Thursday, June 23, 2016

አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ለነጻነት ትግሉ ያለንን ቁርጠኝነት በማደስ ነው!!!

June 23,2016

የወያኔ አገዛዝ በአቡደራቡህ መንሱር ሃዲ ይመራ ከነበረው የየመን መንግሥት ጸጥታ ሃይል ጋር በመመሳጠር አንጋፋውን መሪያችንንና የትግል ጓዳችንን አንዳርጋቸው ጽጌን ከሰነዓ አውሮፕላን ማረፊያ አግቶ በቁጥጥሩ ስር ካስገባ እነሆ ዛሬ ሁለት አመት ሞላው።
የአለም አቀፉን ህግ በመተላለፍ ህወሃት ድንበር ተሻግሮና ባህር አቁርጦ አንዳርጋቸው ጽጌን ከየመን ሲያግት ቢያንስ ሁለት ውጤቶችን ለማግኘት አሰፍስፎ እንደነበር መገመት አያስቸግርም። አንደኛው ሥልጣን ላይ ተደላድሎ ለብዙ አመታት የመቆየት ምኞቱን አደጋ ላይ የጣለበትን የአርበኞች ግንቦት 7 እንቅስቃሴ አከርካሪ በመምታት ትግሉን አሽመደምደዋለሁ የሚል የተሳሳተ ስሌት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ህወሃትን የሚግደራደር ሃይል የትም ቢሆን ሊያመልጥ እንደማይችል በማሳየት የኢትዮጵያን ህዝብ አንገት ለማስደፋትና በፍርሃት አንቀጥቅጦ ለመግዛት የታለመ የእብሪት ውሳኔ ነው።
በዚህም ስሌት ህወሃት አንዳርጋቸው ጽጌን በእጁ ለማስገባት በአፈናው ተግባር ተባባሪ ለሆነው ለመንሱር ሃዲ መንግሥት ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደከፈለ በራሱ አንደበት ሳይደብቅ ለደህንነት አባላቶቹ ሲናገር ተደምጧል። ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ከድህነት ወለል በታች ላለቺው አገራችንና የዕለት ህይወቱን ከአለም አቀፍ ህብረተሰብ በሚለገስ የምግብ ዕርዳታ ለሚገፋው ህዝባችን ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ ነው። በግዜያዊ ጥቅም አይናቸው የታወረዉ የየመን መንግሥት ባለስልጣኖችም ቢሆኑ ለፍትህ፥ ለእኩልነትና ለነጻነት የሚታገልን አንድ ኢትዮጵያዊ በአገሩ አየር መንገድ ሲጓዝ አግተዉ ለወያኔ ሲያስረክቡ ለረጂም አመታት በዘለቀዉና ለወደፊትም ጸንቶ በሚቆየዉ የሁለቱ አገሮች ወዳጅነት ላይ ጥሎት የሚያልፈዉ መጥፎ ጠባሳ የታያቸዉ አይመስልም። የሰነዓውን ኦፕሬሽን በህወሃት በኩል የመራውና አንዳርጋቸዉ ጽጌ እጆች ላይ ካቴና አጥልቆ ለወያኔ ያስረከበው አብረሃም መንጁስም ቢሆን በሱልጣን ሽኩቻ ከነበረበት ሃላፊነት ተፈንግሎ ዛሬ የት እንዳለ ከሱ ከራሱ ዉጭ ሌላ ሰዉ የሚያዉቅ አይመስለንም።
የህወሃት አፈናና ጭቆና የመረረው ህዝባችን አንዳርጋቸው ጽጌን ለማገት የተሄደበት ርቀትና የተከፈለው ዋጋ በነጻነቱ ላይ የተቃጣ ድፍረት መሆኑን ያሳየው “እኔም አንዳርጋቸው ነኝ” በሚል ቁጣ ሆ ብሎ በመነሳት ነው። አገር ውስጥና ከአገር ውጪ የተቀጣጠለው ይህ ህዝባዊ ቁጣ በአንድ አንዳርጋቸው መታገት እልፍ አእላፍ አንዳርጋቸውን ከማፍራቱም በላይ የህወሃት መሪዎችንና ጋሻ ጃግሬዎቻቸው እንደለመዱት ደረታቸውን ነፍተው በሠላም እንዳይወጡና እንዳይገቡ ወደ ሚያሸማቅቃቸው የተግባር እርምጃ ተሸጋግሮአል።
አርበኞች ግንቦት 7 ከአንዳርጋቸው መታገት በኋላ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ቁጣ የአንዳርጋቸዉ የረጅም ጊዜ ምኞትና ትግል ላይ በነበረባቸዉ አመታት በከፍተኛ ደረጃ የደከመበት የልፋቱ ዉጤት ነው ብሎ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 ይህንን ህዝባዊ ቁጣና ህዝባዊ መነቃቃት አስተባብሮና የሚያስፈልገውን አመራር ሰጥቶ ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሙሉ ሃይሉና ጉልበቱ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለወዳጅም ለጠላትም ይገልጻል።
የምንወደውና የምናፈቅረው የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ይህ ጀግና ሰዉ የጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ ያለንን ቁርጠኝነት በማረጋገጥ ነው። ለፍትህ ለእኩልነትና ለነጻነት ሲታገሉ የወያኔ ሠለባ የሆኑ ወገኖቻችንን በፍጹም እንደማንረሳቸዉና በየዕስር ቤቱ በዘረኞች እብሪት እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችን ሁሉ ነጻ እስኪወጡ ድረስ እነሱ አንግበው የተነሱትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ቆራጥነት ትግሉን እንደምንቀጥል ቃል እንገባለን።
የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸዉ ሆይ ! ያንተና እንዳንተ በወያኔ ሰቆቃ የሚፈጸምባቸው ጓዶቻችን ሁሉ የመከራ ዘመን የሚያበቃው የወያኔ የሥልጣን ዕድሜ ለማሳጠር የጀመርከውን ትግል ከዳር ስናደርስ መሆኑን አንተም ታውቀዋለህና እንደምንታደግህ አትጠራጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታሰር የነጻነት ትግሉን አቀጣጥሎታል ሲል አርበኞች ግንቦት7 ገለጸ

June 23,2016

ኢሳት ዜና :- ንቅናቄው የድርጅቱ ከፍተኛ የአመራር አባል የታሰሩበትን ሁለተኛ አመት ለማስታወስ ባወጣው መግለጫ “ ህወሃት አንዳርጋቸው ጽጌን በእጁ ለማስገባት በአፈናው ተግባር ተባባሪ ለሆነው ለየመኑ የቀድሞ መሪ መንሱር ሃዲ መንግሥት ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ቢከፍልም፣ አፈናው በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ ህዝባዊ ቁጣ ከመቀስቀስ እና እኔም አንዳርጋቸው ነኝ የሚሉ ታጋዮች ትግሉን እንዲቀላቀሉ እንዲሁም ወደ ተግባር ትግል እንዲገቡ ከማድረግ ውጭ በድርጅቱ ላይ ያሰበውን ድል አላገኘም ብሎአል።
“የሰነዓውን ኦፕሬሽን በህወሃት በኩል የመራውና አንዳርጋቸዉ ጽጌ እጆች ላይ ካቴና አጥልቆ ለወያኔ ያስረከበው አብረሃም መንጁስም ቢሆን በሱልጣን ሽኩቻ ከነበረበት ሃላፊነት ተፈንግሎ ዛሬ የት እንዳለ ከሱ ከራሱ ዉጭ ሌላ ሰዉ የሚያዉቅ አይመስለንም” የሚለው የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ፣ የአንዳርጋቸው መያዝ የፈጠረው ህዝባዊ ቁጣ የህወሃት መሪዎችንና ጋሻ ጃግሬዎቻቸው እንደለመዱት ደረታቸውን ነፍተው በሠላም እንዳይወጡና እንዳይገቡ ወደሚያሸማቅቃቸው የተግባር እርምጃ አሸጋግሮታል ብሎአል።
ከአንዳርጋቸው መታገት በኋላ የተቀጣጠለው ህዝባዊ ቁጣ የአንዳርጋቸዉ የረጅም ጊዜ ምኞትና በትግል ላይ በነበረባቸዉ አመታት በከፍተኛ ደረጃ የደከመበት የልፋቱ ዉጤት ነው ብሎ እንደሚያምን የገለጸው ድርጅቱ፣ አርበኞች ግንቦት 7 ይህንን ህዝባዊ ቁጣና ህዝባዊ መነቃቃት አስተባብሮና የሚያስፈልገውን አመራር ሰጥቶ ትግሉን ከዳር ለማድረስ በሙሉ ሃይሉና ጉልበቱ እየተንቀሳቀሰ ነው ሲል አክሏል።
ንቅናቄው “የትግል ጓዳችን አንዳርጋቸው ጽጌ የታገተበትን ሁለተኛ አመት ስናስታውስ ይህ ጀግና ሰዉ የጀመረውን ትግል ከዳር ለማድረስ ያለንን ቁርጠኝነት በማረጋገጥ ነው” ያለ ሲሆን፣  ለፍትህ ለእኩልነትና ለነጻነት ሲታገሉ የአገዛዙ  ሠለባ የሆኑ በየዕስር ቤቱ  እየተሰቃዩ ያሉ ሁሉ ነጻ እስኪወጡ ድረስ ትግሉን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በሌላ በኩል በእንግሊዝ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቀኑን በማስመልከት በእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። ሰልፉ በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ መሆኑን ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀጸላ ከስፍራው ዘግባለች ።

Wednesday, June 22, 2016

ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው

June22,2016
“የማይታመኑ ከሆነ “አለመታመናቸውን” ማሳየት አለባቸው”
ambassadors

በተለያዩ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በወሳኝ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በህወሃት ውስጥ ያለው ፍርሃቻና አለመረጋጋት ለሁኔታው አስገዳጅነት ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡ ህወሃት ለዓመታት ያገለገሉትን ሎሌዎች የማያምናቸው ከሆነ እነርሱም “አለመታመናቸውን” ማሳየት ይገባቸዋል፡፡
በአሜሪካ፤ በአውሮጳ፤ በአውስትራሊያና በኢትዮጵያ አጎራባች በሆኑ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በቅርቡ ወሳኝ በሆኑ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ መታሰቡን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አስታውቀዋል፡፡ ለመረጃው ቅርብ እንደሆኑና የአገራቱም ዝርዝር እንዳላቸው የተናገሩት መረጃ አቀባይ የሹምሽሩ ምክንያት ይህ ነው ተብሎ በውል ባይታወቅም ህወሃት ከውስጥና ጫና ተጠቃሽ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡
በኢህአዴግ ተለጣፊና ድቃይ ድርጅቶች ታቅፈው የሥርዓቱ ሎሌ የሆኑት አምባሳደሮች በመጪዎቹ ሳምንታትና በሐምሌ ወር ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እንደሚደረግ ታውቋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚደረግ ዓመታዊ ስብሰባና ግምገማ ተብሎ ሽፋን የሚሠጠው ይኸው አምባሳደሮችን የመጥራት ውሳኔ በህወሃት ሰዎች የተቀነባበረና የትኞቹን አምባሳደሮች በማን ለመተካት እንደታሰበ አስቀድሞ የተወሰነ ነው፡፡ በዓለምአቀፍ የዲፕሎማሲ ህግጋት መሠረት የሚነሱት አምባሳደሮች መረጃ ለየአገራቱ ደርሷል፡፡
ለ25 ዓመታት እጅግ አሰቃቂ ወንጀሎችን በመፈጸም በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን በፍግ እየገዛ ያለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር ከፍተኛ ችግር ውስጥ በሚወድቅበት ጊዜ ታማኝ የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ነባር ታጋዮች ላይ አመኔታውን በማድረግ “ክፉ ጊዜያትን” ሲያልፍ ቆይቷል፡፡ የአሁኑም ጉዳይ ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነገራል፡፡
በተለይ በሰብዓዊ መብት ረገጣ እያደረሰ ያለው ግፍ ከበቂ በላይ በሆነ ማስረጃ በተደጋጋሚ እየወጣበት ባለበት ባሁኑ ጊዜ የወደፊቱ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው መመለስ ያለበት ጥያቄ ሆኗል፡፡ ለዚህም ይመስላል በሰሜኑ ኢትዮጵያ ከአማራው ክልል ጋር ተያይዞ ያለውን አደገኛ ሁኔታ ለማምከን የኤርትራ ካርዱን የመዘዘው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ወራትን ያስቆጠረው የኦሮሞ ወጣቶች ተቃውሞ ከሁሉም በላይ አረመኔነቱንና ለሥልጣኑ ሲል የማይፈጽመው ወንጀል እንደሌለ በግልጽ ያሳየ መሆኑን ሰሞኑን የወጣው የሰብዓዊ መብት ተመልካቹ መ/ቤት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ዘገባ ያሳያል፡፡
በተለይም በያዝነው ዓመት ጥር ወር አካባቢ የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ የሚያስገባ” ባለ 19 ነጥብ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡ በወቅቱ ውሳኔው ኢህአዴግ “ልክ ሊገባ ይሆን” የሚል አመለካከት መጫሩን ጎልጉል ጠቅሶ በጻፈበት ወቅት “ረቂቁ ለውይይት እንዳይቀርብ የቻሉትን ያህል የጣሩት ቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያቸው” አለመሥራቱን፤ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ውሳኔው “ውስጡ በብረት የተወጠረ የቦክስ ጓንቲ ነው” ማለታቸውን ጨምሮ ዘግቦ ነበር፡፡ ይህ በዝርዝር መረጃ ቀርቦበት ለውሳኔ የበቃው ሰነድ ቀኑን ጠብቆ ህወሃት ላይ ሰይፉን እንደሚመዝ የወንጀሉ ተዋናዮች ከማንም በላይ የሚረዱት እውነታ ሆኗል፡፡
በአሜሪካ፤ ወሳኝ በሆኑ የአውሮጳ ከተሞች (ህብረቱ ያለበትንም ጨምሮ) እንዲሁም በኢትዮጵያ አጎራባች አገራት ያሉ አምባሳደሮች በታማኝ የህወሃት ተጋዳላዮች ለመተካት መታሰቡ የዲፕሎማሲው ተጽዕኖ ያስከተለው ጫና ብቻ ሳይሆን በህወሃት ውስጥ ሌላም ፍርሃቻ ስለአለ ነው በማለት ጉዳዩን ከሌላ አንጻር የሚመለከቱ ይናገራሉ፡፡
አሊ ኦጃሊ
አሊ ኦጃሊ
ምዕራባውያን ኃይላት ትኩረታቸውን ሊቢያ ላይ አድርገው ጋዳፊን ከሥልጣን ለማውረድ እንቅስቃሴ በጀመሩበት ወቅት ዓመጹ እየተፋፋመ ሲሄድ በየአገሩ የነበሩ የጋዳፊ ታማኞች መክዳታቸው ይታወሳል፡፡ ጋዳፊ ህይወታቸው በOctober 2011 ከማለፉ ስምንት ወራት በፊት በዋሽንግተን ዲሲ ታማኝ አድርገው ያስቀመጧቸው አምባሳደር አሊ ኦጃሊ ጋዳፊን መክዳታቸው ይታወቃል፡፡ ለጋዳፊ ታማኝ በመሆን አርባ ዓመት ያህል ያገለገሉት አምባሳደሩ በወቅቱ ከከዱ በኋላ የአማጺውን ኃይል ተቀላቅለው ነበር፡፡ ከዚህ አልፈው በአሜሪካ የአማጺው አፈቀላጤና ተወካይ በመሆን ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ የጋዳፊ መውደቅ እውን እየሆነ ሲሄድ አሜሪካ መልሳ በቦታቸው አስቀምጣቸው ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ህወሃትን ያስፈራው ይህንን መሰል የፖለቲካ ቁማር እንደሆነ ይነገራል፡፡
ከሎሌነት ባላለፈ አገልግሎት የሚሰጡትን “የራሴ፤ ታማኞቼ” ከሚላቸው ጋር ፈጽሞ እኩል ሊያደርጋቸው የማይፈልገው ህወሃት የፖለቲካው ትኩሳት አቅጣጫውን የቀየረ ዕለት የአሊ ኦጃሊን መንገድ ሊከተሉ ይችላሉ ብሎ የጠረጠራቸውን በቶሎ ለመተካት መወሰኑ “ከጋዳፊ ተምረናል” የሚል እንድምታ እንዳለው ይነገራል፡፡ በየትኛውም የለውጥ እንቅስቃሴ ጊዜ በተለይ በጎረቤትና በኃያላን አገራት ያሉ አምባሳደሮች መክዳት አልፎም ንቅናቄውን መቀላቀል የአምባገነኖችን ዕድሜ በማሳጠር በኩል ቁልፍ ሚና ይኖረዋል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ህወሃት ምዕራባውያን በተገኘው አጋጣሚ ፊታቸውን እንደሚያዞሩበት በመገመት ይህንን መሰሉን ጥንቃቄ ማድረጉ ሥልጣኑን እንዴት እንደሚንከባከብ የሚያሳይ ነው፡፡ በተለይ የኦህዴድ መሸርሸርና በክልሉ ያለው ዓመጽ እስካሁን አለመብረድ ከአምባሳደር ጀምሮ እስከ በታች እርከን የቆንስላ ተግባራት ላ የተሰማሩ ኦሮሞ ዲፕሎማቶችንና ሠራተኞችን በዓይነቁራኛ እንዲታዩ እያደረጋቸው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር “ለችግር ጊዜ አትታመኑም” ተብለው እንደሸቀጥ እንዲመለሱ የሚጠሩት አምባሳደሮች ቀን ፊቷን ሳታዞርባቸው ለምንስ በእርግጥ “የማይታመኑ መሆናቸውን” ለህወሃት አያሳዩትም በማለት የዜናው አቀባይ ለዲፕሎማቶቹ ጥሪ አዘል ምክር ለግሰዋል፡፡   (ፎቶ: ያለፈው አመት ሹመኞች)
ምንጭ ጎልጉል

Monday, June 20, 2016

BREAKING: Genzebe Dibaba’s coach arrested in doping raid

June 20,2016
image
BARCELONA, Spain (AP) — The coach of World 1500m champion Genzebe Dibaba and other long-distance runners was arrested near Barcelona after Spanish police raided his hotel room and found traces of EPO and other banned substances on Monday.

Jama Aden, a Somalian, was detained along with one of his unnamed trainers from Morocco, as the IAAF tested 30 athletes who were also guests at the Sabadell hotel, about 25 kilometers from Barcelona, where the coach has established annual training camps since 2013.

Police confirmed Aden and his trainer were under arrest on charges of administering and distributing doping substances and endangering public health. After questioning by law enforcement, both detainees should face prosecution within 72 hours.

Local authorities did not expect further arrests to follow.

The athletes, including Dibaba, at the raided hotel were mainly from Somalia, Sudan, Ethiopia or Djibouti.

Dibaba is a heavy favorite to win the Olympic women’s 1500m in Rio de Janeiro.

A simultaneous police raid in Madrid also yielded 16 arrests related to the trafficking of drugs and anabolic steroids.

Despite coinciding in time, law enforcement officers stressed there was no connection between the Sabadell operation and the bust in the Spanish capital, mainly linked to the bodybuilding underground market for steroid users.

Source: AP

” የኢህአዴግ” እና “ህግደፍ” የሰሙኑ ዉጥረት



June 20,2016
(የግል እይታ) – ዑስማን ካዋጃ
Ethiopiaየዛሬ 25 አመት የዓረቦች ታላቅ ህልም እና አጀንዳ በኢህአዴግ እና ህዝባዊ ግንባር ንዲሞክራሲን ፍትሕን (ህግደፍ) ኣስፈፃሚነት ተግባራዊ ሆነ ፡፡ የኢ/ያ ህዝቦችን በመሳርያ አፈሙዝ በማስገደድ ፡ ኤርትራውያንን የፈጠራ ታሪክ በመጋት እና Mass hallusination በመፍጠር ሁለት አገሮች ተፈጠሩ፡፡ ኤርትራ የግላችን ኢ/ያ የጋራችን የሚል የዝርፍያ እቅድ በ “ህግደፍ” ተነድፎ ሁለቱም ባለግዜዎች ለተግባራዊነቱ ተረባረቡ፡፡ እነ ቀይባህር ኮርፖሬሽን ተመስርተው ኢ/ያ ያለምንም ከልካይ ተዘረፈች፡ እነ Horn international bank በብድር እና እና እርዳታ የተገኘውን የውጭ ምንዛሪ በሰአታት ፍጥነት ህጋዊነትን አላብሰው አስመራ አደረሱት፡፡ ስለ አገር መቆርቆር እንደወንጀል ተቆጠረ፡ ምስጋና ለወቅቱ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪ ለነበሩት አቶ ገብሩ አስራት ይህን የዝርፍያ እቅድ በተቻላቸው መጠን ለመከላከል ሞከሩ በውጤቱም በተለምዶ ኢትዮ ኤርትራ የሚባለውን ግጭት ተቀሰቀሰ፡፡
ከ ሁለት ዓመታት ከባድ ጦርነት በኢትዮጵያ ልጆች ከባድ መስዋዕትነት የሻዕብያ ምሽግና ትዕቢት ተናደ፡፡ የኢ/ያ ጦር አሰብን ለመቆጣጠር ጥቂት ኪሎሜትሮች ሲቀሩት ታላቁ ” ባለራአይ” መሪያችን ራዕያችንን እንዳይሆን አድርገው አኮላሹት፡፡
ሰሙኑን የኢትዮ-ኤርትራ ግጭት እንደ አዲስ ተማሙቋል፡ አፍቃሪ ኢህአዴግ ሚድያዎች እና ትናንሽ ካድሬዎት ግቡ ባይታወቅም የጦርነት ነጋሪት እየጎሰሙ ናቸው፡፡ እኔ በግሌ የሰሙኑን የጦርነት አጀንዳ አጥብቄ እቋወማለሁ ለምን ቢባል:
1)ኢህአዴግ ኤርትራ ላይ ባለው ጭንጋፍ አቋም፡
ገዥው ፖርቲ ምን ግዜም ኤርትራ እና ህጋዊ የባህር በር የማግኘት መብታችን በተመለከተ ምን ግዜም ከኢትዮጵያ ህዝቦች በተፃራሪ እነደቆመ ነው፡፡ታድያ ይህን የገዢው ፖርቲ ፀረ ኢ/ያ አቋም ሳይቀየር ምን ለማግኘት ነው ጦርነት ውስጥ የምንገባው? እዚህ ላይ ሻዕብያን አስወግዶ ለኢ/ያ ችግር የማይፈጥር መንግስት ለመመስረት የሚል ውሃ የማይቋጥር ምክንያት በትናንሽ ካድሬዎች ይቀርባል ግን እንበል እና አዲስ የሚመሰረተውስ መንግስት ፀረ ኢ/ያ እንደማይሆን መተማመኛችን ምን ድነው?
2) ቀይ ባህር ላያ የጦር ሰፈሮቻቸው እየገነቡ ባሉ የኢ/ያ ታሪካዊ ባላንጦች ከዚህ አፍራሽ ተግባራቸው በዘላቂነት መከላከል የሚቻለው አስመራ ቤተመንግስት ላይ የሰው ለውጥ በማድረግ ሳይሆን ቀይ ባህርን በቆዋሚነት በመቆጣጠር ነው፡፡ ይህን ማድረግ የሚችል አርቆ አሳቢ መሪ እና ፖርቲ በሌለበት የሚካየድ ጦርነት ኢ/ያን ከባድ ዋጋ ከማስከፈል አልፎ የሚያመጣው ብሄራዊ ጥቅም የለም፡፡
3) የኤርትራውያን ከእንቅልፋቸው አለመንቃት፡
የሆነ ኤርትራዊ የችግራችሁ ምንጭ ምንድነው ብለን ብንጠይቀው መልሳቸው ተመሳሳይ ነው…..ኢሳያስ ኢትዮጵያዊ የደም ሃረግ ስለው ይሉናል ፡፡ታድያ ችግራችሁ እንዴት ይፈታል? የሚል ጥያቄ ብናስከትል አሁንም ገራሚ መልስ ይነግሩናል…..ኤርትራ በንፁህ ኤርትራዊ(ደቂ አባት) ስትመራ ይሉናል፡፡ከኢትዮጵያ ጋር በደም ያልተሳሰረ ንፁህ ኤርትራዊስ ማነው? ማንም ኤርትራዊ ይችን ጥያቄ መመለስ አይችልም፡፡ ታድያ የችግራቸው ምንጭ ትዕቢት፡ክፋት፡ድንቁርና፡ቅዠት፡አዲስ የተፈበረከ የውሸት መንነት: Mass Hallusination መሆኑን መውል ሳይገነዘቡ እና ስህተታቸው ለማረም ከውስጥ እንቅስቃሴ ባልጀመሩበት የኛን በማያገባን ጥልቅ ማለት ምን ለማትረፍ ነው???
እናም የኢህዴግን ባህሪ ባልተቀየረበት ወይም የኢ/ያ ብሄራዊ ጥቅምን ሳይሸራረፍ ሊያስፈፅም የሚችል ፖርቲ ባልተፈጠረበት የሚካየድ ጦርነት ኤርትራውያንን ከኢሳያስ አገዛዝ ነፃ ከማውጣት እና ኢትዮጵያውያን እናቶችን ዳግም ማቅ ከማልበስ ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ስለማያመጣ አጥብቄ እቋወማለሁ፡፡

Ethiopia-Eritrea Wargames of Mass Distraction? – Alemayehu G. Mariam

June20,2016
unnamedthe Global Terrorism Database.
In April 2011, the late TPLF thugmaster Meles Zenawi was talking about war, rumors of war and war with Eritrea and a water war with Egypt.
Here we go again in June 2016.
In the past few days, we are hearing once again talk about war, rumors of war and drumbeats of war signaling a ground war between Ethiopia and Eritrea.
But are we also watching a wargame of mass distraction?
T-TPLF communication minister Getachew “Motor Mouth” Reda said, “There were significant casualties on both sides, but more on the Eritrean side. We used to take precautionary measures against this regime, but this time was much more important in terms of magnitude than the measures that were taken so far.” (Whatever that means!)
Eritrea claimed to have killed 200 Ethiopian soldiers and wounded 300 more.
Hiram Johnson, a famous U.S. Senator from California, long ago said, “The first casualty, when war comes, is truth.”
When the two warring parties agree on the same “truth”, I begin to wonder if truth is the first and only casualty.
I also begin to smell the stench of a rat. I can smell a rat from 10 thousand miles away.
Sniff! Sniff! “Ethiopia- Eritrea War”.
Of course, Johnson’s dictum on the first casualty of war does not apply to wargames.
I have observed over the years that every time the T-TPLF leaders find themselves in a superbad publicity pickle, they conjure up a wargame.
I guess that is the T-TPLF’s way of hard-jamming the bad news and distracting domestic and international attention from their ongoing crimes against humanity, corruption, abuse of power and brutal suppression of all dissent.
There is no question the past few weeks have been all bad news for the T-TPLF.
Last week, the U.S. Securities and Exchange Commission (SEC) slammed the T-TPLF big time and ordered it to cough up $6.5 million it illegally ripped off from its supporters and other favor-seeking and bootlicking Diaspora Ethiopians in the U.S. They have to fork the money over to an independent Administrator appointed by the SEC no later than July 8, 2016.
That has got to be pretty humiliating for the T-TPLF and a big blotch on the memory of the late thugmaster who bragged about building the largest dam in Africa by shaking down the people of Ethiopia and Diaspora Ethiopians.
Imagine building a dam by racketeering in unregistered bonds in the U.S.! Bond protection racket?
I can imagine the T-TPLF leaders chafing over the fact that they got caught with their hands in the cookie jar three years after I had cited to them the chapter and verse the U.S. Code they were violating by selling unregistered bonds in the U.S.
I told them straight up on May 8, 2013. Don’t do it! Don’t sell unregistered bonds. It is a crime under U.S. federal and state laws. Don’t do the crime, it will come back to haunt you in time.
Three years later the crime of selling unregistered bond (It is a crime; See “Securities Act of 1933”, sec. 20 (b)) came back to haunt them.
But the T-TPLF’s snake oil unregistered bond salesmen barely escaped criminal prosecution.
But did they really?
The T-TPLF leaders have been getting away with crimes against humanity for so long that they thought they could also get away thumbing their noses at American laws.
They did not.
On the heels of the SEC revelation and order, Human Rights Watch (HRW) issued a major report entitled, “‘Such a Brutal Crackdown’: Killings and Arrests in Response to Ethiopia’s Oromo Protests.”
That report details the T-TPLF’s “use of excessive and unnecessary lethal force and mass arrests, mistreatment in detention, and restrictions on access to information to quash the protest movement.”
Leslie Lefkow, HRW Deputy Africa Director, said, “Ethiopian security forces have fired on and killed hundreds of students, farmers, and other peaceful protesters with blatant disregard for human life.”
Firing into a gathering of “peaceful protesters with blatant disregard for human life” is a crime against humanity. I just want to say that for the record.
In December 2015, T-TPLF minister Reda said the people killed in the protests were “an organized and armed terrorist force aiming to create havoc and chaos has begun murdering model farmers, public leaders and other ethnic groups residing in the region.”
A bunch of high school and college kids protesting in the streets are “an organized and armed terrorist force”?
It reminds me of Puff the Magic Dragon in the Land of Living Lies where Puff takes a little girl called Sandy, to the Land of the Living Lies. There she meets such famous fibbers as Pinocchio and the boy who cried wolf.
In the Land of Living Lies, Puff and Sandy get to see the famous purple cow that no one has ever seen and pink elephant that some see too often.
In the Land of Living Lies that Ethiopia has become under the T-TPLF, school children and college students are seen as an “organized and armed terrorist force aiming to create havoc and chaos.”
I remember when Ethiopia was known as the “Land of 13-months of Sunshine”.
Anyway, President Uhuru Kenyatta and others were charged in count 2 of the International Criminal Court indictment in 2012 for their involvement in the massacres of nearly 2 thousand innocent and peaceful Kenyans during the 2007 presidential election in Kenya.
HRW called for an independent inquiry into the “Oromo Protest” massacres.
The T-TPLF, as always, has turned a deaf ear.
The T-TPLF has been getting bad publicity for its total incompetence in dealing with the famine situation affecting some 20 million Ethiopians and its shameless efforts to keep news of that devastation from international scrutiny.
In complicity with USAID and the other international poverty pimps, the T-TPLF has succeeded in stonewalling any real time information from the famine-stricken areas and sandbagged journalists from making the effort to discover the truth for themselves.
So far the T-TPLF has been somewhat successful in avoiding accountability for its gross negligence, incompetence and criminality in the famine situation. (See my letter to USAID Administrator Gayle E. Smith.)
It is understandable why the T-TPLF wants to hard-jam all the bad news.
What better strategy is there to hard-jam the news than manufacturing news of war and rumors of war to create mass distraction?
I must confess that I view a “war” between the T-TPLF and its “adversaries” to the north as the equivalent of medieval England’s War of the Roses. It is an in-house fight for power between different members of the same family.
The T-TPLF and their alleged adversaries fought together for years as a band of brothers to dislodge the military regime and seize power. They struggled as comrades-in-arms cooperating and helping each other in military operations and diplomatic offensives. There is ample evidence that various top T-TPLF leaders have family and kinship ties with their “adversaries”.
Once the T-TPLF took over power in 1991, they shared it cheerfully with those they now accuse as adversaries in a curious circus in which the tail wagged the dog. That ended in 1993-94.
Between 1998-2000, the former comrades-in-arms were tangled up in a border war. The Eritreans attacked and captured Ethiopian territory. They were repelled after “an estimated 70,000 to 120,000 soldiers and civilians have died in the conflict.”
The late thugmaster Meles Zenawi declared victory; and in an insidiously calculated act of political capitulation and betrayal agreed to turn over the recaptured territory to Eritrea in international arbitration.
When Zenawi lost in arbitration by conveniently failing to put up a vigorous legal defense, he said the arbitral decision is not worth the paper it is written on.
Now, the former comrades-in-arms say they are fighting a war. They are pointing accusatory fingers at each other.
But are they really fighting a war or just wargaming?
But why are they warring against each other? They don’t say.
A high level Eritrean official alleged that the U.N. report which “accused Eritrean leaders of committing crimes against humanity including torture, murder and enslavement” was orchestrated by Ethiopia: “The gathering of information from ‘witnesses’ organised by Ethiopia allows the latter to advance its propaganda against a country that it aims to destabilize.”
Could the U.N. report be the casus belli (cause for war)?
In his book “Why Nations Fight” (2010), Richard Ned Lebow argues that historically four motives — fear, interest, standing, and revenge – have led states to initiate war. He argues the majority of wars are fought in a quest for standing and for revenge in an attempt to get even with adversary states who had previously made successful territorial grabs.
Is standing, revenge and recapture of territory the cause for “war” between the two states today?
My studies of dictatorships and wars initiated by them suggest an alternative explanation.
Pulling out the “war card” is the oldest trick in the dictators’ handbook.
The “handbook” says, “When the going gets tough, declare war. Declare a real or fake war. It does not matter. Talk about war. Spread rumors of war. Sound the drumbeats of war. Play wargames.”
But why? Because war is a sure and proven method of mass distraction!
From the time of the Roman emperors to the present day, the lords and gods of war have played the war card and stirred up patriotic fever in the population to cling to and prolong their hold on power.
Over the millennia, the technology of war may have changed but the deceit, machinations, sophistry, treachery and modus operandi of war-mongers has remained the same.
Dictators often start with a war of words and flood their population with a propaganda of lies, fabrications and half-truths about the need for war.
The prelude to war launched by dictators follows a predictable pattern. They begin by making grandiose public statements about the necessity of war and demonize their enemies hoping to boost popular support at home.
They magically discover love of country and wrap themselves in their flags and become jingoistic (super-patriotic). They will even promise to reverse territorial losses in an attempt to stoke patriotism.
Dictators brazenly pander to the population using nationalism and chauvinism in an effort to mobilize public support. They manufacture mass hysteria about imminent attacks, invisible enemies, lurking terrorists, loss of sovereignty and the rest of it.
Every chance they get, they try to trigger paroxysms of public anger against the enemy and inflame public opinion with provocative and outrageously concocted stories designed to make themselves look patriotic and their opposition and enemies appear unpatriotic.
When all else fails, dictators openly incite fear and hysteria to distract public attention from their crimes and dictatorial rule.
More often than not, the war of words will not amount to much more than declarations of bravado and hyperbolic accusations and recriminations. It often ends at the stage of skirmishes.
But dictators will often continue to talk about and spread rumors of war long after the guns have been silenced in the battlefield.
But war is a tricky proposition for dictators.
The survival of dictators more often than not depends on whether they win a war they have started.
Defeat in war often means the end of dictators.
Defeated dictators are often ousted in coups or other violent mass upheavals. The likelihood of exile, jail and death for dictators increases geometrically with each war dictators lose.
Some African dictators have remained in power despite losing wars they have launched recklessly. Indeed, they have used defeat as a justification and excuse to brutally suppress their population. They have used their enemies as bogeymen to scare their own population into submission.
Other African dictators have no incentive to win a war they started or joined. They feel so entrenched in power that war becomes a wargame for them; but a war of death and destruction for their population.
No one made the fact of dictator-launched wars more clear than Hermann Goering, Hitler’s right-hand man. He told the following to his interrogator at the Nuremberg Trials in 1945:
Naturally the common people don’t want war. That is understood. But, after all, it is the leaders of the country who determine the policy and it is always a simple matter to drag the people along…Voice or no voice [democratic or non-democratic government], the people can always be brought to the bidding of the leaders. That is easy. All you have to do is tell them they are being attacked, and denounce the peacemakers for lack of patriotism and exposing the country to danger. It works the same in any country.
In April 2011, the late thugmaster Meles Zenawi echoed Goering when he said:
Recently, Eritrea is training and deploying Al Shabab and locally grown destructive forces to terrorize our country. But Egypt is the direct force behind these destructive elements that back them. Until now, our strategy has been defending our sovereignty by speeding up our development. Now, we found that we could not go any longer with passive defense. It’s not possible to take passive defense as the only alternative. Therefore, we have to facilitate ways for Eritrean people to remove their dictatorial regime. We have no intention to jump into their country but we need to extend our influence there. If the Eritrean government tries to attack us, we will also respond proportionally.
In December 2006, Zenawi used the exact same logique de guerre (war logic) at the onset of his unsuccessful 843-day war to dislodge the Islamic Courts Union and crush the Al Shabab in Somalia. He said:
With regard to physical attacks or physical acts of the invasion, what has happened since last summer is that the Islamic courts have been training, equipping and smuggling armed opposition elements into Ethiopia. These elements have been engaged in activities of destabilization in Ethiopia. Hundreds of these have been smuggled and they have been involved in clashes with security forces in Ethiopia. To the extent that the Islamic Courts have trained them, equipped them, given them shelter and transported them to the border for smuggling. To that extent, they are directly involved in an act of aggression on Ethiopia. And that has been going since summer. It is still continuing.
In 2009, after leaving Somalia with his tail between his legs, Zenawi waxed philosophical: “If the people of Somalia have a government, even one not positively inclined to Ethiopia, it would be better than the current situation. Having a stable government in place in Somalia is in our national interests.”
That is the same guy who in December 2006 said he will make mincemeat out of the terrorists in Somalia and be back home in a jiffy.
What Zenawi did was cause the death of tens of thousands of Somalis civilians through indiscriminate shelling and displacement of hundreds of thousands.
How many Ethiopian soldiers died in Zenawi’s war in Somalia?
In 2009, Zenawi told “parliament it does not need to know how many soldiers died in Somalia”.
Dictators can make cannon fodder of their population and tell everyone it is not their business to know how many died in a war.
Now we are told the T-TPLF and Eritrea are banging the drums of war. They are dancing to the drumbeat of war.
Of course, the obligatory warnings against war have come from the usual suspects.
The U.S. State Department issued a statement calling for “cessation of hostilities” and urged “both Ethiopia and Eritrea to cooperate in promoting stability and sustainable peace in the region.”
U.N. Secretary-General Ban Ki-moon called on Ethiopia and Eritrea “to show maximum restraint and abide by the accords that ended their border war seven years ago.”
The bottom line question is whether there is a war between Ethiopia and Eritrea or just wargames?
I do not know!
They are having wargames, methinks.
Both sides claimed to have killed and wounded hundreds.
All that sounds and smells fishy to me. It does not pass my smell test (no pun intended).
What I do know is that I have seen this movie (or is it circus?) before.
In 2011, I saw the political theatre of wargames in a three-ring propaganda circus intended to distract the Ethiopian population and diaspora critics from talking about T-TPLF’s crimes against humanity, corruption, abuse of power and the rest of it.
On the other hand, could it be that all of the talk of war and rumors of war is a cover for another kind of “war” that is deeply troubling the T-TPLF?
In my view, all the pretentious war talk betrays the T-TPLF’s preoccupation with the inevitable loss of power and control as a result of a spontaneous popular uprising. All the war talk reveals the deep anxieties and profound political angst of a regime trapped in a siege mentality.
President Kennedy observed, “In the past, those who foolishly sought power by riding on the back of the tiger ended up inside.”
The prospect of ending up inside an angry and hungry tiger’s belly is what keeps the T-TPLF leaders and supporters from sleeping at night and talking about the nightmare of war all day.
I believe the T-TPLF is deeply concerned about a war, but not a war with Eritrea.
It is concerned about a war with the people of Ethiopia.
The T-TPLF knows I am telling the truth because that is what they talk about to each other all the time. What if the people of Ethiopia….?
I do not know if what we are witnessing in June 2016 is a prelude to war or watching a band of brothers just playing wargames of mass distraction.
Could there be war among those who are on different sides of the same coin? They need each other to remain in power just as Siamese twins need each other to live. They are peas in a pod.
War is one thing neither side needs today; and they know it.
In October 2015, the U.N. Security Council “reaffirmed the arms embargo on Eritrea.”
Prosecuting a war under an arms embargo could prove exceedingly difficult.
The much maligned British Prime Minster Neville Chamberlain said, “In war whichever side may call itself victor. There are no winners. But all are losers.”
In an Ethiopia-Eritrea War, who will be the losers?
There is a familiar old saying about fighting (warring) elephants and the grass.
Why is it not possible for the grass to come out as the real winner in a war among elephants?
In April 2011, I wrote, “Time will show if there will be war or intervention in Eritrea, and a water war with Egypt…. But for now, no one needs to lose sleep over that prospect. The only war being waged today by Zenawi is a war of mass distraction.”
In April 2011, Zenawi threatened to “facilitate ways for the Eritrean people to remove their dictatorial regime.”
The facts of the last 5 years speak for themselves.
Call me naïve. Even say that I was born yesterday and do not understand geopolitics and all that.
It may be true that I am naïve and may have been born yesterday. But I was not born last night!
I will repeat what I said in April 2011 in June 2016. The “Ethiopia-Eritrea War” is a wargame of mass distraction.

Sunday, June 19, 2016

‹‹በኔ አመለካከት ጀነራል ሣሞራ ለመንግስትና ለህዝቡ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው፡፡›› ~ሜጀር ጀነራል አበበ ተ/ሃይማኖት

June 19,2016
Abebe ty

ሜጀር ጀነራል ኣበበ ተክለ ሃይማኖት የታጋይዮች ተወዳጅነት ገና ሳይደበዝዝ ነበር በጥሮታ ሰበብ ከመከላከያው የተገለሉት፡፡በሌላ አባባል ጀነራሉ ወታደር ሳይሆኑ ነበር የታጋይነት መዓርጋቸውን እንደጨበጡ ከድርጅቱ የተሰናበቱት፡፡
ይኸው የታጋይነት ትጥቃቸው አሁንም ድረስ ከርሳቸው ጋር ነው፡፡ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ግዜ ሰጥቶ ማንበብ የግድ ይላል፤ ከጊዜ እጥረት የተነሳ ሙሉውን ማንበብ ለማይችሉት ግን አንኳር አንኳሮቹን እንደሚከተለው አቅርቤያቸዋለሁ፡፡
‹‹
☞በዓለም አቀፍ ህግ የአሰብ ወደብን ማስመለስ እንችላለን
☞ለሕገ መንግስቱ በተሟላ መንገድ መተግበር የአቅሜን ያህል እታገላለሁ፡፡
☞እኔ ከመጀመሪያውኑ ስታገልላቸው ለነበሩ አላማዎች፣አሁንም በፅናት ቆሜያለሁ ነው የምለው፡፡
☞ገዥው ፓርቲ ነው ከትግሉ አላማዎች ወደ ኋላ እየተንሸራተተ ያለው፡፡
☞የፓርቲ አባሎች ሲመለምል ከጥራት ይልቅ ብዛት ላይ በማተኮር በሚልዮኖች መለመለ፡፡ ሲቪል ሰርቫንቱ በብቃት ሳይሆን በአባሎቹ ተሞላ፡፡
☞ከዩኒቨርሲቲ “A” ከማምጣት ከኢህአዴግ “C” ማግኘት ይሻላል ተባለለት፡፡
☞የመልካም አስተዳደር ችግር ፖለቲካዊ ነው፤ የዲሞክራሲ ማጣት ውጤት ነው፡፡
☞ችግሩ የሚጀምረው ከላይኛው አመራር ነው፡፡ እላይ ከተስተካከሉ ከስር ይስተካከላል፡፡
☞ኢህአዴግ ውስጥ መተጋገል የለም፡፡
☞ደርግነት የሚመጣው እንግዲህ ሲቪሉ መግዛት ሲያቅተውና “ወታደሩ እኔ እሻላለሁ” ማለት ሲጀምር ነው፡፡
☞ከዚያ በኋላ እየጨለመ የመጣው ዲሞክራሲ፣ ወደለየለት አምባገነንነት ያመራል ማለት ነው፡፡
☞ዲሞክራሲያዊ ምህዳሩ እየጠበበ ደርግነት እያቆጠቆጠ፣ በመንግስትም ከመንግስት ውጪም ማፍያዎች እየታዩ ነው ስል፡ “ብዙ ሰዎች አንተ አትፈራም እንዴ? ሊገድሉህ ሊያስሩህ ይችላሉ” ይሉኛል፡፡
☞በተዘዋዋሪ መንገድ ግን መታገል አለብህ እያሉኝ ነው፡፡
☞መጀመሪያ በ “ካራክተር አሣስኔሽን”፣ ከዚያም የተለያዩ ጥቃቶች ሊፈፀሙ ይችላሉ፡፡ እንግልት… መሞት… መታሰር ያስፈራል፡፡ ያስጠላልም፡፡
☞እኔ ከሁሉም የምፈራው ፈርቶ በቁም መሞትን ነው፡፡ ፈርቶ የህሊና እስረኛ መሆንን ነው፡፡ በተለይ ወጣቶች ከዚህ የህሊና እስርና በቁም መሞት በላይ ምንም እንደሌለ ተገንዝበው መታገል አለባቸው፡፡
☞“የሀገራችን ችግር በህወሓትና በኢህአዴግ ብቻ ነው የሚፈታው” የሚል የምርጫ ቅስቀሳ ለምን እንደጀመሩ አይገባኝም።
☞የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ኢህአዴግ ከሌለ አይኖርም ማለት እብሪት ነው፡፡ ኢህአዴግንም ህወሓትንም የፈጠረው ህዝብ ነው እንጂ እነሱ ህዝብን አልፈጠሩም፡፡
››
ምንጭ – አዲስ አድማስ

Saturday, June 11, 2016

ህወሃት ጉሮሮውን ሳይታነቅ የበላውን በ30 ቀን “እተፋለሁ” አለ

June 112016
“ህወሃት ሲፈጠርም ጀምሮ ዓለምአቀፋዊ ወሮበላ ነው”
dollar-
ህወሃት በቦንድ ስም ህግ ጥሶ ሲሰበስብ የነበረውን ገንዘብ ክስ ተመስርቶበት ጉሮሮው ሳይታነቅ ወዶ ለመትፋት መስማማቱ ታወቀ። ድርጊቱ ኢትዮጵያን መሳቂያ፣  የምትተዳደረው በህገ አራዊት መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑንና የህወሃትን የወሮበላነት ባህሪ እርቃን ያወጣ ነው ተባለ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከውጭ ምንዛሬ  ገበያ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ምርመራ ሊካሄድ የሚችልባቸው በርካታ አግባቦች እንደሚኖሩ ነው።
ራሱን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ” የሚለው አገዛዝ ከቦንድ ሽያጭ ጋር በተያያዘ ሰሞኑንን ይፋ የሆነበት ዜና “ነጻ አውጪው ሃይል” አሁንም ከጫካ አስተሳሰብ አለመላቀቁን የሚያመለክት እንደሆነ ተጠቆመ። በፍርድቤት ተከስሶ እና ጉሮሮውን ታንቆ ከውርደት ጋር በርካታ የገንዘብ ክፍያ ውስጥ ከመግባቱ በፊት “ጥፋተኛ ነኝ፤ ፍርድቤት አትውሰዱኝ፤ ያላችሁኝን አደርጋለሁ” በማለት ተስማምቶ ራሱን ለክፍያ አዘጋጅቷል፡፡SEC-Headquarters-1
በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል (SEC) Securities and Exchange Commission (የዋስትናዎችና ልውውጥ ኮሚሲዮን) ተብሎ የሚጠራው የአሜሪካ ፌዴራል መንግሥት መሥሪያቤት ከተቋቋም 80ዓመታት ያለፉት ሲሆን ሶስቱ መሠረታዊ ተልዕኮዎቹ ባለሃብቶችን መከላከል፤ የፋይናንስ ገበያው በሥርዓት፣ በብቃትና በእኩልነት እንዲካሄድ ማድረግና የካፒታል ምስረታን ማበረታታት ናቸው፡፡
ኮሚሽኑ ሰኔ 1፤2008ዓም (June 8, 2016) ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በማለት የጠራው ህወሃት/ኢህአዴግ የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (በቀድሞ ስሙ የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን) በአሜሪካ ውስጥ ያልተመዘገቡ ቦንዶችን በመሸጥ ለፈጸመው ወንጀል 6.5 ሚሊዮን ዶላር (በግምት 150ሚሊዮን ብር) ለመክፈል መስማማቱን ገልጾዋል፡፡
በተለምዶ “የአባይ ቦንድ” ተብሎ የሚጠራውን አሜሪካ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለ አሜሪካ መንግሥትና ያለ ኮሚሽኑ ፍቃድ መሸጡ በማስረጃ ሲረጋገጥ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከማምራቱ በፊት Abay-bondህወሃት 6.5 ሚሊዮን ዶላር ለኮሚሽኑ ለመክፈል መስማማቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ አንዳንድ ወገኖች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ቢመራ ኖሮ ከሚያስከትለው ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሣራ በተጨማሪ የቅጣቱ መጠን ከዚህ በእጅጉ እንደሚልቅ ያስረዳሉ፡፡ ሁኔታው ያላማረው ህወሃት ከጠበቆች በተሰጠው ሙያዊ አስተያየት በመነሳት ጥፋቱን አምኖ ክሱን በስምምነት ለመዝጋት መወሰኑን ስለ ጉዳዩ በቅርበት የሚያውቁ ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት ጠቁመዋል፡፡
ጉዳዩ በሕግ የሚታይ በመሆኑ ኮሚሽኑ ይፋ ያደረገው የክስ ማመልከቻ ላይ በግልጽ እንዳመለከተው ኮርፖሬሽኑ እኤአ ከ2011 እስከ 2014 ድረስ ያለ አንዳች ፈቃድ በአሜሪካ በተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች ሕገወጥ ቦንድ ሲሸጥ ቆይቷል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው “ኤምባሲ” (የኢህአዴግ ጽ/ቤት) ድረገጽ፤ እንዲሁም የተለያዩ የሬዲዮና የቲቪ ማስታወቂያዎችን መጠቀሙን ገልጾዋል፡፡ (ኮሚሽኑ ያወጣው ባለሰባት ገጽ የክስ መረጃ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡)
ከሚያዚያ 2011 ጀምሮ በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች በተሸጠው የአባይ ቦንድ አማካኝነት የተሰበሰበው የገንዘብ መጠን ለምሳሌ ያህል ከዚህ የሚከተለው እንደነበር የክሱ ማመልከቻ በግልጽ ያስረዳል፡፡ (የገንዘብ መጠኑ በአሜሪካ ዶላር ነው)
ሃይለማርያም ደሳለኝ በዋሽንግተን ዲሲ ለአባይ ግድብ ቦንድ ተሸጦ የተሰበሰበውንና በመጪዎቹ 30 ቀናት ውስጥ የሚመለሰውን ሰኔ 2012 በተቀበሉበት ወቅት፤ (ፎቶ ምንጭ፡ tigraionline.com)
ሃይለማርያም ደሳለኝ በዋሽንግተን ዲሲ ለአባይ ግድብ ቦንድ ተሸጦ የተሰበሰበውንና በመጪዎቹ 30 ቀናት ውስጥ የሚመለሰውን ሰኔ 2012 በተቀበሉበት ወቅት፤ (ፎቶ ምንጭ፡ tigraionline.com)
ነሐሴ 2011፤ በዴንቨር ኮሎራዶ፤ $130,000.00
ሰኔ 2012፤ በዋሽንግተን ዲሲ፤ $1,500,000.00
ሰኔ 2012፤ በሺካጎ ኤሌኖይ፤ $110,000
ሚያዚያ 2013፤ ሳን ዲያጎ ካሊፎርኒያ፤ $43,000
ሚያዚያ 2013፤ ሒውስተን ቴክሳስ፤ $50,000
ግንቦት 2013፤ ኒው ዮርክ ከተማ ኒው ዮርክ፤ $100,000
ይህ እንደ አመላካች ሆኖ የተሠራ መዘርዝር የቦንዱ ሽያጭ በኤምባሲው ስፖንሰር አድራጊነት በሕዝባዊ አዳራሾች የተሰበሰበውን ለማሳየት የቀረበ ነው፡፡ በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ትኩረት ያደረገው ሽያጭ በሬዲዮና በቲቪ እንዲሁም በኤምባሲውና በሌሎች መንገዶች መቅረቡን የክሱ ማስረጃ ያመለክታል፡፡
ቦንዱ የሚወልድበት ዓመት ከደረሰ በኋላ በየስድስት ወሩ ወለድ የሚከፈል መሆኑን ገዢዎች ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚያስገቡት የማስታወቂያ መመሪያ ላይ የተመለከተ ሲሆን ክፍያው በቀጥታ ወደ ባንክ ሒሳባቸው ወይም ባንክ ቤቱ ድረስ በመቅረብ መቀበል ከሚለው አንዱን በመምረጥ ከ3,100 (ሶስት ሺህ አንድ መቶ) በላይ የሚሆኑ በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከ$5 እስከ $10,000 (ከአምስት እስከ አስር ሺህ ዶላር) ዋጋ ያለውን ቦንድ መግዛታቸውን የኮሚሽኑ የክስ መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዞ እነዚሁ ገዢዎች ያወጡት አጠቃላይ ገንዘብ $5,800,000.00 (አምስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ ዶላር) እንደሆነና ከገዢዎቹ መካከል 64 በመቶው የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
አገር በዘፈቀደ የሚመራው ህወሃት/ኢህአዴግ ይህንን ሕገወጥ ቦንድ ሉዓላዊነቷ በተከበረ አገር ላይ ሲሸጥ በአገር ውስጥ እንደሚያደርገው በአሜሪካም ማንአለብኝነቱን ለማሳየት መሞከሩ ድንበር ዘለል ሕገወጥነቱን እና ወራዳነቱን ያመለክታል የሚሉ ወገኖች ይህ እንደ አገር “አሳፋሪ” ነው ይላሉ፡፡ ቢያንስ “የተማሩ” የሚላቸው “ሚኒስትሮቹና ዴኤታዎቹ” እንዲሁም ከአምባሳደሩ ጀምሮ degree millበተዋረድ ያሉ የኤምባሲው ሹማምንት ይህንን አስቀድመው ለማስቆም ወይም ህጋዊ እንዲሆን ለማድረግ አለመቻላቸው “የዲግሪ ወፍጮቤት ምሩቃን” መሆናቸውን በገሃድ የሚመሰክር፤ ህወሃት/ኢህአዴግም እስካሁን በሕገ አራዊት የሚመራ ዋልጌ መሆኑን ያለተጨማሪ ማስረጃ ገሃድ ያወጣ ተግባር ነው በማለት እነዚሁ ወገኖች ምሬታቸውን ይናገራሉ፡፡
ኮሚሽኑ ባቀረበው ማመልከቻና ህወሃት በፍርድ ቤት ከመከሰሱ በፊት በተስማማው መሠረት የክሱ ትዕዛዝ ከወጣበት ሰኔ 1፤2008ዓም (June 8, 2016) ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ “የበላውኸውን ትፋ” ተብሏል፡፡ በዚህም መሠረት ህወሃት/ኢህአዴግ $6,448,854.87 (በዶላር ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ አራት ሺህ ስምንት መቶ አምሳ አራት ከሰማኒያ ሰባት ሳንቲም) አንዳች ሳይቀንስ በኮሚሽኑ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ገቢ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ህወሃት ከቀነ ገደቡ ቢያልፍ በኮሚሽኑ ሕገ ደንብ መሠረት ከነወለዱ እንዲከፍል የሚገደድ መሆኑን የክሱ ማስረጃ ጨምሮ ያብራራል፡፡ ይህ ከተጠናቀቀ በኋላ በሚቀርበው ማስረጃ መሠረት ቦንዱን የገዙ ግለሰቦች ገንዘባቸው (ተገቢም ከሆነ ከነወለዱ) እንዲመለስ የሚደረግበት ሂደት እንደሚቀጥል መረጃው ጨምሮ ያስረዳል፡፡ የሁኔታውን ግዝፈትና የሚያደርሰውን ኪሣራ ጫና የተመለከቱ ወገኖች “ህወሃት ሰኔና ሰኞ ሳያስበው ገጥመውበታል” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡bond 2014
ውሳኔውን ያስቆጨው አይጋፎረም “ጽንፈኛው ዳያስፖራ (በዚህ ክስ) ያሸነፈ ሊመስለው ይችል ይሆናል፤ ነገርግን ያሸነፈችው ኢትዮጵያ ነች” በማለት ድንቁርና በለገሰው ድፍረት የህወሃትን መንበርከክ እንደ ሽንፈትን አልቀበልም ብሏል፡፡ ከዚህም አልፎ በዚሁ ድንቁርና በመነዳት “አሁን በሕጋዊ መልኩ ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ትሰበስባለች” በማለት ፍቅረ ህወሃት ህልሙን በኢትዮጵያ ስም በማስታወቅ ሰዎችን እንደገና ወደገደል የሚመራ ዕቅዱን ይፋ አድርጓል፡፡ አገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ቀውስ ውስጥ ባለችበትና የዱቤ ደብዳቤ (ኤል.ሲ.) ለመፍቀድ እጅግ በርካታ ወራትን ማስቆጠሩ ነጋዴውን ፍጹም እያስመረረና እያከሰረ ባለበት ሁኔታ ህወሃት ሰብስቦ የበላውን እንዲተፋ መገደዱ የሚያስከትለው የፋይናንስና የገንዘብ ኪሣራ አፍቃሪ ህወሃቶችን እምብዛም ያስጨነቀ አይመስልም፡፡ የጉዳቱን መጠን የሚያውቁት ግን የጠገገ ቁስሉን እንደገና ሲያደሙበት የጣዕር ሲቃ እንደሚያሰማ ስስ ብልታቸው ላይ መመታታቸውን የተረዱ ጩኸታቸው ከሩቅ ይሰማል፡፡
የዛሬ አምስት ዓመት የቦንዱ ሽያጭ ይፋ በሆነ ጊዜ በወቅቱ የንግድ ባንክ ማመልከቻዎችንና የቦንድ ግዢ መመሪያዎችን አባሪ በማድረግ በጉዳዩ ላይ ባለሙያ ለሆነ ጠበቃ የማስተላለፍ ሥራቸውን የሰሩ ይህ ዓይነቱ ጉዳይ ተጠናክሮ መቀጠል ቢችል ህወሃትን ያለብዙ ችግር ማንበርከክ የሚቻል እንደሆነ አስረግጠው ይናገራሉ፡፡ ቀላሉ መንገድ የዶላሩን መስመር መከተል ብቻ ነው፤ እዚያ መስመር ላይ ህወሃትን ማግኘት ብዙም አይከብድም በማለት ሰሚ ባያገኙም አሁንም ይመክራሉ፡፡ ክቡር ከሆነው የሰው ህይወት ይልቅ ገንዘብ አምላኩ የሆነው ህወሃት የአገርን ክብር ያዋረደውና ዜጎችን በእብሪት እየረገጠ ያለው በገንዘብ ኃይል ነው፡፡ በገንዘብ መከታ ዜጎችን ድሃ ያደርጋል፤ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ያፈርሳል፤ ታማኝ ተቃዋሚ ይመሠርታል፤ ያደኸየውን “ያጠግብና” ተገዢ ያደርጋል፤ ሕገወጥ ዳኞችን ይሾማል፤ ሕግ ያወጣል፤ ሕግን በፍትህ ስም ያረክሳል፤ ፍትህንም በሕግ አንቀጽ ያዋርዳል፤ እስከ ዓለምአቀፍ ቦታዎች ድረስ በገንዘብ ኃይል አሽቃባጮቹንና ተላላኪዎቹን ያስሾማል፤ …፡፡ ህወሃት ለጌቶቹ በገንዘብ የተገዛና አንዳች ክብር የሌለው ወራዳ ስለሆነ የገንዘብን ጥቅም ከማንም በላይ ያውቀዋል፡፡ ይህንን በውል የሚረዱ ወገኖች ደግሞ የህወሃትን የገንዘብ ምንጭ በተቻለው ሁሉ ለማድረቅ ሙከራው ቢቀጥል በገንዘብ ከገዛቸው ተራ ካድሬዎች ጀምሮ እርስበርስ መበላላት መጀመራቸው አይቀሬ ይሆናል ይላሉ፡፡
ከዝግጅት ክፍሉ፤ አገራችን እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ ዓይነት በወንበዴ አስተሳሰብ የሚመራ ቡድን የምትገዛ ባትሆን ኖሮ ይህ ዜና ለፍጆታ መቅረብ የሚያስፈልገው አልነበረም፡፡ ይልቁንም እንደ አገርና እንደ ዜጋ ይህ የሁላችንም ገመና በመሆኑ ሁላችንንም የሚያሳፍር መሆን ይገባው ነበር፡፡ ከታላቅ አገራዊ ቁጭትና ጥልቅ ሃዘን ጋር ይህንን ዜና ለፍጆታ ማቅረባችንን አንባቢዎቻችን እንዲረዱልን እንፈልጋልን፡፡
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Wednesday, June 8, 2016

Ethiopia: Parliament approved another cyber law to silence dissent

June8,2016

Ethiopia OKs Law Against Sharing Defamatory Speech Online

(AP) Ethiopia’s parliament on Tuesday approved a law to imprison people who distribute defamatory speech, pornography and spam online, a move that bloggers and activists said is meant to silence dissent.Ethiopian Arrests for Internet Security Training
The law’s most severe penalty is 10 years’ imprisonment for sharing pornography online. Sharing defamatory speech or spam gets at least three years in prison.
Ethiopia’s cybersecurity officials have said the country is subject to more than 1,000 cyberattacks per day, and the government has said the new law will enable it to prosecute such crimes more efficiently.
But rights groups have accused the East African country of restricting freedom of expression and using spyware against dissidents living overseas. An Ethiopian court last month charged an opposition activist over his Facebook posts.
Daniel Berhane, a popular blogger, said the new law is a concern to him as an editor of a website that has several contributors and is an active user of social media.
“It jumbled provisions for cyberattacks with provisions about content, thereby paving the way for a heavy-handedness on online expression,” he said.

Saturday, June 4, 2016

ኢትዮጵያ የኤርትራ ተቃዋሚዎችን እና “ጃሃዲስቶችን “ለማስታጠቅ ፣ ለመደጎም ቃል ገባች

June3,2016
ይሔ “የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ቅኝት”ከየትኛው መንገድ ያደረሰን ይሆን?
መቀመጫውን በፈረንሳይ /ፓሪስ በማድረግ ምስጢራዊ ነክ በሆኑ ዲፕሎማሲያዊ ፣ ወታደራዊ እና የኢንቨስትምነት ጉዳዮች ዙሪያ የሚያውጠነጥነው “አፍሪካ ኢንተለጀንሲ” የተባለው መጽሄት በቅርቡ እንደዘገበው በአዲስ አበባ እና በአሰመራ ገዢዎች መካከል ቀደም ሲል የተፈጠረው ቅራኔን ተከተሎ የ ኢ ሕ አዲግ መንግስት የኤርትራው አቻው ተቃዋሚዎች ጥምረት የሆነው የኤርትራ ብሔራዊ ካውንስል ለዲሞክራሲ እና ለለውጥ (Eritrean National Council for Democractic Change,ENCDC) ለማቀራረብ ጥረት በማድረግ ላይ ነው ሲል አሰነብቧል ።
ዘገባው የ ኢ ሕ አ ዲ ግ መንግስት የ ኤርትራ ተቃዋሚዎችን በአዲስ መልክ ለመቅረብ ከወሳኔ የደረሰበትን ምክንያት ዘገባው ሲያስረዳ “በቅርቡ በ ኢትዮ- ኬኒያ ድንበር አካባቤ የኤርትራ ተቃዋሚ አባላት መታስራቸውን ተክትሎ ነው።” የተባለ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ የቀድሞ የአስመራ መንግስት ደፕሎማቶች እና በውጪ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ያዋቀሩት የኤርትራዊያኖች ብሄራዊ የ ውይይት መድርክ(Eritrean Forum for National Dialogue ,EFND/Medrek) አንሰሳሸነት በኬኒያው ናይሮቢ ባለፈው ሃዳር 28 እስከ 29 የቀድሞው ጄነራል መሰፍን አማን የመሩት አስር የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች የተካሄደው ስብሰባ በመንተርሰስ አጋጣሚውን የተጠቀመው የወቅቱ የኢትዮጵያው ገዢ መንግስት ፣ኢሕ አዲግ፣ ለኤርትራ ተቃዋሚዎች ቀደም ሲል ሲያቀማማ የነበረውን የገንዘብ እና የሎጀስቲክ እገዛውን በአዲስ መልክ ለማጠናከር ቃል መግባቱን የጠቀሰው ዘገባው ኢሕ አዲግ ለአስመራ መንግስት ተቃቃሚዎች “እረዳልሁ” ብሏል የተባለው የገንዘብ ምንጩ ፣መጠኑ እና የሎጀሰቲክ ደጎማው አይነት በተመለከተ ለጊዜው በውል አልተገለጸም ። በአንዳንድ የአሰመራ መንግስት ደጋፊዎች እይታ ከእነዚህ ተደራጁ እና የኢ ሕ አዲግ ልገሳ ሊቸራቸው ነው ከተባሉት የኢርትራ ተቃዋሚዎች መካከል እራሱን የኤርትራ እስላሚክ ጅሃድ እንቀሰቃሴ/Eritrean Islamic Jihad Movemnet በሎ የሚጠራው ቡድን ቢን ላዲንአ ከመሰረተው አክራሪው የአልቃይዳ ቡድን ጋር ቁርኝት አለው እስከማለት ደርሰዋል። ይህ አባባል እና ጥርጣሬ ግን በድርጁቱ በኩል ምላሽ አልተሰጠበትም አሊያም በነጻ ምንጮች አልተረገጋጠም።
የዛሬ 25 አመት የደርግ መንግስትን በመገርሰስ በአ/አ እና በእስመራ ላይ የራሳቸውን መንግስታት በመመሰረት በጦርነት፣ በችግር እና በሰደት ይታወቅ የነበረው የአፍሪካ ቀንዱ አካባቢን በአንጻራዊ ሰላም ተምሳሌነት ለመቀየር ቃል የገቡት ኢ ሕ አዲግ እና ሻቢያ ዛሬ ለሕዝባቸው የሰላም ፣የመረጋጋት እና የእድገት ባለቤት እንዳደረጉት ቢሰብኩም በገሃዱ አለም ያለው ሁኔታ ግን በተቃራኔው እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ ።
በተለይ ደግሞ በድንበር ይገባኛል ጥያቄ ሳቢያ እኤ አ ከ 1998 እስከ 2000 በዘለቀው ውጊያ ሳቢያ ከሁለቱም ሕዝቦች ውስጥ ከሰባ ሺህ በላይ ወጣቶች ሕይወታቸውን የገበሩበት ( በዚህ አጋጣሚ ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ በሰሞነኛው ንግግራቸው ከ 20ሺህ በላይ ወጣት ኤርትራዊያኖች ማለቃቸውን/መሰዋት መሆናቸውን በግላጭ አምነዋል) ዛሬም ድረስ የጦርነቱ ዳመና ሳይገፈፍ “ጦርነት የለም ሸላምም የለም “ በሚል ፍልስፈና የተዘፈቁት ሁለቱም ገዢዎች ድንበሮቹ በወታደሮች እና በከባድ መሳሪያዎች በሚጠበቁበት በእሁኑ ወቅት አንዱ የሌላኛውን ተቃዋሚዎችን በማደረጀት፣ በማስታጠቅ እና መንገድ በመምራት ከበትረሰልጣኑ ለማስወገድ የሚያደርጉት እርብርቦሽን ለተመለከተ “ እውን እነዚህ በውስጣቸው ደሞክራሲያዊ ባህሪይ በጭራሽ ያለተላበሱት የአ/አ እና የአሰመራ አምባ ገነን ገዢዎች ለአካባቢው ሰላም ፣ መረጋጋት እና ዲሞክራሲያዊ ስር አት መሰፈን ካላቸው ጽኑ ምኞት የተነሳ ወይስ 'የጠላቴ ጠላት... 'ከሚለው እና ዛሬ አላማችንን ብትንትኗን እያጠፋ ካለው የመጠላለፍ ቅኝት ላለመውጣት አሰበው ነው?” የሚሉ ጥያቄዎችን በሰከነ መንፈስ የሚያስተጋቡ ወገኖች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

Friday, June 3, 2016

Girl, 9, sues the government over Holloway father being held on death row

June 3,2016

Menabe: ‘They would try harder if my father was a white Englishman’. Right: Andargachew ‘Andy’ Tsege is being held in Ethiopia
Menabe: ‘They would try harder if my father was a white Englishman’. Right: Andargachew ‘Andy’ Tsege is being held in Ethiopia
HE nine-year-old daughter of a Holloway man who has been held on death row in Ethiopia for two years is suing the British government over its alleged failure to demand his release.
Lawyers for Menabe Andargachew, from Clerkenwell, have begun judicial review proceedings in the High Court against the Foreign Office over ministers’ handling of the case of her father, Andargachew “Andy” Tsege.
Mr Tsege, a 61-year-old British citizen, was kidnapped and rendered to Ethiopia by forces of that country in June 2014. He remains held there under a sentence of death imposed in absentia in 2009 in relation to his political opposition to the Ethiopian government.
“I’m pretty sure that every British person deserves the protection of the UK government but my father is not receiving this,” said Menabe, who attends Hugh Myddelton primary school and dreams of a career on Broadway.
“After two years he is finally going to get a lawyer but I don’t think it’s going to actually help my dad. The government needs to demand he comes back – they should have done it ages ago.”
The only contact Menabe, her twin brother Yilak and sister Helawit, 16, who live with their mother Yemi Hailemariam, have had with their father since he was abducted was a single phone call in December 2014.
Foreign Secretary Philip Hammond, who was in Ethiopia this week, said Mr Tsege was “top of the agenda” at meetings with the government. However, while “securing assurances” that the activist would finally be granted access to a lawyer he did not demand Mr Tsege’s release.
“We had been living in hope but this really feels like a slap in the face,” Ms Hailemariam said. “There’s no way someone who has been detained in this way and who was kidnapped is not going to have a fair trial. The problem is that these people don’t have fair trials.
“To think he can get justice there is an insult to us and the subtext, it feels, is that we are not fully British.”
Menabe added: “I think they would try harder if my father was a white Englishman, definitely.”  The family’s case is that, given the illegality of Mr Tsege’s kidnap, detention and death sentence, the UK’s decision not to ask for Mr Tsege’s release is unlawful.
Ms Hailemariam added: “The government is trying to justify the unjustifiable and I think this is unsustainable, so we just have to keep on fighting.”
Speaking from Ethiopia after his meetings on Wednesday, Mr Hammond said: “I have now received a commitment from the Prime Minister that Mr Tsege will be allowed access to independent legal advice to allow him to discuss options under the Ethiopian legal system.
“At my request, a senior Foreign Office official travelling with me was given access to Mr Tsege in prison. Following that visit, I am satisfied he is not being ill-treated and that he is receiving regular visits from family members in Ethiopia.”
Mr Tsege, a naturalised British citizen who has lived in London since 1979, is an outspoken critic of the Ethiopian regime and a member of the exiled opposition group Ginbot 7.
The jazz fan was on his way to an opposition conference in Eritrea when he was kidnapped and handed over to Ethiopian authorities.
Last year, Menabe’s sister Helawit won a human rights award for a play she wrote with her friends about her father’s plight.
Menabe was chosen by her mother to head up the legal challenge because of her articulate campaigning on her father’s behalf. She is being represented by Clerkenwell-based law firm Leigh Day.

Source: (Islington Tribune)

Wednesday, June 1, 2016

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም ግምገማ ላይ ወድቀዋል

June 1,2016
Tewodros Adhanom
ከልዑል ዓለሜ
እጆቹን አስረዝሞ ለመዝረፍ ይመቸዉ ዘንድ የአለም ጤና ድርጅትን ለመምራት አዲስ አቅጣጫ የቀየሰዉ የትግራይ ነጻ አዉጪዉ ቡድን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ የዉጭ ሐገራት በመዘዋወወር የአለም ጤና ርጅትን ለመምራት ቅስቀሳ ሲያደርግ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።
ቅዳሜ እለት ወደ አዲስ አበባ የተመለሰዉ ቴዎድሮስ አድሐኖም ሁለት ቀላል መሳሪያ የታጠቁ ወጣቶች የሚጠብቁት ሲሆን የታርጋ ቁጥሩ ኮድ 2_69183 አአ የሆነ ዘመናዊ ላንድ ሮቨር አዉቶሞቢል ተመድቦለት ይንቀሳቀሳል።
አምባሳደር ሙሌ የካቢኔ ዋና ሹሙና አምባሳደር ቦጋለም ከቴድሮስ አድሐኖም ጋር አብረዉ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን አቶ ህላዌ ዩሱፍ እና የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ከቴድሮስ አድሐኖም ጋር በአንድነት ሆነዉ በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ዙሪያ እየደረሰ ያለዉን የአገልግሎት ኪሳራ በተመለከተ ዉይይት ከማድረጋቸዉ በተጨማሪ በህዝቦች ሽግግር ዙሪያ ከእስራኤል ዲፕሎማኦች ጋር ተወያይተዋል።
የመላዉ ሐገራችንን አንጡራ ሐብት ከግል ጥቅማቸዉ አንጻር እንዳሻ ሲጠቀሙበት ማየት እጅግ ያሳዝናል በማለት ቁጭታቸዉን የገለጹልን ባለስልጣን ከእንግዲህ ወዲህ የትግራይ ነጻ አዉጪዉ ቡድን ሐገራችንን የምምራት ብቅት እንደሌለዉና የሐገሪቷ ብሔራዊ ደንነት አደጋ ላይ መዉደቁን አሳስበዉ ኢትዮጵያን ከአደገኛ ችግር ከመታደግ አንጻር ወያኔ ስልጣኑን ለሰፊዉ ህዝብ እንዲያስረክብ አስጠንቅቀዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!