Saturday, May 3, 2014

የጋዜጠኞችና የፀሐፊዎች እስር የአፈና ዘመቻ ነው በሚል ተወገዘ

May3/2014


ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችና የድረገፅ ፀሃፊዎች (ጦማሪዎች) በአንድ ጊዜ ተይዘው ለእስር ሲዳረጉ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው፡፡ እስሩን በመቃወም ኢንተርኔት ተጠቃሚ ኢትዮጵያዊያን ከእስከዛሬው ሁሉ የበለጠ ድምፅ ማሰማታቸውን ቢቢሲ የዘገበ ሲሆን፤ ዋና ዋናዎቹ ዓለማቀፍ የመብት ተሟጋችና የፕሬስ ነፃነት ተቋማት “የአፈና ዘመቻ ነው” በማለት አውግዘዋል በመንግስት ላይ ተፅእኖ እንዲያሳድሩ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጥሪ የቀረበላቸው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ጆን ኬሪ እስረኞቹ መፈታት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር በበኩላቸው ሀሳባቸውን በነፃነት በመግለፃቸው ብቻ ነው የታሰሩት በማለት የመንግስትን እርምጃ ተቃውመዋል፡፡

የአውሮፓ ህብረት ግን የፕሬስ ነፃነት ይከበር የሚል ጥቅል መግለጫ ከማውጣቱ በስተቀር ስለታሰሩት ሰዎች አላነሳም፡፡ የጋዜጠኞችና የፀሐፊዎች እስር አሳሳቢነት ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን በዓለም ደረጃ ሲያነጋግር ቢሰነብትም፣ የመንግስት አካላትና የመንግስት ሚዲያ አንዳችም መረጃ ያልሰጡበት ምክንያት አልታወቀም፡፡ ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች ላይ ክስ የሚቀርብ ከሆነ በእስር ማቆየት እንደማያስፈልግና በዋስ መለቀቅ እንዳለባቸው የፕሬስ ህጉ ላይ የተጠቀሰ ቢሆንም፤ ዘጠኙ ጋዜጠኞች ፀሐፊዎች የዋስ መብት አልተፈቀደላቸውም፡  

ባለፈው ሳምንት አርብ ምሽትና ቅዳሜ ካሉበት በፀጥታ ሃይሎች ተይዘው የታሰሩት ጋዜጠኞችና ፀሃፊዎች፤ ኢትዮጵያ ውስጥ አለመረጋጋትን ለመፍጠር አስበዋል የሚል ጥርጣሬ እንዳለው ፖሊስ ለፍ/ቤት ገልጿል፡፡ በዚህም ታሳሪዎቹ ከዓለም አቀፍ መብት ተሟጋች ተቋም ጋር በገንዘብና በሃሳብ በመተባበር ወይም በኢንተርኔት ማህበራዊ ድረገፆችን በመጠቀም ተንቀሳቅሰዋል-ብሏል ፖሊስ፡፡ የትኛው አለማቀፍ የመብት ተቋም እንደሆነ በስም ያልገለፀው ፖሊስ፤ ታሳሪዎቹ አለመረጋጋትን ለመፍጠር የፈፀሙት ተግባር ካለም ምን ምን እንደሆነ አልጠቀሰም፡፡ ፖሊስ የምርመራ ጊዜ እንደሚያስፈልገው በመጠየቁ በእስር እንዲቆዩ የተደረጉት ጸሐፊዎችና ጋዜጠኞች ከህግ ባለሙያ ወይም ከቤተሰብ ጋር እንዲገናኙ አልተፈቀደላቸውም ተብሏል፡፡

ሦስቱ ጋዜጠኞች፣ በቀድሞው አዲስ ነገር፤ የእንግሊዝኛው ፎርቹንና አዲስ ስታንዳርድ ላይ በፍሪላንሰርነት ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ የአዲስ ጉዳይ መፅሄት ከፍተኛ አዘጋጅ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ የቀድሞ አዲስ ዘመን ጋዜጠኛ ኤዶም ካሣዬ ናቸው፡፡ ኤዶምን ጨምሮ አቤል ዋበላ፣ ዘላለም ክብረት፣ በፍቃዱ ኃይሌ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፈ ብርሃኔ “ዞን ዘጠኝ” በመባል የሚታወቁ የድረገፅ ፀሐፊዎች (ጦማሪዎች) ናቸው፡፡

ግራ የገባቸው የጋዜጠኛ ማህበራት

መንግስት አፈናውን ለማጠናከር በአዲስ ዙር የእስር ዘመቻ እያካሄደ ነው በማለት ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋችና የፕሬስ ነፃነት ድርጅቶች ተቃውሟቸውን ቢገልፁም፣ የአገር ውስጥ የጋዜጠኞች ማህበራት በበኩላቸው ግራ በመጋባት ሲዋልሉ ነው የሰነበቱት፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ሊቀመንበር አቶ አንተነህ አብርሃም፤ ባለፈው ማክሰኞ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፤ “ታሣሪዎቹ ጋዜጠኛ ስለመሆናቸውና ከስራቸው ጋር በተገናኘ ስለመታሠራቸው ማጣራት ስላለብን፤ ለጊዜው ምንም ዓይነት የአቋም መግለጫም ሆነ ማብራሪያ ለመስጠት ይቸግረናል” ብለዋል፡፡

ከአንድ ቀን በኋላ ሐሙስ እለት ማህበሩ ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ ግን፤ መንግስት ጋዜጠኞቹ እና ጦማሪዎቹ ስለታሠሩበት ጉዳይ ይፋዊ መግለጫ አለመስጠቱ እንዳሣሠበው አመልክቷል፡፡ “በጉዳዩ ላይ የመንግስት ዝምታ አሳስቦናል፤ ከመንግስት የጠራ መረጃ እንፈልጋለን” ያሉት አቶ አንተነህ፤ “ፍ/ቤት ስለቀረቡበት ሁኔታም ከመንግስት የጠራ መረጃ አለማግኘታችንም ያስጨንቀናል” ብለዋል፡፡ ማህበራቸው እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ ጋዜጠኞች ህብረትና የአለማቀፉ የጋዜጠኞች ፌደሬሽን፣ የእስረኞቹን ጉዳይ በትኩረት እንደሚከታተሉት አቶ አንተነህ ገልፀዋል፡፡

በሌላ በኩል “ዩኔስኮ ጦማሪዎች ጋዜጠኞች አይደሉም ብሎ ፈርጇል፣ በኢንተርኔት የማህበራዊ ድረገፅ ሚዲያውም ሃላፊነት የሚሠማው አይደለም፤ ከዚህ አንፃር ለእነዚህ አካላት ጥበቃ ማድረግ እንዴት ይቻላል?” ሲሉ ይጠይቃሉ፤ አቶ አንተነህ፡፡
“ጋዜጠኞቹ የታሠሩት ከሙያቸው ውጪ በሆነ ጉዳይ ከሆነ መንግስት በህግ መጠየቅ ይችላል፤ ጉዳዩን ግን እንከታተላለን፡፡ ከሙያቸው ጋር በተገናኘ ከሆነም ጠበቃ አቁመን ከመከራከር ባለፈ፤ የአለማቀፍ ጋዜጠኞች ህብረትን አስተባብረን መንግስትን ስለጉዳዩ አጥብቀን እንጠይቃለን” ብለዋል አቶ አንተነህ፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር ሊቀመንበር አቶ መሠረት አታላይ በበኩላቸው፤ “እኛ በጋዜጠኝነት አናውቃቸውም፤ ጋዜጠኞችም አይደሉም፤ ብሎገሮች (ጦማሪዎች) ናቸው፤ በእነሱ መታሠር ጉዳይ እኛ የምናውቀው ነገር የለም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

“ሠሞኑን ከታሠሩት መካከል በጋዜጠኝነት የማውቀው ተስፋለም ወልደየስን ብቻ ነው” ያሉት የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞች ማህበር ሊቀመንበር አቶ ወንድወሰን መኮንን፤ “ስለ ዞን 9 ፀሀፊዎች የጠራ መረጃ የለኝም፤ ጦማሪዎች በዩኔስኮ ድንጋጌ መሠረት ጋዜጠኛ አይባሉም፣ ስለጦማሪያኑ መሟገት ቢቸግረንም ስለጋዜጠኛው እስር እና ስለጉዳዩ መንግስት ለህዝብ መግለጽ አለበት” ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በሽብርተኝነት እየተከሰሱ የተፈረደባቸው ጋዜጠኞችም፤ ለመንግስት ያቀረቡት የምህረት ጥያቄ ከግንዛቤ ገብቶ፤ ከእስር እንዲለቀቁ መንግስትን እንደሚጠይቁ አቶ ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡

ጋዜጠኞቹና ፀሃፊዎቹ መታሰራቸው እንዳሳሰበው የገለፀው አዲስ በመቋቋም ላይ ያለው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ)፤ መንግስት የታሰሩበትን ጉዳይ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግና ጋዜጠኞቹ እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡  

ጠንካራ የጋዜጠኛ ማህበር በሌለበት አገር፣ ጋዜጠኞችና ጦማርያን ለእስር መዳረጋቸው አሳዛኝ ነው ያሉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፤ ሃሳብን በነፃነት መግለፅ ባልተከበረበት ሀገር የፕሬስ ቀንን ማክበር ለውጭ መንግስታት ድጋፍ ማግኛ ካልሆነ በስተቀር ትርጉም የለሽ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ “የፕሬስ ቀንን ማክበር ያለበት ፕሬስ ነበር፤ ነገር ግን እንኳን ሊያከብር ህልውናውንም አላረጋገጠም” ብለዋል ምሁሩ፡፡

የጋዜጠኞቹ እና የጦማርያኑ እስራት ሃሳብን መግለፅ እንደ አደጋ የሚታይበት ጊዜ መምጣቱን አመላካች ነው ያሉት ዶ/ር ዳኛቸው፤ በውይይትና በክርክር፣ በውድድርና በፉክክር ሳይሆን የአንድን ቡድን ሃሳብ ብቻ የበላይ በማድረግ ሌላው ፀጥ እንዲል እየተደረገ ነው ሲሉ ይተቻሉ፡፡

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የህግ ባለሙያ በሰጡት አስተያየት፤ የመረጃ ነፃነትን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ፣ ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሃሳቡን የመግለፅ ነፃነት እንዳለው ይጠቅሳል ብለዋል፡፡ “ማንኛውም ሰው ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት የመሰለውን አመለካከት የመያዝ፣ ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ሃሳቡን የመግለጽ ነፃነት አለው፡፡ ይህ ነፃነት ከሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ወሰን ሳያደርግለት በቃል ሆነ በጽሑፍ ወይንም በህትመት በስነ ጥበብ መልክ ወይንም በመረጠው፣ ለማንኛውም የማሰራጫ ጣቢያ ማንኛውም ዓይነት መረጃ የመሰብሰብ፣ የመቀበል ሃሳብ ያካትታል፡፡ ነገር ግን የጦርነት ቅስቀሳዎች፣ ሰብዓዊ ክብርን የሚነኩ የአደባባይ መግለጫዎች በህግ የሚከለከሉ ይሆናል ይላል” ሲሉም የህግ ባለሙያው አስረድተዋል ፡፡

የጋዜጠኞቹንና ጦማሪያኑን መታሠር ተከትሎ መግለጫ ያወጣው አምነስቲ ኢንተርናሽናል፤ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን የማሠር ልምድ እንዳላት ጠቅሶ፤ በአዲስ የአፈና ዘመቻ የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማሪዎች  በአስቸኳይ እንዲለቀቁና አለማቀፉ ህብረተሰብም ግፊት እንዲያደርግ ጠይቋል፡፡

ተቀማጭነቱን በኒውዮርክ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) በበኩሉ፤ “ጋዜጠኞቹንና ጦማሪያኑን በማሠር የኢትዮጵያ መንግስት ሠላማዊ የሆነውን ሃሳብን የመግለጽ መብትን ወደ ወንጀል እየቀየረው ነው” በማለት ዘጠኙ ጋዜጠኞች በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡

“ዞን 9” በሚል የሚታወቁት ጦማሪያን፣ የተለያዩ ዜናዎችንና ትችቶችን የሚያቀርቡ፣ የሀገሪቱ የፕሬስ አፈና የወለዳቸው ስብስቦች ናቸው ያለው ይሄው ተቋም፤ በመንግስት በኩል በደረሰባቸው ወከባ ለበርካታ ወራት ስራቸው ተስተጓጉሎ እንደነበር ገልጿል፡፡ እንደገና ስራቸውን ለመጀመር ማቀዳቸውን በገለፁበት ሳምንት ነው የታሰሩት ብሏል ተቋሙ፡፡

ጋዜጠኞችን፣ የሚዲያ ተቋማትንና አሳታሚዎችን በአባልነት ያሰባሰበው የዓለም ፕሬስ ኢንስቲትዩት (IPI) በበኩሉ፤ ባለፈው ህዳር ወር የልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ እንደተላከ ገልፆ፤ ከመንግስት አካላትና ከጋዜጠኞች ጋር እንደተወያየ በመጠቆም፣ የአገሪቱ ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል፡፡ በሽብር ህጉ ሰበብ ጋዜጠኞች መታሰራቸውን ሲቃወም እንደነበር ተቋሙ አስታውሶ፤ አሁን እንደገና አዲስ የእስር ዙር መጀመሩን አውግዟል፡፡

ተመሳሳይ ውግዘት የሰነዘረው ሂዩማን ራይትስ ዎች በበኩሉ፤ ከአፍሪካ ውስጥ ከፍተኛ ግምት ከሚሰጣቸው አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗን ጠቅሶ፣ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ፤ የዲሞክራሲና የመብት አከባበርን እንደወትሮው ችላ ማለት አይኖርባቸውም ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ የፕሬስ ህግና የመረጃ ነፃነት አዋጅ በተዘጋጀበት ወቅት በመንግስት ፈቃድ በሙያ ምክርና በውይይት አስተባባሪነት እንዲሳተፍ የተደረገው አርቲክል 19 የተሰኘው ዓለም አቀፍ ተቋምም እንዲሁ እስሩን አውግዟል፡፡

ብዙዎች የመብትና የፕሬስ ነፃነት ተቋማት በኢትዮጵያ እንዳይሰሩ እየታገዱ ጥቂት መቅረታቸውን የገለፀው አርቲክል 19፤ ሳይታገዱ ከቆዩት ተቋማት መካከል አንዱ በመሆኔ የፕሬስ ነፃነትን በሚመለከት ለተባበሩት መንግስታት ሪፖርት የማቅረብ በሙያውና ህጋዊ ትንታኔ በዓለም ደረጃ ከፍተና አክብሮትን እንዳተረፈ የሚነገርለት አርቲክል 19፤ ለመንግስታት የህግ ማሻሻያ ሀሳብ በማቅረብና ለጋዜጠኛው የስልጠና ድጋፍ በመስጠት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ከመንግስት አካላት ጋር ፊት ለፊት ፍጥጫ አይታይበትም፡፡ ለብዙ ጊዜ በኢትዮጵያ ሳይታገድ የቆየውም በዚህ ምክንያት ነው ተብሏል፡፡ ባለሙያዎችን እየላከ ጋዜጠኞች ስልጠና እንዲያገኙ ይተባበር እንደነበረም የሚታወቅ መሆኑን ተቋሙ አመልክቶ፣ ለበርካታ ጊዜያት ከኬንያ እየተመላለሰ ስልጠና የሚሰጥ ባለሙያ የዛሬ ወር ገደማ በፖሊስ ተይዞ ከአንድ ቀን በኋላ ወደ ኬንያ እንዲባረር ተደርጓል ብሏል፡፡

ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ሊወያዩበት እንደሚገባ ገልጿል፡፡ ጆን ኬሪ በሰሞኑ ጉብኝታቸው በኢትዮጵያ የፕሬስ አፈና መባባሱ እንዳሳሰበው በመግለፅም፣ የታሰሩት ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡ ፔን የተሰኘው የፕሬስ ነፃነት ማህበርም እንዲሁ ከተመሳሳይ ጥሪ ጋር፤ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ፤ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ሊወያበት እንደሚገባ ገልጿል፡፡

 ጆን ኬሪ በሰሞኑ ጉብኝታቸው ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር የሶማሊያና የሱዳን ግጭት እንዲሁም የኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን በመጥቀስ በሰጡት የማጠቃለያ መግለጫ ላይ የጋዜጠኞቹና የፀሐፊዎቹን መታሰር አልጠቀሱም፡፡ ጉዳዩ የተነሳው ከጋዜጠኞች በቀረበ ጥያቄ ነው፡፡ ጆን ኬሪ በሰጡት ምላሽ፤ የታሰሩት ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች ሊለቀቁ ይገባል ብለዋል፡፡ የዩኤን ሰብዓዊ መብት ኪሚሽነር ከሰሞኑ በጋዜጠኞችና በድረገጽ ጸሃፊዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የእስራትና የማስፈራራት እርምጃ እጅጉን እንደሚያሳስባቸው ገልጸው፣ መንግስት ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን ስለተጠቀሙ በቁጥጥር ስር ያዋላቸውን ጋዜጠኞችና የድረገጽ ጸሃፊዎች እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

መንግስት በስራ ላይ ያዋላቸው የጸረ ሽብር፣ የሲቪል ማህበረሰብና የመገኛኛ ብዙሃን ህጎች፣ የዜጎችን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና የመሰብሰብ መብቶች ለማፈን እየተጠቀመባቸው ነው ያሉት ፒላይ፣ ህጎቹን ከአለማቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ጋር በሚጣጣም መልኩ እንዲያሻሽልም ለኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ሰበር ዜና-ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ ልዩ ምርመራ ተደረገበት

May 3/2014

ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ
በካዛንቺስ አካባቢ የቅስቀሳ ስራ ይሰሩ የነበሩ አባላት የሚሰሩትን ለመዘገብ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የነበረው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ዋና
አዘጋጅ ነብዩ ሐይሉ በታሰረበት የስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ ከተያዘበትና በፍርድ ቤት ከቀረበበት ክስ ጋር በማይገናኝ ጉዳይ ሲቪል
በለበሱ ደህንነቶች ምርመራ እንደተደረገበት ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡

የአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ለሰጠው ሰላማዊ ሰልፍ የቅስቀሳ ስራ ለመስራት ወደ አራት ኪሎና ካዛንቺስ አቅንተው የነበሩት
ሁለት የአንድነት አመራሮችና ጋዜጠኛ ነብዩ ሐይሉ ከትናንት ወዲያ ፍርድ ቤት ቀርበው የአስራ አንድ ቀን ቀጠሮ ተጠይቆባቸው
ወደ ፖሊስ ጣብያው እንዲመለሱ መደረጋቸው ይታወቃል፡፡

ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን በያዘበት ጉዳይ ምርመራ ማድረግ የሚችል ቢሆንም ነብዩን የመረመሩት ሲቪል ለባሾች ከክሱ ጋር
ባልተያያዘ መንገድ‹‹ጋዜጠኛ መሆንህን እናውቃለን፡፡ከዞን ዘጠኝ አባላት ጋር ያላችሁን ግኑኝነትም ደርሰንበታል፡፡አዲሱ
የጋዜጠኞች ማህበር ከውጪ ድርጅቶች ጋር እንደሚሰራ እናውቃለን››በማለት ማስፈራሪያ አዘል ምርመራ እንዳደረጉበት
ምንጮቻችን አጋልጠዋል፡፡
ዘ- ሐበሻ

ኢትዮጵያ በህግ አምላክ የሚባልባት ሀገር መሆኗ ቀርቷል

May 3/2014
ግፈኛውና ዘራፊው የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያ መሬት ከሚሰራቸው ትልልቅ ወንጀሎች አንዱና ምናልባትም ዋነኛው በህግና ሕገ-መንግስት ላይ የሚያካሄደው ቀልድና ጭዋታ ነው። ሕገ-መንግስት ህዝብን ከእብሪተኛ መንግስት መጠበቂያ መሳሪያ መሆኑ ቀርቷል። ህግና ሕገ-መንግስት ለወያኔ ሲፋጅ በማንኪያ ሲበርድ በጣት የሚበላ ነገር ነው። ወያኔና አፋኝ ስርአቱ ህግ የሚጠቅሱት ለራሳቸው ይጠቅመናል ባሉበት ሰዓት ነው። ህግ ለነሱ ካልተመቻቸው ተቀዶ የሚጣል ቆሻሻ ወረቀት ነው።
በኢትዮጵያ ምድር ዋናው ሕገወጥ ተቋም ራሱ ላወጣው ሕግ የማይገዛው ወያኔ/ህወሃት ነው። ለዚህ ነው “ለሚመለከተው አካል ከማሳወቅ ውጪ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ፈቃድ አይጠየቅም” የሚለውን ራሱ ያወጣውን ህግ ጥሶ ሰሞኑን ተቃዋሚዎችን ቁም ስቅላቸውን የሚያሳያቸው። ለዚህም ነው ሃሳብን በጽሁፍና በቃል ለመግለጽ ቅድመ ምርመራ እና እገዳ አይኖርም ብሎ ጽፎ፣ አለም አቀፍ የሰበአዊ መብት ድንጋጌዎች እንዳሉ ተቀብያለሁ ብሎ የተናገሩና የጻፉ ሰዎችን የሚያሳድደውና በሽብርተኝነት የሚከሰው።
ኢትዮጵያ “በሕግ አምላክ” የሚባልባት ሀገር መሆኗ ቀርቷል። ወያኔ ይህን ለህግ ትልቅ ክብር ያለውን የህዝባችንን የዘመናት እምነት ድራሹን በማጥፋት ላይ ይገኛል። ፍትህ በወያኔ አፋኞች መዳፍ እጅ ወድቃለች።
በዚያ አስከፊ የደርግ መንግስት ስርአት እንኳን ዳኞችን “እንዲህ ብላችሁ ፍረዱ” የሚል ትእዛዝ አልነበረም።
ዛሬ በየፍርድ ቤቱ አለም እየታዘበ የሚከናወን አይን አውጣ አሰራር እና የህወሃት የንጹሃን ዜጎችን የፖለቲካ መቀጣጫ ቤት ሆኖ ተለምዶል። ፍትህ እና ፍርድ ቤት እንዲዋረድ ሆኗል። ፍትህና ዳኝነት ራሱ በህወሃት የታሰረበት ጊዜ ነው።
ባለፈው ሳምንት ወያኔ አፍሶ ማእከላዊ በማስገባት የሚያሰቃያቸው የዞን 9 የኢንተርኔት ፌስቡክ ተጠቃሚዎች በሀገሪቱ ህገ መንግስት ከተለመደው መሰረታዊ መብታቸው ውጪ ያደረጉት ቅንጣት ወንጀል የለም። ወያኔ በፈራ እና በደነገጠ ቁጥር ሺህ ህግ ይጥሳል፡፡ ወያኔ ደግሞ ጥላውን የሚፈራ ድንጉጥ ተቋም ነው።
የኢትዮጵያን ህዝብ እንደ ጠላት እንጂ እንደ አብሮ ኗሪ ዜጋ ማየቱን ከተዎ የሰነበተውም ለዚህ ነው።
ዛሬ ራሱ ወያኔም እኛም በሕግና በሕጋዊነት ላይ ያለን ተስፋ ተሟጧል። ስለዚህም ነው ምርጫችን ይህን ህገ ወጥ የወንበዴ መንግስት በትጥቅ አልባም ይሁን በታጠቀ ሁለገብ አመጽ ማስወገድ ብቻ ነው የምንለው።
ት 7 የወያኔን አያያዝ አይተን የሁሉአቀፍ የአመጹን መንገድ ተከትለናል። ፈልገን ሳይሆን ተገደን በወያኔ ምርጫ የተመረጠልንን።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ወያኔ የህግና የሰላም በሩን ሁሉ ዘግቶ የተወልህን እና ሊከለክልህ የማይችለው ምርጫ የራስህን የነጻነት ትግል የአመጽ ሃይል ብቻ ነው። በየአለህበት በእምቢተኝነት ተነሳ!! መብትህንና ክብርህን ከወያኔ መጠበቅ የዋህነት ነውና ተነስ ተቀላቀል! ራስህን ነጻ አውጣ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

የማለዳ ወግ … እነሆ የጨለመው ነጋ ! … ነጻ ወጣሁ ! አመሰግናለሁ (ጋዜጣኛ ነብዪ ሲራክ)

May 3/2014

እነሆ 60 ፈታኝ የመከራ ቀናቶች በትዕግስት ተገፍተው አለፉ ፣ ክፉውን ቀን ለማለፍ የትዕግስት ጽናት ብርታት ተስፋየ ምንጩ በመላ አለም የምትገኙ ወገን ወዳጆቸ ነበራችሁና ላደረጋችሁልኝ እና ላሳያችሁልኝ የሞራል ድጋፍ ልባዊ ምስጋና አቀርባለሁ !አሰልችውን ቢሮክራሲ አልፈው ፣ በማይጨበጠው ቀጠሮ ሳይሰላቹ ሌት ተቀን እኔን ሀፐነው ታመው ጉዳዬን ለምስለኔ አቅርበውድቅድቅ ጨለማው እነወዲገፈፍልኝ ያደረጉትን ለማመስገን ቃላት ያጥረኛል ! ለደህንነታቸው ስል በስም ለማንሳት የማይቻለኝ ወንድሞቸ ብርታት ፈጣሪ ታክሎበት ለዛሬው ንጋት ደርሻለሁ ! ተመስገን ! ነግቶም በአይኔ ሲንቀዋለሉ ከነበሩት ብላቴና ልጆቸና
ከመላ ቤተስብ ዘመደ አዝማድ ጓደኛ አፍቃሪዎቸ ለመገናኘቴ ምክንያት እናነተ በአካል ከጎኔ የቆማችሁ ነበራችሁና በሁሉም ስም ምስጋና ወደር የለውም !

ከማዕከላዊው የብሪማን እስር ቤት ወዳጆቸ …በብሪማን ያላፉ ኢትዮጵያውያንየህግ ታሳሪዎች መካከል በግፍ የታሰሩት አሰገራሚ ታሪኮችን ከእናንተው ጋር በአካል ተገኝቸ ” እህ ” ሰምቸ ተምሬባቸዋለሁ ። በእስር ቤቱ ታዛ እና ግድግዳዎች ላይ የጻፏቸው ማስታወሻና ጥቅሶችን ተመልክቸ ተጽናንቸባቸዋለሁ ። አንዷተደጋግማ የሰማኋት ጥቅስ ውስጥ እኔም በመከራው ሳልፍ ተስፋን ሰንቄ እዚህደርሻለሁ! ” እኔ መውጣት የምፈራው መውጣት ከማልችለው ከመቃብር እንጅ ፣መውጣት ከምችለው የብሪማን ወህኒ አይደለም! ” ትላለች ! አዎ ያ ቤት መቃብር አይደለም … በተስፋ ኑሩ ! አካላችሁ እንጅ አዕምሯችሁን ማሰር የሚቻለው የለምና ብሩህ ተስፋን ሰንቁ ! ፍትህ ርትዕ የጎደለባችሁን ድምጽ ዛሬም እንደ ትናንቱ ለምሰለኔዎቻችን አሰማለሁ ! አይዟችሁ !

ለእነ እንቶኔ መረጃ ቅበላየን ጠልታችሁ ላሳደዳችሁኝና ላልተሳካላችሁ ! ” ወደ ገደል አፋፍ ገፋነው ! ” በትምክህት የታበያችሁ ፣
ህልማችሁ ያልተሳካ እኩዮችም ቢሆን ያለመታከት በመስራታችሁ በመንገላታቴ አልተጎዳችሁኝምና ደስ አይበላችሁ ! እግሬና
እጆቸ በካቴና ታስረው ወደማላውቀው የወህኒ ህይወት ስወረወር የማላውቀውን አውቄ ፣ ተምሬና ኑሮ በመከራ እንዴት
እንደሚገፋ እማር ዘንድ ምክንያት ስለሆናችሁኝ አመሰግናችኋለሁ ! አዎ ዛሬ ነጻ ወጥቻለሁ !

ያሳለፍኳቸው 60 የወህኒ ቀናት ራሴን አዙሬ እንዳይ አድርጎኛል። በቀረጣይ ቀናት አረፍ በፍጥነት ከሚስገመገመው የመረጃ
ቅብብሎሽ አውድ ገለል ማለት ባይቻለኝም ለአፍታ አረፍ ማለትን መርጫለሁ! በቀጣይ እረፍት ቀናቶቸ ወደ ብላቴና ልጆቸና
ቤተሰቦቸ ፣ያለፉ እና በውዝፍ የቀሩትን የቀሩ የአረብ ሃገር ስደቱኛ ህይወት ከጋዜጠኝነት ህይዎት ተሞክሮው ጋር አዙሬ
እመለከተው ዘንድ ግድ ይለኛል!

ከአፍታ እረፍት በኋላ እስክንገናኝ ፣ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ: )

በጎንደር መተማ አቅራቢያ በፌደራል ፖሊስ አምስት ተገድለው ስድስት ቆሰሉ

May3/2014
በጎንደር መተማ አቅራቢያ ልዩ ስሙ ሸዲ እና ገንዳ ውሃ በሚባሉ ቦታዎች የፌደራል ፖሊስ በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ በከፈተው ተኩስ አምስት ሲሞቱ ስድስት ክፉኛ ቆስለው ወደ ጎንደር ሆስፒታል መወሰዳቸውን የደረሰን ዜና ተቁሟል::

የግጭቱ መንስኤ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል አንድ የአካባቢውን ነዋሪ በህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ ሳቢያ በተፈጠረ ግርግር ይገድለዋል:: የአካባቢው ነዋሪዎችም በሰላማዊ ሰልፍ ገዳዩ የፖሊስ አባል ለህግ እንዲቀርብላቸው ለመጠየቅ ሲወጡ: ሌሎች ማህበረሰባዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም አብረው ይዘው ወጡ:: ፌደራል ፖሊስም በወጣው ህዝብ ላይ ቶክስ በመክፈት አራት ተጨማሪ ሰዎችን ሲገድል ስድስት ክፉኛ ቆስለዋል::
Violence in Metema - May 01, 2014 - 6
Violence in Metema - May 01, 2014 - 4
Violence in Metema - May 01, 2014 - 5

Violence in Metema - May 01, 2014 - 3

ኦሮሚያ ካለቀሰች በኋላ – ህዝብ ሃሳቡን ሊጠየቅ ነው

የኢህአዴግ ቴሌቪዥን የቅስቀሳ ዘመቻ ጀመረ
mothers
May3/2014


በአምቦ ህዝብ አዝኗል። የሟቾች ቁጥር ከ22 በላይ እንደሆነ ይገመታል። በድፍን ኦሮሚያ ከ36 ሰዎች በላይ ተገድለዋል የሚሉ መረጃዎች አሉ። ኢህአዴግ ባወጣው መግለጫ 11 ሰዎች መሞታቸውን አምኗል። ታዛቢዎች እንደሚሉት ኦሮሚያ እያነባች ነው። ህዝብ ለቅሶ ከተቀመጠ በኋላ ኢህአዴግ በቴሌቪዥን ቅስቀሳ ጀመረ።
አርብ ሚያዚያ 24፤2006 (2/05/2014) ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በትዊተር ባሰራጩት መረጃ በጉዳዩ ዙሪያ ህዝብ ሃሳቡን እንደሚጠየቅ አመላክተዋል። የዚሁ መነሻ እንደሆነ የተነገረለት የቅስቀሳ ዘመቻ ዛሬ በቴሌቪዥን ተላልፏል። የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ኩማ የድንበር ጉዳይ እንደማይነሳ በመጥቀስ ተቃዋሚዎችን ወቅሰዋል።
ኦሮሚያን ልዩ ዞን ከአዲስ አበባ ጋር ያዋሀደው አዲሱ ማስተር ፕላን ተግባራዊ እንዲሆን እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ በክልሉ ከተካሄዱት ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎች የአምቦው በጉልህነቱ ይጠቀሳል። አምቦ ነዋሪው ግልብጥ ብሎ በመውጣት ተማሪዎችን ተቀላቅሏል። ኢህአዴግ ባወጣው መግለጫ “… በአምቦ ዩኒቨርስቲ የተቀሰቀሰው ሁከት ወደ ከተማ በመዝለቁ እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት በአምቦና ቶኬኩታዮ ከተሞች የሰባት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ባንኩን ጨምሮ በበርካታ የመንግስትና የሀዝብንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል” በማለት ግድያውን ከንብረት ውድመት ጋር ለማያያዝ ሞክሯል። በመደ ወላቡ ሶስት ሰዎች መገደላቸውን፣ በሌላም በኩል “በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በሰላም የእግርኳስ ጨዋታ በቴሌቪዥን በመከታተል ላይ በነበሩ ተማሪዎች ላይ በተወረወረ ፈንጂ ወደ70 ያህል ተማሪዎች የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል” ሲል በህይወት ላይ የደረሰውን ጉዳት አስታውቋል።police12
ኢህአዴግ የሟችና የቁስለኞችን ቁጥር ዝቅ ቢያደርግም የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ኦ.ፌ.ኮን በመጥቀስ እንደዘገበው በአምቦ ለተገደሉት 17 ሰዎች ኢህአዴግን ተጠያቂ አደርጓል። የኦሮሚያ ክልል መንግስት ባወጣው መግለጫ ደግሞ አመጹን ከኋላ ሆነው የመሩትን የማጣራት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል። ክልሉ በመግለጫው ህይወታቸው ስላለፈ ዜጎች ያለው ነገር ስለመኖሩ የኢህአዴግ ቴሌቪዥን ያለው ነገር የለም። ግድያው ስለተፈጸመበት አግባብ የማጣራት ስራ እንደሚከናወን እንኳን አልጠቆመም።
የተለያዩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙትና የጎልጉል የኦሮሚያ ምንጮች እንዳሉት በሰሞኑ ተቃውሞ ከ36 ሰዎች በላይ ተገድለዋል። የሲኤንኤን አይ ሪፖረተር በአምቦ ብቻ 30 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን አመልክቷል። ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች ታስረዋል። የቁስለኞች ቁጥርም ቀላል አይደለም። በዚሁ ሳቢያ የህዝብ ስሜት በቁጭት የተሞላ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። የክልሉ ምክር ቤት ግን ህዝብ ከጎኑ መቆሙን በመጥቀስ ምስጋናውን አቅርቧል።
በአምቦ ከደረሰው ሰብአዊ ጉዳት በመቀጠል በሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ ማንነቱ የማይታወቅ ሰው ወረወረው በተባለ ቦንብ አንድ ሰው መሞቱና 70 መቁሰላቸው አስደንጋጭ ዜና ሆኗል። ቦንቡን ማን ጣለው፣ ከየት መጣ? ማን፣ ለምን ዓላማ ተማሪዎች ላይ ቦንብ መወርወር ፈለገ? ተማሪዎችን መጨረስ ከፈለገ ከተጠቀሰው በላይ ጉዳት እንዳያደርስ ማን ከለከለው? የሚሉትና ተመሳሳይ ጥያቄዎች እየተሰነዘሩ ነው። ምን አልባትም የተቀነባበረ ድራማ ሊሆን አንደሚችልና ጉዳዩን ከብሄር ጋር የማገናኘት ዓላማ ያለው እንደሚሆንእየተሰማ ነው።
ኢህአዴግ በቴሌቪዥን ባሰራጨው የቅስቀሳ ፕሮግራም “ኦሮሚያ መሬት ተቆርሶ ለአዲስ አበባ እንደማይሰጥ፣ ክልሉ ካልፈቀደ የሚሆን ነገር እንደሌለ፣ ክልሉ ቢፈቅድ እንኳን እንደ ቀድሞው ልዩ ዞኑ ውስጥ ያሉት ወረዳዎች በኦሮሚያ ስር እንደሚተዳደሩ፣ የመሬት ቆረሳው ተራ የጠላት ወሬና ፕሮፓጋንዳ” እንደሆነ አቶ ኩማ ደመቅሳን ጨምሮ የተለያዩ ሃላፊዎች ሲናገሩ አሰምቷል።
በዚሁ የፕሮፓጋንዳ ስርጭት “የክልሎች ማንዴት በህገመንግሰት የታሰረ ዋስትና አለው” በማለት የኦህዴድ ሰዎች ሲናገሩ ታይተዋል። ስርጭቱ አዲስ አበባና የልዩ ዞኑ ከተሞች በተቀናጀ ልማት ተሳስረው “ሲያብቡ” የሚያሳይ ዲዛይን በተደጋጋሚ በማቅረብ “ለዚህ ልማት እንረባረብ” የሚል ጥሪ አሰምቷል።
ቪኦኤና የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ እንደዘገቡት የኦሮሚያ ፌዴራል ኮንግረንስ ድርጊቱን ክፉኛ መቃወሙንና ለደረሰው የህይወት ኪሳራ ኢህአዴግ ተጠያቂ አድርጓል። በልማት ስም ከድሃ አርሶ አደሮች ላይ የሚወሰደው መሬት “የመሬት ቅርምት” ስለሆነ ባስቸኳይ እንዲቆም ጠይቀዋል። ክልሎች ህገ መንግስታዊ መብትም ሳይሸራረፍ እንዲከበር አሳስበዋል።
dire dawa universityበተያያዘ ዜና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በሚወጡ ሰልፈኞች ላይ ፍጹም የሃይል ርምጃ እንዲወስዱ የታዘዙ የጸጥታ ሃይሎች ርምጃቸውን እንዲያለዝቡ መታዘዙ ታውቃል። በተወሰደው የሃይል ርምጃ ህዝብ ክፉኛ በመቆጣቱ የሚወሰዱ ርምጃዎች እንዲላዘቡ መታዘዙን ተከትሎ በዛሬው እለት አንዳንድ ከተሞች ተቃውሟቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ገልጸው በሰላም መበተናቸውቸው ሰምቷል። ቪኦኤ እንዳሰማው የድምጽ መረጃ “የነፍጠኞች ሃውልት ይፍረስ” የሚለው ጥያቄ አሁንም እየተስተጋባ ነው።
የኦፌኮው አቶ ገብሩ ገ/ማርያም እንዳሉት አማራውንና ኦሮሞውን ለማጫረስ እየተከናወነ ያለ ሴራ አለ። ለረዥም ዓመታት አብሮ የኖረን ህዝብ ለማናከስ የሚደረገውን ሴራ ድርጅታቸው እንደማይቀበለውም አመላክተዋል። ከዚሁ ነፍጠኛን ከማውገዝ ጋር በተያያዘ “የአዲስ አበባን መስፋፋትና ነፍጠኛነትን ምን አገናኛቸው?” በማለት የሚጠይቁ፣ “ያረጀውን የነፍጥ ታሪክ ከማውራት አሁን ነፍጥ አንስቶ ጥቃት እየፈጸመ ስላለው ህወሃት የሚባለው የአንጋች ቡድን መነጋገር አይሻልም ወይ” ሲሉ ይደመጣሉ። (ፎቶዎቹ ከፌስቡክ የተወሰዱ ናቸው – የየትኛውም ኢትዮጵያዊት እናት ለቅሶ የሁሉም መሆኑን እንዲያሳይ የተጠቀምንበት ነው)
 የጎልጉል

“አውሬነት” – ለማንም አይበጅምና ጠንቀቅ!!

(ርዕሰ አንቀጽ)
police brutalityMay 3/2014


አሁን ከኢህአዴግ ጋር ገድለሃል አልገደልክም የሚል ክርክር የለም። ራሱ ባንደበቱ “ገድያለሁ” ብሏል። ነፍስ ማጥፋቱን አውጇል። ያልገለጸው በጸጥታና በስም እንጂ አንጋቾቹ ህይወት መቅጠፋቸውን አረጋግጧል። ግድያው በዚህ ስለማብቃቱ ማረጋገጫ አልተሰጠም። ተቃውሞውም እየቀጠለ ነው። ከዚያስ? በደም እየታጠቡ፣ ወንጀልን እያባዙና የደም ጎርፍ እየጎረፈ “ህግ” ማስከበር እስከመቼ ያስኬዳል። ያዋጣልስ? የህዝብ እንባስ እንዲሁ ከንቱ ይቀራል?
በርግጥ ህግ ማፍረስ አይደገፍም። ህግ መከበር አለበት። ከሁሉም በላይ ደግሞ ህገመንግስት ክቡር የመተዳደሪያ ዋስትና በመሆኑ ሊናድ አይገባውም። ህግን የማክበርና የማስከበር ጥያቄ አይለያዩም። ኢህአዴግ እንዳሻው የሚምልበትን ህገ መንግሥት እየጨፈላለቀና እየጎራረደ ሌሎች ህግ እንዲያከብሩ መጠየቅ ለምዶበታል። ሰዎች መብታቸውን እንዲለማመዱ አይወድም። ይህ ችግሩ በደም የታጠበ፣ የደም እዳ ያለበት፣ ታሪኩ ሁሉ ከደም ጋር የተሳሰረ እንዲሆን አድርጎታል። እስኪ ወደ ዛሬው ጉዳይ እናምራ!
አልታደልንም
ህዝብን የሚያከብር፣ ለህዝብ ቅድሚያ የሚሰጥ፣ በህዝብ የሚምል፣ ህዝብ ውስጥ የሚኖር፣ ህዝብ እውቅና የሰጠው፣ ህዝብ የሚያምነው፣ ሲፈልግ የሚቀጣው፣ ሲፈልግ የሚያሞግሰው አስተዳደር አጋጥሞን አያውቅም። የቀደመውን ኮንኖ የሚመጣው ከቀደመው የማይሻል፣ ደም የጠማው፣ ጠመንጃ አምላኩ የሆነ አገዛዝ ነው። አገሪቱም፣ ትውልዱም፣ የወደፊቱ እንግዳ ዘርም ሁሉም በስህተት ቅብብል በርግማን ይኖራሉ። ነፍጠኛ፣ ትምክተኛ፣ ጎጠኛ፣ ጠባብ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ አንጃ … ቃላት እንደ ፋብሪካ ምርት እየተፈበረኩልን ስንሰዳደብ እንኖራለን። የሁሉም አስተሳሰብ አንድ ብቻ ነው – የራሱን ህልውና ለማስፈን የሚቃወሙትን ሁሉ መደምሰስ! “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” የሚለው መፈክር ደርግ ቢለውም የራሱ በማድረግ አንግቦ የሚዞረው ግን እጅግ በርካታ ነው፡፡police12
ኢህአዴግ ተቃውሞና የተቃውሞ ድምጽ ያስበረግገዋል?
አዎ!! ኢህአዴግ የተቃውሞ ድምጽ ሲሰማ ይርዳል። የተቃውሞ ድምጽ ሲሰማ ይንቀጠቀጣል። ሲቃወሙት የበረሃ ወባው ይነሳበታል። ከድንጋጤው የተነሳ ይበረግጋል። ይደነብራል። ለምን? ቢባል በደም የተለወሰ ፓርቲ ስለሆነ ነው። ኢህአዴግ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ነፍስ ያላጠፋበት ስፍራ የለም። በመሀል አገር ክቡር የሰው ልጆችን ገሏል። የሚደመደም ነገር ባይኖርም በበላዮቹ ትዕዛዝ ኢህአዴግ ባፈሰሰው ደም መጠን ጠላት አፍርቷል። ወዳጁና አጋሩ ጠብመንጃና በደም የለወሳቸው አባላቱ ብቻ ናቸው። ሌላ ወዳጁ እንዳሻው የሚዘራው የአገሪቱ ሃብት ነው። የህዝብ ሃብት ህዝብን ለማፈን ማዋል!! ሌላው ስጋቱን ለመጥቀስ እንጂ ከዝርፊያ ጋር የተቆራኘውን ታሪኩን ለመዘርዘር አይደለም። ስለዚህ ህዝብ ሲቃወም ያጥወለውለዋል። ይጓጉጠዋል። አውሬ ይሆናል። ህግና ስርዓት አፍርሶ የጫካ ደንብ ይተገብራል። ባጭሩ ይገላል!!
ኢህአዴግ በበረገገ ቁጥር እንሰጋለን!!
ኢህአዴግ የኢትዮጵያ ገዢ ነኝ ካለበት ጊዜ ጀምሮ ህዝብን ያስቀየሙ፣ ያሳዘኑና፣ ያሳፈሩና ቂም ያስቋጠሩ ተግባራትን በግልጽና “በድብቅ ግን የሚታወቅ” አከናውኗል። በተለያዩ ጊዜያት በተግባሩ የተነሳበትን ተቃውሞ ለማፈን ሃይል ተጠቅሟል። አልሞ ተኳሾችን አሰማርቶ ዜጎችን ልባቸውና ግባራቸው አየተመታ እንዲገደሉ አድርጓል። የሚችለውን ያህል አስሯል። ገርፏል። ራሱ ክስ መስርቶ ራሱ እየፈረደ ወህኒ ወርውሯል። ነጻ ፕሬስን ሰቅሎታል። ሃሳብን በነጻ ማራመድን በህግና ህግ በማይጠቀስበት አግባብ አግቷል።
አሁን ኦሮሚያ ላይ የተነሳውን የተቃውሞ አመጽ ተከትሎ ችግሩን በሰላማዊ መንገድ በጥበብ ከማስተናገድ ይልቅ ብረት አንስቶ መግደልን መርጧል። ኢህአዴግ በገደለ ቁጥር አገሪቱ ስጋቷ እየጨመረ፣ የህዝብ ስሜት እየተበላሸ ነው። ይህ እንደሚዲያ ያስጨንቀናል። ኢህአዴግ የዘራው የቂም ዘር በየአቅጣጫው ፍሬው እየጎመራ መሄዱ ያሳዝነናል። ከሁሉም አቅጣጫ መፍትሔ የሚፈልግና ችግር የሚያረግብ አይታይም። አገሪቱ አስተዋይ በማጣቷ በስጋት ደመና እየነፈረች ነው። የአንዱ ለቅሶ ለሌላው ደስታ እየሆነ ነው። ከዚህ በላይ የሚያስጨንቅ ምን አለ? አማራው፣ ደቡብ ክልል ያሉ ዜጎች፣ ኦጋዴን፣ ሶማሌ፣ ሁሉም ጋር ብሶት አለ። የኑሮ ችግር የጠበሳቸው የበይ ተመልካቾች መሯቸዋል። ያልመረራቸው ቢኖሩ ከቁጥር የማይገቡ ባለጊዜዎች ብቻ ናቸው። ይህም ታላቅ ስጋት ነው!!
ምን ይደረግ?
አሁን በኦሮሚያ የተነሳውን የባለቤትነት ጥያቄ ማክበር አማራጭ የለውም። ጸረ ሰላም ሃይሎች ከአመጹ ጀርባ አሉ በሚል መፎከርና ችግሩን ማድበስበስ አያዋጣም። የድሃውን መሬት መቀራመትና መቸብቸብ ይቁም። አርሶ አደሩ በመሬቱ ላይ ብቻ የተመሰረተው የመኖር ተስፋው ይከበርለት። ይህ ሁሉ የኢህአዴግ የመሬት ፖሊሲ ጣጣ ያመጣው ነውና ይታሰብበት። ኢህአዴግ የድሃውን ገበሬ መሬት ከመሸጥ ይቆጠብ። መቃወም ህጋዊ መብት ስለሆነ ኢህአዴግ ተቃውሞን ከመፍራትና እመራቸዋለሁ የሚላቸውን ወገኖች ከመግደል ይልቅ ህዝብን የሚያስቆጣ ተግባር ከመፈጸም ራሱን ያቅብ። “አዲስ የልማት ዘዴ ዘይጃለሁ” ሲል የጉዳዩን ባለቤት በቅድሚያ ያሳምን። ህዝብ ተቃውሞውን ሲገልጸ እየበረገጉ በደም መታጠብ ቆይቶም ቢሆን ዋጋ ያስከፍላልና ይታሰብበት። የጠብ መንጃ ሰላም ዋስትና ቢኖረው ኖሮ ኢህአዴግ እስካሁን ያፈሰሰው ደም በበቃው ነበር። እናም ቅድሚያ ለህዝብ ክብርና ለህግ!! ታሪክ በግልጽ መስክሯል – አውሬነት ለማንም አይበጅምና!!
ጎልጉል

በዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች መልዕክት አስተላለፉ፤ (የረሃብ አድማ መምታት ጀምረዋል)

May 2/2014
በዝዋይ የሚገኙ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ጥያቄያቸው እንዲመለስ ጫና ለመፍጠር የምግብ ማቆም አድማ ጀመሩ። አድማው ለ3 ቀን እንደሚቆይ ታውቋል፡፡ ጥያቄያቸውም፡-

1ኛ፦ የፖለቲካው ሥነ -ምህዳር እንዲሰፋና የፓርቲዎች በነፃነት የመንቀሳቀስና የመደራጀት መብት ሳይሸራረፍ እንዲከበር፣

2ኛ፦ አፋኝ የሆኑት የመያዶች ህግ፣ የፀረ-ሽብር ህግ፣ የፕሬስ ህግ እንዲሻሩና ነፃ የሙያ ማህበራት ላይ የሚደረገው አፈና እንዲቀም፣

3ኛ፦ በግሉ ሚዲያ ላይ የሚደረገው ማስፈራሪትና አፈና በአስቸኳይ እንዲቆምና የፕሬስ ነፃነት ሳይሸራረፍ እንዲከበር፣

4ኛ፦ የመከላከያ፣ የፖሊስና የደህንነት አካላት በህገ መንግሥቱ መሠረት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በገለልተኝነት እንዲወጡ፣

5ኛ፦ ፍርድ ቤቶች፣ የምርጫ ቦርድ፣ የህዝብ ሚዲያው ነፃና ገለልተኛ ሆኖ እንዲዋቀር፣

6ኛ፦ የፖለቲካ እስረኞች፣ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የህዝበ ሙስሊሙ ተወካዮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣

7ኛ፦ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ እስር ቤቶችን በተመለከተ፡-

ሀ) የሰብአዊ መብት ጥሰትን የፈፀሙ ማለትም በድብደባ አካል ያጎደሉና በድብደባ የሰው ህይወት ያሳለፉ የተቋሙ አባላት ህግ ፊት እንዲቀርቡ፣

ለ) በደረቅ ወንጀል ለታሰሩ እስረኞች የሚደረግ ዝውውር፣ ይቅርታ፣ ምህረት እና አመክሮ ህግ በሚፈቅደውና መድሎ በሌለበት ሁኔታ እንዲፈፀም፣

ሐ) በሁሉም እስር ቤቶች ውስጥ ‹‹ጨለማ ቤት›› በመባል በሚጠሩት የብቻ እስር ቤቶች ውስጥ የታሰሩ እስረኞች ከጨለማ ቤቶቹ ወጥተው ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዲቀላቀሉ።

መ) የምግብ፣ የውሃ፣ የአልባሳት፣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲሻሻል እንዲሁም እስረኞች ከሚጎበኟቸው ሰዎች በወር የሚፈቀድላቸው 1ዐዐ ብር በቂ ባለመሆኑ ክልከላው እንዲነሳ፣ የመረጃ በነፃነት የማግኘት መብታችን እንዲከበር (ሬድዩ የማዳመጥና የግሉ ሚዲያ ውጤቶች የሆኑ ጋዜጦች እንዲገቡልን) የርቀት ትምህርት መማር እንዲፈቀድ፣ ከውጭ የሚላኩልንን ፖስታዎች በአግባቡ እንዲደርሱን።

8ኛ፦ በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 28 ላይ በተደነገገው መሠረት በሰው ልጆች ላይ አሰቃቂ ድብደባና አካል ማጉደል ወንጀል መሆኑን በመፃረር በሀገሪቱ ያሉ የምርመራ ጣቢያዎች በተለይም በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ (ማእከላዊ) ውስጥ ይህንን ወንጀል የፈፀሙና እየፈፀሙ ያሉ የፖሊስና የደህንነት አባላት ለፍርድ እንዲቀርቡ።

9ኛ፦ በሀገራችን ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ምስቅልቅል በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥትና ተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች ብሔራዊ መግባባትና እርቅ እንዲያወርዱ። በመጨረሻም በአሁኑ ወቅት ሀገሪቱ ያለችበትን አሳሳቢ ሁኔታ በአግባቡ በመረዳት ልዩነትንና ህልውናን ጠብቆ ለጋራ የነፃነት አጀንዳ በጋራ ተባብሮ መታገል የወቅቱ ዋነኛ ጥያቄ በመሆኑ የሀገሪቱ የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉ ተባብረው እንዲታገሉና የኢትዮጵያ ህዝብም ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ከዚህ በላይ በዝርዝር ያቀረብናቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ትኩረትና ምላሽ ያገኙ ዘንድ ለጊዜው ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረው የፖለቲካ እስረኞች ከአርብ ሚያዚያ 24 ቀን እስከ እሁድ ሚያዚያ 26 ቀን የሚቆይ የ3 ቀን የረሃብ አድማ አድርገናል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
1ኛ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር
2ኛ አቶ ደረጀ አበበ
3ኛ አቶ ናትናኤል መኮንን
4ኛ አቶ ክንፈ ሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ)
5ኛ አቶ አንዷለም አያሌው
6ኛ ሻ/ል የሽዋስ ይሁንአለም
7ኛ አቶ ምትኩ ዳምጤ
8ኛ አቶ አበበ መልኬ
9ኛ አቶ ማንደፍሮ አካልነው
1ዐኛ አቶ ገበየሁ ብዙነህ
11ኛ አቶ ዩሐንስ ተረፈ
12ኛ አቶ መሠለ ድንቁ
13ኛ አቶ ፍቃዱ ባሳዝን
14ኛ አቶ የገባው አለሙ
15ኛ አቶ እሱባለው አሌ
16ኛ አቶ ጥላሁን ባለው
17ኛ አቶ አስቻለው አራጋው
18ኛ አቶ በእውቀት ደሳለኝ
19ኛ አቶ ካሳሁን ጌጡ

ግልባጭ
- ለኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች በሙሉ
- ለተባበሩት መንገሥታት ድረጅት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን
- ለአውሮፓ ህብረት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን
- ለአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መ/ቤት
- ለአፍሪካ ህብረት የሰብአዊ መብት ኮሚች
- ለ Human Rights watch
- ለ Amnesty international
- ለ CPJ እና ለሀገር ውስጥና ለውጭ የሚዲያ ተቋማት በሙሉ፡፡

Addis Ababa’s brutal regime on a killing spree again

May 2/2014
The brutal TPLF minority regime has been arresting, torturing and mercilessly killing Ethiopians for the past 23 years. As recently as last week, the regime in Ethiopia made a house to house search and arrested Blue Party leaders and members who were in the process of staging a peaceful demonstration. This week the regime’s security forces arrested three journalists, social media activists and six pro-democracy bloggers (founders of a group known as Zone Nine). Yesterday, Addis Ababa’s killing machine that has zero tolerance for dissent struck again, killing Oromo students and innocent civilians who protested Addis Ababa’s new Master Plan that enlarges the area of the city by evicting poor Oromo peasants from their ancestral land and annexing surrounding towns against the will of the Oromo people.
On April 30, 2014 armed security forces opened fire on Oromo students who were waging a peaceful protest in the town of Ambo, Western Oromia. According to CNN iReport and eye witness testimonies, the TPLF security forces shot and killed more than 30 people including 8 students, and wounded unspecified amount of protesters.
Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy condemns the killing of peaceful demonstrators in its strongest terms and holds the Ethiopian regime fully accountable for its indiscriminate killing of innocent civilians, and for all political and social unrests that unfold with the killing. Ginbot 7 strongly believes that regardless of their ethnic and religious background, all citizens of Ethiopia have the right to freely express their ideas and wage peaceful demonstrations. Ginbot 7 urges the TPLF regime to immediately and unconditionally alienate itself from the “Gun solves everything” attitude and understand or comprehend that it’s about time to be civil.
The TPLF regime must understand that the Oromo students have every right to protest when the regime uproots their mothers and fathers from their ancestral land and sells the land to foreigners and its surrogates. The demand of the Oromo students is simple and unambiguous; it is to halt the forced eviction of the Oromos from their land. The answer to this legitimate demand is not and will never be killing people.
The recent crackdown and arrest of journalists, bloggers and human right activists took place days before US Secretary of State John Kerry set his foot on the soil of Ethiopia, and yesterday’s killing of peaceful demonstrators happened while Kerry was having talks with those who ordered the killing. It is clear now that the TPLF regime with its ethno-biased economic and political policies is taking Ethiopia to the brink of civil war with impunity. Ginbot 7 believes that if such a scenario unfolds, it could unravel this great multi-ethnic nation and has the potential to destabilize the entire Horn of Africa. It is the responsibility and strong desire of Ginbot 7 to remind the international community, especially the United States and other donor nations to save Ethiopia from this seemingly imminent danger of disintegration. Ginbot 7 also uses this opportunity to make a call to all Ethiopians to come together and save our great nation from the grave danger of disintegration.

Rest in Peace to those who gave their life to the cause of freedom,
We shall overcome !

Friday, May 2, 2014

Ethiopia protest: Ambo - A witness told the BBC that 47 were killed by the security forces

May 2/2014
MINILIK SALSAWI
At least nine students have died during days of protests in Ethiopia's Oromia state, the government has said.

However, a witness told the BBC that 47 were killed by the security forces.

She said the protests in Ambo, 125km (80 miles) west of Addis Ababa began last Friday over plans to expand the capital into Oromia state.

The government did not say how most of the deaths had been caused but the Ambo resident said she had seen the army firing live ammunition

"I saw more than 20 bodies on the streets," she said.

"I am hiding in my house because I am scared."

The Ambo resident said that four students had been killed on Monday and another 43 in a huge security crackdown on Tuesday, after a huge demonstration including many non-students.

Since then, the town's streets have been deserted, she said, with banks and shops closed and no transport.

She said teaching had been suspended at Ambo University, where the protests began, and students prevented from leaving.

In a statement, the government said eight people had died during violent protests led by "anti-peace forces" in the towns of Ambo and Tokeekutayu, as well as Meda Welabu University, also in Oromia state.

It said one person had been killed "in a related development" when a hand grenade was thrown at students watching a football match.

The statement blamed the protests on "baseless rumours" being spread about the "integrated development master plan" for the capital.

BBC Ethiopia analyst Hewete Haileselassie says some ethnic Oromos feel the government is dominated by members of the Tigre and Amhara communities and they would be loath to see the size of "their" territory diminish with the expansion of Addis Ababa, which is claimed by both Oromos and Amharas.

Image

The student protestors are from Ethiopia's biggest ethnic group, the Oromo, numbering around 27 million people.

Oromia is the country's largest region, completely surrounding the capital Addis Ababa, although the city is itself part of the Amhara region.

Its people speak their own language - Oromifa - and see themselves as very different from the Amhara.

The protesters believe they face losing their regional and cultural identity if plans to extend Addis Ababa's administrative control into parts of Oromia get the go-ahead.

Some have also raised fears of the potential for land grabs.

The so called "master-plan" for Addis Ababa is currently out for public consultation and the government says people are being given opportunities to raise their concerns.

Officials say the plan has been well publicised and will bring city services to poor rural areas.

The protestors claim they merely wanted to raise questions about the plan - but were answered with violence and intimidation.
http://www.bbc.com/news/world-africa-27251331
 

ኢቲቪ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ የሚያደርገውን ሰላማዊ ሰልፍ ማስታወቂያ አላስተናግድም አለ፡፡

May 2/2014
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት አላስተናግድም ማለቱን የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ገለጹ፡፡ የህ/ግ ኃላፊው እንደገለጹት ከሆነ ማንኛውንም ህጋዊ አካል ወይንም ዜጋ በእኩልነት ማስተናገድ የሚገባው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳያቀርብ አናስተናግድም ማለቱ አንድ የሕዝብ አገልጋይ ነኝ ከሚል ተቋም የማይጠበቅ እና ተቋሙ በእርግጥም የህዝብ አገልጋይ አለመሆኑን በድጋሚ በተግባር ያረጋገጠበት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ እንደ ህዝብ ግንኙነቱ ገለፃ ፓርቲው ጉዳዩን በቸልታ እንደማያየው እና ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስደውም ታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዢን የማስታወቂያ ክፍል ኃላፊ አቶ ሰይፉ አለምሰገድና ወ/ት ሸዋዬ የማስታወቂያ ክፍል ኤክስፐርት በእጅ ስልካቸው ደውለን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የነሱን ሀሳብ ልናካትት አልቻልንም፡፡

etv

ሰበር ዜና- የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ፕሬዝደንት ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ተሰደደ

May 2, 2014
Journalist Betre Yakobከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ጋባዥነት የኢትዮጵያን ችግርና አፈና በተለይ በሚዲያው ላይ ያለውን ጫና እና ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመግለጽ ወደ አንጎላ አቅንተው ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለአፍካ ህብረትም የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረቡና ለሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ አገሩ ለመመለስ በሚዘጋጅበት ወቅት የዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራትን ጨምሮ ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እሱን ለማሰር የተደረገው ዝግጅት በተጨባጭ ማስረጃ ስላቀረቡለት መሰደዱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ የበትረ ያቆብን ቤት በመፈተሸ ያገኘውን ወረቀት ሁሉ እንደወሰደም ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አንጎላ በተደረገው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኮሚሽነሩን በግል እንዳገኛቸውና ኮሚሽነሩም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በመግለጽ እንዲሚያገኙት ቃል ገብተውለት እንደነበር ተገልጿል፡፡ በተጨማም ከበርካታ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በሚዲያው ላይ ስለሚደረገው ጫና የተወያዩ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተለያዩ መንገዶች እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተውለት እንደነበር ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስብሰባው ወቅት ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጹ ጽሁፎች ለተሰብሰብሳቢዎቹ ተበትነዋል፡፡
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መቋቋም ያስፈራቸው ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት በትረ ያቆብን ለሂውማን ራይትስ ዎች፣ ለሲፒጄ፣ ለአርቲክል 19ና ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት ይሰራል፣ ይሰልላል፣ የእነዚህ ድርጅቶች ተላላኪ ነው፣ ሪፖርት ይጽፋል በሚል በመግለጫቸውና ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ›› በተባለው ፕሮግራም ይከሱት እንደነበር ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አገር ውስጥ በነበረበት ወቅት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

ከአዲስ አበባ ካርታ ጋር በተያያዘ የሚደረገው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

May1/2014
ኢሳት ዜና :












የመስተዳድሩ  ባለስልጣናት ያወጡትን የከተማዋን አዲስ ማስተር ፕላን ተከትሎ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚገኙ የኦሮሞ ተወላጆች የጀመሩት ተቃውሞ ወደ ተለያዩ ዩኒቨርስቲዎችና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመዛመት ላይ ነው። በአምቦ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ተማሪዎች በፌደራል ፖሊሶች ሲገደሉ በድሬዳዋ ደግሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ታስረዋል። በአዳማ የተጀመረው ተቃውሞ የረገበ ቢመስልም ውጥረቱ ግን አሁንም እንዳለ ነው።

ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የ6 ኪሎ ተማሪዎች ተቃውሞ ለማድረግ እንቅስቃሴ በጀመሩበት ወቅት የዩኒቨርስቲው ሃላፊዎች ተማሪዎችን አነጋገርው ተቃውሞውን ጋብ እንዲል አድርገውታል። የክልሉ ባለስልጣናት በነገው እለት ተማሪዎችን ያነጋግራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ለማወቅ ተችሎአል። በግንደ በረት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ባስነሱት ተቃውሞም እንዲሁ በርካታ ተማሪዎች ተጎድተዋል።

ተማሪዎች አርሶደሮችን ከመሬታቸው በህገወጥ መንገድ ማፈናቀሉ እንዲቆም እየጠየቁ ሲሆን፣ የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው እቅዱ በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሉ አርሶ አደሮች ከልማቱ ተጠቃሚ ይሆናል በማለት ህዝቡን ለማሳመን እየጣሩ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአሜሪካየውጪጉዳይሚኒስትርሚስተርጆንኬሪ  አዲስአበባበገቡበትዕለትበኢትዮጽያ የአሜሪካኤምባሲከአዲስአበባ እናኦሮሚያየጋራየማስተርፕላንጋርተያይዞበዩኒቨርሲቲተማሪዎች የተቀጣጠለውንተቃውሞመነሻበማድረግአሜሪካዊያንበተለይወደ አምቦአካባቢእንዳይጓዙመግለጫ አውጥቷል።

ኢምባሲው በአምቦ የተነሳውን ከፍተኛ ተቃውሞ ተከትሎ ወደ አካባቢው የሚሄዱ አሜሪካውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግንቦት7 የፍትህ ፣ የነጻነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ  የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በኦሮሞ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ አውግዟል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑንም ገልጿል።

“የኦሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው” ያለው ግንቦት7፣  የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው ሲል አክሏል።

ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋልሲል የሚኮንነው ግንቦት7፣  ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ እንደሚያገባቸው፣ ድምፃቸው ሊሰማ እንደሚገባ ገልጿል።

“የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል እንደሚያገባው፣ ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ እንደሚያገባውና፣ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም። ” ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድም ጥሪ  አድርጓል።  ”

በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።” ብሎአል።

በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ሆነዋል የሚለው ግንቦት7፣ ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አለመፈታታቸውን ፣ ሀሳባቸውን በቲዩተር እና ፌስ ቡክ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሲገልጹ የነበሩ የዞን ዘጠኝ አባላት በአሸባሪ ድራማ በታጀበ ትዕይንት ወደ ማሰቃያ ሥፍራ ከተወሰዱ ቀናት መቆጠራቸውን” በመግለጽ ይህ ሰቆቃ ፣ ጭፍጨፋና አፈና ይቁም” ብሎአል።

አንድነት ፓርቲ ለኢሳት በላከው መግለጫም እንዲሁ በሰፊው የኦሮሞ ህዝብ እና ልጆች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በአጽንኦት እናወግዛለን ብሎአል።

“ምንም አይነት ህዝባዊ ውይይት ሳይደረግበት ከሰማይ ዱብ ያለው የአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የልማት መሪ ፕላን ያስቆጣቸው የኦሮሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰልፍ በማድረጋቸው የደረሰባቸውን ህገ ወጥ ድብደባና እስራት” አንድነት በእጅጉ እንደሚቃወመው ገልጿል።

ተማሪዎቹ ለተቃውሞ አደባባይ ቢወጡ ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበር በተገባ ነበር ያለው ፓርቲው፣ ነገር ግን ሁሉን ነገር ካልጋትኳችሁ የሚለውና ለዴሞክራሲያዊ ሽንፈት የማይገዛው ኢህአዴግ በተማሪዎቹ ላይ ያደረሰውን ጥቃት እንቃወማለን ብሎአል።

የታሰሩ ተማሪዎችም በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣  የኦሮሞ ተማሪዎችን በገፍ ከዩኒቨርሲቲ የትምህር ገበታቸው በማባረር የሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት ከዚህ ተደጋጋሚ ተግባሩ ታቅቦ ልጆቹን በአስቸኳይ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመልስም ጠይቋል።በአጠቃላይ መሬት የዜጎች መያዣ መሆኑ እንዲቀር እንታገላለን ያለው አንድነት፣  ዜጎች በመሬታቸው የመደራደር እውነተኛ መብት ሊኖራቸው እንደሚገባ ተቃውሞ የሚያነሱ ዜጎችም ድምፅ እንዲሰማም አሳስቧል።

ጋዜጠኛ ነብዩና የአንድነት ሊቀመንበር ታሰሩ – ፖሊስ ህገ ወጥ እስሩን ቀጥሏል አንድነቶችም በእስሩ አልበረገጉም

May1/2014
ዳዊት ሰሎሞን
ጋዜጠኛ ነብዩና የአንድነት ሊቀመንበር ታሰሩ
ጋዜጠኛ ነብዩ ሃይሉ የቀስቃሾቹን እንቅስቃሴ ለመዘገብ በወጣበት ለእስር ተዳርጓል፡፡በካዛንቺስ ፖሊስ ጣብያ ከነብዩ ጋር የአዲስ አበባ የአንድነት ሊቀመንበር ዘካሪያስ የማነብርሃንና ዘላለም ደበበ ይገኙበታል፡፡የጣብያው ኃላፊዎች ‹‹ቤተ መንግስት አካባቢ ቀስቅሳችኋል››የሚል ውንጀላ አቅርበውባቸዋል፡፡
ፖሊስ ህገ ወጥ እስሩን ቀጥሏል አንድነቶችም በእስሩ አልበረገጉም
ከአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ለተቸረው ሰላማዊ ሰልፍ የአንድነት አባላት በራሪ ወረቀት በማደል፣ፖስተሮችን በመለጠፍና በመኪና ቅስቀሳ ሲያደርጉ የእውቅናው ደብዳቤ እውቅና ግልባጭ የደረሰው ፖሊስ አባላቱን በማሰር ስራ መጠመዱ አስገራሚ ቢሆንም የፓርቲው አባላት ቅስቀሳውን ከማድረግ አልተቆጠቡም፡፡
ፖሊሶቹ ለያዟቸው የአንድነት አባላት ወረቀት ለመበተን፣ፖስተር ለመለጠፍና የመኪና ላይ ቅሰቀሳ ለማድረግ ፈቃድ አምጡ በማለት ይጠይቃሉ፡፡ነገር ግን ለሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ከሚሰጥ ወረቀት በስተቀር ለቅስቀሳ ተብሎ የሚሰጥ ወረቀት ባለመኖሩ የፖሊስን እስር አስገራሚም አስተዛዛቢም አድርጎታል፡፡ 
የአንድነት አባላት በአሁኑ ወቅት በካዛንቺስ፣በቦሌና ንፋስ ስልክ ፖሊስ ጣብያዎች ታስረው ይገኛሉ፡፡
6110

miilion v 2

Leave a Reply

- See more at: http://satenaw.com/amharic/?p=439#sthash.h4pkwR8I.dpuf

Thursday, May 1, 2014

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ መፈንቅለ ስልጣን መደረጉ ተነገረ!

May 1/2014

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ መፈንቅለ ስልጣን መደረጉ ተነገረ!
ፕሬዚዳንቱ በሌሉበት ሥልጣናቸውን ተነጥቀዋል!
ረቡእ ሚያዝያ 22/2006

በዶ/ር ሽፈራው እና በደህንነት መስሪያ ቤቱ አማካኝነት የሚመሩት የአዲስ አበባ እና የአማራ መጅሊስ አመራሮች መፈንቅለ ሥልጣን ዛሬ መፈጸማቸውን የቅርብ ምንጮች ገለጹ! ይኸው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስና የአዲስ አበባ መጅሊስን ያመሰ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ስልጣን የፌዴራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት ሸኽ ኪያር ሸኽ መሀመድ አማን፣ የፌዴራል መጅሊስ ዋና ጸሀፊ አቶ ሙሀመድ አሊ፣ ከአዲስ አበባ መጅሊስ ደግሞ ኢንጂነር ተማምና ሌላ አንድ ሀላፊ መነሳታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ከስልጣናቸው ተነሱ የተባሉት ፕሬዝደንቱ ሸኽ ኪያር በአሁኑ ሰአት ከአገር ውጪ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በዛሬው መፈንቅለ ሥልጣን በሸኽ ኪያር ቦታ የኦሮሚያ ክልል ተወካዩ መተካታቸው ሲገለጽ፣ የአማራው ክልል ተወካይም የኡለማ ም/ቤቱን መረከባቸው ተሰምቷል፡፡

በዚህ ዛሬ ተጠናቀቀ በተባለው መፈንቅለ ስልጣን ታጋይ የነበሩት የትግራይ ተወካይና ም/ፕሬዝደንት ሸኽ ከድር፣ የአዲስ አበባው መጅሊስ ፕሬዝደንት ዶ/ር አህመድ እና የአማራ መጅሊስ ተወካይ አይነተኛ ሚና እንደነበራቸው የታወቀ ሲሆን ከኋላቸውም ዶ/ር ሽፈራውና የደህንነት ሀላፊዎች ሲመሩት ቆይቷል፡፡ የስልጣን ሽኩቻው ረዘም ላለ ጊዜ የቆየ ሲሆን በድሬዳዋ ከተማ በተካሄደው ጉባኤ ላይም ፈንድቶ እስከመውጣት ደርሶ ነበር፡፡ የሽኩቻው ዋነኛ ምክንያትም ከመንግስት በኩል በግዳጅ ህዝበ ሙስሊሙ ላይ ለመጫን ሲሞከር የነበረው የአህባሽ አስተሳሰብ ዳግም በህዝበ ሙስሊሙ ላይ መጫኑ እንዲቀጥል በሚፈልጉት ወገኖች እና ‹‹ህዝበ ሙስሊሙ ሲቃወመው የነበረው የግዳጅ ጠመቃ ቆሞ መጅሊሱ ሁሉንም ሙስሊም በአንድነት ሰብስቦ እና አቻችሎ መቀጠል አለበት›› በሚሉት ዛሬ ከስልጣን በተወገዱት ሀላፊዎች መካከል ያለው የአቋም ልዩነት መሆኑ ታውቋል፡፡

እስካሁን በነበረው ሂደት የመጅሊሱ ፕሬዝደንት ‹‹መጅሊሱ ህዝበ ሙስሊሙን የሚጠቅም እና በሰላም እንዲኖር የሚያደርግ እንጂ ችግር ውስጥ የሚያስገባ አካል መሆን የለበትም›› የሚል ፅኑ አቋም ይዘው የነበረ ሲሆን በሸኽ ከድር በሚመራው ቡድን እየተደረገ ያለውን ህዝበ ሙስሊሙን ዳግም ወደ ተቃውሞ ሊያስገባ የሚችል ትንኮሳ በመቃወምም ለተለያዩ የመንግስት አካላት ደብዳቤ መፃፋቸው ታውቋል፡፡

በሕገ ወጡ መጅሊስ ውስጥ ከላይ እስከታች የሚታየው የስልጣን ሽኩቻ የተቋሙን አመራር ሕገ ወጥነት አመላካች ከመሆኑም በላይ በመንግስት የተሰጠውን የቤት ስራ ለመፈጸም የተሰባሰበ ቡድን መሆኑንም ክስተቱ እማኝነት ሰጥቷል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችና ማብራሪያዎች በነገው እለት ይኖሩናል - ኢንሻአላህ!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች ይቀጥላል!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

በኖርዌይ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎች አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ የሚያደርጉትን ሰላማዊ ትግል እንደሚደግፍ አጋርነታቸውን አሳዩ

 May 1/2014 

በዛሬው ቀን በኖርዌይ በተከበረው አለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን ላይ በመገኛት የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎች አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ  በሀገር ቤት እያደረጉ ያሉትን ሰላማዊ ትግል እንደሚደግፋ አጋርነታቸውን ሲያሳዩ ውለዋል::

May 1/2014 በዛሬው ቀን በኖርዌይ በተከበረው አለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን ላይ በመገኛት የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ በሀገር ቤት የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል እንደሚደግፍ አጋርነቱን አሳያ::
ሜይ 1, አለም አቀፍ የላብ አደሮችና የሰራተኞች ቀን በየአመቱ በመላው አለም በተለያዩ አህጉራት በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ይታወቃል:: ይህ መከበር ከጀመረ ከመቶ ሃያ አመት በላይ የሆነው የላብ አደሮችና የሰራተኞች ቀን ዘንድሮም ሜይ 1 ቀን 2014 (ሚያዚያ 23 ቀን 2006 ዓ.ም ) በተለያዩ አህጉራት ተከብሮል::
በዛሬውም ቀን ሜይ 1 ቀን 2014 በኦስሎና በኖርዌይ በተለያዩ ከተሞች በደማቃ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ በሰብአዊ መብትድርጅቶች፣ ሌሎችም ድርጅቶች እንዲሁም በኖርዊይ የሚኖሩ የተለያዩ ሀገራት ማህበረሰብ ክፍሎች (community) የየሀገራቸውን ባንዲራ እና የየድርጅታቸውን አርማ በመያዝ የሰራተኛውን መብት መከበር የሚጠይቁና ሌሎችንም የተለያዩ መፈክሮችን፣ አርማዎችን መያዝ በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል::
በኦስሎ እና በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎች የድጋፍ ድርጅቱ ለአባሎቹ ባደረገላቸው የሰልፍ ጥሪ መሰረት ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በዚሁ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን የሰብዊ መብት እረገጣ የተቃወሙ ሲሆን ለአንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ ያላቸውንም ድጋፍ አሳይተዋል:: በአሁኑ ሰአት የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን የሰበሃዊ መብት እረገጣ ፣አፈና፣ እስራትና ግድያ በመቃወም አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ሰማያዊ ፓርቲ ሰለማዊ ትግል እያደረጉ እንዳለና በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት እየተፋለሙት እንደሆነ ይታወቃል::

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎችና አመራሮች የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ እና በማሰማት ለአንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ ያላቸውን የድጋፍ አጋርነታቸውን በማሳየት በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል::
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!! 

ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

May 1/2014

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲንቅናቄ፣ ዘረኛው ወያኔ በኦሮሚያ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ ይቃወማል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ያስገነዝባል።
የአሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው። የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ነዋሪዎቹን ያላማከረ፣ ግንባር ቀደም ባለጉዳዮችን ባለቤት ያላደረገ፣ የሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ ማስተር ፕላን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም።
ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋል። ኦህዴድ በወያኔ ቅጥረኛነት የኦሮሚያ ወጣቶችን በማስጨፍጨፍ ላይ ያለ እኩይ የአድርባዮች ስብስብ ነው።  ወጣቶች የተቃወሙት ይህንን ነው።እነዚህ ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባቸዋል። ድምፃቸው ሊሰማ ይገባል። የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል ያገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ ያገባናል። በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድ ጥሪ ያደርጋል።  በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።
የወያኔ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይን ያነሱ ወጣቶች ብቻ  አይደሉም። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ናቸው። ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አልተፈቱም።  ይህ ሰቆቃ ማብቃት አለበት።
ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

በኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ መካረረ ስጋት ፈጥሯል

ኦህዴድ የተከፋፈለ አቋም ይዟል፤ ኢህአዴግ ጉልበት መርጧል
demo


በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት በሞከሩና ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ሰልፍ በወጡ ወገኖች ላይ አገዛዙ የ”ከፋ” ነው የተባለ ሃይል መጠቀሙ ተሰማ። ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ታስረዋል። ለተቃውሞ መነሻ በሆነው አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ላይ ኦህአዴድ ተመሳሳይ አቋም መያዝ አልቻለም። ችግሩን በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያልቻለው ኢህአዴግ ጉልበት መምረጡ አገሪቱ ውስጥ ካለው የተከማቸ ብሶቶች ጋር ተዳምሮ አለመረጋጋቱን ያሰፋዋል የሚል ስጋት አለ።
ከኦሮሚያ ክልል አስተዳደር የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት በአቀራረቡ ቢለያይም ከተለያዩ ሚዲያዎች የሚሰሙት ዜናዎች ሊስተባበሉ የሚችሉ አይደሉም። በታችኛው እርከን የሚገኙትን ጨምሮ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በጥቅሉ፣ ገሃድ አይውጣ እንጂ በመዋቅር ውስጥ ያሉ ሰራተኞችና ካድሬዎች የተቃውሞው ተሳታፊና ደጋፊ መሆናቸውን ክልሉም ሆነ ኢህአዴግ አረጋግጠዋል።
የአዲስ አበባ አዲሱ ማስተር ፕላን በዙሪያዋ ያሉትን ስድስት የኦሮሚያን ከተሞችና ስድስት የገጠር ቀበሌዎች የተካተቱበት መሆኑ ያስነሳው ተቃውሞ ቀደም ሲል በክልሉ በምክር ቤት ደረጀ በካድሬዎች ተቃውሞ አጋጠመው። ይህንኑ ተከትሎ ከሳምንት በፊት በአንዳንድ የትምህርት ተቋማት ብልጭ ድርግም ሲል የነበረው ተቃውሞ እየጠነከረ መጣ። የክልሉ የጎልጉል ምንጭ “ተቃውሞው እንደሚጨምር፣ ካድሬውም የተቃውሞው ስውር አጋር እንደሆነ፣ በመረጃ ትንተና አስቀድሞ ይታወቅ ነበር። በዚሁ መሰረት አስቀድሞ አመጹን ማምከን ካልተቻለ የማያዳግም ርምጃ እንዲወሰድ ለፌዴራልና ለመከላከያ አባላት መመሪያ ተሰጥቷል”።
የሰላማዊ ሰልፍ በሚጀመርበት አካባቢ ሌላውን “ሊያስተምር” የሚችል ከበድ ያለ የሃይል ርምጃ እንዲወሰድ በተላለፈው መመሪያ መሰረት ተግባራዊ ቢደረግም ረብሻውና የተቃውሞ እንቅስቃሴው እየሰፋ መሄዱን የጎልጉል መረጃ አቀባይ ይናገራሉ። ከከተማ ወደ ከተማ እየሰፋ የሄደው ተቃውሞ፣ የተቃውሞው አካል በሚመስሉ የስለላ ሰራተኞች በሚያቀብሉት መረጃ መሰረት ለማስታገስ ቢሞከርም አለመቻሉ ኢህአዴግ ውስጥ ጭንቀት ፈጥሯል።
የኦህዴድ አባላት በከፍተኛ አመራር ላይ ያሉትን ጨምሮ ተመሳሳይ አቋም ያልያዙበት አዲሱ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይ በኦሮሚያ የተላዘበውን የፖለቲካ ችግር ሊያባብሰው ይችላል በሚል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኢህአዴግ የፖሊስ የመከላከያ ሃይላት ከልዩ መመሪያ ጋር በተጠንቀቅ እንደቆሙ ምንጩ አመልክተዋል። ይሁን እንጂ በኦህዴድ የታችኛው የቀበሌ መዋቅር ጭምር ተቃውሞው ስለሚደገፍ የአቋም መንሸራተት ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት ከፍተኛ መሆኑንንም አልሸሸጉም።
ከተለያዩ የማህበረሰብ አምዶች ሲደመጥ እንደሰነበተውና ሚያዚያ 22፤2006 (ኤፕሪል 30/2014) ቀን የአሜሪካ ሬዲዮ ከስፍራው ሰዎችን በማነጋገር እንደገለጸው ጅማ፣ አዳማ፣ ነቀምት፣ አምቦ፣ ሃሮማያ፣ ድሬዳዋ፣ በመሳሰሉት ከተሞችና የትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ ላሰሙት የተቃውሞ ድምጽ የተሰጣቸው ምላሽ ዱላና እስር ነው። ከአምቦ በስልክ ስለሁኔታው የተናገሩ እንዳሉት አላፊ አግዳሚው ሳይቀር “ተጨፍጭፏል”።
በተጠቀሰው ቀን ረፋዱ ላይ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ ከሰዓት በኋላ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተቃውሞ ሲወጡ የመከላከያ አንጋቾችና የፌዴራል ፖሊስ አባላት በወሰዱት የሃይል ርምጃ በርካቶች መቁሰላቸውን፣ በነፍስ አውጪኝ አጥር ዘለው የሸሹትን በማሳደድ ጨፍጭፈዋቸዋል። እኚሁ ሰው በስልክ እንደተናገሩት “ሸሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው የመጡትን ተማሪዎች ለምን ቤትህ አስገባህ ተብዬ ተጨፈጨፍኩ፣ ነፍሴን ለማትረፍ መሬት እየተንከባለልኩ ጮህኩ። ሁለት ልጆቼን ወሰዱ” በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል። የአምቦ ቤተመንግሥትም እስረኛ እንደሞላው አመልክተዋል።
ለማቅረብ ከያዟቸው ሶስት ጥያቄዎች መካከል አንዱ “ፊንፊኔ ያለው የአጼ ሚኒሊክ ሃውልት ይነሳ የሚል ነው” በማለት ፈርቶ እንደተሸሸገ የተናገረ ተማሪ ከአዳማ ለቪኦኤ ተናግሯል። የቪኦኤው ዘጋቢ ባለስልጣናትን ለማነጋገር ሞክሮ እንዳልተሳካለት፣ በመጨረሻም ከኦሮሚያ ምክር ቤት ያገናቸው ሰው መልስ ሳይመልሱ እንደመሳቅ እያሉ ስልኩን እንደዘጉት በግብር አሳይቷል።
ከምርጫ 97 በፊት አዳማን የኦሮሚያ ዋና ከተማ መደረጓን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ችግር ከምርጫ 97 በኋላ ቀውሱ እልባት እንደተበጀለት ይታወሳል። በወቅቱ በሜጫና ቱለማ ማህበር አስተባባሪነት አዲስ አበባ ላይ የተካረረ ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበርም አይዘነጋም። በዚያን ወቅትም የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ድሪቢን ጨምሮ በርካቶች ታስረው ነበር። ኢህአዴግ አቋሙን ለምርጫ ቀውስ ማርገቢያ በሚል ሲቀይር፣ ድርጊቱን አስቀድመው በመቃወማቸው የተገረፉ፣ የታሰሩና ከስራ እንዲሰናበቱ የተደረጉ ካሳ ሊሰጣቸው እንደሚገባ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።
አገሪቱ ላይ ከተንሰራፋው የተለያየ ችግር ጋር ተዳምሮ በኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ እንዳይካረር ስጋት የገባቸው ክፍሎች “ኢህአዴግ ጉልበት እየተጠቀመ የሚዘራውን ቂምና ቁርሾ ካላቆመ፣ ጠብመንጃ እጄ ላይ ነው በማለት የሚፈጽመውን ግፍ በማቆም ለእርቅ ካልሰራ አሁን ባለው ሁኔታ ነገሮች ከቁጥጥር ሊወጡ” እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ይሰጣሉ፤ ጂኒው አንዴ ከሳጥኑ ከወጣ በኋላ ልዩነት ሳያደርግ የሚያመጣው መዘዝ ለህወሃት/ኢህአዴግና በቅድሚያ ከዚያም ለሥርዓቱ ባለሟሎች በተዋረድ የሚባላ እሣት እንደሚሆን ታስቦ ካሁኑ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ይላሉ።

ሰሚ ጆሮ ያጣ የሕዝብ እሮሮና ጩኸት እስከመቼ? ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ ሌና

By Gezahegn Abee (Norway Lena )

 ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ ካለችበት የኢህአዲግ ስርአት ለመላቀቅ እና ከገባችበት ፖለቲካዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሜያዊ ውድቀት ወጥታ ህዝቡም ከወያኔ ስርዓት ተላቋ ወደ ተሻለ እና ወደ ተረጋጋ ሕይወት ለመድረስ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እና በሁሉም አቅጣጫ እና በሚችለው መንገድ መታገል ይጠበቅበታል:: ዛሬ ላይ ወያኔ ኢህአዲግ የእምነታችንን ነጻነት እያሳጣን የዜጎቻችን ሰብዓዊ መብት እየረገጠ እና የዜግነት ክብራችንን እና ነፃነታችንን በመግፈፍ የባርነት ኑሮ እየኖርን እንገኛለን::  መቼም በአሁኑ ጊዜ በጨቋኙ የወያኔ ስርአት ያልተማረረ የህብረተሰብ ክፍል ያለ አይመስለኝም ስለሆነም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ ሀይማኖት፣ ዘርና፣ቋንቋ
ሳይዘው ሊጠይቀው የሚገባ የመብትና የነጻነት ጥያቄ ሊሆን የሚገባው  እስከ መቼ ? በወያኔ መንግስት የግፍ ስርዓት  እየተጨቆኑ መኖር ብለን እራሳችንን ልንጠይቅ ያስፈልጋል::

በርግጥ በአሁኑ ሰአት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሀገር ቤትም የሚኖረው ከሀገር ውጭ ተሰዶ የሚኖረውም (ዲያስፖራ) ኢትዮጵያዊ በሚችለው መንገድ ሁሉ ወያኔንን በመቃወም እና በመፋለም የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውንም ግፍ እና በደል ለአለም ህዝብ እና መንግስታቶች ለማሳወቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ  እንዳለ ይታወቃል::በተለይም  በወያኔ መንግስት ጨቋኝ እና ዘረኛ አገዛዝ ተጠቂ የሆነው በሀገር ውስጥ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሕዝባችን ከማንኛውም ጊዜ  በባሰ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ እና እየደረሰበት ካላው ችግር የተነሳ በየጊዜው ድምጹን እያሰማ እንዳለ ይታወቃል:: በሀገር ውስጥም ሆነው መሰዋህትነትን  እየከፈሉ ያሉ  በሰለማዊ ትግል የወያኔን አቅም ማሽመድመድ እና ከስልጣን ማስወገድ ይቻላል በማለት አምነው እና ቆርጠው የተነሱት እንደ ሰመያዊ ፓርቲ እና አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ የመሰሉ ፓርቲዎች ሕዝቡ ብሶቱን እና ምሪቱን በአደባባይ እንዲያሰማ  እያደረጉት ያለው ሰላማዊ ትግል የሚያስመሰግናቸው ነው :: እነዚህ ፓርቲዎችም  የኢትዮጵያ ሕዝብ ህገ መንግስታዊ መብቱን እንዲያስከብርና ለነጻነቱም እንዲታገል እያነቁት ሲሆን ፣ በአሁኑ ሰአት ለመብቱ እና ለነጻነቱ በየጊዜው ድምጹን እያሰማ እና በአደባባይ እየጮኸ  ይገኛል :: ቢሆንም ሀገርን እመራለው ሕዝብንም አስተዳድራለው ብሎ ከተመጠው መንግስት ነኝ ባይ አካል ግን ምንም አይነት የሕዝቡን እሮሮና ጩኸት አዳምጦ የሕዝብን ጥያቄ የመመለስ ነገር አይታይም::

የኢትዮጵያ ሕዝብም ሕገ መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ ሀገርን እመራላው ብሎ ለተቀመጠው አካል ድምጹን ማሰመትና መብቱን መጠየቅ ሕገ መንግስታዊ መብቱ ቢሆንም ነገር ግን ይሄ መብቱ ሲከበርለት አይታይም :: በወያኔ መንግስት በኩል በተቃራኒው የሚሆነው ግን ሌላ ነው ሕዝቡ ብሶቱን ለማሰማት በተነሳ ጊዜ ዜጓችን ማዋከብ፣ ማስፈራራት፣ ማሰርና፣ የተለያዩ በደሎችን በዜጎቹ ላይ መፈጸመ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣ አሳሳቢ የሆነና የወያኔ መንግስት የለመደው የእለት በእለት ተግባሩ ሆኖል::

በርግጥ በአሁኑ ጌዜ የምርጫም ጊዜም እየደረሰ ከመሆኑም የተነሳ ሕዝብን ለማታለልና በኢትዮጵያ ላይ ዲምክራሲ እንዳለ ለማስመሰል በምህራባውያን ዘንድ የፖለቲካ ቁማሩ እንዳይበላሽበት በፓርቲዎች ጥያቄ ሳይወድም ቢሆን በስንት መከራ ሰላማዊ ሰልፎችን የማድረግ መብትን የፈቀደ ቢመስልም  ሕዝብን እና የፖለቲካ ድርጅት አመራሮችን ግን በአይነ ቁራኛ በመከታተል ፣ በማዋከብ፣በማሰር ላይ ይገኛል:: ሕዝቡ በተለያያ ጊዜ በሰላማዊ ሰልፎች በየጊዜው ጩኸቱን እያሰማ ቢሆንም የሕዝብ ጩኸት ግን  አዳማጭ ያገኘ አይመስልም:: በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎች ሕዝቡ  እየጠየቀ ላለው ጥያቄ የወያኔ መንግስት የሕዝብን ጩኸት ሰምቶና አዳምጦ መልስ ይሰጣል ብሎ ማሰብ ሲበዛ እጅግ የዋህነት ይመስለኛል:: የወያኔ መንግስት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር፣ መከራ ምንም የማያሳስበው መንግስት እንደሆነ በተለያየ ጊዜ ያየነውና የተረዳነው ነገር ሲሆን በአለም ላይ በተለያዩ ሀገራት ከሚኖሮ ሕዝቦች መካካል በአሁኑ ጊዜ እንደ ኢትዮጵያ ሕዝብ እየተዋረደና መከራ እየደረሰበት የሚኖር ያለ ሕዝብ ያለ አይመስለኝም በቅርቡ እንኮን እንደምናስታውሰው በሳውድ አረቢያ በጨካኝ አረመኔ አረቦች ሕዝባችን በአደባባይ እንደ በግ ሲታረድ በአለም ዙሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከዳር እስከ ዳር በአንድነት በኢትዮጵያዊ ስሜት በጩኸት ድምጻቸውን ሲያሰሙ በጊዜው በወያኔ መንግስታቶች ዘንድ የሕዝባችን እንደ በግ በአደባባይ መገደል እንደ ምንም ነገር ቦታ ያልተሰጠው ጉዳይ እንደነበር እና የወያኔን መንግስት በብዙዎች ዘንድ ለትዝብት የዳረጋቸው ክስተት እንነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው ::

ይህ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሀገሩ ላይም መኖር አቅቶታል ጮኸቱንም ያሰማል የሕዝቡም ጩኸት ማብቂያ ያለው አይመስልም ሰመያዊ ፓርቲም ቢሆን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ በአሁን ሰአት ሕዝቡ ብሶቱንና በመንግስት ላይ ያለውን ተቃውሞ እንዲያሰማ በየጊዜው የሰለማዊ የተቀውሞ ሰልፎችን እያዘጋጁ እና በወያኔ መንግስት ላይ የተቃውሞ ድምጻቸውን እያሰሙ ቢሆኑም  የወያኔ መንግስት ግን የሕዝብን ጥያቄ የመመለስ አዝማሚያ አይታይበትም  ነገር ግን  በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የሕዝብን እሮሮና ብሶት ማዳመጥ ሕገ መንግሥታዊ ግዴታው ነው፡፡ እነ እስክንድር ፣ርዕዮትና ፣ አንዶለም ሌሎቹም የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞች  በየእስር ቤቶች ውስጥ በእስር በማቀቅ ላይ ባሉበት ሁኔታ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የአለም የሰባሃዊ መብት ተከራካሪዎች ሳይቀሩ ያለበደላቸውና ያለሀጢያታቸው በግፍ በእስር ላይ ያሉ እስረኞች  ከእስር እንዲፈቱ በየጊዜው በመጠየቅና በውጭ ሀገርም በሀገር ውስም የሚኖሩ ኢትዮጵያ ዜጎች በተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎች በመሰብሰብ ስለወገኖቻችን ቢጮኽምጩኸቱም ሰሚ ጆሮ ያጣ ጩኸት እየሆነ ይገኛል::

የኢትዮጵያ ሕዝብ በየጊዜው ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞች ከእስር እንዲፈቱ በሰላማዊ ሰልፎች ይጮኻል ነገር ግን የወያኔ መንግስት ህገ መንግስቱን አክብሮና የሕዝብን ጩኸት ሰምቶ ለሕዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ሲገባው ያለምክንያት ያስራቸውን ዜጓች ከእስር ከመፍታት ይልቅ የሕዝብን ጩኸት ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ከቀን ወደ ቀን ሕዝብን በማተራማስና ሌሎች ንጹሃን ዜጎችንም እያደኑ በመያዝና በማሰር ስራ ላይ ተደምጦል::

 እነ አንዷለም አራጌ ፣እነ በቀለ ገርባ ፣ እና ናትናሄል እና ሌሎችም እስረኞች ከቃሊቲ እንዲወጡ ሕዝብ እየጮኸ ባለበት ሁኔታ ሌሎች በብዙዎች የሚቆጠሩ አንዷለሞች፣ ሌሎች በቀለዎች፣ ሌሎች ናትኖሄሎች ለእስር እየተዳረጉ ነው እነ ርዕዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸትንና ሌሎች በግፍ የታሰሩ ጋዜጠኞች ከእስር እንዲፈቱ እየጮኽን ባለንበት ሁኔታ ሌሎች ርዕዮቶችና ሌሎች እስክንድሮች፣ ሌሎች ውብሸቶች ወያኔ በሚያቀርባቸው የሃሰት ውንጀላዎች እየተከሰሡ ወደ እስር ቤት እየተወረወሩ ሲሆን  ሰሞኑንም እያየን ያለነው ያለነው ይኼንኑ ነው :: ሕዝብን አስሮ የማሰቃየት ሀባዜ የተጠናወጠው አንባ ገነኑ የወያኔ መንግስት በማን አለብኝነት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሌሎች  ጋዜጠኞችን በማያዝ አስሯቸዋል::እነዚህ ወገኖቻችን  ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው ግን ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ያሉና በህገ መንግስቱ መስረት የሕገ መንግስቱን አንቀፅ እየጠቀሱ የሃሳብ የመግለፅ መብታቸውን የተጠቀሙ ሶስት ጋዜጠኞችን እና ስድስት ብሎገሮችን በተለያየ የሀሰት ወንጀል በመወንጀል ለእስር መዳረጉ ወያኔ ምን ያህል በእምቢርተኝነት ልቡን እያደነደነ ያለ አንባ ገነን መንግስት እንደሆነ በገሃድ ቁልጭ አድርጎ ያሳይ ሀቅ ነው::  ይህ ሁሉ ግን የሚያሳያው ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ዜጎችን በተለያየ የሀሰት ውንጀላ በመወንጀል ማሰረኑንና ሕዝብን ማሰቃየቱ እንደማይቀር የሕዝቡም ስቃይ፣ መከራ፣ እስራታ እና ግድያ እስከ መቼ እንደዚህ ይቀጥላል ? የእኔም ጥያቄ የብዙዎቻችን ጥያቄ የወያኔ አንባ ገነንተ እስከ መቼ ? ሰሚ ጆሮ ያጣው የሕዝብ ሮሮ እና  ጮኸትስ እስከ መቼ ?

እንደእኔ አመለካከት ህዝባችን በሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፎች አረመኔው የወያኔ መንግስት ለሕዝቡ ጥያቄ  መቼም ቢሆን መልስ ለመስጠት ፍቃደኛ  ይሆናል ብዪ አላስብም::ነገር ግን የወያኔን መንግስት ይበልጥ ሊያዳክሙ የሚችሉትን ስልቶችን ( strategy) በመንደፍ ትግላችንን ብንቀጥል ወያኔን ማንበርከክ ይችላል የሚል እምነት አለኝ:: ለነገ የሕዝብ እሮሮ እና ጩኸት ተሰምቶ ህገ መንግስቱ የሚከበርባትንና ዜጎች በነጻነት የሚኖሩባት ኢትዮጵያን እየተመኛው ለዛሬ ጹሁፊን ላጠቃል ::

ውድቀት ለአንባ ገነኖች!!
  gezapower@gmail.com