Friday, February 7, 2014

የእኛ ታሪክና የፖለቲካ ውጥንቅጥ፡-

February 7/2014

ጥቂት አሳቦች በሞገደኛው ተክሌ ወሥርጉተ ሥላሴ ጽሑፎች ላይ (ክፍል-፩-) በዲ/ን ኒቆዲሞስ ዕርቅ ሁንይ

ሥርጉተ ሥላሴ የተባሉ ጸሐፊ በተለያዩ ጊዜያት የሚጽፏቸውን በአብዛኛው ታሪካዊ የሆኑ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርስ አዘል፣ በኃይለኛው አገራዊ/ኢትዮጵያዊ ዘዬ፣ ትውፊትና ባህል የተጫነው የሚመስለውንና፤ (ይህን ለማረጋገጥ የሚወድ ጸሐፊዋ ‹‹ኢትዮጵያዊነት የሚነበብ መንፈስ ነው›› በሚል ርእስ ያስነበቡትንና ‹‹የኢትዮጵያዊነትህን መንፈስ በቅጡ ካልተረዳኸውና ካልተቀበልከው ‘ጉግ ማንጉግ’ የኾነ አንካሳ መንፈስ ይጨፍርብኻል፡፡›› እስከ ማለት የደረሱበትን፣ በኢትዮጵያዊነት ወኔ፣ ስሜትና ረቂቅ መንፈስ ፈጽሞ የሰከረውን መጣጥፋቸውን ማየቱ የሚበቃው መስለኛል፡፡) እንዲሁም ምክርና ትችት ዘመም የኾኑ፣ እንዲያም ሲል ‹‹የኢትዮጵያዊነት ወኔና ስሜት›› በእጅጉ ጎልቶ የወጣበትንና ያየለበትን መጣጥፎቻቸውን ለማንበብ ዕድሉ ገጥሞኛል፡፡
ይህችን ‹‹ዘመም›› የምትል አብዮተኛ ቃል ያለ ምክንያት አይደለም እዚህ ጋር የሰነቀርኳት፡፡ የትናንትናው ትንታግና አብዮተኛው ያ ‹‹ሩቅ አላሚ ቅርብ አዳሪ›› የኾነው ትውልድ ‹‹ያለ ምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም!›› ብሎ ያቀጣጠለው የለውጥ አብዮት፣ ወደ ለየለት አሰቃቂና አስፈሪ ነውጥና ፍጅት ተለውጦ፣ በሂደትም ‹‹አብዮት የገዛ ልጆቿን እንኳን ሳይቀር ትበላለች!›› ወደሚል አስፈሪ ፃረ ሞትነት ተቀይሮ ‹‹በግራና ቀኝ ዘመም›› በሚል ምድሪቱን ‹‹አኬል ዳማ/የደም ምድር›› እንድትሆን ያደረገበትን ያን የእምዬ ኢትዮጵያን የጨለማና የሰቆቃ ዘመንዋን እግር መንገዴን ለማዘከር ጭምር ነው፡፡
ያችን በማኅፀንዋ አብራክ ክፋይ፣ በገዛ ልጆቿ የአብዮት ደም ጅረት ታጥባና ተነክራ፣ በኀዘንና በብርቱ ሰቆቃ መንፈሷ ደቆና ቅስሟ ተሰብሮ፣ የኀዘን ከል ለብሳ፣ ከዘመን የተኳረፈችውን ኢትዮጵያን፣ የዛን ጊዜው የቀ.ኃ.ሥ የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ የነበሩት አንጋፋው ምሁርና ዛሬም እንኳን በእርጅናቸው ዘመን፣ በአብዛኛው የጥላቻና የመለያየት ነጋሪት ከሚጎሰምበት ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ጋር ለመፋታት አልሆንልህ ያላቸው፣ ጉምቱው ፖለቲከኛ ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪነታቸው ዘመን በቋጠሯት ግጥማቸው/ስንኛቸው የዛን ዘመኗን እምዬ ኢትዮጵያን እንዲህ ነበር የገለጽዋት፡
-
ይኽው ትታያለች ለሕዝብ በይፋ፣
ጥቁር ተከናንባ ጥቁር ተጎናጽፋ፡፡
እኔስ መስሎኝ ነበር ዘመድ የሞተባት፣
የእናት ሞት የአባት ሞት፣
የልጅ ሞት ያጠቃት፣
ለካ እሷስ ኖራለች ዘመን የሞተባት፡፡
ውድ አንባቢዎቼ ያው እንግዲህ ዘንድሮ አብዮቱ ዐርባ ዘመንም እየሞላውም አይደል እንዴ?! እስከ ጥፋቱና ልማቱም ቢሆን የዚህ የዛሬው ትውልድ አባል የኾንኩ እኔ፣ ያ ትውልድ ለውድ እናት አገሩና ለወገኑ ከነበረው ፍቅርና መቆርቆር የተነሣ በእንባው፣ በላቡና በደሙ የከፈለውን ያን ግዙፍና ታላቅ መሥዋዕትነት የማደንቅ ብቻ ሳልሆን የውለታው ባለ ዕዳ ነኝም ብዬ ነው የማስበው፡፡ እናም እንዲህ እግር መንገዴንም ቢሆን ያን ትንግረተኛ ትውልድ ላነሳሳው፣ ልዘክረው ወደድኹ፡፡
በነገራችን ላይ እናንተ በዲያስፖራ የምትገኙ የዛ ትውልድና የታሪኩ ባለቤቶች የዛን ትንታግ ትውልድ የለውጥ እንቅስቃሴውን ለመዘከር አንዳንች ነገር አላሰባችሁም እንዴ! እስቲ ከጥላቻ ፖለቲካው፣ ከመለያየቱ፣ በጎሪጥ ከመተያየቱና ከመፈራረዱ ለአፍታ ወጣ በሉና እነዛን ደማቸውን ለሕዝቦችህ ፍትሕና ዕኩልነት፣ ለሰው ልጆች መብትና ክብር መስፈን፣ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ዕውን መሆን ሲሉ በየጎዳናው፣ በየጋራ ሸንተረሩና ተራራው ያፈሰሱትን የትውልዳችሁን/የጓዶቻችሁን ታሪክና ውለታ ለእኔና ለትውልዴ በፍቅር፣ በቅንነትና በበጎነት መንፈስ ልታስተላልፉን/ልታሳውቁን ሞክሩ፣ እሹም፡፡
‹‹ንግባኤከ ኀበ ቅድመ ነገር/ወደቀደመው ነገር እንመለስ›› እንዲል መጽሐፉ፡፡ ለዚህ ለዛሬው መጣጥፌ ዐብይ ምክንያት የኾኑኝ በኢትዮጵያዊነት ሕያው መንፈስና ቅናት እየነደዱና እየተቃጠሉ ያሉት ጸሐፊዋ ሥርጉተ ሥላሴ፣ የትናንትናው ወይም የዛሬው የእኔው ትውልድ አባል ይሁን አይሁኑ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ስለ ጉምቱ ብዕረኛው አቶ ተክለ ሚካኤልም ቢሆን እንዲሁ፡፡’
ለማንኛውም ግን ዋና አነሳሴ እነዚህን ብዕርተኞች በትናንትናውም ሆነ በዛሬው የትውልድ ተርታ ለማሰለፍ አይደለም፡፡ በተጨማሪም ታሪኩን በደሙ የጻፈውንና ያጻፈውን የትናንትናውን ትውልድ የትግል እንቅስቃሴውን ለመዘከርና ውለታውንም ለማሰብ ወይም ለማሳሰብ አይደለም፡፡ ግና በዚህ ጽሑፌ ሥርጉተ ሥላሴና አቶ ተክለ ሚካኤል በተለያዩ ጊዜያት ያስነበቧቸው መጣጥፎቻቸው አንዳንች የቅናት ስሜትን ስላጫረብኝ እኔም የበኩሌን ዕዳ ለመወጣት በማለት ነው ብዕሬን በድፍረት ያነሣሁት፡፡
የቀድሞው የኢሳት ቴሌቪዥን ባልደረባ የነበሩት ሞገደኛው አቶ ተክሌ በተለያዩ አገራዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎችና ክርክሮች ዙሪያ የሚያንሸርሽሯቸውን ጽሑፎች እከታተላለሁ፣ አደንቃለሁም፡፡ አቶ ተክሌ ከሰሞኑን ባስነበቡን መጣጥፋቸው በወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጀዋር መሐመድና ደጋፊዎቹ የተነሳውን የሰሞኑን ሚጢጢዬ አብዮት አስመልክቶ ኢህአዴግ ከሚያራምደው የብሔር ፖለቲካ አንፃርና በተቃራኒው ከአንድነት ኃይሎች አቋም ጋር በማዛመድ ‹‹ተወደደም ተጠላ የአንድነት ኃይሎች ለብሔር ፖለቲካ ሰፊ የመጫወቻ ሜዳ ለመስጠት ባለመቻላቸው በኢህአዴግ ተበልጠዋል፡፡
እናም እነ ጃዋርም ኾነ ለረጅም ዓመታት የኦሮሞን የመገንጠል ጥያቄ በብርቱ ሲያቀነቀኑ የነበሩ የኦሮሞ ብሔርተኞች፣ አንጋፋውን የኦነግ ታጋይ እነ ሌንጮን እንኳን ሳይቀሩ ቢያንስ ቢያንስ በመርህ ደረጃ ያን መብታቸውን በሚያከብርላቸውና በራሳቸው ቋንቋ የሚያስተዳድሩትን ክልል በሰጣቸው በኢህአዴግ ጉያ ውስጥ ለመወሸቅ እያኮበኮቡ ነው፡፡›› የሚል አንድምታ ያለው ጽሑፍን አስነብበውናል፡፡
የዲያስፖራውን ፖለቲካ በአለፍ ገደም በመተቸትና የሰሞኑን የኦሮሞ ብሔርተኞች ፀረ-ምኒልክ ዘመቻ አስመልክቶ በአንድነትና በብሔር ፖለቲካ አቀንቃኞች መካከል የተነሣውን፣ በአዲስ አበባውያኑ አራዳዎች የፌስ ቡክ አድማቂዎች ዘንድ ‹‹አቧራው ጨሰ›› የተተረተበትን የሰሞኑን ክስተት በማስመልከት አቶ ተክሌ ያሰፈሩትን አሳብ እህታችን ሥርጉተ ሥላሴ የሚመች ብቻ ሳይሆን የማይቀበሉትም እንደኾነ በሰፊው አትተው ጽፈዋል፣ ተጨባጭ ያሏቸውን ምክንያቶችንም በመደርደር ለመከራከር ሞክረዋል ፡፡
የእነዚህ ብዕረኞች ፍቅር፣ ቅንነትና ጨዋነት የተሞላው የአሳብ ልውውጣቸውና በምክንያት የተደገፈ ክርክራቸውም ይበል ሚያሰኝና አልፎ አልፎ በየድረ ገጹ፣ ጋዜጣውና መጽሔቶች ላይ ባልተገራ ብዕራቸውና ሰብእናቸው ብቅ እያሉ አሳብን በአሳብ ከማሸነፍ ይልቅ ስድብና ጥላቻ፣ ዛቻና ማስፈራሪያ፣ ፉከራና ቀረርቶ ለሚቀናቸውና፣ እንዲያም ሲል የስም ማጥፋት ዘመቻ (character assassination) ውስጥ ለሚዶሉ ጸሐፍቶቻችን ጥሩ ምሳሌና አርዓያዎች ናቸው ብዬ አስባለኹ፡፡
በመሠረቱ የእነዚህ ክቡራን ጸሐፊዎች የወንድማችን የአቶ ተክሌና የእህታችን የሥርጉተ ሥላሴ የሰሞኑን የአሳብ ልውውጥና ሙግት በአብዛኛው ትኩረቱን ያደረገው የብሔር ፖለቲካን በሚያራግቡና በተቃራኒው ደግሞ አንድነትን በሚያራምዱ ፓርቲዎችና ፖለቲከኞቻችን ዘንድ ያለውን ክፍተት፣ ልዩነትና ርቀት ለማሳየት፣ ለመገምገምና ለመተንተን የሞከረ ነው፡፡ ለዚህ የአሳብ ሙግት ዋና መነሻና ማድመቂያ የሆነው ደግሞ ከሰሞኑን ወጣቱ ከያኒ ቴዲ አፍሮ የዓፄ ምኒልክን የግዛት ማስፋፋት ወረራ አስመልክቶ በአንድ በአገር ውስጥ በሚታተም መጽሔት ሰጠው የተባለው ቃለ መጠይቅ በበርካታ የኦሮሞ ተወላጆች/ኦሮሞ ብሔርተኞች ዘንድ የቀሰቀሰው ብርቱ ቁጣ ነው፡፡
ይህን ተከትሎም የካናዳው ተክሌ ‹‹የኛ ነገር፡- የተሸነፈ ርእዮተ አገርና ገፊ ፖለቲካ›› በሚል ርእስ ባስነበቡት ጽሑፋቸው የአንድነት ኃይሉ ከተቸከለበት የአንዲት ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መንፈስ ወጥቶ ብሔርተኝነትን ለሚያቀነቅኑ ብሔርተኛ ፖለቲከኞች ዕድል የሚሰጥ የፖለቲካ አጀንዳን በመቅረፅ ምቹ የመጫወቻ ሜዳ ለማዘጋጀት እስካልቻሉና እስካልደፈሩ ድረስ መጪው ጊዜ ለአንድነት አቀንቃኞች ከአሁን በበለጠ አዳጋችና ፈታኝ እንደሚሆንባቸው ምሳሌዎችን ጭምር በመጥቀስ ለመተንተን ሞክሯል፡፡
በአንፃሩም ሥርጉተ ሥላሴ ‹‹የማረተ ማጭድ ሸክም በሐቅ ጭብጥ ይረታል›› በሚል ርእስ ያስነበቡን ጽሑፋቸውን፣ በእነደ አቶ ተክሌ ያሉ ‹‹ኢትዮጵያዊነትንና የብሔር ፖለቲካን በተመለከተ›› የሚያራምዷቸው ጠንጋራ አመለካከቶች ውለው አድረው የትውልዱን ጤናማ መንፈስ እንዳይበክሉት ቀድሞ መከላከል ይገባል በሚል ጽኑና ቅን መንፈስ ተነሳስተው እንደጻፉት ይነግሩናል፡፡
ጸሐፊዋ ‹‹ኢትዮጵያዊነት የሚነበብ መንፈስ ነው›› በሚለው ጽሑፋቸውም ኢትዮጵያዊነት ለዘላለም ጸንቶ፣ አብርቶና ደምቆ የሚቆይ ረቂቅና ሕያው መንፈስ መሆኑን ለማስረዳት ረጅም ርቀት በመጓዝ የብሔር ፖለቲካ ያደረሰብንን ስብራትና ለወደፊቱም የተሸከመውን ክፉ አደጋ ለማሳየት ደክመዋል፡፡
ጸሐፊዋ በዚህ ስሜትም ‹‹እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያዊነትን ከሚዋጋ ስሜት ያድነን!›› ዘንድም ተማፅነውልናል፡፡ በዚህ መካከል ደግሞ ኢትዮጵያዊነት የዘላላም ቅርሳችንና ቃል ኪዳናችን ነው፡፡ በሚሉና በተቃራኒው ደግሞ፣ ኢትዮጵያዊነት ሳንወደውና ሳንፈቅደው እንደ ኮሶ ተበጥብጦ በግድ እያነገፈገፈን የተጋትነው፣ እየቀፈፈንና እንደ አባ ጨጓሬ እየኮሰኮሰን የተደረበብን ማንነት ብለው በሚሉ ሰዎች ዘንድ እየተካሔደ ያለው አስጥ አገባ ከሰሞኑን ዳግም በአዲስ ኃይልና ጉልበት ተጠናክሮ የኢትዮጵያንና የዲያስፖራን የፖለቲካ ሰማይ ክፉኛ እያወደው፣ እያጠነውና እየናጠው ይገኛል፡፡
የባለፈው ሰሞን በእነ ጀዋርና ደጋፊዎቻቸው እንዲሁም ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ለዘላለም ብለው በሚያቀነቅንቱ መካከል በማኅበራዊ ድረ ገጾች፣ በመጽሔቶችና በጋዜጦች፣ በየድረ ገጾቹ፣ በየፓል ቶኩ የሰማነው ጉድ፣ የጦር አውርድ ቀረርቶና ሽለላ፣ ስድብና ዛቻ፣ ጽንፈኝነት፣ መራር የሆነ ጥላቻና ቂም የሞላባቸው ሰቅጣጭ ሙግቶች የነገይቱን ኢትዮጵያ ህልውና እንደ ሕዝብም ደግሞ በሰላምና በመቀባበል ለመኖር ተስፋችን የደበዘዘ መስሎ እንዲታየኝ ነው ያደረገኝ፡፡
ቢቻለን፣ ብንወድና ብንፈቅድ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር በአንድነት ለመኖር ካልሆነም ደግሞ ተለያይተንም ቢሆን በመልካም ጉርብትና ለመቀጠል የሚያስችለን ፍቅር፣ ቅንነትና በጎነት ምን ያህል እየራቁን እንደሔዱ እንዳስተውል አስችሎኛል፡፡
የረጅም ዘመናት ታሪካችን እንደሚነግረን ትናንትናም ሆነ ዛሬ ኢትዮጵያ ተብላ በምትጠራው ግዛት ውስጥ ያሉ ሕዝቦች የሚያስተሳስሯቸው ተፈጥሮአዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እውነታዎች በርካታ ናቸው፡፡
እስቲ ኤርትራ ሂዱ ማነው ከአማራ፣ ከኦሮሞ፣ ከጉራጌ ሕዝብ ያልተዋለደ፣ ወደ ሰሜንም ወደ ደቡብም ፣ ወደ ምስራቅም ወደ ምዕራብም ተጓዙ ይሄ ሕዝብ በደምና በአጥንት የተሳሰረ ሕዝብ ነው፡፡ እስቲ ወሎን ተመልከቱ ሃይማኖቱ ሳይገድበው ተዋዶና ተዋልዶ የሚኖር ታላቅ ሕዝብ ያለበት አገር/ምድር ነው፤ ወይስ የነበረበት ልበል ይሆን እንዴ!? ‹‹መሐመድ ኤልያስ፣ ትዕግሥት ሁሴን›› ተብለው የሚጠሩ አያሌ ሰዎች ዛሬም ድረስ ያጋጥማችኋል፡፡ የሃይማኖት ልዩነታቸው እንዳለ ሆኖ ግና ፍቅር የተባለ አንዳንች ኃያልና ጽኑ አሸናፊ መንፈስ ሰንሰለት ሆኖ ያስተሳሰራቸው ሕዝቦች!!
በቅርቡ በሀገረ አሜሪካ አገር ሕይወታቸው ያለፈው ዕውቁ የታሪክ ምሁር ፕ/ር ታደሰ ታምራት ለዶክትሬት ድግሪ ድርሳናቸው የሚሆናቸውን ጥናትና ምርምር ለማድረግ ከሚማሩበት የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ተነስተው የውቦች አገር ወሎ ውስጥ ተገኝተው ነበር፡፡
ፕ/ር ታደሰ ለዚሁ ጥናታቸው ወደምታስፈልጋቸው አንዲት ጥንታዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያንን ለመጎብኘት እንደተዘጋጁ በዛች የገጠር ቤ/ን የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠባቂ የሆነ አንድ ግለሰብ የቤተ ክርስቲያኒቱን በር ከከፈተላቸው በኋላ፣ እኔ ሙሰሊም ነኝ እርስዎ ግን መግባት ይችላሉ ብሎ ወደ ውስጥ ይገቡ ዘንድ እንደፈቀደላቸው ተማሪያቸው የኾኑትና በአንድ ወቅት የኢትዮጵያ ታሪክ መምህሬ የሆኑት የአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲው ዶ/ር ውዱ ጣፈጠ ይህን የአስተማሪያቸውን አስደናቂና ልብ የሚነካ ገጠመኝ ሲናገሩ ሰምቼቸዋለኹ፡፡
እንዲህ ዓይነቱን ፍቅር፣ እንዲህ ዓይነቱን መተማመን፣ እንዲህ ዓይነቱን በጎነትና ቅንነት፣ እንዲህ ዓይነቱን ዓለም ሁሉ ምሳሌ ያደረገውን አብሮነት፣ ከመጽሐፍ ቅዱስ እስከ ቅዱስ ቁርአን፣ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ነቢዮ መሐመድ፣ ከግሪክ ጸሐፊዎችና ፈላስፎች እስከ አውሮጳ አሳሾችና ተጓዦች በውብ ቀለም የከተቡለትንና የተናገሩለትን ይህን ውብ የሆነውን አንድነታችንና ውብ ፍቅራችን ዛሬ በነበር ልንዘክረው በቋፍ ላይ ያለን ነው የምንመስለው፡፡
እዚህም ቤት እዛም ቤት የሚሰማው ድምፅ ደግ አይመስልም፣ የበቀል ሰይፎች በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ተመዘው እያፏጩ ያሉ ነው የሚመስለው፡፡ ስለ ሰላም፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ አንድነትና አብሮነት የሚሰብኩንና ወደ ዕርቅ መንገድ ይዘውን የሚጓዙ የዘመኑ ነቢያትም አድራሻቸው ወዴት እንደሆነ ጠፍቶብናል፡፡
የሕዝብ እንባ፣ ብሶት፣ ዋይታና እሮሮ እንቅልፍ፣ ዕረፍት የሚነሳቸው፣ ለፍትሕና ለእውነት ጥብቅና የቆሙ፣ በሕዝባቸው ፍቅር ፈፅመው የነደዱ፣ ‹‹ይህን ሕዝብ በምድረ በዳ በከንቱ ከምታጠፋው እኔ ከሕይወት መዝገብ እስከ ዘላለሙ ደምስሰኝ!›› የሚሉ በነፍሳቸው የተወራረዱ የዘመናችን ሙሴዎች፣ ፍቅርንና ዕርቅን የሚሰብኩ ፖለቲከኞቻችን፣ መሪዎቻችን አድራሻቸው ወዴየት ይሆን!?
የትናንትናም ሆነ ዛሬው መንገዳችን በአያሌው ፍቅርን የተራበ፣ ይቅርታን የተራቆተ፣ አንድ መሆንን የገፋና የተጠየፈ ነው፡፡ ይህ ዛሬ የደረስንበት የአገራችን የፖለቲካ የታሪክ ሒደት ውጥንቅጥና ቀውስ በአብዛኛው የትናንትና ውጤት ነው፡፡ እናም የኢትዮጵያችን የዘመናዊ ፖለቲካ ጅማሮ መንገዱ በደም የተመረቀ፣ በደም የጨቀየ፣ በደም የተፈፀመ፣ የደም መንገድ፣ የደም ጎዳና ነው፡፡ የብዙዎች ወገኖቻችን ደም እንደ ጅረት የጎረፈበትና፡-
‹‹የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣
ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ፡፡›› ተብሎ አሰቃቂ ሙሾ የተወረደበትን የታሪካችንን አብዛኛውን ምዕራፍ በደም ያስዋበ፣ በደም ያወየበ የፖለቲካ ታሪክ ነው ያለን፡፡ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራም ሆነ በወያኔ በኩል፣ በቀይ ሽብርና በነጭ ሽብር፣ በኢሀአፓና በመኢሶን፣ በኢህአዴግና በተቃዋሚው ስም ጎራ ለይቶ የተላለቀው ሕዝብ የአንድ ምድር ልጆች እንደሆኑ ነው የማስበው፡፡
የትናንትናው እንዳይበቃን ዛሬም ደግሞ አስፈሪውና አስደንጋጩ ነገር ደግሞ እዚህም ቤት እዛም ቤት የሚጎሰመው ነጋሪት፣ የሚነፋው መለከት ሞትን የሚያውጅ፣ ጥፋትን የደገሰ መሆኑ ነው፡፡ ዛሬም በትናንትና ታሪካችን ላይ ተቸክለን ለቂም በቀል የምንፈላለግ፣ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ፣ ከአንድነትና ኅብረት ይልቅ መለያየት፣ ከሰላም ድምፅ ይልቅ የጦርነት ነጋሪት ወኔያችን የሚያሞቀው፣ የሚቀሰቅሰው ሕዝቦች የመሆናችን ምሥጢር ነው፡፡
አገሪቱን እያስተዳደረ ያለው መንግሥትም፣ በአገራችንም ሆነ በውጭ ያሉት የሚበዙት በተቃዋሚ ስም የተደራጁ የተቃዋሚ ፓርቲዎችና የፖለቲከኞቻችን መንፈስ ገና ወደ ዕርቅ መንገድ ወደ ፍቅር የልዕልና ከፍታ ሊወጣ፣ ሊያድግና ሊመነደግ እንዳልተቻለው ደግመን ደጋግመን ዐይተናል፣ ታዝበናል፡፡
ከሰሞኑን በአፍቃሪ ምኒልከና በፀረ ምኒልካውያኑ መካከል የነበረው ስድብ፣ ውርጅብኝና የጦር አውርድ ዘመቻና የቃላት ጦርነት ገና በትናንትና ታሪካችን የሆኑትን መልካም ክስተቶች በምስጋና ተቀብለን፣ በአንፃሩ ደግሞ በታሪካችን የሆኑትን ስህተቶች አምነን ተቀብለን ይቅርታ ለመጠየቅ የሚሸነፍ ቅን መንፈስ እንደሌለን ያሳየን ነው ማለት ይቻላል፡፡ እናም ገና ወደ አንድነት፣ ወደ ዕርቅና ፍቅር መንገድ ለመድረስ ረጅም መንገድ በፊታችን ተዘርግቶ ይጠብቀናል፡፡ ይህን መንገድ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባርም ጭምር ተጉዘው ሊያሳዩን የሚችሉ ባለ ራእይና ቁርጠኛ የሆኑ ፖለቲከኞች፣ ከልባቸው የትግል ሰዎች የሆኑ፣ ሰው የሆኑ ሰዎች፣ የእውነትና የፍትሕ ጠበቃዎች በዚህ ዘመን የግድ ያስፈልጉናል፡፡
በቅርቡ በሞት የተለዩን የአፍሪካ ብርቅዬ ልጅ፣ የፀረ አፓርታይድ ታጋይና ነፃነት አርበኛ፣ የሰላምና የፍትሕ ጠበቃ፣ የይቅርታ ጀግና የሆኑት ኔልሰን ሮሂላላ ማንዴላ/ማዲባ እ.ኤ.አ በ1990 በአይርላንድ ፓርላማ አባላት መካከል ተገኝተው ባደረጉት ንግግራቸው እንዲህ ነበር ያሉት፡-
‹‹We are in struggle because we value LIFE and LOVE all humanity!›› ያው ፍቅር ለሚገባቸው፣ ፍቅር ለሚያግባባቸው የማዲባ መልእክት ግልፅ እንደሆነ አስባለሁ፡፡ ፍቅር … ሰላም … ካላግባባን፣ ካላቀራረበን እንግዲህ ምን ያግባባን እንደሆነ እኔጃ፡፡ ግን … ግን … እናንተዬ በሰላማዊም መንገድ ይሁን ነፍጥ አንስተን እንታገላለን የምንል ሰዎች የትግላችን የመጨረሻ ግቡ ምንድን ይሆን?!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
nikodimos.wise7@gmail.com

የአቶ በቀለ ገርባ የአመክሮ መብት መከልከል

February 6/2014

በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ የእስር ጊዜያቸውን ቢጨርሱም ኣመክሮ መከልከላቸው ተሰማ። ህክምናም እያገኙ ኣይደለም ተብሏል። የኮንግረሱ ዋ/ጸኃፊ ለዶቸቬሌ እንደ ነገሩት ከሆነ አቶ በቀለ ገርባ የ 3 ዓመት ከ 7 ወር የእስር ጊዜያቸውን ኣጠናቀው መለቀቅ የነበረባቸው ባለፈው ጥር 11 ቀን ነበር
Symbolbild Justitia Justizia
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሺን በበኩሉ የዚህ ኣይነት ቅሬታ እስከኣሁን እንዳልደረሰው ኣስታውቋል።
ቀድሞ በዶ/ር መረራ ጉዲና ይመራ የነበረው የኦሮሞ ህዝብ ኮንግረስ (ኦህኮ) እና ያኔ በአቶ ቡልቻ ደመቅሳ ይመራ የነበረው የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፈዲን) ተዋህደው የፈጠሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ነበሩ፤ አቶ በቀለ ገርባ። በያዙት ኃላፊነትም ያለ ኣግባብ የታሰሩ ኦሮሞዎችን ጉዳይ እየተከታተሉ ለዓለም ዓቀፍ የመብት ተሟጋቾች እና ለሚመለከታቸው ሁሉ ያሳውቁም ነበር። ይኸው ተግባራቸው ያላስደሰተው የኢትዮጵያ መንግስት ታዲያ የኮንግረሱ ዋ/ጸኃፊ አቶ በቀለ ነጋ እንደሚሉት ኣሸባሪ በሚለው ድርጅት ስም ወንጅሎ ኣስፈረደባቸው። የተፈረደባቸው ስምንት ዓመት ሲሆን በይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ወደ 3 ዓመት ከ 7 ወር ተሻሽሎላቸው ነበር ዝዋይ እስር ቤት የከረሙት።

Wahl in Oromia Äthiopien 23.Mai 2010

አቶ በቀለ ገርባ ከዝዋይ እስር ቤት ጀምሮ ኣሁን በሚገኙበት የቃሊቲ ወ/ቤትም ታመው ህክምና እንዳላገኙም ነው እየተነገረ ያለው። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሺን ሊቀመንበር የሆኑት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ግን የዚህ ኣይነት አቤቶታ እስከ ኣሁን ኣልደረሰንም ባይ ናቸው።
ከኢትዮጵያ መንግስት ወከባና እስራት ሸሽተን በጎረቤት ኣገር እንገኛለን ከሚሉት የኦሮሞ ተወላጆች መካከል ኣንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ ስደተኛ በበኩላቸው ከአቶ በቀለ ገርባ በባሰ ሁኔታ ህክምና ተነፍገው የሞቱ የኦሮሞ እስረኞችም ኣሉ ሲሉ ኣንዳንዶቹን ጠቃቅሷል። ከዚሁ በመነሳ የኢትዮጵያ እስር ቤቶች የስራ ቐንቐ ኦሮምኛ ሆኗል እስከማለትም ተደርሷል። የሰብዓዊ መብት ኮሚሺን ሊቀመንበሩ አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ግን ሊደንቀን ኣይገባም ይላሉ።
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበሩ፤ አቶ በቀለ ገርባ፤ በተፈረደባቸው ዕለት የፍርድ ማቅለያ ኣስተያየት ይሰጡ ዘንድ እድል ቢሰጣቸውም «ሳላጠፋ የፈረደብኝን ፍ/ቤት ይቅርታ ኣልጠይቅም። ይቅርታ መጠየቅ ካለብኝ የሚጠበቅብኝን ያህል ካልሰራሁለት የኦሮሞን ህዝብ ነው ይቅርታ እምጠይቀው» ሲሉ ችሎቱ ፊት ቆመው መናገራቸው አይዘነጋም።
ጃፈር ዓሊ
ተክሌ የኋላ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC 


Thursday, February 6, 2014

Residents of Burayu call police to leave after protest

ESAT News
February 06, 2014
Residents of Burayu town of the Oromia region, Ethiopia, are calling members of the Federal Police Force to leave the town after protests on Monday February 3, 2014. The residents state that their insecurity increased after members of the Force have killed civilian youth of the town.
Officials of the town on the other hand, are attempting to appease the angry residents promising that the killers will be brought before justice.
The clash between the residents and the Force began after a young man named Daniel Aschale, was shot by the Police two days ago. Acclaimed for his good character by his friends, Daniel worked as a driver at a private mineral water producing company, Aqua Addis.
Daniel had reportedly entered a row with a civilian dressed man after the former had pushed the later when they were inside a recreational club. The man with a civilian dress had severely attacked and beaten Daniel together with his friends and threw him out on the asphalt road. Although Daniel was taken to a local health centre and later to a hospital in Addis Abeba for better treatment, he died shortly afterwards.
Carrying the body of the deceased, residents of the town had staged a protest in the street and outside the Town Council asking for the “civilian dressed members of the Federal Police Force” to be apprehended. The windows and doors of the Council have been smashed.
Similarly, youth in Maret area of the town had staged another protest yesterday asking the Federal Police Force to leave the town. The Federal Police still occupies the town.
The Force that has been stationed in the town has reportedly killed at least six civilian youth in the past four months alone.

ስልክ ጠላፊው ሰላይ “ጋዜጠኛ”

February 6, 2014
በማህሌት ነጋ (ሲያትል)

ከሁሉ የእኔን ቀልብ የሳበው የቀጂው ማንነት ነበር። ለማጣራት ያደረኩት ጥረት ብዙም ግዜ አልፈጀብኝም። አበበ ገላው በዚሁ “ሊክድ” በተባለው ቅጂ “እኔ ከሞትኩም እንደ ሃየሎም መጠጥ ቤት በከንቱ መሞት አልፈልግም። መሞት የምፈልገው ለአላማ ነው ይላል።” በዚህ ግዜ አንድ ሳቅ ይሰማል። የኢያጎ ሳቅ። ዳዊት ከበደ ስለመሆኑ ብዙም አልተጠራጠርኩም።

Dawit Kebede Awramba Times editor in restaurant
ሰሞኑን አንድ ሚስኪን ጋዜጠኛ ነኝ ባይ ከአንድ የከሰረ ፖለቲካኛ ጋር ቃለ ምልልስ ሲያደርግ በቪዲዮ ለቆ ስለነበር ለሶስት ደቂቃ ያህል ተምልክቼ ጭንቅላቴን በሃዘን እየነቀነኩ ዘጋሁት። እኔን ጨምሮ በርካቶች ድረ ገጾችን የምናስሰው መረጃ ፍለጋ እንጂ የከሰሩ ግለሰቦችን ደረቅ ወግ ለማዳመጥ እንዳልሆነ ለማንም ግልጽ ነው። በአንድ ወቅት ያዙን ልቀቁን ይሉ የነበሩት ሁለት ግለሰቦች የዛሬን አያድርገውና ኢትዮጵያዊያን እንደ ማንዴላ የነጻነት ታጋዮች አድርገው ያከብሯቸው ስለነበር ድምጻቸው የጎላ በራስ መተማመናቸው ከውስጣቸው ሞልቶ በአፋቸው ይገነፍል ነበር። ዛሬ ግን ድምጽ አጥሯቸው ቀልብ እርቋቸው ሲንሾካሾኩ ያየ ሁሉ እንደ እኔ ከንፈር መጦ የሁለቱን ምስኪኖች ወግ በግዜ ዘግቶ ወደ ስራው እንደሚመለስ ብዙም አያጠራጥርም።
“ምስኪኖች እነማን ናቸው?” እንደማትሉኝ እርግጠኛ ነኝ:: የአውራምባው ዳዊት ከበደና የኢዴአፓው ልደቱ አያሌው ጉዳይ መቼም አንገት ያስደፋል። ሁለቱም ጠላታቸው ወያኔ እንዳልሆነ እነርሱ እንደሌሎች “ጽንፈኛ” እንዳልሆኑ ሌሎችን ከሰው እራሰቸውን ከፍ ለማድረግ ሲጥሩ ላስተዋለ ጠበል የሚወስዳቸው ያጡ በሽተኞች መሆናቸውን ድርጊታቸው ይመሰክራል። ዲያስፖራውና የግል ጋዜጦች በተለይ የጋራ ጠላቶቻቸው ይመስላሉ። እንደው ለመንደርደሪያ እንጂ የዚህ ጹሁፍ አላማ የሁለቱ ምስኪኖች ወግ ስላልሆነ ወደ ቁም ነገሩ ልመለስ::
ሾተላዩ ሰላይ ዳዊትን ለመጀምሪያ ግዜ በአካል ያገኘሁት ወደ ሲያትል የዛሬ ሶስት አመት በመጣ ግዜ ነበር። አስተባባሪዎች መርጠን፣ ገንዘብ አዋጥተን፣ ድግስ ደግሰን፣ ሽልማት አዘጋጅተን ነበር የጀግና አቀባበል ያደረግንለት። ወቅቱ የብርድ እና የበረዶ ግዜ ስለነበር እኔም እንደሌሎች ይህንን “ጀግና ጋዜጠኛ” ለመቀበል ብዙ መስዋእትነት ነበር የከፈልኩት። በተለይ የኢትዮሜድያው አብርሃ በላይና ሼክስፒር ፈይሳ እንግዳውን ተቀብለው ቤታቸው ከማሳደር አልፈው ለዝግጅቱ ስኬት ያበርከቱት አስተዋስኦ ቀላል አልነበረም። ሰላዩ ጋዜጠኛ ግን አብርሃ በላይን አራክሶ፣ ሼክስፒር ፈይሳን ደግሞ ስምህን አጠፋለሁ ብሎ በማስፈራራት ከንቱነቱን ብቻ ሳይሆን የኢያጎ ባህሪውን ፍንትው አድርጎ አጋልጧል።
ይሁንና ኢያጎን (ዳዊትን) በቅርብ የሚያውቁት ሁሉ አትመኑት ማለታቸው አልቀረም። እውነት ለመናገር ዳዊት እነ ውብሸት ታዬ እና ርእዮት አለሙን በማሳሰሩ ድርጊት እጁ አለበት የሚል ሹክሹታ ከወደ አገር ቤት ሲናፈስ ማናችንም የዚህ ጎጠኛ “ጋዜጠኛ” ወዳጆች በቁም ነገር አልወሰድነውም። መቼም ሰው በምልካም ስራው ሲታወቅና ሲወደስ ምቀኛ እንደማይጠፋ ለማንም ግልጽ ነው። ስለዚህም ነበር ዳዊትን አትመኑት የሚለውን የአገርቤት መልእክት ማንም ትኩረት ያልሰጠው። አሁንም ስለዚያ ድርጊቱ ተጨባጭ መረጃ ስለሌለኝ ድርጊቱን ፈጽሟል አልፈጸም ለማለት ባልችልም ከጀርባ የመውጋት ጋህሪውን ለማስተዋል በመቻሌ አያደርግም ብዬ መከራከር አልችልም።
ዳዊት ተራ የሆኑ ጉዳዮችን ሁሉ የመቅዳት ባህሪ አለው። ሰው ሲጎርስ፣ ሲጠጣ፣ ሲናገር፣ ሲቀልድ (ከተቻለውም ሽንት ቤት ሲጸዳዳ) ቪዲዮና ፎቶ ማንሳት ድምጽ መቅዳት ይወዳል። በስውር የሚቀዳበት ሪኮርደርም ይዞ እንደሚዞር ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። ብዙ ሰው ግን የዳዊትን ድርጊት ከጋዜጠኝነት ስራው ጋር ስለሚያያይዘው ተንኮሉን አይጠረጥርም። ነገሩ ያልጠረጠረ ተመነጠረ መሆኑን ነው።
Dawit Kebede's brother besrat amareአሁን እንደምንሰማው ነዋሪነቱ በአሪዞና ፊኒክስ የሆነው የዳዊት ከበደ ታላቅ ወንድም ብስራት ከበደ የሚታወቀው በተመሳሳይ የመቅዳት ባህሪው ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ብስራት ምንም ጭንብል ሳያጠልቅ አይኑን በጨው አጥቦ ስለሚንቀሳቀስ የህወሃት ታማኝ ካድሬና ሰላይ መሆኑ በስፋት ይነገራል። እርሱም
እንደ ወንድሙ የትርፍ ግዜ ስራው ስለሆነ እንኳን ፖለቲከኞችን እና ታጋዮችን በስካይፕም ይሁን በስልክ የሚያናግራቸው ሴቶች ምስልና ድምጽ ሳይቀር እንደሚቀዳ በጉራ ይናገራል፣ ለቅርብ ጓደኞቾም ያሳያል። እዚህ ላይ ግለሰቡን እምታውቁ ሴቶች ጠንቀቅ በሉ ማለት ሳያስፈልግ አይቀርም።
የኢያጎ ጩቤ ወደ ዲሲ ደዋውዬ እንዳጣራሁት ዳዊት ወያኔ አባረረኝ ብሎ ወደ አሜሪካ ፈርጥጦ ሲመጣ የኢሳት ሰዎችም የተቀበሉት በመልካም አይን ነበር። በተለይ ከሲሳይ አጌና፣ ከመሳይ መኮንን እንዲሁም አበበ ገላው ጋር መልካም ወዳጅነት ለማፍራት፣ አብሮ ለመጠጣትና ለመብላት ግዜ አልወሰደበትም። ለጋዜጠኝነት ስነምግባር እጨነቃለሁ የሚለው ይሄው ግለሰብ ወያኔ ጠለፍኩ ያለውን የዶ/ር ብርሃኑን የስካይፕ ውይይት በድህረ ገጹ ላይ በማውጣት የራሱ አጸያፊ ድርጊት መነጋገሪያ ሆኖ እንደ ነበር ይታውሳል። ዳዊት ከበደ በኢሳት፣ ግንቦት ሰባትን እና ዶ/ር ብርሃኑ ላይ በተከታታይ የሰራውን አሳፋሪ ግን ደግሞ የከሸፈ ፕሮፓጋንዳ ሁሉም ስለሚያውቀቅ መድገም አያስፈልግም። ከሁሉ የገረመኝ ሰሞኑን ዳዊት ኢያጓዊ የስለላ ስራውን ለማራቀቅ መሞከሩ ነው። ሞኝ እራሱን ያታልላል ነው ነገሩ።
ልክ እንደ ኢያጎ ዳዊትም ጩቤን በጀርባው ደብቆ ያመኑትን እና ያቀረቡት ሁሉ ላይ ከማሴር ቦዝኖ እንደማያውቅ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ሆኗል። በቅርቡ ለመረዳት እንደቻልኩት በርግጥም የዛሬው ኢያጎ ዳዊት ከበደ መስዋእትነት ከፍሏል፣ መልካምነቱንም በስራው አስመስክሯል በማለት እንደ ትግል አጋር ያዩት ከነበሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን አንዱ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ይገኝበታል። ለዚህም ምክንያት አንዱ ኢያጎ ከእስር ወጥቶ በሲፒጄ ሳይቀር ለፕሬስ ነጻነት ላበረከተው አስተዋጽኦ በታላላቅ የአለማችን ጋዜጠኞች ፊት በኒውዮርክ ቀርቦ ሽልማት ሁሉ መውሰዱ ነው። ይቺም ስኬት ለዳዊት ጥሩ ጭንብል ሆና ቆይታለች።
በወቅቱም ወያኔ ይገለኛል ያስረኛል እንጂ አገር ለቅቄ አልሰደድም ብሎ በየመድረኩ ሲደነፋ በእውነትም የጎልያድ ጠላት ቅዱስ ዳዊትን ነበር የመሰለን። ያሁሉ ተረት ሆኖ ወያኔ ሊያስረኝ ነው ብሎ አገር ጥሎ ሲፈረጥጥ አሜሪካ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ክብርና ፍቅር አልነፈጉትም ነበር። የእኛው ኢያጎ ግን ያን ሁሉ ክብር ትቶ በእኩይ ተግባሩ የነጻንት ትግሉን የሚጎዳና የህወሃት አንባገነኖችን በሚጠቅም እኩይ ተግባራት ላይ ለመሰማራት ግዜ አልፈጀበትም።
በቅርቡ ወያኔዎች ክፉውን ጎልያድ መለስ ዜናዊን በአለም መሪዎች ፊት አዋርዶና አስደንግጦ የመጨረሻና ወሳኝ ስንብት ላደረገለት ጋዜጠኛና አክቲቪስት አበበ ገላውን ለማስጠላት እንዲሁም ኢትዮጵያዊውን ለመከፋፈል በህገወጥ መንገድ የተቀዳ የግል የስልክ ንግግር አዛብተው፣ ቆርጠውና ቀጥለው በኢንተርኔት ላይ ለቀቁ። ይሄም የተለቀቀው በዳዊት ድርገጽ ሳይሆን በቀንዲል የወያኔ የፈስቡክ አቀንቃኝ ዳንኤል በርሄ አማካኝነት በሆድ አደሩ ሹምባሽ ከበደ ካሳ አቀናባሪነት ነው። ደግነቱ የተባለው ሁሉ ምንም ሚስጥር የሌለው ስለነበር እንዳሰቡት ሳይሳካላቸው እነርሱንው መሳለቂያ አድርጓቸዋል።
ከሁሉ የእኔን ቀልብ የሳበው የቀጂው ማንነት ነበር። ለማጣራት ያደረኩት ጥረት ብዙም ግዜ አልፈጀብኝም። አበበ ገላው በዚሁ “ሊክድ” በተባለው ቅጂ “እኔ ከሞትኩም እንደ ሃየሎም መጠጥ ቤት በከንቱ መሞት አልፈልግም። መሞት የምፈልገው ለአላማ ነው ይላል።” በዚህ ግዜ አንድ ሳቅ ይሰማል። የኢያጎ ሳቅ። ዳዊት ከበደ ስለመሆኑ ብዙም አልተጠራጠርኩም። ሳቁ በጣም የተለየች ውስጧ ሸፍጥና ተንኮል ያዘለች ነች። ዳዊትን ለሚያውቁት ወዳጆቼ አስተያየት ሳልሰጥ ይቺን አምልጣ ስትቆረጥ የወጣች ወሳኝ መረጃ አድምጣችሁ የማን ሳቅ እንደሆነ ንገሩኝ ብዬ በኢሜይል አያይዤ ላኩላቸው። አራቱም መልሳቸው አንድ ነው፣ የኛው ኢያጎ ዳዊት ከበደ።
ዳዊት በጣም አሳዘነኝ። ብዙ ተስፋ የጣልንበት “ጋዜጠኛና የነጻነት ታጋይ” እንዴት ከክብር ወንበሩ ወርዶ ቆሻሻ ትቦ ውስጥ ይወድቃል? ለነገሩ ከልብ ያልሆነ ነገር ሁሉ እራሱን መግለጡ አይቀርምና ዳዊትም ከልቡ ኢያጎ እንጂ ሌላ አልነበረም። በጣም ተምታቶበታል። እኛ ግን የበለጠ ነቃን። እነዳዊት ከበደ ግን ግራ እንደተጋቡ እንደሰካራም በየትቦው ውስጥ እየወደቁ ይገኛሉ። ተመስገን ደሳለኝ ከጥቂት ወራት በፊት “የፖለቲካ ስር ቁማርተኞች” በሚል የጻፈው አንጀት አርስ ጹሁፍ ትዝ አለኝ። ተመስጌን የጠየቀው መሰረታዊ ጥያቄ በእኔም አእምሮ ውስጥ ያቃጭላል። ለመሆኑ ወደ አገር ቤት ከአሜሪካ ልክ እንደ አመጣጡ ፈርጥጦ ያስመለሰው ጉዳይ የፕሬስ ነጻነት መሻሻሉና “የጽንፈኞችን” ፖለቲካ በመጸየፉ ነው ወይንስ ደግሞ ኢሳትን የማፍረስ እና በጸረ-ወያኔ ትግሉ ግንባር ቀደም ሚና ይሚጫወቱ ኢትዮጵያዊያንን ለማምታታትና ለመሰለል ስላላመቸው? መልሱ ግልጽ ነው።
ወያኔዊ ኢያጎነት በቀላሉ እንደማይለቅ ከዳዊት መማር ይቻላል። ዲሲ አካባቢ በቅርብ የታዘቡት እንደነገሩኝ ዳዊት ሁለት ነገሮች አብዝቶ ይወዳል፣ መጠጥና ሴት ማባረር። ከአገር ቤት ፈርጥጦ ዲያስፖራ የተቀላቀለው ዳዊት ሲነቃበትና ይሄ የሱስ ጥማት ሲያስቸገረው ፈርጥጦ እነአቦይ ስብሃት እና ሽመልስ ከማል ጋር ብርጭቆ ማጋጨት መጀመሩን ሰማን። ተመሳሳይ ላባ ያላቸው ወፎች አብረው ግር ይላሉ አሉ ፈረንጆች። አበው ሲተርቱ ግም ለግም አብረህ አዝግም እንዳሉት መሆኑ ነው። መልካም እድል፣ መልካም ቅምቀማ ብለናል ከወደ ሲያትል!!

በሦስት የመንግስት ተቋማት ላይ አንድነት ፓርቲ ክስ መሰረተ

February6/2014

ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድልኝን ሰላማዊ ሰልፍ እንዳላካሂድ ከልክለውኛል፤ አባላቶቼን ያለአግባብ በማንገላታት አስረውብኛል፤ ቅስቀሳ እንዳላካሂድ አግደውኛልና ድምፅ ማጉያዎቼን ቀምተውኛል ሲል አንድነት ለዴሞክራሲ ለፍትህና ፓርቲ (አንድነት) በሶስት የመንግስት ተቋማት ላይ ክስ መሰረተ። ፓርቲው በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ፍትሃ ብሔር ችሎት ላይ ክስ የመሰረተባቸው ተቋማት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መሆናቸውን በክስ መዝገቡ ተገልጿል።
ፓርቲው የዘወትር ፖለቲካዊ ስራዎቹን እንዳላያካሂድ መስተጓጉል ተፈጥሮብኛል በማለቱ ክሱ መዘጋጀቱን ለሰንደቅ ያስረዱት የሕግ ባለሙያው አቶ ተማም አባቡልጉ፤ በክስ ዝርዝሩ ውስጥ ፓርቲው በመስቀል አደባባይ የጠራው ሰልፍ እንዳይካሄድ ከመደረጉም በተጨማሪ የቅስቀሳ እገዳ፣ የአባላት መታሰርና የቁሳቁስ መነጠቅ ሁሉ ስለማጋጠሙ በክሱ ውስጥ በዝርዝር ተካቷል ብለዋል።
በከተማዋ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ከፈቃድ ሰጪ አካላት ፈቃድ መገኘት አለበት ቢባል እንኳን ተቋማት የተከተሉት አካሄድ አግባብነት የሌለውና ከሕግም ውጪ በመሆኑ ይህን ለመጠየቅ ክስ መስርተናል ብለዋል። የመንግሥት አካላቱን የሰልፍ እገዳ ተከትሎ አንድነት ፓርቲ ዘጠኝ የሚደርሱ አማራጭ የሰልፍ ቦታዎች ቢያቀርብም አንዱንም ሳይቀበሉ በራሳቸው ምርጫ ጃንሜዳ ላይ ሰልፍ እንዲካሄድ መፍቀዳቸው በሕጉ ላይ ከሰፈረውና ማንኛውም ዓይነት ሰላማዊ ሰልፍ ከጦር ካምፕ በ50 ሜትር ርቀት ላይ መካሄድ አለበት ከሚለው መመሪያ ጋር የማይጣጣም ነው ብለዋል።
ይህም በመሆኑ አንድነት ፓርቲ የመንግስት ተቋማት በጣምራ በመሆን ሕዝብን ለመቀስቀስ የሚደረገውን ጥረት ስልታዊ በሆነ መንገድ አስተጓጉለውብኛል ይላል።
በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የተመሰረተባቸውን ክስ አስመልክተው በችሎት በመገኘት የሚሰጡትን መልስ ለማድመጥ ለየካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ምንጭ ዜና ሰንደቅ

አማራውን በተሳደቡት አቶ አለምነው መኮንን ላይ በባህር ዳር ሰልፍ ሊደረግ ነው፤ በአድዋና አዲስ አበባ የአድዋ ድል በዓል ዝግጅቶች ይኖራሉ

February 5/2014

 አማኑኤል ዘሰላም

የአንድነት ፓርቲ፣ በሶስት ከተሞች ታላላቅ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች፣ ለማድረግ መወሰኑን ከሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነት ፌስቡ ገጽ አነበብኩ። እንቅስቃሴዎቹ የሚደረጉባቸው ከተሞች፣ አድዋ፣ አዲስ አበባ እና ባህር ዳር ናቸው። በአድዋ እና በአዲስ አበባ ከሌሎች ደርጅቶ ጋር በጋራ በመሆን (መኢአድ፣ አረና፣ ትብርር፣ መድረክ..) ፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ሕዝቡ ሁሉ ኩራት የሆነውን የአድዋ ድል በማሰብ ትልቅ አከባባር ለማድረግ ነው የታቀደው። በአድዋና በአዲስ አበባ ባሉ ብዙ ህዝብ ሊይዙ በሚችሉ አደባባዮች አከባበሩ ሊደረግ እንደሚችል ግምት ቢኖርም ፣ የአንድነት ፓርቲ የአከባበሩ ይዘት፣ ሰዓትና ቦታን ገና ይፋ አላደረገም።





























በባህር ዳር የሚደረገዉ ግን ከአድዋና ከአዲስ አበባዉ የተለየ ነዉ የሚሆነው። በቅርቡ የአማራ ክልል ም/ ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው፣ በክልሉ የሚኖረው ሕዝብ ላይ የሰነዘሩት ጸያፍና ከአንድ መሪ የማይጠበቅ አባባሎችን በመቃወም የሚደረግ ሰላማዊ ሰልፍ ነዉ። ጉዳዩ አንድ ሰው የተናገሩት ቢሆንም፣ ኢሕአዴግ እንደዚህ አይነት ሕዝብን የናቀና ያዋረደ አስተያየት የሰጡ ባለስልጣን ከሃላፊነታቸው ወዲያዉኑ እንዲነሱ አለማድረጉ፣ በሕግም አለመጠየቁ፣ ችግሩ ከግለሰብ አልፎ ድርጅታዊ መሆኑንም የሚያመላክትበትም ሁኔታም አለ።
«የአማራው ህዝብ ሰንፋጭ የሆነ ትምክተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ በቤንሻንጉልና በሌሎችም ቦታዎች ለመሰደዱ ምክንያት ሆኖታል»፣ «አማራዉ በባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው»፣ «የአማራዉ ሕዝብ የትምክህት ልጋጉን ማራገፍ አለበት» …. የመሳሰሉ አስተያየቶችን ነበር ባለስልጣኑ የሰነዘሩት።

ሰልፍ መጥራት በራሱ ለዉጥ አያመጣም። በባህር ዳር፣ አድዋ፣ እንዲሁም አዲስ አበባ የሚደረጉ ሰልፎችና ዝግጅቶች በማይሻማ መልኩ ፖለቲካዉን እንዲያናጉት፣ የማያሻማና የሚያስተጋባ መልእክት እንዲያስተላለፉ ከተፈለገ፣ ሕዝብ በነቂስ መዉጣት አለበት። ለዚህም ትልቅ ድርጅታዊና የቅስቀሳ ሥራ መስራቱ የግድ ነዉ። በየወረዳው፣ በየመንደሩ ፣ ቅስቀሳዎች መደረግ አለባችው። በራሪ ወረቀቶች፣ ፓምፍሌቶች በስፋት መዘጋጀትና መበተን ይኖርባቸዋል።



አንድ ነገር አንርሳ። እኛ ኢትዮጵያዉያን ካልደገፍናቸው፣ ከጎናቸው ካልቆምን ፓርቲዎቹ ብቻቸውን በራሳቸው ምንም ሊያመጡ አይችሉም። ገዢው ፓርቲ የሚተማመነው በያዘው ጠመንጃ፣ ባሰማራቸው ሰላዮቹና ካድሬዎችቹ ነዉ። አንድነቶች ግን የሚተማመኑት በሕዝብ ጉልበት ብቻ ነው። እያንዳንዳችን የድርሻችንን ከተወጣን፣ በአዲስ አበባ፣ በአድዋና ባህር ዳር የምንኖር የሚደረጉ ሰልፎችን እና ዝግጅቶችን ከተቀላቀልን፣ ነጋሪና ቀሳቅሽ ሳንፈልግ፣ በኛዉ አነሳሽነት ቅስቀሳ ካደረግን፣ ተዓምር የማንሰራበት ምንም ምክንያት የለም።

በሰልፉ ለመገኘት የማንችል ደግሞ፣ በተለይም በዉጭ አገር ያለን፣ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ከማሳወቁ በተጨማሪ፣ በገንዘባችን ትልቅ ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅብናል።

በሃረር የህዝብ ብሶት ይገነፍላል የሚል ስጋት አይሏል::የሃረሪ ብሄራዊ ሊግ በዘር ማንዘር የተሳሰረ የሙስና ሰንሰለት ዘርግቷል::

February 5/2014

የሐረር ሕዝብ ብሶቱ ቀጥሏል፡፡ አዲስ አበባ ያሉ ባለሥልጣናትም ዝምታቸው ቀጥሏል፡፡

በሃረሪ ብሄራዊ ሊግ የሚመራው የሃእርሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት እያለ ራሱን የሚጠራው ወያኔ ሰራሹ የጎሳ ጁንታ በሃረር እና አከባቢው ህዝብ ላይ ከፍተኛ በደሎችን እየፈጸመ እንዲሁም ሃገርን እና ህዝብን እየዘረፈ በሙስና እና በመልካም አስተዳደር አጣብቂኝ ውስት ተዘፍቆ ህዝቡን እያስለቀሰ መሆኑን ከአከባቢው የሚደርሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ::

በሐረር የሚገኙት የክልሉ ባለስልጣናት ዋና ግባቸው ስለልማትና ስለ መልካም አስተዳደር ሳይሆን ዘርፎ ስለመክበር እና በጫት ሱስ እግርን አጣጥፎ ከቤት ተጎልቶ መዋል ከሆነ አመታቶች ተቆጥረዋል፡፡ የክልሉ መንግስት መዋቅር በጎሳ የተቆጣጠረ በዘመድ አዝማድ፣ በዘር የተያያዘ በመሆኑ ማን ለማን ጥያቄውን አቤቱታውን እና ብሶቱን ማሰማት እንዳለበት አስቸጋሪ ሆንዋል፡፡

 ከዚህ ቀደም አዛውንቶችን በመደብደብ ሰውን ከነህይወት በማቃጠል እና ፍርድ በማጓደል እንዲሁን ከባድ ወንጀሎችን በመስራት የተካነው የሃረሪ ብሄራዊ ሊግ እና አባሎቹ እንዲሁም የኦሕዴድ ተጠሪዎች ማሰር፤ ማባረር በፍርድ ቤት ማስወሰን፣ መቀማት፣ በልዩ ኃይል ማስደብደብ የመሳሰሉትን ድርጊታቸው የእለት እለት ተግባር ስለሆነ ሕዝቡ ለምዷቸዋል፡፡ በሃረር በጎሳ እና ካልተሳሰሩ የገንዘብ ሰንሰለት ካሌለ ባለሀብት የመሆን እድሉ የለም ፡፡ ማንኛውም ነገር የሃሰት እና የይስሙላ ነው፡፡ ለሐረሪ ብሔራዊ ሊግ ገንዘብ ካልከፈለ ባለሀብት መባል ዘበት ነው::

ክልሉ የህዝቡን ትርታ ለማዳመጥ በሚል ለይስሙላ በጠራው ስብሰባ ላይ የተለያዩ ድርጅቶችና የኅብረተሰብ ክፍሎች በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ተሰባስበው ውይይት በተደረገበት፣ የክልሉን ጉድፍ ያጋለጡና የተናገሩ ግለሰቦች በማግሥቱ የሥራ ዕገዳና ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው መደረጉ ነው፡፡ በውይይቱ ላይ የህዝብን ብሶት ያሰሙ የመብት ረገጣ ዛቻ እና ስድብ ደርሶባቸዋል እየደረሰባቸውም ነው::

ይህንን ዘገባ ያጠናከረው ምንሊክ ሳልሳዊ እንዳለው ከከተማው የተሰበሰቡ የህዝብ አስተያየቶች እንደሚጠቁሙት በሐረሪ የህግ ትርጉም በተግባር ሳይሆን በሃሰት-የህዝብ እድገት በጋራ ሳይሆን በወረቀት እና በጎሳ ነው፡፡ ከከፍተኛ የክልሉ አመራር ጀምሮ እስከቀበሌ ሹማምንት በውሸት የተሞሉ ናቸው::ዘረኝነትና የጎጥ መጠራራት ገንኖ፣ የጎሳ ፖለቲካ አክራሪነት ተስፋፍቶ፣ የሰው መብት እንደ ትቢያ በሚበተንበት ክልል፣ መልካም አስተዳደር አለ ተብሎ በፌዴራሉ ቱባ ባለስልጣናት መነገሩ የሚያስተዛዝብ ነው፡፡ ከማእከላዊ የመንግስት ቢሮዎች የሚመጡ የፌዴራሉ ባለስልጣናት የሚቀርብላቸውም ሆነ ይዘውት የሚሄዱት ሪፖት እጅግ አስደንጋጭ መሆኑ እየታወቀ የፌዴራል ባለስልታናት ዝምታ የፖለቲካ ስልጣን ማስጠበቂያ አስመስሎታል:: ህዝብን የሚያዳምጥ አስተዳደር ያጣው የሃረር ነዋሪ ቁጣው ገንፍሎ አደባባይ ሊወጣ ይችላል የሚል ስጋቱ አይሏል::የምንሊክ ሳልሳዊ ዘገባ::

ጥንቃቄ የሚያሻው የኢትዮጵያ ፖለቲካ የትግል ጉዞ (በገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ)

 February 14/2014                                          

ከገዛኸኝ አበበ

አሁን አሁን በፊስቡክ፣ በየሚዲያው  እና በየማህበራዊ ድህረ ገጹ እንደምናየው እና እንደምንሰማው ወያኔ ወይም የወያኔን የልብ አጀንዳ ለማስፈጸም ጎንበስ ቀና እያሉ ያሉ  ቅጥረኞች ድርጅቶች ነን ባዮች  የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማደናገር  በየሚዲያው መንቀሳቀስ ጀምረዋል :: እነዚህ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች በአንድ ጎኑ ወያኔን የሚቃወሙ እየመሰሉ በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔን መንግስት ለመፋለም ቋርጠው የተነሱትን  ጠንካራ  እና እራሳቸውን በማደራጀት ላይ የሚገኙትን ፣ ለወያኔ መንግስት  አስፈሪ እና ስጋት በመሆን ላይ ያሉትን እራሱም ስጋት ይሆኑብኛል ብሎ የሚፈራቸውን የፖለቲካ ድርጅቶችን ወይም የፖለቲካ ሰዎችን በማሳደድ እና በመቃወም  የሚሰሩትን ስራ እና ትግላቸውን በማጣጣል ፣በማንቋሸሽ  የበሬ ወለደ ያህል የሃሰት ቅስቀሳቸውን ሲደሰኩሩ መስማት የተለመደ ነገር ሆኖል:: በእነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች ላይም ሆነ የፖለቲካ ሰዎች ላይ በየሚዲያው የሚደረገው  የሀሰት የወሬ ዘመቻ (propaganda) ሕዝብን ግራ ለማጋባት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ  ለማራዘም የወያኔ መንግስት በስፋት በየ አቅጣጫው ያሰማራቸው ለወያኔ እየሰሩ ያሉ አስመሳዬች የወያኔ ምልምሎች ሲሆኑ ስራቸውም የተቀዋሚዎችን  የፖለቲካ ትግል መሰለል እና ማዳከም  ሲሆን ይህም የሚያሳየው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭም እየተደረገ ያለው ፖለቲካዊ የትግል ጉዞ የወያኔን ባለስልጣኖች ምን ያህል እረፍት እንደነሳቸው እና እንቅልፍ እንዳሳጣቸው ነው  : :

ከዛሬ ዘጠኝ ዓመት በፊት ማለትም በ1997 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ የነበረውን የፖለቲካ መነቃቃት ሁላችንም የምናስታውሰው ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ አይምሮ ሊጠፋ የማይችል አጋጣሚ እንደነበር እና ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የወያኔን የኢሕአዴግን መንግስት የስልጣን እድሜ ሊያሳጥር የሚችል ጥሩ አጋጣሚ ተፈጥሮላት እንደነበር ሁሉም ሰው የሚስማማበት ሀቅ ሲሆን በጊዜው  አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ በወያኔ መንግስት ላይ የነበራቸውን የመረረ ጥላቻ በአደባባይ በመውጣት ለአለም ሕዝብ ያሳዩበት ወቅት ነበር ::በጊዜውም  ሕዝቡም  በወያኔ መንግስት ላይ ያለውን የመረረ ጥላቻ በግልጽ  በማሳየቱ ወጣት ወገኖቻችን በአንባባ ገነኑ የወያኔ መንግስት እንደ ሌባ እና እንደወንበዴ ተቆጥረው በግፍ የተጨፈጨፉበት እና የተገደሉበትን  ጊዜ ማንም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊራሳው የማይችል እውነታ ነው :: በዛን ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ  ለውጥ በመፈለግ እና በወያኔ የዘረኝነት አገዛዝ በመማረር  ታሪክን ሊሰራ ቆርጦ መነሳቶን በተግባር አስመስክሮል:: ለዚህም ማስታወሻ ይሆነን ዘንድ በሚያዚያ 30/1997  በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የወያኔን አንገት ባስደፋ እና ቅስም በሰበረ  መንገድ ከ2.5 ሚሊዮን የሚበለጥ ሕዝብ ማንም ሳያስገድደው አደባባይ በመውጣት ያሳየው ትዕይንት ማረጋገጫ ነው: ::




በወቅቱ በነበረው የሕዝቡ አንድነትእና ህብረት ፣ ሕዝቡ ለለውጥ በነበረው ጉጉት ያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ ለወያኔ መንግስታት አስደንጋጭ ከመሆኑ የተነሳ  ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፍርሀት ደንብረው  በደብረ ዘይት በሚገኘው አየር ሀይል ተሸሸገው ህዝቡ መብራት ጠፍቶበት፣ ደግሞም ዝናብ ዘንቦ ወደ ቤቱ ከተመለሰ በኋላ ወደ መንበራቸው መመለሳቸውን በጊዜው የነበሩ የአይን አማኞች ተናግረዋል::  : ከዛም በመቀጠል ግንቦት 7 19 97 የነበረው ክስተት  በየሰው ፊት ላይ ይነበበ የነበረውን ተስፋ ለመግለጽ ያስቸግር ነበር :: ወጣቶች በሙሉ ሀይላቸው ፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የገቡበት፣ ሁሉም ሰው ፍርሃት እና የፍርሃት ምንጭ የሆነውን የወያኔን አገዛዝ ደህና ሰንብት ያለ ይመስል ነበር በወቅቱ ይሆን እንጂ ምን ያደርጋል በጊዜው ተፈጥሮ የነበረውን የፖለቲካ መነቃቃት በአንዳንድ የበግ ለመድ በለበሱ  አስመሳይ ፖለቲከኞች እንደነ አቶ ልደቱ አያሌው በመሳሰሉ ሰዎች በጊዜው የነበረው የፓለቲካ መነቃቃት (revival ) መኮላሸቱ እና እንደ ጉም በኖ መጥፋቱ እስከ ዛሬም ድረስ አብዛኛውን ለውጥ እና ነጻነት ናፋቂ ሀገር ወዳት ኢትዮጵያ ዜጎችን የሚያስቆጭ እና የሚያንገበግብ ሲሆን ወያኔን ለማንበረከክ እና ከስልጣን ለማስወገድ የነበረው ወርቃማ ዕድል መበላሸቱ አብዛኛውን የኢትዮጵያን ሕዝብ  አስቋጥቷል ተስፋም አስቋርጦል::  በጊዜውም በነበረው ክስተት የአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብም ልብ ተሰብሮል:: እስከዛሬም ድረስ አንዳንድ ሰዎች በኢትዮጵያ የሚደረገውን ማንኛውንም ፖለቲካዊ ትግል በጓሬጥ እና በጥርጣሬ ዳር ላይ ቆመው እየተመለከቱት ይገኛል ::

 የ19 97 ምርጫን ተከትሎ የተፈጠረውን የፖለቲካ መነቃቃት መኮላሸቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ባለፉት ጊዚያቶች የነበሩት የፖለቲካም ሠዎች ሆኑ የፓለቲካ ድርጅቶች ባረጀ እና በገረጀፈ  ጭፍን የፖለቲካ አመራር እና የትም በማያደርስ አመለካከት የወያኔን የስልጣን እድሜ እያራዘሙት ይገኛሉ:: እንደእኔ አመለካከት የወያኔ ኢሕአዲግ የስልጣን እድሜ እስከዛሬ ሊረዘም የቻለበት ዋንኛው ምክንያት በራሱ በኢሕአዲግ ጥንካሬ ሳይሆን በተቃዋሚዎች በደከመ  እና በተልፈሰፈሰ አመራር ነው:: በኢትዮጵያ ውስጥ ያለፉትን 22 አመታቶች ብዙ የተቃዋሚ ፓርቲ ተብለው ስም የተሰጣቸው ስብስቦች ቢፈጠሩም  በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ አንዳችም የፈየዱት ነገር ሳይኖር ብዙ ጊዚያቶች አልፈዋል::  አሁን አሁን ግን እንደምናየው  እንደነ አንድነት፣ አራናት ትግራይ እና ሰማያዊ ፓርቲ ያሉ በወጣቶች የተገነቡ የፓለቲካ ፓርቲ ድርጅቶች መፈጠራቸው  በኢትዮጵያ ፖለቲካ  ተስፋ ቆርጦ የነበረው  ሕዝብ ላይ እስትንፋስ እየዘሩበት ይገኛሉ:: ከምርጫ 97 በኋላ በነበሩት አመታቶች   በኢትዮጵያ ፖለቲካ ልቡ ተሰብሮ እና ተስፋ ቆርጦ የተኛውን የኢትዮጵያ ሕዝብ እየቀሰቀሱት ቢሆንም  ራዕያቸውን ወደ ፊት ለማስጓዝ ብዙ የቤት ስራ ከፊታቸው የሚጠበቅባቸው ይመስለኛል:: በራቸውንም ነቅተው ከጠላት ወያኔ በመጠበቅ በጥንቃቄ መጓዝ ይገባቸዋል:: ምክንያቱም እስከዛሬ ወያኔ  እንደ እስስት እየተለዋወጠ እና እንደ እባብ እየተሽለኳለኳ ስንቶቹን የፖለቲካ ፖርቲ ድርጅቶችን እንደሽመደመዳቸው አይተናልና ::

በምርጫ 97 ጊዜ የነበረውን ቅንጅት ማንም ሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደዛ ፍርክስክሱ ይወጣል ብሎ የጠበቀም የገመተም አልነበረም ነገር ግን ባልተጠበቀ ሁኔታ ባልተገመተ ሰአት ብትንትኑ ሊወጣ የቻለበት ምክንያት ጥንቃቄ በጓደለው አካሄድ እና በተዝረከረከ አሰራር የተነሳ   ለጠላታቸው የወያኔ መንግስት መጠቀሚያ መሆናቸው ነበር :: ወያኔም እንደ እባብ  ተሹለክልኮ በመካከላቸው ለመግባት እና ለመበታትን ጊዜም አልወሰደበትም ነበር : :: በወቅቱም የቅንጅት መፈራረስ ወያኔ እና የወያኔ ካድሬዎች ጮቤ ያስረገጠ ክስተት የነበር ሲሆን ወያኔ እንዳለመው እና እንዳሰበው ለተወሰነም ጊዚያቱችም ቢሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተዳፍኖ የጠነከረ የፖለቲካ ድርጅት በሌለበት በማን አለብኝነት ለአጭር ጊዜም ቢሆን ተረጋግቶ እንዲቀመጥ አስችሎታል:: ይሁን እንጂ አሁን ላይ ግን ነገሮች ሁሉ እየተቀየሩ እና እየተለወጡ በውስጥም በውጭም ያለው የፖለቲካው ትግል እሳት እየነደደ እና እየተፋፋመ ሲሆን በቅርብ እንኮን እንደምንመለከተው የህወሃት  ወያኔ መንግስት የሚመካበት የትግራይ ህዝብ ሳይቀር የህውሃት  መንግስት ለትግራይ ሕዝብ እንደማይመጥን ለወያኔ መንግስት በግልጽ በአደባባይ እየነገሩት ይገኛሉ::በወያኔ መንግስት የስልጣን አገዛዝ መገዛት ያልሰለቸው እና ያልመረረው ብሔር እና የሀገሬቱ ዜጋ የለም ::  ለሆዳቸው እና ለጥቅማቸው ህሊናቸውን ሽጠው ከሚኖሩት  ከራሱ ከወያኔ ካድሬዎች በስተቀር  በመሆኑም እየተፋፋመ ያለው የፓለቲካው ትግል መነቃቃት መላውን  ሀገር ወዳድ የኢትዮጵያ ዜጎችን  ከዳር እስከዳር ማዳረሱ እና ማነቃነቁ የማይቀር ሀቅ ነው :: ስለዚህ የፖለቲካውን እሳት እያጋጋሉ እና  እያፋፋሙ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሆነ የፖለቲካ መሪዎች ባለፈው ከነበረው ስህተት በመማር በራቸውን ከጠላት ወያኔ ተጠንቅቆ በመጠበቅ ትግሉን ማስቀጠል እና ማፋፋም ይጠብቅባቸዋል :: ወጣቱ ለለውጥ ልቡ ተነሳስቷል የወያኔ ኢህአዲግም የስልጣን ዘመን የጭቆና አገዛዝ የሚከስምበት ጊዜ እሩቅ አይሁንም ::

     ኢትዮጵያ በቆራጥ ታጋይ ልጆቿ ከወያኔያዊ አገዛዝ ነጻ ትወጣለች::

   gezapower@gmail.com
       
              ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!






Wednesday, February 5, 2014

ትምህርት ቤታችን እና ኮሚኒቲውን የከበበው አደጋ …!

February 5/2014

school



የመምህራን ማስጠንቀቂያ …
ሰሞነኛው የጅዳዎች ጉዳይ የመኖሪያ ፈቃድን በማስተካከል ዙሪያ ቢሆንም ከ 3000 (ከሶስት ሽህ) በላይ ታዳጊዎችን የሚያስተናግደው የጅዳው አለም አቀፍ ት/ቤት አሁንም አደጋ ላይ መሆኑን እየሰማን ዝም ብለናል!  ከሳምንታት በፊት መምህራን አመጽ አድርገው ነበር። ከቀናት በፊትም  25 መምህራን ስብሰባ ተቀምጠው፣ በአንድ አቋም ጸንተው ጠንከር ያለ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል። ላለፉት 8 ወራት በትምህርት ቤቱ ባለቤት በኮሚኒቲው ጉዳያቸው ቢያዝም እስካሁን ከወሬ ያላለፈ አርምጃ አለማየታቸውን ገልጸዋል።  25 ቱ school letterመምህራን ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር፣ ለኮሚኒቲው፣ ለጅዳ ቆንስልና ለወላጅ መምህራን ህብረት ባስገቡት ደብዳቤ እስከ ቀጣዩ ሳምንት የሁለተኛው የትምህት አጋማሽ መጀመሪያ የመኖሪያና የስራ ፈቃዳቸው ተስተካክሎ ካልተሰጣቸው  በማስተማር መደበኛ ስራቸው እንደማይገኙ በላኩት የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ማስጠንቀቃቸውን በእጀ የገባው ሰነድ ያመላክታል!
የወላጅ መምህራን ህብረት ስብሰባ ጥሪ …
“ወላጅና መምህራን ህብረት” በሚል ካች አምና በመንግስት ትዕዛዝ የወላጅ ኮሚቴን የተካው ኮሚቴ በትምህርት ቤቱ ዙሪያ ለመምከር ለወላጅ ስብሰባ ጠርቷል። ኮሚቴው የሳውዲን የምህረት አዋጅ ማለቅ ተከትሎ የጅዳ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት ለሳምንት ሲዘጋ የሚወክለውን ወላጅም ሆነ መምህራኑን ብሎ ድምጹን አላሰማም። ትምህርት ቤቱ ካንድም ሁለት ሶስቴ በመምህራን ስራ ማቆም አድማ ሲናጥ፣ ከፍተኛ የማህበረሰቡ መዋዕለ ንዋይ ከመጋረጃ ጀርባ ለሚደረጉ የመምህራን እና ሰራተኛ ዝውውር መባከኑ ሲሰማ የዝሆን ጀሮ ስጠኝ ማለቱ አይደንቅ ይሆናል። የመንግስት ሃላፊዎች ትኩረትና ጥበቃ የማይደረግለትን  የትምህርት ማዕከል ህልውና ለማስጠበቅ ስብሰባ መጥራትና ወላጁን ባለማማከሩ ተወቃሽ ከመሆን ግን አላመለጠም። ለሚታየው እንግዳ፣ ለሚሰማው ባዳ መሆናቸው ያስከፋው ወላጅ ከትናንትም ዛሬ ተስፋ ቆርጧል።
ዛሬ የወላጅ መምህራን ህብረት ተብየውን ምን እንዳሰናከለው፣ ምን እንዳሽመደመደው መስማት ባያጓጓም የወደፊት የወላጁን፣ የመምህራንንና የታዳጊዎችን ትምህርት ቤት አደጋ ላይ መውደቅ  እያየ ስለያዘው አቋም መስማት ጓጉተናል። ማስታወቂያ ባወጣ በሳምንቱ፣ ስብሰባውን ሊያደርግ ቀናት ሲቀሩት ደግሞ ዛሬ ምሽት የህብረቱ አመራሮች በጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ሃላፊዎች ለአስቸኳይ ስብሰባ ተጠርተዋል። አሁንም ኮሚቴው በዚህ ስብሰባ ምን በል ሊባልም ሆነ ከወላጅ መምህራን ጋር በሚደረገው ስብሰባ ላይ እንዳይነካ የሚፈለገውን ቦታና  እንዳይታለፍ የሚፈለገው የቀይ መስመር ገደብ ምን ሊሆን እንደሚችል አንገምትም።  ብቻ ሁነኛ ባለቤት አጥቶ አንደ ስደተኛው ተገፊ ወገን ለሚከላተመው የ3000 ታዳጊዎች ትምህርት ቤት መጻኢ ህይዎት ወላጁ በስብሰባው በመሳተፍ መምከር ይኖርበታል።sch letter
በመግስት ሊደራጅ ያታቀደው ኮሚኒቲ …
ዛሬ ያለው ኮሚኒቲ በአዲስ የመተኪያው የምርጫ ጊዜ በቆንስል መስሪያ ቤቱ ትዕዛዝ ተላልፏል። የሚተካው ኮሚቴ ደግሞ የሚደራጀው በመንግስት እንደሆነ እየተነገረን ነው። የምርጫው መዘግየትም ዋናው ምክንያት ይህ እውነት መሆኑ ቆንስል መስሪያ ቤቱ ከመካከለኛው ምስራቅ አገኘሁ ያለውን ሞዴል የኮሚኒቲ ህግና ደንብ ረቂቅ ጊዜውን ለጨረሰው ኮሚኒቲ ይፋ አድርጎታል። ቅንነት በሌለበት መንደር በወረቀት ላይ በሰፈረ ህግና መመሪያ ለወጥ ያመጣ ይመስል የማይገባ ስራ መሰራት ተጀመሯል። የሚጠፋውን ጊዜና የሚባክነውን የማህበረሰብ ንብረት ብክነት ነዋሪው ህብረት ፈጥሮና ማህበሩን ከፖለቲካና ከድርጅት አደረጃጀት ጣለቃ ገብ ሂደት በማስቆም ነጻ ካላወጣው አደጋው የከፋ እንደሚሆን ጥርጣሬው ያየለብኝ ለእኔ ብቻ ቢሆን መልካም ነበር ። ግን አይደለም። ብዙ ነዋሪ አዲሱን አካሄድ አልወደደውም!
ኮሚኒቲውን በአንድ ባንዴራ ስር ከማደራጀት ተወጥቶ በብሔር ብሔረሰብ ስብጥርና የፖለቲካ ድርጅት ሰወች በኮሚኒቲው በማሰግሰግ የሰራነው ስራ እንዳላዋጣን እናስተውለው። ወላጁም ሆነ አብዛኛው የጅዳና አካባቢው ነዋሪ ለአመታት የራቀው ኮሚኒቲ የጥቂቶች መፈንጫ ከሆነ ወዲህ የሆነውን ቆም ብለን እናስብ! እናም ቢያንስ በልጆቻችን ትምህርት ቤትን ህልውና ለማስጠበቅ ኮሚኒቲውን ሊውጠው ከተዘጋጀ ክፉ አውሬ አፍ ለማዳን እንረባረብ!  በኮሚኒቲውና በትምህርት ቤቱ ዙሪያ በሚደረጉ ስብሰባዎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የልጆቻችን ትምህርት ቤት ለመታደግና ለህልናው ወሳኝ የሆነውን ኮሚኒቲ ከወደቀበት አዘቅት አውጥተን ለብሩህ ተስፋ ሂደቱ እንታደገው፣ እናጎልብተው!  ወላጅና መምህራን ህብረት በጠሩት ስብሰባ ተሳታፊ እንሁን፣ በነጻነት ሃሳባችን እናንሸራሽር! የልጆቻችን ትምህር ቤተችን ከአደጋ እንታደገው!  ይህ ማንም የማይገሰው መብታችን ነውና!
ጀሮ ያለው ይስማ!
ነቢዩ ሲራክ

ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች

February5/2014


ግብፅ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ ጀመረች

-የግብፅ የልዑካን ቡድን በህዳሴው ግድብ ላይ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር ሊነጋገር ነው
የግብፅ መንግሥት በታላቁ የህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ በተመለከተ ሱዳን ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ድጋፍ ለማጨናገፍ፣ ሱዳንን ከኢትዮጵያ ለመነጠል ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ መጀመርዋን ዘገባዎች አመለከቱ፡፡
የተለያዩ የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ሰሞኑን እንደዘገቡት፣ የግብፅ መንግሥት የተለያዩ የመንግሥት አመራሮችና ፖለቲከኞች ከሱዳን መንግሥት አቻዎቻቸው ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ጀምረዋል፡፡

ለአብነት ከተጠቀሱት መካከል የግብፅ አል ዋፍድ ፓርቲ ሊቀመንበር ሳይድ አል ባዳዊ በካይሮ ከሱዳን አምባሳደር ከማል ሐሰን ዓሊ ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበር የፀጥታ ጉዳዮች ላይ በዋነኝነት መክረዋል፡፡ በሁለቱ አገሮች ድንበር የጦር መሣሪያ ዝውውር ለማስቆም የተነጋገሩት ሁለቱ ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብና በሱዳን አቋም ላይ ተነጋግረዋል፡፡

ከውይይታቸው በኋላ አል ባዳዊ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሱዳን በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላት አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ተመሳሳይ ነው መባሉ በእውነት ላይ ያልተመሠረተ ተባራሪ ወሬ ነው ብለዋል፡፡ 

በግድቡ ላይ ሦስቱ አገሮች ጥልቅ ውይይት አካሂደው የሁሉንም ወገን ጥያቄዎች በሚመለስ ደረጃ መግባባት ይኖርባቸዋል የሚሉት አል ባዳዊ፣ ሱዳን የግብፅን የውኃ ፍላጐት በሚነካና ብሔራዊ ደኅንነቷን በሚጐዳ ጉዳይ ላይ አሉታዊ አቋም አትይዝም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡ 

የሱዳን የመገናኛ ብዙኃን ባለፈው ሰኞ ዘገባዎቻቸው የሱዳን የመከላከያ ሚኒስትር በዚህ ሳምንት ወደ ካይሮ በማቅናት ከግብፅ አቻቸው ከፊልድ ማርሻል አብዱልፋታህ አል ሲሲ ጋር በሁለቱ አገሮች የጋራ የደኅንነት ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ወደ ግብፅ በዚህ ሳምንት እንደሚያመሩ የሱዳን ትሪቡን ዘገባ ያመለክታል፡፡ 

የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር መሐመድ አብዱል ሙታሊብ ባለፈው ሰኞ በሰጡት መግለጫ ደግሞ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ማቆም እንደሚገባት ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ በዓባይ ላይ የኃይል ማመንጫ ግድብ መገንባት ከፈለገች መጠኑ አነስተኛ መሆን ይገባዋል፤›› ብለዋል፡፡ እንደሳቸው አባባል የህዳሴው ግድብ ግንባታ ከታቀደው ስድስት ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ወደ 30 በመቶ ዝቅ ማለት አለበት፡፡ በዚህ ስሌት የታላቁ የህዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ወደ 1,800 ሜጋ ዋት መውረድ አለበት፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 45 አባላትን የያዘ የግብፅ የዲፕሎማሲ ቡድን ከጥር 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለአምስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ግብፅ በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለአፍሪካ ኅብረት እንደሚያሳውቅና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትንም እንደሚያነጋግር ለመረዳት ተችሏል፡፡

ኢትዮጵያን የሚጐበኘው የልዑካን ቡድን በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ኃላፊ አምባሳደር ዓሊ ኣል ሃዲዴ የሚመራ መሆኑን በኢትዮጵያ የግብፅ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡ የልዑካን ቡድኑ ከአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት ኃላፊና ከኅብረቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ኮሚሽነር ጋር እንደሚመክር የተያዘው ፕሮግራም ያስረዳል፡፡ 

በተጨማሪም ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ዳይሬክቶሬትና ከሕግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ኃላፊዎች ጋር እንደሚነጋገር ታውቋል፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጋር በመገናኘት በህዳሴው ግድብ ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በቅርቡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የወሰንና ወሰን ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅአህመድ ነጋሽ፣ ሱዳን በህዳሴው ግድብ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የወገነችው ለራሷ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ በአጋጣሚ ለድርድር በካርቱም በቆዩባቸው ጊዜያት በተለያዩ መስጊዶች ውስጥ ሳይቀር የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሱዳንን እንዴት ሊጠቅም እንደሚችል ሲሰበክ በግርምት መታዘባቸውን በመግለጽ፣ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጐን ለራሷ ጥቅም ስትል መቆሟን መረዳት ይቻላል ብለዋል፡፡

የግብፅ ባለሥልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር በሚደረገው ውይይትም ሆነ ድርድር ሱዳን የግብፅን ጥቅም የሚፃረር አቋም እንድትይዝ አለመፈለጋቸው ቢነገርም፣ ሱዳን እስካሁን የግድቡን ግንባታ እንደምትደግፍ ነው የሚታወቀው፡፡ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጎን ለመሰለፍ የቻለችው በሦስቱ አገሮች ተወክሎ ሲሠራ የነበረውና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ያካተተው የኤክስፐርቶች ፓነል ሪፖርት ድምዳሜን አገናዝባ ነው፡፡ በሪፖርቱ ግድቡ በሱዳንም ሆነ በግብፅ ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት እንደማያደርስ ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡ ምንም እንኳ የግብፅ ባለሥልጣን የሱዳን አቋም ከኢትዮጵያ ጋር ወግኗል መባሉን ተባራሪ ወሬ ነው ቢሉም፣ የሱዳን ባለሥልጣናት በአደባባይ ድጋፋቸውን መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡
ሪፖርተር

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ አቶ አስራት ጣሴ ፍርድ ቤትን መዝለፍ በሚል ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው

February 5/2014


አቶ አስራት ጣሴ ፍርድ ቤትን መዝለፍ በሚል ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው
-ጉዳዩ ከአኬልዳማ ዶክመንተሪ ጋር የተያያዘ ነው
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የምክር ቤት አባል አቶ አስራት ጣሴ፣ ፍርድ ቤት ፍትሕ የማይሰጥ አካል መሆኑን የሚገልጽ ዘለፋ አዘል ጽሑፍ ጽፈዋል በሚል ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ተላለፈ፡፡ 
የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዘጠነኛ ፍትሐ ብሔር ሁለተኛ የቤተሰብ ችሎት ጥር 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ወጪ ያደረገው የትዕዛዝ ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ አቶ አስራት ጣሴ በአዲስ ጉዳይ ሳምንታዊ መጽሔት ቅጽ 7 ቁጥር 198 የጥር ወር 2006 ዓ.ም. ዕትም አንድ መጣጥፍ አቅርበዋል፡፡ ‹‹… አሁን ደግሞ ከሰሞኑ ‘አኬልዳማ’ ድራማ በድጋሚ በተከታታይ እየቀረበና እየታየ ነው፡፡ ይህ እየሆነ ያለው አንድነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅትን በስም ማጥፋት ወንጀል በፍርድ ቤት ከሶ ገና ውጤት ባልተገኘበት ወቅት ነው፡፡ እሱም ፍትሕ ከኢሕአዴግ ፍርድ ቤቶች ይገኛል ተብሎ ሳይሆን፣ በታሪክ ምስክርነት እንዲመዘገብ ሲባል ነው፤›› የሚል ጽሑፍ ማቅረባቸውን ፍርድ ቤቱ በፖሊስ በኩል ለአቶ አስራት እንዲደርሳቸው ባስተላለፈው የትዕዛዝ ደብዳቤ ላይ ሰፍሯል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከላይ በትዕዛዝ ደብዳቤው ላይ ያሰፈረውንና አቶ አስራት በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ጽፈውታል የተባለውን ጽሑፍ ‹‹ፍርድ ቤት ፍትሕ የማይሰጥ አካል መሆኑን የሚገልጽ ዘለፋ አዘል ጽሑፍ›› ሲል ገልጾታል፡፡

በመሆኑም መዝገቡ ከመመርመሩና ማለትም አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከሳሽ ሆኖ የቀረበበትንና የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅትና የድርጅቱ ሠራተኛ የሆነው ጋዜጠኛ አብዲ ከማል ተከሳሾች የሆኑበት መዝገብ ከመመርመሩ በፊት፣ የአቶ አስራትን ጉዳይ ማጣራት አስፈላጊ ሆኖ ማግኘቱን አስታውቋል፡፡ በመሆኑም አቶ አስራት ጣሴ ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በኩል ደብዳቤው እንዲደርሳቸው ትዕዛዝ ተላልፏል፡፡   

ጐፋ ገበያ ማዕከል ላይ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ 19 መደብሮች ወደሙ

February 5/2014


ጐፋ ገበያ ማዕከል ላይ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ 19 መደብሮች ወደሙ
-በገበያ ማዕከሉ የእሳት ቃጠሎ ሲደርስ ለዘጠነኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ቄራ ጐፋ የገበያ ማዕከል ላይ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ 19 መደብሮች ሙሉ በሙሉ ወደሙ፡፡ 
ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሌሊቱ 7፡15 ሰዓት ላይ የእሳት ቃጠሎው እንደተከሰተ የገለጹት፣ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ ንጋቱ ማሞ ናቸው፡፡ የእሳቱ መነሻ ምክንያትና በንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠን አለመታወቁን ተናግረዋል፡፡
በቄራ ጐፋ የገበያ ማዕከል ውስጥ ቁጥራቸው 500 የሚደርሱ ነዋሪዎችና ነጋዴዎች መኖራቸውን የገለጹት አቶ ንጋቱ፣ ከቤቶቹና ከሱቆቹ አሠራር አኳያ ሲታይ 19 መደብሮችና መኖሪያ ቤቶች ብቻ ተቃጥለው ሌሎቹ መትረፋቸው አስገራሚ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ቤቶቹ ከተሠሩበት ግብዓትና መቀራረብ አኳያ መሆኑን አክለዋል፡፡ 
ከ53 ሺሕ ሊትር በላይ ውኃ በመርጨትና ሌሎች የማጥፊያ ዘዴዎችን በመጠቀም በ1፡30 ሰዓት ውስጥ እሳቱን ለመቆጣጠር መቻሉን ኦፊሰሩ ተናግረዋል፡፡ ቤቶቹ ቆርቆሮ በቆርቆሮ ሆነው ከመሠራታቸው በተጨማሪ፣ እጅግ በጣም የተጠጋጉና መደብሮቹም ውስጥ ለእሳት መቀጣጠል ምቹ የሆኑ ሸቀጣ ሸቀጦች በመኖራቸው ምክንያት ለማጥፋት አስቸጋሪ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡
ባለሥልጣኑ የግምት ባለሙያ ባይኖረውም ከተረፈው ንብረትና በአካባቢው ካሉት የንግድ ባንክና ሌሎች ድርጅቶች መትረፍ አንፃር በእሳቱ የወደመው ንብረት ትንሽ መሆኑን አቶ ንጋቱ አክለዋል፡፡
ሪፖርተር

The Revolutionary Democracy of TPLF

February 5, 2014

The Revolutionary Democracy of TPLF REGIME: When the bullshit hit the fan… what do you do?

by Teshome Debalke   
The BS of Colonial map under Administrative subdivision of Italian
The BS of Colonial map under Administrative subdivision of Italian East Africa and TPLF/Woyane Federal Regional map: Does it mean Eritrea territory extend beyond Badme and Afar to include TPLF’s Tigray Region? If not, why not? How it is invaders decide the fate of independent people and nation that defeated colonial ambition to occupy, divide and rule our people?
The ruling TPLF led regime of Ethiopia’s stooges amazingly aren’t running out of bullshit every turn and  are increasingly getting nastier–coming up with more bizarre BS. It appears they are to the point of no return where the hard core operatives are in a do-or-die position to save the regime. Buried under rubble of BS for far too long they are throwing mud allover to see if it sticks. It isn’t unusual for any group that started with BS to live under piles of it not to see straight to go back or forward. Welcome to the Revolutionary Democracy of Ethnic Federal Apartheid regime of TPLF/Woyane of Ethiopia.
Take for instance the regime’s BS guru Berket Simon. Recently he was uttering the preconditions of transition from the Revolutionary Democracy to Democratic Development State. Frankly, the former mouthpiece of  TPLF led EPRDF regime has no idea what it means–except it is his duty to BS people; thanks to the legendry late Prime Minster Meles Zenawi that masterminded the hoax. Unfortunately, the entire TPLF/Woyane regime is operating on auto-pilot on the ‘legacy’ of the late PM’s BS. We can’t help but admire how he managed to convince thousands of stooges to turn his loaded BS into good legacy worth a Foundation.
As expected, Berket Simon is back spewing the same toxic BS after his extended rehabilitation from exhaustive career of lying. One expects him to learn something better; instead, the infamous former Ethiopian Government Mis-Communication Minster and present babysitter of in-name-only Prime Minster came back as bad if not worse than before.  This time around, he added a new skill of vulgarity. Not that he was known for his good character for decency or to have the manner of Ethiopians he hates to love but, his public BS of two decades admittedly turned out to be real BS and left semi-permanent skid mark.
Here is the real and improved Berket Simon talking in his own words insulting Ethiopians
“የኢትዮጵያ አርሶ አደር እስካሁን በተደረገለት ሥራ በሚገባ የረካ ስለሆነ ‹መንግሥት ሰልፍ ውጣ ቢለው ይወጣል፤ መንግሥት ተኛ ቢለው ይተኛል፤ ግፍ ብንፈጽም እንኳን አርሶ አደሩ ይህንን መንግሥት ይሸከመዋል እንጂ ምንም አይለውም፡፡”
Now my people, be the judge, could a Minster in the Ethnic Federalism of the Revolutionary Democracy of Ethiopia with no ethnic identity of his own have the capacity to rationalize and the crimes of the regime he serves?  You can see what our people are subjected to live under the BS of TPLF led regime.
The saddest things of all is when the collection of stooges and apologist of the regime masquerading as officials, parliamentarian, judges, security personnel, journalist, educators, businessmen, cadres … are mute; scared to their pants to confront the BS of the regime. In reality, Berket was referring to them–sleeping, tap-dancing, and jumping high when the regime tell them to do so.  Again, welcome to the BS Ethnic Federal Revolutionary Democracy regime surrounded by collection of zombies parroting its stench.
As the saying goes, boys will always be boys, so the ethnic jungle boys of TPLF/Woyane.  It seems the regime exercise of futility is running its course and no one knows what to do with it but hide it under piles of more toxic BS. In fact, it is getting beyond recognition even the guru Berket Simon couldn’t contain it anymore. Instead more BSs are thrown at us to sustain a dead-ethnic regime; I might add a self-inflected death. Naturally, Berket is the ideal candidate with extensive experience of spinning and spilling toxic starting with his own fluid character and unknown ethnic identity.
The ‘Ethio-Eritrean’ national supposedly voted in the 1993 Eritrean Referendum for independence (freedom or slavery) and must have voted for ‘slavery’ to remain Ethiopian. Accordingly, the record breaking 99.98% vote for independence left Berket behind in the Federal Nations and Nationality of Ethiopia with no Nation or Nationality to claim. But again, he was given an important Ministerial position, not bad for someone with no ethnic ‘Nation’ to call his own in the BS Ethnic Federalism of the Revolutionary Democracy of TPLF/Woyane he serves or as Berket himself defend it, ‘ the Constitution of Nation and Nationalities’ of Ethiopia. As funny as it sounds coming from a man with no ethnic identity or Region it is another BS concocted by Tigray People Liberation Front (TPLF).
But again, Berket was fostered (implanted) in the Amahra Region. No one knows why he picked the ‘Amahra’ Region to become a State Minster ‘representing’ people he doesn’t belong in violation of the BS Nations and Nationality Constitution.   One should also wonder what his TPLF issued ID would say about his ethnicity as required by TPLF led regime that setup the Apartheid system for the rest of Ethiopians.  Endangered species?  Lost tribe of the former territory?  Unidentified ethnic origin? Whatever it is the regime’s BS extends deeper than what the world is led to believe.
Don’t get me wrong my people or as TPLF/Woyane want me to refer you my Ethnic Nations and Nationalities of peoples.  It is all good and dandy to be proud of our ethnic heritages and the whole enchilada but, what does it has to do with the BS TPLF/Woyane and its hired hands with ever changing identity and BS? Haven’t we been there before with multiple invaders throughout our history?
For over four decades we have been living under pile of BS in-and-on both side of the MerebRiver.  If you ask for my opinion, it is for one reason only; to destroy our glories history as proud and independent people in order to reduce us into collection of tribes under the mercy of foreigners as invaders always wanted us to be. Who is better qualified to do just that but TPLF/Woyane?  But again, what do I know when our learned men and women go along with the BS of TPLF/Woyane to believe Apartheid is Revolutionary Democracy and robbing the people and the nation is Growth and Transformation?
What can I say except BS has no nationality, ethnicity, region or religion, for that matter boundaries or qualification as we are witnessing our peoples suffur in the hands of Woyane and its stooges with questionable identity while most of us watching in silence. And, no one is a living example of the toxicity of TPLF/Woyane ethnic BS than Berket Simon himself.
You see my people; we live under a poisonous regime with endless smut coming our way.  If you think this regime is worthy of anything you must be a born sucker or a hyena roaming the street in the shadow of the darkness preying on our people. Don’t think you are anything but… and don’t for a second believe you can get away with it.
The venom of TPLF/Woyane is plenty to cover here except to say Berket is the prime example of it.  You can imagine what piles of TPLF’s toxic BS did to the hyenas and zombies of the regime all these years. It goes without saying, the entire stooges and apologist of the regime are buried under debris of BS to see and think straight.
What can Ethiopians should make of the BS coming from all directions?
The first thing that comes in mind is when the stateless Berket Simon with unidentified ethnicity accuses Ethiopians for violating the Ethnic Federal Constitutional order; loosely translated TPLF/Woyane’s BS. It is where the problem began and must end.
Thus, we can easily understand the pain and suffering the stooges and the apologist of TPLF/Woyane go through. After all, the fact they aren’t capable of understanding the regime’s BS to become accessories to its heinous crimes should tell us a lot. Call them ignorant, corrupt, or treacherous their behavior of no see, hear…evil is where the problem began and must end.
Surprisingly, the stooges and apologist of regime aren’t the only one around living under rubble of BS. Average Ethiopians–peddling one thing or another against their best judgment come up with all kinds of bizarre behavior that empowered the rotten regime further.
Take for example the selective memory reflected on an article titled ‘A bad day for a career diplomat’ written by Amare Lucas– spinning facts and fictions out of proportion. The fellow piled up more of TPLF’s BS via lambasting David Shinn, the former US Ambassador to Ethiopia known for his own BS.
Amare opened his article rightly defending the people of ‘Tigray’ from being insulted by semi-retired Diplomat. But he didn’t hesitate to insinuate TPLF is the defender of Ethiopian’s interest from Eritrea.  Then, for whatever reason, he went on breaking down the ethnicity of the Eritrean President and most of his trusted aids by the percentage of their Tigrian bloodline.  He said;
“Mr. Ambassador, despite the unnecessary war of 1998 initiated by non-other than Isayas, and notwithstanding the emergence of an Eritrean state, those two Tigrigna speaking people are very much blood related. Do I need to prove that? For starters, Isayas is 75% from Tigryan parents, if not 100%. Most of his trusted aides and advisors are from 100 % Tigryan parents, and some are 50%. In case of Ethiopia, the late PM, Meles is 50% Eritrean. In his recent trip to the US, Sebhat Nega, one of the founders of the TPLF and its first chairman, (I suspect you two have probably met) had an interview with a radio-host in Washington, DC. Answering a question to the host, Sebhat unequivocally declared that he in fact has an Eritrean blood”
It wasn’t clear why he wanted to make Eritrean leaders share the same blood with their counterparts in Ethiopia. What different would it make what bloodline of people that live in different country with Ethnic Federalism as TPLF ruled Ethiopia?
Then, he went on fantasy expedition of the history and geography of Tigray…
“Well, Mr. Ambassador, you and I need a brief question-and-answer session. How much have you read as opposed to being told about Tigray? Have you been to Aksum, Yeha, Gerealta, and other parts of Tigray? Have you ever read about the genius Aksumite, St. Yared? Our session won’t end today. So, let me make it short. Looking at the monuments, underground palaces of King Kaleb, Gebremeskel, Ezana, Queen Sheba, the rock-cut churches all over Tigray—-Would someone in his right mind dare to say what you said about the Tigryans? Mr. Ambassador, Christianity and Islam got their footing in Tigray. The Ethiopian alphabet, literature, music, art, governance, and the first money in coins were all introduced in the then capital of Ethiopia, Aksum, which happens to be in Tigray. Simply put, Tigray is the beginning of Ethiopia and its civilization. Sir, I can present a long list of the many wonders and miraculous architects like Fasil in Gonder, the unparalleled rock-cut church of Lalibela in Wollo, and many more Ethiopian prides and early civilization testaments. But you chose to disparage the Tigryans and my focus for now will be Tigray.”
The sorry fellow went all over the map and trampled on historical facts and timeline to educate us about Tigray via the ‘ignorant’ Ambassador without reviling his credential and the historical facts of his assertions or his ethnic identity he made the central point of the article.
For instance, the inhabitant of the Axumite Empire and the Kings/Queens and nobilities and Ethiopia herself came through Tigray via Axumite Empire.
The Axumite Empire that extends to present day Yemen and Sudan is reduced to none existence Tigray Province or Region.  Never mind there was no place called Tigray, Eritrea, Somali, Sudan, Kenya or Djibouti Assab, or Badem or a language called Tigrigna or Amharic during the Axumite Empire. Forget the fact Christianity and Islam came to Ethiopia way before a place called Tigray or the people called Tigrians.  Even if they did so where is written or stated one human being is superior than the other, we all do not chose our parents and place of birth at the time of coming to this world?
The same kind of BS the late Banda Melse Zenawi use to tell us when he reduced Ethiopia as a collection of tribes created 100 years ago by the legendary King Menlik II came back in rather different spin.
Is the author piling up more BS on the top of TPLF’s to make us believe the new Ethiopia under TPLF/Woyane is reduced between the then none existence Tigray via Axumite Empire and the present Tigray of TPLF led Ethnic Federalism? As our people say ‘አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል’
Indecently, the author conveniently never mentioned the ruling regime TPLF that reduced Ethiopia as 100 year old nor he care to mention the illegitimacy of TPLF/Woyane as he lambasted Eritrea ruled by Isyayas.  What is up with not telling us the whole truth but noting but the truth?
By the way, why would EthioMedia deprived us the background, the identity and the credential of the Amare Lucas so that he can be challenge to tell the whole truth but noting but the truth?   No answer but more questions.
When Tigray/Axumite Empire defender Amare Lucas wasn’t enough BS the Eritrea defender Amanuel Biedemariam came up with his own BS article titled  TPLF: The Dog That Can no longer Bark and went on his own fantasy to fit Eritrea represented by EPLF/Shabiya verses Ethiopia represented by TPLF/Woyane; lambasting the ‘Eritrean’ national Ethiopian Berket Simon as if he is speaking on behalf of Ethiopia representing TPLF. He said,
“The key question, why did Bereket Simon come-out now and made these absurd statements? Moreover, why now, when many particularly the US, for the first time in over 15 years is talking peace did Bereket Simon roll-out this war agenda? The questions are endless.
The answer to all these questions are found on a statement one astute Eritrean political figure made a while back. When asked to respond about outrageous repeated statements by the TPLF against Eritrea, he answered, “When a dog barks uncontrollably disturbing peace, the best option is to talk to the owners of the dog.”
There are three key reasons why Bereket Simon decided to come out and declared the continuation of the hostilities…”
Here again the author conveniently ignored the identity and background of Berket Simon and the illegitimacy of TPLF/Woyane. Nor he cared to mention Berket isn’t TPLF member (at least not officially) and didn’t bother to mention his Eritrean background that voted to remain Ethiopian by adapting Amahra identity.
Thus, the affair of the people of the old ‘Ethiopia’ and new ‘Eritrea’ is reduced  into TPLF/Woyane and EPLF/Shbiya’s love and hate with each wanting to fit their fantasy into historical reality  on the expenses of the people of the divided line.
Let’s put the BS and selective memory of historical facts on all sides in perspective for a change.  It is important not to make up history, facts and timeline to fit the village and tribal fantasy to hold on to power illegitimately and indefinitely. It is an old trick used and abused by dictators and their intellectual prostitutes for far too long and must end.
For example, the ruling TPLF regime is as illegitimate as the Italian regime that occupied Ethiopia for five long years. Any way you shake it or bake it TPLF/Woyane can’t speak on behalf of the people of Ethiopia period. Instead of looking for excuses to prolong its rule by technicality and scapegoating the sooner we accept that reality the better. No matter what kind of BS people come up with nothing will change that reality. Likewise, the ruling regime of Eritrea legitimacy is the problem of Eritreans to sort out when they accepted the 99.98% vote for independence.
Negotiating with TPLF/Woyane isn’t going to help Eritrea/Shabiya come to the reality sooner but widen the conflicts and the misery of our peoples.  The love or hate between TPLF/Woyane and EPLF/Shabiya isn’t the fight between Ethiopians and Eritreans.
Therefore, my advice to BS handlers of TPLF/Woyane or others is simple. Just because the TPLF regime cooked up Ethnic Federalism to say the people of Ethiopia are collections of ethnic groups to deprive us our glories history as the mosaic of relative tranquility and free people with organic justice beyond the capacity of modern-day ethnic peddlers and hyenas to understand doesn’t mean we gave up on our people and country.
Likewise, EPLF/Shbiya or others would be better off to stop the BS and scapegoating and face reality in that; independence from phantom enemy alone isn’t a solution but freedom and democracy.
Therefore, the only choice for all involved is to cut the BS and surrender for the truth and democratic rule. No one should get away with the BS against any people. We will all be better off to accept the fact that’ there is no good dictatorship but a dead one’. It should remind us no nation and its people saw the daylight ruled by the jungle rule.
My advice to my people is, don’t be suckers for modern day dictators, robbers and mercenaries. Our very existence as Ethiopian people depends on our coming together to rid of the scourge off our back.  Anyone that tells you aren’t Ethiopian first but a tribe, a religious sect or an economic class… and promise you milk and honey is setting you up to strip off your dignity and identity as Ethiopians to  prepare you for modern day slavery or as a Weapon-of-Mass-Distraction and exploitation on your own fellow Ethiopians and your country for the benefit of a solid dictatorship as TPLF/Woyane is doing as we speak. Say No to the BS.
The one-and-only demand from one-and-all Ethiopians is the current regime must surrender for the rule of law and democracy regardless of any BS coming from anyone and anyplace and for any reason.
Ethiopia and Ethiopians will live-on and there is nothing anyone can do about the gathering Ethiopianism feeling and force that is paving our nation’s future.
Be ready for the collapse, keep your notes close the time is near where justice will prevail.
People of Ethiopia, Unite, Upraise and Uproot the current system once and for all and protect your people and country.

33ቱ ፓርቲዎች አንድነት ፈጥረው የተቃውሞ ሰልፍ ያደርጋሉ ተባለ

February4/2014

የመግባባት አንድነትና ሠላም ማህበር (ሠላም)፤33ቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አንድነት እንዲመሠርቱ በማድረግ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሠላማዊ ሠልፍ እንዲያካሂዱ እንደሚያተጋቸው ገለፀ፡፡ የአገሪቱን ፓርቲዎች ወደ ሁለት ጐራ ለማሰባሰብ በቅርቡ የተጠራው ስብሰባ የታሰበውን ያህል አለመሳካቱን የገለፁት የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ፤በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ውይይት ለማካሄድ በመጪው የካቲት 1 ድጋሚ ስብሰባ መጥራት አስፈልጓል ብለዋል፡፡ ማህበሩ ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም በጠራው ስብሰባ ላይ ከተሳተፉት የፓርቲ ተወካዮችና ምሁራን ጋር በተደረገው ውይይት የተቃዋሚዎች የተናጠል ትግል የመንግስትን የስልጣን ዘመን እንዳራዘመ፣ ፓርቲዎችንም ለስልጣን እንዳላበቃና የህዝብን ስቃይና እንግልት እንዳሰፋ መግባባት ላይ ተደርሷል ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤የፓርቲዎች የተናጠል ሩጫ መቆም እንዳለበትም ታምኖበታል ብለዋል፡፡

በቀጣዩ ውይይት ላይ ይገኛሉ ተብለው የሚጠበቁት የየፓርቲዎቹ ተወካዮችም በዚያኑ እለት በአንድነት ለመሥራት የሚያስችል ፍንጭ መገኘቱን መነሻ በማድረግ አንድነት የመፍጠር ግዴታ አለባቸው የሚሉት አቶ ፋንታሁን፤የሚፈጠረው አንድነትም የካቲት 8 በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር ጉዳይና በሳውዲ ባሉ ዜጐች ላይ የደረሰውን ጉዳት በማሠብ፣በአዲስ አበባ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ ያደርጋሉ ብለዋል፡፡ ፓርቲዎቹ አንድነት ፈጥረው ሠልፉን ማካሄዳቸው ጫና ማሳረፍ የሚችል ተቃውሞ ለማቅረብ እንደሚረዳ ሥራ አስኪያጁ አክለው ገልፀዋል፡፡ የዛሬ ሳምንት ቅዳሜ በመኢአድ ጽ/ቤት ለግማሽ ቀን የሚደረገው የፓርቲዎች አንድነት የመፍጠር ውይይት በእውቅ ምሁራንና በማህበሩ ተወካዮች የሚመራ ሲሆን በውይይቱ ላይ ጋዜጠኞች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ተቃዋሚ ግለሰቦች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሴቶች እና ወጣቶች ተወካዮች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች ይገኙበታል ተብሏል፡፡ ፓርቲዎች ከበቀል የፀዳች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ እንዲያስረክቡና በአገሪቱ እርቅና መግባባት እንዲፈጠር ማድረግ የተነሣሁበት ዓላማ ስለሆነ በትጋት እታትራለሁ ብሏል - ማህበሩ፡፡