Friday, July 8, 2016

ሰበር ዜና… በወያኔ ወታደራዊ ደህንነት አባላት ላይ እርምጃ ተወሰደ

July 8,2016
በልኡል አለም
በሰሜን የሐገራችን ክፍል በህቡእ የተደራጁ የዉስጥ አርበኞችና የትግል አጋሮች በአንድነት በመተባበር ቀንደኛ እና አደገኛ በሆኑ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን የመከላከያ ሰራዊት የደህንነት አባላት ላይ እርምጃ ወስደዋል። ቢያንስ ከ6 ወራት በላይ የፈጀዉን ድርጊት ከመራዉ የህቡእ ኃይል ህበረት ወስጥ የወጣዉ መረጃTPLF security officers killed in Gondar እንደሚጠቁመዉ።
ወታደር አሳምን ሃለፎም፣
ወታደር በረከት ድረስ፣
ወታደር ሰይድ ይማም፣
ወታደር የትናየት ላቀዉ፣
ወታደር ጀምበሩ ዘለቀ።
የተባሉ እነዚህ እርምጃ የተወሰደባቸዉ አባላት የሕዝብ ጠላትነታቸዉን በግልጽ ያስመሰከሩ ያለ አግባብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉና ወገኖቻችንን የሚያሳድዱ በተለይም በጎንደር አካባቢ መሬታችንን ለሰሜን ሱዳን አሳልፎ ለመስጠት ደፋ ቀና የሚለዉ የወያኔ አገልጋዮች በወልቃይት ጠገዴ አፋኞችና ገዳዮች ሲሆኑ በተለያዩ ወቅቶችና ግዜያቶች ከሰፊዉ ህዝብ ጎን እንዲቆሙ ትእዛዝ ቢሰጣቸዉም አሻፈረኝ በማለታቸዉና በእኩይ ተግባራቸዉ በመቀጠላቸዉ ነዉ።
፣እርምጃዉን የወሰዱት የህቡህ ተደራጅ ሐይ መሪዎች በተለያየ ወቅትና ግዜ እነዚህን የወታደራዊ ደህንነት ሰዎች ካገቷቸዉ በኋላ ከሰሜኑ ግንባር ብሔራዊ ደህንነት ጋር ድርድር ላይ የነበሩ ሲሆን በድርድሩ የወያኔ ጽንፈኛ ቡድን ባደረገዉ ስህተት ምክንያት እርምጃዉን ለመዉሰድ መገደዳቸዉን አስታዉቀዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

No comments: