Wednesday, June 5, 2013

ከተቃውሞ ሰልፉ በሁዋላ በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አመራሮች እየተገመገሙ ነው

ግንቦት ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ባለፈው እሁድ ሰማያዊ ፓርቲ ያካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ በማግስቱ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ አመራሮችን እንዲሁም በፕሮፓጋንዳ መስክ ላይ የተሰማሩትን በመጥራት ዜናውን እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ግምገማ እያካሄደ መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል።

 አብዛኞቹ አመራሮች ሂስና ግለሂሳቸውን እንዲያወርዱ የተጠየቁ ሲሆን፣ የድርጅቱ አባሎች በጸረ ህዝቦች ፕሮፓጋንዳ በመወናበድ እና ለግንባሩ ርእዮተ አለም ትኩረት ባለመስጠት ድርጅቱን ከውስጥ እያዳከሙት ነው የሚል ወቀሳ ከከፍተኛ አመራሮች ተስምቷል።
ግምገማው በክልል ከተሞችም በመካሄድ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል። አብዛኞቹ ነባር አመራሮች ” በጦር ያልተፈታው ኢህአዴግ በወሬ አይፈታም” በማለት በመካከለኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አመራሮች፣ ጸረ ሰላም ሀይሎች ከሚነዙት ፕሮፓጋንዳ ራሳቸውን እንዲያቅቡ ተነግሮአቸዋል።

በግምገማው የተሳተፈ አንድ የድርጅት አባል “እንዲህ አይነት ግምገማ በድርጅቱ ታሪክ ውስጥ አጋጥሞኝ አያውቅም፣ ከእሁድ በሁዋላ ድርጅታችን ታምሷል፣ መሪዎቻችን በጣም ተበሳጭተው መግቢያ እያሳጡን ነው” በማለት ለኢሳት ተናግሯል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራ ቡድን በደቡብ ኢትዮጵያ እየተዘዋወረ የህዝብ አስተያየት በመሰብሰብ ላይ ነው።  አቶ አዲሱ ትናንት በዴቻ ወረዳ  160 ሰዎችን ሰብስበው ስለመልካም አስተዳደርና ስለሌሎች ጉዳዮች አወያይተዋል። በስብሰባው ላይ ለመሳተፍ የጠየቁ ወጣቶች ስብሰባውን እንዳይካፈሉ መደረጋቸው ታውቋል።

Tuesday, June 4, 2013

አርበኞች ግንባር በሁመራ አካባቢ በወያኔ 35ኛ ክፍለጦር ላይ ጥቃት ሰነዘረ

ነበልባሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በሉግዲና በበረከት ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀመ።

ነበልባሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በግንቦት 24-2005 ዓ.ም ከወያኔ መከላከያ ጋር በሉግዲ ባካሔደው ውጊያ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል።

Ethiopian People Patriotic Frontበግንቦት 25-2005 ዓ.ም በቀጠለው ውጊያ በሁመራ ልዩ ስሙ በረከት በተሰኘ ስፍራ ከአምባገነኑ አገዛዝ 35ኛ ክፍለጦር እና ከሚሊሻ ሰራዊት ጋር በተካሄደው ውጊያ በተከታታይ በስምንት/8/ ዙር ፋታ የለሽና እልህ አስጨራሽ ውጊያ 148 ሙት፣ 374 ቁስለኛ፣ 31 ክላሽንኮፍ፣ጠመንጃ 47 የእጅ ቦንብ ፣2 ስናይፐር፣ 3 መትረየስና የተለያዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች ማርኳል።

በእለቱ በተካሄደው ውጊያ የአካባቢው ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ባሳየው ከፍተኛ ወታደራዊ ጀብድ መደነቃቸውንና ድርጅቱ ያለውን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ብቃት ያሳየ መሆኑን ገልፀው ፣ ወጣቶችም በዚህ ሃይል ጠላት ማሽመድመድ የሚችል ድርጅት መሆኑን አስመስክሯል ሲሉ ተናግረዋል።

ለስምንት ዙር ያህል በተካሄደው ውጊያ የአገዛዙ ቅጥረኛ ጦር ቁስለኞች ወደ ዳንሻ፣ ማይካድራ፣ ሁመራ የመሳሰሉት ቦታዎች በሚገኙ የጠላት የሕክምና ተቋማት ቁስለኞችን እየጫኑ ማጓጓዝ ላይ ተጠምደው እንደዋሉና ገሚሶቹ ከፉኛ በመቁሰላቸው ሕክምና እርዳታ ሳይጀመርላቸው መሞታቸው ታውቋል።

ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በደረሰበት ድንገተኛ ጥቃት አከርካሪው የተሰበረው 35ኛ ክፍለ ጦር በድንጋጤና ፍርሃት ውስጥ ተሸብቦ በመጨነቅ ላይ በመሆናቸው የአካባቢውን ማህበረሰብ ያለስራው እየተንገላታ እንደሚገኝ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት አሁንም ቢሆን ወያኔው ለሕዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች መልስ ባለመስጠት አቋሙ የሚቀጥል ከሆነና ስለ አባይ ግድብ እያወሩ ሕዝብን ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ መግዛቴን እቀጥላለሁ የሚል ከሆነ በሁመራ ልዩ ስሙ በረከት እንዲሁም በሉግዲ በ35ኛ ክፍለ ጦርና በሚሊሻ ላይ የተወሰደው አኩሪ ወታደራዊ እርምጃ አይነቱን ቀይሮና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያስታውቃል።

በግንቦት 24 እና  25-2005 ዓ.ም በተካሄደው ውጊያ በድምሩ 192 ሙት 440 ቁስለኛ ቁጥራቸው የበዛ ተተኳሽ መሳሪያዎችን ከነትጥቃቸው በመማረክ የታሪኩ አካል የሆኑ  ተዋጊ አርበኞች እንዳሉት እኛ ለሀገራችን ኢትዮጵያና ሕዝቧ እስከ ሕይወት መስዋዕትነት ለመክፈል ፊት ለፊት በጠመንጃ አረር እየተፋለሙ እንደሚገኙና ትግሉ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚደረግ እንደመሆኑ መጠን የሁሉም ርብርብና ተሳትፎ አስፈላጊና የውዴታ ግዴታ በመሆኑ የአገራችን ችግር መፍትሔ ለመስጠት በአምባገነኑ የወንበዴ ቡድን በሆነው ወያኔ ላይ እንዝመት ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በሰስዊዘርላድ-ጄኔቭ ኢህአዴግ የጠራው የቦንድ ሽያጭ ስብሰባ “ከ ዓባይ በፊት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይገደብ!” የሚል መፈክር ባነገቡ ኢትዮጵያውያን ብርቱ ተቃውሞ ከሸፈ

ግንቦት ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ኢህዴግ -በጄኔቭ  ለ ዓባይ ግድብ ቦንድ ሽያጭ ለማካሄድ ካለፉት ሁለት ወራት ወዲህ በምስጢር ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ ከቆየ በሁዋላ በቅርቡ ለደጋፊዎቹ ብቻ የዝግጅቱን ዕለት፣ቦታ እና ሰዓት አስመልክቶ ጥሪ ያቀርባል።

ይሁንና ኢህአዴግ  መቼ እና የት ዝግጅቱን ሊያደርግ እንዳሰበ የውስጥ መረጃ የደረሳቸው በጄኔቭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጎን ለጎን የተቃውሞ ዝግጅት ሲያስተባብሩ ይከርማሉ።

ከተቃውሞ ሰልፉ አስተባባሪዎች አንዱ የሆኑት አቶ ጴጥሮስ አሸናፊ እንደገለጹት፤በስፍራው የሚገኙት  የ ኢህአዴግ ካድሬዎች ተቃውሞ እንዳይነሳ በማሰብ ዝግጅቱን ከጄኔቭ ወጣ ብሎ በሚገኝና ለትራንስፖር ፈጽሞ አመች ባልሆነ ጭር ባለ ስፍራ እንዲሆን ቢያደርጉም በ ኢትዮጵያኑ ብርቱ ተቃውሞ ሊሳካላቸው አልቻለም።

እንደ አቶ ጴጥሮስ ገለፃ ከትናንት በስቲያ  ቅዳሜ በ ኢትዮጵያ ሰ ዓት አቆጣጠር ከቀኑ 10 ሰ ዓት ጀምሮ ሊካሄድ የታሰበውን የቦንድ ሽያጭ ለመቃወም ከዙሪክ፣ከበርገን፣ከሎዛን እና ከባዝል-ከተሞች  ከ 200 በላይ ኢትዮጵያውያን  አውቶቡሶችንና ሚኒባሶችን በመከራየትና የግል መኪኖቻቸውን በማሽከርከር በዝግጅቱ ቦታ የተገኙት  አንድ ሰ ዓት በመቅደም ነበር።

የ ኢትዮጵያውያን ማህበር በስዊዘርላንድ፣ ግንቦት 7 ለፍትህ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ፣የ ኦሮሞ ነፃነት ግንባር፣የቢላል ኢትዮ-ስዊዝ ማህበር፣የዲሞክራሲያዊና የሰብዓዊ መብቶች አስተባባሪ ወጣቶች ግብረ-ሀይልና የስዊዘርላን ድምፃችን ይሰማ ኮሜቴ በጋራ በመሆን ባስተባበሩት በዚህ ሰልፍ ፦”ከዓባይ በፊት ዘረኝነት ይገደብ! በግፍ የታሰሩ ጋዜጠኞች፣የህዝበ-ሙስሉሙ መሪዎችና የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ!” የሚሉት መፈክሮች መስተጋባት የጀመሩት ገና የ ኢህአዴግ ዝግጅት ሳይጀመር ነው።

ተቃውሞው እያየለ በመምጣቱ የ ኢህአዴግ ደጋፊዎች እንደተጠበቀው ወደ አዳራሹ ሊመጡ አለመቻላቸውን የገለጹት አቶ ጴጥሮስ እስከ ምሽቱ አራት ሰ ዓት ድረስ  ራሳቸውን ተሸፋፍነውና አቀርቅረው ወደ አዳራሹ የገቡት ሰዎች ከ 30 እንደማይበልጡ ተናግረዋል።

በተቃውሞው ማየል ፕሮግራሙ ይጀመራል በተባለበት ሰ ዓት ካለመጀመሩም ባሻገር የዝግጅቱ እንግዳ የነበሩት በስዊዝ የ ኢትዮጵያ አምባሳደር እና ሌሎች የ ኢህአዴግ ባለስልጣናት ወደ ስፍራው ዝር ሳይሉ ቀርተዋል።

በስፍራው የሚገኘው የ ኢሳት ወኪል እንዳጠናቀረው ሪፖርትም፤በሰልፈኞቹ ጩኸት የተደናገጡት ጥቂት ተሰብሳቢዎች ወደፖሊስ በመደወል ተጨማሪ ሀይል እንዲመጣላቸው ባቀረቡት ተማጽኖ መሰረት የፖሊስ ሀይል ቢመጣም፣ ዝናቡ ጉሉበቱን ጨምሮ ቢወርድም፣ ኢትዮጵያውያኑ ያለ አንዳች መነቃነቅ በከፍተኛ ወኔ እና አገራዊ ስሜት ተቃውሟቸውን ቀጥለዋል።

የተቃውሞ ሰልፈኞቹ ከዚህም ባሻገር በዝግጅቱ አዳራሽ ተሰቅሎ የነበረውን ባለ ኮከብ ባንዲራ በማውረድና ፦”ኢትዮጵያውያንን የሚወክለው ባንዲራ ይሄ ነው”በማለት ትክክለኛውን የ ኢትዮጵያ ባንዲራ ሰቅለዋል።

ሰልፈኞቹ በዚህም ሳይወሰኑ   በአዳራሹ ውስጥ የጋዜጠኞችን፣የፖለቲካ እስረኞችንና የታሰሩትን የሙስሊም አመራሮች ፎቶግራፎች ለጥፈዋል።

“በኦሮሞ ነፃነት ግንባር መካከል መለስተኛ ልዩነት የተፈጠረ ቢሆንም፣ በዚህ ሰልፍ ላይ ግን ከሁለቱም ወገኖች ያሉት የግንባሩ አባላት ተገኝተው ከሁላችንም ጋር በአንድ ላይ ድምፃቸውን ማሰማታቸው በጣም ደስ የሚያሰኝና ልዩ ስሜትን የፈጠረብን ክስተት ነበር”ብለዋል-አቶ ጴጥሮስ።

ዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ የሚካሄድበት ዋዜማ መሆኑም ለሰልፈኞቹ ትልቅ ደስታን የሰጠና ተስፋን የፈነጠቀ ነበርም ብለዋል-አስባባሪው።

በ ኢትዮጵያውያኑ ብርቱ ተቃውሞ ገንዘብ የመሰብሰብ እቅዳቸው የከሸፈባቸው የ ኢህአዴግ ካድሬዎች በስተመጨረሻም ያዘጋጁትን ምግብ ሳይቀር የውጪ ዜጎችን በመጥራት በነፃ እስከመጋበዝ ደርሰዋል።

“የ አባይ መገደብ የሁላችንም ደስታ ነው፤ ዓባይ እንዲገደብ እንሻለን። ሰውን ያለ አግባብ እየገደሉና እያሰሩ በሰው ደም ላይ የሚደረግን ልማት ግን እንቃወማለን!ዓባይም ከልማት አልፎ ለፖለቲካ ንግድ መዋሉን ም ፈጽሞ አንቀበለውም! ቅድሚያ ፍትህ፤ነፃነት፣ዲሞክራሲ በአገራችን ይንገስ! ያኔ ዓባይን በጋራ ክንድ እንገነባዋለን!”ብለዋል-አስተባባሪው ስለተቃውሞ ሰልፉ ዓላማ ሲያብራሩ።

ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ መንግስት የሰጠውን ማስፈራሪያ አመራሮች እና የህግ ባለሙያዎች ውድቅ አደረጉት

ግንቦት ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-እሁድ ግንቦት25 ከፍተኛ ህዝብ የተገኘበትን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ የኢህአዴግ የጽህፈት ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን ለሬዲዮ ፋና ሲናገሩ ” የሃይማኖት አክራሪነትን አጀንዳው አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሰማያዊ የፖለቲካ ፓርቲ ጸረ ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴው ዛሬ በጠራው ሰልፍ ተጋልጧል ” ብለዋል።

ፓርቲው ያዘጋጀውን ሰላማዊ ሰልፍ ላልተፈለገ አላማ አውሎታል ያሉት አቶ ሬድዋን ፣ በሰልፉ በአብዛኛው የተንጸባረቀው የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ይፈቱ እየተባለ መስተጋባቱ ፥ ፓርቲው ህገ መንግስቱን በመጣስ በሃይማኖት እጁን መክተቱና በህግ የበላይነት አምናለሁ እያለ በፍርድ ቤት ጉዳያቸው የተያዘባቸው ሰዎች በሁካታ ይፈቱልን ማሰኘቱ ተጠያቂ ያደርገዋል ሲሉ አክለዋል።

የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ሚኒስትር ዲኤታ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማልም እንዲሁ የአቶ ሬድዋንን ንግግር የሚያጠናከር አስተያየት ለኢቲቪ ሰጥተዋል

ጉዳዩን በማስመልከት ጥያቄ የቀረበላቸው   ኢ/ር ይልቃል ጌትነት  መንግስት የሚያቀርበው የሀሰት ውንጀላ ከወደፊቱ ጉዙአቸው እንደማይገታቸው ተናግረዋል **

በእለቱ ተናጋሪ የነበሩት ዶ/ር ያእቆብ ሀይለማርያም ህዝቡ ከ8 አመታት በሁዋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀዳጀው መብት መሆኑን ገልጸው፣ ህገመንግስቱን የጣሰው መንግስት እንጅ ፓርቲው ወይም እርሳቸው አለመሆናቸውን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ዜና ደግሞ ሁለት ታዋቂ ህግ ባለሙያዎች መንግስት ያቀረበውን ውንጀላ ውድቅ አድርገውታል።

 የድምጻችን ይሰማ የሙስሊም አመራሮችን የፍርድ ቤት ጉዳይ የያዙት አቶ ተማም አባቡልጉ ሙሰሊም ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው ተቃውሞአቸውን የማሰማት መብት እንዳላቸው፣ ገልጸዋል። የእኛ ደንበኞች የህገመንግስት መብታቸው በመጣሱ አመለካከታቸውን  በተቃውሞ ማቅረባቸው መብታቸው መሆኑን የገለጹት አቶ ተማም፣ ህገወጥ የሚሆነው ሰዎች ለምን መብታችሁን ገለጻችሁ ተብለው እንዲሸማቀቁ መደረጋቸው ነው ብለዋል።

የርእዮት አለሙ አባት አቶ አለሙ ጎቤቦ በበኩላቸው ህግ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን እንደማይከለክል እና በፍርድ ቤት ላይ የሚኖረው ተጽኖ አለመኖሩን ገልጸው መንግስት ህዝቡን ለማስፈራራት እና ሀሳቡን እንዳይገልጽ ለማድረግ የወሰደው ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል::

Monday, June 3, 2013

በሽዎች የተጀመረው እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች ይሆናል!

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)
Ethiopian People’s Congress for United Struggle (Shengo)


ግንቦት ፳፭ ፣ ፳፻፭

Ethiopian People's Congress for United Struggle (Congress)June 2, 2013

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) በዛሬው እለት  በሰማያዊ ፓርቲ ጠሪነትና በተለያዩ ድርጅቶች ተባባሪነት በአዲስ አበባ ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ያለውን አድናቆትና የትግል አጋርነት በድጋሜ ይገልጣል።

ይህ በሽዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ጎሳ፣ዕድሜ፣ጾታና እምነት ሳይነጥላቸው በአንድ ሆነው የሀገራችንን ህብር በሚያንጸባርቅና በታላቅ ሥነስርዓት የጋለ ስሜታቸውን በይፋ የገለጡበት ህዝባዊ ሠልፍ  ፣ በሕዝባችን ላይ የተጫነው የፍርሀት ድባብ እየተሰበረ መምጣቱን የሚያመለከት ታላቅ እርምጃ ነው።

ይህ  እጅግ ብዙ ወጣቶችን ያሳተፈ፣ ስሜት ቀስቃሽና ታላቅ ወኔ የታየበት የህዝብ ቁጣ፣ ህዝባችን ለዓመታት የተጫነበትን የግፍ ቀንበር ሊሸከም የሚችልበት ጀርባ እንደሌለው በግልጥ ያሳየበት ቀን ነው።

ይህ ስላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ መሰረታዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ እንዲከበር፣ ጎሳ ተኮር የህዝብ ማፈናቀል እንዲያበቃ፣ የኑሮ ውድነት እንዲወገድ፣ በፖለቲካ ጉዳይ በእስር ላይ ያሉ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ነጻ ጋዜጠኞች  በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣ የመደራጀት መብት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር፣ በየሃይማኖቶች የውስጥ ጉዳይ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት እንዲቆምና የታሰሩት የሙስሊሙ ተወካዮች እንዲፈቱ በመጠየቅ የሀገሪቱን ሕዝብ ብሶት በሚገባ  አንፀባርቋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) እነዚህና ሌሎች መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች ባሰቸኳይ እንዲመለሱና  ከዚህም አልፎ የአምባገነንነትና የጎጠኛ ስርዓት አክትሞ ህዝብ በምርጫ የራሱን መንግሥት የመመስረት መብቱ እንዲረጋገጥ ለማስቻል ከተለያዩ ኢትዮጵያዊ ሀይሎች ጋር ተባብሮ ትግሉን እንደሚቀጥል አሁንም ያረጋግጣል።

በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን፣ ከሀገር ውጭም፣ ዓለምአቀፉ ህብረተሰብ፣ ያለውን ሁኔታ ይበልጥ ተረድቶ፣ በመፍትሄ ፍለጋው አንጻር፣ አወንታዊ ሚና እንዲጫወት፣ ሸንጎው የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን አጠናክሮ ይቀጥላል።

የተባበረ የህዝብ ትግልን ሊመክት የሚችል ምንም ሀይል የለምና፣ መብታችንን ለማሰከበር ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥል። ዛሬ የተካሄደው ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ፣ ለተከታታይ ሕዝባዊ ንቅናቄዎች በር ከፋች እንጂ መደምደሚያ እንደማይሆን ሸንጎው ይተማመናል።

ሰላማዊው ትግሉ እንዳይቀጥል የሕወሓት/ኢሕዴግ አሸባሪ አገዛዝ ብዙ ጥረት እንደሚያደርግና ደፍረው በወጡትና ባዘጋጁት ላይም ስበብ እየፈጠረ የሽብር ክንዱን ከመሰንዘር ስለማይመለስ ከወዲሁ ነቅቶ መጠበቅና በጋራ መከላከል የሚቻልበት ዘዴ እንዲፈጠር፣ ተደናግጦና በርግጎም የተጀመረው የነጻነት ጉዞ እንዳይከሽፍና  እንዳይቆም  ሸንጎ ያሳስባል። ሁሉም ዜጋ  የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግም ጥሪ ያደርጋል።

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በቆራጥ ልጆቿ ትግል ተከብረው ለዘላለም ይኖራሉ

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ(ሸንጎ)

Sunday, June 2, 2013

Thousands march for rights in rare Ethiopia protest

(Reuters) - About 10,000 Ethiopians staged an anti-government procession on Sunday in the first large-scale protest since a disputed 2005 election ended in street violence that killed 200 people.
The demonstrators marched through Addis Ababa's northern Arat Kilo and Piazza districts before gathering at Churchill Avenue in front of a looming obelisk with a giant red star perched on top, a relic of Ethiopia's violent Communist past.
Some carried banners reading "Justice! Justice! Justice!" and some bore pictures of imprisoned opposition figures. Others chanted, "We call for respect of the constitution".
A few police officers watched the demonstration, for which the authorities had granted permission.

"We have repeatedly asked the government to release political leaders, journalists and those who asked the government not to intervene in religious affairs," said Yilekal Getachew, chairman of the Semayawi (Blue) Party which organized the protests.
He said the demonstrators also wanted action to tackle unemployment, inflation and corruption.
"If these questions are not resolved and no progress is made in the next three months, we will organize more protests. It is the beginning of our struggle," he told Reuters.
Government officials were not immediately available for comment.
ANTI-TERRORISM LAW
Ethiopian opposition parties routinely accuse the government of harassment and say their candidates are often intimidated in polls. The 547-seat legislature has only one opposition member.
Though its economy is one of the fastest-growing in Africa, Ethiopia is often criticized by human rights watchdogs for clamping down on opposition and the media on national security grounds, a charge the government denies.
Critics point to a 2009 anti-terrorism law that makes anyone caught publishing information that could induce readers into acts of terrorism liable to jail terms of 10 to 20 years.
Last year, an Ethiopian court handed sentences of eight years to life to 20 journalists, opposition figures and others for conspiring with rebels to topple the government.
More than 10 journalists have been charged under the anti-terrorism law, according to the Committee to Protect Journalists, which says Ethiopia has the highest number of exiled journalists in the world.
Muslims, who form about a third of Ethiopia's mostly Christian population, staged mosque sit-ins in 2012, accusing the government of meddling in religious affairs and jailing their leaders.
Ethiopia, long seen by the West as a bulwark against radical Islamists in neighboring Somalia, denies interfering, but says it fears militant Islam is taking root in the country.
(Reporting by Aaron Maasho; Editing by George Obulutsa and Alistair Lyon)

Thursday, May 30, 2013

የግንቦት 7 ንቅናቄ 4ኛ ጉባኤ ህዝቡ ወደ ትግሉ እንዲቀላቀል ጥሪ አቀረበ

         
የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነት፣ የዲሞክራሲ ንቅናቄ 4ኛ ጉባኤ ከግንቦት 11 – 19/2005 አ/ም በበርካታ ወቅታዊ፣ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት እና የድርጅቱን አዲስ ም/ቤት በመምረጥ ወያኔን በማስወገድ ረገድ ሊከተል የሚገባውን ጠቋሚ አቅጣጫዎችንና ውሳኔዎችን ከተሳታፊው በመውሰድ ወሳኝ የሆነ ውይይት አድርጓል።

ንቅናቄው ከተለያዩ አለማት በአባላት የተወከሉ ጉባኤተኞች እና በተለያዩ የስራ ክፍል የሚገኙትን የድርጅቱን አባላት ያሳተፈ፤ ከዚህ በፊት ከተደረጉትም ጉባኤዎች እጅግ የላቀ አባላት የተገኙበት ነበር።

ጉባኤው የነበረውን የም/ቤት ሪፖርት፣ የስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የኦዲትና ማናጅመንት ኮሚሽን፣ የግልግልና ዳኝነት ኮሚቴን እና የፋይናንስ ሪፖርቶችን በማዳመጥ ጥልቅ የሆነ ወይይቶች አደርጓል።

የግንቦት 7 ንቅናቄ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች፤ ደርጅቱ የጀመረውን ወያኔን የማስወገድ ትግል በየትኛውም አቅጣጫ አስፈላጊ ሆኖ የታመነበትን ማናቸውም መንገድ ሁሉ በመጠቀም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የዘረኝነትን ስርአት ድባቅ መምታት፤ አልፎም ዘላቂ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት አስቸኳይና ማንም አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ግዴታው አድርጎ መውሰድ ያለበት አጣዳፊ ስራ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰላም አየርና የዲሞክራሲ ጮራ ሁሌም የሚፈነጥቅባት፣ ህዝብ ካለፍርሃትና ሰቀቀን ወጥቶ የሚገባባት፣ ህዝብ በነጻነት የፈለገውን ፓርቲ የሚመርጥበት፣ የሚያወርድበት፣ ስልጣን የህዝብ መሆኑን የሚረጋገጥበት፣ የመንግስት አካላት ለህዝብ ተጠያቂ የሚሆኑበት፣ ነጻ ሚዲያ ለመልካም አስተዳደር ግንባታ የሚያገለግልበት፣ ፍትህ ለሁሉም በእኩል የሚሰጥበት፣ ዜጎች በየትኛውም የሀገሪቱ ክልሎች የመኖር፣ ሀብት የማፍራት፣ ቤተሰብ የመመስረት፤ ከቦታ ወደ ቦታ ያለምንም ገደብ የሚንቀሳቀሱበት መብት እንዲኖራቸው፣ እና የሃይማኖት ነጻነት ይኖረን ዘንድ የድርጅቱ ጉባኤተኞች ሙሉ መሰዋእት ለመክፈል ዝግጁዎች ነን ሲሉ በድጋሚ ቃል በመግባት መራራ የሆነውን ትግል እጅ ለእጅ ተያይዞ ተራራውን ለመውጣት እና ለማቋረጥ ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል።

ከ4ኛ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ጉባኤተኛው የግንቦት 7ን 5ኛ አመት ምስረታ ታሪካዊ ቀን አስቦ ውሏል። በዚህ በግንቦት 7, 1997 ቀን የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ተሳትፎ ፍትህ፣ ነጻነትና ዲሞክራሲ በሀገሪቱ ይሰፍን ዘንድ ለዘመናት ተጭኖት የነበረውን ጫና ተቋቁሞ የወያኔን ስርአት በድምጹ የጣለበት ልዩ ቀን ነበር። ግንቦት 7, ሁሌም በታሪክ የሚዘከር ልዩ እለት ነው።

ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያዊ ትውልድ በግንቦት 7 ያሳየውን ልበሙሉነት፣ ጀግንነት፣ መሰዋእትነት፣ አንድነትና ወንድማማችነት ለዘለአለም ሲታወስ ይኖራል። ይህንኑ በ97 የተጀመረው የትግል ፍሬ፤ ውጤት ያፈራ ዘንድ አስፈላጊ ያላቸውን ትግሎችን እያደረገ እንደሆነ ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነት፣ የዲሞክራሲ ንቅናቄ 5ኛ አመቱን ከአባላቱ ጋር ሆኖ ሲዘክር ተወያይቷል። ይህም ታሪካዊ የህዝብ ድል ቀን፤ በጠመንጃ ሃይል የነጠቀውን ወያኔን ለማስወገድ እና የህዝብን ድምጽ ለማስመለስ ድርጅታችን ማናቸውንም መንገድ በመጠቀም የሚያደርገውን የትግል ጅማሮ ግብ ለመምታት አሁን ከአለንበት በተሻለ በመጠናከር መሆኑንም ስምምነት ተደርሷል። ድርጅታችን ካለፈው ጉባኤ ጀምሮ ድርጅቱ ያደረገውን እንቅስቃሴ በስፋት ገምግሞ፤ በስራ ሂደት የታዩ ድክመቶችን አፍረጥርጦ ተወያይቶ፤ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች ይበልጥ የሚጎለብቱበትን ሁኔታ ተመልክቶ፤ በድርጅቱ የእስትራቴጂ አካሄድ ላይ የተወሰኑ ማሻሻያዎችን አድርጎ፤ እነኝህን የእስትራቴጂ አቅጣጫዎች በተቀላጠፈ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ወሳኝ የመዋቅር ለውጦችን አጽድቆና ይህን አዲስ መዋቅር የሚያስፈጽሙ ያመራር አባላትን መርጦ፤ በከፍተኛ የጓዳዊ መንፈስና ልዩ በሆነ የትግል ወኔ ጉባኤውን በድል አጠናቋል::

በመሆኑም ግንቦት 7፣ በግንቦት 7 የገባውን ቃል ኪዳን ዛሬም ህያው መሆኑን ሲያረጋግጥና ትግሉ ከመቼውም በበለጠ ጽናትና ቁርጠኛነት እንደሚገፋበት ቃል ሲገባ፣ የሀገራችን ህዝብ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ; አዛውንት፣ ወጣት፣ ጾታ፣ ሃይማኖት፣ ዘር ቀለም ሳይለያችሁ በግንቦት 7/ 1997 የተሰረቀውን፣ የተነጠቅነውን የህዝብ መንበረ-ድምጽ ስልጣን ወደ ትክክለኛ ባለቤቱ እንዲመለስ የምናደረግውን የትግል ጉዞ ትቀላቀሉ ዘንድ ጥሪያችን ይድረሳችሁ!
የሀገራችን ወጣቶች ሆይ፡ ለነጻነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ቱርፋቶች መሰዋእት ሆናችሁ መሰዋእትነታችሁ በጥቁር ህዝብ የኢትዮጵያ ታሪክ ገድል ውስጥ ለዘላለም ተከትቦ ይቀመጥ ዘንድ ኢትዮጵያዊ የሞራል ግዴታ አለባችሁ፡፡ ግንቦት 7 ትግሉን ጀምሯል። ኑ ተቀላቀሉ!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

የአሜሪካ የህግ ባለሙያዎችና አኢጋን በኅብረት ስራ ጀመሩ!

ዓርብ የፖለቲካና የሙስሊም እስረኛ ጠበቆችን ያነጋግራሉ

                       
በኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በተመለከተ የአሜሪካን የህግ ባለሙያዎች ማህበር (ABA – American Bar Association) ሙሉ በሙሉ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ስራ አርብ እንደሚጀምር ተገለጸ። አዲስ አበባ ካሉ የፖለቲካና የሙስሊም ወገን እስረኞች ጠበቆች ጋር የመጀመሪያ ስብሰባ አርብ ግንቦት 23፤2005ዓም ያደርጋሉ። አቶ ኦባንግ ሜቶ የተረሱ እስረኞች ጉዳይም እንደሚካተት ጠቅሰው በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ ለታሰሩ ዜጎች ጥብቅና የቆሙ ካሉ የአዲሲቷን ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ በቀጥታ እንዲገናኙ ጥሪ አቅርበዋል።
 
(ABA) በሚል ስያሜ የሚታወቀውና ከተቋቋመ 135ዓመታትን ያስቆጠረው የአሜሪካ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ከ400 ሺህ በላይ የህግ ባለሙያ አባላት አሉት። ይህ በአሜሪካ ትልቅ የተባለ ማህበር በግፍ ለሚሰቃዩ ኢትዮጵያዊያን እስረኞች ድጋፍ ለማድረግ የወሰነው የአኢጋን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ በይፋ የድጋፍ ጥያቄ ባቀረቡ በቀናት ውስጥ ሲሆን፣ በጋራ በተከናወኑ ንግግሮችና የሰነድ ውይይቶች በወር ጊዜ ውስጥ ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል።
 
aba
ከወር በፊት በተካሄደ የማህበሩ ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ንግግር እንዲያደርጉላቸው በተጋበዙት መሰረት አቶ ኦባንግ ህግን እየተንተራሰ ዜጎችን በቁም እስርና በወህኒ ቤት እያሰቃየ ስላለው የኢህአዴግ አገዛዝ በስፋት ባስረዱበት ወቅት ማህበሩ እሳቸው ከሚመሩት ድርጅት ጋር በትብብር ለመስራት ፈቃዱን አሳይቶ እንደ ነበር አቶ ኦባንግ ለጎልጉል ተናግረዋል።
 
በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ኢህአዴግ ህግን ከለላ በማድረግ በዜጎች ላይ የሚፈጽመውን ግፍና ወንጀል፣ ለአፈና ተግባሩ ማስፈጸሚያም የጸረ ሽብርተኝነትን፣ የመያዶችን፣ ወዘተ ህጎችን በማውጣት ዜጎችን ለወህኒ ቤትና ለቁም እስር፣ ለስደት፣ ለስቃይ መዳረጉን፣ የፍትህ አካላቱን ህግን በሚያከብሩና ፍትህ በሚያስፈጽሙ ገለልተኛ አካሎች ሳይሆን ራሱ በመሠረተው ተቋም እያመረተ የሚጠቀምባቸው የፖለቲካው መሳሪያዎቹ ስለመሆናቸው፣ በመዘርዘርና ማስረጃ በማጣቀስ አቶ ኦባንግ ለጉባኤው መናገራቸውን አመልክተዋል።
 
ቀደም ሲል ጀምሮ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የስራ አስፈጻሚዎች የሚታወቁትም ሆነ ሚዲያው የዘነጋቸው ዜጎች ጉዳያቸው ዓለም ዓቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ በያቅጣጫው እየተደረገ ካለው የተለያየ  ጥረት በተጨማሪ ሲመክርበት የነበረው ጉዳይ እንደሆነ በመግለጽ አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ ኦባንግ “ተጽዕኖ ሊፈጥሩ የሚችሉት አካላት በራሳቸው ሰዎች በቂ መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ ታላቅ ተግባር ነው። ድርጅታችን እንደ ስኬት ይቆጥረዋል። ዓርብ በዝርዝራችን ካገኘናቸው የታዋቂ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪ ጠበቆች ጋር የስካይፕ ስብሰባ ይካሄዳል። በቀጣይ አገር ቤት በመሄድ ባመቻቸው መንገድ ስራቸውን ያከናውናሉ” ብለዋል።
በአሁኑ ጊዜ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ የሙስሊሙን ህብረተሰብ ጥያቄ በማንሳታቸው የታሰሩት ወገኖች፣ ወዘተ ጠበቆች ጋር በስካይፕ ንግግር እንደሚደረግ አቶ ኦባንግ አስታውቀዋል። እስከዛሬ ጆሮ ያልተሰጣቸው ወገኖች ጉዳይ አደባባይ ከማውጣት በተጨማሪ የጋራ ንቅናቄው ባቋቋማቸው ግብረኃይሎች አማካይነት ወደ ህግ የሚሄዱ፣ ሌሎች አብረው መስራት የሚፈልጉ አካላት የሚያቀርቧቸውን አገራዊ ፋይዳ ያላቸውን ጉዳዮች በአገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ክስ መስርቶ ለመሟገት ማህበሩ ዝግጁ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አስፈላጊውን የህግ ድጋፍ የሚፈልጉ ድርጅቶችም ሆኑ ግለሰቦች ጥያቄያቸውን ለጋራ ንቅናቄው ማቅረብ ይችላሉ” ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
 
ማህበሩ መንግስትን የሚያማክሩ፣ የሚመክሩ፣ ፖሊሲ በማርቀቅ ስራ ላይ የተሰማሩ ታዋቂ የህግ ባለሙያዎች፣ ለዓለም ዓቀፍ ሚዲያና ኔትወርኮች ቅርበት ያላቸውና ተሰሚነታቸው የጎላ በመሆኑ እንዲህ ካሉ አካላት ጋር በጨዋነት መስራት በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ለማስተጋባት መልካም አጋጣሚ ማመቻቸት እንደሆነም አቶ ኦባንግ አመልክተዋል።
 
“… ኢህአዴግ በስደተኛነት ስም ደጋፊዎቹን በስርዓቱ የተገፉ በማስመሰል የሃሰት ማስረጃ እያስጨበጠ  በአሜሪካ፣ በካናዳና በተለያዩ የምዕራብ አገራት ያሰማራቸውና በተቀነባበረላቸው መረጃ የስደት መኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ ስደተኛውን እንዲሰልሉና ለሥርዓቱ እንዲሰሩ እያደረገ መሆኑ፤ በተለያዩ አገራት በገቢር የተያዙ መረጃዎችና ዋቢ ክስተቶች መኖራቸውን የተረዳው የባለሙያዎቹ ማኅበር ጉዳዩን በጥልቀት እንደሚያየውና ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል በመጠቀም ከአኢጋን ጋር እንደሚሰራ ከሌሎች ማኀበራት ጋር በመሆንም በተለይ በምዕራቡ ዓለም የተሰገሰጉትን አስመሳይ ስደተኞች ወደ ፍትህ የማምጣቱ ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ለድርጅታቸው አረጋግጠዋል” በማለት ከዚህ ቀደም ለጎልጉል ስለተናገሩት አስተያየት እንዲሰጡ አቶ ኦባንግ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
 
“ኢህአዴግን የሚደግፉ ዜጎችም ቢሆኑ ለጋራ ንቅናቄያችን ልጆቹ ናቸው” በማለት አስተያየታቸውን የጀመሩት አቶ ኦባንግ “ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ጉዳይ ላይ ምስጢረኛ ለመሆን እገደዳለሁ። አንድ ነገር ለማስታወስ ያህል ግን ምዕራባውያን አሠራራቸው መጭበርበሩን ካረጋገጡ ምህረት የላቸውም። ከሰብአዊነትም አንጻር ቢሆን አገሩ መኖር ያልቻለን ዜጋ ስደት አገር ድረስ እየተከታተሉ ማሳደድ በየትኛውም መስፈርት ተቀባይነት የለውም። በህግም አይፈቀድም። እንደዚህ ካሉት ጋር የሚተባበሩ አገሮችን ህግ ፊት በማቆም በህግ ስለፍትህ እንከራከራል” የሚል መልስ ሰጥተዋል።
 
ABA የሚባለው የህግ ባለሙያዎች ማህበር ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት ሲያከብር ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙት አቶ ኦባንግ ሜቶ በርካታ ጉዳዮችን በማንሳት ድጋፍ ጠይቀው አዎንታዊ ምላሽ እንዳገኙ፣ ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል። አቶ ኦባንግ እንደሚሉት አርብ የሚደረገው ንግግር የድጋፉና አብሮ የመስራቱ ሂደት መጀመሪያ ነው። ሥራው ጊዜ የሚወስድና እልህ የሚያስጨርስ መሆኑን ሁሉም እንዲያስተውለውና ፈጣን ውጤት በመጠበቅ ቶሎ ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ ሁሉም ዜጋ አለኝ የሚለውን መረጃ ለጋራ ንቅናቄው በመላክ ትብብሩን እንዲቀጥል ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ኮለኔል ጎሹ ወልዴ እና ዶር ታዬ ወ/ሰማያት ወዴት ገቡ? ዛሬ ካልወጡሰ መቼ?በሎሚ ተራ

ዝነኛውና የማይጠገበው ድምጻዊ (ዶ/ር) ጥላሁን ገሠሠ፤ ሲያንጎራጉር፤ እንዲህ ብሎ ነበር፤
“ጩኸቴን ብትሰሙኝ ፤ ይኸው አቤት አቤት እላለሁ በደል ደርሦብኝ እጮሃለሁ ብያለሁ”

እያለ ያንጎራጎረውን እኔም አቤት አቤት የ ( የመሪ ያለህ!!! ) በዪ እኔም እጮሀለሁ። ምንም እንኳን ሰለኮነሬል ጎሹም ሆነ ሰለ ዶክተር ታዬ ታላቅ ሰራና አገር ወዳድነታቸው አገር የሚያወቀው ያደባባይ ሚሰጥር ቢሆንም ቅሉ፤ ሰሞኑን ግን የተለያዩ የሀገርኛ ጉዳይን የሚያሳዩ ቪዲዩዎችን ሰመለከት ድንገት የኮነሬል ጎሹን ብዙዎችን ያሰደነቀና ያኮራ ሃገር አቀፍ የጥብቅና ንግግር (On the fate of Ethiopia and Eritrea’s Referendum) አየሁና በቁጭት ምን ተብሎ፤ ማን አሰከፍቶት ይሆን ኮነሬሉ ጥግ የያዙት ? ዶክተር ታዬ ወልደሰማያትሰ ? የት ገቡ ? በማለት በቁጭት ለመጠየቅ ብዕሬን አነሳሁ።

 መቼም እንዲህ ያለውን አንገብጋቢ ሃገራዊ ጥያቄ የሚጠይቁ በርካታዎች እንደሚሆኑ ባምንም ጥቂቶች ደግሞ የ ምርጫ 97 ቱን ምሳሌ በማድረግ የሞተ ዘመድ የለውም ወይ? ይኸ ሰው ምን ነካው የሚሉ እንደማይጠፉም አምናለሁ። መልሴ ግን የሞቱ ዘመዶች በርካቷች አሉኛ፤ ተሰፋዪ ግን አይሞትም።ተሰፋ ላንድም ሰከንድ አጥቼ አላውቅም ነው ።

እንዲህ አይነቱ ጥያቄ አገራችን የምትገኝበትን የፖሎቲካ ሂደትና ቀውሰ በሰፊው እንድንጠይቅና ከሰኸተታችንም ታርመን ይቅርም ተባብለን፤ በሃገር ጉዳይ እኔ ማን ነኝ ? ምንሰ ማድረግ ይጠበቅብኛል ? የሚለውን ጥያቄ በቅንነት በመጠየቅ አንተ ትብሰ፤ አንቺ ትብሸ በመባባል እንደገና እጅ ለእጅ ተያይዝን አገራችን እንድትገባበት ከተቆፈረላት ጥልቁ ጉድጓድ የማውጣት አገራዊ ግዴታ አለብን በዬ አምናለሁ።

ከገጠመን እና ከተጋረጠብን የፖሎቲካ ውጥንቅጥ አኳያሰ እባክህ፤ እባክሽ ያሰፈልጋል ወይ ? ብቃት ያላቸው የፖሎቲካ መሪዎችሰ እባካችሁ እሰኪባሉ መጠበቅ አለባችው ወይ ? በሚል የተለያዩ እሣት የሚተፉ እንጉርጉሮዎች ከየጎራው ሊነሱ እንደሚችሉ የሚጠበቅ ቢሆንም ከተጋረጠብን ከፍተኛ አደጋ ባሻገር ምንሰ ብናደርግ አገር ትዳን እንጂ ነው መልሴ።

 ሥለዚህ ሰለጠንካራ የፖሎቲካ አመራር ብቃታቸውና፤ ሰራቸው በርካታ አገር ወዳዶች የሚመሰክሩላቸውን ጠንካራ መሪዎች ዳግም ወደ ፈጠጠው የትግል ጎዳና እንዲመጡ የማይደረግበት ምክነያት ምንም ሊኖር አይችልም። እነ ኮነሬል ጎሹንም እነ ዶክተር ታዬ ወ/ሰማያትንም ሌሎችም አሉ የሚባሉትን ከየ አካባቢያችን ውጡ፤ አገራችን ኢትዮጲያ ትጮሃለች፣ የመሪ የለኸ እያለችም ትጣራለች ብለን የማውጣት ሃገራዊ ግዴታ አለበን። እከሌ ከከሌ ሳንል ጩኸታችንን እናሰማና አገራችንን ተባብረን ከውድቀት እናድን።

“ይሄ – መሪ ትግሉ ይወልዳል የሚለውም ባዶ ጩኸታችን ለ 22 አመት ወልዶ አላሳየንም እና ሁላችንም ቆም ብለን እናስብ፡
የሚዲያ ክፍሎችም በሙሉ፤- እነ ቪ. ኦ. ኤም፣ ዶቼ ቬሌም ፤ እሣትም፣ ሌሎች ሚዲያዎች ሁሉ ካሜራችሁን ወደ አራቱም ማዕዘናት አዟዙሩት ፤ምክነያታቸውንም አሰሙን እያልኩ ጩኸቴን ብትሰሙኛ እላለሁ። በቸር ይግጠመን!!

ESAT Daily News - May 29,2013 Ethiopia

Ethiopian Satellite Television (ESAT) ESAT is the first independent Ethiopian May 29, 2013


 

Wednesday, May 29, 2013

Ginbot 7 holds annual Congress; makes decisions

ESAT NEWS
MAY 28, 2013

Ephrem Madebo, the Public Relations Head of the Ginbot 7 Movement, told ESAT that the Movement held its fourth annual congress for the past four days and has analyzed its activities of the past two years and also activities since its formation.

He said, the Movement’s audit report showed the Movement “did not achieve the goal that it set out to at the beginning”.

Ephrem also stated that the Movement had made basic structural changes.
ESAT will air the full interview that it conducted with the Public Relations Head in the coming days.

Grenade explosion in injures many in Central Ethiopia

ESAT  NEWS May 28, 2013

Six people were injured when a grenade exploded in Sora Cafeteria, Gundomeskel city, Dera Woreda of Northern Shewa, Ethiopia. Sources in the town told ESAT that three of the victims have been critically injured and are being treated in Fiche Hospital while another one is receiving treatment in a local health center. One of the injured is a policeman; another is a businessman while the other two are farmers.

Mesfin, the Head of the Wordea Security, said the cause of the explosion was personal disagreement between those involved.

Meanwhile, after ESAT reported few months ago that an official of the same Woreda had forced his wife to perform humiliating acts on her husband’s genitals and had also mischarged after being beaten by the butt of a riffle, government owned media have recently travelled to the area and also reported the incident by speaking with the victim. ESAT has learnt that the residents of the area and the victim had explained in detail what happened to the government journalists. However, the journalists that have been sent to the location under the order of the Minister of Government Communications, Bereket Simon, have not revealed their reports so far.

The Security Head of the Woreda said that all the evidences on the suspect have been gathered and they are waiting for the court’s verdict. The Head said the suspect committed the acts due to personal reasons. The suspect committed the acts after refusing to hand over his weapon. The victim has been in hospital and is currently said to be in a stable condition.

Tuesday, May 28, 2013

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ፣ ሰላማዊ ትግላችን ይቀጥላል!

ሰላማዊ ትግላችን ይቀጥላል!!!

Addis Ababa, Ethiopia a call for demonstrationሰማያዊ ፓርቲ በመንግስት የሚፈፀሙ ህገ ወጥ ድርጊቶች፣ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እንዲቆሙና የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰድባቸው ለመንግስት አካላት በተለያዩ ጊዚያት ጥሪ ቢያቀርብም ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ ጥሪውን ከፍ ባለ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ለማሰማት በወሰነው መሰረት ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ጥቁር ልብስ በመልበስ እንዲሁም ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም ደግሞ በአፍሪካ ሕብረት ዋና ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ተቃውሞውን ለመግለጽ ጥሪ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡

በዚሁም መሰረት ዜጎች በሐገር ውስጥና ከሐገር ውጭ ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ጥቁር ልብስ በመልበስ መንግስት በሚፈፅማቸው ሕገ ወጥ ድርጊቶች ላይ ያላቸውን ተቃውሞ አሳይተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በአንዳንድ አባላቶቻችን ላይ ወከባና እስር ደርሶባቸዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱን የዜጎችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በመጋፋት የተፈፀሙ ድርጊቶችን እንቃወማለን፤ የታሰሩትም በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡

ግንቦት 17 ቀን ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ሕብረት ዋና ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሊደረግ የታቀደውን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ለሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ ሰልፉ የሚደረግ መሆኑን የማሳወቂያ ደብዳቤ ፓርቲው ቢያደርስም የቢሮው ኃላፊና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ደብዳቤአችንን አንቀበልም ብለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንደዚህ አይነቱን ሕገ ወጥ አሰራር በማውገዝ ሰልፉን ከማድረግ የማይመለስ መሆኑን በመግለጫ ለሕዝብና ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቋል፡፡

 በመጨረሻም የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ በአዋጁ መሰረት የሰላማዊ ሰልፉ የሚደረግበትን ቀንና ቦታ እንዲለወጥ በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት ሁለታችንም አካላት ባደረግነው ድርድር ሰልፉ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲሆንና የሰልፉ መነሻ ቦታ የፓርቲው ፅ/ቤት መድረሻ ቦታ ኢትዮ-ኩባ አደባባይ ወይም ጥቁር አንበሳ ዋናው ፖስታ ቤት ፊለፊት እንዲሆን ተወስኗል፡፡

በዚሁም መሰረት፡-

1ኛ. ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 29 ቀን 2005 ዓ. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የተጠቀሱት ጥያቄዎች እንደተጠበቁ መሆናቸውንና የግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍም ዋና ዋና ጥያቄዎች መሆናቸውን፣

2ኛ. ለረጅም ጊዜ ያለ ህግ ተነፍገን የቆየነውን ሃሳባችንን በሰላማዊ ሰልፍ የመግለፅ መብት በትግላችን ያረጋገጥን በመሆኑ ህዝብ በንቃት እንዲሳተፍበትና በሰልፉ ላይ የሚቀርቡ ጥያቄዎች በሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙ ማሳሰብ ይቻል ዘንድ ሁላችንም የዜግነት ድርሻችንን እንድንወጣና ለሰልፉ መሳካት በምንችለው አቅም ሁሉ አስተዋፅኦ እንድናደርግ ጥሪ የምናቀርብ መሆኑ፣

3ኛ. ሰማያዊ ፓርቲ ላቀረበው ሰላማዊ ታቃውሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና ዜጎች ላደረጋችሁልን ድጋፍ ፓርቲው ምስጋናውን ማቅረብ የሚፈልግ መሆኑንና የፓርቲያችንን ጥሪ ለህዝቡና ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲዳረስ መገናኛ ብዙሃን እና የማህበራዊ ድረ-ገፅ ተጠቃሚዎች ያደረጉት አስተዋፅዖ እጅግ የሚያስደንቅና የሚያስመሰግን መሆኑን ፣
እየገለፅን አሁንም ፓርቲው ያነሳቸው ጥያቄዎች መመለስ አላባቸው ብሎ የሚያምን የፖለቲካ ፓርቲ፣ የሲቪክ ማህበርና ዜጎች በሰልፉ እንዲሳተፉ ፓርቲያችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም

 አዲስ አበባ
Photo: ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ<br /> ሰላማዊ ትግላችን ይቀጥላል!!!<br /> ሰማያዊ ፓርቲ በመንግስት የሚፈፀሙ ህገ ወጥ ድርጊቶች፣ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እንዲቆሙና የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰድባቸው ለመንግስት አካላት በተለያዩ ጊዚያት ጥሪ ቢያቀርብም ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ ጥሪውን ከፍ ባለ የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ለማሰማት በወሰነው መሰረት ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ጥቁር ልብስ በመልበስ እንዲሁም ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም ደግሞ በአፍሪካ ሕብረት ዋና ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ተቃውሞውን ለመግለጽ ጥሪ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡<br /> በዚሁም መሰረት ዜጎች በሐገር ውስጥና ከሐገር ውጭ ከግንቦት 15 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ጥቁር ልብስ በመልበስ መንግስት በሚፈፅማቸው ሕገ ወጥ ድርጊቶች ላይ ያላቸውን ተቃውሞ አሳይተዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በአንዳንድ አባላቶቻችን ላይ ወከባና እስር ደርሶባቸዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱን የዜጎችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በመጋፋት የተፈፀሙ ድርጊቶችን እንቃወማለን፤ የታሰሩትም በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡<br /> ግንቦት 17 ቀን ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ሕብረት ዋና ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሊደረግ የታቀደውን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ለሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ ሰልፉ የሚደረግ መሆኑን የማሳወቂያ ደብዳቤ ፓርቲው ቢያደርስም የቢሮው ኃላፊና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ደብዳቤአችንን አንቀበልም ብለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እንደዚህ አይነቱን ሕገ ወጥ አሰራር በማውገዝ ሰልፉን ከማድረግ የማይመለስ መሆኑን በመግለጫ ለሕዝብና ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቋል፡፡ በመጨረሻም የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ በአዋጁ መሰረት የሰላማዊ ሰልፉ የሚደረግበትን ቀንና ቦታ እንዲለወጥ በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት ሁለታችንም አካላት ባደረግነው ድርድር ሰልፉ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲሆንና የሰልፉ መነሻ ቦታ የፓርቲው ፅ/ቤት መድረሻ ቦታ ኢትዮ-ኩባ አደባባይ ወይም ጥቁር አንበሳ ዋናው ፖስታ ቤት ፊለፊት እንዲሆን ተወስኗል፡፡ በዚሁም መሰረት፡-<br /> 1ኛ. ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 29 ቀን 2005 ዓ. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የተጠቀሱት ጥያቄዎች እንደተጠበቁ መሆናቸውንና የግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍም ዋና ዋና ጥያቄዎች መሆናቸውን፣<br /> 2ኛ. ለረጅም ጊዜ ያለ ህግ ተነፍገን የቆየነውን ሃሳባችንን በሰላማዊ ሰልፍ የመግለፅ መብት በትግላችን ያረጋገጥን በመሆኑ ህዝብ በንቃት እንዲሳተፍበትና በሰልፉ ላይ የሚቀርቡ ጥያቄዎች በሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙ ማሳሰብ ይቻል ዘንድ ሁላችንም የዜግነት ድርሻችንን እንድንወጣና ለሰልፉ መሳካት በምንችለው አቅም ሁሉ አስተዋፅኦ እንድናደርግ ጥሪ የምናቀርብ መሆኑ፣<br /> 3ኛ. ሰማያዊ ፓርቲ ላቀረበው ሰላማዊ ታቃውሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትና ዜጎች ላደረጋችሁልን ድጋፍ ፓርቲው ምስጋናውን ማቅረብ የሚፈልግ መሆኑንና የፓርቲያችንን ጥሪ ለህዝቡና ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲዳረስ መገናኛ ብዙሃን እና የማህበራዊ ድረ-ገፅ ተጠቃሚዎች ያደረጉት አስተዋፅዖ እጅግ የሚያስደንቅና የሚያስመሰግን መሆኑን ፣<br /> እየገለፅን አሁንም ፓርቲው ያነሳቸው ጥያቄዎች መመለስ አላባቸው ብሎ የሚያምን የፖለቲካ ፓርቲ፣ የሲቪክ ማህበርና ዜጎች በሰልፉ እንዲሳተፉ ፓርቲያችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡<br /> ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም<br /> አዲስ አበባ

Ethiopia Refuses to Cooperate With World-Bank-Funding Probe

by William Davison

 Bloomberg


Addis Ababa – Ethiopia’s government said it won’t cooperate with a probe into whether the World Bank violated its own policies by funding a program in which thousands of people were allegedly relocated to make way for agriculture investors.

Ethiopia, Africa’s most-populous nationEthnic Anuak people in Ethiopia’s southwestern Gambella region and rights groups includingHuman Rights Watch last year accused the Washington-based lender of funding a program overseen by soldiers to forcibly resettle 45,000 households. The Inspection Panel of the World Bank, an independent complaints mechanism, began an investigation in October into the allegations, which donors and the government have denied.

“We are not going to cooperate with the Inspection Panel,” Getachew Reda, a spokesman for Prime Minister Hailemariam Desalegn, said in a phone interview on May 22. “To an extent that there’s a need for cooperation, it’s not going to be with the Inspection Panel, but with the World Bank”



Ethiopia, Africa’s most-populous nation after Nigeria, has made 3.3 million hectares (8.2 million acres) of land available to agriculture Companies.

Ethiopia, Africa’s most-populous nation after Nigeria, has made 3.3 million hectares (8.2 million
acres) of land available to agriculture companies. Investors include Karuturi Global Ltd. (KARG) of India, the world’s largest rose grower, and companies owned by Saudi billionaire Mohamed al-Amoudi.

There is a “plausible link” between the Promoting Basic Services program, partly funded by the bank to pay the salaries of local government workers, and a resettlement process also known as villagization in Gambella, the panel said in a Nov. 19 report obtained by Bloomberg News. The World Bank confirmed the authenticity of the report.

‘Potential Non-Compliance’

The concurrent implementation of PBS and the resettlement program may raise issues of “potential serious non-compliance with bank policy,” according to the report.

“From a development perspective, the two programs depend on each other, and may mutually influence the results of the other,” the panel said.

Human Rights Watch, based in New York, made similar allegations about the resettlement program in a January 2012 report. Those findings and the Inspection Panel process are part of a “propaganda campaign being waged against the government,” Getachew said by phone from the capital, Addis Ababa. “It’s not a World Bank inspection panel, it’s a panel that likes to impose its mostly fictitious findings on the decision-making process of the World Bank.”

About 35,000 households voluntarily moved over the past three years in Gambella and now have better access to public services and are growing more food, State Minister of Federal Affairs Omod Obang Olum said in a May 15 interview.

‘Unprecedented’

The complaint to the panel was made on behalf of 26 Anuaks now living in South Sudan andKenya. Refusal to cooperate with the panel by a World Bank member state is “unprecedented,” said David Pred, a managing associate at Inclusive Development International, or IDI, a California-based human-rights group that assisted with the complaint.

“I don’t see how the bank could justifiably continue supporting Ethiopia if the government simply rejects outright any semblance of accountability,” he said in an e-mailed response to questions.
The complaints should be investigated further “as they pertain to the bank’s application of its policies and procedures,” the panel said. The probe should not look at allegations of “specific human rights abuses” or the “underlying purposes” of the resettlement program, it said.

Donor Aid

Donors provided $3.56 billion of aid to Ethiopia in 2011, which was 11.3 percent of gross national income, according to the Organisation for Economic Cooperation and Development.

The World Bank said that while officials on PBS-funded salaries may have “responsibilities related” to resettlement, this doesn’t mean the two programs were “directly linked,” according to the panel.
There was no evidence of “forced relocations or systematic human-rights abuses,” according to reports by two fact-finding missions in 2011 and 2012 by donors including the U.K. and U.S. aid agencies. “Half of the people interviewed said they didn’t want to move” and some said public services hadn’t been provided in new sites, the 2012 report found.

PBS “does not build upon villagization, it is not synchronized with villagization, and does not require villagization to achieve its objectives,” the World Bank’s management said in response to the complaint. “Furthermore the bank does not finance” villagization.

Election Violence

PBS began in 2006 after donors stopped “direct budget support” to the federal government because of violence following a disputed 2005 election. The program provides block grants to regional governments that are mainly spent on education, health, agriculture, water and road workers.

A postponed March 19 discussion of PBS by the bank’s board has yet to be rescheduled, Guang Chen, the bank’s Ethiopia director, said in an e-mailed response to questions. “Staff are not authorized to comment prior to the board discussion,” he said.

Since 2006, PBS has cost donors and the government $13 billion, the panel said. The ongoing phase is funded by the government, the World Bank, the African Development Bank, the European Union, the U.K., Austria and Italy.

The panel also can’t comment at this stage, operations analyst Dilya Zoirova said in an e-mailed response to questions.

Monday, May 27, 2013

በአንባገነኖች የሀሰት ውንጀላ እስር እና እንግልት አንበረከክም! (ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር)


በአንባገነኖች የሀሰት ውንጀላ እስር እና እንግልት አንበረከክም! (ባለራዕይ ወጣቶች ማህበር)

Statement from Baleraey Wetatoch

Meles Zenawi Net Worth $3 Billion


“Zenawi had an MBA from the United Kingdom, and a Masters of science in economics from Netherlands. His net worth currently stands at $3 Billion.” According to TheRichest.Org

Meles Zenawi net worth: Meles Zenawi Asres was the former Prime Minister of Ethiopia who presided over the country from 1995 to his death in 2012. He was also the President of Ethiopia from 1991 to 1995. He was one of the most recent literate and forward thinking leaders of Africa. Zenawi had an MBA from the United Kingdom, and a Masters of science in economics from Netherlands. His net worth currently stands at $3 Billion.

He joined the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) as a member in 1975. Eventually, he was elected as the chairperson of TPLF and EPRDF. Lead by him and other leaders, TPLF was able to assume power in the country in 1991 as the civil war came to an end. Upon becoming the Prime Minister, he introduced a multi-party political system and allowed private press in the country. He agreed to work with the United States against groups and organizations such as Al Qaeda operating out of the country.

He was awarded the Rwanda’ National Liberation Medal and also the “World Peace Prize” for his contributions to global peace. Zenawi also received the “Yara” prize for carrying out a green revolution in the country. Some other awards he had received included the Africa Political Leadership Award in 2008, and the Good Governance award.

He married Azev Mesfin, who is currently a member of the Ethiopian Parliament. Meles Zenawi died at the age of 57 years on the 20th of August, 2012. He died from an infection after having an operation due to a brain tumor.

የኢህአዴግና የሻዕቢያ ድርድር ተበጠሰ

ኢሳያስ፣ ደሚት፣ ግብጽ፣ ኳታር፣ ኢህአዴግ
ኳታር በተናጠል የጀመረችው ኢትዮጵያንና ኤርትራን የማሸማገል ሂደት መበጠሱ ተሰምቷል። ከሽምግልናው ዙሪያ የግብጽ ሚና ስለመኖሩ አመላካች ጉዳዮች አሉ እየተባለ ነው። በድርድሩ ኢህአዴግ በዋናነት እንደ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው የትግራይ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ጉዳይ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
 
አቶ መለስ የኢትዮጵያን ወደብ እንደተራ ጉዳይ አሳልፈው በመስጠት ኤርትራን እንደ አገር እውቅና በሰጡበት ወቅት ድጋፍ ለማሰማት ቀዳሚ የነረችው ኳታር ከበረሃው ትግል ጀምሮ የሻዕቢያ ወዳጅ አገር እንደሆነች ይታወቃል።
 
ከዚሁ የከረመ ወዳጅነት በመነሳት ኳታር በ2008 ከኢህአዴግ ጋር ተፈጥሮ የነበረውን የጸብ ግድግዳ አፍርሳ ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው በዋናነት ሁለቱን አገሮች መልሶ ለማስታረቅ በተያዘ እቅድ ስለመሆኑ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይናገራሉ። በተለይም አሁን ያለው የኤርትራ አስተዳደር እጣ ፈንታ አብዝቶ ያስጨነቃት ኳታር በኤርትራ ወደብ ሊዝ በማድረግ፣ ኢንቨስትመንት ላይ በመሳተፍና ልዩ ድጎማ በማድረግ ቀዳሚውን ስፍራ ስለምትይዝ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ላይ ታች ማለቷ እንደማይደንቅ ስምምነት አለ።
 
ጎልጉል ምንጭ የሆኑ ዲፕሎማት እንዳሉት ኳታር አሁን እርቁን የፈለገችው በኤርትራ መረጋጋት እንዲፈጠርና የኤርትራ ኢኮኖሚ አንዲያገግም ለማድረግ በሚል ነው። በሌላ በኩል ህወሃት የዘወትር ስጋቱ የሆነውን ሻዕቢያን ለማስወገድ ሌት ከቀን እንደሚሰራና ይህም በድርጅት ደረጃ አቋም የተያዘበት ጉዳይ በመሆኑ የኤርትራ መንግስት መሰረታዊ የአቋም ለውጥ ሳያደርግ ከኢህአዴግ ጋር የድርድር ስምምነት ላይ መድረስ አስቸጋሪ እንደሚሆን ሁሉም ወገኖች የሚረዱት ጉዳይ ነው።
ከውስጥም ከውጪም ፖለቲከኞች ትኩረት ሰጥተው እየተከታተሉት ያለው የሁለቱ አገሮች  የሰላም ድርድር ዲፕሎማቱ እንዳሉት ሁለት አብይ ጉዳዮች አሉበት። ሁለቱ አብይ ጉዳዮች ደግሞ ሊነጣጠሉ አይችሉም። በኤርትራ እለት እለት እየሰለለ የሄደው የአገሪቱ ኢኮኖሚና የኑሮ ውድነቱ የኢሳያስን አስተዳደር አናግቶታል። በተጨማሪ ሆን ተብሎ ይሁን በሌላ ምክንያት ከሃያላኑ አገራት ጋር የገጠሙት የረዥም ጊዜ ፍትጊያ የኢሣያስን ትከሻ አዝሎታል። ከዚህም በላይ እድሜ ለመለስ የፍቅር ጊዜያቸው ሲሻግት “አሸባሪ” አድርገዋቸው።
 
ከዓለምና ከአህጉር መድረኮች ሙሉ በሙሉ ተገልሎ የከረመው የኢሳያስ አስተዳደር በተለያዩ ደረጃዎች የደረሰበትን እግድና ቅጣት ለመቋቋም የዲፕሎማሲ ዘመቻ የጀመረው ከውጪ ያለውን ችግር ተከትሎ በአገር ውስጥ የገጠመውን ፈተና ለመቋቋም እንደሆነ ተንታኞች ያስታውሳሉ። በውስጥ የፖለቲካና የኢኮኖሚ አጣብቂኝ ውስጥ ያለው ሻዕቢያ ወንበሩ እየወላለቀ ስለሆነ ከቀድሞው ወዳጁ ህወሓት ጋር ለመወዳጀት ይፈልጋል።
 
ኤርትራ ኢኮኖሚዋ እንዲነቃቃ ኢትዮጵያን የንግድ ሸሪኳ ማድረግ የመጀመሪያው ስራ ነው።  ያለ ስራ “ሙት” ሆኖ የተቀመጠውን የአሰብን ወደብ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ ባነሰ ዋጋ እንድትጠቀምበት ማድረግና ወደቡ ላይ ህይወት መዝራት ዛሬ ላይ ግድ እየሆነ የመጣ ጉዳይ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ጅቡቲ ላይ የራስዋን ወደብ ለመገንባት የጀመረችው እንቅስቃሴና ለጅቡቲ የወደብ ኪራይ የምትገፈግፈው እጅግ ከፍተኛ ወጪ ግማሹ እንኳን ኤርትራ ቋት ውስጥ ቢገባ አሁን የተፈጠረውን የኑሮ ግለት ጋብ እንደሚያደርገው በርካቶች ይስማሙበታል።
 
በዚሁ መነሻ የኢሳያስ መንግሰት ከገባበት የመኖርና አለመኖር ስጋት ለመገላገል እቅድ ተነድፎለት የተጀመረውን ድርድር ኢህአዴግ የህልውና ጥያቄ በመጠየቁ ሳቢያ ብዙም ሳይራመድ በእንጭጩ ተኮላሽቷል። ኢህአዴግ በድርድሩ መሰረታዊ ሃሳብም ሆነ በሌሎች ዝርዝር የኢኮኖሚ ነጥቦች የተፈለገው ርቀት ድረስ ለመጓዝ ፈቃደኝነቱን ለመግለጽ ጊዜ አልወሰደም ነበር። የለበጣም ቢመስልም አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ዝግጁ መሆኑንን ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
የሆነ ሆኖ ኢሳያስ አሁን ባላቸው የፖለቲካ አቋም ከሳቸው ጋር መነገድ የዛለውን ክንዳቸውን ማፈርጠም በመሆኑ ኢህአዴግ እንዳልተዋጠለት የሚጠቁሙት ዲፕሎማቱ “ፖለቲካዊ ይዘቱ ኢኮኖሚያዊ ሽርክናውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል” በማለት ስለማይነጣጠሉት ሁለት ተያያዥ ጉዳዮች አስረድተዋል።
 
ኳታር ሶማሊያ ላይ በነበራት አቋምና የገንዘብ ተሳትፎ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት የዲፕሎማሲ መስመር ከመቋረጡም በላይ “ለሶማሊያ ጉዳይ አባቱ ነኝ” ይሉ በነበሩት አቶ መለስ ክፉኛ ተዘልዝላ ነበር። ያ ሁሉ አልፎ ዛሬ በኢንቨስትመንት ስም እርቅ አውርዳ የገባቸው ኳታር በጀመረችው ድርድር ኢህአዴግ ያነሳው መሰረታዊ የህልውና ጥያቄ አላላውስ ብሏታል።
ተቀማጭነታቸው ሎንደን የሆነ የጎልጉል ምንጭ እንዳሉት የኢህአዴግ ለመደራደሪያ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠው አጀንዳ ኤርትራ ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን የትግራይ ህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደሚት/ ታጣቂ ሃይሎች ተላልፈው እንዲሰጡት ወይም ወደ ትግራይ ድንበር እንዲገፉለት ነው።
 
ቀደም ሲል የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ህወሃት አካል የነበሩት እነዚህ ክፍሎች “ኤርትራ ውስጥ ታግተው የተቀመጡ”  ሃይሎች ስለመሆናቸውና ከ30 እስከ 40 ሺህ የሚደርስ ወታደር እንዳላቸው ለህወሃት ቅርበት ባላቸው የተለያዩ መገናኛዎች መዘገቡ ይታወሳል። በገለልተኛነታቸው የሚታወቁ መገኛዎችም ቢሆኑ የደሚት ሃይል ከአርበኞች፣ ከቤንሻንጉል፣ ከጋምቤላ፣ ከአማራ፣ ወዘተ ብረት አንጋቢዎች ጋር በጥምረት ለመሥራት መዘጋጀቱንና ይህም ሁኔታ ለህወሃት ስጋት እንደሚሆን አመልከተው ነበር።
ከኢህአዴግ የሚወጡ የምርመራ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ህወሃት ደሚትን እየፈራ ነው። ደሚት “በኤርትራ የታገተ ሃይል ነው” በማለት የድርጅቱን ሃይል ለማጣጣል ቢሞከርም፣ የደሚት ሃይል እንደሚባለው አለመሆኑንን የሚያረጋግጡ መረጃዎች አቶ መለስ በህይወት እያሉ ቀርቦላቸዋል። ከዚያ በኋላ ነበር ደሚት ጥንካሬው እንዳይጎለብት ህወሃቶች መስራት የጀመሩት።
 
በወቅቱ ከኢህአዴግ ጓዳ ያፈተለኩ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቀም የሚያስችላት ድርድር ተጀምሮ ነበር። በስዊድን የሚኖሩ የጎልጉል ምንጭ የሆኑ የኤርትራ ተወላጅ ከዓመት ከስድስት ወር በፊት የአሰብ ወደብ እንዲታደስና ስራ እንዲጀምር ተወስኖ እንደነበርና ስራው ሲጀመር ስራ አቁመው የነበሩ ሰራተኞችና አገልግሎት አቋርጠው የነበሩ ድርጅቶች ስራቸውን እንዲጀምሩ መመሪያ ተሰጥቶ እንደነበር ያስታውሳሉ። ስራው አሁን በምን ደረጃ እንደሚገኝ ለጊዜው መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።
 
በተለያየ ወቅት አቶ መለስን ከቀድሞው ወዳጃቸው አቶ ኢሳያስ ጋር መልሶ ለማሻረክ ግብጽን ጨምሮ የተለያዩ አገሮች እንደተሳተፉ የሚገልጹ አሉ። የግብጽን የሸምጋይነት ሚና ጥርጥር ውስጥ በማስገባት አስተያየት የሚሰጡት ዲፕሎማት አሁን ኳታር ከጀመረችው ድርድር ጋርም ግብጽን ያያይዛሉ። ከኳታር ካዝና በሚወጣ ገንዘብ ሻዕቢያ የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች እንዲያደራጅ አጥብቃ የምትሰራውና የምትደጉመው ግብጽ አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያና ኤርትራ አስተማማኝ ሰላም አውርደው በሰላም በጉርብትና እንዲኖሩ አትመኝም።
 
ኳታር ግን በቀድሞው አቋም መቀጠሉ አግባብ እንዳልሆነና በ2008 ከኢትዮጵያ ላይ እጇን እንድታነሳ ተጠይቃ ባለመቀበሏ የተሰበረው የዲፕሎማሲ ግንኙነት ለማቃናት መስራት የጀመረችው ከሊቢያው መሪ ጋዳፊ ሞት በኋላ እንደሆነ የሚገልጹ ክፍሎች ኳታር አሁን በጀመረችው “የትልቅ አገር ነኝ” ስሜትና በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ ፖለቲካ ላይ ያላት ሚና መጎልበት ኢትዮጵያን መወዳጀት ብቸኛው አማራጯ እንደሆነ ይናገራሉ።
 
ሻዕቢያ እየከሰመ ሲሄድ ኢህአዴግ በሌላ በኩል በአፍሪካም ሆነ በዓለም ደረጃ ማደጉ ለንግድና ለፖለቲካ ዝናዋ ኢህአዴግን መወዳጀት አማራጭ የሌለው ጉዳይ የሆነባት ኳታር ሩጫዋ በጊዜ የተኮላሸው ከኢህአዴግ ወገን በተነሳ “የማይታሰብ” በተባለ ጥያቄ ነው። የደሚት የጦር ሃይል ተላልፎ እንዲሰጠው ወይም ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እንዲገፋለት የተየቀው ኢህአዴግ ይህ እስካልሆነ ድረስ ከሻዕቢያ ጋር አንድ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ለመነጋገር አለመቻሉ ለኳታር ሽምግልና የመጀመሪያውና ሊመለስ ያልቻለ ፈተና ሆኗል።
 
ከድሮ ጀምሮ አድብታ የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች በመርዳት የምትታወቀው ግብጽ ኢህአዴግ በፈለገው መልኩ ድርድሩ ሊካሄድ እንደማይችል አቋም ይዛ እየሰራች እንደሆነ፣ ለዚህም ሲባል ከአንዳንድ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ለመነጋገርና በሻዕቢያ አማካይነት ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎት ማሳየቷን የጎልጉል ምንጭ የሆኑት ዲፕሎማት አስረድተዋል። ዲፕሎማቱ በደፈናው ከመናገር ውጪ ግብጽን ያነጋገረቻቸውን የተቃዋሚ ሃይሎች አልዘረዘሩም።
 
ኳታር የምጽዋን ወደብ በሊዝ ከመያዟ በተጨማሪ ለአሰብ ወደብ የነዳጅ ማጣሪያ ማደሻና ለወደቡ ስራ ማስቀጠያ ድጋፍ ማድረጓ አይዘነጋም። ያለ ስራ ተቀምጦ የነበረው ወደብ ለስራ እንዲዘጋጅ የታሰበው ለማን ተብሎና ማን እንዲጠቀምበት ታስቦ ነው ሚለው ጉዳይ ፖለቲካዊ ውሳኔ የሚጠይቅ አብይ ጉዳይ ከሆነ ዓመት ከስድስት ወር አስቆጥሯል። ኢህአዴግ የሚደጉመው የኤርትራ የሽግግር መንግስት አዲስ አበባ መቋቃሙም የሚታወስ ነው።
 

Friday, May 24, 2013

ወያኔ እና እኛ ሙስና ስንል


በቅርቡ በሀገር ውስጥ ገቢና በጉሙሩክ አገልግሎት መስሪያ ቤት የሚሰሩ ጥቂት ባለስልጣኖችና ተባባሪ የተባሉ ግለሰብ ነጋዴዎች፣ በሙስና ተወንጅለው ወህኒ መውረዳቸውን ተከትሎ ወያኔ ፀረ-ሙስና ድርጅት ለመምሰል ከተግባሩ የበለጠ የከበሮ ድምጽ እያሰማን ይገኛል። አንዳንድ የዋህም ይህን ከበሮ በመስማት ሙስናን ለማጥፋት ዘመቻ የተጀመረ መስሏቸው ተስፋ ሲያደርጉ ይታያል።

በመሰረቱ ሙስና በወያኔ ስርአት ውስጥ የስርአቱ መቆሚያ ምሰሶ ከሆነ ውሎ አድሯል። በሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት እየተመናመኑ በሄዱበት ፍጥነት ነው ሙስና እየደራ የሄደው። ከላይ እስከታች በተዘረጋው የወያኔ ስርአት ውስጥ ከቁንጮ ባለስልጣናት እስከታችኛው አገልጋይ ድረስ በሙስና ያልተዘፈቀ የስርአቱ አገልጋይ መፈለግ ከዝንጀሮ ቆንጆ የመምረጥ ያህል ከባድ ሆኗል።

የወያኔ ትላልቅ ሙሰኞች ለምልክት ትንንሽ ሙሰኞችን አልፎ አልፎ በማሰር ፀረ ሙሰኛ መስለው ሊያሞኙን ቢሞክሩ ዛሬ የመጀመሪያቸው አይደለም። ወያኔ ሙስናን ክስ የሚጠቀምበት አንድም በውስጡ ካፈነገጡ ሃይሎች ጋር የፖለቲካ ልዩነትን ለማወራረጃ ወይም ለውጭ ለጋሾች ሙስናን የሚጠላ መስሎ ለመታየት ሲፈልግ ብቻ መሆኑን ከልምድ እና ከተግባሩ ህዝቡ ያውቀዋል።

የወያኔ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ድህነት ማቅ ቁልቁል እያስገባና ሀገሪቱ በእዳ እያስያዘ፣ በአንጻሩ ግን የስርአቱ ቁንጮ ባለስልጣናት በሙስና ተዘፍቀው፣ በልፅገውና ከብረው፤ ራሳቸውን ከሙስና ነጻ ሆኖ ለመታየት ሲያሻቸው ግልገሎቹን በማሰር እና በራሳቸው ሚዲያ አስረሽ ምችው ይጨፍራሉ።

በእኛ እይታ ወያኔ ራሱ ቆሞ የሚሄድ ሙስና ነው። ወያኔና ሙስናን፣ ሙስናንና ወያኔን መለያየት አስቸጋሪም ነው። የወያኔ አባልና ደጋፊ የሚሰበሰበው፣ የሚመለመለው በመንግስት ሀብትና ንበረት ሰዎችን በማባበል ነው። ይህም ሙስና ነው።
ወያኔ ለየእለቱ የፖለቲካ ድርጅታዊ ስራውና በምርጫ ጊዜ በገፍ ካለ አቤት ባይ የሚጠቀመው የመንግስት ገንዝብ፣ ተሽከርካሪ፣ ነዳጅ፣ ቢሮ፣ የሚከፈለው የመንግስት ውሎ አበል፣ የሚገለገልበት የህዝብ ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ፣ ጋዜጣ ወዘተ የሙሰኝነት ስርአታዊነቱ መገለጫ ነው። የመንግስት ስራ እድልን ከተማሩ ዜጎች ሳይቀር እየነጠቀ በዘርና በወያኔ አባልነት መለኪያ ለተመለመሉ አባሎች የሚሰጠው ስጦታ ዘግናኝ ሙስና ነው።

ኤፈርት የተባለው የወያኔ ኩባንያ ከህዝብና ከመንግስት በተዘረፈ ሀብት መመስረቱን እንደማያውቅ ትተን ትላንት ከባንክ ካለተከራካሪ እየተበደረ የሚነግድብን ንግድ፣ ሲከስር ብድሩና ወለዱን መክፈል ሲያቅተው ወያኔ ሙስና ብለን ይህን እንድንጠራው አይፈልግም።

ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔ ተገዶ ወይም ተወግዶ በሀገራችን በህግና ህግ ብቻ የሚሰራ መንግስት መመስረትን እንደ ግብ የምንቆጥረው ለዚህ ነው። ግንቦት 7 በሀገራችን ሙስና ላይ የአመረረ ትግል ማድረግና ሙሰኞችን ማጥፋት የሚቻለው ወያኔን ያስወገድን እለት ብቻ ነው። ስለዚህም የሀገራችን ህዝብ ሆይ ይህን ተረድተህ ትግሉን በአስቸኳይ ትቀላቀል ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Thursday, May 23, 2013

ሰበር ዜና፣ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉን በታቀደው ቦታና ስዓት እንደሚያካሂድ አስታወቀ

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ማብራሪያ

ሕገ ወጥነት ከዓላማችን አይገታንም!!!

ሕግ ምን ይላል?

አዋጅ ቁጥር ፫/፲፱፻፹፫ ዓ.ም

ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት የወጣ አዋጅ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የጠራው አካል ስላለበት ግዴታ በአንቀጽ ፬ ላይ እንዲህ ይላል  አንቀጽ ፬፤ የማሳወቅ ግዴታ፤

፩/ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚያዘጋጀው ማንኛውም ግለሰብ፣ ቡድን ወይም ድርጅት የታሰበው ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ከሚካሄድበት ጊዜ ቢያንስ ከ፵፰ ሰዓታት በፊት በጽሑፍ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
፪/ የማሳወቂያው ጽሑፍ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ በከተማ ከሆነ የሚደረገው ለከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት፤ ከከተማ ውጭ ከሆነ ለአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ይሆናል፡፡
መልስ ሰጪው አካል የከተማ ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ያለበትን ግዴታና ኃላፊነት አንቀጽ ፮ ላይ እንዲህ ብሎ ደነግጋል፡፡

አንቀጽ ፮፤ የከተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊነት፣

፩/ ከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት የሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ጥያቄ በጽሑፍ ሲቀርብለት ሰላምን ከማስፈን ጸጥታን ከማስጠበቅና የሕዝቡን ዕለታዊ ኑሮ እንዳይሰናከል ከማድረግ አንጻር አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ የማድረግ ኃላፊነት አለበት፡፡

፪/ ከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፮ ንዑስ አንቀጽ ፩ የተመለከቱትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለው ምክንያቱን በመግለጽ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ፲፪ ሰዓት ውስጥ በጽሑፍ ለአዘጋጁ ማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው ወይም አውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም፡፡

ምን ተደረገ?

ሰማያዊ ፓርቲ የጠራውን የተቃውሞ ሰልፍ ማወቅ የሚገባው በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ እንዲያውቅ የሚያደርግበትን ደብዳቤ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ.ም ከጧቱ 4፡00 ሰዓት የተጠቀሰው ቢሮ ድረስ አቅርቧል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ደብባቤ አልቀበልም በማለታቸው ከሰዓት በኋላም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ደብዳቤውን እንደገና አቅርቦ አሁንም አልቀበልም በማለታቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ የተለያዩ አካላት እስከ ከንቲባው ፅ/ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉጋዮች ምክትል ኃላፊ ድረስ በመሄድ ደብዳቤውን እንዲቀበሉ ቢጠየቁም “ደብዳቤ እንዳንቀበል ከበላይ ታዘናል” በማለት በቃል ተመሳሳይ የአንቀበልም መልስ ሰጥተዋል፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ከፓርቲው በኩል ሦስት ሰዎች ከማዘጋጃ ቤቱ ደግሞ ሦስት ሰዎች የአይን ምስክርነት ባሉበት በሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ማሰወቂያ ቢሮ ኃላፊ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠው ወጥተዋል፡፡ ከዚህም በጠጨማሪ ደብዳቤው በፖስታ ቤት በኩል በሪኮመንዴ እንዲደርስ ተልኳል፡፡
ምን ይደረጋል?

ሰማያዊ ፓርቲ በሕግ የተቋቋመ ህግ የሚያከብር ፓርቲ ነው፡፡ ፓርቲው የሚገዛው ለህግ እንጅ ለውንብድና ባለመሆኑ ሰልፉን በዚህ መልኩ ለማሰናከል የማይቻል መሆኑን የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዲያውቁት ማሳሰብ ይፈልጋል፡፡ ሰልፉን ለማድረግ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በህግ በኩል የጎደለ አንድም ቅንጣት ነገር ባለመኖሩ ሰልፉ በታቀደው ቦታና ስዓት የሚካሔድ መሆኑን ያሳውቃል፡፡

ግንቦት 15 ቀን 2005 ዓ.ም

 አዲስ አበባ