Wednesday, July 13, 2016

በጎንደር ሶስት የፌዴራል ፖሊሶች ሲገደሉ ሕዝቡ ቁጣው አሁንም እንደገነፈለ ነው። የህወሓት ደጋፊ ንግድ ቤቶች ወድመዋል።

July 13,2016
በጎንደር የሕዝቡ ቁጣ የቀጤለ ሲሆን ሕዝቡን ለማጥቃት ወደ ጎንደር የዘለቁ የፌዴራል ፖሊሶች እና የደህንነት ሃይሎች ጥቃት እየደረሰባቸው መሆኑ ተሰምቷል። ብሶቱ ገንፍሎ ኣደባባይ የወጣው ሕዝብ ራሱን በመሰዋት ነጻነቱን ለማረጋገጥ በመታገል ላይ ሲገኝ ለወያኔ ኣገዛዝ ማነቱን ከማሳየቱም በላይ ኣገዛዙን እንደማይፈልግ በሰልፍ ጭምር ኣረጋግጧል፤ ኣገዛዙ ሕዝብን ከሚያዘናጋባቸው እና ከሚያታልልባቸው መንገዶች ኣንዱ ድርድር ሲሆን የወልቃይት ጉዳይን በተመለከተ የተዋቀረውን ኮሚቴ ኣባላት ኣንዱ ከሆኑት ከኮሎኔል ደመቃ ጋር ድርድር ተቀምጧል የሚሉ መረጃዎች እየወጡ ቢሆንም ለኮሎኔሉ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ግን ኮሎኔሉ ከማንም ጋር መደራደር እንዳልጀመሩ በመግለጽ ሊደራደሩ ቢሉ እንኳን ከወያኔ በኩል ኣስተማማኝ ነገር እንዳሌለና የታሰሩትም እንዳልተፈቱ ገልጸዋል።
የአማራ ገበሬ ጦር ቦታ ይዞ እዬተጠባበቀ ነው። አራቱ ታፍነው የተወሰዱ ኮሚቴዎቻችን በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል። ያ ካልሆነ ከፍተኛ አደጋ እንደሚጥሉ ተናግረዋል። በአራቱም አቅጣጫ ወደ ከተማዋ የአማራ ገበሬ ጦር እዬተመመ ነው። ምንም እንኳ በየኬላው የመከላከያ ጦር ዘግቶ ቢጠብቅም አማሮች መግቢያ አላጡም ።በዛሬው እለት ብቻ ሁለት ከፍተኛ የህወሓት ደህንነቶችና ሶስት የፌዴራል ፖሊሶች ተገለዋል። የህወሓት ደጋፊ ንግድ ቤቶች ወድመዋል። ፩ኛ ሁመራ ፔኒስዬን - ፪ኛ ጣና ሆቴል - ፫ኛ ሮማን ሆቴል - ፬ኛ ቋራ ሆቴል …ከቀላል እስከ ከፍተኛ ውድመት የደረሰባቸው ሆቴሎች ናቸው። ወርቅ ቤቶችም አላመለጡም።ህዝቡ በምሬት የህወሓት ደጋፊ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች ጎንደርን ለቀው እንዲወጡ ሲያሳስብ ውሏል።
ምንጭ ሚኒሊክ ሳልሳዊ

No comments: