Saturday, June 11, 2016

ህወሃት ጉሮሮውን ሳይታነቅ የበላውን በ30 ቀን “እተፋለሁ” አለ

June 112016
“ህወሃት ሲፈጠርም ጀምሮ ዓለምአቀፋዊ ወሮበላ ነው”
dollar-
ህወሃት በቦንድ ስም ህግ ጥሶ ሲሰበስብ የነበረውን ገንዘብ ክስ ተመስርቶበት ጉሮሮው ሳይታነቅ ወዶ ለመትፋት መስማማቱ ታወቀ። ድርጊቱ ኢትዮጵያን መሳቂያ፣  የምትተዳደረው በህገ አራዊት መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑንና የህወሃትን የወሮበላነት ባህሪ እርቃን ያወጣ ነው ተባለ። ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከውጭ ምንዛሬ  ገበያ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ ምርመራ ሊካሄድ የሚችልባቸው በርካታ አግባቦች እንደሚኖሩ ነው።
ራሱን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ” የሚለው አገዛዝ ከቦንድ ሽያጭ ጋር በተያያዘ ሰሞኑንን ይፋ የሆነበት ዜና “ነጻ አውጪው ሃይል” አሁንም ከጫካ አስተሳሰብ አለመላቀቁን የሚያመለክት እንደሆነ ተጠቆመ። በፍርድቤት ተከስሶ እና ጉሮሮውን ታንቆ ከውርደት ጋር በርካታ የገንዘብ ክፍያ ውስጥ ከመግባቱ በፊት “ጥፋተኛ ነኝ፤ ፍርድቤት አትውሰዱኝ፤ ያላችሁኝን አደርጋለሁ” በማለት ተስማምቶ ራሱን ለክፍያ አዘጋጅቷል፡፡SEC-Headquarters-1
በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል (SEC) Securities and Exchange Commission (የዋስትናዎችና ልውውጥ ኮሚሲዮን) ተብሎ የሚጠራው የአሜሪካ ፌዴራል መንግሥት መሥሪያቤት ከተቋቋም 80ዓመታት ያለፉት ሲሆን ሶስቱ መሠረታዊ ተልዕኮዎቹ ባለሃብቶችን መከላከል፤ የፋይናንስ ገበያው በሥርዓት፣ በብቃትና በእኩልነት እንዲካሄድ ማድረግና የካፒታል ምስረታን ማበረታታት ናቸው፡፡
ኮሚሽኑ ሰኔ 1፤2008ዓም (June 8, 2016) ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በማለት የጠራው ህወሃት/ኢህአዴግ የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (በቀድሞ ስሙ የኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን) በአሜሪካ ውስጥ ያልተመዘገቡ ቦንዶችን በመሸጥ ለፈጸመው ወንጀል 6.5 ሚሊዮን ዶላር (በግምት 150ሚሊዮን ብር) ለመክፈል መስማማቱን ገልጾዋል፡፡
በተለምዶ “የአባይ ቦንድ” ተብሎ የሚጠራውን አሜሪካ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለ አሜሪካ መንግሥትና ያለ ኮሚሽኑ ፍቃድ መሸጡ በማስረጃ ሲረጋገጥ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከማምራቱ በፊት Abay-bondህወሃት 6.5 ሚሊዮን ዶላር ለኮሚሽኑ ለመክፈል መስማማቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ አንዳንድ ወገኖች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ቢመራ ኖሮ ከሚያስከትለው ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሣራ በተጨማሪ የቅጣቱ መጠን ከዚህ በእጅጉ እንደሚልቅ ያስረዳሉ፡፡ ሁኔታው ያላማረው ህወሃት ከጠበቆች በተሰጠው ሙያዊ አስተያየት በመነሳት ጥፋቱን አምኖ ክሱን በስምምነት ለመዝጋት መወሰኑን ስለ ጉዳዩ በቅርበት የሚያውቁ ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት ጠቁመዋል፡፡
ጉዳዩ በሕግ የሚታይ በመሆኑ ኮሚሽኑ ይፋ ያደረገው የክስ ማመልከቻ ላይ በግልጽ እንዳመለከተው ኮርፖሬሽኑ እኤአ ከ2011 እስከ 2014 ድረስ ያለ አንዳች ፈቃድ በአሜሪካ በተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች ሕገወጥ ቦንድ ሲሸጥ ቆይቷል፡፡ ይህንንም ለማድረግ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው “ኤምባሲ” (የኢህአዴግ ጽ/ቤት) ድረገጽ፤ እንዲሁም የተለያዩ የሬዲዮና የቲቪ ማስታወቂያዎችን መጠቀሙን ገልጾዋል፡፡ (ኮሚሽኑ ያወጣው ባለሰባት ገጽ የክስ መረጃ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡)
ከሚያዚያ 2011 ጀምሮ በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች በተሸጠው የአባይ ቦንድ አማካኝነት የተሰበሰበው የገንዘብ መጠን ለምሳሌ ያህል ከዚህ የሚከተለው እንደነበር የክሱ ማመልከቻ በግልጽ ያስረዳል፡፡ (የገንዘብ መጠኑ በአሜሪካ ዶላር ነው)
ሃይለማርያም ደሳለኝ በዋሽንግተን ዲሲ ለአባይ ግድብ ቦንድ ተሸጦ የተሰበሰበውንና በመጪዎቹ 30 ቀናት ውስጥ የሚመለሰውን ሰኔ 2012 በተቀበሉበት ወቅት፤ (ፎቶ ምንጭ፡ tigraionline.com)
ሃይለማርያም ደሳለኝ በዋሽንግተን ዲሲ ለአባይ ግድብ ቦንድ ተሸጦ የተሰበሰበውንና በመጪዎቹ 30 ቀናት ውስጥ የሚመለሰውን ሰኔ 2012 በተቀበሉበት ወቅት፤ (ፎቶ ምንጭ፡ tigraionline.com)
ነሐሴ 2011፤ በዴንቨር ኮሎራዶ፤ $130,000.00
ሰኔ 2012፤ በዋሽንግተን ዲሲ፤ $1,500,000.00
ሰኔ 2012፤ በሺካጎ ኤሌኖይ፤ $110,000
ሚያዚያ 2013፤ ሳን ዲያጎ ካሊፎርኒያ፤ $43,000
ሚያዚያ 2013፤ ሒውስተን ቴክሳስ፤ $50,000
ግንቦት 2013፤ ኒው ዮርክ ከተማ ኒው ዮርክ፤ $100,000
ይህ እንደ አመላካች ሆኖ የተሠራ መዘርዝር የቦንዱ ሽያጭ በኤምባሲው ስፖንሰር አድራጊነት በሕዝባዊ አዳራሾች የተሰበሰበውን ለማሳየት የቀረበ ነው፡፡ በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ትኩረት ያደረገው ሽያጭ በሬዲዮና በቲቪ እንዲሁም በኤምባሲውና በሌሎች መንገዶች መቅረቡን የክሱ ማስረጃ ያመለክታል፡፡
ቦንዱ የሚወልድበት ዓመት ከደረሰ በኋላ በየስድስት ወሩ ወለድ የሚከፈል መሆኑን ገዢዎች ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚያስገቡት የማስታወቂያ መመሪያ ላይ የተመለከተ ሲሆን ክፍያው በቀጥታ ወደ ባንክ ሒሳባቸው ወይም ባንክ ቤቱ ድረስ በመቅረብ መቀበል ከሚለው አንዱን በመምረጥ ከ3,100 (ሶስት ሺህ አንድ መቶ) በላይ የሚሆኑ በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከ$5 እስከ $10,000 (ከአምስት እስከ አስር ሺህ ዶላር) ዋጋ ያለውን ቦንድ መግዛታቸውን የኮሚሽኑ የክስ መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዞ እነዚሁ ገዢዎች ያወጡት አጠቃላይ ገንዘብ $5,800,000.00 (አምስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ ዶላር) እንደሆነና ከገዢዎቹ መካከል 64 በመቶው የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ያስረዳል፡፡
አገር በዘፈቀደ የሚመራው ህወሃት/ኢህአዴግ ይህንን ሕገወጥ ቦንድ ሉዓላዊነቷ በተከበረ አገር ላይ ሲሸጥ በአገር ውስጥ እንደሚያደርገው በአሜሪካም ማንአለብኝነቱን ለማሳየት መሞከሩ ድንበር ዘለል ሕገወጥነቱን እና ወራዳነቱን ያመለክታል የሚሉ ወገኖች ይህ እንደ አገር “አሳፋሪ” ነው ይላሉ፡፡ ቢያንስ “የተማሩ” የሚላቸው “ሚኒስትሮቹና ዴኤታዎቹ” እንዲሁም ከአምባሳደሩ ጀምሮ degree millበተዋረድ ያሉ የኤምባሲው ሹማምንት ይህንን አስቀድመው ለማስቆም ወይም ህጋዊ እንዲሆን ለማድረግ አለመቻላቸው “የዲግሪ ወፍጮቤት ምሩቃን” መሆናቸውን በገሃድ የሚመሰክር፤ ህወሃት/ኢህአዴግም እስካሁን በሕገ አራዊት የሚመራ ዋልጌ መሆኑን ያለተጨማሪ ማስረጃ ገሃድ ያወጣ ተግባር ነው በማለት እነዚሁ ወገኖች ምሬታቸውን ይናገራሉ፡፡
ኮሚሽኑ ባቀረበው ማመልከቻና ህወሃት በፍርድ ቤት ከመከሰሱ በፊት በተስማማው መሠረት የክሱ ትዕዛዝ ከወጣበት ሰኔ 1፤2008ዓም (June 8, 2016) ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ “የበላውኸውን ትፋ” ተብሏል፡፡ በዚህም መሠረት ህወሃት/ኢህአዴግ $6,448,854.87 (በዶላር ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ አራት ሺህ ስምንት መቶ አምሳ አራት ከሰማኒያ ሰባት ሳንቲም) አንዳች ሳይቀንስ በኮሚሽኑ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ገቢ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ህወሃት ከቀነ ገደቡ ቢያልፍ በኮሚሽኑ ሕገ ደንብ መሠረት ከነወለዱ እንዲከፍል የሚገደድ መሆኑን የክሱ ማስረጃ ጨምሮ ያብራራል፡፡ ይህ ከተጠናቀቀ በኋላ በሚቀርበው ማስረጃ መሠረት ቦንዱን የገዙ ግለሰቦች ገንዘባቸው (ተገቢም ከሆነ ከነወለዱ) እንዲመለስ የሚደረግበት ሂደት እንደሚቀጥል መረጃው ጨምሮ ያስረዳል፡፡ የሁኔታውን ግዝፈትና የሚያደርሰውን ኪሣራ ጫና የተመለከቱ ወገኖች “ህወሃት ሰኔና ሰኞ ሳያስበው ገጥመውበታል” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡bond 2014
ውሳኔውን ያስቆጨው አይጋፎረም “ጽንፈኛው ዳያስፖራ (በዚህ ክስ) ያሸነፈ ሊመስለው ይችል ይሆናል፤ ነገርግን ያሸነፈችው ኢትዮጵያ ነች” በማለት ድንቁርና በለገሰው ድፍረት የህወሃትን መንበርከክ እንደ ሽንፈትን አልቀበልም ብሏል፡፡ ከዚህም አልፎ በዚሁ ድንቁርና በመነዳት “አሁን በሕጋዊ መልኩ ኢትዮጵያ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ትሰበስባለች” በማለት ፍቅረ ህወሃት ህልሙን በኢትዮጵያ ስም በማስታወቅ ሰዎችን እንደገና ወደገደል የሚመራ ዕቅዱን ይፋ አድርጓል፡፡ አገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ቀውስ ውስጥ ባለችበትና የዱቤ ደብዳቤ (ኤል.ሲ.) ለመፍቀድ እጅግ በርካታ ወራትን ማስቆጠሩ ነጋዴውን ፍጹም እያስመረረና እያከሰረ ባለበት ሁኔታ ህወሃት ሰብስቦ የበላውን እንዲተፋ መገደዱ የሚያስከትለው የፋይናንስና የገንዘብ ኪሣራ አፍቃሪ ህወሃቶችን እምብዛም ያስጨነቀ አይመስልም፡፡ የጉዳቱን መጠን የሚያውቁት ግን የጠገገ ቁስሉን እንደገና ሲያደሙበት የጣዕር ሲቃ እንደሚያሰማ ስስ ብልታቸው ላይ መመታታቸውን የተረዱ ጩኸታቸው ከሩቅ ይሰማል፡፡
የዛሬ አምስት ዓመት የቦንዱ ሽያጭ ይፋ በሆነ ጊዜ በወቅቱ የንግድ ባንክ ማመልከቻዎችንና የቦንድ ግዢ መመሪያዎችን አባሪ በማድረግ በጉዳዩ ላይ ባለሙያ ለሆነ ጠበቃ የማስተላለፍ ሥራቸውን የሰሩ ይህ ዓይነቱ ጉዳይ ተጠናክሮ መቀጠል ቢችል ህወሃትን ያለብዙ ችግር ማንበርከክ የሚቻል እንደሆነ አስረግጠው ይናገራሉ፡፡ ቀላሉ መንገድ የዶላሩን መስመር መከተል ብቻ ነው፤ እዚያ መስመር ላይ ህወሃትን ማግኘት ብዙም አይከብድም በማለት ሰሚ ባያገኙም አሁንም ይመክራሉ፡፡ ክቡር ከሆነው የሰው ህይወት ይልቅ ገንዘብ አምላኩ የሆነው ህወሃት የአገርን ክብር ያዋረደውና ዜጎችን በእብሪት እየረገጠ ያለው በገንዘብ ኃይል ነው፡፡ በገንዘብ መከታ ዜጎችን ድሃ ያደርጋል፤ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ያፈርሳል፤ ታማኝ ተቃዋሚ ይመሠርታል፤ ያደኸየውን “ያጠግብና” ተገዢ ያደርጋል፤ ሕገወጥ ዳኞችን ይሾማል፤ ሕግ ያወጣል፤ ሕግን በፍትህ ስም ያረክሳል፤ ፍትህንም በሕግ አንቀጽ ያዋርዳል፤ እስከ ዓለምአቀፍ ቦታዎች ድረስ በገንዘብ ኃይል አሽቃባጮቹንና ተላላኪዎቹን ያስሾማል፤ …፡፡ ህወሃት ለጌቶቹ በገንዘብ የተገዛና አንዳች ክብር የሌለው ወራዳ ስለሆነ የገንዘብን ጥቅም ከማንም በላይ ያውቀዋል፡፡ ይህንን በውል የሚረዱ ወገኖች ደግሞ የህወሃትን የገንዘብ ምንጭ በተቻለው ሁሉ ለማድረቅ ሙከራው ቢቀጥል በገንዘብ ከገዛቸው ተራ ካድሬዎች ጀምሮ እርስበርስ መበላላት መጀመራቸው አይቀሬ ይሆናል ይላሉ፡፡
ከዝግጅት ክፍሉ፤ አገራችን እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ ዓይነት በወንበዴ አስተሳሰብ የሚመራ ቡድን የምትገዛ ባትሆን ኖሮ ይህ ዜና ለፍጆታ መቅረብ የሚያስፈልገው አልነበረም፡፡ ይልቁንም እንደ አገርና እንደ ዜጋ ይህ የሁላችንም ገመና በመሆኑ ሁላችንንም የሚያሳፍር መሆን ይገባው ነበር፡፡ ከታላቅ አገራዊ ቁጭትና ጥልቅ ሃዘን ጋር ይህንን ዜና ለፍጆታ ማቅረባችንን አንባቢዎቻችን እንዲረዱልን እንፈልጋልን፡፡
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Wednesday, June 8, 2016

Ethiopia: Parliament approved another cyber law to silence dissent

June8,2016

Ethiopia OKs Law Against Sharing Defamatory Speech Online

(AP) Ethiopia’s parliament on Tuesday approved a law to imprison people who distribute defamatory speech, pornography and spam online, a move that bloggers and activists said is meant to silence dissent.Ethiopian Arrests for Internet Security Training
The law’s most severe penalty is 10 years’ imprisonment for sharing pornography online. Sharing defamatory speech or spam gets at least three years in prison.
Ethiopia’s cybersecurity officials have said the country is subject to more than 1,000 cyberattacks per day, and the government has said the new law will enable it to prosecute such crimes more efficiently.
But rights groups have accused the East African country of restricting freedom of expression and using spyware against dissidents living overseas. An Ethiopian court last month charged an opposition activist over his Facebook posts.
Daniel Berhane, a popular blogger, said the new law is a concern to him as an editor of a website that has several contributors and is an active user of social media.
“It jumbled provisions for cyberattacks with provisions about content, thereby paving the way for a heavy-handedness on online expression,” he said.

Saturday, June 4, 2016

ኢትዮጵያ የኤርትራ ተቃዋሚዎችን እና “ጃሃዲስቶችን “ለማስታጠቅ ፣ ለመደጎም ቃል ገባች

June3,2016
ይሔ “የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ቅኝት”ከየትኛው መንገድ ያደረሰን ይሆን?
መቀመጫውን በፈረንሳይ /ፓሪስ በማድረግ ምስጢራዊ ነክ በሆኑ ዲፕሎማሲያዊ ፣ ወታደራዊ እና የኢንቨስትምነት ጉዳዮች ዙሪያ የሚያውጠነጥነው “አፍሪካ ኢንተለጀንሲ” የተባለው መጽሄት በቅርቡ እንደዘገበው በአዲስ አበባ እና በአሰመራ ገዢዎች መካከል ቀደም ሲል የተፈጠረው ቅራኔን ተከተሎ የ ኢ ሕ አዲግ መንግስት የኤርትራው አቻው ተቃዋሚዎች ጥምረት የሆነው የኤርትራ ብሔራዊ ካውንስል ለዲሞክራሲ እና ለለውጥ (Eritrean National Council for Democractic Change,ENCDC) ለማቀራረብ ጥረት በማድረግ ላይ ነው ሲል አሰነብቧል ።
ዘገባው የ ኢ ሕ አ ዲ ግ መንግስት የ ኤርትራ ተቃዋሚዎችን በአዲስ መልክ ለመቅረብ ከወሳኔ የደረሰበትን ምክንያት ዘገባው ሲያስረዳ “በቅርቡ በ ኢትዮ- ኬኒያ ድንበር አካባቤ የኤርትራ ተቃዋሚ አባላት መታስራቸውን ተክትሎ ነው።” የተባለ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ የቀድሞ የአስመራ መንግስት ደፕሎማቶች እና በውጪ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ያዋቀሩት የኤርትራዊያኖች ብሄራዊ የ ውይይት መድርክ(Eritrean Forum for National Dialogue ,EFND/Medrek) አንሰሳሸነት በኬኒያው ናይሮቢ ባለፈው ሃዳር 28 እስከ 29 የቀድሞው ጄነራል መሰፍን አማን የመሩት አስር የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች የተካሄደው ስብሰባ በመንተርሰስ አጋጣሚውን የተጠቀመው የወቅቱ የኢትዮጵያው ገዢ መንግስት ፣ኢሕ አዲግ፣ ለኤርትራ ተቃዋሚዎች ቀደም ሲል ሲያቀማማ የነበረውን የገንዘብ እና የሎጀስቲክ እገዛውን በአዲስ መልክ ለማጠናከር ቃል መግባቱን የጠቀሰው ዘገባው ኢሕ አዲግ ለአስመራ መንግስት ተቃቃሚዎች “እረዳልሁ” ብሏል የተባለው የገንዘብ ምንጩ ፣መጠኑ እና የሎጀሰቲክ ደጎማው አይነት በተመለከተ ለጊዜው በውል አልተገለጸም ። በአንዳንድ የአሰመራ መንግስት ደጋፊዎች እይታ ከእነዚህ ተደራጁ እና የኢ ሕ አዲግ ልገሳ ሊቸራቸው ነው ከተባሉት የኢርትራ ተቃዋሚዎች መካከል እራሱን የኤርትራ እስላሚክ ጅሃድ እንቀሰቃሴ/Eritrean Islamic Jihad Movemnet በሎ የሚጠራው ቡድን ቢን ላዲንአ ከመሰረተው አክራሪው የአልቃይዳ ቡድን ጋር ቁርኝት አለው እስከማለት ደርሰዋል። ይህ አባባል እና ጥርጣሬ ግን በድርጁቱ በኩል ምላሽ አልተሰጠበትም አሊያም በነጻ ምንጮች አልተረገጋጠም።
የዛሬ 25 አመት የደርግ መንግስትን በመገርሰስ በአ/አ እና በእስመራ ላይ የራሳቸውን መንግስታት በመመሰረት በጦርነት፣ በችግር እና በሰደት ይታወቅ የነበረው የአፍሪካ ቀንዱ አካባቢን በአንጻራዊ ሰላም ተምሳሌነት ለመቀየር ቃል የገቡት ኢ ሕ አዲግ እና ሻቢያ ዛሬ ለሕዝባቸው የሰላም ፣የመረጋጋት እና የእድገት ባለቤት እንዳደረጉት ቢሰብኩም በገሃዱ አለም ያለው ሁኔታ ግን በተቃራኔው እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ ።
በተለይ ደግሞ በድንበር ይገባኛል ጥያቄ ሳቢያ እኤ አ ከ 1998 እስከ 2000 በዘለቀው ውጊያ ሳቢያ ከሁለቱም ሕዝቦች ውስጥ ከሰባ ሺህ በላይ ወጣቶች ሕይወታቸውን የገበሩበት ( በዚህ አጋጣሚ ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ በሰሞነኛው ንግግራቸው ከ 20ሺህ በላይ ወጣት ኤርትራዊያኖች ማለቃቸውን/መሰዋት መሆናቸውን በግላጭ አምነዋል) ዛሬም ድረስ የጦርነቱ ዳመና ሳይገፈፍ “ጦርነት የለም ሸላምም የለም “ በሚል ፍልስፈና የተዘፈቁት ሁለቱም ገዢዎች ድንበሮቹ በወታደሮች እና በከባድ መሳሪያዎች በሚጠበቁበት በእሁኑ ወቅት አንዱ የሌላኛውን ተቃዋሚዎችን በማደረጀት፣ በማስታጠቅ እና መንገድ በመምራት ከበትረሰልጣኑ ለማስወገድ የሚያደርጉት እርብርቦሽን ለተመለከተ “ እውን እነዚህ በውስጣቸው ደሞክራሲያዊ ባህሪይ በጭራሽ ያለተላበሱት የአ/አ እና የአሰመራ አምባ ገነን ገዢዎች ለአካባቢው ሰላም ፣ መረጋጋት እና ዲሞክራሲያዊ ስር አት መሰፈን ካላቸው ጽኑ ምኞት የተነሳ ወይስ 'የጠላቴ ጠላት... 'ከሚለው እና ዛሬ አላማችንን ብትንትኗን እያጠፋ ካለው የመጠላለፍ ቅኝት ላለመውጣት አሰበው ነው?” የሚሉ ጥያቄዎችን በሰከነ መንፈስ የሚያስተጋቡ ወገኖች ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።

Friday, June 3, 2016

Girl, 9, sues the government over Holloway father being held on death row

June 3,2016

Menabe: ‘They would try harder if my father was a white Englishman’. Right: Andargachew ‘Andy’ Tsege is being held in Ethiopia
Menabe: ‘They would try harder if my father was a white Englishman’. Right: Andargachew ‘Andy’ Tsege is being held in Ethiopia
HE nine-year-old daughter of a Holloway man who has been held on death row in Ethiopia for two years is suing the British government over its alleged failure to demand his release.
Lawyers for Menabe Andargachew, from Clerkenwell, have begun judicial review proceedings in the High Court against the Foreign Office over ministers’ handling of the case of her father, Andargachew “Andy” Tsege.
Mr Tsege, a 61-year-old British citizen, was kidnapped and rendered to Ethiopia by forces of that country in June 2014. He remains held there under a sentence of death imposed in absentia in 2009 in relation to his political opposition to the Ethiopian government.
“I’m pretty sure that every British person deserves the protection of the UK government but my father is not receiving this,” said Menabe, who attends Hugh Myddelton primary school and dreams of a career on Broadway.
“After two years he is finally going to get a lawyer but I don’t think it’s going to actually help my dad. The government needs to demand he comes back – they should have done it ages ago.”
The only contact Menabe, her twin brother Yilak and sister Helawit, 16, who live with their mother Yemi Hailemariam, have had with their father since he was abducted was a single phone call in December 2014.
Foreign Secretary Philip Hammond, who was in Ethiopia this week, said Mr Tsege was “top of the agenda” at meetings with the government. However, while “securing assurances” that the activist would finally be granted access to a lawyer he did not demand Mr Tsege’s release.
“We had been living in hope but this really feels like a slap in the face,” Ms Hailemariam said. “There’s no way someone who has been detained in this way and who was kidnapped is not going to have a fair trial. The problem is that these people don’t have fair trials.
“To think he can get justice there is an insult to us and the subtext, it feels, is that we are not fully British.”
Menabe added: “I think they would try harder if my father was a white Englishman, definitely.”  The family’s case is that, given the illegality of Mr Tsege’s kidnap, detention and death sentence, the UK’s decision not to ask for Mr Tsege’s release is unlawful.
Ms Hailemariam added: “The government is trying to justify the unjustifiable and I think this is unsustainable, so we just have to keep on fighting.”
Speaking from Ethiopia after his meetings on Wednesday, Mr Hammond said: “I have now received a commitment from the Prime Minister that Mr Tsege will be allowed access to independent legal advice to allow him to discuss options under the Ethiopian legal system.
“At my request, a senior Foreign Office official travelling with me was given access to Mr Tsege in prison. Following that visit, I am satisfied he is not being ill-treated and that he is receiving regular visits from family members in Ethiopia.”
Mr Tsege, a naturalised British citizen who has lived in London since 1979, is an outspoken critic of the Ethiopian regime and a member of the exiled opposition group Ginbot 7.
The jazz fan was on his way to an opposition conference in Eritrea when he was kidnapped and handed over to Ethiopian authorities.
Last year, Menabe’s sister Helawit won a human rights award for a play she wrote with her friends about her father’s plight.
Menabe was chosen by her mother to head up the legal challenge because of her articulate campaigning on her father’s behalf. She is being represented by Clerkenwell-based law firm Leigh Day.

Source: (Islington Tribune)

Wednesday, June 1, 2016

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም ግምገማ ላይ ወድቀዋል

June 1,2016
Tewodros Adhanom
ከልዑል ዓለሜ
እጆቹን አስረዝሞ ለመዝረፍ ይመቸዉ ዘንድ የአለም ጤና ድርጅትን ለመምራት አዲስ አቅጣጫ የቀየሰዉ የትግራይ ነጻ አዉጪዉ ቡድን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ የዉጭ ሐገራት በመዘዋወወር የአለም ጤና ርጅትን ለመምራት ቅስቀሳ ሲያደርግ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።
ቅዳሜ እለት ወደ አዲስ አበባ የተመለሰዉ ቴዎድሮስ አድሐኖም ሁለት ቀላል መሳሪያ የታጠቁ ወጣቶች የሚጠብቁት ሲሆን የታርጋ ቁጥሩ ኮድ 2_69183 አአ የሆነ ዘመናዊ ላንድ ሮቨር አዉቶሞቢል ተመድቦለት ይንቀሳቀሳል።
አምባሳደር ሙሌ የካቢኔ ዋና ሹሙና አምባሳደር ቦጋለም ከቴድሮስ አድሐኖም ጋር አብረዉ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን አቶ ህላዌ ዩሱፍ እና የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ከቴድሮስ አድሐኖም ጋር በአንድነት ሆነዉ በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ዙሪያ እየደረሰ ያለዉን የአገልግሎት ኪሳራ በተመለከተ ዉይይት ከማድረጋቸዉ በተጨማሪ በህዝቦች ሽግግር ዙሪያ ከእስራኤል ዲፕሎማኦች ጋር ተወያይተዋል።
የመላዉ ሐገራችንን አንጡራ ሐብት ከግል ጥቅማቸዉ አንጻር እንዳሻ ሲጠቀሙበት ማየት እጅግ ያሳዝናል በማለት ቁጭታቸዉን የገለጹልን ባለስልጣን ከእንግዲህ ወዲህ የትግራይ ነጻ አዉጪዉ ቡድን ሐገራችንን የምምራት ብቅት እንደሌለዉና የሐገሪቷ ብሔራዊ ደንነት አደጋ ላይ መዉደቁን አሳስበዉ ኢትዮጵያን ከአደገኛ ችግር ከመታደግ አንጻር ወያኔ ስልጣኑን ለሰፊዉ ህዝብ እንዲያስረክብ አስጠንቅቀዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Tuesday, May 31, 2016

Freed From Prison, Ethiopian Bloggers Still Can’t Leave The Country

May 31,2016

Ethiopia's Zone9 bloggers says "thank you"
(NPR)— Zelalem Kibret remembers the day: July 8, 2015. He was in a prison library reading a biography of Malcolm X, his own copy, when some guards called his name and handed him a piece of paper. The message: All charges against him were withdrawn. He was being released.
“I was asking why,” says Zelalem, a 29-year-old lawyer and blogger. “And nobody was giving us a reason.”
Zelalem, who’d been in jail for more than a year on terrorism charges related to his blog posts, suspected the reason. His release, he believes, was a “personal gift” to President Obama, then three weeks away from an official visit to Ethiopia, the first ever by a U.S. president.
The U.S. had been pushing quietly the release of Zelalem and five other members of Zone 9, his blogging crew. Zone 9 takes its name from the eight zones of the infamous Kality Prison outside Addis Ababa, where political prisoners and journalists are held. Activists joke that the 9th Zone is everything outside the prison walls — the rest of Ethiopia.
“Zone 9 is Ethiopia with relative freedom, but still you felt that you are in detention,” Zelalem explains.
Zelalem and the other Zone 9 bloggers had been critical of corruption and repression by the Ethiopian government, but their blogs and Facebook posts were seen as a relatively safe space for criticism in a country with about 3 percent internet penetration.
But the arrest of six bloggers, including Zelalem, and three other journalists in 2014 sent a signal that as Facebook was becoming more popular in Ethiopia, digital reportage might now become just as censored as print journalism. Journalists are regularly imprisoned under Ethiopia’s wide-ranging anti-terrorism law, which makes it a crime to have contact with any group that the Ethiopian government deems is trying to overthrow it.
At a press conference during Obama’s visit, Prime Minister Hailemariam Desalegn conceded, “We need many young journalists to come up.” But, he said, “We need ethical journalism. There is also capacity limitations in journalism.”
The phrase “capacity limitations” — and its cousin, “capacity building” — came out of development lingo of the 1990s. Ethiopian officials often use “capacity” explanations to assert that journalists are jailed not because they are critical of the government — but because they are less professional, more unethical and more incendiary than Ethiopia’s fledgling democracy can tolerate.
In keeping with this theme, Hailemariam nodded to Obama’s traveling press corps and asked them to “help our journalists to increase their capacity.”
Obama had offered an opportunity for just that, promoting his Young African Leaders Initiative, which gives scholarships for 1,000 African leaders to study in the U.S. each summer.
Zelalem, out of prison but unable to get back his university teaching job, followed Obama’s advice. He applied and was accepted to the Young African Leaders Initiative. This summer, he was supposed to study civic leadership at the University of Virginia.
He won’t be going. Ethiopian immigration officials confiscated his passport at Bole International Airport in November. They also took away the passports of four of his five colleagues who were released in advance of Obama’s visit.
That’s when Zone 9 became more than a metaphor. They were literally imprisoned in their own country.
Zelalem sees this as evidence of a new strategy. In past years, Ethiopia has been willing to let its critical citizens flee the country. (For several years, Ethiopia has ranked on or near the top of the list of countries with the most exiled journalists, according to the Committee to Protect Journalists.) Now, Zelalem says, the government may be deciding that it’s better to keep critics close by.
“Especially for people like us working on social media,” Zelalem says. “Whether we are here or in America or somewhere else, we may write and we can reach our audiences. Therefore, it’s better to keep [us] here and silence [us].”
When I brought up Zelalem’s case with Ethiopia’s Minister of Communication, Getachew Redda, he said he wasn’t familiar with it. But he offered a different explanation for the blogger’s rough treatment at the hands of Ethiopian Immigration: Ethiopia’s young institutions, he said — including its judges and immigration officials — could zealously overstep their bounds. They could even make mistakes that would take months or years to correct.
The minister’s solution? “More capacity building.”

Wednesday, May 18, 2016

የኢየሩሳሌም ተስፋው ደብዳቤ ከቃሊቲ እስር ቤት – ግንቦት 7

May 18,2016
ከእየሩሳሌም ተስፋው (ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት)


(እየሩሳሌም ተስፋው የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ስትሆን፣ በነብርሃኑ ተክለያሬድ መዝገብ ‹ግንቦት 7›ን ሊቀላቀሉ ሲሄዱ ተይዘዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸው አሁን የመከላከያ ምስክር ለማስደመጥ በቀጠሮ ላይ ናቸው፡፡ እየሩሳሌም ተስፋው ይህንን ደብዳቤ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት በግንቦት 7፣ 2008 እንዲታተም ያወጣችው ቢሆንም፤ በተለያዩ እንቅፋቶች በዕለቱ ለሕዝብ ሳይደርስላት ቀርቷል፡፡) (የ እጅ ጽሁፏን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) ይህቺ ቀን ከዛሬ 11 ዓመት በፊት በ1997 ዓ.ም. በዕለተ እሁድ ኢትዮጵያ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን ለመረጠው ፓርቲ ሊሰጥ የተሰለፈበት ዕለት ነበረች፡፡ ሕወሓት/ኢሕአዴግ እስቲ እንያቸው ምን ያመጣሉ በማለት ከዛ በፊትም ከዛ በኋላም ተደርጎ በማይታወቅ ሁኔታ የምርጫ ምኅዳሩን ገርበብ አድርጎ ከፍቶ በሩን አልፈው እንዲገቡ ፈቀደላቸው፡፡ በዛች በር ገብተው ብዙ ነገር ሠሩ፡፡ በውጭ ሚዲያ ላይ እምናውቀውን hard talk በአገራችን ላይ በአገራችን ሚዲያ ለማየት በቃን ተስፋችንም ለመላው ይህ ትውልድ ታሪካዊ (ዕድለኛ) ትውልድ ነው አልን፡፡ ለአገራችን ታሪከ ለመጀመሪያ ጊዜ በመረጥነው መንግሥት ልንተዳደር ነው፡፡ በሠላማዊ መንገድ (በምርጫ) የመንግሥት ለውጥ ልናይ ነው እያልን ስንደሰት ወዲያው በዛች ቀን ምሽት ምርጫው ተጠናቆ ወደቆጠራው ሲገባ ሕወሓት/ኢሕአዴግ አልበዛም?! በሚል መልኩ እስርና ግድያውን ጀመረ፡፡ ብዙ ሺሕ ዜጎቻችንን እንደቀልድ አጣናቸው፡፡ በአልሞ ተኳሽ ግንባር ግንባራቸውን እየተባሉ በየደጃፋችን ተደፍተው ቀሩ፡፡ ኮሎኔል መንግሥ?ቱ ኃ/ማርያም ከዛሬ ጀምሮ ብሎ – መስቀል አደባባይ ላይ ቀይ ሽብርን እንዳወጀ – ታሪክ ራሱን ደገመና ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ዕዝ ስር በማለት የሞቱን ዐዋጅ ዐወጀ፡፡
ትዝ ይለኛል የዛሬ 3 ዓመት አካባቢ 2006 ላይ ሰኔ 3፣ 1997 ዓ.ም. በግፍ የተገደሉትን ንፁኃን ዜጎች ለማሰብ በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ተሰባስበን ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም እንባቸው በጉንጮቻቸው እየወረደ ‹የማይታመን አምነን ወገኖቻችን አለቁ፡፡ ሰው እንዴት መለስን ያምናል? እንዴት ሕወሓት/ኢሕአዴግ ይታመናል?› እያሉ በቁጭት የተናገሩት ትዝ አለኝ፡፡ አዎ፣ የማይታመነውን አምባገነን በዚች ዕለት ወገኖቻችን የጥይት ራት ሆኑ!! እነሆ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሠላማዊ ትግል በር ተዘጋ ብለው ያመኑ ድምፃቸው የታፈኑ መብታቸው የተረገጠ ንፁኃን ዜጎች እንዲሁም ከዚህ ቀን በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ ሠላማዊ ትግል ተዘጋ ሲሉ ግንቦት 7 አሉት፡፡ ይህ ሕዝባዊ ኃይል የተመሠረተበት ዋናው ዓላማ የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በትጥቅ ትግል ለማስወገድ በሃገር ወዳድና ለሕዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወጣቶች ምሁራንና ዜጎች ግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይልን መሠረቱ፡፡ ይህ ሕዝባዊ ኃይል ሰንቆ የተነሳው ራዕይ “የሕዝብ ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠበት የዜጎች መብቶች፣ አገራዊ አንድነት፣ ደኅንነትና ጥቅም የተከበሩባት ጠንካራና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እውን ሆና ማየት” ሲሆን ተልዕኮው ደግሞ “መንግሥትን በኃይል የማስወገድ ሠላማዊና የሥልጣን ሽግግር በአገሪቱ እንዲኖር የማስቻል እና ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ጋር ያልወገኑ ነጻ እና ጠንካራ ብቃት ያላቸው ሕገ-መንግሥታዊ የመከላከያ የፖሊስና የደኅንነት ተቋማት እንዲኖሩ ማድረግ” ነው፡፡Eyerusalemነገር ግን ሕወሓት/ኢሕአዴግ ለሕዝብ ድምፅ ሥልጣን ላይ የወጣ ፓርቲ አይደለምና በየዕለቱ የሚፈጠረው ኮሽታ ስለሚያስበረግገው እንዲሁም ንፁኃንን ለማሰር እና ለመግደል ምክንያት ይፈልግ ነበርና ይህ ሕዝባዊ ኃይል እንደተመሠረተ “ሽብርተኛ” ስለፈረጀው መስራቾቹን እንዲሁም ወደሃገር እንዲገቡ የማይፈልጋቸውን ተቃዋሚዎች በዚህ አጋጣሚ “አሸባሪዎች” ሲል ፈረጃቸው፡፡ ከዚህ ጊዜ በኋላም ለሥልጣኔ ያሰጉኛል ያላቸውን ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የሲቪክ ማኅበራት አመራሮች፣ ጦማሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች በአጠቃላይ ለም ብለው ጥያቄ እሚያነሱ ዜጎችን ግንቦት 7 በማለት በየወኅኒው እያሰራቸው ይገኛል፡፡
እንግዲህ ይህ ሕዝባዊ ኃይል ከላይ እንደገለጽኩላችሁ አሸባሪ ሊያሰኘው የሚችል ዓላማ፣ ራዕይም ሆነ ተልዕኮ የለውም፡፡ ለሠላማዊ መንገድ የተነጠቀውን መብቱን በሁለገብ ትግል ለማስከበር ዓልሞ የተነሳ ድርጅት ነው፡፡ ሠላማዊ ትግል ብቻውን ሕወሓት/ኢሕአዴግ ከወንበሩ እንደማያነቃንቀው እስካሁን የታዩት ሙከራዎች በቂ ናቸው ለዚህም ነው በዚህ ሰዐት ብዙ ወጣቶች ይህን ሕዝባዊ ኃይል በቆራጥነት እየተቀላቀሉት የሚገኙት፡፡
ሕወሓት/ኢሕአዴግ ባወጣው የፀረ-ሽብር ዐዋጅ (በነገራችን ላይ ይህን የፀረ-ሽብር ዐዋጅ ልብ ብላችሁ ካያችሁት ሕወሓት/ኢሕአዴግ ለራሱ ያወጣው ይመስላል፡፡ ለምሳሌ ሽብር በሌለበት ሽብር መንዛት አሸባሪነት ነው ይላል፡፡ ታዲያ በአገር ሠላም፣ በጠራራ ፀሐይ ቦንብ አፈነዱ እያለ documentary የሚሠራ ሕወሓት እንጂ ግንቦት 7 ነው እንዴ? በተረፈ ሁሉንም አንቀፆች ተመለከቷቸው ከግንቦት 7 ይልቅ ለሕወሓት ይቀርባሉና ገና ጫካ እያሉ የሕዝብን ተቀባይነት ለማግኘት ሲሉ በገዛ ሕዝባቸው (በሓውዜን) ላይ የጀመሩት እልቂት በደርግ ማሳበብ፣ አሁንም ከ25 ዓመት በኋላ ሳይቀነስ ሳይጨመር እንዳለ ነው፡፡ አሸባሪ ማነው?
እንግዲህ ይህ ሁሉ የተፈፀመው በዚህች ዕለት ነው፡፡ “ግንቦት 7” ይህቺ ቀን የትናንት አሰቃቂ ትዝታችን የዛሬ ክሳችን የነገ ተስፋችን ናት፡፡
ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ ያልተማረ ዜጋ አይገኝም፡፡ ሁሉም ነጻነትን ይናፍቃል፡፡ ነጻ ለመውጣት ግን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ ይፈራል፡፡ የሆነ አካል መጥቶ ነጻ እንዲያወጣው ይፈልጋል፡፡ ይህ ደግሞ ሊሆን አይችልም፡፡ ነጻ ለመውጣት መጀመሪያ ራስን ከታሰሩበት የፍርሓት እስር ነጻ በማውጣት ትግሉን መቀላቀል ነው፡፡ ድርጅታችን ግንቦት 7 ለነጻነት፣ ለፍትሕና ለዴሞክራሲ የተቋቋመ ነጻ አውጪ ድርጅት እንጂ አሸባሪ አይደለም፡፡ ስለዚህ በድፍረት እናገራለሁ፡፡ እኔ ግንቦት 7 ነኝ፤ እናንተስ? ሁሌም እንደምለው የታሰረው አካሌ እንጂ ልቤ ቀይ ባሕርን ተሸግሮ ከጓዶቼ ጋር በኤርትራ በረሃ ነው፡፡ ይህቺ ቀን ለብዙዎች ሞት፣ አካል መጉደል፣ እስራት አብቅታለች፡፡ መራራውን ሳያልፉ ጣፋጭ፤ ሳይሞቱ ትንሳኤ የለምና ባለፈው ከመፀፀት ባለፈ እልህ አስይዞን ይህንን ዘረኛና አምባገነን የሽፍታ ቡድን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መንግለን ለመጣል እንዘጋጅ፡፡ ከላይ እንዳልኩት የትላንት ጥቁር ጠባሳ፣ የዛሬ ግርፋትና እስራት፣ የነገ ተስፋ ናትና እንኳን ለዚች ቀን አደረሳችሁ፡፡ ይህች ቀን፣ የነጻነት እንዲሁም የድል ቀናችን እንደምትሆን አልጠራጠርም፡፡ ግንቦት 20 በግንቦት 7 እንደመስሰዋለን!!
የነጻነት ታጋዩ ጀግናው አንዳርጋቸው ፅጌ አንድ ጊቢ ብንኖርም መገናኘት አልቻልንም፡፡ እንኳን አካልህን ወሬህንም በስንት ስቃይ ነው፡፡ እምሰማው ያንተ መታፈን ወያኔ እንደጠበቀው ትግሉን አላሽመደመደውም፡፡ እንደውም፣ ይበልጥ አጦዘው ለኛ ከቤት መውጣት ምክንያት አንተ ነህ፡፡ እኛ የአንተ ፍሬዎች ነን፡፡ ዛሬ ታፍነህ ቀንና ሌሊቱን መለየት የማትችልበት ሁኔታ ውስጥ ብትሆንም የነጻነት ቀን ቀርባለችና እስከዛው ዕድሜህን ያርዝምልን፡፡

Tuesday, May 17, 2016

Ethiopia: More soldiers desert the army, join opposition groups

May 17,2016
(ESAT News)— The number of soldiers deserting the Ethiopian army that’s riddled with corruption and joining opposition forces is on the rise.
22 defected Ethiopian soldiers in Eritrea
The Tigray People’s Democratic Movement (TPDM) said in a statement on Monday that several soldiers of the minority regime in Addis Ababa have joined the Movement. TPDM has released a list of the names and other information of those who recently deserted the regime’s army. Some of the deserters had higher ranks in the army.
The soldiers said they had enough of the regime that’s using the army to prolong its stay in power. They said they would rather join democratic forces and fight to save the country from disintegration.
Adem Mohammed and Beshir Yosef said nepotism and corruption were rampant in the army. They said the rank and file were marginalized by the higher officers and generals who hail from one ethnic group. As a result, there is no unity and cohesion in the army, they said, adding that no soldier wish to stay in the army on his will; everyone wants to abandon the army, according to these soldiers.
Unbridled plunder of resources by a handful of generals when the rank and file eke out a living has been one of the causes of the rise in defection; in addition to refusal by some members of the army not to serve as a hit squad for the regime against people who are deemed to be political opponents.

Sunday, May 15, 2016

የመከላከያ ሰራዊት የሚገኝበትን ስፍራና አድራሻ ለተቃዋሚዎች መረጃ አሳልፋችሁ ተብለው ወታደሮች ታሰሩ

May 15,2016

የመከላከያ ሰራዊት የሚገኝበትን ስፍራና አድራሻ ለተቃዋሚዎች መረጃ አሳልፋችሁ ሰጥታችኋል በሚል ወታደሮቹ በጥርጣሬ በወንጀል መታሰራቸው ታወቀ።

መረጃው እንዳስረዳው የተሰጣችሁን አገራዊ አደራ ወደ ጎን ትታችሁ የመከለካያ ሰራዊት ስፍራና አድራሻ ለተቃዋሚ ድርጅቶች ታስተላልፋላችሁ ተብለው የተጠረጠሩ ወታደሮች ያለ ምንም ማስረጃ በግብረ ሽበራ በሚል በወንጀል ክስ እንደተመሰረተባቸው መረጃው አስረድቷል።

የፊዴራሉ አቃቢ ህግ የላይኛው ፍርድ ቤት የ1ኛው ወንጀል ችሎት ተከሳሾቹ በርከት ያሉ ወታደሮች ሲሆኑ፣ የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያህል፣ አስራ አለቃ አጀናው ታደሰ፤ ምክትል አስራ አለቃ ቻሌ ነጋና ሌሎችም የቀረበላቸው ክስ እንዳስረዳው በኢትዮ_ ኤርትራ ዳር ድምበር ትጥቅ ያነገቡ ተቃዋሚ ድርጅቶች፣ የመከላከያ ሰራዊት በ6ተኛውና በ25ተኛ ክፍለ ክፈለጦር የሚገኙትን የሬጅመንቶች ብዛትና የት እንደሚገኙ መረጃ በዝርዘር አስልፋችሁ ትሰጣላችሁ በሚል በከባድ ወንጀል ቢከሰሱም ፣ለቀረበላችው ጥያቄ ስላልተቀበሉት በህግ ጠበቃ ለግንቦት 15 /2008 ዓ/ም ቀጠሮ እንደተሳጣቸው አስገነዘበ።

በመጨረሻ በአሁኑ ግዜ በመከላከያ ሰራዊት ያለመተማምንና መጠራጠርን እንደ ተፈጠረና በዚህ ምክንያትም ብዙ ወታደሮች አሃድዋቸውን ትተው እግራቸው ወዳመራቸው እየጠፉ መሆናቸውን ታወቀ።

Tuesday, May 10, 2016

Crestfallen But Resolute! Co-Blogger Zelalem Workagegnehu Sentenced To Five Years And Four Months

May 10,2016
Zelalem Workagegnehu, co-blogger of De Birhan Blog and whose works had appeared on various Diaspora websites, has been sentenced to five years and four months by the Ethiopian regime controlled court in Addis Abeba, Ethiopia today.
zelalem
Zelalem has already been detained for nearly two years – 672 days today.
Zelalem was finishing his Masters Degree in Public Administration at the Addis Abeba University, in July 2014 when he was detained together with nine other opposition politicians, netizens, and activists.
The Court had acquitted  five of the defendants  in August 2015 and two more of Zelalem’s co-defendants on April 15, 2016 when it found Zelalem and two other co-defendants of Zelalem guilty of “supporting terror in any way.”
The movement he is accused of supporting is known as Ginbot 7 (Arebgenoch Ginbot 7 Movement), a pro-democracy movement founded by Professor Berhanu Nega, an Ethiopian economist, who lectured in Bucknell University, U.S.A. The Ethiopian government labelled his movement as well as few other Ethiopian opposition groups as “Terrorist Groups” in 2010.
Like several Ethiopian activists, journalists and politicians, Zelalem was initially accused of being a member and local leader of Ginbot 7 although the charges were later changed to recruiting members to start an Arab Spring styled revolution in Ethiopia and applying for a digital security course.
Zelalem in his defense statements maintained that he has never been a member of Ginbot 7 and does not believe Ginbot 7 is a terror organisation, he does stand for a social change only through a nonviolent means and is against any form of violence.
Zelalem Workagegnehu’s Trial Timeline 
July 8, 2014 – Zelalem Workagegnehu along with seven of his friends and one of his brothers was detained by the Ethiopian Federal Police and Securities. Few months later his older brother and four of his friends were later released after going through long interrogations and torture.
One of his colleagues and distant relative, Eyob, who faced the most torture and ordeal, had agreed with the prosecutors to testify against Zelalem and his colleagues and thus was subsequently released.
October 31, 2014 – After four months of investigation, torture and interrogation, 10 people were officially charged. The 10 were charged under the file of Zelalem Workagenehu :
1. Zelalem Workagenhu – a postgraduate student of Addis Abeba University and a writer
2. Habtamu Ayalew – Public Relations Head of the Unity for Democracy and Justice Party (UDJ) – now acquitted but still battling the Prosecutor’s appeal
3. Daniel Shibeshi – Organisational Affairs Head of UDJ – acquitted
4. Abraha Desta – Central Committee member of Arena Party and lecturer at Mekele University – Acquitted but still in prison
5. Yeshiwas Assfea – Council member of Blue (Semayawi Party) – acquitted
6. Yonatan Wolde – charged with applying for a digital security course – acquitted
7. Abraham Solomon – linked with Zelalem in the Charge – acquitted
8. Solomon Girma – found guilty
9. Bahiru Degu – charged with applying for a digital security course – acquitted
10. Tesfaye Teferi – found guilty
The two main morals of the charges were one “working together with terrorist organisations” and “membership in Ginbot 7 and participation in criminal activities”.  The first defendant Zelalem has been charged with being a leader of Ginbot 7, sending information to Diaspora based websites and recruiting members to start an Arab Spring styled revolution in Ethiopia” and is centrally linked with this writer, Tedla, who is also implicated in the same charge.
The 2nd, 3rd, 4th and 5th defendants have been charged of using legally registered opposition party as a cover to pursue the aims of Ginbot 7 and also using social media to contact Fasil Yenealem, whom the charge referred to as a member of the Movement and others.
Nov. 20, 2014 – They were all denied bail. The Court ordered the prosecutor to complete its evidences on the detainees and submit them on 27 November, 2014.
December 18, 2014 – given another appointment to reappear in Court on December 25, 2014. Reappointed.
Feb. 3, 2015 – Court Declines To Accept The Objections And Defense Of Writer Zelalem Workagegnehu Et Al. Adjourned the hearing to February 19, 2015.
Feb.19, 2015 – They given another appointment to appear again on March 4, 2015 by the Lideta Court.
 March 19, 2015 – Court appointed the defendants to May 21, 22 and 25, 2015 respectively to hear the prosecutors witnesses.
 June 08, 2015 – The Criminal Bench of  the Lideta Federal High Court  in Addis Abeba started hearing the prosecutor’s witnesses.
 June 11, 2015 –  Court tells Zelalem to appear in Court on Monday June 15, 2015 for decisions after witnesses testimony was heard.
June 17, 2015 –  Court adjourns for July 8, 2015 to give verdict on the Public Prosecutor’s evidences.
August 20, 2015 – Five, charged under the file of De Birhan’s Co-blogger Zelalem, acquitted, Zelalem told to Defend. Court adjourned their case to  November 7-9, 2015
August 24, 2015 – Prosecutor lodges an appeal against the acquitted.
November 23, 2015 – Hearing of defense witnesses begins.
November 27, 2015 – hearing postponed to next week Dec.4, 2015 due to incomplete judicial panel.
February 24, 2016 – Andargachew didnot testify, Court postpones co-blogger Zelalem’s trail due to judges absence and Court takes Andargachew’s failure to testify as Zelalem’s own fault.
April 26, 2016 – Prosecutor submits sentencing aggravation statement. Sentencing adjourned to May 10, 2016.
May 10, 2016 – Co-Blogger Zelalem Workagegnehu sentenced to five years and four months.
We are crestfallen but remain resolute! Days will tell! 



Source: De Birhan Blog

Wednesday, May 4, 2016

ኦባንግ አባ “ቃኘው” የደቡብ ኮሪያ ዳግም ዘማች!

May 4,2016
በኮሪያ የተዘጋው የመረጃ ግድግዳ ተወገደ!
obang sk
የመን ትነድዳለች ኢትዮጵያውያን ግን ወደዚያው ያቀናሉ። ሶማሊያ ዋስትና ቢርቃትም ወገኖች ሊረማመዱባት አሁን ድረስ ምርጫቸው ናት። በሲና በረሃ ሰው በቁሙ ይበለታል። ለእኛ ኢትዮጵያውያኖች ግን አሁንም አማራጭ መንገድ ነው። ሲኦል መሆኑ እየታወቀ እህትና ወንድሞች ወደ አረብ አገር ይተምማሉ። ኬንያን፣ ታንዛኒያን፣ ዛምቢያን፣ … አቆራርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚጓዙ ቁጥራቸው ሲቀንስ አይታይም። በደቡብ አፍሪካ ወገኖች በእሳት ሲቃጠሉና በገጀራ ሲጨፈጨፉ ማየት ወደዚያ የሚደረገውን ጉዞ አልቀነሰውም። ለምን?
በቀይ ባህርና በሜዲትራንያን የሰመጡ ወገኖች መርዶ ሳያሰልስ ሌሎች መሰመጥ የመጨረሻ አማራጭ መሆኑን እያወቁ ይገቡበታል። ሊቢያ የታረዱትን ወገኖች እያዩ ሌሎች ወደ ሊቢያ ለማቅናት አያቀማሙም። ለምን? በኩባ ቪዛ ተነስተው መከራቸውን ለወራት በበረሃ የሚያሳልፉ ወገኖች ቁጥር … ስንቱ ይዘረዘራል? ኢትዮጵያውያኖች እንዲህ ያለውን መከራና አጥንት ዘልቆ የሚገባውን ሃዘን ሳይፈሩ ስደትን የመጨረሻ አማራጭ ያደረጉት ለምን ይሆን? ለገዢውም ሆነ ለተገዢው የሚቀርብ ጥያቄ ነው።
ከሁሉም በላይ ዜጎች በየጊዜው እርዳታ ሲፈልጉና በነፍስ ውጪ ግቢ ውስጥ ሆነው የድረሱልኝ ምልጃ ሲያቀርቡ ሰሚና ተቆርቋሪ የላቸውም። ህወሃት ለእንዲህ ያለው የወገኖች ጥሪ መልሱ “ጥሪ አይቀበልም” መሆኑ ደግሞ ከችግሩ በላይ ቅስም ሰባሪ ነው። ወገኖቻችን ሲታረዱ “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ቆይ ላጣራ” የሚል ገዢ ቢኖር ህወሃት ብቻ ነው። ዶላር ባለበትና የስልጣን ጊዜን የሚያራዝም እስከሆነ ብቻ ተጣድፎ ምላሽ የሚሰጠው ህወሃት፣ በቅርቡ በጋምቤላ ለተጨፈጨፉት ወገኖች የሰጠው ምላሽ የዚሁ ተግባሩ መገለጫው ነው።
ሳይደግስ አይጣላም እንዲሉ በበርካታ ጉዳዮች የሚያዝኑ ወገኖች የሚጽናኑበት አንድ ሰው አግኝተዋል። የተግባር ሰው! በሩ ለሁሉም ወገኖች ክፍት የሆነ። ቂምና በቀልን አጥብቆ የሚጠላ፤ ተንኮልን የሚጸየፍ። ወገኖቹን የሚላላክ፤ ለአንድ ግለሰብም ለብዙሃንም በእኩል የሚቆም። ክብሩ አገልጋይነት ብቻ የሆነ። ዝማሬና ሙገሳ የሚጠላ። በውሱን ድጋፍ ወሰን የሚያልፍ፣ አህጉር የሚያቋርጥ ሥራ የሚያከናውን። ብዙ ሊባልለት ሲገባው ግን ያልተባለለት፤ ያልተጨበጨበለት፤ ያልተዘፈነለት፤ … ሥራውን የሚያውቁ ግን “የጥቁር አልማዝ” የሚሉት!!
“ለወገን ደራሽ” ስሙ ነው። በተጠራበትና ችግር አለ በሚባልበት ቦታ ሁሉ ወገኖቹን ተሟግቶ ነጻ ያወጣል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ክብር የሚገባው ግን ክብር ያልተሰጠው” በሚል በማህበራዊ ድረገጾች ስሙ እየተነሳ ነው። የእርሱ ፍላጎት ባይጠየቅም “አንተ ምራን” የሚሉት እየበረከቱ ነው። ጀርባው ሁሉ ከምንም የጸዳ በመሆኑ ብዙዎች “እናምነሃለን፣ እናከብርሃለን፣ እንወድሃለን፣ አምላክ ይጠብቅህ …” እያሉት ነው።
ለሰው ልጆች ክብርና እኩልነት ዋጋ መክፈል እንደሚያስደስተው ደጋግሞ ይናገራል። “ሁላችንም ነጻ ካልወጣን ማንም ነጻ አይወጣም” በሚለውና ግንባሩ ላይ በታተመው “ከጎሣ በፊት ለሰብዓዊነት ቅድሚያ እንስጥ” በሚል መሪ ቃል ይታወቃል። በሚመራው ድርጅት ውስጥ ባሉት ባልደረቦቹ የሚታመን። ይህ ሰው ኦባንግ ሜቶ ይባላል። በይቅርታ አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለማቆም ከመሰሎቹ ጋር ደፋ ቀና ይላል። ርምጃው በተለያዩ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገሮች መነጽር ውስጥ ከቶታል። ኢትዮጵያን በመወከል በከፍተኛ ቦታዎች የወገኖቹ ድምጽ ከሆነ ሰነባብቷል። ከሚያከናውናቸው በርካታ ተግባሮች ገሃድ ወጥቶ የሚናገረው በጣም ጥቂቱን ነው። ስለ እሱ ጠንቅቀው የሚያውቁ “ኦባንግ አሁን የኢትዮጵያ ምስል ሆኗል” እያሉ ነው። የጎልጉል የኬኒያ ዘጋቢ በቅርቡ ሰፊቃለ ምልልስ ለማካሄድ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቆናል። በዚሁ ሰፊ ቃለምልልስ በማህበራዊ ገጾች ስለሚነሱት ጥሪዎች ምላሽ ይሰጣል።Ethiopian_soldiers_Korea_war
የደቡብ ኮሪያ ዳግም ዘማች – አባ “ቃኘው
ስደት እንደ ጨው ከረጫቸው ወገኖች መካከል በደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ወገኖችን ያስታወሳቸው አልነበረም። ባለፉት ሳምንታት የተሰማውን ዜና አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ጥቁሩ ሰው” በተለይ ለጎልጉል ሲናገር “የተዘጋን በር አስከፍተናል” ነበር ያለው። ወደዚያው ማቅናቱን የሰሙ “የደቡብ ኮሪያ ዳግም ዘማች አባ – ቃኘው” ሲሉ ጠርተውታል።
“ዘመን የማይሽረው ወዳጅነት ኮሪያና ኢትዮጵያ፤ በኮሪያ ጦርነት የኢትዮጵያ ጦር ተሳትፎ” በሚል ርዕስ ደራሲ ቲኢ-ጂኢ-ውን የጻፉትና በጋሻው ድረሴ ወ/ሰማያት ወደ አማርኛ የመለሱት መጽሃፍ መግቢያ ላይ ከዛሬ 64 ዓመት በፊት ኮሪያን ነጻ ለማውጣት ዘምቶ የነበረው የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት መጠሪያ ስሙ “ቃኘው” እንደሚባል አስታውሶ ትርጉሙም “ድብልቅልቁን ሥርዓት አስይዘው” ማለት እንደሆነ ተመልክቷል። ለዚህም ይመስላል ኦባንግ “አባ ቃኘው” የሚል ስም የተበረከተለት።
በመጽሐፉ መግቢያ ላይ ይህ ተጽፎ ይገኛል “… በጦርነቱ ለማያውቁት ሀገርና አይተውት ለማያውቁት ህዝብ በኮሪያ ጦርነት የህይወት መስዋዕትነት ለከፈሉት ያለንን ጥልቅ ሀዘን እንገልፃለን፡፡ ዕድሜ ለኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት የኮሪያ ሪፐብሊክ ከጦርነቱ ቁስል ለማገገም ችላለች፡፡ (በአሜሪካዊው) ጄነራል ማክአርተር በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት ለመግለፅ “እነዚህ ሰዎች ይህቺን ሀገር እንደገና ለመስራት 100 ዓመት ያስፈልጋቸዋል” ተብሎ ከተገለፀበት ሙሉ ውድመት ተነስተን ኮሪያን እንደገና ገንብተናታል፡፡ ዛሬ እንደ G20 እና የ2012 ሶውል ኑክሊየር ስብሰባዎች የመሳሰሉት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ የምንመረጥበት ክብር ላይ ደርሰናል፡፡ ይህ ሁኔታ የሚመሰክረው የኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት ከንቱ ሆኖ አለመቅረቱን ነው፡፡ ዛሬ ከእርዳታ ተቀባይነት ወደ ሰጭነት በተሸጋገርንበትና ከዓለማች 10 የበለፀጉ ሀገሮች ሰልፍ በተቀላቀልንበት ሁኔታ ለኢትዮጵያውያን መስዋዕትነት ብድር መላሽ ለመሆንና ከድህረ ጦርነት በኋላ ለመጣውም ትውልድ ዕውነታውን በስፋት እንዲታወቅ ጠንክረን እንሠራለን…”።
በመጽሐፉ ላይ ይህ የሰፈረ ቢሆንም በዚያ የሚገኙ 130 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሁሉም ዓይነት በር ጠብቆ የተዘጋባቸው፣ የህግ ከለላ የሌላቸው፣ በቂ የዕለት ማቆያ የማይቆረስላቸው፣ ጠበቃ ማግኘት የማይችሉ፣ በማይታወቅ የስደተኞች ህግና መመሪያ የሚስተናገዱ፣ ሚዲያው የዘነጋቸው፣ ፍትህ ፍለጋ የሚሄዱበት ያጡ፣ ሳይጨልም ለዓመታት የጠቆረባቸው፣ ሲታመሙ ለመታከም የማይችሉ፣ እዛ የተወለዱ ልጆቻቸው የሚንገላቱባቸው፣ ተዘርዝሮ የማያበቃ መከራ የተሸከሙ እንደሆኑ አቶ ኦባንግ ያስረዳል። “ገሃድ አውጥቼ ልናገረው የማልችለው አሳዛኝ ችግሮችን ስሰማ ውስጤ ታመመ” ያለው ኦባንግ ወደ ደቡብ ኮሪያ ያቀናው በዚያው የሚኖሩ የአኢጋን ቤተሰቦች አማካይነት መረጃው ደርሶት ነው። በዚህ አጋጣሚ ጉዞውን የተቃና በማድረግ ከመጀመሪያው አንስቶ እስከ መጨረሻው ሥራውን በትጋት ለሠራው ሱራፌል አሰፋ እንዲሁም ለአጋሮቹ መቅደስንና ቢኒያምን ታላቅ ምስጋና እንደሚያቀርብ ተናግሯል፡፡  obang sk2
ኦባንግ ወገኖቹን ሰብስቦ ማዳመጥ የመጀመሪያ ተግባሩ ነበር። አስቀድሞ ችግሩን እንደሰማ ወደ ስፍራው ለማምራት ቢወስንም በአካል ከተገኘ በኋላ እንባ የተቀላቀለበት ስብሰባ ላይ በሰማው ሁሉ ሃዘን ገባው። “አሁን አናለቅስም” ሲል ኦባንግ ሥራውን ጀመረ። “ዛሬ ተደራጁ፣ እንደራጅ፣ በተናጠል አትሩጡ፣ በወሬ ሳይሆን ራሳቸሁን አክብራችሁ ሌላውን ማክበር በምትችሉበት ጥልቅ ስሜት ተዛዘሉ፣ ተረዳዱ፣ አንድ ሁኑ፣ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች ስለሆናችሁ ባገራችሁ ስም ተሰባሰቡ…” ሲል የተደበላለቀውን ስርዓት ማስያዝ ጀመረ።
“እናንተ አሁን ሜዲትራንያን ባህር ውስጥ እየተንሳፈፋችሁ አይደለም፣ ሲና በረሃ አይደላችሁም፣ ደቡብ አፍሪካ በጎማ እየተቃጠላችሁ አይደለም፣ በበረሃ ውስጥ አይደላችሁም፣ መብታቸውን እንደጠየቁ የኦሮሞ ልጆች እስር ቤት አልታጎራችሁም፣ በጥይት እየተደበደባችሁ አይደለም። የማንነት ጥያቄ በማቅረባችሁ ህወሃት በጥይት እየፈጃችሁ አይደለም፣ 20 ሚሊዮን ህዝብ በችጋር ሲጠበስ እናንተ ምግብ አላጣችሁም … አዎ በታሪክ ተመዝግቦብን የማያውቅ ውርደት ውስጥ መውደቃችን ባይካድም ዛሬ በህብረት እንቆማለን። እኛ ሁላችን ከተባበርን ከችግሮቻችን ሁሉ በላይ እንሆናለን…” በማለት ጥቁሩ ሰው የዛለውን መንፈሣቸውን አነቃቃው።
ኦባንግ እንደሚለው ወገኖቹ ላይ የደረሰውን በደል መዘርዘሩ ፋይዳ የለውም። በዚህም የተነሳ በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት ጉዞ ወደ ኢሚግሬሽን ቢሮ ሆነ። አቶ ኦባንግ የደቡብ ኮሪያን ምድር ከረገጠበት ሰዓት ጀምሮ በመንግሥት ለደህንነቱ ልዩ ጥበቃ ተመድቦለት ነበር። ይህ የሆነው በሱ ጥያቄ ሳይሆን “የመታፈን ችግር እንዳያጋጥመው” ለጥንቃቄ ነበር። ይህንን ያስረዱትም ራሳቸው ናቸው ። በዚሁ መሠረት በኢሚግሬሽን ቢሮ ተገኝቶ ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኘ። ለኦባንግ ቅርብ የሆኑ እንደሚሉት “the shaker ወይም አባ ነቅንቅ” ያሰኘውን ንግግር አቀረበላቸው። ኢትዮጵያ ላይ የተንሰራፋውን ግፈኛ ኃይልና ተግባሩን አስረግጦ ዘረዘረላቸው።
“የአያቶቻችን ውለታ ይህ ነው? ኢትዮጵያዊያን ህክምና ለማግኘት እንኳን አይመጥኑም? በደቡብ ኮሪያ ሰላማዊ ዋስትና ለማግኘት ብቁ አይደሉም? ጠበቃ ለማግኘትና ጉዳያቸው እስኪታይ የሥራ ፈቃድ አግኝተው እየሰሩ ለመኖር ሚዛን አያነሱም?” ኦባንግ ከማብራሪያው በኋላ ለባለስልጣኖቹ ያቀረበው ጥያቄ ነበር።obang sk3
ኦባንግ ቀጠለ “… ራሳችሁ በከተማችሁ ያቆማችሁትን ለናንተ ነጻነት ደም ያፈሰሱት ኢትዮጵያዊያን መታሰቢያ ለምን ታፈረሳላችሁ? እነዚህ ወጣቶች እኮ የነሱ ልጅ ልጆች ናቸው” ሲል ታሪክን እያጣቀሰ አስረዳ። አሁን ያለው አገዛዝ ጋዜጠኞችን “አሸባሪ” ብሎ የሚያስር፣ ዘረኛና ለትውልዱ የማያስብ አምባገነን አገዛዝ መሆኑን በግብሩ እያስቃኘ የስደተኛ ህጋቸውን ከአለም አቀፍ ህግ ጋር አዛምደው እንዲያሻሽሉ አስገነዘበ። ጉዳዩንም ለዓለም ይፋ እንደሚያደርገው አስጠነቀቀ። ከሰፊ ውይይትና መረዳዳት በኋላ ባለሥልጣናቱ የማስተካከያ ርምጃ እንደሚወስዱ ቃል ገቡ። ከስደተኞች ዓለም አቀፍ ህግ ጋር ብዙም ትውውቅ ስለሌላቸው የተሰራ ስህተት ስለመኖሩ አምነው ተለያዩ። በስተመጨረሻም ኦባንግ ሁሉም ጥገኛ ጠያቂዎች ከለላ እንደሚያሻቸው አሳምኖ ቢሮውን በክብር ለቀቆ ወጣ።
በሲዑል የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የስደተኞች መስሪያ ቤትም ኦባንግ ተገኝቶ ሁኔታውን አሰረድቷል። ባለስልጣናቱ ከዚህ ቀደም ስለ ስደተኞቹ ሰምተው እንደማያውቁ ገልጸው ጉዳዩን የኮሪያ ባለሥልጣናት በዓለምአቀፉ ህግ መሰረት  እንዲያስኬዱት ማሳሰቢያ እንደሚሰጡ ቃል ተገባ። መደራጀታቸው አግባብ በመሆኑ ወኪላቸውን በየጊዜው በማግኘት ችግሩ እልባት እስኪያገኝ ድረስ አብረው እንደሚሰሩ ማረጋገጫ አገኘ “ቃኘው” የተዘጉትን በሮች አስከፍቶ ወጣ። ዝርዝሩን በቃለ ምልልስ እናትመዋለን።
አስገራሚው – የመረጃ ድርቅ በሴዑል
ኦባንግ በሴዑል ቆይታው ሰፊ ጊዜ ወስዶ ካነጋገራቸው መካከል በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰሩ የማህበረሰብ ክፍሎች ይገኙበታል። እነዚህ ክፍሎች አገራቸው ሚዲያ፣ ከለላ፣ ርዳታ፣ ህክምና፣ ሥራ፣ ወዘተ ተከልክለው ስለሚኖሩት ኢትዮጰያዊያን መረጃ የላቸውም ነበር። የሚያሳዝነው ህወሃት በሚገዛት ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞች “አሸባሪ” እየተባሉ ወኅኒ እንደሚወረወሩ አያውቁም ነበር። ኦባንግ ጉዞ ከመጀመሩ በፊት በያዘው እቅድ መሰረት እነዚህን ክፍሎች በቂ ግንዛቤ አስጨበጠ። የነበረውን የመረጃ ድርቅ ህይወት ዘራበት።
ከ30 በላይ የሲቪል ማህበረሰብ አካላትና ጠበቆችን ካነጋገረ በኋላ ባገኘው ምላሽ መገረሙን ኦባንግ አልሸሸገም። ደንግጠው “በአገራችሁ ሁሉ ነገር እንደዚህ ከሆነ  የአውሮፓ አገሮች እንዴት አብረዋቸው ይቆማሉ” ሲሉ ጥያቄ ሰነዘሩ። “በአሸባሪ ስም የነሱን ጦርነት ይዋጉላቸዋል” በማለት ስለ ሁኔታው ዝርዝር ምላሽ ሰጠ። በስተመጨረሻም ከጥገኝነት ጠያቂዎቹ ወኪሎች ጋር በመሆን ያገራቸው ህዝብ በቂ መረጃ እንዲያገኝ፣ መንግስታቸውም የከለላ ጥያቄያቸውን እንዲያስተናግድ ሁሉን ዓይነት ጥረት እንደሚያደርጉ አረጋገጡ።
የመረጃው በር ሲከፈት – ሚዲያ ኦባንግ ዘንድ መጣ
የጥቁሩ ሰው የመጨረሻ እቅድ ያገሪቱን መገናኛዎች በመጠቀም የደቡብ ኮሪያን ህዝብ ማንቃት፣ እንዲያስብ ማድረግና የመከራከሪያ አጀንዳ አቀብሎ ሴዑልን መሰናበት ነበር። በዚሁ እቅድ መሰረት የደቡብ ኮሪያ ታዋቂዎቹ obang sk6ሁለት ሚዲያዎች ኦባንግ አለበት ዘንድ መጡ – በኮሪያ ሲታተም 96ዓመታት ያስቆጠረው Dong-A Ilbo የተሰኘው ጋዜጣ እና በደቡብ ኮሪያ ዋንኛው የእንግሊዝኛ ጋዜጣ የሆነው The Korea Herald። ከጥቂት ዓመታት በፊት አቶ ኦባንግ በህንድ አገር ተገኝቶ በዩኒቨርስቲ ውስጥ ያደረገው ንግግር ድፍን ድጋፍ ያገኘውና ካሩቱሪ ካገሪቱ ባንኮች ብድር እንዳያገኝ የከፈተው ዘመቻ ያስመዘገበውን ውጤት ያስታወሰ ክስተት ተደገመ።
ያገሪቱ ሁለት ታዋቂ ሚዲያዎች በየተራ ሲያነጋግሩት ኦባንግ ከ65 ዓመት በፊት የተከፈለውን የደምና ያጥንት ታሪክ ግንባር አደረገ። የኮሪያ ሚዲያዎች ከዚህ ወርቅ አገር ለመጡ የጀገኖች የልጅ ልጆች በር መቆለፋቸውና ጀርባ መስጠታቸውን ለራሳቸው ህዝብ አሳበቀባቸው። ህግና ደንብ ጠቅሶ ወገኖቹ ከለላ ሊሰጣቸው እንደሚገባ አስረዳ። የኮሪያ አዲሱ ትውልድ ተደብቆት የኖረውንና ባገሩ ምድር እየተፈጸመ ያለውን ችግር አቀረበ። ሚዲያዎቹ ይህንን ከፍተኛ ችግር ዝም ሊሉ እንደማይገባ አሳሰበ። ህወሃት ምን አይነት አገዛዝ እንደሆነም ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለውንና የደረሰውን ግፍ በማተት መረጃ አስተላለፈ።
ስንብት – አደራና ክትትልobang sk4
ኦባንግ እና ወገኖቹ ኮሪያ ዘምተው ህይወታቸው ላለፈና አካላቸው ለጎደለ ኢትዮጵያዊያን ማስታወሻ በቆም መታሰቢያ ስር ተሰባሰቡ። ሻማ አብርተው ወገኖቻቸውን አሰቡ። በዚያውም “በኢትዮጵያ ዘረኝነትን፣ የጎሳ ከፋፍልህ ግዛውን አስከፊነት ለመጪው ትውልድ ለማስተማሪያነት የሚውል ምስል በአገራችን እናቆማለን። በዚሁ አስከፊ አገዛዝ ሳቢያ ካገር ሲኮበልሉ ህይወታችው ያለፈ፣ በበረሃ የቀሩ፣ ውሃ የበላቸው፣ የተገደሉ፣ የታሰሩ፣ የታፈኑ፣ የደረሱበት የማይታወቁ፣ የተሰወሩ ወዘተ ስማቸው ከያለበት ተፈልጎ በዝርዝር የሚታይበትና መጪው ትውልድ ያለፉትን መሪዎቹን በተግባር የሚያየበት ይሆናል” ተባብለው ተለያዩ።
obang sk1ኦባንግ ለመጨረሻ ጊዜ ሲለይ “አንድ ሁኑ። አያቶቻችንና አባቶቻችን በኮሪያ ምድር አንድም ምርኮኛ ሳያስመዘግቡ ታሪክ የሰሩት በኢትዮጵያዊነት ኅብረት ነው እንጂ በጎሣ ወይም በወገን ተከፋፍለው አልነበረም፤ ስለዚህ በኅብረታቸው ድል እንደነሱ እናንተም በፍቅር ተዋደዱ፤ አትበታተኑ። አንድ ስትሆኑ ትደመጣላችሁ። አንድ ስትሆኑ ጭብጨባችሁ ይሰማል። አንድነት ነጻ ያወጣችኋል። አንድነታችሁን ጠበቁ … እከታተላችኋለሁ። ሌሎች ወገኖችም ካሁን በኋላ ያስቡዋችኋል!!” በማለት አባ “ቃኘው” የመጀመሪያ ዙር ዘመቻውን አጠናቀቀ። (በዚህ ዘገባ አቶ ኦባንግን “አንተ” ብለን የጠቀስነው በምክንያት ነው)

Saturday, April 30, 2016

ፍሪደም ሃውስ ኢትዮጵያና ኤርትራን የጋዜጠኞች ወህኒ ቤት ብሏቸዋል

April 30,2016
ዋና ጽ/ቤቱን በአሜሪካ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ ባወጣው ሪፖርት ሁለቱን የምስራቅ አፍሪካ አገራት ኢትዮጵያና ኤርትራን ከሰብ ሰሃራን አገራት መካከል ዋነኞቹ የጋዜጠኞች እስር ቤት በማለት ሰይሟቸዋል፡፡
Eskinder-Nega-ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ የተወሰኑ ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን ከእስር ብትፈታም ሪፖርቱ ከኤርትራ በመቀጠል ዋነኛዋ ጋዜጠኞችን አሳሪ አገር በማለት ፈርጇታል፡፡
ሪፖርቱ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ጋዜጠኞች ባለፈው ዓመት የፖለቲካ ጫናዎች ተደርጎባቸዋል ብሏል፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የብሩንዲው ፕሬዘዳንት ህገ መንግስቱን በማሻሻል ለሶስተኛ ጊዜ ለምርጫ እንደሚቀርቡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ ነጻ የነበሩ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ተዘግተዋል ወይም እንዲጠፉ ተደርገዋል በማለት ጠቅሷል፡፡
እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በምስራቅ አፍሪካ በ2016 መጀመሪያ በኡጋንዳ በተካሄደው ምርጫ ጋዜጠኞች ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ሽፋን በመስጠታቸው ከፍተኛ አድልኦ ተደርጎባቸዋል፡፡በኬንያ ገዳቢ ህጎችን በሚዲያው ላይ ከማውጣት አንስቶ ስልታዊ የሆኑ ጫናዎች በጋዜጠኞች ላይ መደረጉን አጋልጧል፡፡
በፍሪደም ሃውስ ማውጫ መሰረትም ኢትዮጵያ፣ኤርትሪያ፣ሱዳን፣ደቡብ ሱዳን፣ሶማሊያና ጂቡቲ ከሌሎች 20 የአፍሪካ አገራት ጋር ነጻ ሚዲያ የሌለባቸው ተብለው ተቀምጠዋል፡፡
እንደ ሪፖርቱ ከሆነም ያለፈው ዓመት ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት በ12 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ እጅግ ዝቅተኛ ነጥብ የተመዘገበበት በመሆን ተጠናቅቋል፡፡
በ2007 ሱዳንና ግብጽ ከፍተኛ የሆነ ማሽቆልቆል የተመዘገበባቸው አገሮች በመሆን ተመዝግበዋል፡፡
ሪፖርቱ ከአለማችን ህዝብ 41% በአንጻራዊነት ነጻ ሚዲያን የሚያገኝ ሲሆን 46% የሚሆነው ደግሞ ነጻ ሚዲያ በሌለበት ከባቢ ውስጥ ይኖራል ብሏል፡፡
ምንጭ ፍሪደም ሃውስ

Sunday, April 24, 2016

የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንትና ሪክ ማቻር የተሳፈሩባት መኪና በሰልፈኞች ጥቃት ደረሰባት

April 23,2016
ስለፈ
 በጋምቤላ ክልል ጃዊ በተባለ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ በደቡብ ሱዳን ሱደተኞች ተጨፍጭፈው ከ17 የሚልቁ ኢትዮጵያዊያን መገደላቸው ቁጣን ቀስቅሷል፡፡
በዛሬው ዕለት ድርጊቱን ለማውገዝ የጋምቤላ ከተማና አካባቢዋ ህዝብ ወደ አደባባይ ወጥቷል፡፡ሰልፈኞቹ ኢትዮጵያዊያኑን በግፍ በገደሉ ስደተኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለመጠየቅ በሞከሩበት ሰዓት ፌደራል ፖሊሶች ሰልፈኞቹን ህገ ወጥ ሰልፍ በመሆኑ እንዲያቆሙ በመንገር ጥይት መተኮስ በመጀመራቸው ሰላማዊው ሰልፍ መልኩ ተቀይሯል፡፡ሰልፈኞቹ ወደ ስደተኞቹ ካምፕ በማምራት ደቡብ ሱዳናዊያን ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከሩ ቢሆንም በወታደሮች ታግተው የተወሰኑት መታሰራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ሰልፈኞቹ በጋምቤላ የደቡብ ሱዳናዊያን ናቸው ያሏቸውን ሆቴሎች ፣መኖሪያ ቤቶችና መኪኖችን በድንጋይ መደብደባቸው የተሰማ ሲሆን የደቡብ ሱዳኑ ሪክ ማቻርና የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንት  ጋትሏክ ቱት የተሳፈሩባት መኪና በሰልፈኞቹ በድንጋይ መደብደቧን ነገር ግን በሰዎቹ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱ ተሰምቷል፡፡

Saturday, April 23, 2016

በወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ሰቆቃ፤ ሞትና ስደት ለማስቆም ሁላችንም ጠንክረን እንታገል!!!

April 23,2016
የአርበኞ ግንቦት 7 ሳምንታዊ ርዕስ አንቀጽ
አፕሪል 22 2016
ህወሃት ሥልጣን ከተቆጣጠረበት 1983 ጀምሮ በህዝባችንና በአገራችን ላይ እየተፈጸመ ያለው ወንጀል ቁጥር ስፍር የለውም። እስከ አምናና ካቻምና የሆነውን እንኳ ትተን በዚህ በያዝነው አመት ብቻ በወገኖቻችንና በአገራችን ላይ ከተፈጸሙት ወንጀሎች ጥቂቶቹን ብናስታውስ የሚከተሉትን እናገኛለን ፤
በጎንደር በኩል አገራችንን ከሱዳን ጋር የሚያዋሰነውን ለምና ድንግል መሬት ቆርሶ ለርካሽ የፖለቲካ ጥቅም ማራመጃ ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት የተፈጸመውን ስውር ስምምነት የተቃወሙ በርካታ ወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ ስቃይና እንግልት ተፈጽሞአል።
ለዘማናት ተዋህዶ የኖረውን የቅማንትና የአማራ ህዝብ በማንነት ጥያቄ ለመከፋፈልና ለማጋጨት በተደረገው ደባ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ህይወት እንዲቀጠፍ ተደርጎአል።
የወልቃይት ህዝብ ያነሳውን የማንነት ጥያቄ ለማዳፈን ሲባል ለዓመታት ወደ ክልሉ ተሰዶ በሠላም ሠርቶ የሚኖረውን የትግራይ ተወላጅ በማስታጠቅና በማነሳሳት በሁለቱ መሃል ጥላቻና ቂም እንዲረገዝ ተደርጎአል።
በደቡብ የአገራችን ግዛት የማንነት ጥያቄ ያነሱና ወያኔ ለሚያካሂደው የስኳር ምርት ከመሬታቸው አንፈናቀልም ባሉ የኦሞ ሸለቆ ነዋሪዎች ላይ ግዲያና እስር ተፈጽሞአል። በባሪያ ፈንግል ዘመን ይካሄድ በነበረ አዋራጅ ሁኔታ ዜጎች ራቁታቸውን እጅና አንገታቸውን በገመድ ታስረው በወታደር መኪና ሲጓጓዙ ታይቶአል።
በአርባምንጭ ፤ በቴፕና ማጂ በአገዛዙ ዘረፋና ሙስና የተማረሩና ተቃውሞ ያነሱ ዜጎች ሽብርተኛ ተብለው ተደብድበዋል፤ ተገድለዋል፤ ታስረዋል፤ ከሥራቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ተጥለዋል።
በብዙ ድካምና ጥረት ያገኙትን ገንዘብ አጠራቅመው ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው መጠለያ ቤት በአነስተኛ ቦታ ላይ የገነቡ በርካታ ዜጎች የሠሩት ቤት ለከተማ ውቤት አይመጥንም ተብሎ በላያቸው ላይ በቡልዶዘር እንዲፈርስ ተደርጎ ለበረንዳ አዳሪነት ተዳርገዋል።
በአፋርና በሱማሌ ክልሎችም እንዲሁ ከመሬት ነጠቃ ጋር በተያያዘ ወንጀል ከመሬታችን አንፈናቀልም ያሉ ዜጎች ታስረዋል ፤ ተገድለዋል ፤ ለስደት ተዳርገዋል።
ሃሳባቸውን በነጻነት ለመግለጽ የሞከሩ፤ የአገዛዙን ዘረኛ አካሄድና ዘረፋ የተቃወሙ በርካታ ዜጎች በተቀነባበረ የሽብርተኝነት ወንጀል እየተከሰሱ ዝብጥያ ወርደዋል፤ እስር ቤት ውስጥ እያሉም በጨካኞችና አረመኔዎች አሰቃቂ ድብደባና ማሰቃያ እርምጃ ተፈጽሞባቸዋል።
ለወያኔ ባለሥልጣናት ከፍተኛ የሃብት ምንጭ የሆነውን የመሬት ዘረፋ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሥም ለማካሄድ የተደረገውን እንቅስቃሴ ተቃውመው አደባባይ በወጡ የኦሮሚያ አካባቢ ተወላጆች ላይ መጠነ ሰፊ የሆነ ጭፍጨፋ በአጋዚ ጦር እንዲካሄድ ተደርጎአል። በዚህም የተነሳ ከ400 በላይ ዜጎች ህይወት ተቀጥፎአል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ከትምህር ገበታቸው ታድነው እስር ቤት ተወርውረዋል፤ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ዜጎች አካባቢያቸውን ለቀው ተሰደዋል።
ህዝባችን ከፍተኛ የረሃብ አደጋ አንዣቦበት አለም አቀፍ ለጋሾች ህይወት ለማዳን በሚራወጡበት ወቅት ለባለሥልጣናቱ መኖሪያ ዘመናዊ ቪላ ለመገንባት ከመንግሥት ካዜና በብዙ መቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ እንዲሆን ተደርጎአል።
የወያኔ መሪዎች ከደሃው ህዝብ ጉሮሮ እየዘረፉ ወደ ውጪ ከሚያሸሹት በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ውስጥ አምስት ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ በአንድ የወያኔ አባል በሻንጣ ተይዞ እንግሊዝ አገር ለማስገባት ሲሞከር ተይዞአል።
በቅርቡም በቻይና አየር ማረፊያ በተመሳሳይ መንገድ የተገኘ ብዙ ሺህ የአሜሪካን ዶላር ለሥርዓቱ ቅርበት እንዳለው በተገለጸ ሰው እጅ ተገኝቶ በቁጥጥር ሥር ከዋለ ቦኋላ በባለሥልጣናቱ ጣልቃገብነት መለቀቁ ተዘግቦአል።
ይህ ሁሉ ሰቆቃና ግዲያ መንግሥት ነኝ በሚለው የህወሃት አገዛዝ በወገኖቻችንና በአገራችን ላይ መፈጸሙ አንሶ ድንበር አቋርጠው ገቡ የተባሉ ታጣቂ ሃይሎች ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ከ230 በላይ ወገኖቻችንን ገድለው ከ150 በላይ ህጻናትን ከእናቶቻቸው ጉያ ነጥቀው ተሰውሮአል። በጣም የሚያሳዝነውና አገራችን ያለቺበትን የውድቀት ደረጃ ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው ደግሞ በሁለት ቀናት ዕድሜ እንዲህ አይነት ጭፍጨፋ በወገኖቻችን ላይ ፈጽሞ ወደመጣበት የተመለሰ የውጭ ታጣቂ ሃይል ማንነት እስከዛሬ አልታወቀም መባሉ ነው ።
ሌላው አሳዛኝ ክስተት በአገራቸው ተስፋ የቆረጡና ኑሮ የምድር ስኦል ሆኖባቸው በስደት የተለያዩ አፍሪካ አገሮች ውስጥ በመንከራተት ላይ ከነበሩ ኢትዮጵያዊያን መካከል በጀልባ ወደ አውሮጳ ለማምለጥ ሲጓዙ ከ200 በላይ የሚሆኑት ሜዲትራንያን ባህር ውስጥ ሰጥመው የአሳ እራት ሆነዋል። በታንዛኒያ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙ በርካታ ወጣቶች ለረጅም ወራት በታንዛኒያ እስር ቤት ውስጥ ሲማቅቁ ቆይተው ከተለቀቁ ቦኋላ የታንዛኒያ መንግሥት አገልግሎቱን እንደጨረሰ ዕቃ ኬንያ ጠረፍ ላይ ወስዶ አራግፎአቸዋል። በእርምጃው ደስተኛ ያልሆነው የኬንያ ፖሊስም ወጣቶቹን አፍኖ ወደ መጡበት ታንዛኒያ ምድር በመመለስ አውላላ ሜዳ ላይ አራግፎአቸው ተመልሶአል። አዛኝና ተቆርቋሪ መንግሥት የሌላቸው እነዚህ ወጣቶች በማያውቁት አገር ለጅብ እራት አሳልፈው ተሰጥተዋል ። ይህ ሁሉ መከራና ስቃይ በወገኖቻችን ላይ ሲፈራረቅ ህዝባችንን ለዚህ ሰቆቃ የዳረጉት ወያኔና ግብረአበሮቹ ከህዝብ በዘረፉት ገንዘብ ፎቅ ላይ ፎቅ በመገንባት በዶላር እያከራዩ ሃብት ላይ ሃብት ያከማቻሉ። ልጆቻቸውንና የቅርብ ዘመዶቻቸውን በዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ከአገር እየሸኙ ውድና ምርጥ በተባሉ ትምህርት ቤቶች ያስተምራሉ ።
አርበኞች ግንቦት 7 በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው ሰቆቃ ፤ ግዲያ ፤ እስርና ስደት መቆም የሚችለው የአፈናው ፤ የግዲያው እና የስደቱ ምንጭ የሆነው የወያኔ አገዛዝ ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ መወገድ ሲችል ብቻ ነው ብሎ ያምናል። ለአገሩና ለወገኑ የሚቆረቆር ማንኛውም ዜጋ የዚህን ዘረኛና ከፋፋይ አገዛዝ የሥልጣን ዕድሜ ለማሳጠር የተጀመረውን ሁለገብ ትግል አቅሙ በፈቀደ መንገድ ሁሉ እንዲያግዝና ትግሉን እንዲቀላቀል አርበኞች ግንቦት 7 ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል። ሁላችንም ጠንክረን በመታገል በአገራችንንና በወገኖቻን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ፤ ግዲያና ስደት ማስቆም እንችላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!