፍት በጥንቃቄ በመያዝ ሀላፊነትና የአገር አደራ ለሚሰማዉ በህዝብ የተመረጠ መንግስት አንድታስረክቡ አደራ እንላችኋለን። ከአሁን በኋላም ቢሆን የወያኔን ፀረ አገርና ፀረ ህዝብ ስራ እየተከታተላችሁ እንድታከሽፉና በሚያልፈዉ ህይወታችሁ የማያልፍ ታሪክ ሰርታችሁ ወያኔን በማሰወገዱ ዘመቻ ዉስጥ ሙሉ ተሳትፎ አንድታደርጉ አገራዊ ጥሪ እናስተላለፋለን።

Saturday, November 22, 2014

30 ደቂቃዎችን በዝዋይ እስር ቤት (ግዞት)

November 22,2014
‹‹በብርቱ ታምሜያለሁ›› አበበ ቀስቶ
በላይ ማናዬ
ዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በቦታው ተገኝቼ ለመጠየቅ እቅድ ከያዝኩ ረዘም ያሉ ቀናት አልፈዋል፡፡ እንዲያውም ጉዞው ከወዳጆቼ ጋር ሰብሰብ ብለን ቢሆን እንደሚመረጥ ተነጋግረንበት ነበር፡፡ ሆኖም ግን የዕለት ከዕለት ሩጫችን አላወላዳ ብሎን ባቀድነው ጊዜ ወደ ዝዋይ መጓዝ ሳንችል ቆይተናል፡፡ አርብ ህዳር 12/2007 ዓ.ም ግን እንዳሰብነው ሰብሰብ ብለንም ባይሆን በመጨረሻ አብሮኝ ከተጓዘው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ባልደረባ ወጣት ፍቅረማርያም አስማማው ጋር ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስተን ወደ ዝዋይ አምርተን ለ30 ደቂቃዎች ያህል የናፈቅናቸውንና የናፈቁንን እስረኞች ልንጎበኝ በቅተናል፡፡

ዝዋይ ለመድረስ ከ2 ሰዓት በላይ ጉዞ ማድረግ ነበረብን፤ በጠዋት ቃሊቲ መነሐሪያ በመገኘት የዝዋይን ትራንስፖርት ለመያዝ ስንገኝ መልካም አጋጣሚ ተከሰተ፡፡ አጋጣሚው እኛ ወደምንሄድበት ዝዋይ እስር ቤት ሊሄዱ የተሰናዱትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እና ሌላ የስራ ባልደረባውን ያገናኘ ነበር፡፡ ቁጥራችን መጨመሩ ለእኛም ለምንጠይቃቸው እስረኞችም መልካም ነበር፡፡

ከተማዋ እንደደረስን ወደ አንድ አብረውኝ የተጓዙት ወዳጆቼ የሚያውቁት ቤት አመራን፤ ቡና በፔርሙስ ለመያዝ፡፡ ‹‹ተመስገን ደሳለኝ በእጅጉ ቡና ይወዳል አለኝ›› ታናሽ ወንድሙ፡፡ ቡናውን አስቀድተን ከከተማዋ ትንሽ ወጣ ብሎ ወደሚገኘው እስር ቤት አመራን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጋሪ ነበር፡፡ ወደእስር ቤት የሚወስደው መንገድ እጅግ አቧራማ በመሆኑ ተጓዦች አቧራውን መልበሳቸው እሙን ነው፡፡ በእግር ለመጓዝ የፈቀደ ካለ ድልህ ቲባን በጫማዎቹ ልክ ይዋኝበታል፡፡ የእኛ ጉዞ በጋሪ ቢሆንም ከአቧራው ማምለጥ ግን አይቻልም፡፡

እስር ቤቱ በር ደርሰን ከጋሪ እንደወረድን ወደጥበቃዎቹ ቀርበን የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስም ሰጥተን የእኛን ሙሉ አድራሻ አስመዘገብን፡፡ የምንጠይቃቸውን እስረኞች ስናስመዘግብ ‹‹ምኑ ነህ?›› የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…እያልን አስሞላን፡፡ መዝጋቢ ፖሊሶቹ ቀና እያሉ በጥያቄ ያዩናል፡፡ ኢትዮጵያውያን ወገኖች ‹ጓደኛ፣ ወንድም፣ ዘመድ…› ተብለው እንጂ ሌላ በምን ይገለጻሉ ታዲያ! በዚህ መሰረት የአራት እስረኞችን ስም አስመዘገብን፤ እነሱም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ናቸው፡፡ ጥብቅ ፍተሻውን አልፈን ልናያቸው የጓጓንላቸውን እስረኞች ወደምንገናኝበት ቦታ አመራን፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ቦታው ላይ ስንደርስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሶስት ፖሊሶች ተከብቦ ቀድመውን ከደረሱ ወዳጆቹ ጋር እያወራ ነበር፡፡ ከአጥር ወዲህ እና ወዲያ ማዶ ሆነን ግማሽ አካል ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ ደስ አለን፤ ተመስገንም ደስታው በመላ ፊቱ ሲበራ ተመለከትን፡፡ በደስታው ድጋሜ ደስ ተሰኘን፡፡ በእኛ በኩል ትንሽ ስለ ጤንነቱ፣ በእሱ በኩል ስለቤተሰብ እና ስለእኛ ደህንነት ተጠያየቅን፡፡ በመካከላችን ትንሽ ዝምታ ሰፈነ፡፡ እኛም ተመስገንም ቀና ብለን ፖሊሶችን ተመለከትን፡፡ ከዚያም ተመስገን ጥያቄ ወረወረ፡፡

‹‹ውጭ ያለው እንዴት ነው? አንድነትና ሰማያዊ….›› ተሜ የጀመረውን ሳይጨርስ ሁለቱ ፖሊሶች አንባረቁብን፡፡
‹‹ፖለቲካ አታውራ! እናንተ ፖለቲካ አታውሩ! ዝም ብላችሁ ሌላ ሌላ አውሩ!...›› አሉን ፖሊሶች አንዴ እኛን አንዴ ከአጥር ማዶ የተቀመጠውን ተመስጋንን እየተመለከቱ፡፡ የፖለቲካ ድርጅቶችን ስም መጥራት ፖለቲካ ማውራት ሆኖ ተሰማቸው፣ እዚያ ለነበሩ ፖሊሶች፡፡ የአንድነትን እና የሰማያዊን ስም ጠርቶ ተሜ ምን ሊያወራ እንደፈለገ እንኳ ለመስማት አልተዘጋጁም፡፡ በየዕለቱ መረጃ የሚያነፈንፍ፣ ያገኘውን መረጃ ደግሞ ወደህዝብ የሚያደርስ ሙያ ላይ እንደነበር ለእነሱ አልገባቸውም፡፡ አዎ መረጃ ምን ያህል እንደሚርብ ለፖሊሶቹ የተገለጸላቸው አልመሰለኝም፤ ለዚያውም ለጋዜጠኛ፡፡

ተሜ ጋር ልናወራ ያሰብነው ብዙ አብይ ጉዳዮች ቢኖሩም ክልከላው የሚያወላዳ አልሆነም፡፡ በበኩሌ በኋላ ተመስገን ላይ ሊያደርሱበት የሚችሉት ጫና ይኖራል ከሚል ርዕሱን መቀየሩን መርጬ ነበር፡፡ ተመስገን ግን ‹‹እናውራበት›› በሚል ትንሽ ከፖሊሶቹ ጋር ተከራከረ፡፡ ተሜ ድፍረቱ በብዕሩ ብቻ አይደለም፡፡ መብቱን ለማስከበር ወደኋላ የማይል ብርቱ ሰው መሆኑን ከሁኔታው አነበብኩ፡፡

በመሐል ላይ ሌሎች እስረኞችን እንዲጠሩልን ስም ዝርዝር ሰጥተን ስለነበር ሲዘገዩ ጊዜ ‹‹እነ ክንፈሚካኤልና አሳምነውን ጥሩልን እንጂ!›› አልናቸው፡፡ አንደኛው ፖሊስ ቆጣ ብሎ ‹‹ቆይ እሱ ጋር ጨርሱ!›› አለን፡፡ ከተመስገን ጋር ያለንን ቆይታ ማለቱ ነበር፡፡ እኛም እስኪመጡ እንደምንጨርስ በመጥቀስ አስጠሩልን አልናቸው፡፡ በዚህ መሐል ትንሽ ጭቅጭቅ ድጋሜ ተፈጠረ፡፡ ‹‹እንዲያውም ስማቸውን በትክክል አልጻፋችሁም፤ ስለዚህ አንጠራላችሁም አሉን፡፡›› እኛም የሰጠናቸውን የስም ዝርዝር የጻፉት የራሳቸው ባልደረቦች እንጂ እኛ አለመሆናችንን ጠቅሰን ነገርናቸው፡፡

ካፈርኩ አይመልሰኝ በሚመስል መልኩ አንጠራላችሁም አሉን፡፡ ‹‹በቃ አምጣው እንደገና አስተካክለው እንዲጽፉ አድርገን እናምጣው!›› አልናቸው፡፡ በእርግጥ ትክክለኛ ምክንያታቸው የስም ስህተት እንዳልሆነ እናውቅ ነበር፡፡ ሲጀመር አሳምነው ፅጌን ከእኛ ከወጣቶች ይልቅ እነሱ ከበረሃ ጀምረው ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ ስለሆነም ‹‹እገሌ የሚባል ሰው የለም፤ እዚሁ ተወለደ ካላላችሁን›› እያሉ ሲናገሩ በውስጤ እየሳቅሁ ነበር፡፡ እንዲያውም፣ ‹‹አዲስ ታሰረ ካላላችሁ በቀር አዲስ እንደማይወለድ ታውቃላችሁ፤ ሴትና ወንድ የት ይገናኛሉና ነው!›› አልኩ፡፡ የግዳቸውን ፈገግ አሉ፡፡

በዚህ መሰል ጭቅጭቅ ከተመስገን ጋር ያለንን ጊዜ ተሻሙብን፡፡ ይህ የገባው ተመስገን ደሳለኝ በጭቅጭቁ ጣልቃ ገብቶ፣ ‹‹ሰዎቹ ከአዲስ አበባ ነው የመጡት፡፡ ስለሆነም ከሩቅ ቦታ መጥተው ሳያገኟቸው ቢመለሱ ደስ አይልም›› አላቸው፡፡ ወዲያው አንደኛው ወደ እኛ ዞሮ ‹‹ናትናኤል መኮንንን የት ነው የምታውቀው?›› አለኝ፡፡ ጥያቄውን ወደጓደኛየም ወሰደው፡፡ ‹‹ይህን ጥያቄ ምን አመጣው›› ብዬ ጥያቄውን በጥያቄ ከመመለሴ፣ ጋዜጠኛ ተመስገን ቀበል አድርጎ ‹‹ኢትዮጵያዊ ወገኑን ሳያውቀውም ቢሆን መጠየቅ ይችላል!›› አለ፡፡ ተመስገን ተቆርቋሪነቱ ደስ ይላል፡፡ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ እስረኞቹ ሊጠሩልን ስምምነት ላይ ደረስን፡፡ እስኪመጡ ድረስም ከተመስገን ደሳለኝ ጋር ‹‹ከፖለቲካ ውጭ›› ባለ ድባብ ጨዋታችንን ቀጠልን፡፡

ተሜ ስለሚዲያ አብዝቶ ጠየቀኝ፡፡ ያለው ሁኔታ ከሚያውቀው እውነታ እንዳልተለወጠ ገለጽኩለት፡፡ ከዚያም ወደወንድሙ ዞሮ ስለቤተሰባዊ ጉዳዮች ሲያወራ ዓይኖቼን ወዳስጠራናቸው እስረኞች መምጫ አማትር ያዝኩ፡፡ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ ከርቀት አንድ ላይ ሆነው ሲመጡ ተመለከትኩ፡፡ ከፖሊሶች ጋር ባለው እሰጣ ገባ ስሜቴ ተረብሾ ነበር፡፡ ይህ ስሜቴ ግን ድንገት ሶስቱ ሰዎች ከርቀት በፈገግታ ታጅበው ወደ እኛ ሲመጡ ሳይ በንኖ ጠፋ፡፡

ሞገደኛው አበበ ቀስቶ እና የተጓደለው ጤናው ጉዳይ

ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ፣ ፖለቲከኞቹ ናትናኤል መኮንን እና ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) ካለንበት ስፍራ ደርሰው ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አቤት እንዴት ደስ እንዳላቸው! ሙሉ ፊታቸው ያበራል፡፡ ‹‹እኛን ልትጠይቁ መጣችሁ?›› እያሉ በደስታ ተቁነጠነጡ፡፡ እውነት ለመናገር ደስታው የእነሱ ሳይሆን የእኛ ነበር፡፡ በበኩሌ በእስር ላይ ያሉ ወንድም እህቶቼን መጠየቅ ምን አይነት የህሊና እረፍትና ደስታ እንደሚሰጠኝ የማውቀው እኔው ነኝ፡፡

ይህ ደስታችን ታዲያ ተመስገን ደሳለኝ ጋር በነበረው መልኩ ድንገት ደፈረሰ፡፡ ፖሊሶቹ አሁንም እሳት ለበሱ፡፡ ከውጭ ያለውን ነገር የተራቡት እነ ክንፈሚካኤል እነዚያን የፓርቲ ስሞች ጠቅሰው ጥያቄ ሰነዘሩ፡፡ ‹‹አንድነትና ሰማያዊ…›› ካፋቸው ቀልበው ፖሊሶቹ አንባረቁ፡፡ ‹‹አንተ ፖለቲካ አታውራ!›› በማለት ያዙኝ ልቀቁኝ አሉ፡፡ እንዲያውም ምንም ሳናወራ ተነሱና ግቡ አሏቸው፡፡ በዚህ ጊዜ አበበ ቀስቶ በኃይለ ቃል መልሶ ፖሊሶቹ ላይ አፈጠጠ፡፡ ፖሊሶቹ ትንሽ ድንግጥ በማለት ‹‹ሌላ ሌላ አውሩ በቃ!›› አሉን፡፡

ዝዋይ እስር ቤት ካሉ እስረኞች ጋር የሚገናኝ ጠያቂ ‹‹ደህና ነህ፣ እንዴት ነህ…›› ብቻ ብሎ እንዲመለስ ነው የሚፈለገው፡፡ ከሁሉም ጋር ያለውን ማህበራዊና የጤና ሁኔታ አንስተን ስንጨዋወት አበበ ቀስቶ ወደእኔ አንገቱን ሰገግ አድርጎ ‹‹አሞኛል፣ በብርቱ ከታመምኩ ቆይቻለሁ›› አለኝ፡፡ ከዚህ ቀደም በጤናው ላይ እከል እንደገጠመው አውቅ ነበር፡፡ የአሁኑ ህመሙ ምን ይሆን በሚል የበለጠ እንዲነግረኝ እኔም አንገቴን ሰገግ አድርጌ ጆሮዎቼን ሰጠሁት፡፡

‹‹የሚያመኝ ይሄን የጆሮየን አካባቢ ነው፡፡ በብርቱ ታምሜያለሁ፡፡ አብሮኝ የሚተኛው ናትናኤል መኮንን ባይሆን ኑሮ ምን እንደሚውጠኝ አላውቅም፡፡ ቁስል አበጅቶ መጥፎ ጠረንም ፈጥሯል›› አለኝ፡፡ እኔም የህመሙ ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቅኩት፡፡

‹‹ያኔ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ እያለሁ የደረሰብኝ ድብደባ ነው ዛሬም የሚያሰቃየኝ›› አለኝና ከዚያ ወዲህ እንዴት እየተሰቃየ እንዳለ አስከትሎ አስረዳኝ፡፡ እኔም ‹‹ህክምና…›› ሳልጨርሰው ተቀበለኝ፡፡ ‹‹ህክምና የሚባለውን ተወው፡፡ ይሄው ስንት ጊዜ እንዲያሳክሙኝ የምጮኸው! ሰበቡ አያልቅባቸውም! ምንም በቂ ህክምና አላገኘሁም፡፡ መቼስ….›› ብሎ ያ ከደቂቃዎች በፊት በሳቅ፣ ከዚያም በንዴት ውስጥ የነበረው ቆፍጣናውና ቀጭኑ ፖለቲከኛ በትካዜ አንገቱን ደፋ፡፡ ውስጤ በማላውቀው ስሜት ተላወሰ፡፡ አበበ ቀስቶ በስካርቭ ጨርቅ ሙሉ ጆሮ ግንዱን ጠምጥሞ የመጣበት ምክንያት ገባኝ፡፡ ቁስሉን ለመሸፈን ነው፡፡

ከአበበ ጋር ይህን ስናወራ ሌሎች ወዳጆቼ ከእነ አሳምነው እና ናትናኤል ጋር ስለተለያዩ ጉዳዮች (‹ከፖለቲካ ውጭ›) እያወሩ ነበር፡፡ ‹‹እስኪ ደግሞ ከእነሱ ጋር አውራ፣ ጊዜህን እኔ ብቻ ወሰድኩብህ›› አለኝ አበበ ቀስቶ ወደ ናትናኤልና አሳምነው እየተመለከተ፡፡ እኔም በአለችው ትንሽ ደቂቃ ከሌሎቹ ጋር ጨዋታ ያዝኩ፡፡ በዚህ መሐል ግን ቀልቤ የአበበ ቀስቶ ጤንነት ላይ ነበር፡፡ እንዴት ሰው አካሉ እንዲያ ቆስሎ ህክምና አይሰጠውም?


ስንብት

በፖሊሶች ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ለሰላሳ ደቂቃዎች ብቻ የነበረን ቆይታ ማብቃቱን ስንረዳ 30 ደቂቃ ምን ያህል አጭር እንደሆነ ተገነዘብን፡፡ ስድስት ሰዓት ደርሶም ስለነበር መለያየታችን ግድ ሆነ፡፡ ስንገናኝ እንዳደረግነው ሁሉ እንደገና ለስንብትም ተቃቀፍን፡፡ በእቅፎቻችን መካከል የተሰነቀረው አጥር ደግሞ የመለያየታችን ደንቃራነት ማሳያ ነበር፡፡

ከእነ አበበ ቀስቶ ጋር ያለኝን ስንብት ጨርሼ ወደ ተመስገን ደሳለኝ ስጠጋ በእጆቹ አንገቴን ሳብ አድርጎ ወደ ጆሮዬ ጠጋ በማለት ‹‹ስርዓት ሲፈርስ የሚያደርገውን ያጣል፡፡ ስርዓቱ እየፈረሰ ነው›› አለኝ፡፡ ምንም አልመለስኩለትም፡፡ በእጆቼ ትከሻውን መታ መታ በማድረግ የተናገረውን መስማቴን አረጋገጥኩለት፡፡

The tale of TPLF fairytale regime of Ethiopia: From ethnic liberation to Federal banditry

November 22, 2014
It is rather baffling TPLF’s crimes are all around us but yet barrage of books, articles and news pieces are written and bogus institutions and Medias created to make the fairytale TPLF led regime looks real and acceptable. Whether they do it because they believe TPLF is a legitimate entity or simply to take advantage of the chaos it was empowered to create to divide-exploit the people and the nation is not clear. But one thing is abundantly clear for all; Ethiopians are under occupation of a confused mercenary like ethnic regime led by TPLF. If institutions, including Medias can’t see this reality, either they are as bogus as the fairytale regime –tangled up with their own petty interest or part-and-partial of TPLF willingly conspiring to commit crimes.
by Teshome Debalke
A strange phenomenon is happening with Tigray People Liberation Front (TPLF). It appears the inevitable identity crisis of to be-or-not-to-be a Tigray Chiefdom it claimed to fight for or a Federal bandit it turned out to be in Nations and Nationality it created and occupied is coming home to roost. That is not all; it still agonizing whether to stick with the Marxism ideology it was baptized to control and brutalize the population or the crony capitalism it adapted along the way to extort and robe the people and the nation.
Intoxicated by political power and daylight robbery its enablers afforded it, it is having difficulty to choose between the empty bravado it pumps up its juveniles in the imaginary ethnic ‘Tigray’ people it liberated (use and abuse) in an imaginary Region (open air prison) and the Nations and Nationalities of Ethiopia it crafted to divide and exploit as a make-believe Federal government.
To make matter worst, the self-professed ‘Tigray’ liberators turn bandits actually believe they duped Ethiopians and the world –telling their fairytale over-and-over again with crafty propaganda—aimlessly drifting away from reality to believe it themselves. In fact, it is amazing how many fairytale story tellers mushroomed in the last decade alone around the fairytale regime in order to sustain its rule and unprecedented corruption.
It all started in one unfaithful day four decades ago when a half-dozen Ethiopian `juvenile armed with Marxist books sat around a table in a tearoom in Addis Ababa and decided to start a revolution to ‘free’ the ‘oppressed people’ of Ethiopia from ‘Feudalism’ as many of their contemporaries did. With too many ‘revolutionaries’ competing to free the same people in the name of the same ideology, the sorry juveniles with too much time on their hand figured out the only chance they got in the competition was to curved out an imaginary ethnic group called Tigray and made their newly minted identity a rallying cause for liberation-leaving the rest of the ‘oppressed people’ Ethiopia behind.
‘Imaginary ethnic group to liberate out of the way, they had to come up with an imaginary territory to match their newly minted identity and began drawing and redrawing territories to fit a fairytale history out of their back pockets. Short of the Fascist Italian occupied territory their Arabs led ‘Eritrean’ Liberation Front comrades declared their own, they started slicing and dicing wherever their juveniles mind took them to curve out a territory called Tigray and became a fairytale Liberation Front and found out they were conspiring in a territory they declared an enemy they no longer belong. Read more…
The Horn of Africa Peace and Development Center
(Left to right), Professor Ephraim Isaac , Director of the Institute of Semitic Studies at Princeton University, Dr. Haile Selassie Belay, Former governor of Tigray Province and former Dean of Alemaya University, Dr. Tilahun Beyene, Associate Dean of the University of Maryland Dr. Ahmed Moen, Associate Professor and Interim Director Health Management Sciences of Howard University Dr. Mulugeta Eteffa, Former Ambassador of Ethiopia and the Ethiopian Permanent Mission in New York Source: Peace and Development Center-
Dr. Astair GM Amante, Associate Professor at Arizona State University and one of the Founder of HAPDC picture `not found.

ተቃዋሚዎች - ግብታዊነት እና የሆያሆዬ ፖለቲካ መቆም ያለበት ጉዳይ

November 22,2014
በምንሊክሳልሳዊ‬
ከመጠላለፍ ከወሬና ሃሜት ከሴራና ደባ ይልቅ እስትራቴጂ ያለው የፖለቲካ መስመር መከትል ወሳኝ ነው::

‪ሃገሪቷ ህገ መንግስት አላት ቢደሰኮርም በስርኣት አልበኞች እየተጣሰ ህግ በህግ እየተሻረ እና ባለስልጣናት እየሸረሸሩት አማራጭ የፖለቲካ አመለካከቶች እና አስተሳሰቦች እንዳይንሸራሸሩ እና እንዳይወዳደሩ በማድረግ በህግ የተረጋገጠውን የብዙሃን የፓርቲ ስርኣት እንዳይሰፍን እንቅፋት ቢሆኑም ይህ ደሞ ከስርአቱ አምባገነንነት ጎን ለጎን የተቃዋሚዎች ድክመት ታይቶ የሚወሰድ እርምጃ ነው:: ደህንነቱ ሰራዊቱና ሚዲያው ምርጫ ቦርዱ ህዝባዊ ባልሆኑበት የአንድ ፓርቲ ወገንተኛ እና አገልጋይ በሆኑባት ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሃዊ እና ነጻ ምርጫ አለ የሚል እምነት በፍጹም የለኝም:: ስለወያኔ ምርጫ እና በምርጫው ስለመሳተፍ የፓርቲዎቹ መብት ቢሆንም ሕዝቡ እምቢኝ ብሎ አደባባይ እንዲወጣ ለማድረግ በጋራ እንዲሰሩ ይህንን ለመናገር እወዳለሁ::

ብቁ እና ጠንካራ የፖለቲካ ፓርቲ አለመገኘቱ -የአገር ጉዳይ የአንድ ሰሞን ሆሆይታ እና ትኩሳት ተከትሎ ማውራቱ በፖለቲካ ሴራ እና ጠልፎ መጣል አባዝ የተሞሉ -ፖለቲካ የትርፍ ሰአት ስራ- መሆኑ ያልበሰሉ ስሜታዊ እና የፖለቲካ ስልታዊ እውቀት ያሌላቸው በፓርቲዎች ዙሪያ መሰባሰባቸው - በሚገባ የተደራጀ፣ አቅሙን እያጎለበተና ለሕዝቡ የተሻለ አማራጭ የሚያቀርብ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት አለመኖር የፓርቲዎቹ አባላት እና ካድሬዎች አንድ ስትራቴጂ ሳይኖራቸው በነፈሰበት እየነፈሱ በጥቂት ድላሮች እየተሽከረከሩ አቧራ ከማጨስ ውጪ አንድ ባልፈየዱበት ሕዝባዊ እምቢተኝነትን ለመፍጠር በሚደረገው ሩጫ ውስጥ ሆን ተብሎ በሚፈጠረው መንቀራፈፍ የወያኔን እድሜ ማስረዘማቸው በጎሳ ፖለቲካ የሚናጠው የዲያስፖራው ዶላሮች የሚፈጥሩት ግብታዊ ተጽእኖዎች በኢትዮጵያ የሚፈለገውን ለውጥ አለማምጣቱ የታወቀ ጉዳይ ነው::ሰበብ የማያጡት ተቃዋሚዎች ይህንን ማድረግ ያልቻልነው ወያኔ እንዳንጠናከር እያዳከመን እያንገላታን እያሰረን ነው ቢሉም ይህንን አሰራር የወያኔው ጁንታ እንዲቀይር መስዋትነት ለመክፈል ምንም ያደረጉት ነገር የለም::

በእርግጥ የወያኔው ጁንታ በፖለቲካ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ጫና በማድረግ ድርጅቶቹ እንዲቀጭጩ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ሚናውን እየተጫወተ ነው:: ሆኖም ግን ተቃዋሚዎች ከታጋይነት ይልቅ ባለፈ ታሪክ የመኮፈስ- እርስ በእርስ የመወቃቀስ- ያለፉትን ስርኣቶች የመናፈቅ-ህዝብን በታሪክ ስም ለመደለል መሞከር-ከመስዋትነት ይልቅ ለጥቅም መገዛት-መረጃ መሸጥ -ለስልጣን መጓጓት የመሳሰሉት ድክመቶች ያሉባቸው ሲሆን ስሜታዊ እና ያልበሰሉን ሰብስቦ ቲፎዞ በማድረግ መንጠራራትም ያልቀረፉት ችግራቸው ነው::የወያኔ ተጽእኖ እና ጫና እዳለ ድርሻው ሳይካድ መጀመሪያ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን ማጽዳት ይጠበቅባቸዋል::በውስጣቸው የሚታየውን ችግር ቢያድበሰብሱትም በአደባባይ እያየነው ያለ ጉዳይ ነው፡፡

አንድ ፓርቲ ከተለመደው ስልት ወጥቶ በአዲስ ስትራቴጂ ራሱን ሲገነባ ከፓርቲው ውጪ ያሉ ስለ ፓርቲው ምንም አይነት እውቀቱ እና ግንዛቤው የሌላቸው አባል ያልሆኑ የጠልፎ መጣል ኋላቀር ፖለቲካ ተጠቅመው ፖለቲካው አዲስ ባህል እንዳይኖረው ለመጠላለፍ እና ለማልፈስፈስ ትራካቸው ላይ ከመሮጥ አልፈው ከሴራ ፖለቲካ፣ ከሀሜት፣ ከወሬ አውጥተን መሬት በረገጠ፤ በእስትራቴጂ የሚመራ እውነተኛና ዘላቂ ፖለቲካዊ ምህዳር እንፈጥራለን ያሉት ፓርቲዎች ለማክሸፍ እየተራውጡ ነው። የአንድ ወቅት ሆያሆዬ በየጊዜው በህዝቡ ላይ የፈጠረው አጉል ተስፋ ህዝቡ የፈጠረው ተስፋ መቁረጥ በዓይናችን እያየን ነው፤ ይህ ሁሉ የመጣው ፖለቲካው በስልትና በእስትራቴጂ ሳይሆን በግብታዊነት የሚመሩ ፖለቲከኞች በመብዛታቸው ነው።

ተቃዋሚዎች ራሳቸው ቆራጦች፣ ጠንካሮች፣ ቅኖችና ለመስዋዕትነት ዝግጁዎች ቢሆኑ ኖሮ ከዚህ በላይ የተጠናከሩ ይሆኑ ነበር፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከባድ እና ሊቃለል እንኳን ያልቻለ የመንግስት ጫና ....ተቃዋሚ ፓርቲዎች በውስጣቸው በተሰገሰጉ የወያኔ ሰላዮች የታጠሩ ናቸው::ተቃዋሚ ፓርቲዎች የአንድነት ችግር ....ተቃዋሚ ፓርቲዎች የአደረጃጀት ችግር ...ተቃዋሚ ፓርቲዎች የአመለካከት ችግር ...ተቃዋሚ ፓርቲዎች የውስጥ የዲሞክራሲ ችግር.....ተቃዋሚ ፓርቲዎች የደጋፊና የአባል ብዛት ችግር ....ተቃዋሚ ፓርቲዎች የፋይናንስ አቅም ችግር ... ተቃዋሚ ፓርቲዎች የፖለቲካ መስመር፣ የስትራቴጂና የታክቲክ ችግር አለባቸው፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ችግሮችን የሚፈቱበት መንገድ ራሱ ችግር አለበት፡፡

ተቃዋሚዎች ከዚህ በላይ ለተተቀሱት ነገሮች አትኩሮት መስተት እና ማስተካከል አለባቸው ስሜታዊነት እና የሆያሆዬ ፖለቲካ መቆም ያለበት ጉዳይ ነው::በውስጣቸው ያለውን አንድነት ማጠናከር እና የስርኣቱን ተላላኪዎች ማስወገድ ይጠበቅባቸዋል:: የአደረጃጀት መዋቅራቸውን ማስተካከል በበሰሉ እና ወደፊትን ግብ በሚያደርጉ ጠንካራ እና ብቁ ፖለቲከኞች መታጠር አለባቸው:: አመለካከታቸውን ካረጀ እና ከታሪክ ምርኩዝነት አውጥተው በሰለጠነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ራሳቸውን ማስተሳሰር እና አማራጭ ሃሳቦችን በማሸራሸር ጠንካራ ብሄራዊነት መፍጠርና ለላሸቀው የዲያስፖራው ፖለቲካ ፊት አለመስጠት ስለ ፖለቲካ እውቀት ያሌላቸው ሰዎች በደመነፍስ ፖለቲከኛ እየሆኑ መምጣት የፖለቲካ ስትራቴጂ እና ታክቲክ እንዳይኖር አድርጓል:: ስለዚህ እነዚህ ጉዳዮች በጥራት እና በአጽንኦት አትኩሮት ከተሰጠባቸው ትግሉ ሊያብብ ይችላል:: ከዚህ ውጪ አሁን ባሉበት ሁኔታ ተቃዋሚዎች ከቀጠሉ የወያኔን እድሜ ከማስረም ዉጪ ምንም ፋይዳ የለውም::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Friday, November 21, 2014

የአ.አ አስተዳደር ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል በሰማያዊ ፓርቲ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

November 21,2014
• ‹‹ማስጠንቀቂያውን እንደ ቁም ነገር አንቆጥረውም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

• ‹‹ስርዓቱ ምን ያህል ዝቅጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል›› አቶ ግርማ በቀለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህዳር 7/2007 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ ያስተባበረው የ9ኙ ፓርቲዎች የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ ፀረ ህገ መንግስት በመሆኑና ነዋሪዎችን ሰላምና ፀጥታ በማወኩ በቀጣይ ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ካደረገ ለህዝብ ሰላምና ደህንነት ሲባል እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ፡፡

አስተዳደሩ ትናንት ህዳር 11/2007 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ፤ ህዳር 6 ቀን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ለህዝብ የተሰራጨው በራሪ ወረቀት ህገ ወጥ መሆኑን፣ ህዳር 7/2007 ዓ.ም በኢንጅነር ይልቃል ጌትነት መሪነት ሊደረግ የነበረው አደባባይ ስብሰባ ህገ ወጥ እንደነበርና በወቅቱ የስብሰባው ተሳታፊዎች ከፖሊስ ጋር ግብ ግብ ከመግጠማቸውም በተጨማሪ የአካባቢውን ህዝብ ሰላምና ፀጥታ አውከዋል ሲል ከሷል፡፡ አስተዳደሩ አክሎም ፓርቲው የአደባባይ ብጥብጥና ሁከት በመፍጠሩ እርምጃ እወስዳሉ ሲል ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ልኳል፡፡

በሌላ በኩል ሰማያዊ ፓርቲ በቀን 5/3/2007 ዓ.ም ለአስተዳደሩ የእውቅና ደብዳቤ ያስገባ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ አመራሮች አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ከገዥው ፓርቲ ፍርሃት የመነጨ በመሆኑ ከእንቅስቃሴያቸው እንደማይገታቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብርና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ደብዳቤው ስርዓቱ የደረሰበትን መጠነ ሰፊ የፍርሃት ደረጃና ትግሉን ይበልጥ አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን የሚያሳይ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂው የደረሰው ሰማያዊ ፓርቲና የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ‹‹የረዥም ጊዜ የመንግስት ታሪክ ባላት አገር የከተማ አስተዳደር ነኝ ያለ አካል እንዲህ አይነት ደብዳቤ መጻፉ ኢትዮጵያ ምን ያህል ውድቀት እንደገጠማትና እኛም እንደ ህዝብ የውረደት ካባ መከናነባችን በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡ እንደ ሰማያዊ አሊያም የትብብሩ ሊቀመንበርነት ሳይሆን እንደ አንድ ይህን ያህል ውርደት እንደገጠማት አገር ዜጋ ሀፍረት ይሰማኛል፡፡›› ሲሉ አስተዳደሩ የላከው ደብዳቤ ላይ አስተያየታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ማስጠንቀቂያው በቀጣይ የፓርቲውም ሆነ የትብብሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚያመጣው ችግር ካለ በሚል ለኢንጅነር ይልቃል ላነሳነላቸው ጥያቄም ‹‹ደብዳቤው የኢህአዴግ ፍርሃት ገደብ መልቀቁንና ትግሉም ይበልጥ መጠናከር እንዳለበት የሚያሳይ ነው፡፡ ኢህአዴግ ሰላማዊ ህዝባዊ እንቅስቃሴን ብቻ ሳይሆን የራሱን ጥላም አለማመን ደረጃ ላይ መድረሱን ያሳያል፡፡ እኛ ይህን የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደቁም ነገር አንቆጥረውም፡፡ ይበልጡንም ለትግሉ በተጠናከረ መንገድ ንድንነሳሳ ይገፋፋናል›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ የትብብሩ ፀኃፊና የኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ግርማ በቀለ ‹‹ማስጠንቀቂያው ትብብሩ በየሳምንቱ ያቀዳቸውን መርሃ ግብሮች ለማደናቀፍ ያለመ ነው፡፡ ከአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲህ አይነት አሳፋሪ ደብዳቤ መጻፉ ስርዓቱ ምን ያህል ዝግጠት ውስጥ እንደገባ ያሳያል፡፡ ሆኖም ማስጠንቀቂያው ከእንቅስቃሴያችን አይገታንም፡፡ እንዲያውም ለዚህ የስርዓቱ ዝቅጠት የሚመጥን ስልት ነድፈን በጋራ እንድንሰራ ያደርገናል፡፡›› 
ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

L

ከ400 በላይ ህዝብ የተፈናቀለበት መሬት በሙስና ተቸበቸበ

November 21,2014
በደቡብ ወሎ ዞን በኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 11 በተለምዶ ጋሪሳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ይኖሩ የነበሩ 470 ሰዎች ቦታው ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል ተብሎ ሰብአዊ መብታቸው ተጥሶ እንዲፈናቀሉ ከተደረገ በሁዋላ፣ በካሬ ሜትር 1 ብር ከ46 ሳንቲም መሬታቸው እንዲጨጥ ተደርጓል።
ጉዳዩ የህዝብ መነጋገሪያ ሆኖ ከቆየ በሁዋላ ሰሞኑን ከህዝቡ እየጨመረ የመጣውን ግፊት ተከትሎ በተደረገ ህዝባዊ ስብሰባና የካቢኔ አባላት ስብሰባ፣ የወረዳው አዛዦች ከተፈናቃዩ ደሃ ህዝብ የወሰዱትን መሬት በሙስና መቸብቸባቸውን እርስ በርስ እየተገላለጡ ይፋ አድርገዋል።
የወረዳው ላይዘን ኦፊሰር አቶ ሃብቶም የተባሉ ግለሰብ፣ አስተዳዳሪውን አቶ አበራ አበረን በአዲስ አበባና በባህርዳር መሬት ገዝተው ቤት መስራታቸውንና ቡልዶዘሮችን ገዝተው እያከራዩ መሆኑን ሲያጋልጡ፣ ምክትል ከንቲባው ደግሞ በባንክ ሂሳባቸው 8 ሚሊዮን ብር እንደተገኘባቸው እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች ቤቶችን መገንባታቸውን አጋልጠዋል። አጋላጩ አቶ ሀብቶምም በከተማዋ ሁለት ቦታ ገዝተው ቤት መስራታቸውን መቀሌ ላይ ተጨማሪ ቦታ መግዛታቸው በሌሎች ባልደረቦቻቸው ተጋልጧል።
ሶስቱም ባለስልጣኖች ለጊዜው ከስራቸው ቢታገዱም እስካሁን የተወሰደባቸው እርምጃ የለም። አንዳንድ ተፈናቃይ አርሶደአሮች ለኢሳት እንደገለጹት አቤቱታ ቢያቀርቡም ሰሚ በማጣታቸው ለስደትና ለረሃብ መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል ። ሰዎቹ ከስራ ቢሰናበቱም ወደ ሌላ ቦታ ተዛውረው መስራታቸው አይቀርም ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በደቡብ ክልል በጉራፈርዳ ወረዳ ከ100 በላይ አርሶደሮች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። አርሶ አደሮቹ የመሬት ዋስትና ወረቀት እንዲሰጣችሁ በነፍስ ወከፍ 4 ሺ 500 ብር ክፈሉ ተብለው የተጠየቁ ቢሆንም፣ አርሶአደሮች ግን እስከዛሬ ግብር እየከፈልን ኖረናል፣ አሁን ተጨማሪ አንከፍልም በማለት ተቃውመዋል። ይህ ተከትሎ መሬታቸውን እየተቀሙ መሬቱ ለኢንቨስተር እየተባለ እየተቸበቸበ ነው።
አብዛኞቹ ባለስልጣኖች ከኢንቨስተሮች ጋር አክሲዎን እንዳላቸው መንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። በአካባቢው የሚታየው ተደጋጋሚ ግጭት ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ።
ምንጭ  ኢሳት ዜና

Journalism professor aids UN in Ethiopia

November 21,2014
A UA journalism professor recently embarked on a trip to Addis Ababa, Ethiopia, to form part of a Fulbright specialist mission with the U.N. Economic Commission to Africa, aiding in the development of a think tank for the African Union.
22157_n112014profilejourcourtesyrgbf
By Courtesy of Shahira Fahmy / The Daily Wildcat Journalism professor Shahira Fahmy visited Addis Ababa, Ethiopia, with the U.N. to aid in the development of a think tank. Fahmy spent her two weeks in Africa assessing strategic communication skills with the U.N.
Shahira Fahmy, a tenured journalism faculty member, spent two weeks assessing strategic communication skills through a U.N. and Fulbright Scholarship partnership. Her latest published academic work, “Visual Communication Theory and Research: A Mass Communication Perspective,” was granted an award for the most outstanding book in visual communication for this year’s National Communication Association meeting in Chicago, according to a press of release from the School of Journalism.
“She is a prolific researcher and is well-known for her research on how the media visually portrays [people around the world],” said David Cuillier, director of the School of Journalism. “She represents the university well [through] her research.”
While Fahmy was in Ethiopia, she conducted interviews and focus groups to get a better understanding of the African Union’s situation.
By Courtesy of Shahira Fahmy / The Daily Wildcat
Journalism professor Shahira Fahmy visited Addis Ababa, Ethiopia, with the U.N. to aid in the development of a think tank. Fahmy spent her two weeks in Africa assessing strategic
communication skills with the U.N..
One factor that Fahmy said she noticed was a longing to become more active through social media, which was difficult due to age differences. The lack of knowledge on social media was something Fahmy particularly focused on improving.
Although the trip was diplomatic, Fahmy faced several problems while in Ethiopia.
There were threats by al-Shabaab, a terrorist group that pledged allegiance to al-Qaida, which limited Fahmy and others visiting the area to a tight-but-safe schedule.
“I received a note from the university that there was a terrorist threat directed to the U.S. Embassy where Westerners go to,” Fahmy said. “They decided to … continue life as normal, but avoid any crowded areas.”
Because of its geographical location, Ethiopia was not considered to be a possible location for an Ebola outbreak; however, measures taken to ensure the population’s safety.
“I got to the airport [and there were two Ebola checkpoints and] as soon as I got there, I had people getting my temperature,” Fahmy said.
According to the School of Journalism’s press release, Fahmy also had the opportunity to attend a fact-gathering conference on command by the U.S. Department of State public diplomacy program. While attending the conference, Fahmy said she realized the members’ need to develop better presentation, persuasion and networking skills. It was crucial for them to learn how to speak to the media when trying to pitch ideas as well as discussing any topics with policy makers, Fahmy said.
Another important goal was educating the people of Ethiopia’s African Union to present themselves as the group’s spokespeople and hopefully develop a think tank for the country, Fahmy added.
“Every single person that I met there had an amazing story and everyone there spoke different languages,” she said. “I suddenly felt right at home.”
http://www.wildcat.arizona.edu/

ምርጫ ሲባል አማራጭ ሳያሳጡ መሆን ይኖርበታል!!!

November 21,2014
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

un3በሀገራችን ኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ ሀገራዊ ምርጫ እንደሚደረግ በመንግስት በኩል በከፍተኛ ደረጃ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት የተከናወኑት አራት ምርጫዎች ያየን እንደሆነ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ወደፊት ሊወስዱ እንዳልቻሉ እሙን ነው፡፡ ይህም ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ፍላጎት በተለያየ መንገድ ሲገልፅ ቆይቷል፡፡ በተቃራኒው መንግስትና ገዢው ፓርቲ በፍፁም መለየት በሚያስቸግር ሁኔታ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሆነው ተቀናጅተው ለአንድ ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እየሰሩ እንደሆነ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህ የመንግሥትና የገዢው ፓርቲ ተግባር ምርጫን ያለ አማራጭ እንዲሆነ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡
በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አባላት ላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ዘመቻ በሚባል ደረጃ እየተካሄደ ያለው አፈናና እስር፤ ከዚህም ባሻገር ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከህዝብ ጋር እንዳይገናኙ ክልከላውና ወከባው ተጠናከሮ መቀጠሉ፤ ገዥው ቡድን የምር ተቃዋሚ ፓርቲ ናቸው ብሎ የሚያስባቸው ፓርቲዎች ለማዳከምና ከምርጫው ውድድር ውጪ ለማድረግ ያለው ቁርጥ አቋም የሚያሳይ ነው። ይህ የገዢው ቡድን አካሄድ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ የሆነ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲመሰረት ፍላጎት እንደሌለው በደንብ የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ ምርጫ የሚፈልገውን ፓርቲ እንዲመርጥ እድል ሊጠሰው ሲገባ በሥርዓቱ በእኩል ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳያካሄድ የተለያዩ ጫናዎች እየተደረጉበት የሚካሄዱት ምርጫዎች ሁሉ ትርጉም አልባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ የገዢው ቡድን ሀላፊነት የጎደለው እንቅስቃሴ በተግባር የሚደግፈው ከሠላማዊ ትግል ይልቅ የኃይልና የአመፅ መንገድ እንደሚሆን የተረዳ አይመስልም፤ ይልቁንም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉትን ፓርቲዎች ወደ አላስፈላጊ መስመር በመግፋት ሀገራችን ወደ ብጥብጥና ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንድትገባ የሚያደርግ ሁኔታ እየተከተለ ነው የሚገኘው። በሥልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ይህ አሳሳቢ ሁኔታ በትክክል እንዳያዩ ጭፍን የሥልጣን ጥም ጋርዷቸዋል፡፡
በቀጣይ ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚደረገው ምርጫም በመንግስት በኩል የመድበለ ፓርቲን ስርዓት ለማጎልበት ምንም ዓይነት ምቹ ሁኔታ እንዳይፈጠር ከአሁኑ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመደርደር ላይ ነው። የአንድነት አመራሮችና አባላት በግፍ በማሰር ፓርቲው በምርጫው እንዳይሳተፍ ከፍተኛ የሆነ ጫና እየተደረገ ቢሆንም አንድነት ፓርቲ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሆኖ ህዝቡ እንዲሳተፍ በመቀስቀስና በማበረታታት የተዘጋውን የዴሞክራሲ በር በምርጫ ካርዱ ሊያስከፍት እንደሚችል ከፍተኛ እምነት አለው፡፡
ከሁሉም በላይ ደግሞ እንደከዚህ ቀደሙ ኢህአዴግ ደጋፊዎቼ የሚላቸውን ብቻ በመራጭነት አስመዝግቦ ምርጫ የሚያደርግበት ሁኔታ ማብቃት ይኖርበታል ብለን እናምናለን፡፡ ይህ ተግባራዊ እንዲሆን በእኛ በኩል ደጋፊዎቻችን በመራጭነት እንዲመዘገቡ ከማበረታት ጀምሮ የህዝብና የፓርቲ ታዛቢ በመሆን የምርጫ ሂደቱን በሙሉ በንቃት እንዲከታተል እንዲሳተፍ የበኩላችንን ጥረት በማድረግ የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ከጅማሮው ህዝባዊ እንዲሆን ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡ ይህ እርምጃም ህዝቡን የስልጣን ባለቤት ለማድረግ ወሳኝ እርምጃ ነው የሚል እምነት አለን፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ በገዥው ቡድን መልካም ፍቃድ ወይም በማንኛውም ውጫዊ ተፅዕኖ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደማይሰፋ ሊገነዘብ ይገባል። ምህዳሩ የሚሰፋውና ትክክለኛ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ለውጥ የሚኖረው ህዝቡ በጠቅላላ ከፍርሀት ቆፈን ተላቆ በሙሉ ልብ ለመብቱ ሲቆም፣ ለፓርቲዎች ተገቢው ድጋፍ ሲሰጥ፤ ከፍ ሲልም ወደ ትግሉ ሲቀላቀል መሆኑ መገንዘብ ያስፈልጋል።
በዚህ አጋጣሚ አንድነት ፓርቲ ከህዳር 14 እስከ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚቆይ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች” የሚል የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ አዘጋጅቷል። በዚህ ዘመቻ ለመንግስት ባለስልጣናት፣ ለታዋቂ ግለሰቦች፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለልዩ ልዩ የሚዲያ ድርጅቶች በኢንተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በእኩል መልዕክት በመላክ በሀገራችን ያሉት የፖለቲካ እስረኞች ሁኔታና አያያዝ በተመለከተ መረጃ በመስጠት ተገቢ የሆነ አያያዝ እንዲኖራቸው፤ ከእስር እንዲፈቱ፣ በሰላማዊ መንገድ የሚታሉትን ማሰርና ማዋከብ እንዲቆም በመንግስት ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለመፍጠር ያለመ ነው። በዚህ ዘመቻ ላይ ሚሊዮኖች ለሚያውቁትና ተፅዕኖ ማሳደር ይችላል ለሚሉት ሰው ሁሉ መልዕክት በኢተርኔትና በሶሻል ሚዲያ በመላክ ድምፃቸውን ያሰሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)
ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን ያጣል

November 21,2014
ታሪክ ለሰው ልጅ ስሩና መሠረቱ ነው።ታሪኩንና መምጫውን የማያውቅ ህዝብ መድርሻውን የማያውቅና ራሱንም ለባርነት አሳልፎ የሰጠ ይሆናል፡፡ ለክብሩ ለእርሱነቱ ለህብረቱና ለነፃነቱ ፀንቶ መቆየት እና የጥንካሬውና ተሳስሮ የመዝለቂያው ሰንሰለት ታሪኩ መሆኑ ይታወቃል፡፡
የአሜሪካ ባርያ ፈንጋዮች ትናንት በገፍ ከአፍሪካ በባርነት ያመጡዋቸው አፍሪካውያን አንድ ቀን በአንድ ቆመውና በህብረታቸው ጠንክረው ራሳቸውን ነፃ ለማውጣት እንዳይነሱ ሀ ብለው የነጠቋቸው ማንነታቸውን፤ ታሪካቸውንና መገኛቸውን ነበር፡፡ እንደ እቅዳቸውም እነሆ ዛሬ አብዛኛው ጥቁር አሜሪካዊ እኔ ማን ነኝ? መምጫዬስ ከወደየት ነው? በሚሉና በመሳሰሉ ጥያቄዎች ተተብትቦ ለምላሹ ሲውተረተር መገኘቱ፤ እንዲሁም ዛሬም ከተገዢነት መንፈስ ራሱን አላቆ በሁለት እግሩ ለመቆም ሲታትር ይገኛል፡፡
ሌላው የኢጣልያ ወራሪን ሀይል ቅስም የሰበረውና በአለም አቀፍ ደረጃ ቅሌት ያከናነበው የአድዋ ጦርነት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ቅሌት በደም አጥቦ ሀያልነቱን ለአለም ለማሳየት በሞከረበት ሁለተኛው ወረራ ወቅት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የአድዋ ጦርነት የመሩት የአፄ ሚንሊክ ሀውልትን ከጥልቅ ጉድጓድ መቅበር እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ባጠቃላይ አንድ ህዝብ እንደ ህዝብና ሀገር ጠንክሮና በነፃነት ኮርቶ ለመኖር ብሎም ከትውልድ ትውልድ መሸጋገር መቻል ከማረጋገጫው አንዱ የትናንት ማንነቱና የመገኛ ታሪኩ መሆኑን ከላይ በምሳሌነት ያነሳናቸው ነጥቦች ያረጋግጣሉ፡፡
ታሪክ ለአንድ ህዝብ የማንነቱ መገኛ፤ የመገኛው ምንጩና መምጫውን የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን የነገ መዳረሻውን የመመልከቻ መነፅርና ጠንክሮ የመንቀሳቀሻው ጉልበቱ ሆኖ የሚያገለግል ትልቅ መሳሪያ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ አንድ ህዝብ ታሪኩ ከጠፋ ሊገጥመው የሚችለው ችግርና ፈተና እንዲህ በቀላሉ የሚገመት ያለመሆኑንና እንደ ህዝብ እንደ ሀገር ቀጣይነቱን በቀላሉ መፍትሄ ከማይገኝለት ፈተና ውስጥ ይከተዋል ማለት ነው፡፡
ኢትዮጵያችን ዛሬ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ህልውናዋ አደጋ ላይ የወደቀበት መሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ባለፉት 23 አመታት በዘረኞቹ የወያኔ ጉጅሌዎች እጅ ከወደቀችበት እለት ጀምሮ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መገለጫ የሆኑ የታሪካችንና የባህልችን ዋና ዋና እሴቶች ዋነኛ ኢላማ ሆነዋል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚና በግልፅ ከወያኔው መሪ እስከ ተራ ደጋፊው የሚወረወረው በትር ያረጋግጣል፡፡ ጉጅሌዎቹ የነፃነት ምልክት የሆነውንና በዕልፍ አዕላፋት ደም መሥዋዕትነት ፀንቶ የቆየውን ሰንደቅ ዓላማ በሶ መጠቅለያ ጨርቅ ከማድረግ ጀምረው ዛሬ በምሁራን ጥረትና በእያንዳንዱ ዜጋ ድጋፍ የተሰባሰቡት የታሪኮቻችን መዛግብት በጥንቃቄ ከተቀመጡበት (ቤተ-መዛግብት) እያወጡ ከማውደምና ለስኳር መጠቅለያነት እስከ መሸጥ ደርሰዋል፡፡
ታሪካዊ ገዳማት ፈርሰዋል፤ ታሪካዊ ቅርሶች ለባእዳን አልፈው ተሽጠዋል፤ የነፃነት ታሪካችን እየተደለዘ በወያኔያዊ ዘረኛ የፈጠራ ታሪክ መተካቱ ቀጥሏል፤ ታሪካዊ ጀግኖቻችንን ማዋረድና ማውገዝ የእለት ተእለት ስራቸው ሁኗል። ወ ያኔዎች ኢትዮጵያዊነት ቅዝት ሆኖባቸዋል፤ ስለዚህም ቀንደኛ ጠላታቸው አድርገው ፈርጀውታል፡፡ ይህ የዘረኝነትና የዘረፋ ስርዓታቸው ውሎ ማደር የሚረጋገጠው ኢትዮጵያዊነት መመታት ሲችል ብቻ ነው ብለውም በፅኑ ያምናሉ፡፡ ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊነታችንን ሊያዳክም ብሎም ሊያጠፋ ይችላል ብለው የገመቱትን ሁሉ ከመፈፀም የማይመለሱት፡፡ ለዚህም ነው በስንት ጥረትና በብዙዎች ድካም ተሰባስቦና ተደራጅቶ የቆየውን የታሪክ መዛግብትና መፅሀፍት ከቤተ-መዘክር አውጥቶ በኪሎ ለመቸብቸብ የበቁት፡፡
ታዲያ ኢትዮጵዊ ነን የምንል ሁሉ ዘሬም እንደትናንቱ ይህን በማንነታችን ላይ የሚደረግ የጥፋት ዘመቻ ለማስቆም መነሳት ግድ ይለናል። እየተፈፀመ ያለው የታሪክ ማጥፋት ዘመቻ ለነፃነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ከምናደርገው ትግል እኩል ጎን ለጎን ለታሪካዊ ቅርሶቻችንና መዛግብቶቻችን ከጥፋት የመከላከልና የማዳን ስራ የመስራት የትውልድ ኃላፊነት አለብን፡፡ አለበለዚያ መምጫውን የማያውቅ መድረሻውን አያውቅምና የምናደርገው የነፃነት ትግል የተሟላ ውጤት ማስገኘቱ ጥያቄ ውስጥ መግባቱ አይቀሬ መሆኑን መገንዘብ ይገባናል፡፡ ተገንዝበንም ወያኔን በቃህ ልንለው ይገባል፡፡
በመጨረሻም ጂኦርጅ ኦርዌል ‘The most effective way to destroy people is to deny and obliterate their understanding of their own history” ብሎ ጽፎ ነበር። ህወሃቶች የዚህ ፍልስፍና ተከታዮች መሆንን በመምረጥ ለራሳቸው ውረደትን ፤ለአገራቸውም ውደቀትን ተመኝተዋል። ኢትዮጵያችን መንግስት በጠላትነት ተሰልፎ ከአገራችን ከህዝብና ለአገሪቷ እሴቶች ጋር የሚዋጋበት አገር ሁናለች። ህወሃት በብዙ መልኩ ሲታይ የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላት መሆንን የመረጠ ቡድን ነው። የህወሃት በኢትዮጵያ ላይ በጠላትነት መቆሙ ያስቆጣቸው ወጣቶች እምቢ ለአገሬ፤ እምቢ ለክብሬ ብለው ተነስተው ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ተሠማርተዋል።ግዜው ከእነዚህ ወጣቶች ጎን የምንቆምበትም ጭምር ነውና ተነሱና ለነፃነታችንና ለአገራችን ዝና ለህዝባችን ክብር አብረን ታግለን ጠላትን የመረጠውን ህወሃትን እናስወግድ እና ንፁህ አገር እንፍጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

Wednesday, November 19, 2014

የትብብሩ ፓርቲዎች እነማን ናቸው? እንዴትስ ተሰባሰቡ?

November 19,2014
- ወደ ዘጠኝ ዝቅ ያሉትስ በምን ሁናቴ ነው? 

ዮናታን ተስፋዬ (የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ)

አንዳንዴ ነገሮች በተጨባጭ ሳይሆን በመሰለን ነገር ብቻ እየተመለከትን እውነታውን እንዘነጋውና ችግር ናቸው ለምንላቸው ነገሮች ሌላ መላ ለማምጣት ብዙ እንደክማለን፡፡ መድከማችን ግን የችግሮቹን ወይም የሁነቶቹን አነሳስና አካሄድ ካላገናዘበና ከግምት ካላስገባ ከንቱ ድካም ይሆንና በስህተት ላይ ሌላ ማረሚያ ስህተት እየፈጠርን ችግሩን የባሰ እናወሳስበዋለን፡፡

ይህን ታሳቢ በማድረግ ሰሞኑን በትብብሩ ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስም ማብራሪያም ይሆን ዘንድ አጀማመራቸውንና 9 ከመሆናቸው በፊት ስንት እንደነበሩ፣ እነማን በምን ምክንያት ትብብሩን እንዳልተቀላቀሉ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ በዚህ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን የማስተናግድ ሲሆን በተረፈ ግን ሊጠየቁ የሚገቡ አካላት በአግባቡ እንዲጠየቁ እና በማነሳቸው ነጥቦች ላይ አስተያየትና መልስ እንዲሰጡ እጋብዛለሁ፡፡

በ9ኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር የተግባር ስምምነት ከመፈራረማቸው በፊት ሰማያዊ፣ አንድነትና መድረክን ጨምሮ 12 የሚደርሱ ፓርቲዎች ከ3 ወራት በላይ በጠረጴዛ ዙሪያ በልዑኮቻቸው በኩል ተወያይተውበታል፡፡ በነዚህ ወራት ውስጥም በጥቅሉ ባለፉት የፖለቲካ ውጣ ውረዶች የነበሩትን ድክመቶች በመፈተሽ እና በምን መልኩ በጋራ መስራት እንደሚቻል በሰፊው በመነጋገር ሰነዱን ለህዝብ ይፋ አድርገዋል፡፡ (በትብብሩ የተዘጋጁ ሰነዶችን በሰማያዊ ፓርቲ የፌስቡክ ገፅ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡)

ይህን ሰነድ በውይይት አዳብረው ለማጽደቅ የደረሱት ፓርቲዎች ዝርዝር ይህን ይመስላል፡-
1- ሰማያዊ ፓርቲ
2- መድረክ (እንደ ቡድን በመወከል)
3- አንድነት ለፍትህ እና ዴሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት)
4- መኢአድ (የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት)
5- መኢዴፓ (የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ)
6- ኢብአፓ (የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ)
7- ኦፌኮ (የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ)
8- አረና ትግራይ
9- የኦሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት
10- መዐህድ (የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት)
11- የከምባታ ህዝቦች ኮንግረስ
12- የጌድኦ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት
ናቸው፡፡

ከላይ ከተዘረዘሩት ፓርቲዎች መካከል በመድረክ የታቀፉት እና አንድነት ፓርቲዎች በጋራ ሲመክሩበት ከነበረው ስብስብ እና ባፀደቁት ሰነድ መሰረት በአንድ ምክንያት ብቻ ወደፊት መቀጠል ተስኗቸው ነበር፡፡

በመድረክና በአንድነት መካከል የተፈጠረው ቅራኔ በንግግር ባሳለፉበት ወራቶች ውስጥ ረግቦ የነበረ ቢሆንም ፓርቲዎቹ ወደ ተግባር ተኮር ፊርማ ሲያቀኑ ግን ዳግም አገርሽቶ ሂደቱንም ጭምር ማጓተት ጀመረ፡፡ መድረክ ‹‹ከጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ውጪ ከአንድነት ጋር መስራት ይቸግረናል፣ በመሀከል ያለው ጉዳያችን ሳይፈታ ወደ ፍርርም መሄድ አንችልም - በመሆኑም አንድነት ከመድረክ መውጣቱን ይፋ ያድርግ›› ሲል፤ አንድነት በበኩሉ ‹‹መድረክ እገዳውን ያንሳ ወይ በይፋ አንድነትን ከመድረክ ያስወጣው እንጂ እኛ ወጥተናል የምንልበት ምንም ምክንያት የለም›› ሲሉ ተከታከሩ፡፡ በዚህ መሃል ፓርቲዎቹ ለምርጫ ቦርድ በፃፉት ደብዳቤ ላይ ከአንድነት በስተቀር ሁሉም ፓርቲዎች ማህተምና ፊርማቸውን በማኖር ወደ ተግባር መንደርደር ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በግልፅ ትብብሩን ለህዝብ ይፋ ለማድረግና ቅርፅ ለማስያዝ ለመፈራረም በመድረክና በአንድነት በኩል ያለው ችግር በፓርቲዎቹ መሃከል በሚደረግ ውይይት አለመፈታቱ ሂደቱን አዘገየው፡፡

በትብብር ለመስራት ሲወያዩ የነበሩት ፓርቲዎች (በሙሉ) ከነደፉት የትግል ስትራቴጂ መካከልም ሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ መስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ አንደኛው ምርጫውን በተመለከተ የአጭር ጊዜ እቅድን ያካተተ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የረዥም ጊዜ ሆኖ የሀገሪቱን መፃዒ እድል ለመወሰን የሚያስችል እቅድን ያካተተ ነው፡፡ ከዚህ በመነሳትም ከ3 ወር በላይ የተካሄደው ውይይት ወደ ተግባር ለመግባት የመቋጫ ፊርማ የሚደረግበት ጊዜ ከላይ ባነሳሁት የመድረክና የአንድነት ጉዳይ ከሚጠበቀው በላይ መጓተት ከማስከተሉም በላይ ፓርቲዎቹ በየግል የሚያከናውኗቸው ተግባራት ላይ ድብታን አስከተለ፡፡

በመሆኑም ፓርቲዎቹ በየግላቸው (መድረክ በጠቅላላ ጉባኤው አንድነት በምክር ቤቱ) ችግሩን እንዲፈቱ የተቀሩት ፓርቲዎች ግን ወደ ስራ እንዲገቡ ስምምነት ላይ ስለተደረሰ ከእነዚሁ ፓርቲዎች ውጪ 9ኙ ወደ ፊርማ አመሩ፡፡

ይህ በሆነበት ሰሞንም አንድነት ውስጥ የነበረው የውስጥ ችግር አቶ ግዛቸው ሺፈራው (ኢንጂነር) በፈቃዳቸው ስልጣናቸውን በመልቀቃቸው በምትኩም አቶ በላይ ፈቃዱ የአንድነት ፕሬዘዳንት ሆነው በመሾማቸው የተነሳ አንድነት በትብብሩ ውስጥ የነበረው ሚና ቀነሰ፡፡ የተፈጠረው የስልጣን ክፍተት ማለትም አቶ ግዛቸው (ኢንጂነር) እንዲሁም ለትብብሩ የተወከሉት ሰዎች ለአዲሱ የፓርቲው መሪ አቶ በላይ በምሉዕነት መረጃ እና ሂደቱን ባለማካፈላቸው (አቶ ግዛቸው/ኢንጂነር/ ለሰንደቅ ጋዜጣ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ልብ ይሏል) ከትብብሩ ፊርማ ሳይሳተፉ ሲቀሩ፤ መድረክ በበኩሉ አንድነት ላይ ባሳደረው ጥርጣሬ የተነሳ ጠቅላላ ጉባኤውን ለመጠበቅ በማሰብ ከፊርማው ለጊዜው ታቀበ፡፡ ይህ ከሆነ ከሳምንታት በኋላ አንድነት ይበልጥ ትብብሩን ቢርቅም (ምክንያቱን አንድነት ቢመልሰው መልካም ነው) በመድረክ አባል ፓርቲዎች (በተለይም አረና እና ኦፌኮ) በኩል ደግሞ በትብብር ለመስራት ቁርጠኝነት ነበር፡፡

በሌላ በኩል ከሁለት ሳምንት በፊት የተደረገው የመድረክ ጠቅላላ ጉባኤ በትብብሩ ላይ መልካም ያልሆኑ ነገሮች (ለሚዲያ የማይበቁ እና ገንቢ ያልሆኑ) የተንፀባረቁበት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ዋናው ጉዳይ ይህ አይደለምና ውሳኔው ምን ነበር የሚለውን ማየቱ መልካም ነው፡፡ ከትብብሩ ጋር ሊያያዝ የሚችል የመድረክ ጠቅላላ ጉባኤ ካሳለፋቸው ውሳኔ ውስጥ አንዱ የአንድነት ጉዳይ ሲሆን መድረኩ አንድነት በ15 ቀን ውስጥ ውሳኔውን ካላሳወቀ ከስብስቡ በራሱ እንደወጣ ይቆጠራል የሚል ነበር፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የመድረኩ ፓርቲዎች በጋራ ስለትብብሩ ያሳለፉት ውሳኔ የለም፡፡ ይህንንም የመድረኩ አባል ፓርቲዎች ወይም መድረክ ራሱ ቢመልሰው መልካም ይሆናል፡፡

ለማጠቃለል - ከላይ ከሰፈሩት 12 ፓርቲዎች መሀል 9ኙ ትብብሩን ተፈራርመው ወደ ተግባር ቢገቡም ባጠቃላይ የነበረው ሂደት ግን ይሄን ይመስል ነበር፡፡ ከዚህ ያጎደልኩት ካለ በትብብሩ የረዥም ጊዜ ውይይት ተሳታፊ የነበሩና ክንውኑን ከስሩ በደንብ ሊያስረዱ የሚችሉት አቶ ግርማ በቀለ (የኦሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ኅብረት ሊቀመንበር) የበለጠ እንዲሉበት እጋብዛለሁ፡፡ የጨመርኩት ወይም ያዛባሁት ካለም እታረማለሁ፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ በመድረክ የታቀፉ ፓርቲዎችም ሆኑ አንድነት ወደ ትብብሩ እንዲመጡና ትግሉን ተቀላቅለው እንዲያጠናክሩት ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ ይህ ትብብር ለነፃነት በጋራ መታገልን ያለመና እየተንሰራራ ያለውን የትግል መንፈስ ወቅቱን በመጠነ መልኩ አጠናክሮ ለማስቀጠል ነውና ማንም በምንም ምክንያት ከመሳተፍ እዲገለል ሰማያዊም ሆነ የትብብሩ ፓርቲዎች አይሹም፡፡ በግሌም ቢሆን ትግሉን መቀላቀል ያለውን ፋይዳ ለናንተ መንገር ሳያሻኝ የፓርቲ ፖለቲካውን ትግል ጋብ አድርገን በጋራ ለነፃነት ትግሉ እንድንቆም በትህትና ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

ኑ! በተባበረ ክንድ ኢትዮጵያን ነፃ እናውጣ፤ መፃዒ እድላችንንም በጋራ እንወስን!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ሽመልስ ከማልና ፈትያ የሱፍ በፕሬስ ድርጅት እየተወዛገቡ ነው

November 19,2014
‹‹ችግሮች በአስቸኳይ ካልተፈቱ ለበላይ አካል እናሳውቃለን›› ፈትያ የሱፍ
‹‹ችግሮቹ ውጫዊ ናቸው›› አቶ ሽመልስ ከማል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የባህልና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ የሱፍ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዙሪያ እየተወዛገቡ እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

አቶ ሽመልስ ከማል የፕሬስ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሲሆኑ፣ ላለፉት አራት አመታት ድርጅቱ በተለያዩ ችግሮች ተዘፍቆ እያለ በቦርድ ሰብሳቢነታቸው ችግሮቹን መፍታት የነበረባቸው ቢሆንም ተደጋጋሚ ማሳሰቢያዎችን ችላ በማለት ድርጅቱ ከእነ ችግሮቹ እንዲዘልቅ አድርገዋል በማለት የባህልና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ የሱፍ ተናግረዋል፡፡ ሰሞኑን የ2007 የበጀት እቅድን ለመገምገም በተገናኙበት ወቅት የፕሬስ ድርጅት ቦርድ እና አስተዳደር በበርካታ ችግሮች ዙሪያ ወቀሳ እንደደረሰበትና ችግሮቹ እንዲፈቱም ማስጠንቀቂያ እንደተሰጠ በራሱ ድርጅት እየታተመ የሚወጣው ኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ በቅዳሜ እትሙ አስነብቧል፡፡

በድርጅቱ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር ብልሹነት መኖሩን የተናገሩት ፈትያ የሱፍ፣ ‹‹በራሱ ድርጅት በችግር የተተበተበ ጋዜጠኛ እንደምን የሌሎችን ድርጅቶችና ግለሰቦች የአሰራር ችግሮች ሊያጋልጥ ይችላል?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም በተደጋጋሚ ችግሮቹ ለድርጅቱ አስተዳደር በሰራተኞች ሲቀርቡለት የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ እያለ ማለፉን የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አውስተዋል፡፡

ፈትያ የሱፍ እንደሚሉት የፕሬስ ድርጅት ቦርድ እና አስተዳደር ችግሮቹን በአስቸኳይ የማይፈታ ከሆነ ወደሚመለከተው ከፍተኛ አካል ለማስተላለፍ ከውሳኔ ላይ መደረሱን አስረድተዋል፡፡

የድርጅቱ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው የድርጅቱ ችግሮች ውጫዊ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ድርጅቱ የበጀት ችግሮች እንዳለበት ያወሱት አቶ ሽመልስ፣ በተጨማሪ ግን በድርጅቱ ላይ መጥፎ እይታ ያላቸው እና መጠቀሚያ ለማድረግ የሚፈልጉ አካላት በሰራተኞች ስም አላማቸውን ለማስፈጸም የሚሯሯጡ ወገኖች አሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

‹‹የግል እና የመንግስት ሚዲያ ይለያያሉ፤ በአመለካከት፣ በአሰራርና በጥራት ልዩነት አላቸው›› በማለትም ሰራተኞቹ ፕሬስ ድርጅት እንደ ግል ሚዲያ ሊሰራ እንደማይችል ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰብስቤ ከበደ እና አቶ ሽመልስ ከማል ከፍተኛ የሆነ የጥቅም ትስስሮሽ እንዳላቸው የሚገልጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች፣ በዚህ ትስስራቸው የተነሳም የአቶ ሽመልስ ከማል ባለቤት ያለምንም ውድድር በድርጅቱ በጋዜጠኝነት ተቀጥራ ምንም ስራ ሳትሰራ ደመወዝ ትወስድ እንደነበር፣ በኋላ ግን ‹ስራውን አልቻልኩትም› በሚል ከድርጅቱ እንደወረጣች ይናገራሉ፡፡

አቶ ሰብስቤ ከበደ በሰራተኞች ዘንድ ተቀባይነት የሌላቸው እና በተለያዩ ስብሰባዎች በይፋ ‹አልቻልክም ድርጅቱን ልቀቅ› ተብለው በሰራተኞች እንደተነገራቸው ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ግን ከአቶ ሽመልስ ከማል ጋር ባለቸው የጥቅም ትስስር በስልጣናቸው እስካሁን እንደሚገኙ፣ ይህም ድርጅቱን እና ሰራተኞችን እየጎዳ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Photo: ሽመልስ ከማልና ፈትያ የሱፍ በፕሬስ ድርጅት እየተወዛገቡ ነው

‹‹ችግሮች በአስቸኳይ ካልተፈቱ ለበላይ አካል እናሳውቃለን›› ፈትያ የሱፍ
‹‹ችግሮቹ ውጫዊ ናቸው›› አቶ ሽመልስ ከማል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የባህልና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ የሱፍ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዙሪያ እየተወዛገቡ እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

አቶ ሽመልስ ከማል የፕሬስ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ ሲሆኑ፣ ላለፉት አራት አመታት ድርጅቱ በተለያዩ ችግሮች ተዘፍቆ እያለ በቦርድ ሰብሳቢነታቸው ችግሮቹን መፍታት የነበረባቸው ቢሆንም ተደጋጋሚ ማሳሰቢያዎችን ችላ በማለት ድርጅቱ ከእነ ችግሮቹ እንዲዘልቅ አድርገዋል በማለት የባህልና ቱሪዝም ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ፈትያ የሱፍ ተናግረዋል፡፡ ሰሞኑን የ2007 የበጀት እቅድን ለመገምገም በተገናኙበት ወቅት የፕሬስ ድርጅት ቦርድ እና አስተዳደር በበርካታ ችግሮች ዙሪያ ወቀሳ እንደደረሰበትና ችግሮቹ እንዲፈቱም ማስጠንቀቂያ እንደተሰጠ በራሱ ድርጅት እየታተመ የሚወጣው ኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ በቅዳሜ እትሙ አስነብቧል፡፡

በድርጅቱ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር ብልሹነት መኖሩን የተናገሩት ፈትያ የሱፍ፣ ‹‹በራሱ ድርጅት በችግር የተተበተበ ጋዜጠኛ እንደምን የሌሎችን ድርጅቶችና ግለሰቦች የአሰራር ችግሮች ሊያጋልጥ ይችላል?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም በተደጋጋሚ ችግሮቹ ለድርጅቱ አስተዳደር በሰራተኞች ሲቀርቡለት የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ እያለ ማለፉን የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ አውስተዋል፡፡ 

ፈትያ የሱፍ እንደሚሉት የፕሬስ ድርጅት ቦርድ እና አስተዳደር ችግሮቹን በአስቸኳይ የማይፈታ ከሆነ ወደሚመለከተው ከፍተኛ አካል ለማስተላለፍ ከውሳኔ ላይ መደረሱን አስረድተዋል፡፡

የድርጅቱ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል በበኩላቸው የድርጅቱ ችግሮች ውጫዊ መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ድርጅቱ የበጀት ችግሮች እንዳለበት ያወሱት አቶ ሽመልስ፣ በተጨማሪ ግን በድርጅቱ ላይ መጥፎ እይታ ያላቸው እና መጠቀሚያ ለማድረግ የሚፈልጉ አካላት በሰራተኞች ስም አላማቸውን ለማስፈጸም የሚሯሯጡ ወገኖች አሉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ 

‹‹የግል እና የመንግስት ሚዲያ ይለያያሉ፤ በአመለካከት፣ በአሰራርና በጥራት ልዩነት አላቸው›› በማለትም ሰራተኞቹ ፕሬስ ድርጅት እንደ ግል ሚዲያ ሊሰራ እንደማይችል ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ 

የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰብስቤ ከበደ እና አቶ ሽመልስ ከማል ከፍተኛ የሆነ የጥቅም ትስስሮሽ እንዳላቸው የሚገልጹት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች፣ በዚህ ትስስራቸው የተነሳም የአቶ ሽመልስ ከማል ባለቤት ያለምንም ውድድር በድርጅቱ በጋዜጠኝነት ተቀጥራ ምንም ስራ ሳትሰራ ደመወዝ ትወስድ እንደነበር፣ በኋላ ግን ‹ስራውን አልቻልኩትም› በሚል ከድርጅቱ እንደወረጣች ይናገራሉ፡፡ 

አቶ ሰብስቤ ከበደ በሰራተኞች ዘንድ ተቀባይነት የሌላቸው እና በተለያዩ ስብሰባዎች በይፋ ‹አልቻልክም ድርጅቱን ልቀቅ› ተብለው በሰራተኞች እንደተነገራቸው ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ግን ከአቶ ሽመልስ ከማል ጋር ባለቸው የጥቅም ትስስር በስልጣናቸው እስካሁን እንደሚገኙ፣ ይህም ድርጅቱን እና ሰራተኞችን እየጎዳ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Tuesday, November 18, 2014

‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

November18,2014
ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››
Photo: ‹‹ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ

ቀጥሎ ያለው አጭር መልዕክት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር በሚገኝበት ቃሊቲ ለተገኘው የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የገለጸው መልዕክቱ ነው፤ እንዲህ ቀርቧል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ

‹‹ነገሮችን ማወሳሰቡ ለማናችንም አይጠቅምም፡፡ ደግሞ በማናቸውም መልኩ የተወሳሰበ ችግር በመካከላችን ያለ አይመስለኝም፤ የለምም፡፡ እኛ እንደ ሀገር እና ህዝብ ከልዩነታችን ይልቅ አንድነታችን ይልቃል፡፡ ጥልቅ የሆነ ትስስሮሽ በመካከላችን አለ፡፡ በመነጣጠልና የህዝብ ተቆርቋሪዎችን በማሳደድ ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ የሚሮጡትን ወደጎን መግፋት ይኖርብናል፡፡ ከምንም በላይ ህዝብ እና ሀገር ይቀድማል፡፡

‹‹አሁን እዚህ እስር ቤት ውስጥ ስላለው ነገር ብነግርህ ብዙ ጊዜ ልወስድብህ እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ፈረንሳያውያን አንድ አባባል አላቸው፤ ‹ፊቴን፣ አካባቢየን ካየህ በቂ ነው፣ ነገሮችን ከእኔ እና አካባቢየ ላይ ማንበብ ትችላለህ› የሚል ነው አባባሉ፡፡ እዚህ ግቢ ስትገባ ያለው ሁኔታ ደስ እንደማይል ማንበብ አያቅትህም፡፡ ብዙ ነገሮች አሉ፣ ጊዜ ጠብቀው ይፋ ይሆናሉ፡፡

‹‹እንደ እናንተ ሁሉ ሰዎች መጥተው ሲጠይቁኝ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ለምሳሌ በዛሬው የእናንተ መምጣት ምክንያት ለ15 ቀናት ያህል ተረጋግቼ እሰነብታለሁ፡፡ ትልቅ የሞራል ስንቅ አለው፡፡ እንዳልኩህ ግን መሰረታዊው ጉዳይ በሀገር ደረጃ ያለውን ትስስሮሽ ከችግሮቻችን መውጫ መንገድ አድርጎ መጠቀም መቻሉ ላይ ነው፡፡ ይህ ነው የሁላችንንም ተስፋ ወደ እውነታ የሚለውጠው፡፡ ስለ ወደፊቱ ማሰብ ይኖርብናል፡፡ አሁን ያለንበት ሁኔታ ወደ ተሻለ ነገር መለወጥ አለበት፡፡››

Hearing On the Human Rights Dilemmas in Ethiopia

November 18, 2014

Tom Lantos Human Rights Commission – Hearing On the Human Rights Dilemmas in Ethiopia – Testimony of Felix Horne, Researcher, Africa Division

Press Release

Mr. Chairman and members of the committee, thank you for providing me the opportunity to speak today about the human rights situation in Ethiopia.

The other panelists have articulated some of the critical issues that are facing Ethiopia ahead of the May 2015 elections. I would like to elaborate on human rights concerns associated with Ethiopia’s many development challenges.

Ethiopia is the one of the largest recipients of development assistance in the world, including more than $800 million in 2014 from the US government. Many of Ethiopia’s 94 million people live in extreme poverty, and poverty reduction is rightly one of both the US and Ethiopian government’s core goals. Improving economic and human development is fundamental to ensuring that Ethiopians are able to enjoy their rights to health care, education, shelter, food and water, and Ethiopia’s government, civil society, international donors and private investors all have important roles contributing to the realization of these rights.

But sustainable development also requires a commitment to the full range of human rights, not just higher incomes, access to education and health care, but the ability for people to express their views freely, participate in public policy decision-making, join associations of their choice, have recourse to a fair and accessible justice system, and live free of abuse and discrimination.

Moreover, development that is not rooted in respect for human rights can be counter-productive, associated with abusive practices and further impoverishment of people already living in situations of extreme poverty. In Ethiopia, over the past few years Human Rights Watch has documented disturbing cases where international donors providing development assistance are turning a blind eye to government practices that fail to respect the rights of all beneficiaries. Instead of improving life in local communities, these projects are proving harmful to them. And given the repression of independent voices, media and associations, there are no realistic mechanisms for many local communities to express their views to their government. Instead, those who object or critique the government’s approach to development projects face the prospect of intimidation, harassment and even serious abuse.

In 2011 in Ethiopia’s western region, Gambella, Human Rights Watch documented such abuses during the implementation of the first year of the government’s “villagization” program. Gambella is a region populated by indigenous groups who have suffered from political marginalization and lack of development for decades. In theory the villagization program aimed to address some of these concerns. This program required all indigenous households in the region to move from their widely separated homes into larger villages – ostensibly to provide improved basic services including much-needed schools, health clinics and roads.

I was in Gambella for several weeks in 2011 and travelled to 16 different villages in five different districts. I met with people who had not yet moved from their homes and others who had been resettled. I interviewed dozens of people who said they did not wish to move but were forced by the government, by police, and by Ethiopia’s army if necessary. People described widespread human rights violations, including forced displacement, arbitrary arrest and detention, beatings, and rape and other sexual violence. Thousands of villagers fled into neighboring countries where they became refugees. At the same time, in the new villages, many of the promised services were not available and the food security situation was dire.

The villagization program has also been implemented in other marginalized regions in Ethiopia. These regions are the same areas where government is leasing large pieces of land to foreign investors, often from India, China and the Gulf states, without meaningful consultation with local communities, without any compensation being paid to local communities, and with no benefits for local communities other than low-paying labor jobs on the plantations.

In the Omo valley in southern Ethiopia, Human Rights Watch found that the combination of sugar and cotton plantations and hydroelectric development is causing the displacement of up to 200,000 indigenous people from their lands. Massive amounts of water are being used for these projects which will have devastating impacts for Lake Turkana across the border in Kenya and the 300,000 indigenous people who live in the vicinity of the lake and depend upon it. The displacement of communities in the Omo valley is well underway. As in Gambella, communities in the Omo valley told Human Rights Watch about coercion, beatings, arrests and threats from military and police to force people to move to new settlements.

Human Rights Watch also found politically motivated abuse in development programs. In 2010, we documented discrimination and “political capture” in the distribution of the benefits of development programs especially prior to the 2010 elections. Opposition party supporters and others who did not support the ruling party were denied access to some of resources provided by donor-funded programs, including food aid, micro credit, seeds, fertilizers, and other critical agricultural inputs needed for food security, and even employment opportunities. Schools, funded as part of education programs by the US and other development partners, were used to indoctrinate school children in ruling party ideology and teachers were required to report youth perceived to support the opposition to the local authorities. These government practices, many of which continue today, show the intense pressure put on Ethiopian citizens to support the ruling party, and the way in which development aid is manipulated to discriminate against certain communities.

All of these cases have several common features. First, the Ethiopian government routinely denies the allegations without investigation, claiming they are politically motivated, while simultaneously restricting access for independent media and investigators. Second, these programs are directly and indirectly funded by Western donors, who seem unwilling to acknowledge, much less address human rights concerns in Ethiopia.

Monitoring and evaluation of these programs for human rights abuses is inadequate. Even when donors carry out assessments to look into the allegations, as has happened in Gambella, they are not conducted rigorously and do not ensure victims of abuses can speak freely and safely. In the current environment in Ethiopia, it is essential for anyone seeking to investigate human rights violations to go to locations where victims can speak openly, to understand the dynamics of the local communities, and recognize the depths of the fear they are experiencing.

All of these problems are exacerbated by the ongoing government crackdown on the media and civil society. The independent press has been ravaged since the 2010 election, with the vast majority of journalists terrified to report anything that is remotely critical of the government. In October I was in a country neighboring Ethiopia where over 30 journalists have fled in the past few months alone. I spoke to many of them: their papers were closed, their families were threatened, and many had been charged under repressive laws merely because they criticized and questioned the Ethiopian government’s policies on development and other issues. I spoke with someone who was forced to seek asylum abroad because he had questioned in writing whether the development of Africa’s largest dam on the Nile River was the best use of money in a country where poverty is pervasive.

As for Ethiopian civil society, it has been decimated by another law, the Charities and Societies Proclamation. It has made obtaining foreign funding nearly impossible for groups working on human rights, good governance, and advocacy. Leading members of the human rights movement have been forced to flee abroad.

Some people take to the streets to peacefully protest. Throughout 2014 there were various protests throughout Ethiopia. In many of these protests, including during the student protests in the Oromia region in April and May of this year, the security forces used excessive force, including the use of live ammunition against the students. We don’t even know how many Oromo students are still detained because the government publicizes no information, there is no comprehensive human rights monitoring and reporting, and family members are terrified of reporting the cases. Members of the Muslim community who organized protests in 2012 against what they saw as government interference in religious affairs have also paid an enormous price for those demonstrations, with many beaten or arrested and most of the protest organizers now imprisoned on terrorism charges.

Finally, bringing about change through the ballot box is not really an option. Given that 99.6 percent of the parliamentary seats in the 2010 election went to the ruling party and that the political space has shrunk dramatically since then, there is little in the way of a viable opposition that can raise questions about government policy, including development plans, or other sensitive topics.

This situation leaves Ethiopians no real means to express concerns over the policies and development strategies imposed by the government. They either accept it, they face threats and imprisonment for speaking out, or they flee their country as thousands have done. The refugee communities in countries neighboring Ethiopia are full of individuals who have tried to raise concerns in all of these ways, and are now in exile.

To conclude, we all recognize that Ethiopia needs and requires development. The problem is how development is being undertaken. Development projects need to respect the rights of the local communities and improve their quality of life, regardless of ethnicity or political perspective. The United States and Ethiopia’s other major partners can and should play a leading role in supporting sustainable, rights-respecting development. The US should not accept arguments that protecting human rights is in contradiction to development goals and implementation.

In 2014, the appropriations bill required the US to scrutinize and suspend funding for development programs in Ethiopia that might contribute to forced evictions in Ethiopia, including in Gambella and Omo. This was an important signal that the abuses taking place were unacceptable, and this should be maintained in the upcoming FY15 appropriations bill, whether it is a stand-alone bill or a continuing resolution.

As one of Ethiopia’s key partners and supporters of Ethiopia’s development, the US needs to do more to ensure it is rigorously monitoring and consistently responding to human rights abuses in Ethiopia, both bilaterally and multilaterally. The US should be pressing the Ethiopian government to ensure that there is genuine consultation on development initiatives with affected communities, that more robust monitoring is put in place to monitor for potential abuses within programs, and that independent civil society, both domestic and foreign, are able to monitor and report on rights abuses. Respect for human rights is first and foremost a concern of all Ethiopians, but it is also central to all US interests in Ethiopia, from security to good governance to sustainable development.

Monday, November 17, 2014

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ

November 17,2014
በቢሮክራሲያዊ ሴራ የዜጎችን ህገመንግሥታዊ መብት ማፈን ሠላማዊ ትግሉን አያቆመውም!!

ዘጠኝ /9/ ህጋዊ ሰውነት ያለን ፓርቲዎች በትብብር ለመሥራት በተስማማነው መሠረት የአጭር ጊዜ የጋራ ዓላማችንን ማስፈጸሚያ ተግባራት የመጀመሪያ ዙር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የአንድ ወር ዕቅድ አውጥተን ወደ ሥራ መግባታችን ይታወሳል፡፡ የዚሁ የአንድ ወር ዕቅድ አካል ከሆኑት ተግባራት ቅዳሜ በ6/03/07ዓ.ም ‹‹ዲሞክራሲያዊ ምርጫና የአፈጻጸም መርሆዎች›› በሚል ርዕስ የአዳራሽ ውይይት በተሳካ ሁኔታ አከናውነን በትናንትናው ዕለት በ07/03/07ዓ.ም ደግሞ ከአዲስ አበባ ሰሜን ምስራቅ /ከአራት ኪሎና አካባቢው / ህዝብ ጋር በአደባባይ በቤልኤር ሜዳ ተገናኝተን በምርጫ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የትብብራችን አባል የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባውን እንዲያስተባብር በሰጠነው ኃላፊነት- የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1983 የምጠይቀውን ሁኔታ አሟልቶ ለከንቲባ ጽ/ቤቱ የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በ02/03/07 ደብዳቤ ማስገባቱ፣ የጽ/ቤቱ ክፍልም ለደብዳቤው በ04/03/07 ዓ.ም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ከክፍሉ የተጻፈለት ደብዳቤ፡-

1. የተሰጠው መልስ ዕውቅናውን በተመለከተ ግልጽ ያለመሆኑን፤

2. ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ መሰረት አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ የተገለጸውን የሚጻረር መሆኑን፣

3. በአዋጁ አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ ከተደነገገው ጋር የሚቃረን፤
በጥቅሉ በክፍሉ የተጻፈው ደብዳቤ በአዋጁ መሰረት በ12 ሰዓት ውስጥ የተሰጠ ምላሽ ካለመሆኑም፣ ጊዜና ቦታውን ለመቀየር እንኳ አማራጭ ያልቀረበበት፣ ለስብሰባው ዕውቅና ለመንፈግ እንደ ምክንያት የቀረበውም ግልጽ ሆኖ ባለመቅረቡ ፓርቲው የተጻፈውን ደብዳቤ አሳማኝ ሆኖ እንዳላገኘውና እንዳልተቀበለው፣ በመሆኑም ስብሰባው አስቀድሞ በተገለጸው ቦታና ጊዜ እንደሚካሄድ በ05/03/07 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ መልስ በመጻፍ ለክፍሉ ገቢ አድርጎ ዝግጅቱን ቀጥለናል፡፡ ከዚህ በኋላ ባለው ጊዜ ክፍሉ በደብዳቤም ሆነ በአካልና ስልክ ሳያገኘን ዝግጅታችንን አጠናቀን በዕለቱ በተገጸው ሰዓት ወደ ቦታው ስንሄድ ያጋጠመን ሁኔታ ፡-

1ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 9 የተቀመጠውን ‹‹የህገመንግስት የበላይነት›› ያልተከተለ፤

2ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 10(2) የተቀመጠውን የዜጎች መብት በመዳፈርና ለማፈን፤

3ኛ/በህገ መንግስቱ አንቀጽ 12 የተቀመጠውን ‹‹የመንግስት አሠራር ተጠያቂነት›› በጣሰ
ሁኔታ፤

4ኛ/ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 13 የተቀመጠውን የህገ መንግስት ‹‹ተፈጻሚነትና አተረጓጎም›› በመተላለፍ፤

የተፈጸመ ኢህገመንግሥታዊና ኢ-ዲሞክራሲያዊ፤ በሠላማዊ ዜጎችና በፖሊስ መካከል ግጭት የሚፈጠርበትን ሁኔታ የሚጋብዝ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ ይህ ሁኔታ በወቅቱ በቦታው የተገኙት
የአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ ባልደረባና የተልዕኮው ቡድን መሪ ከመሆናቸው ውጪ የራሳቸውን ማንነት/ሥምና ኃላፊነት ለመግለጽ ድፍረት በማጣታቸው፣ በአንድ በኩል ‹‹የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባቸው የታዘዙትን የማስፈጸም ግዳጅ›› በሌላ በኩል ከስብሰባው አስተባባሪዎችና የትብብሩ አመራሮች ለቀረቡላቸው አዋጁን ያጣቀሱ ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄዎች ‹‹አሳማኝ መልስ ለመስጠት በመቸገራቸው ›› በጭንቀት ውስጥ መውደቃቸውን አረጋግጠናል፡፡ በቦታው የነበረን ቆይታ በተራዘመና ጥያቄኣችንም በተደጋገመ መጠን በአንድ በኩል ‹‹የቡድን መሪው›› ጭንቀት ወደ ኃፍረት፣ ብስጭትና የግጭት ስሜት የፖሊስ አባላቱ መንፈስ ደግሞ ወደ ሥጋት ሲሸጋገር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የስብሰባውን ጥሪ ተቀብለው የመጡ ዜጎች ‹‹ስብሰባው ይጀመር፤ እዚህ የመጣነው በመብታችን ልንደራደር አይደለምና የሚያመጡትን እናያለን ›› ግፊት እያየለ በተሰብሳቢውና በፖሊስ መካከል እሰጥ አገባውና ፍጥጫው እየተጠናከረ ሄዷል፡፡

የትብብራችን አመራር መስተዳድሩ በደብዳቤው የገለጸውን ማለትም ‹‹ጥያቄ በቀረበበት ቀን ቀድም ብሎ ዕውቅና የተሰጣቸው ፕሮግራሞች ስላሉ በዕለቱ የፀጥታ አስከባሪዎች የኃይል እጥረት ሊያጋጥም ስለሚችል›› የተባለውን በወቅቱ በህዝቡ ውስጥ ፈሶ ከነበረው ከ100 በላይ የአዲስ አበባና ፌዴራል ፖሊስ ቁጥርና በተጠባባቂነት በአንድ ማክ መኪና ተጭኖ በጋራዥ ውስጥ ተደብቆ ይጠባበቅ ከነበረ የፖሊስ ኃይል ጋር በማገናዘብ በሂደቱ ሴራ እንዳለበት ማረጋገጥ ችሏል፡፡ በመሆኑም አመራሩ ሂደቱን ከትግሉ ዓላማና መርህ ፣ለዓላማው ማስፈጸሚያ በተከታታይና በቀጣይነት በታቀደው ሰላማዊ ትግል ላይ ከሚያስከትለው አሉታዊ ተጽዕኖ፣ ለእንዲህ ዓይነቱ ሴራ ከተደረገው ዝግጅትና በፖሊስ በኩል ከታየው የ‹‹ጭንቅ›› ስሜትና ተደጋጋሚ ውትወታ ካለበት ኃላፊነት ጋር በማገናዘብ የዕለቱ ፕሮግራም በሰላም እንዲጠናቀቅ የማረጋጋት ተግባር በማከናወን ህዝቡን በሠላም አሰናብቷል፡፡ ከዕለቱ ውሎ በመነሳት አመራሩ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የሚከተሉትን የጋራ ግንዛቤዎች ጨብጧል፡፡

1ኛ/ ትብብሩ በመርሃ ግብሩ መሰረት በዕለቱ የተሞከረው ህዝባዊ ስብሰባ ለታሰበለት የድምር ውጤትና የትግሉን ቀጣይነት የማረጋገጥ ፋይዳ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል፤

2ኛ/ የዕለቱ ውሎ ገዢው ፓርቲ የደረሰበትን የፍርኃት እርከን የሚመለክት ነው፤ ደፍሮ ባይናገረውም በተግባር በሠላማዊ ህዝባዊ ንቅናቄዎች የቱን ያህል እንደሚሸበር በተግባር ያረጋገጠበት ነው፤

3ኛ/በስብሰባው ላይ የተገኙ ኢትዮጵያዊያን ያሳዩት ቆራጥነትና ለመብታቸው ለመቆም ያላቸው ጽናትና የቱንም ዋጋ ለመክፈል ያላቸው ዝግጁነት ለቀጣዩ ትግል ከፍተኛ ሥንቅ ነው፡፡ይህም ለተያያዝነው የጋራ ትግል በእጅጉ አበረታች ነው ፤

4ኛ/ገዢው ፓርቲ/መንግሥት ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜት ለመውጣት ያስቀመጠው የሴራ መፍትሄ መስዋዕትነቱን ይጨምር እንደሆን እንጂ፣ ትግሉን አያቆመውም፡፡

ከእነዚህ ግንዛቤዎች በመነሳት-

1. በተለይ ፡-

1.1.ከገዢው ፓርቲ የማስፈራሪያ ፕሮፖጋንዳ ራሳችሁን ነጻ አውጥታችሁ በተጠራው ስብሰባ ላይ ተገኝታችሁ ለነጻነታችሁና መብታችሁ ያላችሁን ቀናኢነት የገለጻችሁ፣ የቱንም መስዋዕትነት የመክፈል ዝግጁነታችሁን ላረጋገጣችሁ ኢትዮጵያዊያን ያለንን አድናቆት እየገለጽን ትግላችን ጥያቄዎቻችን እስኪመለሱና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አውን እስከሚሆን ተከታታይና ቀጣይ ስለሆነ የተጽዕኖ አድማሳችሁን አስፍታችሁ የበለጠ ተሳታፊ ይዛችሁ በትግሉ እንድትቀጥሉ፤

1.2. በህዝብ ኃይል የሚተዳደሩ መገናኛ ብዙሃን ሙሉ በሙሉ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ውለው ገዢውን ፓርቲ ከማገልገል አልፈው በሠላማዊ ትግል የፖለቲካ ኃይሎች ላይ አፍራሽ ፕሮፖጋንዳ በሚነዙበት ወቅት የህዝብ ዓይንና ጆሮ ሆናችሁ የምታገለግሉ በአገር ቤትና በውጪ የምትገኙ የመገናኛ ብዙኃን ሁሉ ስላደረጋችሁልን ድጋፍ እያመሰገንን፣ በቀጣይም በህዝብ ወገናዊነታችሁ በመቀጠል ከጎናችን እንድትቆሙ፤

1.3.ገዢው ፓርቲ ከገባበት ከፍተኛ ሥጋትና ፍርኃት ለመውጣት እየተከተለ ካለው የሴራ ፖለቲካ ወጥቶ የህዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ ራሱን ለለውጥ እንዲያዘጋጅ፤

1.4. እንደ ፖሊስ ኃይል ያላችሁ የመንግሥት አስፈጻሚ አካሎች ለገዢው ፓርቲ ሴራ ራሳቸውን በማጋለጥ ከሠላማዊ የመብት ታጋዮች ጋር አላስፈላጊ ግጭት ውስጥ እንዳይገቡና ከህገ መንግሥቱና ከህዝብ ጎን ቆመው ከህግና ታሪክ ተጠያቂነት ራሳቸውን ነጻ እንዲያወጡ፤

2. በአጠቃላይ፡-

2.1. የትግሉ ዓላማ የአገርና የህዝብ፣ቀዳሚ ባለቤቱም እኛው - ነጻነታችንም በእጃችን ነውና በጋራ ‹‹በቃን›› በማለት ለነጻነት በምናደርገው ትግል በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጪ የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ አገራችንን ከወረደችበት አዘቅት እኛም ከሚደርስብን ጭቆናና ሥቃይ ለመውጣትና የዜግነት ክብራችን ለማስመለስ በሚደረገው ቀጣይና ተከታታይ ሠላማዊ ትግል ለምናቀርበው ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ፤

2.2. የትግሉ ባለቤት ሁላችንም በመሆናችን ብቻ ሣይሆን ‹‹አገራችን ላለችበት ምስቅልቅል ሁኔታ በተናጠል ተመጣጣኝና ዘላቂ መፍትሄ መስጠት ከአንድ ፓርቲ አቅም በላይ ነው›› ከሚለው የጋራ ድምዳሜያችን አንጻር በትብብሩ ያልታቀፋችሁ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋችሁ የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረማችሁና እስከዛሬም ያልተመለሳችሁ እንዲሁም ሌሎች ሠላማዊ ዲሞክራቲክ የተቃውሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ እንድትቀላቀሉ፤
2.3. የዓለም አቀፉና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት መንግስታት ተለዋዋጭና አላፊ፣ አገርና ህዝብ ግን ቋሚ ናቸውና በግንኙነታችሁ የህዝብ ለህዝብ ዘላቂ ጥቅምንና የአገራትን ታሪካዊና ፖለቲካ ግንኙነት ከግምት በማስገባት ሰልፋችሁን ከህዝቡ ጎን እንድታደርጉ፤

ጥሪያችንን ስናስተላልፍ በእኛ በኩል ለአገራችንንና ህዝቧ የምናደርገው የጋራ የተባበረ ትግል የሚጠይቀንን መሥዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል ያለንን ዝግጁነትና ቁርጠኝነት በድጋሚ እናረጋግጣለን!

የተቀናጀና የተባበረ ህዝባዊ ሠላማዊ ትግልን አሸንፎ በሥልጣኑ የዘለቀ አንድም አምባገነናዊ መንግሥት ዓለማችን አታውቅም!!

ስለሆነም እናሸንፋለን!!

ሕዳር 08 ቀን 2007 ዓ.ም

አዲስ አበባ