Thursday, October 23, 2014

የሐብታሙ አያሌው የጤንነት ጉዳይ አሳሳቢ ሆኗል (በዳዊት ሰለሞን)

October 23,2014
‹‹ኢህአዴግ ከታሪክ እንዲማር››ባገኘው መድረክ ሁሉ ከመምከር ተቆጥቦ የማያውቀው ወጣቱ ፖለቲከኛ ሐብታሙ አያሌው በጸና መታመሙ ከተሰማ ረዘም ያሉ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡
እጅግ ቀዝቃዛ ክፍል ውስጥ በማዕከላዊ መታሰሩ ሳያንስ ዝናብ በሚዘንብበት ሰዓት ከክፍሉ እያወጡት አሸንዳ ስር በማስቀመጥ ዝናብ እንዲቀጠቅጠው ያደርጉ እንደነበር ዘግናኙን ቅጣት የተከታተሉ እስረኞች ከተናገሩም ቀላል የማይሰኙ ወራቶች አልፈዋል፡፡
Habtamu Ayalew
Habtamu Ayalew

መንፈሰ ጠንካራው ሐብታሙ በጀርባ ህመም እየተሰቃየ መሆኑን ለፍርድ ቤት ተናግሮ የነበረ ቢሆንም ህገ ወጦቹ አሳሪዎች ታምሚያለሁ ማለቱን እንደ ድል በመቁጠር ህክምና እንዲያገኝ በምርመራ ወቅት እንዲተባበራቸው መደራደሪያ በማድረግ አቅርበውለት ነበር፡፡
ደምበኞቻቸውን ህጉ በሚፈቅድላቸው መሰረት ማግኘት ባለመቻላቸው ጠንከር ያለ ተቃውሞ ያሰሙት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ሐብታሙ መታመሙን ቃለምልልስ ባደረግኩላቸው ወቅት ነግረውኝ ነበር፡፡
አሁን ማዕከላዊዎች ሐብታሙን ሆስፒታል መውሰዳቸው ተሰምቷል፡፡ነገር ግን ሐብታሙ መርማሪዎቹ ህገ ወጥ ድርጊት በምርመራ ወቅት ሲፈጽሙበት የተመለከታቸው በመሆኑ እነርሱ ወደ ህክምና ወስደውት ጤንነቱን እንዲያገኝ ይረዱኛል ብሎ ሊያምን አይችልም፡፡
ለሐብታሙ የሚደረግ ህክምና እምነቱን ሊያሳድርበት በሚችልበት መንገድ፣ቤተሰቦቹ በተገኙበት ጠበቃው ሁኔታውን ሊከታተሉ በሚችሉበትና ፓርቲው አንድነት የሚያውቀው መሆን ይጠበቅበታል፡፡
—–ህክምና ማግኘት ተፈጥሯዊ መብት የመሆኑን ያህል በሚሰጠው ህክምናም ታካሚዎች እምነታቸውን ማሳደራቸው ተፈጥሯዊ መብት ተደርጎ ሊወሰድ ይገባዋል——

ባነሰ ወጪ ድልን መቀዳጃ አመቺ ጊዜ ላይ ነን – እንጠቀምበት!

October 23,2014

በአለፈው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በምንም የማይገናኙ እና የተመሰቃቀሉ የሚመስሉ፤ በጥልቀት ላያቸው ግን የተያያዙና የተደጋገፉ ከመሆናቸው አልፎ እንደከዋክብት ፈለግ አቅጣጫን የሚያመላክቱ በርካታ ክስተቶች ተስተውለዋል። የጊዜ ቅደም ተከተላቸውን ሳንጠብቅ አንዳንዱን ለአብነት ያህል እናንሳ።
በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የዘነበው የዘለፋና የዛቻ ውርጅብኝ ህወሓት በቀጥታ በማይቆጣጠራቸው ማኅበራት ላይ ሁሉ ሲደርስ የቆየው ነፃ ማኅበራትን የማፍረስ ዘመቻ አካል መሆኑን መገንዘብ ቀላል ነው። ህወሓት የእስልምና እምነት ተከታዮችን ነፃ ማኅበርን በቁጥጥሩ ውስጥ ካስገባ በኋላ ፊቱን ወደ ክርስትና በተለይም ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማዞሩ የተረጋገጠ ነገር ሆኗል። ወያኔ በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ ማንም ከጥቃት እንደማያመልጥ፤ ለምንም ጉዳይ ይቋቋም ወያኔ የማይቆጣጠረው ማኅበር እንዲኖር የማይፈልግ መሆኑ ከዚህ በፊት የሚታወቅ ቢሆን በድጋሚ ማረጋገጫ የሰጠበት አጋጣሚ ሆኗል።
በመዠንግር ከአስራ አምስት በላይ የሥርዓቱ ታጣቂዎች ከነመሣሪያዎቻቸው አገዛዙን ክደው ጠፍተዋል። የጠፉትን ለማደን የመጡ ወታደሮች ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በፈጠሩት ግጭት በርካቶች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በዚህ ግጭት ብቻ ከ40 በላይ ወታደሮች መገደላቸው ይነገራል። በጋምቤላ እና በቤንሻንጉልና ጉሙዝ ወረዳዎች ውጥረት ሰፍኗል። ከመሃል አገር ሄደው ኑሮዓቸውን እዚያው ያደረጉ ዜጎች ላይ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚደርስባቸው አፈናና እንግልት ጨምሯል። ግድብ እየተሠራበት ነው በሚባለው አካባቢም ከአሁኑ የፀጥታ ችግር እየደረሰ መሆኑ መረጃዎች ይጠቅማሉ። ወያኔ በምሥራቅ ኢትዮጵያ ኦጋዴን ውስጥ የገባበት ዓይነት ማጥ በምዕራብና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያም እየመጣ መሆኑ አመላካች ነው። የመከላከያ ሠራዊት አባላት መፍለስና የነፃነት ታጋዮችን መቀላቀል የእለት ለእለት ትዕይንት እየሆነ ነው። ወያኔ በመሃል አገር በሙስሊም እና በክርስቲያን ወገኖቻችን የእምነት ማኅበራት ላይ በከፈተው ግንባር “ጠብ ያለሽ በዳቦ” ሲል ዳር ዳሩን ሠራዊቱና ሕዝቡ ለማይቀረው ፍልሚያ እየተዘጋጁ ነው።
በርካታ ጋዜጠኞችና አሳታሚዎች ለስደት ከተዳረጉ ጥቂት ሣምታት በኋላ “የሚመጣውን ሁሉ አገሬ ውስጥ ሆኜ እቀበላለሁ” ያለውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ አሳዛኝም አስቂኝም በሆኑ ክሶች ጥፋተኛ ተብሎ ወደ ወህኒ ተግዟል። በጋዜጠኞች ሕይወትና ሞት ወያኔ የፓለቲካ ቁማር መጫወቱ አጠናክሮ ቀጥሏል። በአንፃሩ ደግሞ በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያን አምርረዋል። የወያኔ ሹማምንት በአሜሪካ እና አውሮፓ የሚዘዋወሩት በሰቀቀን ሆኗል፤ በየደረሱበት ውግዘትና ውርደት ይጠብቋቸዋል። የወያኔ ሹማምንት በኢትዮጵያዊያን የተጠሉና የረከሱ ተደርገዋል።
የዩ.ኤስ. አሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ከኢትዮጵያ ቴሌቬዥን ባላነሰ ወያኔን በልማት አምጭነት አሞካሽተዋል። የአውሮፓ መንግሥታት በሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ወያኔን እየተቹም ቢሆን ወያኔ በሚሰጣቸው ቁጥር እየማለሉ “እውነትም ልማት እየተፋጠነ ነው” በሚል ተስፋ ማበረታቻ እየሰጡት ነው። በዚህ ደስታ አቅሉን ያጣው ኃይለማርያም ደሣለኝ የውሸት ቁጥሮችን የመፈብረክ ሥራ ከስታትስቲክስ ጽ/ቤት ነጥቆ የራሱ የሥራ ድርሻ አድርጎታል። በዚህ አዲሱ ሥራውም ውጤት እያስመዘገበ ነው። ሁለት መቶ አምሳ (250) ሚሊዮን ኩንታል ሰብል አመረትን ባለ በሶስት ወሩ ሶስት መቶ (300) ሚሊዮን ኩንታል አመረትን በማለት በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ የ20 በመቶ የግብርና ምርቶች የውሸት እድገት ፈጥሯል።
የውሸት ቁጥሮች ፈጠራ እንዲህ ቢፋፋምም፤ ቁጥሮቹን የሰሙ ኦባማ፣ የአውሮፓ መንግሥታት ሆነ ዓለም ባንክ ቢያወድሱትም አገር ውስጥ ያለው ሀቅ አልቀየረም። ስኳር፣ ዘይት፣ እንቁላልና ሌሎች የምግብ ግብዓቶች የደረሱት የሚያውቅ ጠፍቷል። ውሃ የለም፤ መብራት የለም፤ ኔት ዎርክ የለም። የአዲስ አበባ ጎዳናዎች በመቸውም በባሰ መጠን በነዳያን እና በቤት አልባ በረንዳ አዳሪ ዜጎች ተጥለቅልቀዋል። ድህነት ከጎጆዎች ወጥቶ ጎዳናዎች ላይ ፈሷል። የገንዘብ ዋጋ ወርዶ ወርዶ ብር ቁራጭ ወረቀትን ማከል አቅቶታል። በጥቂት በዝርፊያ በደለቡ የህወሓት ሹሞችና በብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ መካከል ያለው የኑሮ ልዩነት ማነፃፀር እንኳን እንዳይቻል ሆኖ ተራርቋል።
የመከላከያ ሠራዊት አባላት በኑሮም በዘረኝነትም እየተማረሩ ነው፤ አለቆቻቸው ግን አሁንም በዝምድና እየተፈላለጉ እየተሿሿሙ ነው። አሁንም በዝምድና እየተፈላለጉ እርስ በራሳቸው እየተሿሿሙ ጄኔራሎች ሁሉ ዘመዳሞች ሆኑ፤ በሥራቸው ያለውን ኢትዮጵያዊውን ወታደር ግን እንደ ግል አሽከራቸው እንኳን ማየት ተጠይፈዋል። በጄኔራሎችና በሠራዊቱ መካከል ያለው ግኑኝነት ከጌታና ሎሌም የባሰም ሆኗል።
እነዚህ ምስቅልቅል ያሉ ሁኔታዎች ምንን ያመለክታሉ?
እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ ምስቅልቅል ያሉ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ የተነተነ ሰው በምስቅልቅነታቸው ፋንታ ሥርዓት የያዙ ፈለጎችን ያገኛል። ከእነዚህ ፈለጎች አንዱ የሚያመላክተው መጪዎቹ ጥቂት ወራት ለኢትዮጵያ ወሳኝ ጊዜያት እንደሚሆኑ ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ ምስቅልቅል ውስጥ ያለው ወያኔ ነው። ወያኔ፣ በድንገት አዕምሮዉን እንደሳተ ሰው ይይዘው ይጨብጠው ጠፍቶታል። በዚህ ምስቅልቅል ወቅት ውስጥ በቢሊዮን የሚገመት የሕዝብ ሀብት አውጥቶ፤ የማይረቡ ድርሳናትን ጽፎ የአገሪቱን ዜጋ በሙሉ ካላሰለጠንኩ ሞቼ እገኛለሁ ማለቱ ራሱ የውስጡን መመሰቃቀል ማሳያ ነው። ስልጠናውን ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆን አሰልጣኞችም ጭምር የጠሉት ቢሆንም ፋታ የሚሰጠው መስሎት ገፍቶበታል። የነፃነት ኃይሎች በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ ኃይላችንን አሰባስበን ከገጠምነው ባነሰ ወጪ ድልን መቀዳጃ አመቺ ጊዜ ይሆናል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ያለንበት ወቅት ወሳኝነት በመገንዘብ ከመሰል ድርጅቶች ጋር ውህደት በመፍጠር፤ ከሌሎቹ ጋር በጥምረት ትግሉን ለማፋጠን ቆርጦ ተነስቷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የወቅቱን ልዩ ባህሪ በመገንዘብ በአንድ ልብ ለትግል እንዲነሳ ግንቦት 7 ጥሪ ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

ከምርጫ ’97 ‹የተማረው› ኢህአዴግና የሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ

October 23,2014
በላይ ማናዬ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ከሰሞኑ ለመነሻ ያህል የቀረበ ነው በሚል ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ለፓርቲዎቹ ለማስተዋወቅ ሞክሮ ነበር፡፡ ይህን የጊዜ ሰሌዳና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ከፓርቲዎቹ ጋር ለመምከር በሶስት ዋና ዋና ከተሞች (አዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ) ፓርቲዎቹን ከፋፍሎ ለውይይት ጠርቶ የነበረ ቢሆንም ጥቂት የማይባሉ ፓርቲዎች መድረኩን ጥለው መውጣታቸው የሚታወስ ነው፡፡ 

ፓርቲዎቹ የምርጫ ጊዜውን በተመለከተ ከመነጋገራችን በፊት በርካታ ልንነጋገርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገቡና በደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ የገለጽናቸው ጉዳዮች ስላለሉ ለእነዚያ ጉዳዮች ቅድሚያ መሰጠት ይገባዋል ከሚል መነሻ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ቦርዱ የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ እንዳለ የቀጠለ ቢሆንም፡፡

ያም ሆነ ይህ ምርጫ ቦርድ ለውይይት ያቀረበው ረቂቅ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳን ስንመለከት አንድ ነገር እንድንገነዘብ ያደረገ ሆኗል፡፡ ይኸውም ቦርዱ ቅድመ ምርጫ ዝግጅቶችን በተመለከተ ለሚሰሩ ስራዎች በቂ ጊዜ ያለመመደቡን ነው፡፡ ለፓርቲዎቹ የክርክርና የቅስቀሳ ጊዜ የተመደበውን ስናይ ፕሮግራሙ በእጅጉ ወደፊት የተገፋ መሆኑንና በቂ ጊዜ ያለመስጠቱን መመልከት ይቻላል፡፡ ይህም በተለይ ለገዥው ፓርቲ በብዙ መልኩ ጠቃሚ ሆኖ ይስተዋላል፡፡ ገዥው ፓርቲ፣ አንድም ልክ እንደ 97 ምርጫ ከተቃዋሚዎቹ ጋር በግልጽ የክርክር መድረክ ሀሳቦቹን ማቅረብ አለመሻቱን (የደረሰበትን ሁሉ ስለማይዘነጋ)፣ ሁለትም ህዝብ በቂ የቅስቀሳ ጊዜ ተመድቦ አማራጮችን በሚገባ ለማየት እድል እንዳይኖረው መፈለጉን በገደምዳሜ በቦርዱ ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ በኩል ያንጸባረቀ ይመስላል፡፡

በእርግጥ መንግስት/ገዥው ፓርቲ ከምርጫው በፊት ‹የቤት ስራዎችን› በሚገባ ሰርቷል ለማለት ያስደፍራል፡፡ ነጻውን ፕሬስ አፍኗል፣ የህዝብ ልሳኖችን ዘግቷል፣ ጋዜጠኞችን፣ ጦማሪዎችን፣ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞችን አስሯል፤ እንዲሰደዱም አድርጓል፡፡ ስለሆነም በምርጫው መድረክ ኢህአዴግን ሊያጋልጡት የሚችሉ አካላት ላይ ሁሉ የማሳደድ ስራውን ሰርቷል፡፡ በመሆኑም ገዥው ፓርቲ የዘንድሮውን ምርጫ ደካማ የህዝብ ተቀባይነቱን በመገምገም በህዝብ እንደማይመረጥ በመገንዘቡ አፈናውን ቀድሞ ጀምሮታል፡፡ በዚህም ልክ እንደ ምርጫ 97 አንጻራዊ ነጻነትን በመስጠት በህዝብ መድረክ ሽንፈትን ከመከናነብ ይልቅ ጭል ጭል የምትለውን ነጻነት ማፈንን ምርጫው አድርጎ ይታያል፣ ከ97 ምርጫ ‹የተማረው› ትምህርት መሆኑ ነው፡፡

ወደ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳው ስንመለስ ፕሮግራሙ ረቂቅ የመነሻ ሰሌዳ ነው ቢባልም እምብዛም ለውጥ እንደማይደረግበት መገመት ይቻላል፡፡ ለማነኛውም በፕሮግራሙ መሰረት ‹ከህዳር 15-30/2007 ዓ.ም በምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ተገኝተው የመወዳደሪያ ምልክታቸውን ይመርጣሉ› ሲል ያስቀምጣል፡፡ በዚህ ጊዜ ሰሌዳ መሰረትም ፓርቲዎቹ እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ የመወዳደሪያ ምልክታቸውን አያውቁም/ይፋ አያደርጉም ማለት ነው፤ ምንም አይነት የምርጫ ክርክርም ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም፡፡ በምርጫ 97 ወቅት በዚህ ወር (ህዳር) በፓርቲዎች መካከል የምርጫ ክርክር ተጀምሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ዘንድሮ በሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ ታህሳስ 1/2007 ዓ.ም የምርጫ ክልል ጽ/ቤቶች ተከፍተው በይፋ ስራ የሚጀምሩበት እንደሚሆን የጊዜ ሰሌዳው ላይ ሰፍሯል፡፡ ታህሳስ 12/2007 ዓ.ም ደግሞ መራጩ ህዝብ ‹በይፋ በሚደረግለት ጥሪ መሰረት በሚካሄደው የአንድ ቀን ስብሰባ የምርጫ ጣቢያ የህዝብ ታዛቢዎችን የሚመርጥበት› እንደሆነ ያስረዳል፡፡ በቀናት ልዩነት ውስጥ ደግሞ፣ ከታህሳስ 16/2007 እስከ ጥር 25 ቀን 2007 ዓ.ም የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ምዝገባ በየምርጫ ክልሉ ጽ/ቤት የሚካሄድበት ይሆናል ይላል፡፡ በመሆኑም ምርጫው አራት ወራት ያልሞላ ጊዜ እስኪቀረው ድረስ እጩዎቹ ምዝገባ አያከናውኑም ማለት ነው፡፡ ይህም የእጩዎቹን የምረጡኝ ቅስቀሳ ጊዜ ያሳጠረ ይሆናል፡፡

በሌላ በኩል ታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው፣ ከጥር 1 ቀን እስከ የካቲት 10 ቀን ድረስ የመራጮች ምዝገባ በየምርጫ ጣቢያው እንደሚካሄድ የጊዜ ሰሌዳው ላይ ሰፍሯል፡፡ በነገራችን ላይ እጩዎች የእጩነት ማረጋገጫ መታወቂያ ካርድ የሚሰጣቸው ከየካቲት 2-7/2007 ዓ.ም ባሉት ቀናት መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ይህም ለምርጫው ሶስት ወራት ብቻ ሲቀረው መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ስለሆነም እስከ የካቲት 7 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ ምንም አይነት ይፋዊ የምርጫ ውድድር እንቅስቃሴ አይኖርም እንደማለት ነው፡፡ ምክንያቱም በጊዜ ሰሌዳው መሰረት የካቲት 7 ቀን 2007 ዓ.ም የዕጩዎች የምርጫ ውድድር እንቅስቃሴ በይፋ የሚጀመርበት መሆንን አስቀምጧል እና ነው፡፡

በዚህ መልኩ ለሶስት ወራት ያህል ክፍት ሆኖ የሚቆየው የምረጡኝ ቅስቀሳ እንቅስቃሴ ግንቦት 13 ቀን ከምሽቱ 12፡00 በይፋ የሚጠናቀቅ ይሆናል፣ በፕሮግራሙ መሰረት፡፡ ግንቦት 16 ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ምሽቱ 12፡00 ደግሞ የሚጠበቀው ምርጫ የድምጽ መስጫ ዕለት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

የምርጫ ውጤት ይፋ ስለማድረግ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ደግሞ ጊዜያዊ ውጤት ግንቦት 21 የሚገለጽ ሲሆን፣ አጠቃላይ ውጤቱ ደግሞ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ እንደሚደረግ የምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል፡፡ በዚህ መሰረት ይፋዊ የምርጫ ውጤትን ለማወቅ አንድ ወር ሙሉ መጠበቅ ግድ ሊል ነው ማለት ነው፡፡

በዚህ ጊዜ ውስጥ በርካታ ጉዳዮች የታሰቡ ይመስላል፡፡ በተለይም ኢህአዴግ ለተቃውሞ አደባባይ እንዳይወጡ የሚፈራቸው ተማሪዎች ትምህርት ቤቶች ስለሚዘጉ ይበተናሉ፡፡ ሰኔ ላይ ገበሬው ስራ የሚበዛበት ወቅት ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ክረምት በመሆኑ የምርጫ ታዛቢዎች በገጠር አካባቢ እንዳሻቸው ተዘዋውረው ስራቸውን ለማከናወን ዝናብና ጭቃ ይፈትናቸዋል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ማንን ሊጠቅመው እንደሚችል ሳይታለም የተፈታ ነው፤ እሱም በምርጫ 97 ‹ትምህርት የቀሰመው› ኢህአዴግ ይሆናል፡፡

መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

October 23.2014
Temesgen‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ሰው ሆኖ ለእስር ይወጣል››
‹‹ተመስገን፣ የህዝብ ልጅ ነው፤ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ‹‹ስለተመስገን ደሳለኝ ሃሳቤን አስተላልፍልኝ›› ካለኝ የተወሰደ
ከትናንት በስትያ፣ ሰኞ ዕለት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆነውን አቶ አንዷለም አራጌን በ2007 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ላገኛቸው ችዬ ነበር – ለአቤል አለማየሁ ጋር፡፡ ባለፈው ሳምንት የ‹‹ባንዲራ ቀን›› በተከበረበት ዕለት ቃሊቲ ከወዳጄ እዩኤል ፍስሐ ጋር ሄጅ እነስክንድርን መጠየቅ ሳንችል ተመልሰን ነበር፡፡
የሆኖ ሆኖ፣ ከእስክንድር ጋር ለ15 ደቂቃ ያህል ለማውጋት ችለን ነበር፡፡ እስኬው፣ ሁሌም መንፈሱ ጠንካራ ነው፡፡ ሰኞም ያ አስደማሚ ጥንካሬው፣ ትህትናው፣ እውነተኛ ቅንነቱ፣ ብርታቱ፣ ቀናኢነቱ…አብረውት ነበሩ፡፡
ሰዓት ደርሶ ከእስክንድር ጋር ቻው ከተባባልን በኋላ ‹‹ኤልያስ፣ አንዴ ላናግርህ›› ብሎ ከጠራኝ በኋላ ‹‹እባክህ አንድ መልዕክት ስለተመስገን ደሳለኝ አስተላፍልኝ›› አለኝ፡፡ እስንክድር፣ ሁሌ ሀሳቤን አስተላልፍልኝ ሲለኝ ግልጽነቱ እጅግ ይማርካል፡፡
‹‹እሺ›› አልኩት››
‹‹ተመስገን፣ ጥሩ ታጋይ እና ጥሩ ሰው ሆኖ ከእስር ይወጣል፡፡ ተመስገን የህዝብ ልጅ ነው፡፡ ነገም ከነገወዲያም የህዝብ ልጆች ይፈጠራሉ፡፡ እስሩ ስለሀገሩ ያበረታዋል፤ ያጠነክረዋል፡፡ ብዙ ነገር እንዲረዳ ያደርገዋል፡፡ ሰዎች ይታሰሩ እያልኩ አይደለም፡፡ ይሄ አንዱ የሰላማዊ ትግል መስራት ውጤት ነው፡፡ በለውጥ እና በትግል መስመር ላይ ያሉ ኢትዮጵኖች መታሰራቸው ነገ ለውጥ ያመጣል፡፡››
ካለኝ በኋላ ለሁሉም ‹‹እወዳችኋለሁ፣ አከብራኋለሁ፣ በተሰማራችሁበት የህይወት መስመር፣ በሰላማዊ መንገድ በርትታችሁ ለለውጥ ታገሉ!›› በልልኝ ብሎኛል፡፡
እኔም ዛሬ ‹‹የሀገሪቱን ህዝቦች አንድነት እንዲፈርስ እና በሀገሪቱ ሕዝቦች መካከል ጸብና ቁርሾ እንዲፈጠር በማሰብ …›› የሚል ከባድ ክስ ብቀበልም የእስክንድርን መልዕክት ለማስተላለፍ አልተቆጠብኩም፡፡
ፍቅር ያሸንፋል!
Elias Gebru Godana

አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው ፓርቲ ነው!

October 23,2014

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

UDJአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ በአሁኑ ሰዓት ከመቼም ጊዜ በላይ በጠንካራ አቋም ላይ ይገኛል። በፓርቲው ውስጥ ጎልቶ እየታየ የመጣው የለውጥና የማንሰራራት ፍላጎት ተገንዝበው የፓርቲው ፕሬዚደንት የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው በራሳቸው ፍቃድ መልቀቃቸው የፓርቲው የዴሞክራሲ ባህል የላቀ ደረጃ ላይ መድረሱን በትክክል የታየበት፤ ፓርቲው በተሻለ ቁመና ላይ እንዲጓዝ በር የከፈተ ትልቅ እርምጃ በመሆኑ ሊደነቅ የሚገባ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ብሄራዊ ምክር ቤቱ ጥቅምት 2/2007 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የኢንጂነር ግዛቸውን የመልቀቂያ ጥያቄ አዳምጦ ካፀደቀ በኋላ የፓርቲው መተዳዳሪያ ደንብ በሚፈቅደው መሰረት አስመራጭ ኮሚቴ አቋቁሞ ፓርቲውን በቀጣይነት የሚመራ ሰው በዕለቱ ከቀረቡት ሶስት እጩዎች መካከል አቶ በላይ ፍቃዱን በከፍተኛ ድምፅ የፓርቲው ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጠዋል።
አንዳንድ ወገኖች በዚህ ፍፁም ደንባዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ ሂደት ያለፈና የፀደቀ ጉዳይ የደንብ ጥሰት የተፈፀመ በማስመሰል ጫጫታ ለመፍጠር የተንቀሳቀሱበት ሁኔታ ቢኖርም፤ በዚህ ዴሞክራሲያዊ የሆነ የስልጣን ሽግግር ላይ ምንም ዓይነት የደንብ ጥሰት ያልተፈፀመ መሆኑ አፅንኦት ሰጥተን ለመግለፅ እንፈልጋለን። አንድነት ውስጣዊ የዴሞክራሲ ባህል ያለው፤ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት የሚችልና በዚህ ለሌሎችም ትምህርት የሚሆን ልምድ ያለው ፓርቲ ነው።
በአሁኑ ሰዓት አዲሱ ፕሬዚዳንት በአዲስ መንፈስ ካቢኔያቸውን አቋቁመው በፍጥነት ወደ ስራ የገቡበት ሁኔታ ነው ያለው። ፓርቲው የተሻለ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ ውስጡን የማጥራትና የማስተካከል ስራ እየተሰራ ከመሆኑም ባሻገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን ቤት እንዲሆንና ብቃት ያላቸው አመራሮች ወደፊት እንዲመጡ በማድረግ አንድነት በሰላማዊ ትግሉ ታግሎ በማታገል የስርዓት ለውጥ ማምጣት የሚችል ህዝባዊ መሰረት ያለው ፓርቲ እንዲሆንና ጠንካራ ቁመና እንዲኖረው ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። ህዝቡ ይህን ተገንዝቦ እንደ ከዚህ ቀደሙ ከጎናችን እንዲቆም፤ ለነፃነትና ለዴሞክራሲ በምናደርገው ትግልም ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ኢትዮጵያ በነፃነቷና በአንድነቷ ለዘላለም ትኑር!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ
ጥቅምት 12/2007 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

Ethiopian Federal police says it has charged suspected rebels, opposition under 36 files

October 22, 2014
The Ethiopian Federal Police Commission has said that it has charged suspected members of the Oromo Liberation Front (OLF), Ginbot 7 Movement for Freedom, Justice and Democracy, Ogaden National Liberation Front (ONLF), Gambela People’s Liberation Movement (GPLM), Benishangul People’s Liberation Movement (BPLM) and Al Shabaab under 36 files in the past Ethiopian year 2006.
The Force said to loca media that out of the 36 terrorism files, investigation had been completed on 27 of them and the files were sent the relevant department. Out of which four were members of the OLF, six Ginbot 7, one ONLF, three GPLM, two BPLM and two Al Shabaab members.
These suspects were trained and sent over here by the Eritrean government, it said. Police said 119 suspects were found guilty and were sentenced from one to twenty-five years imprisonment.
Meanwhile, the Commission preferred to keep quiet regarding the huge casualties that the Force sustained in the Sheko Mezenger area of Southern Ethiopia.
Although the Commission said its capacity of fighting terrorism has increased, it has been internationally criticised for linking and detaining bloggers, journalists and politicians with the named rebel groups using the internationally condemned Ethiopian Anti Terrorism Proclamation.

Wednesday, October 22, 2014

የህዝብ ግንኙነት ካድሬዎች በማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ሊዘምቱ ነው

October 22,2014
ኢሳት ዜና :-በአቶ ሬድዋን ሁሴን የሚመራው የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አሰልጥኖ በፌዴራል የመንግስት ተቋማት በህዝብ ግንኙነት ኃላፊነት ለመደባቸው ካድሬዎች የሁለት ቀናት የማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀም ስልጠና በመስጠት በተለይ በግንቦት ወር ከሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ እንዲሳካ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ አደራ ተጥሎባቸዋል፡፡

የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን እንደገለጸው የኮምኒኬሽን ጽ/ቤቱ በሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 158/2001 ሲቋቋም በመንግስትና በሕዝቡ መካከል ቀልጣፋ ውጤታማ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማስቻል አንዱና ዋና ዓላማው ያደረገ ቢሆንም በተግባር ግን የሰለጠኑና ልምድ ያካበቱ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችን የአመለካከት ችግር አለባቸው በሚል በማባረርና በማንሳፈፍ ካድሬዎችን በለብለብ ስልጠና ሲመድብ ቆይቷል፡፡ ዘርፉ ልምድና በቂ ስልጠና በሌላቸው ካድሬዎች በመያዙ በመረጃ አሰጣጥ በኩል ያለው ችግር እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል፡፡

ጽ/ቤቱ የመደባቸው ካድሬዎች በተለይ በማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀም ደካማ በመሆናቸው ምክንያት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን በሰበሰቡዋቸው ቁጥር ከፍተኛ ብስጭት የኢህአዴግን አቁዋም እንኩዋን መናገር የማይችሉ በማለት እስከመዝለፍ ደርሰዋል፡፡


የዜና ምንጮቻችን እንደጠቆሙት በአዲስአበባ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው ዋሽንግተን ሆቴል ባካሄደው ስልጠና ካድሬዎቹ እንደፌስ ቡክና ቲዎተር ባሉ ማህበራዊ ድረገጾች ላይ እንዴት መጠቀም እንደሚችሉና የመ/ቤታቸውንና የመንግስትን አቋም ከማስረዳት ባለፈም ጸረ መንግስት አቋም ያላቸውን መረጃዎች በማጣጣልና በማስተባበል ረገድ የበኩላቸውን የተከላካይነት ሚና እንዴት እንደሚወጡ በመሰልጠን ላይ ናቸው። በተለይ የማህበራዊ ድረገጾች መንግስትን በሚቃወሙ ሃይሎች ሙሉ በሙሉ ቁጥጥር ስር እንደወደቀ የአቶ ሬድዋን ቢሮ የሚያምን ሲሆን ይህን ለመመከት የሚያስችል ብቃት ያለው የኮምኒኬሽን ባለሙያ ባለመኖሩም ካድሬዎቹ በተደጋጋሚ ወቀሳ ሲሰነዝርባቸው መቆየቱን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ለዘጋቢያችን ተናግረዋል፡፡


በአሁኑ ወቅት የአንዳንድ የፌዴራል መ/ቤት ተቋማት የህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ካድሬዎች በተለይ በፌስቡክ ፈራተባ እያሉ መረጃዎችን መልቀቅና በሚጻፉ የተለያዩ ጉዳዮች አስተያየት መሰንዘር በመለማመድ ላይ ናቸው፡፡

ሰበር ዜና፣ ህውሃት “የመለስ ትሩፋቶች” መጽሃፍን ለስለላ እየተጠቀመበት መሆኑ ታወቀ

October22,2014
ሰበር ዜና፣ ህውሃት “የመለስ ትሩፋቶች” መጽሃፍን ለስለላ እየተጠቀመበት መሆኑ ታወቀ
በቀድሞው የመንግስት ኮሚውንከሽን ጉዳዮች ሚንስትር ድኤታ አቶ ኤርምያስ ለገሰ የተጻፈውን እና በብዙ በአለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተነባቢ የሆነው “የመለስ ትሩፋቶች” የተስኘው መጽሃፍ የኢህአዴግን መንግስት በተለይም ደግሞ የህውሃትን የጥፋት ዘመቻ በሰፊው  ያጋለጠ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም መጽሃፉ ወደ PDF File  ተቀይሮ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ በኢሜይል ሲሰራጭ ቆይቷል። መጽሃፉ በተለይ በዲሞክራሲ አክቲቪስቶች ዘንድ ተፈለኣጊነት እንደሚኖረው በማወቅ
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የደህንነት ምንጮቻችን በዛሬው እለት እንዳስረዱን የህውሃት ኢህአዴግ የስለላ ማእከል ይህንን ፋይል ፊን ፊሸር ከተባለ የስለላ ቫይረስ ጋር በማጣመር በአሁኑ ሰአት በከፍተኛ ፍጥነት በኢሜይል በማሰራጨት ላይ ይገኛል።
ይህ ቫይረስ ከ“የመለስ ትሩፋቶች” ፍይል ጋር ተጣብቆ ወደ ኮምፒውተር ዳውንሎድ ከተደረገ፣ ኮምፒውተሮት ላይ ያለውን የግል ፍይሎች ወድ ህውሃት የስለላ ማእከል ከመላክ እልፎ  የሚከተሉትን ማድረግ ይችላል፥
1)  የህውሃት ይስለላ ኤጀንቶች በኮምፒውተሮት ላይ ሙሉ ለሙሉ ቁጥጥር እንዲኖራቸው ያደርጋል
2)  ይህ ማለት በፈለጉት ሰዕት የኮምፒውተሮትን ካሜራ እና ማይክሮፎን በመጠቀም የግል እንቅስቃሴዎን መከታተል እንዲችሉ ያደርጋል
3) በኮምፒውተሮት ላይ በኢንተርኔት  የሚስገቧቸውን እንደ ክሬዲት ካርድ እና ሶሻል ሴኵሪቲ ያሉ ሚስጥራዊ ቁጥሮችን  በቀላሉ ማግኘት ያስችላቸዋል
4) በኢንተርኔት ላይ የሚጎበኟቸውን ድረ ገጾች እንዲሁም  በግልዎ የሚሳተፉባቸውን የማህበርዊ ሚድያ አካውንቶች እስከ ዩዘር ስም እና ፓስዎርዳቸው በቀላሉ ማግኘት ያስችላቸዋል
5)  ከቤተሰብዎ እና ከጏደኞችዎ ጋር የሚያደርጉትን የኢሜይል እና የስካይፒ ግንኙነት በቀላሉ ማንበብ እና ማዳመጥ እንዲሁም አካውንቶቹን ሌላ ጥቅም ላይ ማዋል ያስችላቸዋል
6)  በድርጅት ውስጥም ሆነ በግልዎ ለስብአዊ መብትዎ ወይም ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ የሚሟገቱ ከሆነ፣ እርስዎን በሃሰት ወንጅሎ ለእስር አና ለስቃይ ለመዳረገ መንገድ ይከፍትላቸዋል
ስለዚህ ይህ “የመለስ ትሩፋቶች” የሚል የPDF ፍይል በኢሜይል ከተላከልዎ የኢሜይል መልእክቱን ሳይከፍቱ ዲሊት በማድረግ እራስዎን ከጥቃት ያድኑ።
አባይ ሚዲያ 

የፓርቲዎች ትብብር ስምምነቱን ላልፈረሙት ጥሪ አቀረበ

October 22,2014
• ኢትዮጵያውያንም የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል
ዘጠኝ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትናንት ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም በጋራ ለመስራት የትብብር ስምምነት መፈረማቸውን በማስመልከት ዛሬ ጥቅምት 12/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ትብብሩን የፈረሙት ፓርቲዎች ትብብሩን ያልፈረሙት ሌሎች ፓርቲዎች ስምምነቱን እንዲፈርሙ በይፋ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው፣ ‹‹በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋችሁ በተለያየ ምክንያት በትናንትናው ቀን የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረማችሁም ሆነ የአገርና ህዝብን ጉዳይ ከፓርቲ ጥቅምና ዓላማ አብልጣችሁ የምትመለከቱና ለዚህም በጋራ ለመስራት ዝግጅቱና ቁርጠኝነቱ ያላችሁ ሌሎች ሰላማዊ የተቃውሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን›› በማለት ፈራሚዎቹ ፓርቲዎች ይፋዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተገኙት የትብብሩ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነትና ዋና ጸሐፊው አቶ ግርማ በቀለ እንደገለጹት ትብብሩ ያለፉትን ድክመቶች የፈተሸና ወደፊት እንዴት እንጓዝ የሚለውን አቅጣጫ ያስቀመጠ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ፓርቲዎቹ ለትብብሩ መነሻ የሆናቸውን ምክንያት ሲያብራሩም፣ ‹‹በገዢው ፓርቲ/መንግስት የሚፈጸሙ ኢ-ህገ-መንግስታዊ እና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ተግባራት በአገራችን የመድብለ ስርዓትን እውን ለማድረግ ከማያስችሉበት ደረጃ በመድረሱ የተፈጠረውን ምስቅልቀስል ለመሸከምም ሆነ ተመጣጣኝ መፍትሄ መስጠት በማስፈለጉ መሆኑ ነው›› ብለዋል፡፡

በመሆኑም ዘጠኙ ትብብሩን የፈረሙ ፓርቲዎች የትብብር ስምምነት ያስፈለገበት ምክንያት፣ ‹‹ነጻ፣ አሳታፊና ታአማኒ ምርጫ እንዲካሄድ በትብብር ለመስራት፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና የዜጎችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ በጋራ ለመታገል›› መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የትብብሩ ፈራሚ ፓርቲዎች ሰማያዊ ፓርቲ፣ መኢዴፓ፣ መዐህድ፣ መኢአድ፣ ሶጎህዲድ፣ ኢብአፓ፣ ኦህዲህ፣ ከህኮ እና ጌህዴድ መሆናቸው ታውቅል፡፡

በተመሳሳይ ‹‹ከዓላማችን ለሚያደርሱን ተግባራት ተፈጻሚነት በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ተሳትፎ አስተዋጽኦ ያለው ድርሻ ከፍተኛ ስለሆነ ከጎናችን በመቆምና በንቃት በመሳተፍ የዜግነት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ›› ሲሉ ለህዝቡ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
 (9 photos)

Tuesday, October 21, 2014

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩም እንደገና ተከሰሰ

October 21,2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) በኢትዮጵያ ውስጥ በነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች ላይ እየደረሰ ያለው ወከባ እስር አሁንም እንደቀጠለ ነው። በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከሃያ በላይ ጋዜጠኞች አገር ለቀው ተሰደዋል። ሌሎች ጋዜጠኞች “አሸባሪ” የሚል ቅጽል ተሰጥቷቸው በእስር ቤት ይማቅቃሉ። በጣት የሚቆጠሩት ብቻ አገር ቤት ሆነው የሚመጣውን ለመቀበል የተዘጋጁ ይመስላል። በቅርቡም ተመስገን ደሳለኝ ወደ እስር ቤት እንዲወርድ መደረጉ የሚታወስ ነው።
አሁን ደግሞ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጎዳና ማዕከላዊ ሄዶ ክሱን እንዲወስድ በስልክ ተነግሮታል። ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በራሱ ብዕር ስለሁኔታው ሲገልጽ እንዲህ ብሏል። “እንግዲህ፣ ‹‹ማዕከላዊ ናና ክስህን ውሰድ›› ተብያለሁ” ብሎ ይጀምራል፤ ዛሬ በላከው ማስታወሻ ላይ።
ኤልያስ ገብሩ
ኤልያስ ገብሩ
*********************************
ከቀኑ አስር ሰዓት ላይ ሞባይል ስልኬ አቃጨለች፡፡ ከጎኔ ወዳጄ አቤል አለማየሁ ነበር፡፡ የመስመር ስልክ ነው፡፡ አነሳሁት፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ›› የሚል የሴት ድምጽ አደመጥኩ፡፡ ‹‹አዎን›› በማለት መለስኩላት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ መስመር ላይ ጠብቅ›› አለችኝ፡፡
ወዲያው አንድ ወንድ አነሳና ሰላምታ ሰጥቶ አናገረኝ፡፡ የሚደውለው ከፌዴራል ፖሊስ መሆኑን ጠቆመኝና ‹‹ባለፈው ተቋርጦ የነበረው ክስህ ስለተዘጋጀ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ቁጥር 76 መጥተህ ውሰድ›› አለኝ፡፡ ስለጉዳዩ ጥቂት ቃላቶች ተለዋወጥን፡፡ 
‹‹እሺ ሰሞኑን መጥቼ እወስዳለሁ›› አልኩት፡፡ ‹‹ዛሬም የምትችል ከሆነ መምጣት ትችላለህ›› አለኝ፡፡ ጎሳዬ ሲልም ስሙን ነገረኝ፡፡
…በውድ ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ መታሰር ሳይኖርብህ ትታሰራለህ፡፡ ዋስትና መከልከል ሳይኖርብህ ትከለከላለህ፡፡ ዳኛ የሰጠው የተጨማሪ የምርመራ ቀን ሳይደርስ ‹‹ስንፈልግህ ትመጣለህ፤ ዋስ አምጥተህ ውጣ›› ትባልና ከእስር ትለቀቃለህ፡፡ ከአምስት ወራት በኋላ ደግሞ ትጠራና ‹‹ከስህ ተዘጋጅቷል ና›› ትባላለህ፡፡ …ነገ የሚሆነውን ነገር ደግሞ አታውቅም፡፡ …እንግዲህ እንዲህ ነች የዛሬዋ ኢትዮጵያ!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
==============
ከላይ ያቀረብነው የኤልያስ ገብሩን ጽሁፍ ሲሆን፤ አሁን በስደት የሚገኘው የስራ ባልደረባው ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ደግሞ እንዲህ ብሏል።
=============
ፍትህ በየት አለሽ?
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ማዕከላዊ መጠራቱንና የጥሪው መንስኤም ከዚህ ቀደም ለእስራት የተዳረገበት ዕንቁ መጽሔት ላይ በሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አማካኝነት የወጣ ጽሁፍ እንደሆነ ነግሮናል፡፡
የኤልያስን ክስ፣የፍርድ ቤት ውሎና የማዕከላዊ ቆይታውን በቅርበት ይከታተል እንደነበረ ሰው የአሁኑ ጥሪ ግርም ቢለኝ የተወሰኑ ነጥቦችን ለማንሳት ወደድኩ፡፡
የመገናኛ ብዙሃንና የመረጃ ነጻነት አዋጅ አንቀጽ 43/ቁጥር 1 ‹‹በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ፣ጠቅላይ አቃቤ ህጉ ካልወሰነ በስተቀር በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 59/2/እና 3 ድንጋጌዎች መሰረት ፣ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ ለፍርድ ቤት መቅረብ አለበት፡፡..በማለት በማያሻማ መልኩ ቢደነግግም ጽሁፉ በወጣበት ወቅት የዕንቁ ዋና አዘጋጅ የነበረው ኤልያስ በማዕላዊ መርማሪዎች ትዕዛዝ ቀበቶውን ፈትቶ ታሳሪዎችን እንዲቀላቀል ተደረገ፡፡
ኤልያስ ከእስሩ ሁለት ቀናት በኋላ አራዳ ምድብ ችሎት እንዲቀርብ ተደረገ ፣ከሳሽ የማዕከላዊ መርማሪ ተጠርጣሪው የተያዘው በመጽሔቱ ላይ በወጣ ጽሁፍ የተነሳ በጅማ ዩኒቨርስቲ ብጥብጥ ተነስቶ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ተናገረች፡፡
ኤልያስ በበኩሉ አዋጁን ጠቅሶ ለእስር መዳረግ እንደሌለበትና ጉዳዩን በውጪ ሆኖ መከታተል እንደሚችል ገለጸ፡፡
ዳኛው ለደቂቃዎች ካቀረቀሩበት ቀና ብለው‹‹እውነት ነው አዋጁ ጋዜጠኛው መታሰር እንደሌለበት ይናገራል፣ነገር ግን ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ አለብኝ ስላላ የ7 ቀን ጊዜ ሰጥቻለሁ በማለት አረፈው፡፡
ኤልያስ ወደ ማዕከላዊ ተመለሰ፡፡በነጋታው ግን የማዕከላዊ ሰዎች 30.000ብር ዋስ እንዲያቀርብ አድርገውት ለቀቁት፡፡
በቀጠሮው ቀን ኤልያስ ፍርድ ቤት የመሄድ ፍላጎት ነበረው፤ ግን አጠገቡ የነበርን ሰዎች ‹‹እነርሱ ሲፈልጉ ክሱን ሊቀሰቅሱት ይችላሉ እስከዛው ዝም ብለህ ጠብቅ” አልነው፡፡
እውነትም እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ኤልያስን የፈለገውም አልነበረም፡፡አሁን መዝገቡን ከቆለፉበት ክፍል አውጥተውት ‹‹ና››ብለውታል፡፡
አወይ ፍትህ?አቤት ፍርድ ቤት?ከወራት በፊት በዚሁ ጉዳይ ኤልያስን ያናገሩት ዳኛ አሁን ሲመለከቱት ምን ይሉ ይሆን?ምን ችግር አለው ‹‹ባለፈው ቀን ምን ላይ ነበር ያቆምነው››ብለውም ይጀምሩ ሆነዋል፡፡
——-መልካሙን ሁሉ ወዳጄ ሆይ እመኝልሃለሁ፡፡——–

‘Ethiopia Should Free Journalists From Jail and Exile’

October 21, 2014
Million Shurube was the founder and managing editor of the defunct weekly Maraki Magazine
Million Shurube
The Federation of African Journalists (FAJ), the Africa regional group of the International Federation of Journalists (IFJ), has today called on the Ethiopia Government to free all journalists jailed and to allow the exiled journalists to come back and work for the mother country, Ethiopia.
The FAJ made this call while mourning the untimely death of exiled Ethiopian journalist, Million Shurube, who passed away at the Kenyatta National Hospital in Nairobi (Kenya), on Monday, 13 October, 2014 after a brief illness.
“We offer our heartfelt sympathies to the family of Shurube and the entire journalists’ fraternity in Ethiopia”, said the President of the Federation of African Journalists (FAJ), Mohamed Garba. “Such situations are difficult for every family, most especially when one reflects on the fact that Shurube was forced into exile because of his job and his right to freedom of expression”.
Journalists have been on the receiving end of various forms of repression, across the globe this year, resulting in deaths, tribulations and immense suffering. “The Ethiopia Government must review its engagement with journalists and see them as crucial partners in development rather than opponents that need to be silenced” Garba added.
According to reports, Million Shurube was the founder and managing editor of the defunct weekly Maraki Magazine, and was one of a dozen of Ethiopian journalists forced into exile recently, having been harassed, threatened, accused, and charged with terrorism offenses. He fled to Kenya last September to escape from imprisonment, and had been in Nairobi for only a month.
He fell ill last week and was rushed to Mama Lucy Hospital in Nairobi and then transferred to Kenyatta National Hospital, where he died on Monday October 13.
Million Shurube had also worked for different publications including the now-defunct Abay, Ethiop, and Google newspapers, was known for his exciting writings on issues including art, religion, tradition, and was also outspoken and inspiring with articles on the political and human rights in Ethiopia.
The President of the Federation of African Journalists (FAJ), Mohammed Garba, also extended his sincere condolences to the family and his gratitude to journalists and media fraternity in Kenya and Ethiopia, and to the Eastern Africa Journalists Association (EAJA) who have put their acts together to support the family to return the body home in Ethiopia for burial.
The FAJ President called on Ethiopia government to be more tolerant to journalists and the media and to bring their media laws into conformity with internationally recognized standards.
According to the FAJ President, “the repressions, intimidations, harassments and sufferings that most journalists face today are simply because of the unfriendly laws that govern the media in the country”.
EAJA, the Federation of African Journalists (FAJ) and the International Federation of Journalists (IFJ) officers met and held discussions with the Ethiopian Government Communication Affairs Office Minister, Redwan Hussien, in September and raised the situation of Ethiopian journalists in jail and in exile.
The meeting with the Ethiopian Minister came following concerns over the high number of Ethiopian journalists who have been fleeing into exile and the cases of those either in jail or facing court cases following government crackdown on the media and journalists.

Monday, October 20, 2014

የአዲሱ ወጣት የአንድነት መሪ፣ በላይ ፍቃዱ ቃለ ምልልስ

October 20,2014
Belay Fekadu
አቶ በላይ ፍቃዱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት
“ማር እንኳን 23 አመትት ቢላስ ይመራል ። 23 አመት እንደ ኢሕአዴግ ላለ ፓርቲ እጅግ በጣም ረጅም አመት ነው”
“ሕዝቡ ለዉጥ ይፈልጋል። በዚህ ላይ ምንም አነት ጥርጣሬ የለም፡፡በመላው ኢትዮጵያ ሲኬድ ይሄን አይነትት ስሜት አለ”
“ትልቁ ነገር አማራጭ ሆኖ ሕብረተ ሰቡ ተስፋ ሊይደርገው የሚችል ፓርቲ ሆኖ መዉጣት የውወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ይመስልኛል”
“አንድነት የሁሉም ኢትዮጵያዊያኖች ቤትና ፓርቲ እንዲሆን ለመስራት ከፍተኛ ትጋት እናደርጋለን። በፕሮግራም በደንብ ደረጃያአንድነት ከሁሉም ፓርቲ በሚለይ መንግድ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያኖች በሚያቅፍ ሁኔታ የተዋቀረ ነው። በአሰራርና ቶበአካሄድ አንዳንድ ክፍተቶች አሉብን ፣ ስለዚህ እነዚህ ክፍተቶችን የመሙላትና፣ በቀን ተቀን ስራዉ ሁሉም ኢትዮጵያዉያኖችን ማቅቀፍ የሚችል መሆኑን ማሳየት አለብን።”
ከላይ የተጠቀሱት ፣ አቶ በላይ ፍቃደ፣ አዲሱ ወጣት የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት፣ ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን ለአንድነት ራዲዮ ከተናገሩት የተወስደ ነው።
አቶ በላይ ለመረጧቸዉና ለደገፏቸው ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ከርሳቸው የተሻለ ሌሎች አሉ ብለው ሌሎችን ለደገፉ ከፍተኛ ክብርርና አድናቆት እንዳላቸው የገለጹት ሲሆን፣ አሁን ግን የመሰባሰብና የስራ ጊዜ እንደሆነም አስረድተዋል።
የተቃዋሚዎች መዳከምና አማራጭ ሆኖ አለመገኘት ለኢሕአዴግ መቆየት ምክንያት እንደሆነ የሚናገሩት አቶ በላይከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብረዉ እንደሚሰሩ፣ ከወዲሁ ንግግሮች እንደትጀመረና ሁኔታው በሂደት እንደሚገለጽ ሳይጠቁሙ አላለፉም።
“ኑና አብረን እንስራ” ሲሉ፣ በአገር ውስጥና ከአገር ዉጭ ላሉ ኢትዮጵያዉያን መልእክታቸውን ያጠናቀቁት አቶ በላይ፣ ትግሉ የጥቁቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች እንደመሆኑ፣ ሁሉም ዜጋ ትግሉን እንንዲሳተፍና እንዲተባበር ተማጽኖ አቅርበዋል።

በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ላይ ጫናው በርትቷል

October 20,2014
• ‹‹ሰላማዊ ትግል የሚባል ነገር አይሰራም፤ ጫካ ገብታችሁ ሞክሩን፡፡››
የብአዴን አመራሮች
በምስራቅ ጎጃም ዞን የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ከገዥው ፓርቲ ባለስልጣናት የሚደርስባቸው ጫና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረታ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ የምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ጸሃፊ የሆነው ጠበቃ ሳሙኤል አወቀ በእሱና በሌሎች የፓርቲው አመራሮችና አባላት ላይ ዛቻ እንደሚፈጸምባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
የምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ ቢሮ በ2006 ዓ.ም የእቅድ ግምገማ እና የ2007 ዓ.ም የስራ አፈጻጸም እቅድ በተወያየበት እና የሁሉም ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የስራ ሂደት ባለቤቶች በተገኙበት፣ ‹‹ሳሙኤል አወቀ የሚባል በጥብቅና ሽፋን የመሬት ፖሊሲውን የሚታገል፣ ለተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና ደጋፊ አርሶ አደሮች ጥብቅና የሚቆም፣ ከአሸባሪ ጋር ግንኙነት ባለው ድርጅት አመራር የሆነን ግለሰብ በህግ ሽፋን እስር ቤት እንዲወርድ ያላደረገ አቃቤ ህግ አቃቤ ህግ አይደለም›› ተብሎ በህግ ስም እርምጃ እንዲወሰድበት ትዕዛዝ መተላለፉን ጠበቃው ገልጾአል፡፡
በተለይ የደብረማርቆስ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት አቃቤ ህጎች ዋነኛ ችግራቸው ጠበቃ ሳሙኤልን በህግ ስም ማስቀጣት አለመቻላቸው እንደሆነ ተገምግመዋል ተብሏል፡፡ ጠበቃው ወዲያውኑ የፈጠራ ክስ እንደተመሰረተበት፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ‹‹ለፍትህ ስርዓቱ አጋዥ ባለመሆኑ›› በሚል መከሰሱንና ባልተከራከረበት ፍርድ ሂደትም 8000 ብር ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት ገልጾአል፡፡
ጠበቃው በ28/1 እናርጅ እናውጋ ለቀጠሮ ባቀናበት ወቅትም የእናርጅ እናውጋ አስተዳደርና ጸጥታ ኃላፊ አቶ ስራው በረኩ እና የብአዴን የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ መኳንንት አበበ እና ሌሎችም ከፖሊስና ከጸጥታ የመጡ አመራሮች ‹‹ምን ልታደርግ ነው? ልትቀሰቅስ ነው?›› በሚል እንዳዋከቡትና አቶ ስራው በረኩ ‹‹አንጠልጥዬ ነው እስር ቤት የማስገባህ፡፡ ማንም ሊያድንህ አይችልም›› ብለው እንደዛቱበት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
‹‹የሰማያዊ ፓርቲ አባል ሆነህ በፍትህ ስርዓቱ መገልገል አትችልም፣ ጥብቅናህን መልቀቅ አለብህ፣ ነገረ ኢትዮጵያ ላይ ትጽፋለህ፣ የፍትህ መምሪያ ሃላፊውን (ጸጋየ መንግስቴ) ችግር እንደሚፈጽምብህ በነገረ ኢትዮጵያና በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ ጽፈህበታል፣ እንዲህ እያደረክ መኖር አትችልም፣ አንተን ገሎ መጣል ቀላል ነው፣ ለነፍስህ የምታዝን ከሆነ አገር ልቅቅ›› ብለው እንደዛቱበት ገልጾአል፡፡
ሌሎች ጠበቃ ጓደኞቹ ከእሱ ጋር እንዳይሄዱ ‹‹እሱ ማለት ሰማያዊ ነው፡፡ ሰማያዊ ደግሞ የአክራሪ ሙስሊም ፓርቲ ነው፡፡ እናንተ ለምን ከእሱ ጋር ትሄዳላችሁ?›› ብለው እንደሚያስፈራሯቸውና ደንበኞቹ ከእሱ ጋር እንዳይሰሩ ማስጠንቀቂያ እንደሚደርሳቸው ጠበቃው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ጠበቃውን ጨምሮ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት የሰማያዊ ፓርቲ አመራርና አባል ሆነው ማደራጀት መብታቸው መሆኑን ሲገልጹ የብአዴን አመራሮች ‹‹እናንተ እኛን ስለማትረዱን ነው፡፡ እኛ ጋር ሰላማዊ ትግል የሚባል አይሰራም፡፡ ወንድ ከሆናችሁ ጫካ ገብታችሁ ሞክሩን›› በሚል ለህግ የማይገዙና ለሰላማዊ ትግል ቁርጠኝነት እንደሌላቸው አሳይተውናል ብለዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲና አመራር የሆኑ ነጋዴዎች ከፓርቲው እንዲለቁ ለማድረግ የንግድ ድርጅታቸውን እንደሚዘጉ እያስፈራሩ እንደሆነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለአብነት ያህልም አቶ ይኸይስ ቀጸላ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር ‹‹ሻይ ቤት ከፍተው እያደራጁ ነው፡፡ የንግድ ድርጅቱን እንደ ጽ/ቤት ይጠቀሙበታል፡፡ በመሆኑም ካላረፉ ሻይ ቤቱን እንዘጋዋለን›› እያሉ እንደሚያስፈራሩ ታውቋል፡፡
የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት የገዥው ፓርቲ ዛቻና ማስፈራሪያ እንዲሁም እርምጃዎች እየተጠናከሩ ቢሆንም እርምጃው እነሱ ተጽዕኖ በመፍጠራቸው የመጣ በመሆኑ ይበልጡን እንደሚያበረታታቸውና የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
አቶ መኳንንት አበበን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችን የእጅ ስልካቸው ላይ በመወደል ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡

Sunday, October 19, 2014

“የዲግሪና የዲፕሎማ ወፍጮ ቤቶች”

October19,2014

ተፈጭና ተመረቅ – አስተምሮ መለስ
degree mill

በእንግሊዝኛው አጠራር የዲፕሎማ/የዲግሪ ወፍጮ ቤት (diploma/degree mills) ይባላሉ፡፡ በርካታዎቹ ሠለጠነ በሚባለው ዓለም ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ “ወፍጮ ቤቶች” የ“ትምህርት መረጃ” ለማግኘት በጣም ቀላል ነው፡፡ ዋናው መስፈርት አስፈላጊውን “የትምህርት ክፍያ” መፈጸም ብቻ ነው ፡፡ ከዚያ በወርቅ ቅብ የተንቆጠቆጠ “የባችለር” ወይም “የማስተርስ” ወይም “የዶክትሬት (ፒ.ኤች.ዲ.)” ዲግሪዎችን ማፈስ ነው፡፡ በቀጣይ የሚሆነው የ…ሚ/ር ወይም የ…ሚኒስትር ደኤታ ወዘተ መሆንና “በሹመት መዳበር” ነው፡፡ ከዚያ ህዝብ አናት ላይ “በስያሜ” ተቀምጦ መጋለብ ነው።
ከዓመታት በፊት የአሜሪካው የመንግሥት ተጠያቂነት ቢሮ በዚህ ጉዳይ ላይ ምርመራ አካሂዶ ነበር፡፡ ያገኘውንም ውጤት ለእንደራሴዎች ምክር ቤት ሲያቀርብ “የወፍጮ ቤቶቹን” አሠራር በግልጽ ዘርዝሯል፡፡ ለምርመራው ያነሳሳው በአሜሪካ የመንግሥት መ/ቤቶች ውስጥ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ድረስ የሚሠሩ “ከወፍጮ ቤቶቹ” የትምህርት ማስረጃ የሸመቱ መኖራቸውን በማረጋገጡ ነበር፡፡ ይህንንም ተከትሎ ቢሮው ያቋቋመው መርማሪ ቡድን ለሦስት ዓመታት በርካታ ዲፕሎማዎችንና ዲግሪዎችን ከአሜሪካና ከሌሎች የውጭ አገራት በቀላሉ በድብቅ ለመግዛት መቻሉን አረጋግጧል፡፡
አሠራሩን እንዴት እንደሆነ ሲገልጽም፤ ከመርማሪ ቡድን አባላት አንዱ ተማሪ በመምሰል “የትምህርት ተቋማቱን” ዲግሪ እንደሚፈልግ መስሎ ይጠይቃቸዋል፡፡ ክፍያ ካጠናቀቀ መግዛት እንደሚችል “ወፍጮ ቤቶቹ” በነገሩት መሠረት የሳይንስ ባችለር ዲግሪ በባዮሎጂ እንዲሁም የሳይንስ ማስተርስ ዲግሪ በሜዲካል ቴክኖሎጂ “ሸምቷል”፡፡ ክፍያ ለጨመረም ሥራ ቀጣሪዎች የትምህርት ማስረጃውን ለማረጋገጥ ሲደውሉ ሊያነጋግሩበት የሚችሉበት የስልክ መስመር አብሮ ይሰጣል፤ በዚሁ አንጻር በየዲግሪዎቹ “የማዕረግ ተመራቂ” መሆን እንደሚቻል ተረጋግጧል፡፡ በአሜሪካ!!!
diploma-millተማሪዎች ክፍል ገብተውም ሆነ በተልዕኮ ትምህርታቸውን የመከታተል ግዴታ እንደሌለባቸው፤ ሙሉውን ክፍያ በአንድ ጊዜ ሲፈጽሙ ለትራንስክሪፕት እንዲያመች ክፍያው በኮርስ ተሸንሽኖ ደረሰኝ እንደሚቆረጥላቸው በምርመራው ተደርሶበታል፡፡ ክፍያው በጨመረ ቁጥር የሚገኘው አገልግሎት እየጨመረና ዲግሪው “እውነተኛ” እየመሰለ እንደሚሄድም ተጠቁሟል፡፡
እንዲህ ያለው ምርመራ ከተካሄደ ዓመታት ያለፉ ቢሆንም አሁንም አሠራሩ ቀጥሏል፡፡ “ወፍጮ ቤቶቹ” አሁንም ዲግሪ መቸብቸባቸውን አላቆሙም፡፡ ከዚህም አልፎ ለዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ የሚሆን ጽሁፍ (ዲሰርቴሽን) አብሮ ተገዝቶ በገዢው ስም እንደሚሰጥ፤ አከፋፈሉ ካማረም ጽሁፉ የሸማቹ መመረቂያ ጽሁፍ ሆኖ በስሙ በኢንተርኔት ይበተናል። እንዲህ ያለው አሰራር አሁን ድረስ ይሰራበታል፡፡ በዚሁ “ወፍጮ ቤት” አማካይነት ተፈጭተው “ዶ/ር” እየተባሉ የመጠራት ጥማት ያላቸው በተለይ የሦስተኛው ዓለም ባለሥልጣናት ገበያውን መቆጣጠራቸው ይታወቃል፡፡
“አቅም ግንባታ” እና “የወፍጮ ቤቶቹ” ሚና በኢህአዴግ
ወደ አገራችን ስንመለስ “በነጻአውጪ” ስም በረሃ የቆዩና አጫፋሪዎቻቸው ለሥልጣን ሲመቻቹ አስቀድሞ የሚደረገው የ“አቅም ግንባታ” ማከናወን ነው። በዚሁ መለስ በነደፉት አቅም አልባ የሚያደርግ የ“አቅም ግንባታ” በርካታዎች “ከወፍጮ ቤት” ደጅ እንዲገረደፉና እንዲፈጩ ተደርገዋል። አሁንም ለመፈጨት ተራ የሚጠብቁና እየተፈጩ ያሉ አቅም አልባ ካድሬዎቹ ቁጥር ቀላል አይደለም። በዚህ አሠራር ቀዳሚዎቹ የትግራይ ተወላጆች ቢሆኑም የሌሎቹ ድቃይ ድርጅቶች አባላትም በሸመታው ዋንኛ ተሳታፊ መሆናቸው ራሳቸው ሸማቾቹ የሚመሰክሩት ሐቅ ነው፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሲናገሩ በአንድ ወቅት ያገኙት በመከላከያ ሚ/ር የሚሠራ የህወሃት ባለስልጣንን የትምህርት ሁኔታ ይጠቅሳሉ፡፡ ግለሰቡ በትግራይ ነጻ አውጪነት ተሰልፎ በነበረበት ጊዜ ራሱ እንደተናገረው የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን አላጠናቀቀም ነበር፡፡ “ከድል” በኋላ ግን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ብቻ ሳይሆን የኮሌጅ ትምህርቱን “አጠናቅቆ” በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪውን እንደተቀበለ ወዲያዉኑ የማስተርስ ዲግሪውን በመቀበል አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እንዲሁም መከላከያ ሚ/ር ውስጥ በኮሎኔል ማዕረግ የመምሪያ ኃላፊነት ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግሯል፡፡ “ይህንን ሁሉ በርካታ ዓመታት የሚፈጅ ትምህርት እንኳን ተምሮ፣ በታክሲ ወይም በአውሮፕላን ተሳፍሮ ቢጋልብ፣ እንደ ጥይት አረር ቢተኮስ ሊደርስበት አይችልም፤ ከብርሃን ፍጥነት ጋር በሚስተካከል መተኮስ ለዚህ ሁሉ በመብቃቱ “የብርሃን ዲግሪ” ልንለው እንችላለን” በማለት አስተያየት ሰጪው ተሳልቀዋል፡፡
ህወሃት/ኢህአዴግ በውጭ ካሉት “የዲግሪ ወፍጮ ቤቶች” የሚሻውን የትምህርት ማስረጃ፣ ለሚወደው ለመሸመትና ያለከልካይ ለመጠቀም እንዲችል “ባለራዕዩ” መለስ ሥልጣን ላይ እንደወጡ ያደረጉት የመንግሥት አመራራቸውንም ሆነ የአስተዳደር ፖሊሲያቸውን አብጠልጥለው ብትንትኑን ሊያወጡ የሚችሉ 42 የኢትዮጵያን ድንቅ ምሁራን በዱሪ መሐመድ ሁለት መስመር ደብዳቤ ማባረር ነበር፡፡ ይህ ለኢትዮጵያ የተደገሰው አዲሱ “የአቅም ግንባታ” መሆኑ ነው። ከዚያም “ሲቪል ሰርቪስ” የተባለ “የዲግሪ/ዲፕሎማ ወፍጮ ቤት” አገር ውስጥ ከፈቱ፡፡ የህወሃት ሹማምንት ከውጪዎቹ “ወፍጮ ቤቶች” የፈረንጅ ዲግሪ ሲገዙ የተላላኪዎቹ ፓርቲዎች አባላት ደግሞ “ከአገር ውስጥ የመለስ ወፍጮ ቤቶች” እንዲሸምቱ ተደረገ፡፡ecsc
ይህ በሥርዓትና በጥናት የተደረገ አካሄድ መለስ በአንድ ወቅት ሚኒስትሮች ሲሾሙ በወቅቱ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የተሹዋሚዎቹን የትምህርት ደረጃ እንዲሁም ችሎታ በዝርዝር ይቅረብልን፤ ለቦታውም እንዴት ሊመጥኑ እንደቻሉ ይነገረን በማለት እንዲጠይቁ አድርጓቸዋል፡፡ “በዲግሪ ወፍጮ ቤት ምሩቃን” ራሳቸውን ከብበው “ቆራጡ፣ አስተዋዩ፣ ብልሁ …” መሪ ሲባሉ የነበሩት መለስ ሲመልሱ መሐይምም እንኳን ቢሆን የኢህአዴግን ዓላማ እስካስፈጸመ ድረስ ሚኒስትር መሆን ይችላል ብለው ነበር፡፡
መለስ የከተማ ጥሩንባ ነፊዎች ነበሩዋቸው። ቅጠል ከሚመነዠክበት የሴሰኞች ሰፈር ጀምሮ እስከ ላይ መለስን ሲያውድሱ የሚውሉ ድርጎ ለቃሚዎች ነበሩ። እነዚህ ድርጎ ለቃሚዎች “አንድ መለስ ብቻ” በማለት የመለስን ዝናና “ልዩ ብቃት፣ ስማርት መሆን” ሲሰብኩ ይውላሉ። መለስ ባይኖር ኢህአዴግ የሚባለው ድርጅት፣ ህወሃት የሚባለው “ነጻ አውጪ” አፍታ እንኳ እድሜ ሊኖረው እንደማይችል ይጠነቁላሉ። መለስ ዋለታና ምሰሶ ባይሆኑ አገር ጨለማ እንደሚውጣት ያስፈራራሉ። ወሬ ፈጣኑ እየነጎደ መለስን አገነነ።
መለስ በባህሪያቸው የሚፎካከራቸውና እሳቸው የሚያስቡትን አስቀድሞ የሚረዳ የትግል አጋር ስለማይወዱ ህወሃት ላይ የወሰዱት የማጽዳት ዘመቻ ምስክር ነው። እነ ተወልደ /ውህዳኑ/ ብዙ ማለት ይችላሉ። ታዲያ የሚፎካከሯቸው ከሌሉ “አላዋቂዎችን ሰብስበው ገነኑ” እንዳይባል በዙሪያቸው ያሉትን ሚስታቸውን ጨምሮ ከ“ወፍጮ ቤት ዲግሪ” ሸመታ ደጅ ማሰለፍ ነበረባቸው። በዚሁ እንደ ግንፍልፍል ምግብ ባስቸኳይ በክፍያ ብቻ በሚሰጥ ዲግሪ ያንበሸበሿቸውን ካድሬዎች ሰብስበው ሲፈላሰፉ ብቻቸውን አዋቂ ሆነው አረፉት፤ “ስማርት መሪ ተባሉ”። በዚያው ስሜት “ተሰው”፤ ይህ ቀድሞ የተሰራና የተፈጠረ ስሜት ካድሬውን ውጦት ስለኖረ የመለስ “መሰዋት” ማረፊያው የማይታወቅ ጉድጓድ ሆነባቸው። ከመለስ ይልቅ ራሳቸው ላይ ሞትን አውጀው በሙት መንፈስ ለመመራት ተማማሉ። ሲማሩ ሳይሆን ሲፈጩ መኖራቸውን መሰከሩ።
online-college-scamsየመጀመሪያ ዲግሪያቸውን የት እንዳገኙ የማይታወቀው መለስ የሥልጣን መንበሩ ላይ እንደተፈናጠጡ በትምህርት መስክ ራሳቸውን ለመቻል ባስመዘገቡት ፈጣን ሪኮርድ መሠረት በኢትዮጵያ ሃብት በከፈሉት ገንዘብ ሁለት የማስተርስ ዲግሪዎች ከአውሮጳ በፖስታ ቤት ተልኮላቸዋል፡፡ ከግለታሪካቸው ጋር አብሮ የሚጠቀሱት የትምህርት ማስረጃዎችም እነዚሁ በፈጣን መልዕክት አገልግሎት የተላኩላቸው የፖስታ “ዲግሪዎች” ናቸው፡፡ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጭንቅላት ለሁለት ዓስርተ ዓመታት ሲበጠብጡ ቆይተው በመጨረሻም የራሳቸውን በጥብጠው “የተሰዉት” መለስ አጠገባቸው በራሳቸው ልክ እያሰፉ “በፈጠሯቸው” የዲግሪና የዲፕሎማ ሸማቾች ተከብበው በመኖራቸው ከዝንጀሮዎች መካከል እንደተገኘች “ቆንጆ” እና “ብልጥ” ጦጣ አድርጓቸው እንደነበር ብዙዎች ይስማማሉ።
በምዕራቡ ዓለም በተለይ በአሜሪካ እነዚህ የዲፕሎማ ወፍጮ ቤቶች በርካታ ከመሆናቸው የተነሳ እጅግ አደናጋሪ ናቸው፡፡ እነዚህ “ኮሌጆች” ለመግቢያ የሚያስፈልጉ ፈተናዎችን አይጠይቁም፡፡ በተለይ ለማስተርስ የዲግሪ ትምህርት መግቢያ የሚያስፈልጉትን ዓለምአቀፍ ዕውቅና ያላቸውን GMAT ወይም GRE ፈተናዎች ተመዝጋቢው እንዲወስድ አይጠይቁም፡፡ አቶ መለስ በፖስታ ከተላከላቸው ዲግሪዎች አንዱ MBA – Master of Business Administration ሲሆን ይህንን ዲግሪ ለማግኘት አብዛኛዎቹ ዕውቅና ያላቸው ተቋማት ተመዝጋቢው GMAT (Graduate Management Admission Test) ፈተና እንዲወስድ የግድ ይላሉ፡፡ ዲግሪው በፖስታ የሚላክ ከሆነ ግን ፈተናውን የመውሰድ አስፈላጊነት አይኖረውም፡፡ ፓርቲያቸው በግድ መሪ ሁን እያለ የሥራ ጫና እያበዛ የሰዋቸው መለስ ከፈተና አምልጠው ለዲግሪ መብቃታቸው ለሁለተኛ ሙት ዓመታቸው የተሠራው “ያልተጠኑ ገጾች” ዘጋቢ ፊልም ውስጥ ሳይካተት ያመለጠ “ያልተጠናው የመለስ ገጽ” ነው፡፡
አቶ መለስ ሁለተኛውን የማስተርስ ዲግሪያቸውን በፖስታ ቤት ፈጣን መልዕክት በተቀበሉበትdog and cat 2004እኤአ በአሜሪካ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት ዳላስ ከተማ ከሚገኝ Trinity Southern University ከተባለ “የዲግሪ ወፍጮ ቤት” ኮልቢ ኖላን የተባለ ድመት $299 ዶላር በመክፈል የባችለር ዲግሪውን ተቀብሏል፡፡ በድመታቸው ስም ማመልከቻውን ያስገቡትና በወቅቱ “ወፍጮ ቤቶቹን” እየመረመሩ የነበሩት የፔንስቬኒያው ግዛት ጠቅላይ አቃቤ ጄሪ ፓፐርት ነበሩ፡፡ ድመቱ የማመልከቻ ደብዳቤውን ሲልክ ከዚህ በፊት ሌሎች ኮርሶችን የወሰደ መሆኑን እንዲሁም ልጅ በመጠበቅ፣ ትኩስ ምግብ መሸጫ ቤት በአሻሻጭነትና በጋዜጣ አዟሪነት የሰራ መሆኑ በተጨማሪ ተገልጾ ነበር፡፡ ይህንን የትምህርት “ብቃት” እና “አመርቂ የሥራ ልምድ” የመረመረው “ዩኒቨርሲቲ” ለኮልቢ በላከው የምላሽ ደብዳቤ የሥራ ልምዱን እና በተጨማሪ የወሰዳቸውን ኮርሶች በመመልከት ለExecutive MBA ብቁ ስለሆነ $100 ዶላር ከጨመረ የባችለር ዲግሪውን ወደ [አቶ መለስ ዓይነት] MBA ዲግሪ እንደሚያሳድግለት ማረጋገጫ ልኮለታል፡፡
በ2010ዓም ደግሞ ለታወቀ የሕግ ኩባንያ የሚሠሩ ማርክ ሃዋርድ የተባሉ የሕግ ባለሙያ ውሻቸው ሉሉ ከኮንኮርዲያ ዩኒቨርሲቲ MBA ዲግሪ እንዲቀበል አድርገውታል፡፡ ሉሉ “ዲግሪውን” በማዕረግ መቀበል መቻሉ በወቅቱ አብሮ የተነገረ ሲሆን “በዩኒቨርሲቲውም” በአካል ተገኝቶ ክፍል ስለመከታተሉ (ስለውሻ እንደሚመሰክር ያላወቀው ምስክር) በሃሰት መስክሮለታል፡፡
ከላይ ለማለት እንደተሞከረው “የወፍጮ ቤቶቹ” መብዛት አደናጋሪነታቸውን የሰፋ አድርጎታል፡፡ በተለይም ደግሞ ከሚሰበስቡት ገንዘብ አንጻር የሚያካሂዱት የተጠና የማስታወቂያ ሥራ “እውነተኛ” እንዲመስሉ አድርጓቸዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አንዳንድ መረጃ ለመሰብሰብ የሚፈልጉ በተለያዩ ፎረሞች ላይ ምርምር ሲያደርጉ “ወፍጮ ቤቶቹ” ያሰማሯቸው “ካድሬዎች” የሚሰጡት ምላሽ በብዙዎች ዘንድ እንደ ትክክለኛ ምላሽ ይወሰዳል፡፡
በዚህ የዲግሪ “ወፍጮ ቤት” ሙያ ከተካኑት መካከል የሚጠቀሱት ካፔላ ዩኒቨርሲቲ አንዱ ሲሆን በተደጋጋሚ እጅግ በርካታ ክሶችና ወቀሳዎች ደርሰውበታል፡፡ የሃሰት ዲግሪ በመስጠት፣ ብቃት የሌላቸው መምህራን በመቅጠር፣ የሚቀጥራቸው መምህራን ከአሜሪካ ውጪ የመጡና የትምህርት ማስረጃቸውን እርግጠኝነት መናገር የማይቻል መሆኑ፣ በቂ ገንዘብ እስከተከፈ ድረስ ማንኛውንም ዓይነት ዲግሪ (ዶክትሬትም ቢሆን) እንደሚሰጥ፣ … fake-diploma1እጅግ ብዙ ተብሎበታል፡፡ በአሜሪካ የሚገኘው ብሔራዊው የሕዝብ ሬዲዮ (NPR) ከዚህ ጋር ተዛማጅነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ የምርመራ ዘገባም ሰርቶበታል፡፡ “ዩኒቨርሲቲው” ብዙውን ነገር ለማሻሻል የሞከረ ቢሆንም ከዚያ ይልቅ ግን እየወሰደ ያለው እርምጃ ባሰማራቸው የማስታወቂያ ካድሬዎቹ አማካኝነት ስሙን እያደሰ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ፡፡
ካፔላ ዩኒቨርሲቲ እያተመ በፖስታ የሚልከው ዲግሪ ለብዙ ከፋዮች ደርሷል፤ የአንዳንዶችም “ማዕረጋቸውን” ከአቶነት ወደ “ዶ/ር” አስቀይረውበታል፡፡ አድዋ ተወልደው ያደጉትና የህወሃት የስለላ ሞተር እንዲሁም ዋንኛ የስልክ፣ የሬዲዮ፣ ወዘተ ሞገድ ጠላፊ የሆኑት “ዶ/ር” ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የካፔላ ዩኒቨርሲቲ “ምሩቅ” ናቸው፡፡ አሽቃባጭ ደጋፊዎቻቸው የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከሃርቫርድ የተቀበሉ ለማስመሰል በየቦታው በሚለጥፉት ግለህይወታቸው ላይ ፕሮፓጋንዳ ለመንፋት ቢሞክሩም ካፔላ “ወፍጮ ቤት” ዩኒቨርሲቲ ግን “ዶ/ር” ብዬ ለዚህ ያበቃኋቸው እኔ ነኝ በማለት በማስረጃ የተደገፈ ምስክርነቱን ይሰጣል፡፡
ገዢው ኢህአዴግና ቁንጮው ህወሃት በዚህ መልኩ ታማኞቹን “አቅም እየነሳ” በየዘርፉ አሰማርቷቸዋል። በሽታውና ችግሩ ለህወሃት ባይሆንም አገርን ጤና እየነሳ ነው። ህወሃት እንደስሙ መቼ ነጻነቱን አውጆ አገር እንደሚሰራ ባይታወቅም በራሱ ምድር፣ ለራሱ “የተስፋ ቀበሌ” የተለያዩ “ስፔሻል” የሚባሉ እቅዶች እንዳሉት አይዘነጋም። በልዩ ክትትል የሚያስተምራቸው ተተኪ ካድሬዎችም እያመረተ ነው። የሚዋኝበት ሃብትም ሰብስቧል። ጉዞው ቀጥሏል። መለስ አስፈጪ የሆኑበት ወፍጮ የሚፈጫቸውና የተፈጩት ባለስልጣናት አልመው የሚያደቁት ህዝብ መጨረሻ ምን ይሆን? በዚህ ጉዳይ ላይ በውክልና ካድሬዎችን ወፍጮ ቤት /በሊደርሺፕ ስልጠና ስም/ የሚያጠምቁት ፕሮፌሰሩ ፓስተር ምን ይሉ ይሆን? “ተቋማቸው” በግልጽ ማስረጃ ከነፎቷቸው በዘረዘረው መሠረት ሃይለማርያም ደሳለኝ (ፊንላንድ በወጉ ተምረው በውክልና ሊደርሺፕ ተፈጭተዋል)፣ አባዱላ ገመዳ፣ አዲሱ ለገሰ፣ በረከት ስምዖን፣ አብዲ ሞሐመድ ዑመር፣ ጁነዲን ሳዶ፣ ኩማ ደመቅሳ፣ ሙክታር ከዲር፣ ሽፈራው ተክለማርያም፣ ሬድዋን ሁሴን፣ ሽፈራው ሽጉጤ፣ አስቴር ማሞ፣ ድሪባ ኩማ፣ ዘነቡ ታደሰ፣ ካሳ ተክለብርሃን፣ አርአያ ገብረእግዚአብሔር፣ ኦሞድ ኦባንግ፣ … ዝርዝሩ ሊያልቅ አይችልም፡፡ እነዚህ ሁሉ በአገር ውስጡ “ወፍጮ ቤት” የተመረቱና “በሊደርሺፕ የተጠመቁ” ናቸው – የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አንጋፋ ምሁራን! እዚህ ላይ ከቅቅል ባቄላ ውስጥ አንድ ጥሬ እንደማይጠፋ አለመዘንጋቱ ይስተዋላል፡፡
ህወሃት በሚነዳት አገራችን አውራ ዶሮ “አኩኩሉ” ሲል በሚያሳይ ማስታወቂያ እስከ ገጠር ዘልቆ ብር እያመረተ ካለው ኮሌጅ ይቅርታ “ወፍጮ ቤት” ጀምሮ በበቅሎ ጀምረው በሃመር ገጠር ገብተው በራሪ ወረቀት የማሰራጨት ደረጃ የደረሱትን ማን ይመርምራቸው? የትምህርት ጥራት ገደል ገባ እየተባለ ደረት ሲመታ ማን ዋናውን ችግር ይንካው? አላቅሙ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምር፣ አላቅሙ ሚኒስትር የሚሆን፣ አላቅሙ አገር የመምራት ጭነት የሚጫንበት … ሁሉም አላቅሙ በከመረው የውድቀት ክምር ይኮራል፤ በእርሱ አላዋቂነት አገርን ያከለ ታላቅ ነገር ሲወድምና ትውልድ ሲጠፋ ምንም አልሰማ ብሎት ደንዝዟል፤ ስብ ደፍኖታል፡፡ በውድመቱ ውስጥ ግን የራሱን ማንነት ጨምሮ ልጆቹና የልጅ ልጆቹ አብረው እየወደሙ መሆናቸው አይታየውም፤ በሞራ የተሸፈነው ዓይኑ የሩቁን እንዳያይ ጋርዶታል፡፡ ይህ ውርደቱ ሊሆን ሲገባው እንዲያውም ኩራቱ ነው፡፡ በቃኝ፣ እኔ ለዚህ አልመጥንም፣ እስከዛሬ ያለ እውቀቴ ሳንቦራጭቅ ኖሬያለሁና ይቅርታ የሚል ትውልድ ሳናይ ሁለት መንግስታትና አንድ ቅኝ ገዢ ነዱን። ይህ መሰሉ በሽታ የገዢዎቻችን ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚዎቻቸውም መሆኑ ችግሩን እጅግ የባሰ አድርጎታል፡፡ ግን እስከመቼ?
አሜሪካ ፓርላማ/ምክር ቤት ስላላት ጉዳዩን መረመረች። በጀት መድባ ሰለለች። መረጃውን በማስረጃ አረጋግጣ እውነቱን ደረሰችበት። እኛ ምን ፓርላማ አለን? ቢኖረንስ ማንን ሊመረምሩና ሊያስመረምሩ? አስፈጪውና ተፈጪው ብቻ ሳይሆን የወፍጮ ቤቱ ባለቤት ሁሉ አብረው ቀጥለዋል፤ ወፍጮው አሁንም ይፈጫል። የቀድሞውን አስፈጪ የተካቸው በግልጽ አልታወቀም። ለኢትዮጵያ አቅም ግንባታ መፈጨት አማራጭ የለውም። “ተፈጭና ተመረቅ” አስተምህሮተ መለስ!! ለጊዜው!!

በአፋር ክልል በተለያዩ ሞያዎች ሲሰሩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ወደ ክልላቸው እንዲመለሱ ታዘዘ

October 19,2014
አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የአማራ ተወላጆች ላለፉት 20 አመታት በአፋር ክልል በተለያዩ ሞያዎች ሲያገለግሉ ቆይተዋል። አሁን ከአፋር ክልል ሾልከው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከሆነ እነዚህ የአማራ ተወላጆች በአስቸኳይ ወደ ክልላቸው እንዲመለሱ በአማራ ክልላዊ መንግስት ታዘዋል። በጉዳዩ ላይ የአማራ ክልልና የአፋር ክልልን መንግስታት የተስማሙ ሲሆን «ይህ ውሳኔ በህወሓት ሆን ተብሎ በአፋር ክልል ለኢህአዴግ ታማኝ የሆኑ የወያኔ ደጋፊ ትግሬዎች ተወላጆችን ለመተካት የተደረገ ነው» ሲሉም ምንጮቻች ያስረዳሉ።
ወያኔ በተለይ በሶማሌ ክልልና በአፋር ክልል የሚሰሩ የአማራ ተወላጆችን «ከተቃዋሚዎች ጋር ይተባበራሉ» የሚል ስጋት እንዳለውና ከመጪው ምርጫ በፊት ከአፋር ክልል የአማራ ተወላጆችን አስወግደው በወያኔ ቤተሰብ እንዲተኩ አስቧል። በአፋር ክልል ብዙ በተለያዩ ሞያዎች በመጀመሪያ ዲግሪና በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ምሁራን ስራ የማያገኙበት ሁኔታ እያለ ክልላችን የህወሓት መጫወቻ መሆኑን የአፋር ወጣቶችን ሞራል የሚነካ ተግባር ነው ሲሉ አንዳንድ አስተያየት ሰጭዎች ይናገራሉ። በንግድም ቢሆን የአፋር ክልልን የወያኔ ደጋፊ ትግሬዎች ተወላጆች ብቻ እንዲቆጣጠሩ እየተደረገ ሲሆን በአሁን ወቅት ይሄ ሁሉ ሴራ የሚያሴሩት በተንዳሆ ሱኳር ፋብረካ እያሰሩ የሚገኙት የቀድሞው የህወሓት ታጋይ አቶ ሚካኤል ናቸው።

አቶ ሚካኤል በየእሁድ በአፋር ክልል ለሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች በሎግያ ከተማ ስብሰባ የሚያደርጉ መሆኑንና የስብሰባ ቦታቸውም ናዝሬት ሆቴል ቁጥር 1 የሚባለው ሲሆን የናዝሬት ሆቴል ባለቤት በንግድ የአፋር ክልልን የወያኔ ደጋፊ ትግሬዎች ብቻ እንቆጣጠሩ የሚለፉ የትግራይ ሀብታም ናቸው። አሁን ለአቶ ሚካኤል ይህ የመንግስት ሰራተኞችን የማባረር ሴራ ከተሳካላቸው የአፋር ክልል መሉ በሙሉ በወያነ ቤተሰቦች ይያዛል ማለት ነው፣ የአፋር ህዝብም ቢሆን ከከተማ እያስወጡ ወደ ገጠር እየመለሷቸው ነው። ይህ ደግሞ ለወደፊት ከጀቡቲ ታኮሪ ወደ መቀሌ ለሚሰራው የባቡር ሀዲድ ዝርጋታና ወደ ፊትም የትግራይ ክልል የኢንዱስትሪ ዞን የማድረግ አላማ ስላላቸው የአፋር ክልልን በቀላሉ ለመቆጣጠር ነው።

“እኔ ብቻ” ቢያክሙት የማይሽር የወያኔ በሽታ

October 19,2014
ዘረኝነት፤ ጎጠኝነትና ዕብሪት የወያኔ አዲሰ ባህሪያት ሳይሆኑ አስራ ሰባት አመት ጫካ ዉስጥ በቆየባቸዉ አመታትና ዛሬም ከጫካ ወጥቶ አገር እየመራ በቆየባቸዉ ሃያ ሦስት አመታት አብረዉት የኖሩ መታወቂያ ካርዶቹ ናቸዉ። ዘረኝነት፤ አማራ ጥላቻና የትግራይ ሪፓብሊክ ህልም ዋና ዋናዎቹን የወያኔ መሪዎች ደደቢት በረሃ ከገቡ በኋላ በድንገት የለከፋቸዉ በሽታ ሳይሆን ከና ከልጅነታቸዉ ተጠናዉቷቸዉ አብሯቸዉ ያደገ በሽታ ነዉ። ወያኔ ጨካኝ ነዉ፤ ወያኔ ዉሸታም ነዉ፤ወያኔ ከሃዲ ነዉ፤ ወያኔ ለኢትዮጵያ ዳርድንበርና የግዛት አንድነት ደንታ የሌለዉ ባዕድ አካል ነዉ። እነዚህ ሁሉ የወያኔን ማንነትና ምንነት በትክክል የሚገልጹ የወያኔ በሽታዎች ናቸዉ። በዛሬዉ ቆይታችን በልዩ መነጽር አብረን የምንመለከተዉ የወያኔ በሽታ ግን በአይነቱ ከእነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት በሽታዎቸ ጋር ተመሳሳይ ቢሆንም በጠባይና በአገላለጽ ግን ለየት ያለ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ለአመታት እንዳየዉም ሆነ ሀወሓትን መስረተዉ ለስልጣን ያበቁትና ህወሓት ለእነሱም አልበጅ ብሏቸዉ ጥለዉት የወጡት ግለሰቦች በቃልም በጽሁፍም እንደነገሩን ወያኔ የጫካ ዉስጥ ጠባዩን ዛሬም ያልለቀቀ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ዛሬማ ጭራሽ ብሶበት ያየዉን ነገር ሁሉ ነጥቆ የራሱ ካላደረገዉ ወይም ሙሉ ለሙሉ ካልተቆጣጠረዉ አርፎ የማይተኛ ድርጅት ሆኗል። ብዙዎቻችን የወያኔ ስም በተነሳ ቁጥር ትዝ የሚለን ዘረኝነቱ ነዉ። በእርግጥም ወያኔ ግለሰብንና ግለሰቦችን ወይም የተለያዩ ቡድኖችን በዘር መነጽር ብቻ የሚመለከት ዘረኛ ድርጅት ነዉ። ሆኖም ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት ለመደምሰስ የሚደረገዉ ትግል የወያኔን ዘረኛ ገጽታ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የወያኔ ገጽታዎች ማጋለጥና መዋጋት አስፈላጊ ነዉ። ለምሳሌ ወያኔ በፕሮፓጋንዳዉ ይዋጋናል፤ በዲፕሎማሲ ዘርፍ ይዋጋናል፤ በማህበራዊ ሜዲያዉ ዘርፍ ለተሳዳቢዎች ገንዘብ እየከፈለ ይዋጋናል፤ ከዚህ በተጨማሪ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ፤ መከላከያና የደህንነት ተቋሞች አማካይነትም ይዋጋናል። አዎ ! ወያኔ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ተቋሞች አማካይነት እንቅልፉን ትቶ ቀንና ማታ ይዋጋናል። ዉድ አድማጮቻችን እቺን ወያኔ በቁጥጥሩ ስር ባደረጋቸዉ ተቋሞች አማካይነት ይዋጋናል የምትለዋን አባባል ጠበቅ ያደረግነዉ አለምክንያት አይደለም። ዛሬ ብዙ የምናወራዉ ስለዚሁ “ሁሉን ነገር መቆጣጠር” ስለሚለዉ የወያኔ አባዜ ነዉ።
በወያኔ የበላይነት የተጻፈዉ የኢትዮጵያ ህገ መንግስት – የኢትዮጵያ ብሄር፤ ብሄረሰቦች፤ ህዝቦች የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሥልጣን ባለቤቶች ናቸዉ ይላል። ሆኖም የዚህ ሉዓላዊነት መገለጫ በሆነዉ ፓርላማ ዉስጥ 38 መቀመጫዎች ብቻ ያለዉ ህወሓት 509 መቀመጫዎች ያላቸዉን ከትግራይ ዉጭ ያሉትን ሌሎቹን የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች የፖለቲካ ህይወት ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራል። የሚገርመዉ ወያኔ የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያን ህዝብ የፖለቲካ ህይወት ብቻ አይደለም። የኢትዮጵያን የኤኮኖሚና የማህበራዊ ዘርፎችም ሙሉ በሙሉ በወያኔ ቁጥጥር ስር የወደቁ ናቸዉ። በአጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ በዬትኛዉም ዘርፍ ከላይ እስከታች እሱ የማይቆጣጠረዉ ምንም ነገር እንዲኖር አይፈለግም። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ዉሰጥ በወያኔና በሁለቱ ግዙፍ የአገራችን ሐይማኖቶች መካከል ለአመታት የዘለቀዉ ንትርክ፤ አተካሮና ፍጥጫም የዚሁ የወያኔ ሁሉንም ነገር እኔ ብቻ ካልተቆጣጠርኩት የሚል ክፉ አባዜ ዉጤት ነዉ።
የወያኔ “እኔ ብቻ” አባዜ አዲስ አበባ ገብቶ ሥልጣን ከያዘ በኋላ የተጀመረ አዲስ እብደት ሳይሆን ወያኔ ገና በረሃ ዉስጥ እያለም ሰፊዉን የትግራይ ጫካ እኔ ብቻ ካልተቆጣጠርኩት የሚል በሽተኛ ድርጅት ነበር። ይህ ደግሞ ወያኔን ስለምንቃወመዉ ብቻ የምንለዉ ተራ ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ወያኔን ፈጥረዉ ለዛሬዉ ሥልጣን ካበቁትና ዛሬ የወያኔ አካሄድ አንገሽግሿቸዉ ይህንን ድርጀት በአይናችን አናይም ብለዉ ከማሉ የትግራይ ተወላጆች አንደበት የወጣ ሐቅ ነዉ። እነዚህ የወያኔን ታሪክ የተረኩልን ወይም በመጽሐፍ ጽፈዉ ያስነበቡን ግለሰቦች ወያኔ አንዳንድ እንደነሱ ጫካ ገብተዉ ትግል የጀመሩ የትግራይ ድርጅት መሪዎችን ለስብሰባ ጠርቶ ማታ በተኙበት ቦታ አንገታቸዉን እንዳረደ ሳይደብቁ ነግረዉናል። ወያኔ የትግራይን ጫካና በረሃ ብቻዬን ካልተቆጣጠርኩ በሚል ከኢዲህና ከኢህአፓ ጋር በተከታታይ ደም የተቃባ ድርጅት ነዉ። በተለይ ኢህአፓዎችን የትግራይ መሬት የናንተ አይደለምና ለቅቃችሁ ካልወጣችሁ እያለ ዛሬም ድረስ በየቦታዉ የሚጠቀምበትን “ክልሉን ለቅቃችሁ ዉጡ” የሚለዉን የዘረኝነት ፓሊሲዉን ገና ከጧቱ በረሃ ዉስጥ እያለ አሳይቶናል።
ወያኔ የትጥቅ ትግል ጀምሮ ጫካ ዉስጥ በቆየባቸዉ ግዜዎች ሁሉ ያሳየዉ ጠባይና አንዳንድ የወሰዳቸዉ እርምጃዎች ዛሬም ድረስ አብዛኛዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ግራ ያጋቡና ዛሬም ድረስ መልስ ያልተኘላቸዉ እንቆቅልሾች ናቸዉ። ለምሳሌ ለህዝብ መብት፤ ነጻነትና እኩልነት እታገላለሁ ባዩ ወያኔ የሱን የመሰለ ተመሳሳይ አላማ የነበራቸዉን ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ህልዉናቸዉ እስኪጠፋ ድረስ በመሳሪያ ጭምር ተፋልሟቸዋል። በወቅቱ መሳሪያ አንግበዉ ለኤርትራ ህዝብ ነጻነት ይታገሉ የነበሩትን ጀብሃንና ከሻዕቢያን በተለይ ሻዕቢያን ግን ልክ እንደፈጣሪዉ ተመልክቶ ለፈጠሪ አምላክ ብቻ የሚሰጠዉን ስግደትና ማደግደግ ለሻዕቢያ ካለምንም ይሉኝታ ሰጥቷል። በትጥቅ ትግሉ ዘመን በነበረዉ የወያኔና የሻዕቢያ ግንኙነት የወያኔ መሪዎች ከሻዕቢያ ጋር ባልተስማሙባቸዉ ግዜዎቸም ቢሆን ወያኔ ሻዕቢያን እንደ ጌታዉ ማየቱንና ለሻዕቢያ መታዘዙን ያቆመበት አንድም ግዜ እንዳልነበረ ዛሬ በወቅቱ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የነበሩ ግለሰቦች በቁጭት የሚናገሩት ሐቅ ነዉ። የወያኔና የሻዕቢያ አላማ ተመሳሳይ እንዳልነበረ ለሁሉም ሰዉ ግልፅ ይመስለናል። ከሁለቱ የለየላቸዉ ከሀዲዎች ከመለስ ዜናዊና ከስብሀት ነጋ ዉጭ የአብዛኛዉ የህወሓት መሪና አባል አላማ የትግራይ ህዝብ መብትና ነጻነት በኢትዮጵያ የግዛት አንድነት ዉስጥ ተከብሮ እንዲኖር ነዉ። የጀብሀና የሻዕቢያ አላማ ግን ከዚህ ፍጹም የተለየ ነበር። ሆኖም ወያኔ ከሱ ጋር ተመሳሳይ አላማ ያላቸዉን ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ድርጅቶች እየወጋ ለየት ያለ አላማ ላለዉ ሻዕቢያ ግን እጁን ሰጥቶ በወዶ ገባነት የኖረ ድርጅት ነዉ። ባጠቃላይ የአገራችን የክርስትና እምነት መሠረት በሆነችዉ ትግራይ ዉስጥ ተወልደዉ ያደጉት የወያኔ መሪዎች ሻዕቢያን እንዳምላካቸዉ ስለሚያዩ አጠጋባቸዉ ካለችዉ አክሱም ፅዮን ይልቅ ኤርትራ ድረስ እየሄዱ ለሻዕቢያ እንደ ታቦት ጎንበስ ብለዉ ሰግደዋል። ዛሬ እነዚህ የሻዕቢያ የእልፍኝ ዉስጥ ተላላኪዎችና ሻዕቢያ እንደ ልጅ ሳይሆን እንደ ማደጎ ልጅ ያሳደጋቸዉ ከሃዲዎቹ የወያኔ መሪዎች ናቸዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነጸነት፤ እከኩልነትና ሰላም የሚታገሉ ድርጅቶችን ከሻዕቢያ ጋር ይሰራሉ እያሉ ክስ የሚያቀርቡት። ደንቆሮዎቹ የወያኔ መሪዎች ምንም ነገር ስለማይገባቸዉ ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱ ሆን ብለዉ በቆፈሩት ጉድጓድ ዉስጥ ገብቶ ቁም ስቅሉን እያየ ነዉ። የዚህ ህዝብ ፍላጎት ከዚህ የምድር ላይ ገሀነም ከሆነ ጉድጓድ ዉስጥ መዉጣት ብቻ ነዉ። በሻዕቢያ በኩል ይዉጣ፤ በኬንያ ወይም በጂቡቲ በወያኔ እሳት የሚለበለበዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደዚህ አይነቱን የቅንጦት ምርጫ ለማስተናገድ ግዜም ትዕግስትም የለዉም።
ወያኔ በ1983 ዓም አዲስ አበባን ተቆጣጥሮ የሽግግር መንግስት ሲያቋቁም ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ከሆነባቸዉ ነገሮች አንዱ የሽግግር መንግስቱን የማቋቋሚያ ሂደትም ሆነ በሚቋቋመዉ የሽግግር መንግስት ዉስጥ የሚወሰኑ ዉሳኔዎች ሁሉ በወያኔ ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚወሰኑ ዉሳኔዎች መሆናቸዉን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህ ነዉ የትግራይን ህዝብ ሰባትና ስምንት ግዜ እጥፍ የሚበልጠዉን የኦሮሞን ህዝብ እወክላለሁ የሚለዉ ኦነግ ገና ከጥዋቱ የሽግግር መንግስቱን ዘፈንና ጭፈራ ከተመለከተ በኋላ “ከዚህስ ጎመን በጤና” ብሎ ሁለተኛ ዙር የትጥቅ ትግሉን የጀመረዉ። በሽግግር መንግስቱ ዉስጥ ህገመንግቱን ማርቀቅን፤ የፌዴራል ስርዐት ማቋቋምንና የክልል አመሰራረትን ጨምሮ የሽግግር መንግስቱንና ከዚያም በኋላ የተፈጠረዉን የዉሸት መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ ሁሉንም ስራ የሰራዉ ህወሐት ብቻ ነዉ፤ ሌሎቹ ከአጃቢነት ዉጭ ሌላ ምንም አይነት የጎላ ሚና አልነበራቸዉም።
በኢትዮጵያ የሙያ ማህበራት ታሪክ ዉስጥ ረጂም ታሪክና ጉልህ የአስተባባሪነትና የህዝባዊ ትግል መሪነት ሚና የነበራቸዉ ሁለቱ አንጋፋ የሙያ ማህበራት የኢትዮያ ሰራተኞች ማህበር (ኢሰማ) እና የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር (ኢመማ) ነበሩ። እነዚህ ሁለት የሙያ ማህበራት ዛሬም መኖራቸዉ ጥርጥር ዉስጥ እስኪገባ ድረስ ደብዛቸዉ የጠፋዉ ወያኔ ሁለቱንም ማህበራት በቁጥጥሩ ስር በማድረጉ ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ በማቆጥቆጥ ላይ የነበሩ የሲቪክ ማህበራትና የዲሞክራሲ ግንባታ ተቋሞች ከዉጭ አገር ምንጮች እርዳታ እንዳያገኙ በማድረግ እነዚህ ተቋማት ወይ በወያኔ ቁጥጥር ስር እንዲደራጁ አለዚያም እንዲጠፉ አድርጓል። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ እንቅስቃሴያቸዉን ብቻ ሳይሆን ህልዉናቸዉን ጭምር ሙሉ በሙሉ የማይቆጣጠር ምንም አይነት ህዝባዊ ተቋማት ወይም የሙያ ማህበራት የሉም።
ወያኔ ቄስ፤ ሼክ፤ መምህር፤ አሰልጣኝ፤ የአገር መሪ፤ ነጋዴ ወዘተ ሁሉንም ነገር መሆን የሚፈልግ ብቻ ሳይሆን መሆን የማይችለዉን ካልሆንኩ እያለ አገር የሚያበላሽ ችኮ ድርጅት ነዉ። ወያኔ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ ከቤ/ክርስቲያን ህግና ደንብ ዉጭ የተሾመ ጳጳስ እያለ የራሱን ታጣቂ ጳጳስ የሾመ ዉግዝ ከመአሪዮስ የሆነ ድርጅት ነዉ። ወያኔ የክርስቲያን ተቋሞችን መቆጣጠሩ አልበቃ ብሎት ፊቱን ወደ መጂሊስ አዙሮ የእስላምና እምነት ተከታዮችንም ከእምነታቸዉ ዉጭ እምነት ካልሰጠኋችሁ ወይም ካልተቆጣጠርኳችሁ እያለ ያስቸገረ እኩይ ድርጅት ነዉ። ዛሬ ወያኔ ከእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር የገባዉ ከፍተኛ ቅራኔና በጥቁር ህዝብ ታሪክ ዉስጥ በጥንታዊነቷ የምትታወቀዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ህጋዊዉ ሲኖዶስና የወያኔ ሲኖዶስ ተብላ ለሁለት የተከፈለችዉ ወያኔ የሙስሊሞቹን መጅሊስና እቺን ጥንታዊት ቤ/ክርስቲያን ለመቆጣጠር እጅግ በጣም ፀያፍ የሆነ እርምጃ በመዉሰዱ ነዉ።
ኢትዮጵያ ዉስጥ የሐይማኖት ነጻነት ተረጋገጠ ብሎ የነገረን ወያኔ ባጳጳስ ላይ ጳጳስ ሾሞ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን የተቆጣጠረዉ ገና በጧቱ ነበር። ወያኔ ጳጳስ ብሎ የሾማቸዉ የአድዋዉ ተወላጅ አባ ጳዉሎስ ጳጳስ ሆነዉ ባገለገሉባቸዉ አመታት ሁሉ ወገባቸዉን ባጭር ታጥቀዉ ያገለገሉት የሰማዩን አባታቸዉን ሳይሆን የአድዋዉን ወንድማቸዉን መለስ ዜናዊን ነዉ። ፍርድ የማይሳነዉ እግዚአብሄርም ይህንን ምህረት የማይገባዉ በደል ተመልክቶ ነዉ እነዚህን ሁለት አመጸኞች መንፈቅ በማይሞላ ግዜ ዉስጥ ተራ በተራ የወሰዳቸዉ። ወያኔ አይናቸዉ ገንዘብና ንብረት ካየ በፍጹም አርፈዉ የማይተኙ ስግብግቦች ስብሰብ ቢሆንም የኢተዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያንን ይቆጣጠራል ወይም ተቆጣጠረ ስንል ወያኔ የሚቆጣጠረዉ የቤ/ክርስቲያኒቱን ገንዘብና ንብረት አይደለም፤ ይልቁንም ወያኔ በቅርብ የሚቆጣጠረዉ የቤ/ክርስቲያኒቱን ዋና ዋና ዉሳኔዎችና ቤ/ክርስቲያንቱ በማህበረሰቡ ላይ ማድረስ የምትችለዉን ተፅዕኖ ነዉ። ዛሬ ወያኔ “ማህበረ ቅዱሳን” በሚል ስያሜ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ስር የተደራጁ የእምነታቸዉ ቀናተኞችን ዉስጣችሁ ካልገባሁ እያለ የሚያዉካቸዉ አብሯቸዉ ፈጣሪን ለማምለክ ሳይሆን ያንን ሁሉንም ነገር ካልተቆጣጠርኩ የሚለዉን አባዜዉንና ስስቱን ለማርካት ሲል ብቻ ነዉ።
የሚገርመዉ ወያኔ የኢትዮጵያ ህዝብ ከሱ ቁጥጥር ዉጭ ሲተነፍስም ደስ ስለማይለዉ አንድ ለአምስት የሚባል የኮሚኒስቶች አደረጃጃት ይዞ መጥቶ ወጣቶችን፤ ሴቶችን፤ ሰራተኞችን፤ ገበሬዎችንና መምህራንን በአንድ ለአምስት አደራጅቶ አንዱ ስለሌላዉ በየቀኑ መረጃ እንዲሰበስብና ለበላይ አካላት እንዲያሳዉቅ አድርጓል። ስለሆንም ይህንን የወያኔን “እኔ ብቻ” የሚል አባዜ ከስሩ መንግሎ ለመጣል ብቸኛዉ መንገድ ወያኔን እራሱን በተባበረ ክንድ መንግሎ መጣል ነዉ እንጂ ዋልድባ፤ መጅሊስ፤ ወይም ማህበረ ቅዱሳን እያልን በተናጠል የምናደርገዉ ትግል ዋጋ የለዉም፤ ወይም ወያኔ ወደ እያንዳንዳችን አናት ላይ እስኪወጣ መጠበቅ የለብንም። ወያኔ ሌሎችን ሲያጠቃ “እኛ የለንበትም” ብለን ቁጭ ብለን እየተመለከትን የወያኔ ዱላ እኛጋ ሲደርስ የምናሰማዉ የድረሱልኝ ጩኸት ሰሚ አያገኝም – ማግኘትም የለበትም። የወያኔን ዘረኝነትና “እኔ ብቻ” የሚያሰኝ ክፉ በሽታ ለማጥፋት ብቸኛዉ መንገድ ወያኔንና ስርዐቱን በህዝባዊ ትግል ገርስሶ መጣል ብቻ ነዉ፤ ህዝባዊ ትግል ደግሞ መቀራረብን፤ መከባበርን፤ መተሳሰብን፤ አንድነትንና ትብብርን ይጠይቃል። እንግዲህ እንደ ትናንቱ ሁሉ የዛሬዉም ጥሪያችን ኑና ወያኔን በተባበረ ክንድ እንጣል የሚል ነዉ።