Monday, June 23, 2014

አቡጊዳ – በሺሆች የሚቆጠሩ ከወለጋ «አማራን አንፈልግም» ተብለው ተፈናቀለ- ኦህዴዶች ፈርተው ነው ይላሉ

June23/2014
የአሜሪካን ድምጽ ራዲዮ አማርኛዉ ክፍል ባቀረበው ዘገባ በሺሆች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ኢትዮጵያዉያን ከቅያቸው እንደተፈናቀሉ ታወቀ። ከምዕራብ ወለጋ ጊምቢና ቀለም የተፈናቀሉ ወገኖች፣ ሲሆን፣ «ተባረርን ቤት ንብረታችን ወደመ፣ ተቃጠለ» ሲሉ የደረሰባቸውን ሰቆቃ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በዝርዝር ገልጸዋል።
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት የክልሉ ባለስልጣናት ዜጎች መፈናቀላቸውን ያመኑ ሲሆን፣ «ተገደው ሳይሆን ፈርተው ነው የሄዱት» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሕወሃት/ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ የዘረጋው የዘር ፖለቲካ በብሄረሰቦች እና በብሄረሰቦች መካከል መከፋፈልና መፈራራትን እንዲመጣ ያደረገ መሆኑ የገለጹት በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ፣ «ዜጎች በአገራቸው መኖር ካስፈራቸው የተዘራው ጥላቻ ምን ያህል ሥር እንደሰደደ የሚያሳይ ነው» ሲሉ ሁሉም ዜጎች፣ ሕዝብን ከሕዝብ ሊያጨራርስና የሩዋንዳ አይነት እልቂት ሊያመጣ ከሚችል ዘረኝነት አጥብቆ መወጋት እንዳለበት ይናገራሉ።
በሕዝብ ቆጠራ ዉጤት መሰረት ፣ በቀለም ወለጋ ዞን 97% የየሚሆኑ ነዋሪዎች አንደኛ ቋንቋቸው አፋን ኦሮሞ እንደሆነ ያስረዱት እኝሁ ተንታኝ፣ የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የዘገበው አይነት የዘር ማጽዳት ወንጀል ከቀጠለ፣ ቀለም ወለጋ ሙሉ ለሙሉ፣ የኦህደድ አክራሪዎች «አቢሲኒያዎች» ከሚሏቸው የጸዳች ልትሆን እንደምትችል ለመገመት አያስቸግርም በማለት በወለጋ የታየውን አሳዛኝ ብለዉታል።
በቅርቡ የጥላቻ ሃዉልት የሚባለው የአኖሌ ሃዉልት በሚሊዮንች ብር በሚሆን ከሕዝብ ካዝና በተገኘ ወጭ በኢሕአዴግ ተገንብቶ፣ በክልሉ አስተዳዳሪ አቶ ሙክታር ከድር መመረቁ ይታወሳል። በኦሮሚያ ሕገ መንግስትም፣ የኦሮሚያ ግዛት ባለቤት፣ ኦሮምው ብቻ እንደሆነ የተቀመጠ ሲሆን ሌሎች ኢትዮጵያዊያን በኦሮሚያ እንደ ዉጭ አገር ዜጋና እንግዳ እንዲታዩ የሚያደርግ የፖለቲካ ሲስተም መዘርጋቱ በግልጽ የታወቀ ነው።

Sunday, June 22, 2014

የ2007 የመንግሰት በጀት ሚስጥር

June 22/2014
ከግርማ ሰይፉ ማሩ

የኢትዮጵያ በጀት በደንብ አድርጎ ለመረመረው ሀገሪቱ ያለችበትን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህም ማለት በበጀቱ ውስጥ የቻይና፣ ምዕራባዊያን ሀገሮች እንዲሁም የምዕራብ ሀገሮች ይዞታ የሚባሉት አለም አቀፍ ባንኮች እጅ በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ እንደምታውቁት መንግሰት ለ2007 ዓመተ ምህረት ያቀረበው በጀት ብር 178.6 ቢሊዮን ነው፡፡ ዘጠኝ ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ ማለት ነው፡፡ መደበኛው ወጪ እና የክልሎች ድጋፍ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የሚሸፈን ሲሆን ዋና ዋና የካፒታል በጀት ደግሞ ከመደበኛ ወጪ እና ክልሎች ድጋፍ ከሚተርፈው አነሰተኛ የሀገር ውስጥ ገቢ እና ለበጀት ጉድለት ለመሸፈን ከታሰበው ከሀገር ውስጥ ባንኮች ብድር ይሸፈናል ተብሎ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከአጠቃላይ በጀቱ 19.2 በመቶ ከእርዳታና ብድር ይሸፈናል በዝርዝር ሲታይ ግን የመደበኛ በጀቱ 21.8 ከመቶ፣ የካፒታል በጀቱ ደግሞ 36.5 ከመቶ የሚሸፈነው ከብድርና እርዳታ ነው፡፡

ስንት ሰው እንደሚያስታውስ ባላውቅም የቀድሞ አዲስ ጉዳይ ጋዜጣ (ሁሌም ጋዜጣ ሳስብ የሚናፍቀኝ) በአንድ ወቅት የቀረበን በጀት ይህ በጀት ኢትዮጵያዊ በጀት ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አንሰቶ ነበር፡፡ የበጀትን ዜግነት የጠየቀበት ገፊ ምክንያት በዚያን ሰሞን መወያያ፤ በአሁኑ ጊዜ ጠርናፊ ህግ የሆነውን የሲቪል ማህበራት ህግ ነበር፡፡ ይህ አፋኝ ህግ ማነኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሰቪል ማህበር በጀቱ ከአስር በመቶ በላይ ከውጭ ከሆነ ኢትዮጵያዊ አይደለም ነው የሚለው፡፡ አሁን በሀገራችን የሚንቀሳቀሱት ብዙዎች መንግሰታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተመዘገቡት በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን “ረዚደንት” በሚል ቅፅል ነው፡፡ አዲስ ጉዳይ ጋዜጣ ይህን በጠየቀበት ወቅት የሀገሪቱ በጀት ከ40 በመቶ በላይ ከውጭ እርዳታ ሰለነበር ይህ መንግሰት ይህን ያህል ከውጭ የሚያገኝ ከሆነ ኢትዮጵያዊ አይደለም የሚል መከራከሪያ ይዞ ወጥቶ ነበር፡፡ ይህን ሰፋ አድርገው በመተርጎም አንድ አንድ ሰዎች የገቢ ምንጭ ዜግነት የሚወስን ከሆነ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ከውጭ ከሚኖሩ ዘመዶቻቸው በሚላክላቸው ገንዘብ የሚተዳደሩ ስለሆነ ዜግነታቸው ኢትዮጵያዊ መሆን የለበትም ብለው ነበር፡፡ ስላቅ መሆኑ ነው፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ የሚልኩላቸው ዘመዶቻቸው ዜግነት ያልቀየሩ በመኖሪያ ፍቃድ (ረዚደንት) የሚኖሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡

የሰዎችን ወይም የድርጅቶችን ዜግነት ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ ለማድረግ የገቢ ምንጭ መስፈርት መሆን የለበትም የሚለውን መከራከሪያ መንግሰት በዋዛ ያለፈው እንዳይመስላችሁ፡፡ መፍትሔ ብሎ የያዘው በተቻለ መጠን መንግሰት በጀቱን በመከፋፈል እና የተወሰኑት ወደ ጎን በማድረግ የብድርና የእርዳታ ገንዘቡ እንዳይታይ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም ነው መንግሰት ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ከሚፈስባቸው የመሰረተ ልማቶች ውስጥ ዋና ዋና የሆኑትን ለምሳሌ እነ ቴሌ፣ መብራት ሀይል፣ ባቡር፣ የመሳሰሉት በሪፖርት ውሰጥ በስፋት እንደሰኬት ተካተው በበጀት ውስጥ ግን አይታዩም፡፡ ሉሎች ፋብሪካዎች ለምሳሌ ስኳር ፋብሪካ፣ ማዳበሪያ ፋብሪካ የመሳሰሉት ትልልቅ የመንግሰት ፕሮጀክቶቸ በበጀት ውስጥ የሉም፡፡ እነዚህ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ የፈሰሰላቸው የመንግሰት ኢንቨስትመንቶች ከበጀት ውሰጥ እንዲወጡ የተደረጉት ደግሞ ብዙዎች በብድር የሚሰሩ ናቸው፡፡ የእነዚህ ፕሮጀክቶች የብድር ሂሣብ በበጀት ውስጥ ቢደመር የመንግሰትን በጀት ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ ላይሆን ነው ማለት ነው፡፡ ለነገሩ በሲቪል ማህህበራት ትርጉም እነዚህ ሁሉ ተቀንሰው አሁን የቀረበው የመነግሰት በጀት ኢትዮጵያዊ በሚያደርገው ደረጃ ላይ አይለም፡፡ ምክንያቱም ከአጠቃላይ በጀቱ 19.2 በመቶ ከውጭ ብድርና እርዳታ የሚገኝ ስለሆነ ማለት ነው፡፡

መንግስት በበጀት ውስጥ ያካተታቸው በእርዳታና ብድር የተገኙ አብዘኞቹ የካፒታል ወጪዎች ለኤኮኖሚ ሴክተር መንገድ፣ ግብርና እና ውሃ ሲሆን፤ እርዳታው ደግሞ ለጤናው ሴክተር የተመደበ ነው፡፡ የእነዚህ ገንዘቦች ዋናኛ ምንጮች ደግሞ የኒዎ ሊብራል አራማጆች የሚባሉት መንግሰታት እና የእነዚሁ መንግሰታት ይዞታ ናቸው የሚባሉት ባንኮች የሰጧቸው ብድሮች ናቸው፡፡ እነዚህ መንግሰታት እና በቁጥጥራቸው ስር ያሉት የፋይናንስ ተቋማት ኢትዮጵያዊያን ጤናቸው እንዲጠበቅ የተሻለ መንገድ እንዲኖረን፣ ምርታማ ግብርና እንዲሁም ንፁህ ውሃ እንዲኖረን ዕርዳታና ብድር እየሰጡን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ብጥብጥ እንዲነሳ የቀለም አብዮት ይደግፋሉ ብሎ ስጋት ውስጥ መውደቅ አይቃረንም ወይ? ይህ በእውነት የአብዮታዊ ዲሚክራሲ ወይም የልማታዊ መንግሰት ቅዠት ይመስለኛል፡፡

በጣም የሚያስገርመው ደግሞ በዋነኝነት ከፍተኛ እርዳታ የሚሰጡን መንግሰታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በኩል አድርገው በቀለም አብዮት ሊያጠፉን ነው የሚባሉት የኒዎ ሊብራል አራማጅ ተብለው የተፈረጁት ሀገሮች መንግሰታት ናቸው፡፡ ከነዚህ ውሰጥ ቻይና እንደ መንግስት የምትሰጠን እርዳታ በሀገር ውስጥ ከውጭ ሀገር ዜጎች ምዝገባና የስራ ፈቃደ ከምናገኛው ያንሳል፡፡ ከሌሎቹ ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ደግሞ ከአንድ መቶኛ ያነሰ ነው፡፡ ቻይና ሀገራችን በበጀት ውስጥ ከተካተተው ብድር ከ59 በመቶ በላይ ሰጥታናለች፡፡ ይህ ቻይና የሰጠችን ብድር ብዙ ስለሆነ ሳይሆን መንግሰታት ለኢትዮጵያ የሰጡት ብድር እጅግ ዝቅተኛ ከመሆኑ የመጣ ከፍተኛ የመቶኛ ድርሻ ነው፡፡ ቻይና በጀት ውስጥ ባልገባው ብድር ከፍተኛ አበዳሪያችን ነች፡፡ የቻይና ብድር በዋነኝነት በበጀት ውስጥ ባለተካተቱት ከፍተኛ የመንግሰት የመሰረተ ልማቶች እና የኤኮኖሚ ሴክተሮች ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ከበጀት እንዲወጣ የተደረገውን የቴሌን ማስፋፊያ ብቻ ብንወሰድ ወደ 32 ቢሊዮን ብር ወይም 1.6 ቢሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር በ2007 በጀት ተብሎ የተያዘውን 18 ከመቶ ይሆናል፡፡ ይህ ገንዘብ በጀት ውስጥ ቢታይ እና የመንግሰትን የዜግነት መስፈርት ብንጠቀም መንግሰት ኢትዮጵያዊ ነው ለማለት ይቻላል ወይ? በጀት የመንግሰትን አቅም የሚያሳይ መለኪያ ነው በሚለው ልማዳዊ መለኪያ ለመጠቀም ለሚፈልግ ለቀጣይ ዓመት የቀረበው በጀት ትክክለኛውን የመንግስት ጡንቻ የሚያሳይ ነው ብለን ለመውሰድ እንቸገራለን፡፡

የኢኮኖሚና ፋይናንስ ሚኒሰትሩ አቶ ሶፊያ አህመድ በዚህ ጉዳይ በተደጋጋሚ በግንባር ቀደምነት የሚያነሱት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዕዝ ኢኮኖሚ በሚባለው በደርግም ጊዜ ቢሆን ሪፖርቱን በይፋ ያቀርባል አቶ ሶፊያ ግን ይህን እንዲያደርግ ያለበትን ዓለማ አቀፋዊ ጫና የምንረዳ አይመስላቸውም፡፡ ያለበለዚያ ቦይንግ መግዣ ገንዘብ ሊገኝ እንደማይችል ግልፅ ነው፡፡ አሁን እኛ የግልፅነት ችግር አለባቸው እያልን ያለነው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪን የሚባለው አስማተኛ ድርጅት የሚሰራው ሰራ የሚያገኘው ገቢና ወጪው በግልፅ አይታወቅም ነው፡፡ እጅግ ብዙ ሀብት ፈሶበትም የሚያመጣው ትርፍ ተመጣጣኝ አይደለም እያልን ነው፡፡ በቅርቡ ከመንግሰት ድርጅቶች ይገዛው የነበረውን የወዳደቁ ብረቶች ግዢ እንዲያቆም መታዘዙ ይታወቃል፡፡ ለምን? የፀረ ሙስና እና ሰነምግባር ኮሚሸን እነዚህ ተቋማት ለምዝበራ እንደሆነ ሪፖርት አቅርቧል፡፡ ለነገሩ ይህ ድርጅት ተጠሪነቱም ለመንግሰት የልማት ድርጅት አይደለም፡፡ ሌሎቹም ኮርፖሬሽኖች ለምሳሌ የሰኳር ኮርፖሬሽን ስር ነው የሚባለው ተንዳሆ የሰኳር ፕሮጀክት ያለበትን ጉድ የማያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡ በጀት ውስጥ የገባውን የመከላከያ በጀት ስንመለከት ደግሞ በየሳምንቱ እሁድ በሚያቀርበው የቴሌቪዥን ፕሮግራ በነፃ ገበያ ሰርዓት እየተወዳደረ መነገዱን ቢነግረንም፡፡ በግልፅና በሰውር የሚሰራቸው የገቢ ማስገኛ ገንዘቦች እንዳሉት እየታወቀ ከውስጥ ገቢ የሚባል አንድም የገቢ ርዕስ በጀቱ ላይ አይታይም፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ የመከላከያ በጀት ይህ ብቻ ነው ብሎ ለመውሰድ አይቻልም፡፡ የመንግሰት ጡንቻ በመከላከያ በኩል ከዚህ እንደሚበልጥ ለማወቅ ደግሞ ልዩ እውቀት አይጠይቅም፡፡ ለዚህ ነው የመንግሰትን ትክክለኛ ቁመና የሚያሳይ በጀት አይደለም የምንለው፡፡

እነዚህ እርዳታ እየሰጡን ብድር የማይሰጡን መንግሰታት ምክንያታቸው ምንድነው? ብሎ መጠየቅም ተገቢ ይመሰለኛል፡፡ በኒዮሊብራል አሰተሳሰብ ተፈርጀው ሀገራችን ላይ የቀለም አብዮት ሊያመጡ ያሴራሉ የሚባሉት ሀገራት በዋና ዋና የንግድ እና ኢንቨስትምነት ውስጥ እጃቸውን ለማስገባት ወደኋላ ያሉት ለምንድነው? በተቃራኒው ደግሞ ቻይና በእነዚህ ወሳኝ የኤኮኖሚና የንግድ ኢንቨስትመንት ውስጥ እጇን በሰፊው የምትዘረጋው ለምንድነው? ብሎ መጠየቅ እና መልስ መሻት ግድ ይላል፡፡ በእኔ እምነት የምዕራባዊያን መንግሰታት በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ መስኮች ውስጥ ለመሳተፍ ውሳኔ የሚሰጡት መንግሰታት ሳይሆኑ በየሀገሮቻቸው ያሉት የግል ባለሀብቶች ናቸው፡፡ የመንግሰታት ድርሻ ለባለሀብቶች ትክክለኛ መረጃ እንዲደርሳቸው ማድረግ እና ተገቢውን ከለላ መስጠት ነው፡፡ የግል ባለሀብቶች ደግሞ መረጃ የሚያገኙት ከኢቲቪ አይደለም፡፡ ለያየ መልኩ በሀገራችን ያለውን ሁኔታ አብጠርጥረው ያውቁታል፡፡ እንደ ምሳሌ በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የተከሰተው ዓይነት ብሔርን መሰረት ያደረገ ብጥብጥ ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ አንድ አንዶች እንደሚያስቡት በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ያሉ ከተሞች የተቀናጀ ማሰትር ፕላን ዝግጅት ነው ብለው አይወስዱትም፡፡ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችና የሰጋት ደረጃ የሚተነትኑ ድርጅቶች የሚያወጧቸው ሪፖርቶች ትርጉማቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ በሀገሪቱ ውሰጥ ያለው የዲሞክራሲያዊ ሰርዓት በተለይም በየምርጫ ወቀት የሚፈጠሩ ሰጋቶች፤ መንግሰት የሚያወጣቸው አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች ተገማችነት፤ በአጠቃላይ ለኢንቨስትመንት ያለው ምቹ ሁኔታ ወሳኝ ግብዓቶች ናቸው፡፡ ዝም ብሎ በኢቲቪ የሚለፈፍ የገፅታ ግንባታ ፕሮፓጋንዳ ተጠቅመው የኢንቨስትምነት ውሳኔ አይሰጡም፡፡

በተቃራኒው የቻይና መንግሰት በከፍተኛ ደረጃ አፍሪካን ለመቆጣጠር ባለው ፍላጎት መነሻ እንዲሁም ውሳኔ የሚሰጡት የግል ባለሀብቶች ሳይሆን የቻይና መንግሰት በመሆኑ ውሳኔዎች በአብዛኛው ኤኮኖሚያዊ አዋጭነት ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ ጭምር ናቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቻይና በዓለም ላይ ከፍተኛ ብድር ሰጪ ሀገር ነች፡፡ ለአማሪካ ጭምር፡፡ በቻይና የግል ሴክተሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስት ለማድረግ ገና አልደረሱም፡፡ ቻይና እንደ ሀገር ያላትን ከፍተኛ ቁጠባ በዓለም ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እየተጠቀመችበት ነው፡፡ ቻይና በሙሉ በሚባል ደረጃ የምትሰጠንን ብድር የሚጠቀሙበት የቻይና ኩባንያዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ኩባንያዎች ያለውን ስጋት በሚያካክስ ደረጃ ትርፋቸውን በአጭር ጊዜ ለማግኘት ይገባሉ በአሁኑ ሰዓት ቴሌን የወሰዱት ሁለት የቻይና የመንግስ ኩባንያዎች ናቸው፡፡ በተለያየ ስም የሚሰሩ፡፡ ቻይና የምታስገርመው እነዚህ የመንግሰት ኩባንያዎች ጉቦ የመሰጠት ጭምር አቅም አላቸው፡፡

እንደ ማጠቃለያ ለኢትዮጵያ የተበጀተው በጀት ብር 178.6 ቢሊዮን በጀት እንደ ሀገር ሲታይ አጅግ ዝቅተኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ 90 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርባት ከመሆኗ አንፃር እና በቅርቡ ደግሞ ዓመታዊ የነብስ ወከፍ ገቢያችን ብር 11 ሺ (550 የአሜሪካዶላር) ደርሶዋል ከተባልን ይህ በጀት ከእያንዳንዱ ሰው በወር የገቢውን 1.5 ከመቶ መዋጮ ሊሸፍነው የሚችለው ነው፡፡

ቸር ይግጠመን

አንድነት ፓርቲ በአዋሳ ሊያደርገው የነበረው ሰልፍ አመራሮችንና አባላትን በማሰር ከተማዋን በፀጥታ ኃይሎች በመውረር ተደናቀፈ

June22/2014
በዛሬው ዕለት በአዋሳ ከተማ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሀዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አባላት ከሐሙስ ዕለት ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ ከ30 በላይ በፖሊስ የታሰሩ ሲሆን የሲአን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ላንቃሞ ለምን ይታሰራሉ ብለው በመጠየቃቸው እሳቸውንም አስረው ከምሽቱ 3፡30 ለቀዋቸዋል፡፡ በቅስቀሳው ወቅት ወረቀቶች የተበተኑ በመሆኑ ህዝብ በነቂስ ሊወጣ እንደሚችል ስጋት ያደረባቸው የደህዴን ካድሬዎች ትላንት ማታ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ተጨማሪ 7 የአንድነት የሀዋሳ አመራሮችና አባሎች በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ የደቡብ ክልል የደህዴን ካድሬዎች ከተለቀቁ ነገ ሰልፉን ከማድረግ ወደኋላ አይሉም በሚል ለሁለት ተከፍለው ሲሟገቱ ማምሸታቸውንና አቶ መንድሙ ወታንጎ የተባሉት የደህንነት ኃላፊ መፈታት የለባቸውም መፍታት እንኳን ካለብን የሰልፉ ሰዓት ካለፈ በኋላ ነው በማለታቸው በእስር ቤት እንዲያድሩ መወሰኑና በዛሬውም ዕለት የሀዋሳ ከተማ በፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥበቃ ሥር መሆኗን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገልፀዋል፡፡
ሳም ቮድ ሶን's photo.
ሳም ቮድ ሶን's photo.

ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ዘርፈው ጠፉ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ

June 22/2014
ከተጠርጣሪዎቹ ሁለቱ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ናቸው
የውጭ ገንዘቦችን መደበኛ ባልሆነ ግብይት ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢ የሚዘረዝሩ ሰዎችን፣ አንድ መቶ ሺሕ ዶላር እንዳላቸው በመግለጽ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ላይ ዘርፈው ጠፍተዋል በሚል የተጠረጠሩ ስድስት ግለሰቦች፣ ድርጊቱን ከፈጸሙ ከግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. በኋላ ባሉት አጭር ቀናት ውስጥ መያዛቸው ታወቀ፡፡ 
ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ሁለቱ የፌዴራል ፖሊስ አባላት የሆኑት የአድማ በታኝ ተሽከርካሪ ሾፌሮች ኢንስፔክተር ዘለቀ አየለና ዋና ሳጅን ቀለብ ባዜ ሲባሉ፣ ሌሎቹ በተለያዩ የሥራ መስኮች የተሰማሩ መሆናቸው የተገለጸው ተጠርጣሪዎች መሠረት ወዳጄ፣ ትዕዛዙ መለስ፣ ብርሃኑ ዳምጠውና ወንዴ ማኔ እንደሚባሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 
ተጠርጣሪዎቹ ድርጊቱን የፈጸሙት ግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. መሆኑን፣ የድርጊቱ አፈጻጸም ምንጮች ለሪፖርተር ሲያስረዱ፣ አንድ ወጣት በተደጋጋሚ ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢ ካሉ የውጭ ገንዘብ መንዛሪዎች ዘንድ በመሄድ የተለያዩ ገንዘቦችን እየመነዘረ ወዳጅነት ይመሠርታል፡፡ 
ወጣቱ ሌሎች ደንበኞችንም እየላከላቸው ከመንዛሪዎቹ ጋር ወዳጅነቱን በማጥበቁ ምክንያት በፈጠረው ቀረቤታ፣ በተጠቀሰው ዕለት አንድ ግለሰብ የአንድ መቶ ሺሕ ዶላር ምንዛሪ እንደሚፈልግ ይነግራቸዋል፡፡ 
በደህና ቀን ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት መንዛሪዎቹ ከጓደኞቻቸውና ከራሳቸው በማሳሰብ 2.2 ሚሊዮን ብር በኰንትራት ላዳ ታክሲ ይዘው ወደ ሲኤምሲ ማምራታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ቡና ንግድ ድርጅትን፣ ዲሚትሪ መጋረጃ ሥራንና ጃክሮስን ሲያልፉ መጀመሪያ ወደ መንዛሪዎቹ የመጣው ወጣት ስልክ በመደወል ከሌላ ሰው ጋር ከተነጋገረ በኋላ፣ ትንሽ እንደሄዱ አንድ በእጁ ጥቁር ቦርሳ የያዘ ሰው ዘንድ ሲደርሱ ያቆሙለትና ወጣቱ ወርዶ እሱ ይገባል፡፡
ጥርጣሬ የገባቸው መንዛሪዎች፣ ‹‹የያዝከው ገንዘብ የታለ? እኛ የምንሰጥህንስ ገንዘብ በምን ትይዘዋለህ?›› በማለት እየጠየቁት ሲጓዙ፣ ከፊት ለፊታቸው አንድ የፌዴራል ፖሊስ ተሽከርካሪ ድንገት መጥቶ ይቆምና የደንብ ልብስ የለበሱ ሁለት የፌዴራል ፖሊስ አባላትና አራት ሲቪል የለበሱ ግለሰቦች በመውረድ ላዳ ታክሲው ላይ መሣሪያ ይደግኑበታል፡፡ 
በላዳው ተሳፍረው የነበሩትን በሙሉ በማጉላላትና በሰደፍ በመምታት ወደ ፌዴራል ፖሊስ ተሽከርካሪ በማስገባት ‹‹በሕገወጥ ድርጊት ተጠርጥራችኋል›› ብለው ታክሲውን ‹‹ተከተለን›› በማለት መንገድ ሲጀምሩ፣ የታክሲው አሽከርካሪ ወደኋላ በመመለስ ማምለጡን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 
መንገድ ላይ የተሳፈረውና ጥቁር ቦርሳ ይዞ ነበር የተባለው ግለሰብ፣ ‹‹እኔ የመጣሁት ከእስራኤል ነው፡፡ አሁንም ለሕክምና ልመለስ ነው፡፡ ይኼንን ቦርሳ ውሰዱትና እኔን ተውኝ፤›› ሲላቸው መንገድ ላይ አውርደውት 2.2 ሚሊዮን ብር የያዙትን መንዛሪዎች ይዘዋቸው መሄዳቸውንም ጠቁመዋል፡፡ 
ገንዘባቸውን ያስረከቡዋቸውን መንዛሪዎች ወደ አንድ ጫካ ውስጥ በመውሰድ በሆዳቸው እንዲተኙ ካደረጉ በኋላ፣ ተጠርጣሪዎቹ በያዙት ተሽከርካሪ ወደኋላ በመመለስ በተለምዶ ወሰን ግሮሰሪ በሚባለው አካባቢ ገንዘቡን ተከፋፍለው ለጥቂት ቀናት ተሰውረው መክረማቸውን ምንጮች ተናግረዋል፡፡ 2.2 ሚሊዮን ብር የተዘረፉት ግለሰቦች ለፖሊስ ሪፖርት በማድረጋቸው፣ ፖሊስ ባደረገው ከፍተኛ ክትትል በጥቂት ቀናት ውስጥ ሁሉም በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ መሆናቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡            

Saturday, June 21, 2014

ድርብ አኃዝ ዕድገት ወይስ ድርብ ድህነት?

June 21/2014

poor1


በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ልማት ትምህርት ክፍል ሥር የኢኮኖሚ ጥናት የሚያካሂደው የኦክስፎርድ የድህነትና የሰብዕ ልማት ማዕከል (The Oxford Poverty and Human Development Initiative (OPHI)) ሰሞኑን ባወጣው የ2014 የጥናት መረጃ ደሃ ከሚባሉት አገራት ዝርዝር ኢትዮጵያ ከመጨረሻው ሁለተኛ መሆኗን ገለጸ፡፡ የጥናቱ ዘገባ ኢህአዴግ በየጊዜው ከሚያቀርበው የዕድገት ስሌት ጋር በግልጽ የሚጋጭ መሆኑ ተነገረ፡፡
በዓለማችን በሚገኙ 108 በማደግ ላይ ባሉ አገራት በየጊዜው ጥናት የሚያካሂደው ማዕከል ጥናቱን በሚያካሂድበት ጊዜ 10 መለኪያዎችን እንደ ግብዓት እንደሚጠቀም ይናገራል፡፡ እነዚህም በሦስት ዘርፎች የተጠቃለሉ ናቸው – ትምህርት፣ ጤና እና የኑሮ ሁኔታ፡፡ በተለይ በኑሮ ሁኔታ ሥር ኤሌክትሪክ፣ ጽዳት፣ የሚጠጣ ውሃ፣ የንብረት ባለቤትነት፣ ወዘተ በግብዓትነት ተወስደዋል፡፡
በዚህ ዓይነት እኤአ ከ2002 እስከ 2011 ድረስ ያለውን መረጃ በማጠናቀር በወጣው ዘገባ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ ከ100 ሰዎች መካከል 87ቱ ድሃ ተብለው የሚጠሩ ሲሆን 58ቱ ሰዎች ግን መናጢ ደሃ ተብለው የሚጠሩ መሆናቸውን ይናገራል፡፡ ድህነቱ በገጠር እጅግ የከፋ እንደሆነ በመጠቆም ከ100 ሰዎች ውስጥ 96ቱ ደሃዎች እንደሆኑ፤ በከተሞች አካባቢ ግን ከ100 ሰዎች መካከል 46ቱ ደሃ ተብለው የሚጠሩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአጠቃላይ የአገሪቷ ክፍሎች ከ100 ሰዎች መካከል 31ዱ በቀን ከ20ብር በታች በሚገኝ ገቢ እንደሚኖሩ ጠቁሟል፡፡
ድህነቱ የከፋባቸው “ክልሎች” ብዙም ልዩነት እንደሌላቸው የሚያሳየው የጥናቱ ዘገባ ከሁሉም ግን ሶማሊ በደሃነት ቀዳሚ ነው፡፡ በጥቂት ነጥብ ልዩነት ኦሮሚያ፣ አፋር፣ አማራ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ በቅደም ተከተል ተቀምጠዋል፡፡ በእነዚህ አምስት ክልሎች ከ100 ሰዎች ውስጥ 90 እና ከዚያ በላይ የሚሆኑት ደሆች መሆናቸው በጥናቱ ተዘርዝሯል፡፡
የ108 በማደግ ላይ ያሉ አገራት የድህነት መለኪያ ዝርዝር የያዘው ዘገባ በግልጽ እንደሚያሳየው የመጨረሻዋ ደሃ አገር ኒጀር ስትሆን ከዚያ ቀጥላ ኢትዮጵያ ነች፡፡ እስከ 10 ባሉት የመጨረሻ አገራት ውስጥ ማሊ፣ ቡርኪናፋሶ፣ ላይቤሪያ፣ ጊኒ፣ ሶማሊያ፣ ቡሩንዲ፣ መካከለኛው አፍሪካ እና ጊኒ ቢሳው ከ3 – 10 ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡
በየጊዜው የኢትዮጵያ ዕድገት “ድርብ አኻዝ” እንደሆነ ለሚናገረው ኢህአዴግ ይህ ዓይነቱ ዓለምአቀፋዊ ዘገባ የከፋ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በአስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ይነገራል፡፡ በተለይ “ምርጫ” እየቀረበ ባለበት ወቅት ይህ ዓይነቱ በታዋቂ ዩኒቨርሲቲ የሚመራ ማዕከል የወጣ የጥናት ዘገባ የሚያመጣው ተጽዕኖ ከፍባለ ሁኔታ ለመጠቀም ተቃዋሚ ፓርቲዎች በቂውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ፡፡ ኢህአዴግ የማይስማማውን ማንኛውንም ዓይነት ዘገባ “የልማት ጸሮች” ያወጡት፣ “የአሸባሪዎች እጅ ያለበት”፣ “የኒዎ ሊበራል አቀንቃኞች ዘገባ”፣ “የኪራይ ሰብሳቢዎች ምኞት”፣ ወዘተ እያለ እንደሚያጥላላውና እንደሁኔታው የተለመደውን “ማጣፊያ” በኢቲቪ ወይም ሌሎች ድቃይ “የሚዲያ” ክፍሎች ላይ እንደሚያቀርብ ጎልጉል አስተያየት የጠየቃቸው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ተቋም ምሁር ገልጸዋል፡፡
ይህ የኦክስፎርድ ማዕከል ይህንን ጨምሮ በየጊዜው የሚያቀርባቸው የጥናትና ምርምር ውጤቶች በበርካታ ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች፣ በፖሊሲ አውጪዎች እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና ሌሎች ተመሳሳይ ተቋማት ጥቅም ላይ እንደሚያውሉት በድረገጹ ላይ አስታውቋል፡፡
የጥናቱን ዘገባ በPDF ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ በቀጥታ ከማዕከሉ ድረገጽ ላይ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

Friday, June 20, 2014

በጎንደር የአንድነት ፓርቲ አባል ለአቤቱታ ባህርዳር ሄዶ የደረሰበት አልታወቀም

June 20/2014

Photo: በጎንደር የአንድነት ፓርቲ አባል ለአቤቱታ ባህርዳር ሄዶ የደረሰበት አልታወቀም
---------------------------------------------------------
በሰሜን ጎንደር ምዕ/አርማጨሆ ወረዳ አብርሃጅራ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የወረዳ የፋይናንስና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ  የሆነው አቶ ደስታው ተገኝ ከአ.አ ዩኒቨርስቲ በ2000 ዓ.ም በቢዝነስ ኢዱኬሽን የመጀመሪያ ዲግሪ ካገኘ በኋላ በሐረር፣ በጎንደር ያስተማረ ሲሆን  በም/አርማጨሆ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት የመማር ማስተማር ጉዳይ ፈፃሚ ሆኖ ከ4 ዓመት በላይ አገልግሏል፡፡ በት/ቢሮው ለማስትሬት ትምህርት ዕድል ብቸኛ ተወዳዳሪ የነበረ ቢሆንም ለ3 ዓመታት ተከልክሏል፡፡  በትምህርት ቤቱ በሚደረጉ የመማር ማስተማር ሂደቶችን የሚፈጸሙ ስህተቶችን  በስብሰባ በመግለጹ ኃላፊውን ሰድበሃል፤ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ቁጥራቸው 4 ሆኖ ሳለ 40 እና 80 እየተባለ ሪፖርት ሲደረግ በውሸት መመራት መቆም አለበት በማለቱ የአንድ ወር ደሞዝ ቅጣትና  ከነበረው ደሞዝ 2249 ወደ 1400 ብር ዝቅ ብሎ ለ 1 ዓመት ከ6 ወር እንዲሰራ የወረዳው ት/ቢሮ ጽ/ቤት ወስኖበታል፡፡ ት/ቢሮው ያለአግባብ የወሰነበት ውሳኔ ተገቢ ባለመሆኑ  ለአቤቱታ ወደ ባህር ዳር ሲቪል ሰርቪስ ሄዶ ሲቪል ሰርቪሱ ለት/ቢሮው ግንቦት 5 እና በድጋሚ ግንቦት 15 ደብዳቤ ጽፎ እንዲቀርቡ ቢልም ለመቅረብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ለመጨረሻ ጊዜ ለግንቦት 29 እንዲቀርቡ የተጻፈውን ደብዳቤ አንቀበልም በማለታቸው በፖሊስ ሳጅን ፍቃዱ አማካይነት ደብዳቤውን ተቀበሉ፡፡ ምዕ/አርማጨሆ አብርሃ ጅራ ት/ቢሮ ጽ/ቤት መልስ ሰጪ በዕለቱ በቀጠሮ ቢገኙም አቤቱታ አቅራቢው አቶ ደስታው ተገኝ አልተገኘም፡፡ ከግንቦት 29,2006 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ አቶ ደስታው ተገኝ የእጅ ስልኩ አይሰራም ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ለ14 ቀን  ያለበትን  ሁኔታ ባለማወቃቸው በድንጋጤ ላይ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል እንደገለጹት በወረዳው ያሉ የብአዴን አመራሮች “በመለስ ተቃዋሚን ዜሮ ማድረስ” በሚል መፈክር የተቃዋሚ አባሎች ላይ የሚደረግ እስርና እንግልት እንዳለና አቶ ደስታው ተገኝም የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ለአቤቱታ በሄደበት ሳይታፈን እንዳልቀረ  ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡በሰሜን ጎንደር ምዕ/አርማጨሆ ወረዳ አብርሃጅራ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የወረዳ የፋይናንስና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ የሆነው አቶ ደስታው ተገኝ ከአ.አ ዩኒቨርስቲ በ2000 ዓ.ም በቢዝነስ ኢዱኬሽን የመጀመሪያ ዲግሪ ካገኘ በኋላ በሐረር፣ በጎንደር ያስተማረ ሲሆን በም/አርማጨሆ ትምህርት ቢሮ ጽ/ቤት የመማር ማስተማር ጉዳይ ፈፃሚ ሆኖ ከ4 ዓመት በላይ አገልግሏል፡፡ በት/ቢሮው ለማስትሬት ትምህርት ዕድል ብቸኛ ተወዳዳሪ የነበረ ቢሆንም ለ3 ዓመታት ተከልክሏል፡፡ በትምህርት ቤቱ በሚደረጉ የመማር ማስተማር ሂደቶችን የሚፈጸሙ ስህተቶችን በስብሰባ በመግለጹ ኃላፊውን ሰድበሃል፤ የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ቁጥራቸው 4 ሆኖ ሳለ 40 እና 80 እየተባለ ሪፖርት ሲደረግ በውሸት መመራት መቆም አለበት በማለቱ የአንድ ወር ደሞዝ ቅጣትና ከነበረው ደሞዝ 2249 ወደ 1400 ብር ዝቅ ብሎ ለ 1 ዓመት ከ6 ወር እንዲሰራ የወረዳው ት/ቢሮ ጽ/ቤት ወስኖበታል፡፡ ት/ቢሮው ያለአግባብ የወሰነበት ውሳኔ ተገቢ ባለመሆኑ ለአቤቱታ ወደ ባህር ዳር ሲቪል ሰርቪስ ሄዶ ሲቪል ሰርቪሱ ለት/ቢሮው ግንቦት 5 እና በድጋሚ ግንቦት 15 ደብዳቤ ጽፎ እንዲቀርቡ ቢልም ለመቅረብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ለመጨረሻ ጊዜ ለግንቦት 29 እንዲቀርቡ የተጻፈውን ደብዳቤ አንቀበልም በማለታቸው በፖሊስ ሳጅን ፍቃዱ አማካይነት ደብዳቤውን ተቀበሉ፡፡ ምዕ/አርማጨሆ አብርሃ ጅራ ት/ቢሮ ጽ/ቤት መልስ ሰጪ በዕለቱ በቀጠሮ ቢገኙም አቤቱታ አቅራቢው አቶ ደስታው ተገኝ አልተገኘም፡፡ ከግንቦት 29,2006 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን ድረስ አቶ ደስታው ተገኝ የእጅ ስልኩ አይሰራም ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ለ14 ቀን ያለበትን ሁኔታ ባለማወቃቸው በድንጋጤ ላይ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል እንደገለጹት በወረዳው ያሉ የብአዴን አመራሮች “በመለስ ተቃዋሚን ዜሮ ማድረስ” በሚል መፈክር የተቃዋሚ አባሎች ላይ የሚደረግ እስርና እንግልት እንዳለና አቶ ደስታው ተገኝም የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ለአቤቱታ በሄደበት ሳይታፈን እንዳልቀረ ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

የአቶሬድዋንሁሴንየ”Corporal Interest” ትንታኔ

June 20/2014
በኢህአዲግ ውስጥ ካሉት ቁንጮ ባለስልጣናት መካካል በሞጋችነታችው እና የተሳካለት የቃላት መደርደር ችሎታቸው አቶ ሬድዋን ሁሴንን የሚተካከላቸው አለ ብዬ አላምንም:: እናም በዚያን ሰሞን የአውራምባው ጋዜጣ ባለቤት አቶ ዳዊት ከበደ እኝሁን ባለስልጣን ቃለ መጠይቅ ሲያደርግላቸው የተለመደውን ባዶና ካድሬያውዊ መልሳቸውን አፈሰሱት:: ታዲያን የእኔን ቀልብ የሳበው ነገር ደጋግመው የጠቀሱት ”Corporal Interest” ብለው የደነቀሩት ቃላትና ስለ ምንነቱም የእኔ መንግስት ጭብጥ ግንዛቤ ነው ብለው ያሉት ነገር ነበር:: አዎን ቃላቱ ልክ እዚህ እንደምታነቡት ነው ጥቅም ላይ የዋለው። ለእንደኔ ብጤው እንግሊዝኛ እንደ ቁምጣ ለሚያጥረው አንድ በቋንቋው ተክኛለሁ የሚል የዚህን ቃል ትርጉምና አጠቃቀም እስካላስረዳኝ ድረስ አባባሉ ሰውየው እንደተጠቀሙበት አይነት አጠቃቀም አንብቤም ሰምቼም ነበር ለማለት ድፍረቱ የለኝም። ትልቁ ትዝብት ያለው ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ እየገዛ ካለ መንግስት አፈ ቀላጤ አሳፋሪ ሊባሉ የሚችሉ የአቅም ማነስና የብስለት መታጣት መንፀባረቃቸው ላይ ነው። ለነገሩ በዚያች ሀገር ማፈር ከጠፋ ሰንበትበት ብሏል።ሌላው ቢቀር ቢሯቸውና የስልጣን ቦታቸው የሰጣቸው አጋጣሚና የተመቻቸ ዕድል ከጥቅም ላይ አውለው የራሳቸውን ግላዊና ቡድናዊ የዕውቀት አድማስ ማበልፀግ አለመቻላቸው ወይም አለመፈለጋቸው ዋነኛው አሳዛኝ ነገር ነው። በጣሙን የምንሽማቀቀው ደግሞ ይህን መሰሉ ክስተት ምሁር ነን ፣ ተምረናል ከሚሉ የመንግስቱ ባለሟሎች ጎራም ስናያ ነው።
በአንድ ወቅት በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የህግ ምሁሮች በአሜርካን የተወካዮች ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ዲሞክራሲና ተጠያቂነት እንዲኖር ሊደነግጉት ባሰቡት ሰነድ ላይ ሊተቹ ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ ሰነዱን የ”Human Right (watch)” ያቀረበው ነው ብሎ ንግግሩን ሲጀምር ብዙዎች ስል እሱ አፈር በገባሁ ብለው እንዳሉ አስታውሳለሁ። በምሁሩ ዘንድ “HR 2003” ከአሜርካን “House of Representatives “ የወጣ ሰነድ መሆኑን አጣርቶ ሳያውቅ ነው እንግዲህ ምሁራዌ ትችት ልስጥ ብሎ የተነሳው። እንዲም ሆኖ ዝርዝሩ ላይ ፍሬ ያለው ነገር ቢናገር ደህና ነበረ። ሰነዱ ዳግም ውጫሌን ሊያመጣብን ነው ፣ ቅብርጥሴ ሲል ነው የተደመጠው። በዚህ ዙሪያ አንድ በለን ካላችሁኝ በዚያኛው ሰሞን ስለ ፕሬስ ነጻነት ሲውያዩ አንዱ የምዕራቡን አለም አውቀዋለሁ የሚል የሚመስል ተከራካሬ በሙሉ ልብ ሲደሰኩረው የነበረውን ላካፍላችሁ። እንደ ሰውየው አባባል አሜርካን ኢራቅን እንድትወር ያደረጉት ጋዜጠኞችና የሚዲያ አባላት ናቸው።ይህን ሰው ጨምሮ በርካታ የኢህአዲግ ባለስልጣኖች ለንጽጽር ይረዳቸው ዘንድ የአሜርካንን ሚዲያ በተለይም “CNN” እና “FOX NEWS”ን እንደ ምሳሌ ሳያጣቅሱ ያለፉበትን ጊዜ አላስታውስም:: እነዚህ ሁለት ተቋማት ተቃራኒ የሚመስሉ ሃሳቦች ያናጸባርቃሉ ማለቱ ተገቢ ቢመስልም የኢህአዲጎቹ ችግር ግን የአሜርካን ሚዲያ ማለት ቆጥረው የሚጨርሱት፣ልክ በኪሳቸው እንዳለው እና እነሱ ብቻ እንደሚዘውሩት የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን አድርገው መውሰዳቸው ላይ ነው::
ስለ ቃላትና ሃሳብ አገላለጽ ግድፈት ይህን ያህል ካልን ከላይ የጠቀስናቸው አቶ ሬድዋን ሁሴን ለማሳተላለፍ ስለፈለጉት ፍሬ ነገር እናውራ። እኔ እንደገባኝ ሚንስቲሩ የሚያወሩት የነበረው የጊዜው የኢህአዲግ ነጠላ ዜማ ሆኖ ዳናኪራ የሚመታበት ጋዜጠኝም ይሁን ሌላ “በነውጥ ስርአቱን ሊያፈርስ” የሚነሳውን ቡድን ከውጪ ሃይሎች ጋር የማያያዝ ጨዋታ ነው።የሚገርመው ነገር ይህ የውጪ ሃይል የተባለው ከወደ አሜሪካን የሚመነጨው የ”Corporate Interest” ተደርጎ የመወሰዱ ፌዝ ነው:: ኢህአዲጎች በአጭሩ የሚሉት ከዩክሬኑ የቀለም አብዮት እስከ አረቡ ስፕሪግ የተደረገውን የለውጥ እንቅስቃሴ ከኋላ ሆነው የመሩት አሜሪካን ሃገር የሚገኙ ተቋማት ናቸው:: እንደ የአቶ ሬድዋን ሁሴን መንግስት እምነት የነዚህ ተቋማት ቀዳሚ ፍላጎት በሃገሮች ውስጥ እነሱ እንደሚሉት ዲሞክራሲ ለማምጣትና ሰባዓዊ መብቶችን ሊያከብሩ የሚችሉ ቡድኖች መንግስት እንዲሆኑ ለማስቻል ሳይሆን የገዛ ራሳቸውን የ”Corporate Interest” ለማሳጠበቅ ብቻ ነው። ያም ሆኖ ግን ጥረታቸው ሁሉ ሳይሳካ እንደቀረና ይልቁንም አብዮት የተደረገባቸው ሃገራት ወደ ከፋ ችግር ውስጥ እንደገቡ ነው ለማሳየት የሚሞከረው። ዞሮ ዞሮ ይህ የኢትዮጵያ መንግስት አመለካከት ከምን እንደመነጨ ማንም ሰው የሚያውቀው ነው። ኢህአዲጎችም በደንብ እንድናውቀው ነው የሚሹት::ለምን ቢባል የዞን ዘጠኝ አባላትን ወንጀለኛ ለማድረግ አዋጪ መስሎ የታያቸው ይህንኑ ውሃ የማይቋጥር ክርክራቸውን በህዝቡ ጭንቅላት ውስጥ ማስገባት ስለሆነ ይመስለኛል።ህዝቡ ይቀበለዋል አይቀበለውም ሌላ ጨዋታ ነው:: ባይቀበልስ ምን ያመጣል የሚለውም እንደዚሁ::
ይህን በመሰለው ህሳቤ ነበር አቶ ሬድዋን በቀጥታም ባይሆንም “Human Right Watch” ፣ “Freedom House” እና መሰሎቻቸው የዞን ዘጥኝ አባላትን በማስልጠንና በገንዘብ እየረዱ ነው የምትል ክስ ብጤ የሰነዘሩት:: ይህን የሚያደርጉት ደግሞ የራሳቸውን ርዮት አለም ለማስፋፋት ነው ብለዋል:: የዚህ እውነታማ እስከዛሬ ድረስ እንዴት እንዳልተገለጠላቸው ከገረሙኝ ነገሮች አንዱ ነው:: መጋፈጥ የነበረባቸው ይህ ጊዜ የፈተነውንና ብዙዎች የአለማችን ሃገሮች እሰየው ብለው የተቀበሉት ርዮት አለም ለኢትዮጵያ ይጠቅማል ወይም አይጠቅምም የሚለውን ክርክር ነበረ:: አይጠቅምም ብለው የሚሉበት አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ስለማይችሉ ይህቺን መሰሏን ክርክር ደፍረው አይነኳትም:: እረስተውት እንደሆነ ነው እንጂ የራሳችው ፓርቲ የአልባንያና የሌላም ሶሻሊዝም ዝባዝንኬ እርግፍ አርጎ ትቶ ነበር እኮ የምዕራቡን ርዮት አለም ተቀበልኩ ያለው:: እንዲያው ለመሆኑ ይህ ከውጪ ሊጫንብን ነው ከሚሉት ርዮት አለም የትኛው ይሆን ለሃገራችን የማይጠቅመው ወይም የሚጎዳው:: ዲሞክራሲ አስፍኑ ፣ የሰውን ልጅ እንደሰው በእኩልነት ተመልከቱት ብሎ ማለት ምኑ ላይ ይሆን የሚያስፈራው? ርዮት አለሙ ሲሰራጭ አብሮት ስርጭቱን የሚያቀላጥፍ ብዙ ገንዘብ ይሰጣል።ህይወት አትራፊው ስንዴማ ያለ ርዮት አለሙም ይመጣል:: አቶ ሬድዋን ዳር ዳሩን እያሉ የፎክሩትማ እንዳው በታሪካችን የውጪ ሃገሮች በሚሉን ስለማንሄድ አሁንም የባህር ማዶ ሰዎች አድርጉ ለሚሉል ነገር ደንታ የለንም የሚሉ ይመስላሉ:: እኔ እስከማውቀው ድረስ የኢትዮጵያ መንግስት ላለፉት ጥቂት አመታት ብዙ ቢሊዮን ዶላር እርዳታ የጎረፈለት ምዕራባውያኑ ለእነሱ የሚበጃቸውን ተግባሮች አድርግ ሲሉት እሺ ጌቶች ብሎ ተግባሮቹን ስለፈጸመ ብቻ ነበር::
አቶ ሬድዋን እዲህና እንዲያ እያሉ ነበር ቃለ መጠይቃቸውን ገፍተው አንድ እሳቸውንም ሆነ የሚውክሉትን መንግስት በእጅጉ የሚያሳንስ አስተያየት የሰነዘሩት:: ሚንስትሩ “Human Rights Watch” እና “Freedom House” ከመሰሎቻቸው ጋር በመሆን በመንግስታቸው ላይ ሊሰሩት የተዘጋጁትን ክፉ ነገር እናውቃለን በሚል እንድምታ በድርጅትቹ ውስጥ ያሉት እያንዳዳቸው ግለሰቦች ማን ማን እንደሆኑና ከዚህ ቀደም ምን እና የት ይሰሩ እንደነበረ ጭምር መንግስታቸው ጠንቅቆ እንደሚውቅ ከእኛ ወዲያ ላሳር በሚል መተማመን ተናገሩ:: ለምን እንደሆነ ባላውቅም ይህን ስሰማ በአእምሮዬ ድቅን ያለብኝ ያ የቦሌው ፖሊስ የቪኦኤን ጋዜጠኛ ያለህበት መጥቼም ቢሆን አስርሃለሁ ያለው ነገር ነበረ:: ምናልባትም አቶ ሬድዋንም ፣ ያም ፓሊስም የሚናገሩትን የማያውቁና የማመዛዘንና ጉድለት ያለበት አእምሮ ተሸካሚዎች ስለሆኑ ይሆናል:: ለነገሩ ኢህአዲግ ያፈራቸው ደናቁርት ባለስልጣኑ የተናገሩትን ከጠቢብና ምሁር እንደወጣ አድርገው ሊወስዱት እንደሚችሉ መገመት አያዳግትም:: ነገር ግን እንደው አገሪቷ ውስጥ ሰው ከተገኘ ስለተቋማቶቹ ማንነትና ስለሰዎቻቸው በቀላሉ እየድህረ ገጾቻቸው ሄዶ ማወቅ ይችላል:: የእናቶ ሬድዋንን ለእኛ ብቻ ነው የተገለጥን የሚባለውን ዲስኩር ሳይሰማ ማለት ነው:: እኔም ያደረኩት ይኸው ነበረ:: በሁቱም ተቋሞች ድህረ ገጾች ላይ ድርጅቶቹ መቼና እንዴት እንደተመሰረቱ መርሆቻቸዎ ምን እንደሆኑ ምን እንደስሩና ማን ገንዘብ እንደሚለግሳቸው በግልጽ ተቀምጧል:: የቦርድ አባላቶቻቸውና መሪዋቻቸው ማን እንደሆኑ የት ይሰሩ እንደነበረ በይፋ ይታያል:: ሰዎቻቸው በመንግስትም ይሁን በግሉ ዘርፍ በጣም ውጤታማ ስራ ሰርተው የተደላደለ ኑሮ እንዳላቸው ይገመታል:: አዋን አሚሪካኖች ከግል ምቾታቸው ባላነሰ ለሰው ልጅ ደህንነት ሲባል የሚችሉትን ሲረዱ የህሌና እረፍት ያገኛሉ:: ለዚያም ነው እነዚህ ተቋማት እንደ ኢትዮጵያ ባሉት ሃገሮች የሰው ልጅ መብት ይከበር ዲሞክራሲም ይበጃችኋል እያሉ ሃባታቸውን የሚያፈሱት::የመርህ ሰዋችና ፈሪሃ እግዛብሔብር ያደረባቸው ስለሆኑና በስራቸውም የህሌና ደስታን ስለሚያገኙ ብቻ:: የለም ለእነ ሬድዋን ይህ አይደለም ምክንያቱ:: ሌላ “Corporate Interest” የሚሉት ድብቅ አላማ አለ:: አቶ ሬድዋን ይህ ድብቅ አላማ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል:: እንድ እሳቸው ከሆነ እነዚህ ድርጅቶች ጠንክረው የሚንቀሳቀሱት በማዕድን ሃብት በተንበሸበሹ ሀገሮች ላይ ነው:: መዕልክቱ ልክ እንደ ድሮው ዘመን የደሃ አገሮችን ሃብት ሊዘርፉ ነው የሚል ይመስላል:: ጉድ በሉ አንባብዮች:: አቶ ሬድዋን አክለውም ተቋማቱ የኢትዮጵያን የመንግስት ባንኮችንና ቴሌን ወደ ግል ይዞታ ቀይሩ ብለው የሚወተውቱት እራሳቸው ሊግዙት ስለ አሰቡት ነው ብለው ያምናሉ። እንደዛማ ካልሆነ ሪፎርም አድርጉ እያሉ መጨቅጨቅ፣የዞን ዘጠኝ አባላትን ማሰልጠንን ምን አመጣው ብለው ይጠይቃሉ::
የተፈጥሮ ሀብት ፍለጋ አሜርካኖች አለምን ሲያስሱ የነበረበትን ዘመን አላስታውስም:: ያ ዘመን አለ ቢባልም እንኳን አፍሪካ ላይ እምብዛም ነው ባይ ነኝ:: እንዲው ለነግሩ በጣም የሚፈልጉትን ነዳጅ እንኳን በሱዳን ላይ እያዩት አልፈውት የለም:: እዚህ ላይ ግን መታወቅ ያለበት የአሜርካን ኩባንያዏች የአለም ሃገራት በሙሉ ወደ ሃገራቸው መጥተው መዋለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ሲለምኗቸው ነው የሚታየው:: እስኪ የአቶ ሬድዋንና የመንግስታቸውን የአስተሳሰብ ችሎታ መዝኑልኝ:: እስከ ትሪሊየን ዶላር በ”Asset” የሚያንቀሳቅስ አንድ የመሜሪካን ባንክ ይህችን ከትንሽ ምንዛሪ በላያ የማታወጣን የኢትዮጵያን ንግድ ባንክ ለመግዛት ሲል በእነዛ ተቋሞችና ዘጠኝ ብሎግሮች በኩል መንግስት እንዲወድቅ ሲያግዝ ይታያችሁ:: ወይም በመቶ ሚቆጠሩ ሃገራት እየሰራ ያለ የሜሪካን የስልክ ኩባንያ የኢትዮጵያውን ቴሌ ለመግዛት ሲል ስርአቱና የስርዓቱ ፓሊሲዏች ይቀየሩ ብሎ ሲለፋ አስቡት:: የሚግርመው ነገር እንዲህ የውጪን “Corporate Interest” ፈራነው የሚሉት እነሬድዋንና መንግስታቸው ከነጻ ቀጥሎ ባለ ዋጋ የሃገሪቱን ለም መሬት ገበሬና ሰራተኛ ሳይቀር ይዘው ለመጡት ህንዶችን ቻያናዋች መቸብቸባቸው ነው:: እግዛብሔር ብሎትማ አሜሪካኖቹ ወደ ሀገራችን መዋለ ንዋይ ሊያፈሱ ቢመጡ ሌላው ቢቀር ፍታሃዊ ክፍያ፣ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በርካታ ስራና የመንግስት ገቢ ያመጡ ነበር::
በመጨረሻም የዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነውን ካለ መጠይቅ ያደረገው የአውራምባ ታይምሱ አቶ ዳዊት ከበደ ይህቺንም መጣጥፍ በድህረ ገጹ ላይ በመለጠፍ ሚዛናዊነቱን እንድናወድስ ቢያደርግ ደስ ይለኛል::
እርሳሱ መሬ

ኢትዮጵያ: አሁንስ ተስፋሽ እግዚአብሔር አይደለምን?

June 20/2014
(ዶ/ር ዘለዓለም እሸቴ ይመር)
ethio zelalem


ነገሩ ግራ የገባው ነው!
ለመሆኑ አሳባችን ምንድነው? እንዲሁ ስንጨቃጨቅና ስንነካከስ ምን ያህል ልንዘልቅ ነው? ንትርኩና መተላለፉ እጅ እጅ ብሎንና ሰልችቶን ሁሉን ትተን የእርቅ ያለህ! ለማለት ጊዜው ለመሆኑ መቼ ይሆን? ከጥል ወደ ፍቅር፤ ከመከፋፈል ወደ አንድነት፤ በስምምነት ለማደግ ቀጠሮ የያዝነው ለመቼ ነው?
በፖለቲካው ውድድር ውስጥ ያለንን የበላይነት ለማስከበር የሞት የሽረት ትግል ስለምናካሄድ፤ የጋራ የሆነውንና የሁላችንም ችግር የሆነውን ይህን የእርቅ ጥያቄ እንዲስተናገድ ማን ቦታ ይስጠው? ይህ የእርቅ ችግር ግን እንደ ድልድይ ሆኖ ሁሉንም ጎራ ያገናኝ ነበር። በራሱ ችግራችንን ሁሉ ባይፈታም እንደ ጥሩ መነሻ ያገልግላል።
ይህ የጋራ የሆነ የእርቅ ጉዳይ መደማመጥን ሊጠይቅ ነው። እኛ ደግሞ የለመድነው ሌላ ነው። ታዲያ ስንተላለፍና ስንዘላለፍ ችግራችንን አክርረነው እና ነገራችንን እጡዘነው የባሰ ተራርቀን እንታያለን። ሁላችንም ነገርን የምናየው በየራሳችን መነፅር ብቻ ስለሆነ ሌላው የሚናገረው አይገባንም። ስለዚህ ሁልጊዜ መተላለፍ ብቻ ሆኖብናል።
አይዞን!
እግዚአብሔር ስለ ተስፋው ቃል እንዲህ ሲል ይናገራል
“አንተም የዘንዶውን ራሶች ቀጥቅጠህ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው።”(መዝሙር 74፥14)። የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያ ልጆች አይደላችሁምን?” ይላል እግዚአብሔር (አሞጽ9፥7) “ኢትዮጵያ ፈጥና እጆቿን ወደ አግዚአብሔር ትዘረጋለች። (መዝሙረ ዳዊት 68፡31)
ምድራችን የመሪዎቻችንን ክብር ስታስተናግድ ለዘመናት ኖራለች። እጃችንን ስንዘረጋ ደግሞ አዲሲቷ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔርን ክብር ታስተናግዳለች።
የእስራኤል ሕዝብ ጥሪ በአንድ ሰው ያውም በአብርሃም ላይ የተመሰረተ ነው። ስለሆነም ያዕቆብ እስራኤል በመሆን የቃል ኪዳኑን ሕዝብ መሰረተ።
የኢትዮጵያ ጥሪ ግን በሕዝብ ላይ የተመሰረተ ነው። ስለሆነም ኢትዮጵያ እጆቿን በመዘርጋት የተስፋው ቃል ሕዝብ ትሆናለች። ለሕዝቡም ምግባቸውን ይሰጣቸዋል። ይህም ተጽፏል። ስለተጻፈም ይፈጸም ዘንድ ግድ ነው።
እግዚአብሔር የሰጠን ተስፋ ዓይናችንን ከሰው ላይ አንስተን ፈጣሪያችን ላይ እንድናደርግ ይጠራናል። የሚያስተሳስረንም በእግዚአብሔር ያለን እምነት ብቻ ነው። እግዚአብሔር ኢትዮጵያ የማንኛውም አንድ ሃይማኖት አገር ሳትሆን በእግዚአብሔር ስር ያለች የፍቅር አገር ያደርጋት ዘንድ እናምናለን።
ምልክት ይሁነን!
ባንዲራችንን የቃል ኪዳን ምልክት እናድርገው።
መላ ከላይ ይምጣልን ስንል ለምልክት ባንዲራችን የተስፋችን አመልካች የሆነው የተዘረጉ እጆች ይኑርበት። ስሙኝና።
ባንዲራችን እኛን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ኩራት እንደሆነ ይታወቃል። በባንዲራችን ላይ ያለው አርማችን ግን መንግሥት በተቀየረ ቁጥር እየተቀየረ ዕድሜው በመንግሥታት ዕድሜ ልክ ብቻ የሚቆጠር መሆኑ ይታወቃል።
መላው ጠፍቶን እጆቻችንን እንደዘረጋን አምላክ ይወቅልን ስንል ኢትዮጵያ ከጥሪዋ ጋር የሚሄድ አርማ (የተዘረጉ እጆች) በባንዲራችን ላይ እንዲያርፍበት እናድርግ የሚል ምኞት አለኝ።
ይህ ዓርማ ታሪካዊ በሆነው ባንዲራችን ላይ ቢቀመጥ ሊሰጠን ያለውን ምልክት በጥቂቱ እንመልከት።
1ኛ/ የተሰጠን ዓርማ ከአምላክ የተወሰነልንን የበረከት ጥሪ ለመቀበል እሺ በማለት እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እንዲባርካት ፍቃደኝነታችንን ያሳያል።
2ኛ/ የተሰጠን ዓርማ የኢትዮጵያን ሕዝብ ማንነት ያንፀባርቃል። የሰዎች ምኞት የሚያንፀባርቅ ሳይሆን የተስፋው ቃል ሕዝብ ለመሆናችን ምስክር ይሆናል።
3ኛ/ የተሰጠን ዓርማ ከማናቸውም መንግሥታት ጋር ስለማይወግን ዘላቂነት ይኖረዋል።
4ኛ/ የተሰጠን ዓርማ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለውን ሃሳብ እንጂ ኢትዮጵያዊ ሰው የፈጠረው አይደለም።  ስለዚህም ከአምላክ የተሰጠን ስጦታ ነው።
5ኛ/ የተሰጠን ዓርማ በሺህ የሚቆጠር ዘመን ታሪክ ያለው ታሪካዊ ነው። ስለዚህም ታሪካዊ በሆነው ባንዲራችን ላይ ታሪካዊ ለሆነችው አገራችን ምቹ ነው።
6ኛ/ የተሰጠን ዓርማ ለኢትዮጵያ ብቸኛ መለያ ይሆናል። በሌላ በኩል ግን የብዙ አገሮች ባንዲራ ኮከብ አለበት።
7ኛ/ የተሰጠን ዓርማ ከማናቸውም ሃይማኖት ጋር አይወግንም። ከማናቸውም ሃይማኖት ምልክቶች ጋር አይያያዝም። ሃይማኖት እንደማይከፋፍለን ምልክት ይሆንልናል።
8ኛ/ የተሰጠን ዓርማ በፊት ለአፍሪካ ኩራት የነበረውን ባንዲራችንን ለዛሬ የአፍሪካ ተስፋ በማድረግ ይበልጥ ያከብረዋል።
9ኛ/ የተሰጠን ዓርማ ኢትዮጵያ የብዙ ሃይማኖቶች አገር ብትሆንም ቅሉ በሃይማኖት ሳንከፋፈል በመያያዝ እዲስ በሆነ መልክ የእግዚአብሔርን እርዳታ ጠይቆ ማግኘት ምን እንደሚመስል ለዓለም ያበስራል።
10ኛ/ የተሰጠን ዓርማ እግዚአብሔር አዲሲቷን ኢትዮጵያ ገፅታ ለውጦ የዓለም ሞዴል ሲያረጋት ለእግዚአብሔር ታማኝነትና ታላቅነት መታሰቢያ ይሆናል።
ኢትዮጵያ ሆይ፡ ምርጫሽ የቱ ይሆን?
——
ዶ/ር ዘላለምን ለማግኘት በዚህ አድራሻ መጻፍ ይችላሉ፡ one@EthioFamily.com

ቀና ብለን የምንሄድበት ጊዜ አየመጣ ነው! ጎበዝ ተነሳ!

June 19/2014
ጉጅሌዎቹ አይገባቸውም እንጂ የኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች የለውጥን ደመና ኣርግዘዋል። ወንዞችም ተራሮችም የለውጥ ማዕበል ማቆብቆቡን አያበሰሩ ናቸው። የቀደሙት ገዢዎች መረጃ የሚያገኙት እረኛ ምን ይላል ብለዉ እየጠየቁ ነበር። የአሁኖቹ አገር አጥፊ ገዢዎች ምሳሌ ያደረጉት ካድሬዎቻቸውን ብቻ ሆነ እንጂ ዛሬም የአገራችን እረኞች የለውጥን መምጣት በሚያምር ቅላጽያቸው አያንጎራጎሩ እንዲህ አያሉን ነው፣
የሀገሬ ጉብል የሰማውን እንጃ
የጎንደሬው ጉብል የሰማውን እንጃ
ከብቱን አየሸጠ ገዛ ኣሉ ጠብመንጃ።
የወለጋው ጉብል የሰማውን እንጃ
ቡናውን ሻሽጦ ገዛ ኣሉ ጠብመንጃ።
መልእክቱ ግልጽ ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች አገራቸውን በክቡር ደማቸው ሊታደጓት ቆርጠው በመነሳት ወያኔን በማስወገድ የሀገራቸው ባለቤት ለመሆንና ያልተከፋፈለች ውብ ኢትዮጵያን ማየትን ለማረጋገጥ ጥርጊያውን መጀመራቸው ነው።
ላለፉት ፵ አመታት አምባገነኖች ባደረሱብን ጭቆና እና እንግልት የተነሳ የራሳችን የሆነ መንግሥት ሳይኖረን አንገታችንን ደፍተን ጀግኖቻችንን ስንገብር ኖረናል። በተለይም ባለፉት ፪፫ አመታት ጉጅሌዎቹ በአራት ኪሎ ከነገብን ጀምሮ በአንድ ላይ አንዳንቆም በማድረግና እና አርስ በራሳችን በማጋጨት ሲያባሉን ኖረዋል።
ዛሬ ሁኔታዎች ተለውጠዋል፤ በውጭም በአገር ውስጥም ለውጥ አየታየ ነው። የእንቅስቃሴው ማእበል አይሎ እየመጣ ነው። ዛሬ ሁሉም የዴሞክራሲ ሀይሎች ማለት በሚቻል ደረጃ በሁለት ነገሮች ላይ ስምምነት አለ፣
፩. ተቃዋሚዎች በግል ከሚያደርጉት ትግል ይልቅ በጋራ የመሰባሰብን አስፈላጊነት ተረድትው መሰባሰብ መጀመራቸው
፪. በአንድ ላይ መሰባሰብ ካልቻሉም እርስ በራስ ላለመጠላለፍ መስማማት መቻላቸውና አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ግዜ ሁሉ መረዳዳት መጀመራቸውና በግልም ከወያኔ ጋር የሚደረገውን ትግል ማፋፋም የቻሉበት ሁኔታ አየታየ መሆኑ የሕዝብ ወገኖችን እያስደሰተ ይገኛል።
በአገር ቤት የሚገኙ የዴሞክራሲ ኃይሎችም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሕዝቡ ከፍርሀት ተላቆ ለመብቱ አንዲነሳ የሚያደርጓቸው አንቅስቃሴዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከሩ መጥተዋል። ለዚህም በቅርቡ በአዲስ ኣበባ መድረክ፣ ኣንድነትና ሰማያዊ ፓርቲዎች የጠሯቸው ሰልፎች ይበል የሚያስብሉ ናቸው።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ በዚሀ ኣጋጣሚ ለዴሞክራሲና ለነፃነት ታጋዮች ሁሉ ያለውን አክብሮትና ኣድናቆት ይገልጻል።
በሌላም በተለያዩ አቅጣጫዎች ወያኔን በኣመጽ ለመፋለም የወሰኑ ኃይሎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ወያኔን ለመፋለም ቆርጠው በጋራ ክንዳቸውን ኣቀናጅተው ለመፋለም አየተዘጋጁ ያሉበት ሁኔታ አበራታች ነው። እነዚህ ኃይሎች አዳዲስ የነጻነት ታጋይ አርበኞችን በተከታታይ በማስመረቅ ያሉ መሆናቸውና ከዚህም በተጨማሪ ከመላው የአገሪቱ አካባቢዎች ወጣቶች በገፍ ትግሉን እየተቀላቀሉ መሆኑን ስንሰማ ልባችን በደስታ ይሞላል።
በወያኔ ጉያ ውስጥ ያሉ የሕዝብ ወገኖች ደግሞ የቻሉትን በውስጥ ሆነው መቃብሩን እይቆፈሩለት ሲሆን፣ ያልቻሉትም የወያኔን ሚስጢር ይዘው በመውጣት የሕዝብ ወገንተኝነታቸውን አየገለጹ ይገኛሉ።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ለመላው ሕዝባችንና በተለይም ለወጣቱ ትውልድ በተደጋጋሚ አንደሚለው የሀገራችን ባለቤት ለመሆን የምናደርገውን ትግል ተቀላቀሉ!!! መቀላቀል ያልቻላችሁም በኣካባቢያችሁ ከምታምኗቸው ወገኖቻችሁ ጋር ተሰባሰቡ፣ በህዋስ ተደራጁ። ግንቦት 7 በዚህ ትግል የዳር ተመልካች ሳይሆን መሪ እንድትሆኑ ኣገራዊ ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Thursday, June 19, 2014

Political Prisoners in Ethiopia Packed in Cells Like “Slaves”

June19&2014
The 2014 Golden Pen of Freedom Award Winner Eskinder Nega of Ethiopia

Swedish Journalist: Political Prisoners in Ethiopia Packed in Cells Like “Slaves”

SKETCHES By Ana Marie Pamintuan (The Philippine Star) |
TURIN – In the darkened auditorium in this Italian city, some forum participants could be seen dabbing at their eyes while others could be heard blowing their nose.
It wasn’t anything in the air in the 90-year-old former Fiat automobile plant that is now the Lingotto Conference Center that made the delegates misty-eyed the other day. What touched the audience was the speech by a Swedish journalist who spent time in an Ethiopian prison for “terrorism.”
I have attended several of the annual gatherings of the World Editors Forum, where a Golden Pen of Freedom is traditionally awarded to a journalist who embodies the continuing struggle for press freedom around the world.
The typical participants in this forum are senior journalists who tend to be hardened and even jaded to suffering. Monday’s event was the first time that I saw anyone moved to tears by a colleague’s story.
“The first screams were always the worst,” Swedish journalist Martin Schibbye began his personal story of life in Addis Ababa’s notorious Kaliti prison. He would never be free of those screams, he said.

He described regular beatings, of inmates being hanged upside down. In the detention cells they were packed “like slaves” and had to sleep on their side. “Once a month an inmate leaves with his feet first,” he narrated.
Opinion ( Article MRec ), pagematch: 1, sectionmatch: 1
More than the torture and disease, Schibbye recalled, the hardest part was “the fear of speaking.”
“It’s not the guard towers with machine guns that keep the prison population calm. It is the geography of fear. People who speak politics are taken away. They disappear,” Schibbye recounted. “It went under my skin… I would wake up wondering if I had said something against the government in my sleep.”
The Ethiopian government continues to toss critical journalists in jail for “treason” and “terrorism.” Schibbye served only 14 months of his 11-year sentence. He and his photographer Johan Persson were pardoned and freed in September 2012. But Ethiopian journalist Eskinder Nega, on whose behalf Schibbye accepted the Golden Pen of Freedom, has been in prison since his arrest in 2011 and may have to serve his full 18-year sentence.
Nega was initially joined in prison by his wife, who in her 17 months of incarceration gave birth to their son. She at least has been freed and is currently seeking asylum in the United States.
“They will never break him,” Schibbye said after reading a letter written by the Ethiopian to an older son.
Even if they have robbed Nega of almost all his freedoms including “the freedom to drink or eat, and even to [deleted],” what they can’t take away from him is the freedom to be what he wants to be, Schibbye said: “Eskinder is a journalist. And every day that he wakes up in the Kaliti prison is just another day at the office.”
“It’s not us that are fighting for his freedom,” Schibbye said as he concluded his speech, “but rather he who is fighting for ours. Ayzoh Eskinder! Ayzoh!” (The Ethiopian word means “be strong, chin up.”)
Most Filipinos have forgotten the systematic torture of political dissidents during the Marcos dictatorship and may not care what happens in Ethiopia, seen as a hopelessly failed state.
Unfortunately for us, however, instead of being detained and tortured, Filipino journalists are simply killed.
Journalism in the Philippines, as in other countries, also faces new threats that have emerged as technology allows states, private groups and crime gangs to monitor digital communication, and as governments invoke national security to clamp down on press freedom.
* * *
Journalists are facing traditional threats in delivering the news in places where civil liberties are currently being curtailed, such as Thailand and Ukraine. But because of the war on terrorism and because states are increasingly equipped to increase surveillance of individuals, press freedom is under threat even in its traditional bastions: the United States, the UK and other Western European nations.
At one of the sessions here, Associated Press president and CEO Gary Pruitt narrated how the American wire agency cooperated with their government in May 2012 and deferred publication of a foiled al-Qaeda bomb plot in Yemen because, AP was told, certain individuals could be compromised and lives could be placed at risk.
Later it was learned that the US government had secretly seized AP phone records including text messages to find out who leaked the story.
Aghast over what Pruitt described as one of the worst intrusions in its 168-year history, AP asked the US Justice Department to safeguard the records and strengthen their rules governing such cases. The US government agreed and promised that no journalist would be prosecuted for doing his job.
It was good to know no one would be sent to jail “for committing journalism,” Pruitt said, but the incident “created a very real chilling effect” on AP’s sources.
The British press, for its part, has not yet recovered from the phone hacking scandal, which has paved the way for UK officials to impose rules that tend to curtail press freedom.
“We have gone from hero to zero,” said Guy Black, executive director of the UK’s Telegraph Media Group. “Where once we could draw on our history of free speech, now we are held as a shining example that we are shackling the press.”
Why are trends in the US and UK worrisome? As Claudio Paolillo of Uruguay noted, Latin American journalists used to look up to the American and British media as models of press freedom. “Not anymore,” he said.
Worse, Paolillo said, the moves of the US and British governments to curtail press freedom in the name of national security were inspiring despots. The attitude, he said, is, “If the US can do it, I can do it too.”
* * *
I know prominent Filipinos who think the Philippine press could use tighter regulation, but government intrusions on journalists’ work can quickly get out of hand.
Borrowing a line from Winston Churchill, Pruitt reminded the audience, “The media is the worst check on government except for all the others. It’s all we’ve got.”
What can journalists do in the face of increasing government surveillance even in Western democracies? Panel moderator Kai Strittmatter of Germany urged the audience: “Let’s not start getting used to this. Let’s not find some of these things normal.”
“All our freedoms stem from (press freedom),” Black said. “We have to fight.”
Eskinder Nega is doing just that, in the worst conditions. He is showing, Schibbye said, “that they can jail journalists but they can never succeed in jailing journalism.”

http://betinews.com/?p=1151

ጋዜጠና እስክንድር ነጋን እና ሌሎችንም በሃስት በመክሰስ እና በመመስከር ለዕስር ከዳረጉ ህሊና የሌላቸው ግለሰቦች በትቂቱ ይህን ይመሰላሉ ::

June 19/2014
ጋዜጠና እስክንድር ነጋን እና ሌሎችንም በሃስት በመክሰስ እና በመመስከር ለዕስር ከዳረጉ ህሊና የሌላቸው ግለሰቦች በጥቂቱ ይህን ይመሰላሉ ::
አሽባሪው አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ በታማኝነት ህውሃቶችን በማገልገል በርካታ ንጽሃን በሃስት ከሶ ለዕስር እና መከራ ዳርጎ በአሁኑ ግዜ ከቤተሰቡ ጋር በአሜሪካ ሃገር በሜሪላንድ ሲልበርስፕሪንግ በሰላም ኑሮውን እየመራ ይገኛል:: አቃቤ ህግ ቴድሮስ ባህሩ እስክንድር ነጋን ጋዜጠኛ ርዮት አለሙን እንዲሁም በሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊና ዋና ዋና በተባሉት ላይ ታላቅ ሚና የተጫወተ ግለሰብ ነው::
የጋዜተኛን እስክንድር ነጋን ንብረት እንዲወረስ ታላቅ ሚና የተጫወተው አቃቢ ህግ ብርሃኑ ወንድማገኝ ... በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት በመቅረብ በዚህ ንብረት ላይ ለሚመለከታቸው በአድራሻቸው ልናገኛቸው አልቻልንም ፣:: የጥሪ ወረቀት ለመላክ አልቻልኩም ሲል ደጋግሞ ለፍርድ ቤቱም ገልጻል:: ፍርድ ቤቱም ተጨማሪ ቀናት ሲሰጠው ቆይቷል :: ንብረቷ እንደታገደ በዜና ሲነገር የሰማችው የጋዜጤኛ እስክንድር ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካለም ፍሲል፣ ይህ ግለሰብ በተደጋጋሚ ሲዋሽ በቦታው በመገኘት ሰትከታተል ከቆየች በኋላ አቶ ብርሃኑ በተደጋጋሚ የሚመለከታቸውን ልናገኝ አልቻልንም ሲል ጋዜተኛ ሰርካለም ፍሲል ከታዳሚው መሃከል እጇን በማውጣት ለፍርድ ቤቱ ማንነቷን ከገለፀች በኋላ በዚህ ጉዳይ ላይ ማንም እንዳላናገራት ለፍርድ ቤቱ በመግለጽ ፍርድ ቤቱም ሌላ ቀጠሮ ለመሰጠት ሲሞክርም ሰርካለም ሁሉንም እንደተከታተለች እና ንብረቱን እሷም ሆነች ባለቤቷ እስክንድር ነጋ እንደማይፈልጉት በመግለጽ ንብረቱን መውሰድ እንደሚችሉ ለፍርድ ቤቱ አሳውቃለች ::
ዜጎች ላይ ግፍ ሲሰሩ ከከረሙ በኋላ በውጭ አለም የራሳቸውን ህይወት በተደላደለ ሁኔታ "ሀ "ብለው የሚጀምሩ እንደ ቴድሮስ ባህሩ አይነት ግለሰቦች በርካታ ናቸው :: እነዚህን ወንጀለኞች በመረጃ ለፍርድ የሚቀርቡበት ግዜ ዕሩቅ አይሆንም ::
ታላቅ ምስጋና
ለጋዜጠኛ አበበ ገላው
ልትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !!!
በተጨማሪ ለማዳመጥ ይህንን ሊንክ ይጫኑ

አሽባሪው ቴድሮስ ባህሩ እና ግብረአበሮቹ !!!





ጦማሪያኑን እና ጋዜጠኞቹን በተመለከተ ችሎቱ ለፖሊስ ጠንካራ ትዕዛዝ አስተላለፈ

June 19/2014

በቁጥጥር ስር ከዋሉ ባለፈው ቅዳሜ (ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም) 50ኛ ቀናቸውን በእሰር ያሳለፉት ስድስቱ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ለአራተኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዶባቸዋል። ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት ከዞን 9 ጦማሪያን መካከል ዘላለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኔ ሲሆኑ፤ ጋዜጠኞቹ ደግሞ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ እና አስማማው ወ/ጊዮርጊስ ናቸው። በዕለቱ ችሎቱ መርማሪ ፖሊስ የሚያቀርባቸውን ተደጋጋሚ ምክንያት አጠንክሮ በመፈተሽ በቀጣይ ቀጠሮ ፈፅሟቸው ሊመጣ የሚገቡ አራት ተግባራትን በግልፅ በማስቀመጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀለ ችሎት በዕለቱ የቀረቡት ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ፖሊስ የመሰረተባቸውን የሽብርተኝነት ክስ በተመለከተ የደረሰበትን ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ ለማሰማት ነበር። በችሎቱ ጥበት ምክንያት አንዳችም የውጪ ሰው ወደ ውስጥ ሳይዘልቅ የተከናወነው ችሎቱ በብዙዎች ዘንድ “የዝግ ችሎት ነው ወይ?” የሚያሰኝ ጥያቄን ቢያስነሳም ለጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ በጥብቅና የቆሙት ጠበቃ አመሃ መኮንን ግን ችሎቱ ጠባብ በመሆኑ ነው የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። በዕለቱ በግቢው ውስጥ በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞች ዲፕሎማቶችና የታሳሪዎቹ ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተው ነበር።
ፍርድ ቤቱ የማዕከላዊ ፖሊስ በታሳሪዎቹ ላይ ካለፈው ቀጠሮ መልስ አገኘዋቸው የሚላቸውን መረጃዎችና ሰራዋቸው የሚላቸውን ተግባራት በተመለከተ ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ፤ በከፊል ሰነዶችን ማስተርጐሙን፤ በከፊል የባንክ ማስረጃዎችን ማግኘቱንና በከፊል የቴክኒክ ማስረጃዎችን ስለማሰባሰቡ ቢገልፅም በደፈናው ግን “ብዙ ስራ ሰርተናል፤ ብዙ ስራም ይቀረናል” ሲል ለፍርድ ቤቱ ማስታወቁን ጠበቃው ከችሎት መልስ ተናግረዋል።
በዚህም ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎች ሲቀርቡ፤ በጥቅል መቅረብ እንደሌለባቸውና በዝርዝር እንዲቀርብለት ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም ጥቅል ማስረጃን ማድመጥ እንደማይፈልግ አስታውቋል። ፖሊስ ለስራው መጓተት አሁንም እንደቀደመው ጊዜ ካቀረባቸው ምክንያቶች ውስጥ የምስክሮችን ቃል ስለአለመቀበሉ፤ ተባባሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል መቸገሩንና ወደ ክልል ሀገር ሄደውብኛል በሚል አባሎቹን ልኮ በቁጥጥር ስር ለማዋል እየተከታተለ መሆኑን ከመግለፁም በተጨማሪ አሁንም ሰነዶችን አስተርጉመን አልጨረስንም ሲል አብራርቷል።
የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዱ ለአራተኛ ጊዜ በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስታውሰው፤ የቱንም ያህል ውስብስብ ወንጀል ቢሆን ተጠርጣሪዎቹ እጃቸው ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ ያለው 50 ቀናት በቂ ናቸው የሚል መከራከሪያ አሰምተዋል። ጠበቃው አክለውም ይህ የሚያሳየው ፖሊስ ከመነሻው አንድም ማስረጃ ሳይሰበስብ ልጆቹን የያዛቸው መሆኑና ይህም ሕግን የጣሰ ተግባር ነው ሲሉ አስረድተዋል። ሌላው በጠበቆች በኩል የቀረበው አቤቱታ ፖሊስ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ተመሳሳይ ምክንያቶች በመሆናቸው የቀረቡትን ምክንያቶች ውድቅ አድርጐ ተጠርጣሪዎቹን በዋስ እንዲለቅ፤ አልያም ፍርድ ቤቱ ሕጋዊ ምክንያት አለኝ ብሎ የሚያምን ከሆነ ይህ የመጨረሻ የጊዜ ቀጠሮ ይሁንልን ሲሉ ስለመጠየቃቸው ጠበቃው ተናግረዋል።
የግራ ቀኙን ኀሳብ ያዳመጠው ፍርድ ቤቱም፤ ፖሊስ በተደጋጋሚ ከሚያነሳቸው ምክንያቶች ውስጥ አራት ጉዳዮችን በመምረጥ በቀጣዩ ቀጠሮ እልባት ሰጥቷቸው እንዲመጣ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ እነዚህ አራት ተግባራትም ተባባሪዎቻቸውን አልያዝንም፣ የምስክሮችን ቃል አልተቀበልንም፣ ሰነዶች ተተርጉመው አልመጡልኝምና ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ በባንክ የተላከላቸውን ገንዘብ በተመለከተ ደብዳቤ ጽፈን ምላሽ እየተጠባበቅን ነው የሚሉትን ጉዳዮች በተመለከተ ከዚህ በኋላ ለጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ምክንያት ሆነው ሊቀርቡ እንደማይችሉ በመግለፅ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የጊዜ ቀጠሮውን የመጨረሻ ነው እንዳላለ ጠበቃው ተናግረዋል።
በሌላም በኩል የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸው መሰናክል መኖሩንና፤ በተለይም ጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስ የወገብ ሕመም ያለበት መሆኑን በመግለፅ ወንበር ወደክፍሉ እንዲገባለት መጠየቁን ነገር ግን አሁንም ድረስ አለመፈፀሙን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። ፍርድ ቤቱም በበኩሉ መርማሪ ፖሊሶቹ በዚህ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ ያዘዙ ሲሆን፤ የተጠርጣሪዎቹን ቤተሰብ መጐብኘትን በተመለከተ ከተደራራቢ ስራና ከአስተደደር ጋር የተያያዘ መሆኑን በመጥቀስ የመከልከል ደረጃ ግን አልተደረሰም ሲል የተፈጠሩት ክፍተቶች እንደሚያሻሽሉ አስረድቷል። የጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስን ጥያቄ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በጤና ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ድርድር የለም በሚል የሰጠውን ትዕዛዝ ለመፈፀም እንደሚቻል አሳውቀዋል።
     የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ፖሊስ የጠየቀውና ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ለሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ አዟል።

Honorees of the Fourth Ethiopian Heritage Festival

June 19, 2014

Poet Laureate, Young Scholar and Journalists to be honored:

• An Ethiopian Poet Tsegaye Gebremedhin will be honored for his Contribution to the Advancement of Humanity
• The Zone Nine bloggers: Free press Journalist for reporting the truth, corruption, and the human rights condition in Ethiopia at great personal sacrifice and risk.
• Nahom Marie, a 17 Years old, software and iOS app developer who will be attending MIT.
Poet Laureate, Young Scholar and Journalists to be honored
These are among those who will be primarily honored, celebrated, and remembered at the upcoming Ethiopian Heritage Fourth annual Festival to be held from Friday, July 25 to 27th 2014.
Laureate Tsegaye “Giant” and “Icon”
Poet Laureate Tsegaye Gebremedhin was a renaissance man. He was poet, playwright, essayist, historiographer, philologist, art director, humanist, and peace activist. Born in 1936 Ambo, Ethiopia, Tsegaye Gebremedhin’s artistic talent was noticed early on by his grade school teacher. Into adulthood, he advanced to become a prolific playwright and poet. Throughout his life time, he has published over 11 research papers, over 40 plays and poetry in Amharic, and translated more than 16 plays in Amharic and English, some being his work.
Moreover, he has also held several positions such as was General Manager of the Ethiopian National Theatre, Vice-Minister of Culture and Sports, editor at the office of Oxford University Press, assistant professor at department of Education at Addis Ababa university from (1977-1978) and much more. His awards include the following: Emperor Haile-Selassie I International Prize for Amharic Literature in 1966, The Gold Mercury Ad Persona Award in 1982, 4 Fulbright Senior Scholar Resident Fellowship Award; Human Rights Watch Free Expression Award in New York in 1994, and Honorable Poets Laureate Golden Laurel Award. In addition, his literary contribution particularly to Ethiopia is immense and remains as an icon etched not only in Ethiopian history and identity, but to Africans as well.
Unsung Heroes- Zone9 bloggers
Zone9bloggers are a group of bloggers dedicated to presenting the various pertinent social issues such as political repression and human rights activism. The six bloggers are Atnaf Berahane, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Befeqadu Hailu, Zelalem Kiberet, Abel Wabela, and 3 journalists; Edom Kassaye, Tesfalem Weldeyes and Asmamaw Hailegorgis of Addis Guday magazine. After much surveillance and harassment, as of April 26th they have been charged with terrorism and imprisoned at Maeklawi prison which is notorious for torture. The ESHNA acknowledges the diligent work zone9bloggers have contributed to human rights and the idea of free expression.
Young scholar- Nahom Marie
Nahom Marie is a bright 16 years old high school student whose academic achievement is exemplary. Nahom’s exceptional academic began whilst in Kindergarten where he exhibited a higher understand that advanced him to several classes beyond his age.
Nahom Marie is an aspiring software and iOS app developer from San Jose, California. He has worked on different types of apps from BOOM, a music recognition app that utilizes the capabilities of the Pebble smart watch, to an in-progress tutoring app that looks to make the process of tutoring and/or finding a tutor tailored to compatibility and several preferences.
Graduating this summer, Nahom has received several awards and scholarships to various universities such as Princeton, Sanford, Harvard, MIT and many more. Besides his academic achievement, he has engaged himself in working within the Ethiopian community. He often volunteered after school to help students with their homework’s, and acting not only as their tutor but as mentor as well.
Ethiopian Heritage Festival to be an Interesting Event
Along with the ceremonial honorees, the Ethiopian Heritage Festival will offer venues for members of the Ethiopian Diaspora Community and their American neighbors to learn about and celebrate the Ethiopian experience. These include art, crafts, and jewelry exhibitions. Plenty of delicious Ethiopian cuisine, traditional music and dancing, soccer and running sports, and plenty of activities for the youngsters will keep everybody interested.
Main days of the Ethiopian Heritage Festival: Opening Friday, July 25 at Silver Spring Civic building 1 Veterans Pl, Silver Spring, MD 20910 and Saturday July 26 through Sunday, July 27, 2014, on the campus of Georgetown University in Washington, D.C
For more info please visit our website www.ehsna.org
Or email us @-pr@ehsna.org

የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ጥናት ኢትዮጵያን ከዓለማችን ደሃ ሀገራት ከመጨረሻው ሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡

June19/2014
 Multidimensional Poverty Index (MPI) የተባለውና የዓለማችንን 108 በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን የድህነት ደረጃ የፈተሸው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲው ጥናት ኢትዮጵያን ከ108ቱ ሀገራት ከኒጀር ብቻ በልጣ ከመጨረሻው ሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡ ደረጃው በትምህርት፣ ጤና እና የኑሮ ሁኔታ ላይ የሚያጠነጥኑ 10 መስፈርቶች ሲኖሩት ከ10ሩ መስፈርቶች አንድ ሦስተኛውን እንኳ ያላገኘን ደረጃው ዘርፈብዙ ደሃ (Multi-dimensionally poor)ሲለው፣ ከመስፈርቱ ዝርዝር ውስጥ አንድ ሦስተኛው ያህል የተሟላለትን ደግሞ ለኑሮ መሰረታዊው ነገር ያልተሟሉለት (Destitute) ይለዋል፡፡ በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ህዝብ 87.3% ያህሉ ዘርፈብዙ ደሃ በሚለው ክልል ውስጥ ሲገኝ 58.1%ቱ ደግሞ መሰረታዊው ነገር ያልተሟሉለት (Destitute) በሚለው ክልል ውስጥ እንደሚገኝ የጥናት ውጤቱ ያስረዳል፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ውስጥ መሰረታዊው ነገር ያልተሟሉላቸው (Destitute) ዜጎቿን ቁጥር በመቀነስ ረገድ ጥሩ ውጤት ብታስመዘግብም ኢትዮጵያ አሁንም የ76 ሚሊየን ዘርፈብዙ ደሃ ህዝብ ሀገር ናት ይላል የጥናት ውጤቱ፡፡ ይህም ቁጥር በዓለማችን ካሉ መሰል በርካታ እጅግ ደሀ ሕዝብ ከያዙ ሀገራት ማለትም ከህንድ፣ ቻይና፣ ባንግላዴሽ እና ፓኪስታን በመቀጠል ኢትዮጵያ በ5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ የደረጃው ዝርዝር የገጠሪቱን ኢትዮጵያ አስመልክቶ 96.3% የገጠሪቱ ኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት ውስጥ እንደሚገኝ ሲገልጽ በአንጻሩ ከከተማ ነዋሪው 46.4 %ቱ በድህነት ውስጥ እንዳለ ያስረዳል፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች የሚስተዋለውን የድህነት ደረጃ አስመልክቶም በሶማሊያ 93% በኦሮሚያ 91.2% በአፋር 90.9 % በአማራ 90.1 % በትግራይ 85.4 % ህዝብ በድህነት ውስጥ እንዳለ ይገልጻል፡፡ ከተሞችንም በተመለከተ አዲስ አበባ ከሌሎች ከተሞች ይልቅ አነስተኛ ደሃ (20%)ያለባት ስትሆን ድሬዳዋና ሐረር ደግሞ አነስተኛ ደሃ በመያዝ በ54.9% እና በ57.9% ይከተላሉ፡፡

http://www.diretube.com/articles/read-ethiopia-ranks-second-poorest-country-in-the-world-%E2%80%93-oxford-university-study_5513.html#.U6Kj2_l_tSQ

Ethiopia ranks second poorest country in the world – Oxford University Study


ዜጎችን መታደግ የማይችሉ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ የመቀላቀል ግዴታ አለባቸው።:-ምንሊክ ሳልሳዊ

June 18/2014
ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እን በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ ነው። ይህ የማይዋጥለት አሊያም የሚክድ ካለ እውነት የማይደላው ብቻ ነው።
Co_existanceየኢትዮጵያ ጨቋኝ መንግስታት የሆኑ ከጥንት እስከ ዛሬ የተንሰራፉ በህዝብ ላይ የሚያደርጉት ጭቆና እና በደል ታሪክ የማይሽረው ጠባሳ በሰው ልጆች የትውልድ ሂደት ላይ መፍጠሩ እንደተጠበቀ ሆኖ የሃይማኖቶች ሚና ግን እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ዜጎች በግፍ በጨቋኝ መንግስቶች ሲታረዱ በመባረክ የመንግስታቱን እድሜ አስረዝመዋል አሁንም እያስረዘሙ ነው። የመንግስት እና የሃይማኖት ቁርኝት የሚፈለገው ስልጣንን አደላድሎ ለመያዝ እና ህዝብን ረግጦ ለመግዛት ካለ ምኞት እንጅ ለዜጎች ከመቆርቆር የመነጨ አይደለም። የሃይማኖት አባቶች በሃይማኖታዊ የመንፈስ ጥኡም ሰበካና ዜማ ጋር በማጣፈጥ የጨቋኞችን የበላይነት በመስበክ ማስፈራራት እና ማሸማቀቅ የጳጳሳት እና የሼህዎች አብይ ተግባር ነው።
በኢትዮጵያ ውስጥ ተገዝተው አሊያም አድርባይ ሆነው በመስራት ላይ ያሉ የሁሉም ሃይማኖት መሪዎች እጅግ ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ በዜጎች ላይ የሚደርሱ ግድያዎች ድብደባዎች እስሮች እና መንገላታቶችን እንደ አንድ መንፈሳዊ የሃይማኖት መሪ እንደ ሰብአዊ ተፈጥሮ አሊያም መጽሃፋቸው እንደሚያዛቸው ለዚጎች ሲደራደሩ ሲከራከሩ ሲዋያዩ ሲሆንም አንተም ተው አንተም ተው ሲሉ አልታዩም ከዚህ በከፋ መልኩ በልማታዊ ዲሞክራሲ የፖለቲካ ፉጨት ስር ተደብቀው በለው በሚል አብዮታዊ ዜማ ዜጎችን እያስፈጁ ይገኛሉ።
አንድ የሃይማኖት አባት የታመመ ሲጠይቅ፤ የሞተ ሲቀብር ፤የተቸገር ሲረዳ ፤የታሰረ ዞሮ በመጎብኘት ሲያጽናና እንጂ ሲፖተልክ አሊያም ሲወሸክት ማየት ያማል። በሃገራችን ምእመናንን እንምራለን የሚሉ ሕዝብን መንፈስ እንመግባለን የሚሉ የለሊት ወፍ የሆኑ የክርስትና እና እስልምና የሃይማኖት መሪዎች ዜጎችን መታደግ የማይችሉ ከሆነ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ መቀላቀል ግዴታ አለባቸው። ይህ ጉዳይ የብዙሃኑ የዜጎች ጉዳይ ስለሆነ ክርስቲያን እስላም የሚባልበት ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ ነው።
በሃገሪቱ ዜጎች በአለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በነጻነት በመጻፋቸው የእኩልነት እና የነጻነት ጥይቄ በማንሳታቸው ብቻ አሸባሪ ተብለው እስር ቤት በታጎሩባት ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስኪ ላስጠናው ላጥናው ያለ የሃይማኖት መሪም ይሁን የሃይማኖት ሃራጥቃ የለም። እንዲሁም በታሰሩ ሰዎች እና በአሳሪዎች መካከል እርቀ ሰላም እንዲወርድ ለወደፊቱ ስህተቶች ካሉ እንዳይደገሙ ነገሮችን ለማግባባት እና ለማቻቻል የፈቀደ አንድም የሃይማኖት መሪ የለም። ይብስኑ የሃይማኖት መሪዎቹ በየስብሰባው እና በየጭብጨባው ዜጎች የመንግስታዊ ሽብር ዱላ ሰለባ እንዲሆኑ እያበረታቱ ይገኛሉ ።
የዜጎች ሁኔታ ያሳሰባቸው የሃይማኖት መሪዎች በከፍተኛ ዛቻ እና ማስፈራራት እንዲሁም በጥቅም በማሰር እንዳይንቀሳቀሱ አሊያም በተዘዋዋሪ ባልሰሩት ወንጀል ለማጥመድ ሴራ በመጎንጎን እያስፈራሩ የህዝቦችን የሰብ አዊ መብት ጥያቄዎች እንዳያነሱ በማስደንገጥ እንዲሁም በጥቅማ ጥቅም እና በገንዘብ በመደለል አባትነታቸውን ለስጋዊ ባለስልጣናት እንዲሸጡ እና የፖለቲካ ምንዝር እንዲፍጽሙ እየተደረገ ሲገኝ ይህንን የምንዝር ጌጥ ከመለማመዳቸው የመጣ የሃይማኖት አባቶች ከጨቋኞች ብሰው በሕዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እንዲፈስም ከባዱን ሚና እየተቻውቱ ይገኛሉ ።
የሃይማኖት አባቶች ሰጥ ለጥ ብለው ስለልማት ብቻ እንዲሰብኩ የእስላሙንም ሆነ የክርስቲያኑን ጥያቄዎች በተገኙበት እንድያስተጋቡ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው አባቶች መካከል አቡነ ማትያስ አቡነ ሉቃስ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው እንዲሁም የወያኔ መንግስት በቅርቡ ለሾማቸው የእስልምና ምክር ቢት ሼሆችን ከፍተኛ የሆነ ምክር አዘል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል። እኔ ስጨፈጭፍ እናንተ አጨብጭቡ የሚለው አሸባሪው የወያኒ መንግስት ሃይማኖቶችን በራሱ አይዲኦሎጂ በመቀጽ ቀሚሳቸውን ያንዥረገጉ ሰላዮችን እና የሃይማኖት ነቅእዞችን በመመደብ ዜጎችን በተመለከተ የሚደርሱ በደሎች እና ገፈፋዎች ጠያቂ እንዳያገኙ አስታራቂ እንዳይሹ አድርጓል። ፓትርያርኩ ተንገላተው ከተለቀቁ በኋላ በማህበራዊ ድህረገጾች ላይ ብዕራቸው ለምን ታቀበ? ከፋሲካ ክብረ በአል በኋላ በትዊተር ላይ እንዳልተገኙ የሚነገርላቸው ፓትርያርኩ ራሳቸውን ከማንኛውም አንደፋዳፊ ንግግር በመቆጠብ በተረጋጋ መልኩ አንገታቸውን እንዲሰብሩ እና በቅርባቸው ለተመደቡላቸው የመንግስት ደህንነቶች /አማካሪዎች ተገዢ እንዲሆኑ ተደርጓል።
7d2898c3630feea92ec1553d16389ff6_XLዜጎቹን የማይታደግ የሃይማኖት መሪ ቆቡን አውልቆ ከፖለቲካው ጎላ ይቀላቀል አሊያም ገለልተኛ ሰው ሆኖ እንዲቀመጥ ለመምከር እንፈልጋለን ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሃይምኖቶች ለመንግስታዊ ሽብር ተገዢ እና ታዛዥ እንዲሁም የሽብር ሰባኪ ሆነው ዜጎችን በአደባባይ እያስግደሉ ዜጎች ከሞቱ በኋላ በሃይማኖታቸው ስር አት እና ደንብ እንዳይቀበሩ ተጽእኖ በማድረግ ለምድራዊው የጨቋኝ ምደብ ተባባሪ እና አስተባባሪ በመሆን ከባድ ወንጀል እየፈጸሙ ይገኛሉ። ስለዚህ በዜጎች ላይ የሚደርሱ በደሎች የማይቆረቁራቸው የሃይማኖት አባቶች ሊወገዱ ይገባል።
ማሳሰቢያ ፦ በዛሬው እለት በኦርቶዶክስ በእስልምና በካቶሊክ እና ከመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን የተዘዋወረው የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ቡድን ያሰባሰበውን ጉድ የያዘ መረጃ በቅርቡ በይፋ እናወጣዋለን ይጠብቁን። ‪