Tuesday, May 6, 2014

ያምማል! አፍንጫን ሲመቱት ዓይን ያለቅሳልና!! – በደቡብ ኮርያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድምጽ

May 5/2014
እኛ የኦጋዴን፣ የኣማራ፣የኦሮሞ፣የትግራይና የደቡብ ብሄር ተወላጆች ኣዲስ ኣበባን ለማስፋፋት በሚል ሽፋን በኣዲስ ኣበባ ዙሪያ የሚገኙ ድሃ የኦሮሞና ሌሎች ገበሬዎችን ግፍ በጥብቅ የምናወግዝ ሲሆን በቅርቡ በሃረማያ፣ በኣምቦ እና በሌሎች ኣካባቢዎች የሚኖሩ የኦሮሞ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የኢትዮጵያ መንግስት የወሰደውን ግድያና በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን ሊገልጹ በወጡ ተማሪዎች ላይ እየተወሰደ ያለውን የድብደባና የማጉላላት ዘመቻ በጥብቅ እናወግዘዋለን። ገዳዮቹም የጊዜ ጉዳይ እንጂ በፍትህ ፊት ቀርበው የእጃቸውን እንደሚያገኙ ኣንጠራጠርም።
እኛ ኢትዮጵያዊያን ልብ ልንል የሚገባው ጉዳይ ባለፉት ዘመናት እንደታዘብነው የኢህዓዴግ መንግስት ሲያሻው ብሄር እየለየ ሲያሻው በጅምላ ሰላማዊና ለውጥ ፈላጊ ዜጎችን ሲያሰቃይ ሲገድል ቆይቱኣል። ኣንዴ ኦሮሞን፣ ኣንዴ ደቡብ ሲዳማን፣ ኣንዴ ኣማራን፣ ኣንዴ ኦጋዴንን፣ኣንዴ ጋምቤላን ወዘተ ሲያጠቃ ተላላ ሆነን የተጠቃው ቡድን ብቻ ለብቻው ትንሽ ጮሆ ዝም ስለሚል የግፉ ጊዜ ሊረዝምብን ችሏል። ኣሁን ግን የኢትዮጵያ ህዝብ የመንግስትን የከፋፍለህ ግዛው ዘዴ ሊነቃበትና ኣፍንጫን ሲመቱት ኣይን ያለቅሳል እንደሚባለው ኣንዱ ሲጠቃ ሌላውም ሆ! ብሎ በመነሳት ይህንን ኣስከፊና በዓለም የሌለ ብሄርተኛ ኣገዛዝ ኣሽቀንጥሮ መጣል ይገባዋል።በሌላ በኩል የኦሮሞ ወገኖቻችን ያነሱትን የፍትህ ጥያቄ ለማጣመምና ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት የኢህዓዴግ ካድሬዎች ሊሯሯጡ እንደሚችሉ እየተገነዘብን ይህንን ጉዳይ የኦሮሞ ተማሪዎች ይስቱታል ብለን ኣናምንም። መንግስት በተለይ በኣሁኑ ሰዓት የቀለም ዓብዮት ሊነሳብኝ ይችላል የሚል ትልቅ ስጋት ስላለበት ህዝቡን በሃይማኖትና በብሄር በመከፋፈልና ከፍተኛ የሆኑ የፍትህና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች በጋራ እንዳይነሱ ስለሚፈልግ ብሄርተኝነትንና ጠባብነትን ለብሶ እንደለመደው እያጋጨ በስልጣን ለመቆየት መፍጨርጨሩ ኣይቀርምና በማናቸውም ተቃውሞዎቻችን ውስጥ ለወያኔ እድል ፈንታ መስጠት የለብንም።
በሌላ በኩል ለውጥ ለማምጣት የሚታገሉ ዴሞክራት የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ኣንድ ብሄር ተለይቶ ሲጠቃ ሁሉን
የማንቀሳቀስና ለጋራ ትግል ቆራጥ የጥሪ ደወል የማሰማት ሃላፊነት ኣለባቸው ብለን በጽናት እናምናለን።
የጀግናው ብእረኛ እስክንድር ነጋ ነገር፣ በቅርቡ ደግሞ ወደ ዘብጥ የወረዱት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ጉዳይ እንቅልፍ የነሳን ጉዳይ ነው። እነዚህ ወጣት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን በሰፊው እስር ቤት የሚገኘውን የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት እጦት ኑሮ ተምሳሊት ኣድርገው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ለጋ ወጣቶች ወደ እስር ቤት መውረዳቸው ከሰፊው እስር ቤት ወደ ጠባቡ መግባታቸውን ከማሳየቱም በላይ የታሰሩት ግለሰቦቹ ብቻ ሳይሆኑ ኣላማቸው በመሆኑ ሌላው የዞን ዘጠኝ እስረኛ የሆነው ኢትዮጵያዊ ሁሉ መንግስት የነጻነት ጥያቄውን ወደ ወህኒ መወርወሩን የሚያሳይ በመሆኑ ምን ያህል መንግስት በጭካኔ ስራው ሊቀጥል እንደ ወሰነ ያሳያል። በመሆኑም የነዚህ ወገኖች መታሰር፣ የፖለቲካው ምህዳር ምን ያህል እየጠበበ መምጣቱን፣ መንግስት ለህዝቡ ያለው ንቀት ጫፍ መርገጡን ያሳያል። በመሆኑም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በብሄርና በሃይማኖት ሳይከፋፈል የኦሮሞ ወገኖቻችንን ወቅታዊ ጥያቄና የጋዜጠኖቹን እስር ጉዳይ ወደ ኣጠቃላይ ፍትህና ዴሞክራሲ ጥያቄ ከፍ ኣርገን በያለንበት እንነሳ :: ዴሞክራሲና ፍትህ ሲሰፍን ጥያቄዎቻችን ሊፈቱ ይችላሉና ኢትዮጵያዊያን በጋራ ለለውጥ እንድንነሳ ወገናዊና ወንድማዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!
የማትከፋፈል ኢትዮጵያን ለትውልድ እናሳልፋለን!

አንድነት ፓርቲ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረገ! (ቪዲዮ እና ፎቶዎች ይዘናል)

May5/2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) – ዛሬ ሜይ 4 ቀን፣ 2014 ዓ.ም. የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ እጅግ በደመቀ ሁኔታ ተከናውኗል። የሰላማዊው ሰልፍ ጥሪ ለመጀመሪያ ግዜ በሸገር ሬድዮ የተላለፈ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ማስታወቂያውን “አላቀርብም” ብሎ የነበረው ኢቲቪ ከሰልፉ በኋላ፤ የተቃውሞውን ምስል ቆራርጦም ቢሆን በዜና እወጃው ላይ አቅርቦታል።
ሰልፉ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ የተደረገ ነው። ከዚህ ቀደም በሰበብ አስባቡ ሲከለከል የነበረው “የእሪታ ቀን” ዛሬ እውን ሲሆን፤ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሰልፉን ተቀላቅለውታል።
"መንገድ ዘግታችኋል ቶሎ ቶሎ ሂዱ" ፖሊስ። "መንገዱ ለኛ የተፈቀደ ነው ሰዓታችንን እንዴት እንደምንጠቀም እናውቃለን" አመራሮች
“መንገድ ዘግታችኋል ቶሎ ቶሎ ሂዱ” ፖሊስ።
“መንገዱ ለኛ የተፈቀደ ነው ሰዓታችንን እንዴት እንደምንጠቀም እናውቃለን” አመራሮች
አንድ ሁኔታውን የታዘቡ ግለሰብ እንዲህ ዘግበዋል። “የዛሬውን የአንድነት ፓርቲ ህዝባዊ ተቃውሞን በቦታው ተገኝቼ እንደታዘብኩት” ብለው ነው የጀመሩት… በዛሬው እለት ከጠዋቱ ሶስት ሰዐት ጀምሮ በርካታ የከተማይቱ እና የአካባቢው ነዋሪዎች የተገኙበት ታላቁ የእሪታ ቀን በድምቀት የተካሄደ ሲሆን በሠልፉ ላይ በርካታ መፈክሮች ተሰምተዋል፡፡
በዛሬው የሰላማዊ ሰልፍ ያሬድ አማረ ወኔ የተሞላባቸውን መፈክሮች ሲያሠማ የነበረ ሲሆን ከእርሱ መፈክሮች በተደጋጋሚ ከጓደኞቼ ጋር ፈገግ ሲያደርገን የነበረው “እመነኝ” የሚላት ቃል ናት፡፡
በሰለማዊ ሰልፉ ከኢ/ር ግዛቸው እስከ ወጣቱ ሃብታሙ አያሌው  ድረስ ያሉ ፖለቲከኞች በብዛት ይታዩ ነበር፡፡ ዳዊት ሰለሞን የአንድነት መኪና ውስጥ ሆኖ መረጃዎችን በማህበራዊ ድህረ ገፆች ሲያከፋፍል…. ነበር፡፡
ሁሉም ነገር ባዶ!
ሁሉም ነገር ባዶ!
ሰልፉ በአድዋ ድልድይ አድርጎ የመከላከያ ቤተሰቦች መኖሪያ ኢካባቢ በተለምዶ ሲግናል ተብሎ ከሚጠራው የመካላከያዎች ቤት ውስጥ የሚኖሩ የስርዐቱ ደጋፊዎች በተደጋጋሚ በመሀል ጣታቸው ሰልፈኛውን በመሳደብ ስሜታዊ ለማድረግ ሲሞክሩ ነበር፡፡
ሰልፉ በዚህ ሁኔታ ቀጥሎ ወረዳ 8 ፊት ለፊት በሚገኘው ሜዳ ላይ ኢ/ር ግዛቸው ባደረጉት ንግግር ተቋጭቷል፡፡
የአንድነት ፓርቲ የአመራር አባል የሆነው ሃብታሙ አያሌው ሲያደርግ የነበረውን ቅስቀሳ ለማየት ከዚህ በታች ያለውን ቪድዮ ይመልከቱ። 
እኛ ስለሰላማዊ ሰልፉ ተጨማሪ ዝርዝር ከምንሰጥበት የበለጠ እነዚህ ፎቶዎች እና መፈክሮች ብዙ ይናገራሉና… የአንድነትን ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ በፎቶ የተደገፈ እንቅስቃሴ፤ ከዚህ በታች  ይመልከቱ።

Monday, May 5, 2014

በላዛሪስት ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ድብደባ ደረሰባቸው (ነገረ ኢትዮጵያ )

May 5, 2014
ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ ፖሊስ ይዟቸው ላዛሪስ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ድብደባ ደረሰባቸው፡፡ በተለይ ‹‹አንተን የሚጠብቅ ፖሊስ የለንም ተብሎ›› ፈተና እንዳይፈተን የተደረገው ዮናስ ከድር ከፍተኛ ድብደባ የደረሰበት ሲሆን በአሁኑ ወቅት ዮናስ ከድር መንቀሳቀስ እንደማይችል አብረውት ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ገልጸውልናል፡፡
ሳምሶን የተባለና ኮድ ሁለት 16321 መኪና የሚይዝ ደህንነት ለምን አትፈታም እንዳለውና ዮናስም ‹‹የታሰርኩበት ምክንያት ህጋዊ ስላልሆነ ህጉ እስክልተከበረ ድረስ አልፈታም›› የሚል መልስ እንደሰጠው ታውቋል፡፡ ደህንነቱም ‹‹እኔ ነኝ እንዳትፈተን ያደረኩህ፡፡ ለእናትህም ደውዬ የነገርኳት እኔ ነኝ፡፡ ስትፈታም ወደ ዩኒቨርሲቲው ተመልሰህ አትገባም፡፡ ወደ ቤትህ ነው የምትመለሰው›› እንዳለው ታውቋል፡፡
በእስር ላይ የሚገኙ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላትም ድብደባ እንደረሰባቸው የታወቀ ሲሆን ደህንነቶችና የእስር ቤቱ ኃላፊዎች ተጨማሪ ድብደባ እንደሚደርስባቸው እያስፈራሩዋቸው መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ለአብነት ያህል በእስር ላይ የምትገኘው እየሩስ ተስፋው እዮኤል የተባለውን የእስር ቤቱ ኃላፊ ‹‹አንተ ነህ የምታስደበድበን›› ባለችው ወቅት ‹‹አሁንም ትደበደባላችሁ፡፡ ወጥታችሁ ተደብድባችሁ መመለስ ብቻ ነው ምንም አታመጡም›› እንዳላት ገልጻለች፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ታሳሪዎቹን ለመጠየቅና ሁኔታውን ለማጣራት ወደ እስር ቤት በሄደበት ወቅትም እስር ቤቱ ውስጥ የሚሰራ አንድ ፖሊስ ‹‹እኔ ነኝ ያስደበደብኩት፡፡ ምንም አታመጡም፡፡ ከፈለጋችሁ በደንብ እዩኝና ክሰሱኝ፡፡ አሁን ከእኔ ጋር መነጋገር አትችሉም ከግቢ ውጡ›› ብሎ እየገፈተረ እንዳስወጣቸው ገልጾአል፡፡
በላዛሪስት ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላለፉት ሁለት ቀናት በረሃብ አድማ ላይ መሆናቸውና በዚህም ምክንያት መዳከማቸው የታወቀ ሲሆን ፖሊስና ደህንነት በዚህ ሁኔታ ላይ ሆነው እንኳ ከፍተኛ ድብደባ እያደረሱባቸው መሆኑ እንዳሳዘነው አቶ ብርሃኑ ጨምሮ ገልጸአል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የርሃብ አድማ ከማድረጋቸውም በተጨማሪ 32 የሶማሊያ ስደተኞች ያለ ምንም ምግብ፣ ልብስና ውሃ መታሰራቸውን ገልጸው ችግራቸው እልባት እንዲያገኝ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡ በተመሳሳይ መታሰራቸው ህገ ወጥ ሆኖ እያለ 5500 ብር ከፍላቭሁ ውጡ መባላቸውን በመቃወም ‹‹አንፈታም!›› ማለታቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ብርሃኑ ‹‹ደህንነትና ፖሊስ ታሳሪዎቹ ላይ ከፍተኛ ድብደባ የሚያደርሱበት ምክንያትም ታሳሪዎቹ ህግን ለማስከበር በሚያደርጉት ጥረት ነው›› ብለዋል፡፡

open latter to honorable secretary of state John Kerry

May 5/2014
secretary





















By Ephrem Madebo (this article reflects the views and feelings of Ephrem Madebo, and Ephrem 
Madebo alone)

Mr. Secretary, last year when you went to Ethiopia, for the 50th anniversary of the OAU/AU, many Ethiopians including myself expected that your stay in Addis Ababa (other than the jubilee celebration) will include important issues such as human right abuse, torture, freedom, democracy and good governance in Ethiopia. In fact, most of us wanted to see you voice your disagreement with the dreadful human rights record of Ethiopia, or at least rebuke Ethiopia’s dictators whom your department annual report depicts as enemies of liberty, justice and democracy year after year. Mr. Secretary, I remember, in your speech to the AU leaders, you said the following words:
“The United States joins with so many other nations – the Secretary General, Russia, many other friends that are here – all to applaud the remarkable accomplishments, to work together and solve peace, security challenges, trade, defense, democracy, good governance, and human rights”
Mr. Secretary, when I read your government’s promise of working together with others to solve peace, democracy, good governance, and human rights challenges in Africa, I was elated and my expectation grew by the day because I know for sure these are the problems that plagued my native country Ethiopia. In May 2013, I was also moved when I saw your picture with Ethiopian blogger Nathaniel Feleke, one of the founders of the renowned Zone –nine bloggers. Mr. Secretary, last week when you went back to Ethiopia, Nathaniel Feleke whom you gave a big hug with chanting smile was being tortured inside the notorious Makelawi prison.
Mr. Secretary, a week ago, a journalist who actually happens to be a friend of Nathaniel Feleke asked you the following very important question:  Is your concern about press freedom real or "just lip service"  Here is how you addressed the question:  “I make clear to Ethiopian officials that they need to create greater opportunities for citizens. To be able to engage with their fellow citizens and with their government by opening up more space for civil society. And we shouldn’t use the anti-terrorism proclamations as mechanisms to be able to curb the free exchange of ideas” Well, Mr. Secretary, if this is not lip service then what?  Besides, what about if the Ethiopian officials are not willing to create greater opportunities for citizens, and instead they keep on arresting and killing innocent citizens like they have been doing since 1991?
Mr. Secretary, a week before your recent visit to Ethiopia started, the Ethiopian regime arrested Blue Party leaders and members. As if this was not enough, just days before your scheduled arrival to Addis, Ethiopia arrested journalists and bloggers, and on April 30 2014 when you were in Addis, the regime killed more than 30 demonstrators and wounded and arrested undetermined number peaceful demonstrators. Mr. Secretary, I still have to hear your public statement on this “In your face” act of the Ethiopian regime that your government has been baby-sitting for more than two decades?
Mr. Secretary, the US government has always been the first to condemn indiscriminate killings by totalitarian regimes around the globe for a long time. In addition to this, the department you lead (the US Department of State), has exposed dictators and human rights violators through its annual human rights reports. But, the US government has abnormally been silent when the TPLF regime has been killing peaceful citizens throughout its twenty two years stay in power.  I wonder how many Ethiopians should die before the US government goes beyond publishing annual reports and starts condemning and holding responsible the killing machine in Addis Ababa!
Mr. Secretary, the most recent killing in Ethiopia that ended the life of more than 30 innocent people took place while you were in Addis having good time with the very people that ordered the killing. Millions of Ethiopians who thought your visit will bring at least a temporary change of heart were staggered by the savage killing. Mr. Secretary, It is not just the killing that took millions of Ethiopians by surprise, it is the calculated timing of the arrest and the killing immediately before and after you set your foot on the soil of Ethiopia. Mr. Secretary, this is a deliberate move by the TPLF leaders who are seeking a divorce from the US and looking for another partner in Asia.
Mr. Secretary, while the people of Ethiopia were mourning their death, we heard that you met with PM Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom to discuss efforts to advance peace and democracy in the Horn of Africa. Mr. Secretary, to me this is like teaming up with Cuba to advance democracy in Latin America. It’s also ironic that the United States Secretary of State meets with vicious killers to discuss efforts to advance peace and democracy in the Horn of Africa, in a country where more than thirty people were killed by government forces. I have never seen and I don’t think I would ever see again or hear such insensitivity for a loss of humans, especially from a country that reacts vigorously when animals are mistreated by humans.
I remember, during the 2009 Iranian protest, President Obama condemned the violence against the protesters and said the following two statements that have been travelling around the globe ever since he said them:  “It would be wrong for me to be silent” - “The protesters in Iran will be 'on the right side of history’ ”.  Mr. Secretary, does the President’s silence when more than 30 Ethiopians were killed by the Ethiopian regime mean that – it would be right for him to be silent? What about the protesters in Ethiopia? Are they in the wrong side of history?
Dear Mr. Secretary, its geopolitical location, large population size (Christian & Moslem) and diverse ethnicity has made Ethiopia a strategically placed country in the Horn of Africa. If Ethiopia plays its hand wisely, it can be a critical force for good in the region. Unfortunately, ruthless dictatorships that ruled over Ethiopia for the past 23 years have darkened the fate of their own people let alone playing a positive role in democratizing the Horn of Africa.
We believe the relationship between Ethiopia and the United States has to be reconstituted on the basis of shared values of freedom, democracy, and promotion of mutual interests. To realize this, the United, and other democratic countries need a strong democratic partner in the Horn of Africa. The Horn of Africa is a volatile region characterized by political instability, and it is no secret that the TPLF dictators are one of the architects of instability in the Horn of Africa.
Dear Mr. Secretary, from all of its actions, particularly since 2005, it is clear that the TPLF regime has closed all avenues for a peaceful democratic opposition and is determined to stay in power by force including committing the most heinous crimes against its own people. The extra judicial killings in different parts of the country, the 2005 massacre, and the genocide in Gambella are glaring examples of crimes committed by a regime which once was praised as the “Hope” of Africa.  Today, it is obvious that Ethiopia’s is not and cannot provide a trusted leadership and the democratic credentials to be a credible partner to the United States and the international community at large. The TPLF regime has become an embarrassment to its own people and to the international community. It is high time for the United States and the international community to embrace change in Ethiopia.

የአራቱ ሃዋርያት በትግራይ ጉብኝት አነጋጋሪ ሆኗል

May5/2014
ከአስገደ ገ/ስላሴ፣ መቐለ

ሰሞኑን ባልተለመደ መንገድ ከትግራይ ክልል የሰልጣን መዋቅር እርከን ወጣ ያለ የክልሉን ስልጣን የተጋፋ (የነጠቀ) የስለላ ስራ የሚመስል እንቅስቃሴ ከ23 አመት የህ.ወ.ሃ.ት አገዛዝ በኃላ አራት አዛውንት የለውጥ ሃዋርያት መስለዉ በመላው ትግራይ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ ከዛም አልፎ በቀበሌ ከተሞች ሳይቀር በልዩ ሃይል ታጅበዉ እየዞሩ ሰንብተዋል።

የነዚህ ሃይል ሃዋርያት ጉብኝት አላማዉ ለህዝቡና የክልል መዋቅር ሰራተኞች ለህ.ወ.ሃ.ት ታጋዎች ግልፅ አልነበረም። ነገር ግን እንቅስቃሴአቸዉ በ3ትመንገድ ይፈፅሙት ጀመሩ። ከነዚህም አንደኛ በየከተማዉ ያለዉ ከንቲባ ስብሰባ አስጠርተዉ ከተሰብሳቢዉ ህዝቡ ላይ ችግር ምን አለ፤ ነፃ ሁናችሁ ንገሩንና ችግሩን አብረን እንፈታዋለን። ሁለተኛ ከነዋሪዎች ቤት ለቤት እየዞሩ የስለላና የመረጃ አሰባሰብ ግለሰቦች ን በማነጋገር ያለዉን ችግር ይጠይቃሉ። ሶስተኛ በ17ትአመቱ የትጥቅ ትግል ጊዜ ልጆቻቸዉ የሞቱባቸዉ አዛውንት ወላጆች ነባር ሚሊሻዎችና ነባር የፓርቲ አባላት ለነበሩና ነባር ታጋዮች የነበሩ የጦር አካል ጉዳተቾች በተናጠል አነጋግረዋል፤ ይህ ተግባር በሁሉም ከተሞችና ገጠሮች ይሰሩት ነበር።

  Read more http://www.ethiomedia.com/16file/aratu_hawaryat.pdf

የአንድነት ፓርቲ ያካሄደው ሠላማዊ ሠልፍ

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ እሁድ፤ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓም «የእሪታ ቀን» በሚል አዲስ አበባ ውስጥ የተቃውሞ ሠላማዊ ሰልፍ አካሄደ። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተለያዩ ብሶቶችን የሚያንፀባርቁ መፈክሮች፥ የተሰሙበትና አልባሳትም የታዩበት እንደነበር የደረሰን ዘገባ ይጠቁማል።
ሰልፈኞቹ፤ መንግሥት የመብራት፣ የስልክ፣ የውሃና ሌሎች የመሰረተ-ልማት አቅርቦቶችን እንዲያሻሽልና መልካም አስተዳደርን እንዲያሰፍን ጠይቀዋል። የታሰሩ ጦማሪያን፣ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱም አሳስበዋል። የአንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በሰልፉ ላይ ባሰሙት ንግግር፤ ባለፉት ቀናት በተለያዩ አካባቢዎች፣ ዩኒቨርስቲዎች እና ትምህርት ቤቶች፤ የተካሄደዉ የግድያ የድብደባ እና የእስራት እርምጃዎችን «ግዙፍ የሠብዓዊ መብት ጥሰቶች» ሲሉ በጥብቅ አዉግዘዋል።
በያዝነዉ ሳምንት መጀመርያ አዲስ አበባን የጎበኙት የአሜሪካን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ኢትዮጵያ ለሲቪክ ማኅበራትና ለጋዜጠኞች የተሻለ ነፃነት እንድትሰጥ መጠየቃቸዉ እና ባለፈዉ ሳምንት ማለቂያ የታሠሩት የድረ-ገፅ ጸሀፍትና ጋዜጠኞች ጉዳይም እንዳሳሰባቸዉ መግለፃቸዉ ይታወቃል። ጋዜጠኞች በህትመት፤ በኢንተርኔትም ሆነ በትኛዉም ዓይነት መገናኛ ብዙሃን የሚያከናዉኑት ኅብረተሰቡን እንደሚያጠናክር፤ እንደሚያነቃቃና ፤ለዴሞክራሲም መጠናከርና ድምፅ ሊሆን እንደሚችልም ኬሪ መግለፃቸዉ ይታወሳል። 

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተለያዩ ብሶቶችን የሚያንፀባርቁ መፈክሮች እና አልባሳትም የተሰሙበትና የታዩበት እንደነበር የደረሰን ዘገባ ይጠቁማል። ሠልፉን በቦታው ተገኝቶ የተከታተለው ወኪላችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር የሚከተለውን ዘገባ አጠናቅሮ ልኮልናል።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምፅ ማጫወቻውን ይጫኑ። 
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC


Sunday, May 4, 2014

በማእነደ ሁልጊዜው ሁሉ ህገ መንግስታዊ መብቶቻችን መጠየቅ እንቀጥላለን ሰርና በመደብደብና በመግደል የአገር ችግር አይፈታም !!!!!

May 4, 2014

ክቡራን የዞን ዘጠኝ ነዋሪያን

ሳምንቱ በአራማጅነት ቆይታችን ከነበሩን ጊዜያት መካከል በጣም ከባድ ሆኖ አለፈ። የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጅ ጋዜጠኛ ጓደኞቻችን ከታሰሩ 7 ቀናትን አሳለፋ፡፡ በሳምንቱ ውስጥ ቤተሰብና የህግ ባለሞያ ሳያገኛቸው እሁድ ቀን ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከመስማት ውጪ አያያዛቸውንም ሆነ ያሉበትን የጤንነት ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ እስካሁንም ቤተሰብም ሆነ የህግ ባለሞያ እነዲያያቸው አልተፈቀደም፡፡ ይህ በግልጽ ህገ መንግስቱን የሚጥስ የምርመራ ሂደት በማእከላዊ ሲካሄድ አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ በፌት የነበሩ የፓለቲካ እስረኞችም በተመሳሳይ ሁኔታ የመታየት መብታቸው ከማእከላዊ ጀምሮ ተነፍጎ አሁንም ቤተብሰብም ሆነ ወዳጅ እነዳይጎበኛቸው የተደረጉ እንዳሉ ይታወቃል ፡። ዞን 9 ከመጀመሪያ ዘመቻዎች አንስቶም ህገመንገስቱ አንዲከበረ ስንጠይቅ መቆየታችን ይታወቃል፡። ይህ መሆኑ ሳያንስ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን ሲጠቀሙ የነበሩ (ሶስተኛው የዞን ዘጠኝ ዘመቻ) የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች እስር የአካል ጉዳትና ሞት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ይህ በመላው አገሪትዋ እየታየ ያለውን ተቃውሞ መንግስት ምላሽ እየሰጠ ያለበት መንገድ አሳሳቢ አስፈሪና አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ ሳምንቱንም በሰብአዊ መብቶች ረገድ በጣም የከፋ ያደርገዋል፡፡Zone 9 bloggers
መንግስት የዞንዘጠኝ አባላትንና ጋዜጠኞቸን ሰርተዋል ብሎ ያቀረበው ወንጀል በማህበረሰብ ሚዲያ በመጠቀም ህዝብን ለብጥብጥ ማነሳሳት ነው ሲል የመንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው በጻፉት ሳይሆን በወንጀል በመሰማራታቸው ነው የታሰሩት ብለዋል፡፡ ወንጀሉ ፓሊስ እንዳቀረበው ደግሞ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥን የማንሳት ተግባር ከአገር ውጨ ከሚገኝ ራሱን ከሰብአዊ መብት ብሎ ከሚጠራ ተቋም ጋር ተባብረው ብጥብጥ ማስነሳት ነው ብሎታል ፡፡ ክሱ በአጭሩ ሁለት ነገሮችን ይይዛል፡፡ አንደኛው በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማስነሳት ሲሆን ሁለተኛው በሃሳብና በገንዘብ ከውጪ ድርጅቶች ጋር መተባበር ነው ፡፡
ማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ?
በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማንሳት የሚል ክስ ለማቅረብ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ የሚያስበሱ መልእክቶቸን ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ ማንኛውም የዞን 9 ነዋሪያን እነደሚመሰክሩት ህገ መንግስታዊ መብቶች እነዲከበሩ ከመጠየቅና መንግስትን የሚተቹ ጽሁፎችን ከማቅረብ ባለፈ አንድም የዞኑ ስራ ለብጥብጥ እና ለሁከት ምክንያት ለመሆን የሚበቃም አይደለም፡፡ ይህንነ ለመረዳት የዞኑን ዘመቻዋች እና ጽሁፎች ማየት ብቻውን የክሱን አስቂኝነት ለማስረዳት ይበቃል፡፡ እስከዛሬ በጻፍናቸው የመንገስት ትችቶች ካልሆነ በስተቀር ባነሳሳናቸው ብጥብጦች አንታወቅም ፡፡ ለዚያም ነው በጽሁፋቸው አይደለም የታሰሩት የሚለውን የመንግሰት ማስተባበያ አስቂኝ የሚያደርገው ፡። በጽሁፍ ካልሆነ በምንድነው የዞን 9 አባላትን እንድ ላይ እንደቡድነ ሰብስቦ መክሰስ የሚቻለው??
ከውጨ ድርጅት ጋር መተባበር
ዞን 9 ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት ሁለት አመታት በነበረው ቆይታ የተለያዩ አጋርነቶችነ ከተለያዩ አካላት ጋር ፈጥሮአል፡። በዚህም በተለያየ ጊዜ እነደግለሰብም አንደቡድን ተወካይ በመሆን አባላቱ አገሪትዋ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብጥ ጥሰት አያያዝ አስመልክቶ ለተለያዩ ቦታዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ ኢንተርኔት ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደርጋቸውን አስተዋእጾም አስመልክቶ በቡድንም በነጠላም በተለያዩ ቦታቸዎች ላይ በመገኘት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡ ይህ መንግስት ሲፈልግ የሚፈቅድላቸው ሲፈልግ ወንጀል የሚያስመስለው ተግባር ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጲያዊ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ዜጎች በመጓዛቸው ስራቸውን እና ልምዳቸውን በማካፈላቸው እነዲሁም ራሳቸውን ብቁ በማድረግ የሚሰሩትን የሰብአዊ መብት እነቅስቃሴ ለሌሎች መናገራቸውን ወንጀል ለማስመሰል የሚደረገውን ጥረት አሁንም ቢሆን እንደዞን 9 አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ ከዚህ በፌትም እነደተናገርነው በህግ እስካልተከለከለ ድረስ ህጋዊ እንቅስቃሴዎቸን መንግስት ስላልወደዳቸውና ህገ ወጥ ስላስመሰላቸው የምናቆምበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ሁሉም የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆች በፓርላማ በህገ ወጥነት ከተፈረጁ ተቋማት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አልነበራቸውም የላቸውምም፡። ለዞን ዘጠኝ ስራም ምንም አይነት የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተን አናውቅም፡፡ (በመሰረቱ የፋይናንስ ድጋፍ የማያስፈልገው የበጎ ፍቃደኝነት ስራ ነው የምንሰራው ) ከዚያ ውጪ ግን በፓርላማ ህገ ወጥ እስካልተባሉ ወይም ከልካይ ህግ እስካልመጣ ድረስ ከተለያዩ በተባበሩት መንግስታት እውቅና ካላቸው የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት ወንጀል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አንቀበለውም፡።
አንዳንድ አስቂኝ የመንግስት ወዳጆች በህቡህ ተደራጅተው የሚል ክስም ሲለጥፉብን ሰምተናል፡፡ ህቡህ ማለት ምን ማለት እነደሆነ ትርጉሙን እንዲያጣሩ ከመጠየቅ ባለፈ ምንም የምንጨምረው ነገር የለንም ፡፡ ባለፉት ሁላት አመታት ቆይታችን ፎቶአችን የሚታይ ሙሉ ህጋዊ ስማችን የሚታወቅ አገር ውስጥ የምንኖር ኢንተርኔት ላይ የተናገርነውን በግንባር የምንደግም ህጋዊ ዜጎች ነን፡። ከዞን ዘጠኝ እሴቶች መካከልም አንዱ ለተናገሩትም ሆነ ለሚያስተላልፉት መልእክት ሙሉ ሃላፌነትን መውሰድም ጭምር ነው ፡፡ በመሰረቱ ኢንተርኔት ላይ ቡድን መመስረት በየትኛውም ህግ የማይከለከል ህጋዊ ተግባር መሆኑን ለመንግስትና የመንግሰት እርምጃ ለደገፉ ለማስታወስ አንወዳለን፡፡
ባለፉት ቀናት ስንናገር እንደነበረው መንግሰት የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆችን እነዲፈቱ መጠየቁን አሁን ደግሞ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም በጋራ ድምጻችንን ማሰማታችንን እንቀጥላለን፡፡ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እየተደበደቡና እየሞቱ የዞን9 አባላትን እስር ብቻ ለይተን ዘመቻ ማድረጉን ሃላፌነት የሚሰማው ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም ሁለቱ ጉዳዪች ላይ አተኩረን የሚመለከተው አካል ሃላፌነቱን እነዲወጣ ግፌት ለማድረግ እንሞክራለን፡። ዞን ዘጠኝ እንቅስቃሴን በማሰር ለመገደብ ቢሞክርም ብዙ የዞኑ ነዋሪያን ጋር በመተባበር ከምርጫ ጋር የተያያዙ ስራዎችን የመስራት እቅዳችነን አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡።
ከነገ ሚያዝያ 25 ጀምሮ የዞን 9 ጦማርያንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን መፈታት እነዲሁም በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የምን ቃወምበት መጠነ ሰፌ ዘመቻ እንጀምራለን፡፡ እስካሁን በተናጠል ላሳያችሁን ህብረት በከፍተኛ ሁኔታ እያመሰገንን በጋራ የአገራችንን “ዞን ዘጠኝተነት” በመቃወም ህብረታቸንን እናሳይ ፡።
የዘመቻውን ዝርዝር በሚቀጥሉት ፓስቶች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

አራት የአንድነት ፓርቲ የአመራር አባላት ታሰሩ

May 3/2014-
ርድ ቤት ቀርበው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)አራት ከፍተኛ አመራሮች ሚያዝያ 22 እና 23 ቀን 2006 ዓ.ም. በፀጥታ ኃይሎች መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ሁለት አመራሮች በ1,500 ብር ዋስትና መለቀቃቸውም ተገልጿል፡፡ 
አንድነት ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም. ለሚያደርገው ሰላማዊ ሠልፍ ለቅስቀሳ ወጥተው የነበሩት የፓርቲው የአዲስ አበባ ልዩ ዞን ሰብሳቢ አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን፣ የሕዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባልና የምክር ቤቱ አባል አቶ ዘለዓለም ደበበ፣ እንዲሁም የፓርቲው ልሳን የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ነብዩ ኃይሉ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ተይዘው መታሰራቸውን፣ የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ልዩ ዞን የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል መታሰራቸውን አስረድተዋል፡፡

ሦስቱም ግለሰቦች በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መታሰራቸውን የገለጹት አቶ ሀብታሙ፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ሜክሲኮ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ቀርበዋል፡፡

በመሆኑም ፖሊስ አባላቱ ፈቃድ ሳይዙ በሕገወጥ መንገድ ሲቀሰቅሱና ሲረብሹ መገኘታቸውን ገልጾ፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት 11 ቀናትን መጠየቁን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡ የታሰሩት የፓርቲው አባላት ለቅስቀሳ የወጡት፣ ለአስተዳደሩ አሳውቀውና ይሁንታ አግኝተው መሆኑን ቢያስረዱም፣ ፖሊስ ፈቃድ ያገኙት ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ እንጂ ለቅስቀሳ አለመሆኑን በማስረዳት የጠየቀው ጊዜ እንዲፈቀድለት በድጋሚ ሲጠይቅ ጊዜው እንደተፈቀደለት አስረድተዋል፡፡ ከፓርቲው አመራሮች ጋር የተከራዩት የመቀስቀሻ ተሽከርካሪ  ከነሾፌሩ የታሰሩ ቢሆንም፣ ተሽከርካሪው 500 ብር ተቀጥቶ ሲለቀቅ ሾፌሩ ግን መታሰሩን አቶ ሀብታሙ አክለዋል፡፡

ሌላው የፓርቲው አባላት በቅስቀሳ ላይ እያሉ የታሰሩት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ ሀብታሙ አባላቱ አቶ አሸናፊ አሳመረ፣ አቶ ኤፍሬም ሰለሞንና አቶ ስንታየሁ ቸኮል እንደሚባሉ ገልጸዋል፡፡

እነሱም የታሰሩት በቅስቀሳ ላይ እያሉ መሆኑን የገለጹት ሕዝብ ግንኙነቱ በአካባቢው ባለው ፍርድ ቤት ቀርበው በፖሊስ ጣቢያ አካባቢ የቅስቀሳ ፈቃድ ሳይዙ ሲቀሰቅሱ ፖሊስ ማግኘቱን ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ፣ ፍርድ ቤቱ ዋስትና የማይከለክል መሆኑን በመግለጽ፣ እያንዳንዳቸው 1,500 ብር ከፍለውና የራሳቸውን መታወቂያ ኮፒ አስይዘው እንዲፈቱ ማዘዙን ተናግረዋል፡፡

ግብፅ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ የሚከታተል ሳተላይት ማምጠቋን ገለፀች


May 3/2014

ግብጽ 43 ሚሊዮን ዶላር ያወጣችበትንና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ የግንባታ ሂደት በአየር ላይ ሆኖ እየተከታተለ መረጃ የሚሰጣትን ወታደራዊ ሳተላይት ከሁለት ሳምንት በፊት ማምጠቋን በይፋ እንደገለፀች   አህራም ኦንላይን ዘገበ፡፡

ኢጂሳት የሚል ስያሜ የተሰጠው ሳተላይቱ፤ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቁመት፣ ውሃ የመያዝ አቅምና የሚለቀውን የውሃ መጠን የተመለከቱ መረጃዎችን እየተከታተለ የሚያቀርብ እንደሆነ የገለጹት የግብጽ ብሄራዊ የሪሞት ሴንሲንግና ስፔስ ሳይንስስ ባለስልጣን ምክትል ፕሬዚደንት አላ ኤልዲን ኤል ናህሪ፣ ሳተላይቱ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከሚከናወንበት አካባቢ በተጨማሪ፣ የአባይ ወንዝ በሚፈስባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በማተኮር፣ ከፍተኛ የጥራት ደረጃ ያላቸው ጠቃሚ ፎቶግራፎችን እያነሳ እንደሚልክ  ሰሞኑን በካይሮ በተካሄደ ሴሚናር ላይ ተናግረዋል፡፡

ለሁለት ወራት ከሚቆይ የሙከራ ጊዜ በኋላ፣ በመጪው ሰኔ ወር አጋማሽ ላይ መደበኛ ስራውን ይጀምራል የተባለው  ሳተላይቱ፣ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እየተከታተለ ለግብጽ ባለስልጣናት መረጃ ከማቀበል ባለፈ፤ የኮንጎ ወንዝን ተፋሰስ በመከተል በሚያነሳቸው ፎቶግራፎች፣ ወንዙን ከአባይ ጋር ለማገናኘት ታስቦ የተረቀቀውን የፕሮጀክት ሃሳብ ውጤታማነት በተመለከተ የራሱን ፍተሻ ያደርጋል ተብሏል፡፡ የግብጽ መንግስት ሳተላይቱ ከሚያቀርባቸው መረጃዎች የሚያገኘው ውጤት፣ ከኢትዮጵያ ጋር በግድቡ ዙሪያ የጀመረው ክርክር ተጠናክሮ እንዲገፋ እንደሚያደርገው ያምናል ያሉት አላ ኤልዲን ኤል ናህሪ፣ ግድቡን ከታለመለት የሃይል ማመንጨት ስራ ውጭ ለማዋል በኢትዮጵያ በኩል ማናቸውም አይነት እንቅስቃሴዎች ቢደረጉና ጉዳዩ ወደ አለማቀፍ ግልግል የሚያመራ ከሆነም፣ የግብጽ መንግስት ይሄንኑ የሳተላይት መረጃ ለክርክሩ የህግ ድጋፍ ለማግኘት እንደሚጠቀምበት አል አህራም ለተባለው  ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡

አል አረቢያ ድረ-ገጽ በበኩሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ላይ የምታነሳቸውን ቅሬታዎች ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለማቅረብ ከወሰነች፣ ኢትዮጵያ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ባለፈው ሳምንት መናገራቸውን ዘግቧል፡፡

የግድቡ መገንባት የአባይን ወንዝ የውሃ መጠን በመቀነስ ተጎጂ ያደርገናል በሚል ተቃውሞአቸውን በተደጋጋሚ የገለፁት የግብጽ ባለስልጣናት፣ ሳተላይቱ የሚሰጣቸውን መረጃ መሰረት በማድረግ የሚደርሱበት ውጤት፣ በግድቡ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር በሚያደርጉት ክርክር ይዘውት የቆዩትን አቋም እንደሚያጠናክርላቸው ተስፋ ማድረጋቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡ የግብጽን ሳተላይት ማምጠቅ በተመለከተ፣ አንዳንድ ድረገጾች ቀደም ብለው መረጃ ያወጡ ቢሆንም፣ የአገሪቱ መንግስት ስለጉዳዩ ይፋዊ መግለጫ ሲሰጥና ድርጊቱን ሲያምን የአሁኑ የመጀመሪያው  ነው፡፡

Saturday, May 3, 2014

በዩኒቨርስቲዎች በተነሳው ተቃውሞ በርካቶች ሞቱ

May 3/2014


የከፋ ጉዳት የደረሰው በአምቦ፣መደወላቦ እና ሐረማያ ነው
ተቃውሞው እስከ ሃሙስ በመንግስት ሚዲያ አልተነገረም

አዲስ አበባንና በዙሪያዋ የኦሮሚያ ከተሞችን በማካተት የተዘጋጀውን የጋራ ማስተር ፕላን የሚያወግዙ የክልሉ ተማሪዎች፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ሲያካሂዱት በሰነበቱት ተቃውሞ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግጭት የበርካታ ሰዎች ህይወት ጠፋ፡፡ በትንሹ ወደ መቶ የሚጠጉ ሰዎችም እንደቆሰሉና ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል፡፡ በተቃውሞዎቹ ዙሪያ ቀጥተኛ ዘገባ ሲያስተላልፍ የነበረው የመንግስት ሚዲያ ሐሙስ እለት ከመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት የወጣውን መግለጫ ያቀረበ ሲሆን በአምቦና በመደወላቡ 3 ተማሪዎችን ጨምሮ 7 ሰዎች እንደሞቱ አትቷል፡፡ ሲኤንኤንና ሌሎች የሚዲያ ተቋማት በርካታ ሰዎች መሞታቸውን በመጥቀስ የተለያዩ ዘገባዎችን ያሰራጩ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ 30 ሰው መሞቱን እንደተናገሩ ጠቅሰዋል፡፡ የእግር ኳስ ጨዋታ በቴሌቭዥን የሚመለከቱ የሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በተወረወረ ፈንጂ አንድ ተማሪ እንደሞተና 70 ሰዎች እንደቆሰሉም መግለጫው አስታውሶ፤ ዩኒቨርስቲዎች እንደተረጋጉ መንግስት ቢገልፅም በስልክ ያነጋገርናቸው የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራን ግን ግጭቱና ውጥረቱ እንዳልበረደ ተናግረዋል፡፡

በአዳማ፣ በጅማ፣ ሃሮማያ፣ አምቦ፣ ነቀምት፣ መደወላቡ እና ድሬደዋ ዩኒቨርሲዎች በተነሳው ተቃውሞ እስካሁን ከተገለጸው በላይ የሞትና የአካል ጉዳት በተማሪዎች ላይ እንደደረሰ የየአካባቢው ምንጮች የገለፁ ሲሂን፣ በርካቶች እንደታሰሩም ጠቁመዋል፡፡ በሃሮማያ ፍንዳታ የሞቱት ተማሪዎች ሁለት መሆናቸውን የገለፁ ምንጮች፣ በብሄር ተወላጅነት የተቧደኑ ተማሪዎች ጎራ ለይተው በፈጠሩት ግጭት በርካታ ተማሪዎች እንደተደባደቡ ተናግረዋል፡፡

አዲስ አበባንና በዙሪያዋ ያሉ ከተሞችንም ያስተባብራል ተብሎ የጋራ ማስተር ፕላን የተዘጋጀው ከከተማ አስተዳደርና ከአሮሚያ ክልል መስተዳደር ተውጣጥቶ በተቋቋመ ቡድን ሲሆን፤ ፕላኑን የተቃወሙ ተማሪዎች “የኦሮሚያ መሬትን የሚቆርስ ህገ መንግስቱን የሚፃረር ነው፡፡ ሃገራችንን ትተን ወዴት እንሂድ!” የሚሉ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡

ማክሰኞ ማታ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው ተቃውሞ፤ ረቡዕ እለት ከምሳ በኋላ ረገብ ቢልም ማተሚያ ቤት እስከገባንበት ሰዓት ድረስ ውጥረቱ እንደነበር ለማወቅ ችለናል፡፡ የመማር ማስተማር ትምህርት እንደተቋረጠና ወደ ግቢ መግባት እንጂ መውጣት እንደተከለከለ የገለፁት ምንጮች፤  አንዳንድ ተማሪዎች በአጥር ሾልከው እየወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ ረቡዕ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ በቴሌቪዥን እግር ኳስ ሲመለከቱ የነበሩ ተማሪዎች ላይ የፈንጂ ጥቃት ከደረሰ በኋላ የተቀሰቀሰው ሁከት ብሄር ወደ ተቧደነ ግጭት እንደተለወጠ የጠቆሙት ምንጮች፤ ግጭቱ ከፌደራል ፖሊስ ከቁጥጥር ውጪ እስከ አርብ ድረስ እንዳልበረደ ጠቁመዋል፡፡

ከዩኒቨርሲቲው መውጣትና መግባት ተከልክሎ ቢቆይም፣ ወደ ቤተሰቦቻችን እንመለስ የሚሉ ተማሪዎች በመበራከታቸው ትናንት አርብ ከሰአት በኋላ ጀምሮ እንዲወጡ ተፈቅዷል፡፡

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያነሱት ተቃውሞ ከሌሎች የጠነከረ እንደነበር የጠቆሙት ምንጮች፤ ተቃውሞው ከዩኒቨርሲቲም ውጭ እንደተስፋፋ ገልፀዋል፡፡ 25ሺ ያህል ሰዎች ከተቃውሞ ወደ አደባባይ መውጣታቸው የተዘገበው አል አፍሪካ፤ ከባድ ግጭት መከሰቱን አትቷል፡፡ በተጨማሪ መረጃ ባይረጋገጥም፣ ከአካባቢው ነዋሪዎች ግን 30 ሰዎች መሞታቸውን ተናግረዋል ሲኤ ሲሴን ኤን የዘገበ ሲሆን፤ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሐሙስ ባወጣው መግለጫ የሟቾች ቁጥር 7 እንደሆነ ጠቅሶ በመደወላቡ ዩኒቨርሲቲ በተነሳው ተቃውሞ ከገለልተኛ ወገኖች ማረጋገጥ ባይቻልም መንግስት 3 ተማሪዎች መሞታቸውንና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስታውቋል፡፡ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጉዳት ስለመድረሱ የተባለ ነገር የለም፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ፤ ሐሙስ ጠዋት ተማሪዎች ወደ ግቢ መግባትም መውጣትም ተከልክለው ነበር፡፡ የፌደራል ፖሊስ አባላትም በቡድን በቡድን በአካባቢው ሲንቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን ከሰዓት ለተቃውሞ የተሰበሰቡ ተማሪዎች የተለያዩ መፈክሮችን አሰምተዋል፡፡

ከፖሊስ ጋር የተፈጠረ ግጭት ያልነበረ ሲሆን ተቃውሞ ሲያሰሙ የነበሩት ተማሪዎች ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር የሚወያዩበት መድረክ እንደሚዘጋጅ የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች መናገራቸውን ምንጮች ገልጸው፤ በዚሁ ምክንያት ከፖሊስ ጋር ግጭት አለመፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡

መንግስት በበኩሉ፤ ተቃውሞውና ግጭቱ ጥቂት ጸረ ሰላም ሃይሎች በሚያሰራጩት አሊባልታ ምክንያት የተፈጠረ ነው በማለት በሁከቱ ጉዳት መድረሱ እንዳሳዘነው ገልጿል፡፡

አንድነት ፓርቲ ትናንት “በአፅንኦት እናወግዛለን” ሲል ባወጣው መግለጫ፤ መሬት በግል አለመያዙ ብዙ ችግሮችን እያስከተለ እንደሆነ ገልጿል፡፡ የተቃውሞ ድምፅ በሚያሰሙ ሰዎች ላይ መንግስት የሚወስደውን እርምጃ እንደሚያወግዝም ፓርቲው አስታውቋል፡፡