Sunday, March 15, 2015

እንግሊዝ በኢትዮጵያ ያለው ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት አፈጻጸም ያሰጋኛል አለች!!!

March 15,2015
የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ላልተገባ ዓላማ እየዋለ ነው በሚል ተችታለች

የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መጋቢት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ባወጣው የ2014 (እ.ኤ.አ.) የሰብዓዊ መብትና የዴሞክራሲ ሪፖርት፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ ኢትዮጵያ በምትፈጽማቸው ገደቦች ሥጋት እንደገባው አስታወቀ፡፡ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ ላልተገባ ዓላማ እየዋለ ነው በሚልም ተችቷል፡፡

የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ሥራ ላይ ከዋለ በኋላ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችና ሌሎች አካላት ሕጉ ተጠቅሶ የተከሰሱት የመሰብሰብና ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን ለመጠቀም ሙከራ ሲያደርጉ እንደሆነ ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡
በዓመቱ የዞን ዘጠኝ አባላት የሆኑ ሰባት ጦማሪያንና አቶ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ 17 ጋዜጠኞች በቁጥጥር ሥር እንደዋሉም ሲፒጄን በመጥቀስ ሪፖርቱ አትቷል፡፡ ይህም ጋዜጠኞችን በማሰር ኢትዮጵያ ከዓለም በአራተኝነት ደረጃ እንደሚያስቀምጣት አመልክቷል፡፡ 30 ጋዜጠኞች በዓመቱ ከአገር እንደተሰደዱ የገለጸው ሪፖርቱ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የመክሰስ ሐሳብ ስለሌለው ሊመለሱ ይችላሉ ማለቱንም ጠቅሷል፡፡

እንግሊዝ ኢትዮጵያ የኦሮሚያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት 20 ጋዜጠኞች የተባረሩት በክልሉ የተከሰተውን የተማሪዎች አመፅ በዘገቡበት ተቺ አቀራረብ የተነሳ እንደሆነም እንደሚታመን ጠቅሷል፡፡ የአምስት መጽሔቶችንና የአንድ ጋዜጣ ኅትመት የተቋረጡትም በመንግሥት ውሳኔ እንደሆነ አመልክቷል፡፡ በአገሪቱ የኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ተደራሽነት የተገደበ እንደሆነም ሪፖርቱ ጠቅሷል፡፡ የግል አሳታሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋና በአስተማማኝ ሁኔታ የማተሚያ ቤት አገልግሎት ማግኘት አለመቻላቸውም እንደ ሳንካ እንደሚቆጠር ገልጿል፡፡ ለጋዜጠኞች የሙያ ሥልጠና በመስጠትም ረገድ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚጠበቅበትን እየሠራ እንዳልሆነ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
ሪፖርቱ የእንግሊዝ መንግሥት በሚዲያ ነፃነት ላይ መንግሥት የሚፈጽማቸውን ገደቦች በሚመለከት ከኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መነጋገሩንም ያስታውሳል፡፡ በተለይም በመስከረም 2007 ዓ.ም. በተመድ የሰብዓዊ መብት ካውንስል በዓለም አቀፍ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ግምገማ (UPR) ላይ፣ ኢትዮጵያ ምርጫ 2007 ከምርጫ 2002 በተቃራኒ ወካይና አሳታፊ እንዲሆን ተጨባጭ ዕርምጃ እንድትወስድ የእንግሊዝ መንግሥት ምክረ ሐሳብ ሲሰጥ ተቀብላው የነበረ ቢሆንም፣ ዕርምጃዎቹ እስኪወሰዱ እንግሊዝ አሁንም እየጠበቀች እንደሆነ ገልጿል፡፡

እንግሊዝ በፕሬስ ነፃነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖራቸዋል ብላ ያመነችባቸውን ጉዳዮች በፍርድ ቤት መከታተሏንና ይህም ዓለም አቀፍ ደረጃ መሟላቱን ለመገምገም እንደረዳ ተገልጿል፡፡ ባለፈው ዓመት በግንቦትና በሐምሌ ወራት የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምኅዳሩና ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት አስፈላጊ እንደሆነ በመግለጫው መጠቆሙን ያስታወሰው ሪፖርቱ፣ ኅብረቱ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ጦማሪያን፣ ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች የፍርድ ሒደት ሰብዓዊ መብታቸውን ባከበረ መንገድ እንዲካሄድ መጠየቁን አመልክቷል፡፡

የእንግሊዝ መንግሥት የፕሬስ ነፃነትን ማክበር የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ እንደሚያጠናክርና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ በአገሪቱ ዘላቂ መረጋጋትን ለማስፈን እንደሚያግዝ እምነት እንዳለው ሪፖርቱ ገልጿል፡፡

በሪፖርቱ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ያለውን አስተያየት የተጠየቁት የመንግሥት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ‹‹ኢትዮጵያ ራሷን ከሽብርተኝነት ለመጠበቅ የምታደርገው ዕርምጃ አግባብ አይደለም የሚሉ አካላት ለተመሳሳይ ሥጋት ተመሳሳይ ዕርምጃ ሲወስዱ፣ የእነሱ ድርጊት ተገቢ የመንግሥት ሥራ የሚሆንበት አመክንዮ አይገባኝም፤›› ብለዋል፡፡ ይሁንና መንግሥት ሪፖርቱን በዝርዝር ከተመለከተ በኋላ ምላሽ  እንደሚሰጥበት ገልጸዋል፡፡

Friday, March 13, 2015

በህወሓት ላይ የሚቀርቡ ተቃውሞዎች ሁሉ ወደ እምቢተኝነት ይደጉ!

March 13,2015
pg7-logoየኢትዮጵያ ሕዝብ በአለፉት 23 ዓመታት በህወሓት ዘረኛ አገዛዝ የደረሰበት ስቃይ እንዲቀንስ፤ ገዢዎቹ ከጫንቃው እንዲወዱ፤ ህወሓትን አውርዶ የሚፈልጋቸው መሪዎችን በነፃነት እንዲመርጥ ሲጠይቅና አቤቱታ ሲያሰማ ቆይቷል። በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሕዝብ ምኞት የሚሳካ መስሎ የታየ የነበረ ቢሆንም በአገዛዙ አረመኔዓዊ እርምጃ ተሰናክሏል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ “ድምፃችን ይሰማ” የሚሉ አቤታዎች ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች መምጣት ጀምሯል – “ድምፃችን ይሰማ ሙስሊሞች”፣ “ድምፃችን ይሰማ ኦርቶዶክሶች”፣ “ድምፃችን ይሰማ መምህራን”፣ “ድምፃችን ይሰማ ተማሪዎች”፣ … ወዘተ። በተለይ ሙስሊም ወገኖቻችን በተደራጀ መንገድ “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ ሲወተውቱ ሦስት ተከታታይ ዓመታት አልፈዋል። ወገኖቻችን “ድምፃችን ይሰማ” በማለታቸው ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል።
አቤቱታ የሚሰማ ጆሮ የሌለው አገዛዝ ሲገጥም ምን ይደረጋል? ለአቤቱታ አቅራቢው ያለው ምርጫ ከሁለት አንድ ነው። ወይ አቤቱታን እርግፍ አድርጎ ጥሎ በደልን ተቀብሎ “እህህ !” እያሉ መኖር፤ አሊያም “በቃኝ፣ እንቢ አልገዛም” ማለት፤ ሦስተኛ ምርጫ የለም።
አቤቱታ ሰሚ ሲያጣ እና ሕዝብ መሮት “እንቢኝ፣ አልገዛም” ሲል ነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተቀሰቀሰ የሚባለው። ሕዝባዊ እምቢተኝነት ብዙ መልኮችና ቅርጾች ቢኖሩትም ዋነኛዎቹ መገለጫዎች ሁለት ናቸው። አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የሚፈልገውን አለማድረግ እና/ወይም አገዛዙ ሕዝብ እንዲያደርግ የማይፈልገውን ማድረግ።
ለምሳሌ፣ አገዛዙ ሹማምንቱ እንዲከበሩ፣ ሕዝብ እንዲታዘዝላቸው ይፈልጋል፤ እንቢ ያለ ሕዝብ ግን የአገዛዙን ሹማምንት ይንቃል፣ በየደረሱት ያዋርዳቸዋል፣ “አልታዘዛችሁም” ይላቸዋል። ማንኛውም መንግስት የዳኝነት ሥርዓቱ እንዲከበርለት ይፈልጋል፤ በደል የመረረው ሕዝብ ግን የአምባገነኖች ችሎት ውሳኔ አይቀበልም፤ ዳኞችንም ዳኝነትንም አያከብርም። ሕዝብ የመንግሥትን ግብር በወቅቱ እንዲከፍል የማንኛውም መንግሥት ፍላጎት ነው። በመንግሥት ያመረረ ሕዝብ ግን ግብር አይከፍልም፤ መክፈል ግድ ከሆነበትም አዘግይቶ፣ አስለፍቶ ነው። የመረረው ሕዝብ ምሬቱን መፃፍ በሌለበት ቦታ ይጽፋል። በደል የበዛበት ሕዝብ “ዝም በል” ሲሉት ይናገራል፤ “ተናገር” ሲሉት ዝም ይላል።
አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ የሕዝባዊ እምቢተኝተኝነት እርምጃዎች ጅምሮች እየታዩ ነው። በአማራ ክልል፣ ሕዝብ በሹማምንት ላይ የራሱን እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሕዝብ ራሱ የፓሊስንም የፍርድ ቤትንም ሥራ ተክቶ እየሠራ ነው። ይህ መበረታታት ያለበት ትልቅ እርምጃ ነው። እንደዚሁም ሁሉ በተለይ ወጣቶች ብሶቶቻቸውን በብር ኖቶች ላይ ጽፈው ገበያው እንዲያዘዋውራቸው እያደረጉ ነው። ይህም “የወረቀት ገንዘብን ለተሠራበት ዓላማ ብቻ ተጠቀሙ” የሚለውን ህግ በመጣስ ለቅስቀሳ ሥራ መጠቀም በመሆኑ የሕዝባዊ እምቢተኝነት አካል ነው። በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ውስጥ በርካታ የወረቀት ገንዘቦች በምሬት መግለጫነት ይውላሉ ተብሎ ይገመታል።
በተጓዳኝ በርካታ አማራጭ ስልቶች ሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ተቀማጭ ገንዘብን ከህወሓት ባንኮች ማውጣት በቀላሉ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ስልት ነው። በውጋጋን ባንክ ተጀምሮ ወደ አንበሳ ኢንተርናሽናል ከዚያም ወደ ንግድ ባንክ ማሸጋገር ይቻላል።
በወገኖቻችን ላይ የግፍ ፍርድ የሚያስፈርዱ አቃቢያነ ህግ እና የግፍ ብይኖችን የሚሰጡ ዳኞች በቸልታ ሊታለፉ አይገባም። በእስር ቤቶችም በወገኖቻችን ላይ ሰቆቃ እየፈፀሙ ያሉ ጨካኞች ከሰላማዊ ሕዝብ ጋር ተደባልቀው ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሩ ሊፈቀድላቸው አይገባም። እነዚህ ሁሉ ሊወገዙ፣ ሊገለሉ፣ በየደረሱበት ሊዋረዱ ይገባል።
በአገዛዙ መንግሥታዊ መዋቅር ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችን በሥራቸው ላይ መለገም ተቀባይነት ያለው በጎ ተግባር እንደሆነ ሰፊ ግንዛቤ ሊያገኝ ይገባል። ከአምባገነን ሥርዓት ጋር መተባበር እኩይ ተግባር ሲሆን አምባገነን ሥርዓትን ከውስጥ መቦርቦር ደግሞ የሚበረታታ ሰናይ ሥራ ነው።
ለወያኔ አገዛዝ ግብር መክፈል የምናቆምበት ሰዓትም ተቃርቧል። በራሳችን ገንዘብ ገዳዮቻችን እንዲሰለጥኑብን መፍቀድ የለብንም። ስለሆነም “ግብር አንከፍልም”፤ “መዋጮዎቻችሁ አይመለከቱንም” የምንልበት ቀን ቀርቧል።
በፋይዳ የለሽ ምርጫ የሀገር ሀብት ሲመዘበር ማየት አንሻም። በአግባቡ ለማይቆጠር ድምፃችን አንድም ደቂቃ የምናባክንበት ምክንያት የለምና ሁላችንም የምርጫ ካርዶቻችንን ቀዳደን ቁርጭራጮቹን በየመንገዱ ልንበትናቸው ይገባል።
እነዚህን እነዚህን የመሳሰሉ ናቸው የሕዝባዊ እምቢተኝነት የመጀመሪያ ደረጃዎች። እነዚህን እያደረግን በምስጢር መደራጀታችንን እንቀጥል። ከጥቂት በኋላ አምባገነኑን ሥርዓት የሚያንበረክክ ኃይል እንፈጥራለን። ጥቃት ቢደርስ የሚመክት ኃይል የተደራጀ በመሆኑም ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽ ተቀናጅተው እንዲሄዱ ይደረጋል።
አርበኞች ግንቦት 7:የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሕዝባዊ እምቢተኝነትንና ሕዝባዊ አመጽን አቀናጅቶ ለመምራት የተዘጋጀ፤ ለዚህ የሚያበቃው ድርጅታዊ አቅም እየገነባ ያለ ድርጅት ነው። አርበኞች ግንቦት 7 “እንሰባሰብ በወያኔ ላይ የምናቀርባቸው ተቃውሞዎች በሙሉ ወደ እምቢተኝነት ከፍ እናድርጋቸው” ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Ethiopia: Human Rights Abusers should be barred from the United States

March 13, 2015
Laura Hruby
Ethiopian Desk Officer
Office of East African Affairs
Bureau of African Affairs
Washington D.C. 20520
Tel: (202) 647-6473
Email: HrubyLP@state.gov
Date: March 11. 2015
Re: Human Rights Abusers should be barred from the United States.
We are writing this letter to lodge a formal complaint to why Mr. Abdi Mohamud Omar, the Somali Regional President of Ethiopia, was permitted an entry visa to the United States. To the best of our knowledge, this is the third time Mr. Abdi Mohamud Omar was allowed to enter the United States, despite his cruel human rights record which the State Department is clearly knowledgeable. In January of 2011, Mr. Omar’s first visit to the United States, the good offices of our two Minnesota Senators, Senator Amy Klobuchar and Senator Al Franken, as well as Congressman Keith Ellison have personally contact the State Department and pleaded to stop Mr. Omar’s entry to the United States.
Mr. Abdi Mohamud Omar, the Somali Regional President of Ethiopia
Mr. Abdi Mohamud Omar, the Somali Regional President of Ethiopia
We are again at your mercy to consider our request. We are vehemently protesting the decision to allow Mr. Omar to enter the United States. Mr. Omar and his delegation are known human rights violators who have earned despicable record in their part for the suffering of the Ogaden Somali civilians in Ethiopia. Mr. Omar, who leads the delegation, is the person who is responsible for the creation and maintenance of the brutal paramilitary force called Liyuu Police whose mission is to perpetuate dreadful crimes against innocent civilians. Under the supervision of Mr. Omar, thousands of people have been mass executed, tortured, raped, and displaced. The crimes he is responsible for has been cited in many reputable reports published by independent organizations like the Human Rights Watch, Amnesty, and your own Department of State’ yearly Human Rights report which highlights these unspeakable crimes in details. Mr. Omar uses the Liyuu Police to solely created fear of terrorizing the population. The Liyuu Police are systematically unleashed on the population to commit crimes against humanity. The magnitude of their oppression is intense and widespread. Please view the attached testimonies as evidences to show you that Mr. Omar’s forces perpetuating unabated arbitrary arrests, open executions, torture, imprisonment without fair trail, and mass disappearances. Moreover, Mr.Omar’s troops are using rape as a weapon to suppress innocent and defenseless women.
We believe it was wrong for the State Department to issue a diplomatic visa to a registered human rights violator and his associates. The United States law prohibits entry to anyone with this distained record. We should comply with these rules when issuing visas. We are respectfully requesting from your office to enforce the rule governing “No Safe Haven: Law Enforcement Operation against Human Rights Violator in the U.S. Law”. It is only fair that Mr. Omar and his delegation should immediately be removed from the United States ‘soil. We appreciate for your understanding in this urgent matter.
Evidences against Mr. Omar and his delegation.
Abdullahi Hussein’s testimony at Frontline Club Oslo, Norway. Abdullahi Hussein was Abdi Mohamud Omar’s personal assistant and cameraman.
https://vimeo.com/88461621
Ethiopian military displays dead bodies of civilian & freedom fighters for public fear
https://www.youtube.com/watch?v=18PC38rplr0
Dictator Meles Zenawi’s Ogaden Genocide – Ethiopia
https://www.youtube.com/watch?v=UeR3AmFOzOc
https://www.youtube.com/watch?v=TcSZg_lgFxM
Human Rights Watch Publication
http://www.hrw.org/news/2008/06/12/ethiopia-army-commits-executions-torture-and-rape-ogaden
Martin Plaut
https://martinplaut.wordpress.com/2014/01/31/silence-and-pain-ethiopias-human-rights-record-in-the-ogaden/
Martin Schibble and Johan Persson testimony
https://www.youtube.com/watch?v=gL6p6GgUKts
http://www.tesfanews.net/ethiopia-may-stand-trial-for-genocide/
http://www.svt.se/nyheter/varlden/in-english-a-wave-of-ethiopian-atrocities-against-villages-in-ogaden
U.S. Department of State Human Rights Report 2013
http://www.ice.gov/human-rights-violators-war-crimes-unit
CC. Linda Thomas-Greenfield, Assistant Secretary of State for African Affairs.
CC. Governor of Minnesota, Mark Dayton
CC. Senator Amy Klobuchar
CC. Senator Al Franken
CC. Congressman Keith Ellison
CC. Congressman Erik Paulsen
CC. Congresswoman Betty McCollum
CC. Mayor Betsy Hodges
CC. Department of Homeland Security
CC. Immigration and Customs Enforcement
CC. National Public Radio
CC. Huffington Post
Thank you,
Ogaden American Community of Minnesota.
3055 Old Hwy 8,
Minneapolis, MN 55418

Tuesday, March 10, 2015

‹‹ኢህአዴግ እያታለላችሁ ነው፡፡ እናንተም ለመታለል ዝግጁ ሆናችኋል›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

March 10,2015
(ነገረ ኢትዮጵያ) የአውሮፓ ህብረት ዛሬ መጋቢት 1/2007 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው ጽ/ቤቱ ባደረገው ስብሰባ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በተጋባዥ እንግዳነት ተገኝተው ከህብረቱ ተወካዮች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ኤምባሲ ያላቸው 20 ያህል የህብረቱ አባል አገራት በተገኙበት ስብሰባ ላይ አብዛኛዎቹ በአምባሳደሮቻቸው እንዲሁም ቀሪዎቹ በምክትል አምባሳደሮቻቸው ተወክለው የተገኙ ሲሆን ተወካዮቹ ወቅታዊ የምርጫ ሂደት እንቅስቃሴና የሰማያዊን የምርጫ እንቅስቃሴ፣ በምርጫው ሂደት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች፣ የፓርቲው አማራጭ ፖሊሲዎች፣ የድርጅቱን ጥንካሬ፣ የአንድነት አባላት ወደሰማያዊ መምጣታቸው ለትግሉ የሚኖረው ትርጉምና ሌሎችም ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለኢ/ር ይልቃል ጌትነት ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በበኩላቸው ሰማያዊ ፓርቲ ከ200 በላይ ዕጩዎች በህገ ወጥ መንገድ እንደተሰረዙበት፣ የፓርቲው የቅስቀሳ መልዕክቶቹ ከ6 ጊዜ በላይ በሚዲያ እንዳይተላለፍ መከልከሉን፣ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ድብደባ፣ እስራትና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ጠቅሰው በምርጫ ሂደት ኢህአዴግ አፋኝነቱን አጠናክሮ መቀጠሉን ገለጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የአንድነት አባላት ሰማያዊን መቀላቀላቸው ትግሉን እንደሚያጠናክረው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንድነትና መኢአድ ላይ የተፈፀመው ህገ ወጥ ተግባር መሆኑን እንዲሁም ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን በኃይል እያጠፋ ‹‹ከእኔ ውጭ አማራጭ የለም›› የሚል አቋሙን ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ማሳየት እንደሚፈልግ ለህብረቱ ተወካዮች አስረድተዋል፡፡

‹‹የአውሮፓ ህብረት ችግር የኢትዮጵያን ችግር በአውሮፓውያን ተቋማትና የስነ ልቦና ልክ ማየቱ ነው›› ያሉት ኢ/ር ይልቃል የአውሮፓ ህብረት ‹‹የተቃዋሚዎች አማራጭ ፖሊሲያቸው ምንድን ነው?›› በሚል የሚያነሱትን ተደጋጋሚ ጥያቄ አስታውሰው መደረጀትና መናገር ያልቻለውን የኢትዮጵያን ህዝብ በአውሮፓ ተቋም አይን አይቶ እንዲህ አይነት ጥያቄዎችን ማንሳቱ ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ብዙም እርባና እንደሌለው ገልጸዋል፡፡ ‹‹በእኛ አገር የፖለሲ አማራጭ ለማቅረብ አይቻልም፡፡ ሚዲያው በገዥው ፓርቲ የተያዘና የተቃዋሚዎችን ሀሳብ የማያስተናግድ ዝግ ሆኗል፡፡ እናንተ እንደምትገምቱት የፖሊሲ አማራጭ ለማቅረብ አመች ሁኔታዎች ቢኖሩ ተቃዋሚዎች ከኢህአዴግ የተሻለ ምሁርራንና ሀሳብ ስላላቸው ዝርዝር ፖሊሲያቸውን ለማቅረብ አይቸገሩም ነበር፡፡›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ኢህአዴግ ‹‹ተቃዋሚዎች የተበታተኑና የተዳከሙ በመሆናቸው ለቀጠናው ሰላም አማራጩ እኔ ብቻ ነኝ›› ብሎ የአውሮፓ ህብረትን እንደሚያታልል የገለጹት ኢ/ር ይልቃል ‹‹ኢትዮጵያውያን ካላቸው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ማየት ስላልቻላችሁ ኢህአዴግ እያታለላችሁ ነው፡፡ እናንተም ለመታለል ዝግጁ ሆናችኋል፡፡›› ሲሉ የአውሮፓ ህብረትን ወቅሰዋል፡፡

Monday, March 9, 2015

የኢትዮጵያ ጠላት ወያኔ – ወያኔ ብቻ ነዉ!

March 9,2015
pg7-logoባለፈዉ ሳምንት አይጋፎረም የሚባለዉና የወያኔን ቱልቱላ በዉጭ አገሮች የሚያናፍሰዉ ድረገጽ ከነብስ አባቱ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ በአደራ የተሰጠዉን አንድ የመላምት ድርሰት የፊት ለፊት ገጹ ላይ ለጥፎት የህዝብን ስሜት የኮረኮረ እየመሰለዉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ ከሁለት ሺ አመታት በኋላ ይሁዳዊ ክህደት ሲክድ እጅ ከፍንጅ ተይዟል። የሚገርመዉ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር ሆኖ ሳለ ያንን የመሰለ የክህደት መንፈስ ልቡ ዉስጥ ያስቀመጠለት ሰይጣን እንደሆነ ሁሉ አዲስ ዘመንና አይጋ ላይ የወጣዉን ጽሁፍ የጻፈዉ ግለሰብም የወያኔ ጌቶቹን ምክር ተቀብሎ አሜን አለ እንጂ የዚህ የዉሸት ድርሰት ጠንሳሾች በሰይጣን የሚመሰሉት የወያኔ መሪዎች ናቸዉ። የጽሁፉ ደራሲ ነኝ ግለሰብ የወያኔን ትዕዛዝ ከመቀበል ዉጭ ያደረገዉ ነገር ቢኖር ስሙ ከፅሁፉ አርዕስት ስር እንዲቀመጥ መፍቀዱ ብቻ ነዉ – ለዚያዉም የብዕር ስም!
አገሮች፤ ድርጅቶች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች የፕሮፓጋንዳ ጦርነት ዉስጥ ሲገቡ በዉሸት ዉስጥ እዉነት ወይም በእዉነት ዉስጥ ዉሸት እየሸነቆሩ ነዉ የፕሮፓጋንዳቸዉ ኢላማ የሆነዉን የህብረተሰብ ክፍል ቀልብ ለመግዛት የሚፍጨረጨሩት እንጂ ዉሸትን በዉሸት ለዉሰዉ ቢያቀርቡማ ህዝብ እንኳን ሊያምናቸዉ ደግሞ ሊሰማቸዉም ፈቃደኛ አይሆንም። ይህ ከሰሞኑ አይጋፎርምና አዲስ ዘመን ላይ የወጣዉ ጽሁፍ ግን ምንም አይነት የፕሮፓጋንዳ ህግ አይከተልም፤ ምክንያቱም ጽሁፉ የተጻፈዉ ህግ የሚባል ነገር በሌለባትና ወያኔና ግብረ አበሮቹ እራሳቸዉ ህግ በሆኑበት አገር ዉስጥ ነዉ። ጽሁፉ ሲጀምር በዉሽት ይጀምርና መሀል ላይ ዉሸቱን በዉሸት አጠናክሮ በዉሸት ይደመደማል። እንደዚህ አይነት የዉሽት ክምር የሚመጣዉ ደግሞ ከሌላ ከየትም ሳይሆን በዉሸት ተወልደዉ፤ በዉሸት አድገዉ በዉሸት ከሸበቱት የወያኔ መሪዎች ብቻ ነዉ። ዉድ አድማጮቻችን የዚህ ጽሁፍ አላማ ለሻዕቢያ ጥብቅና መቆም አይደለም፤ ሻዕቢያ ከኛ በላይ ለራሱ ጥብቅና መቆም ይችላል። የዚህ ጽሁፍ ብቸኛ አላማ የኢትዮጵያ ህዝብ ገንበዙን፤ ሀብቱንና ጉልበቱን አስተባብሮ መዋጋት የሚገባዉ ቀንደኛ ጠላቱ ወያኔ መሆኑን መናገር ነዉ። ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ትናንት ሲከናዉን የምናዉቀዉንና አይናችን ፊት ተፈጽሞ ከ “ሀ” ወደ “ፐ” የተጻፈዉን ታሪክ ዛሬ ወያኔና ቡችሎቹ ከ “ፐ” ወደ “ሀ” ሲያነብቡትና የኢትዮጵያን ህዝብ ለማሳሳት ሲሞክሩ ዝም ብለን አንመለከትምና ይህንን የዉሸት ክምር ከመሰረቱ መናድ እንፈልጋለን።
ይህንን በዉሸት የተጀቦደ የወያኔ ቡትቶ እንዳለ ማቅረቡ የአድማጭን ጆሮ ማደንቆር ስለሚሆን አንሞክረዉም። ሆኖም ወያኔ በተከበበና አንድ እርምጃ ወደማይቀረዉ ዉድቀቱ በቀረበ ቁጥር የሚመዝዛቸዉን አገር የሚገዘግዙ መጋዞች የኢትዮጳያ ህዝብ ከአሁኑ አዉቆ እንዲጠነቀቅ ስለምንፈልግ የፅሁፉን ጎላ ጎላ ያሉ የዉሸት ምሶሶዎች እንዳሉ ለማቅረብ እንገደዳለን።
የመመሪያዉ አይን ያወጣ ዉሸት “በወቅቱ ኢሕአዴግ ከበረሀ ይዞት የመጣው መደበኛ ያልሆነ ሰራዊት ብቻ በእጁ ነበር። ቀድሞ የነበረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሀይል፣ የምድር ጦሩ፣ ታንከኛው፣ መድፈኛው፣ አየር መከላከያው፣ አየርሀይሉ፣ ባህር ኃይሉ፣ ኮማንዶው ሰራዊት፣ ፖሊስና ሌሎችም ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል” ይላል። ይህ ዉሸት ከተለመዱት የወያኔ ተራ ዉሸቶች ጋር ሲተያይ ተጠንቶበት በጥንቃቄ የተዋሸ ዉሸት ይመስላል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ወራዊት ሰራዊት አባላት በገዛ ፈቃዳቸዉ የተበተኑ ይመስል የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ የቀድሞዉ የመከላከያ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተበትነዋል እያለ ነዉ የሚነግረን። በእርግጥም ቁጥሩ ከ300 መቶ ሺ በላይ የሚሆን ሰራዊት የኢትዮጵያ ሠራዊት መሆኑ ተረስቶ የደርግ ጦር፤ የትምክህተኞች ኃይል ወይም የነፍጠኞች ምሽግ እየተባለ በወያኔ ዘረኞች ተበትኖ በምትኩ በአንድ ዘር የበላይነት ላይ የተመሰረተ የመከላከያ ኃይል ተገንብቷል። የቀድሞዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የማን ሠራዊት እንደነበር፤ ለምንና በማን እንደተበተናና በምትኩም የተገነባዉ ሠራዊት ለማን ጥቅም እንደቆመ የኢትዮጵያ ህዝብ አንደ ጥቁር ነጭ ለያይቶ የሚያዉቀዉ ሀቅ ነዉና ከዚህ በላይ የምንለዉ ምንም አይኖርም።
ከአንድ ወር በፊት የኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቭዥንና ሬድዮ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያና በኤርትራ ህዝብ መካከል ሊኖር የሚገባዉን ግኑኝነትና ኤርትራ ዉስጥ እየተካሄደ ነዉ የሚባለዉን የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት ትግል እንቅስቃሴ አስመልክቶ እዉነቱን ለህዝብ ለማሳወቅ ታሪካዊ ጉዞ ወደ አስመራና የኤርትራ በረሀዎች አድርገዉ ነበር። በጉዟቸዉ ወቅት ጋዜጠኞቹ ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን የዳሰሰ ቃለ መጠይቅ ከኤርትራዉ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር አድርገዉ ነበር። ይህ ማን ምን ሰራ የሚለዉን ጥያቄ በታሪክ ወደ ኋላ እየሄደ የሚመልሰዉና በአይነቱ ልዩ የሆነዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለመጠይቅ በመገናኛ አዉታሮች መሰራጨት ሲጀምር የኢትዮጵያ ህዝብ ከደደቢት ዉሸትና ተረት ዉጭ ሌላ ሲሰማ የሚያመዉ ወያኔ እንደለመደዉ ሲወራጭና እዉነትን ለመጋረድ ሲፍጨረጨር ታይቷል።
የኢትዮጵያን ህዝብ እንዳሰኛቸዉ የሚረግጡት፤ የሚያስሩት፤ የሚገድሉትና በተለይ በቅርቡ የመስፋፋትና የማፈናቀል ፖሊሲያቸዉን የሚቃወመዉን ሁሉ “ልክ እናስገባዋለን” ብለዉ የዛቱት የወያኔ መሪዎች የእነሱን ጠላትነትና ስር የሰደደ ፀረ ኢትዮጵያ አቋም ሸፍነዉ ኤርትራን የኢትዮጵያ ዋነኛ ጠላት አድርገዉ ማቅረብ ጀምረዋል። የሚገርመዉ ይህ ሁሉ አልበቃ ብሏቸዉ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ በኢሳት ቴሌቪዥን በሚተላለፍበት ወቅት በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይ ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ቀድሞዉኑም ከብልጭ ድርግም አልፎ የማያዉቀዉን አሌክትሪክ ጭራሽ እንዲጠፋ አድርገዋል።
ሻዕቢያና ህወሓት የትጥቅ ትግል በሚያካሄዱበት ግዜ የተነሱበትን ዋነኛ አላማ ለማሳካት የተለያዩ የፕሮፓጋንዳ ጨዋታዎችን ተጫዉተዋል። ከእነዚህ የፕሮፓጋንዳ ጨዋታዎች ዉስጥ አንዱ ኢትዮጵያ ኤርትራን በቅኝ ግዛትነት ይዛለች የሚለዉ ፕሮፓጋንዳ ነዉ።የሚገርመዉ ይህንን ፕሮፓጋንዳ ከባለቤቱ ከሻዕቢያ ይበልጥ የተሸከመዉና ያርገበገበዉ ህወሓት ህወሓት ዉስጥ ደግሞ መለስ ዜናዊና ስብሀት ነጋ ናቸዉ። ይህ ደግሞ ዛሬ እኛ ፈጥረን የምናወራዉ ወሬ ሳይሆን በቦታዉ የነበሩና ህወሓትን የፈጠሩት እን ገብሩ አስራትና እነ ገ/መድህን አርአያ በግልጽ የሚናገሩት እዉነት ነዉ። የትናንቱን የኢህአፓ የበረሃ ዉስጥ ታሪክ ትዝ ለሚለን ደግሞ ህወሓትንና ኢህአፓን ጦር አማዝዞ ለአያሌ ኢትዮጵያዉያን ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆነዉ ኢህአፓ ይህንኑ የወያኔን ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት የሚለዉን መዝሙር አልዘምርም በማለቱ ነበር። እንግዲህ ዛሬ ይህ ሁሉ መረጃና ይህ መረጃ በእጃቸዉ ላይ ያለ ሰዎች በህይወት እያሉ ነዉ የወያኔ አይነ አዉጣዎች “ከመጀመሪያዉም ሻዕቢያ እንደሚለፈልፈዉ ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት አልነበረችም፤ ይህ የእነ ኢሳያስ እብደት ነዉ እያሉ የራሳቸዉን ቀን የቆጠረ ዕብደት የሚነግሩን። በ1967 ዓም እግራቸዉ የደደቢት በረሃን ከረገጠበት ግዜ ጀምሮ በ1983 ዓም አዲስ አበባን እስከተቆጣጠሩበት ግዜ ድረስ በወዶ ገባነት ከገበቡበት ከሻዕቢያ ጉያ ያልተለዩትና አጠገባቸዉ ያለችዉን አክሱም ፅዮንን ትተዉ ሻዕቢያን ሲሳለሙ የከረሙት የወያኔ መሪዎች ዘንድሮ ሳይታሰብ በድንገት ቀኝ ኋላ ዙር ብለዉ ከሻዕቢያ ጋር የነበራቸዉን አለመግባባት መናዘዝ ጀምረዋል። በተለይ “ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ናት” ብለዉ እራሳቸዉ በጻፉት ማኒፌስቶ ዉስጥ ያሰፈሩትን ቃል ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ የረሳ መስሏቸዉ የክህደት ጫጫታ መደርደር ጀምረዋል።
አገራችን ኢትዮጵያ በየዘመኑ በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ ላይ የዘመቱ ብዙ ታሪካዊ ጠላቶች ነበሯት፤ ዛሬም አሏት፤ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ በረጂም ዘመን ታረኩ ዉስጥ እንደ ወያኔ ህልዉናዉን፤ አንድቱንና የወደፊት ተስፋዉን ያጨለመበት የዉጭም የዉስጥም ጠላት አጋጥሞት አያዉቅም። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸዉ፤ ነጻነታቸዉና እኩልነታቸዉ ተከብሮ የኖሩበት ዘመን ባይኖርም ኢትዮጵያ እንደ ወያኔ ዘመን በዘር የተከፋፈለችበትና የመበታተን አደጋ ያጋጠማት ግዜ የለም። ዛሬ የኢትዮጵያን አንድነትና የህዝቦቿን መብትና ነጻነት መከበር አጥብቀዉ የሚሹ ወገኖች ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሊዋጉት የሚገባ ብቸኛ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ጠላት ወያኑ ወይም ህወሓት ነዉ። የኢትዮጵያህዝብ መከፈል የሚገባዉን መስዋዕትነት ከፍሎ ወያኔን በአጭር ግዜ ዉስጥ ካላስወገደ የአገራችን ህልዉና በቀላሉ የማይጠገን አደጋ ዉስጥ መዉደቁ አይቀርም።
ይህ የአገራችን አንድነት አደጋ ላይ የመዉደቁ ዜና እጅግ በጣም የሚያስፈራና የሚያሳዝን ዜና ነዉ። ደግነቱ የሚያስደስተን፤ ተስፋችንን የሚያለመልምና አንገታችንን ቀና የሚያሰደርግ ዜናም አለ። ወያኔ አገራችን ላይ ይዞት የመጣዉ አደጋ ከወዲሁ የታያቸዉ ኢትዮጵያዉያን የአባቶቻችዉን ፈለግ ተከትለዉ ዱር ቤቴ ብለዉ ወያኔን በሚገባዉ ቋንቋ ለማነጋገር ተዘጋጅተዋል።የኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት ደምስሶ ፍትህ፤እኩልነትና ነጻነት የሰፈነባትን ኢትዮጵያ ለመገንባት በሚየደርገዉ ትግል የመጀመሪያዉ ምዕራፍ ዉስጥ እንደ ኤርትራ ህዝባነ መንግስት አጋር ሆኖ የተሸከመዉ ሌላ አገርም መንግስትም የለም።የኤርትራ ህዝብና መንግሰት ወያኔ የሚባል ነቀርሳ ከስሩ እስካልተነቀለ ድረስ የአፍሪካ ቀንድ የሰላም አየር እየተነፈሰ በሠላም መኖር እንደማይችል ከተረዱ ቆይተዋል። ስለዚህም ነዉ የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት አርበኞች አስጠግተዉ አስፈላጊዉን እርዳታ ሁሉ የሚያደርጉላቸዉ። ዛሬ ኢትዮጵያንና ኤርትራን የሚመሩ መሪዎችና መንግስታት ዘሏአለማዊ አይደሉም፤ የሁለቱ አገሮች ህዝብ ወንድማማችነትና ጉርብትና ግን ዘለአለማዊ ነዉ። በዚህ ዘሏአለማዊ ወዳጅነትና ጉርብትና ዉስጥ የስግብግቦቹ የወያኔ መሪዎች አመለካከት “እኔ ከሞትኩ ሠርዶ አይብቀል” ካለችዉ እንስሳ የሚለይ አይደለም።ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ቃለመጠይቅ በግልጽ እንደሰማነዉ በኤርትራ በኩል ያለዉ አመለካከት ለኢትዖጵያነ ለኤርትራ ህዝብ ታሪካዊ ትስስር፤ ጉርብትናና ወደፊት ወዳጅነት እጅግ በጣም ከፍተኛ ግምት የሚሰጥ አመለካከት ነዉ። አርበኞች ግንቦት ሰባትና የኤርትራ መንግስት በኤርትራና የኢትዮጵያ ህዝብ የተሳሰረ የጋራ ዕድገት፤ ብልጽግናና መልካም ጉርብትና ላይ እንደ ነቀርሳ የተተከለዉ ዘረኛዉ የወያኔ ስርዐት ነዉ ብለዉ ያምናሉ። ይህ ነቀርሳ በተባበረ የህዝብ ትግል መነቀል አለበት ብለዉም ያምናሉ።
“አህያዉን ፈርቶ ዳዉላዉን እንዲሉ” ዛሬ ወያኔ “ኤርትራ” “ኤርትራ” እያለ የአዞ የሚያነባዉ እሱ ባልተገራ አንደበቱ ሊነግረን እንደሚፈልገዉ ኤርትራ በእርግጥም የኢትዮጵያ ጠላት ሆና አይደለም። ጉዳዩ ወዲህ ነዉ። ወያኔ በኤርትራ አሳብቦ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነጻነት የቆሙ ኃይሎችን ቆርጦ ተነስቷል፤ ይህንን ለማወቅ ደግሞ ብዙ መረጃ መሰብሰብ አያስፈልግም። እራሳቸዉ የወያኔ መሪዎች በየመድረኩ የተናገሩትንና ቡችሎቻቸዉ ደግሞ በቅርቡ አዲስ ዘመን ላይ የጻፉትን ጽሁፍ ማንበቡ ይበቃል – እንዲህ ሲሉ ነበር የጻፉት “አለም አቀፍ ሕጉን ማክበር በሚል እንጂ ዛሬ ይህንን ደባና ሴራውን በጣጥሦ በመጣል ከነሎሌዎቹ ድባቅ በመምታት ከነበረ ወደአልነበረ በመለወጥ ያለአንዳች እንቅፋት ይሕንን ዘመን የማይሽረው ጸረ ኢትዮጵያ ሀይል ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና እፎይታ ማስገኘት ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያ ቆርጣ ስትነሳ የሚገታት አንድም ሀይል የለም” የኢትዮጵያ ወጣት፤ ሠራተኛ፤ ገበሬ፤ የመከላከያ ሠራዊት አባላትና ባጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ወያኔ ምን ያህል አንተንና አገርህን አንደሚጠላ ባለፉት ሃያ አራት አመታት በግልጽ አሳይቶሀል። ዘንድሮ ደግሞ በተለይ ባለፉት ሦስት ሳምንታት አንተና ልጆችህ በየቀኑ እያደገ በሚሄደዉ የኑሮ ዉድንት እየነደዳችሁ ወያኔ ግን አገራችንን በዘር ከፋፍሎ ለመግዛት የመሠረት ዲንጋይ ያኖረበትን ቀን ለማክበር ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ አባክኗል። ከዚህ በተጨማሪ ነብሰ ገዳይ ፖሊሶቹን አሰማርቶ አባቶችህ አድዋ ላይ ያጎናፀፉህን አንጸባራቂ የጥቁር ህዝብ ድል በሆታና በእልልታ እንዳታከብር አድርጓል።
ባጠቃላይ አርባኛዉ አመት የህወሓት ምስረታና የኢትዮጵያ ህዳሴ የሚል አዲስ የመላምት ታሪክ እንዲጻፍ እያደረገ በአባቶችህና በእናቶችህ ደም የደመቀዉን ትልቁን የአድዋ ድል ታሪክ እንዲደበዝዝ አድርጓል። የኢትዮጵያ ህዝብ ጨዋ ነዉ- በእርግጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ጨዋ ነዉ። ኢትዮጵያዉያን ታጋሾች ናቸዉ? ያለምንም ጥርጥር ኢትዮጵያዉያን አለም የሚያዉቃቸዉ ታጋሾች ናቸዉ። ነገር ግን ትዕግስትም ሆነ ጨዋነት ትርጉም የሚኖራቸዉ ህዝብ መብቱና ነጻነቱ ተከብሮ በማንነቱ ኮርቶ መኖር ሲችል ብቻ ነዉ። እየተረገጠ፤ ልጆቹ ከጉያዉ እየተወሰዱ እየተረሸኑና ታሪኩ ፤ አንድነቱና ብሄራዊ ማንነቱ ሲዋረድ የሚታገስና አንገቱን ደፍቶ የሚኖር ህዝብ የለም። በሳምንቱ መግቢያ ላይ ያከበርነዉ የአድዋ ድል በዐልም የሚያሳስበን ይህንን እዉነት ነዉ። የዚህ ዘመን ኢትዮጵያዊ አባቶቹና እናቶቹ በነጭ ፋሺስቶች ላይ በተጎናፀፈት የአድዋ ድል መኩራት ብቻ ሳይሆን የሱም ልጆች አባቶቼ ብለዉ አንዲኮሩበት የአድዋን ድል በዛሬዎቹ ጥቁር ፋሺስቶች ላይ መድገም አለበት። አድዋ የእኛ የኢትኦጵያዉያን ብቻ ሳይሆን የአለም ጥቁር ህዝብ በነጭ ወራሪዎች ላይ የተጎናፀፈዉ አንፀባራቂ ድል ነዉ። አድዋ ትዕግስትና ጨዋነት ለማይገባቸዉ እብሪተ ችና ትዕቢተኞች ቆራጡና ጀግናዉ የኢትዮጵያ ህዘብ የማይረሳ ትምህርት ያስተማረበት ቦታ ነዉ። ዛሬ ደጃፋቸዉ ላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የሰራዉን ገድል የረሱና አድዋ ላይ ታሪክ ሲሰራም ቢሆን ባንዳዎች የነበሩ የባንዳ ልጆች ከቅኝ ገዢዎች ባልተለየ ጭካኔ፤ ዝርፊያና ጥላቻ አገራችን ኢትዮጵያን እንዳልነበረች እያደረጓት ነዉ። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ከዚሁ ከአድዋ አፈር በቅለዉ በራፋቸዉ ላይ ህዝብ የሰራዉን ታሪክ እየፋቁ የራሳቸዉን የመላ ታሪክ የሚጽፉ ከዲዎችን አባቶቹ ለፋሺስቶች ያስተማረዉን ትምህርት ለነዚህ ፋሽስቶችም እንደገና ማስተማር አለበት።

Ethiopia: Digital Attacks Intensify (Human Rights Watch)

March 9, 2015
(New York) – The Ethiopian government has renewed efforts to silence independent voices abroad by using apparent foreign spyware, Human Rights Watch said today. The Ethiopian authorities should immediately cease digital attacks on journalists, while foreign surveillance technology sellers should investigate alleged abuses linked to their products.Ethiopia: Stop Using Anti-Terror Law to Stifle Peaceful Dissent
Independent researchers at the Toronto-based research center Citizen Lab on March 9, 2015, reported new attempts by Ethiopia to hack into computers and accounts of Ethiopian Satellite Television (ESAT) employees based in the United States. The attacks bear similarities to earlier attempts to target Ethiopian journalists outside Ethiopia dating back to December 2013. ESAT is an independent, diaspora-run television and radio station.
“Ethiopia’s government has over the past year intensified its assault on media freedom by systematically trying to silence journalists,” said Cynthia Wong, senior Internet researcher at Human Rights Watch. “These digital attacks threaten journalists’ ability to protect the safety of their sources and to avoid retaliation.”
The government has repressed independent media in Ethiopia ahead of the general elections scheduled for May, Human Rights Watch said. Many privately owned print publications heavily self-censor coverage of politically sensitive issues or have shut down. In the last year, at least 22 journalists, bloggers, and publishers have been criminally charged, at least six publications have closed amid a campaign of harassment, and many journalists have fled the country.
Many Ethiopians turn to ESAT and other foreign stations to obtain news and analysis that is independent of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front. However, intrusive surveillance of these news organizations undermines their ability to protect sources and further restricts the media environment ahead of the elections. Government authorities have repeatedly intimidated, harassed, and arbitrarily detained sources providing information to ESAT and other foreign stations.
Citizen Lab’s analysis suggests the attacks were carried out with spyware called Remote Control System (RCS) sold by the Italian firm Hacking Team, which sells surveillance and hacking technology. This spyware was allegedly used in previous attempts to infect computers of ESAT employees in December 2013. If successfully installed on a target’s computer, the spyware would allow a government controlling the software access to activity on a computer or phone, including email, files, passwords typed into the device, contact lists, and audio and video from the device’s microphone and camera.
Citizen Lab also found that the spyware used in the attacks against ESAT appeared to have been updated as recently as December 2014. On November 19, a security researcher, Claudio Guarnieri, along with several nongovernmental organizations, publicly released a tool calledDetekt, which can be used to scan computers for Hacking Team RCS and other spyware. Citizen Lab’s testing determined that Detekt was able to successfully recognize the version of RCS used in a November attack, but not the version used in a December attack. Citizen Lab concluded that this may indicate that the software had been updated sometime between the two attempts.
These new findings, if accurate, raise serious concerns that Hacking Team has not addressedevidence of abuse of its product by the Ethiopian government and may be continuing to facilitate that abuse through updates or other support, Human Rights Watch said.
Hacking Team states that it sells exclusively to governments, particularly law enforcement and intelligence agencies. The firm told Human Rights Watch in 2014 that “we expect our clients to behave responsibly and within the law as it applies to them” and that the firm will suspend support for its technology if it believes the customer has used it “to facilitate gross human rights abuses” or “who refuse to agree to or comply with provisions in [the company’s] contracts that describe intended use of HT [Hacking Team] software.” Hacking Team has also stated that it has suspended support for their product in the past, in which case the “product soon becomes useless.”
Media reports and research by independent human rights organizations in the past year have documented serious human rights violations by the Ethiopian government that at times have been facilitated by misuse of surveillance powers. Although spyware companies market their products as “lawful intercept” solutions used to fight serious crime or counterterrorism, the Ethiopian government has abused its counterterrorism laws to prosecute bloggers and journalists who merely report on public affairs or politically sensitive issues. Ethiopian laws that authorize surveillance do not adequately protect the right to privacy, due process, and other basic rights, and are inconsistent with international human rights requirements.
Hacking Team previously told Human Rights Watch that “to maintain their confidentiality” the firm does not “confirm or deny the existence of any individual customer or their country location.” On February 25, 2015, Human Rights Watch wrote to the firm to ask whether it has investigated possible abuse of its products by the Ethiopian government to target independent media and hack into ESAT computers. In response, on March 6 a representative of the firm emailed Human Rights Watch that the company “take[s] precautions with every client to assure that they do not abuse our systems, and, we investigate when allegations of misuse arise” and that the firm is “attempting to understand the circumstances in this case.” The company also stated that “it can be quite difficult to get to actual facts particularly since we do not operate surveillance systems in the field for our clients.” Hacking Team raised unspecified questions about the evidence presented to identify the spyware used in these attacks.
Human Rights Watch also asked the company whether contractual provisions to which governmental customers agree address governments’ obligations under international human rights law to protect the right to privacy, freedom of expression, and other human rights. In a separate March 7 response from the firm’s representative, Hacking Team told Human Rights Watch that the use of its technology is “governed by the laws of the countries of our clients,” and sales of its technology are regulated by the Italian Economics Ministry under the Wassenaar Arrangement, a multilateral export controls regime for dual-use technologies. The company stated that it relies “on the International community to enforce its standards for human rights protection.”
The firm has not reported on what, if any, investigation was undertaken in response to the March 2014 Human Rights Watch report discussing how spyware that appeared to be Hacking Team’s RCS was used to target ESAT employees in 2013. In its March 7 response, the company told Human Rights Watch that it will “take appropriate action depending on what we can determine,” but they “do not report the results of our investigation to the press or other groups, because we consider this to be an internal business matter.”
Without more disclosure of how Hacking Team has addressed potential abuses linked to its business, the strength of its human rights policy will be in question, Human Rights Watch said.
Sellers of surveillance systems have a responsibility to respect human rights, which includes preventing, mitigating, and addressing abuses linked to its business operations, regardless of whether government customers adequately protect rights.
“Hacking Team should publicly disclose what steps it has taken to avoid abuses of its product such as those alleged against the Ethiopian government,” Wong said. “The company protects the confidentiality of its customers, yet the Ethiopian government appears to use its spyware to compromise the privacy and security of journalists and their sources.”

Saturday, March 7, 2015

በአዋሳ በተማሪዎች ላይ የሕወሃት ሰራዊት ተኩስ እንደከፈተ ተዘገበ

March 7,2015
Hawasa University
የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት እንደዘገበው:-

 በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ካምፓስ ዉስጥ የሕወሃት ታጣቂዎች በተማሪዎች ላይ ተኩስ እንደከፈቱ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
በዩኒቨርሲቲ ዛሬ ትምህርት ያልነበረ ሲሆን፣ በርካታ ፌዴራል ፖሊሶች ካምፓሱን ተቆጣጥረዉታል። ጩኸትና ረብሻም ተሰምቷል።

የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በገጠማቸው የውሀ እጥረት ምክንያት ሲሆን ረብሽ ያነሱት፣ በካምፓስ ዉስጥም ከፍተኛ ግርግር ጩኸትና ተኩስ እንደነበር ታውቋል። በግርግሩም ተማሪዎች እንደተጉዱ በርካታ የፌድራል ፖሊሶች የዩኒቨርሲቲውን ግቢ እንደ ወረሩት ተማሪዎቹንም እየደበደቡና እያፈሱ ወደተለያየ እስር ቤቶች እንደወሰዷቸው ታውቋል ፡፡

 ተማሪዎቹ እንደሚሉት ለበርካታ ቀናት ውሀ አጥተው መቸገራቸውን ይህንንም ጉዳይ ለትምህርት ቤቱ ሀላፊዎች ማመልከታቸውን ነገር ግን ችግሩን ሊፈቱላቸው እንዳልቻሉ ተናገረዋል፡፤ ተያይዞም በአከባቢው የሚገኙ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ተማሪዎቹን በመደገፍ አመፁን መቀላቀላቸው ተነገሯል፡፡ አሁን ግርግሩ ቀዝቀዝ ያለ ሲሆን በርካታ የፌድራል ፖሊስ አባላት ከግቢው ውጭ ቆመው ይገኛሉ፡፡ 

Friday, March 6, 2015

ተዋቂው ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ የህዝቡን ትግል ተቀላቀለ !

March 6,2015
2_1812
ጋዜጠኛው በኢትዮጵያዊነቱ አያሌ በደሎች እንደ ተፈጸሙበት ያወጋል ! በተለይ ይላል ጋዚጠኛ አለምነህ ዋሴ ፍትህ እኩልነት በሌለባት ሃገሬ ጋዜጠኛ ርዩት ዓለሙ ላይ የተፈፀመው ኢሰባዊ ድርጊት ከሁሉም በላይ ከህሊናው ሊጠፋ የማይችል ዘግናኝና አረምኔያዊ ድርጊት መሆኑን ይገልጻል ። ጋዜጠኛው ልጆቹን ከማሳደግ ባሻገር ሃገሩ ላይ ሲኖር ደስተኛ እንዳ ልነበረ በመጥቀስ ክእንግዲ አለ ጋዜጠኛ አለምንህ ዋሴ « ፍትህ እኩልነትና ነጻነት እስኪሰፍን » ሃገር አለኝ ብዬ ፊቴን ወደ ኢትዮጵያ አልዞርም ብሏል ። ጋዜጠኛው ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጀት ገለልተኛ ሆኖ ወገኑን ማገልገል እንዳልቻለና የገዢው ስረአት ወሬአቀባይ ሳይሆኑ ገለልተኛ ሆኖ በነጻነት ኢትዮጵያ ውስጥ ሰርቶ መኖር ለህልውና አደገኛ መሆኑን የራሱን ተሞክሮ በመጥቀስ ያብራራል። በስራው ላይ ይደረግበት በነበረ ጫና የማስታወቂያ ስራዎቹ ለአየር እንዳይበቁ በደል እስከመፈጸምና በሙያው በቀን 10 በር ብቻ ተከፍሎት እንዲሰራ የተገደደበት አጋጣሚ እንደነበረ ለኢሳት በሰጠው መረጃ አጋልጦል። ጋዜጠኛው በአሁኑ ሰዓት አስራኤል ውስጥ ስደት ቤቴ ብሎ መኖር የጀመረ ሲሆን ለኢሳት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ዙሪያ ከኢህአ ዴግ መንግስት ባለስልጣናት በኩል ምንም የተባለ ነገር ባይኖረም ጋዜጠኛው ወደ ሶስተኛ ሃገር ካልተሸጋገረ የደህነት ሁኔታው እንደ ሚያሰጋቸው አይሌ ኢትዮጵያውያን ይገልጻሉ። መንግስት ጋዜጠኞች ላይ የሚወስደውን እርምጃ ተስፋ መቁረጥ የሚሉ እንዚህ ታዛቢዎች ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ከተዋቂው ጋዜጠና ዳሪዎስ ሞዴና ነጋሽ፡መሃመድ ቀጥሎ የጋዜጠኛ አለምንህ ድምጹ በተፈጥሮ የህዝብን ልብ ሰብሮ የመግባት ሃይል ስላለው ምናልባት መንግስት ደልሎ አሊያም በሃይል ወደ ሃገር ሊመልሰው እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ ።
ኢትዮጵያን ሃግሬ ጅዳ በዋዲ

Thursday, March 5, 2015

Ethiopia: Amnesty International Report 2014/15

March 5 ,2015
Federal Democratic Republic of Ethiopia
Head of state: Mulatu Teshome Wirtu
Head of government: Hailemariam Desalegn
AmnestyInternational2014-151Freedom of expression continued to be subject to serious restrictions. The government was hostile to suggestions of dissent, and often made pre-emptive arrests to prevent dissent from manifesting. Independent media publications were subject to further attack. Peaceful protesters, journalists, and members of opposition political parties were arbitrarily arrested. The Charities and Societies Proclamation continued to obstruct the work of human rights organizations. Arbitrary detention and torture and other ill-treatment were widespread, often used as part of a system for silencing actual or suspected dissent.
Background
Economic growth continued apace, along with significant foreign investment including in the agriculture, construction and manufacturing sectors, large-scale development projects such as hydroelectric dam building and plantations, and widespread land-leasing, often to foreign companies.
The government used multiple channels and methods to enforce political control on the population, including politicizing access to job and education opportunities and development assistance, and high levels of physical and technological surveillance.
The politicization of the investigative branch of the police and of the judiciary meant that it was not possible to receive a fair hearing in politically motivated trials.
Federal and regional security services were responsible for violations throughout the country, including arbitrary arrests, the use of excessive force, torture and extrajudicial executions. They operated with near-total impunity.
Armed opposition groups remained in several parts of the country or in neighbouring countries, although in most cases with small numbers of fighters and low levels of activity.
Access to some parts of the Somali region continued to be severely restricted. There were continuing reports of serious violations of human rights, including arbitrary arrests and extrajudicial executions. There were also multiple allegations of the rape of women and girls by members of the security services.
Excessive use of force ‒ extrajudicial executions
In April and May, protests took place across Oromia region against a proposed “Integrated Master Plan” to expand the capital Addis Ababa into Oromia regional territory. The government said the plan would bring services to remote areas, but many Oromo people feared it would damage the interests of Oromo farmers and lead to large-scale displacement.
Security services, comprising federal police and military special forces, responded with excessive force, firing live ammunition at protesters in Ambo and Guder towns and Wallega and Madawalabu universities, resulting in the deaths of at least 30 people, including children. Hundreds of people were beaten by security service agents during and after the protests, including protesters, bystanders, and parents of protesters for failing to “control” their children, resulting in scores of injuries.
Thousands of people were arbitrarily arrested. Large numbers were detained without charge for several months, and some were held incommunicado. Hundreds were held in unofficial places of detention, including Senkele police training camp. Some detainees were transferred to Maikelawi federal police detention centre in Addis Ababa. Over 100 people continued to be detained in Kelem Wallega, Jimma and Ambo by security service agents after courts ordered their release on bail or unconditionally.
Many of those arrested were released after varying detention periods, between May and October, but others were denied bail, or remained in detention without charge. Others, including students and members of the Oromo Federalist Congress (OFC) opposition political party, were prosecuted and convicted in rapid trials on various charges relating to the protests.
Freedom of expression, arbitrary arrests and detentions
2014 saw another onslaught on freedom of expression and suggestions of dissent, including further targeting of the independent media and arrests of opposition political party members and peaceful protesters. Several attempts by opposition political parties to stage demonstrations were obstructed by the authorities. The Anti-Terrorism Proclamation continued to be used to silence dissidents. Opposition party members were increasingly targeted ahead of the 2015 general election.
In late April, six bloggers of the Zone 9 collective and three independent journalists associated with the group were arrested in Addis Ababa, two days after the group announced the resumption of activities, which had been suspended due to significant harassment. For nearly three months, all nine were held in the underground section of Maikelawi, denied access to family members and other visitors, and with severely restricted access to lawyers.
In July, they were charged with terrorism offences, along with another Zone 9 member charged in their absence. The charge sheet cited among their alleged crimes the use of “Security in a Box” – a selection of open-source software and materials created to assist human rights defenders, particularly those working in repressive environments.
Six of the group said they were forced to sign confessions. Three complained in remand hearings that they had been tortured, but the court did not investigate their complaints. The trial continued at the end of 2014.
Early in 2014, a “study” conducted by the national Press Agency and Ethiopian News Agency and published in the government-run Addis Zemen newspaper targeted seven independent publications, alleging that they had printed several articles which “promoted terrorism”, denied economic growth, belittled the legacy of former Prime Minister Meles Zenawi, and committed other “transgressions”. In August, the government announced that it was bringing charges against several of the publications, causing over 20 journalists to flee the country. In October, the owners of three of the publications were sentenced in their absence to over three years’ imprisonment each for allegedly inciting the public to overthrow the government and publishing unfounded rumours.
The OFC opposition party reported that between 350 and 500 of its members were arrested between May and July, including party leadership. The arrests started in the context of the “Master Plan” protests, but continued for several months. Many of those arrested were detained arbitrarily and incommunicado. OFC members were among over 200 people arrested in Oromia in mid-September, and further party members were arrested in October.
On 8 July, Habtamu Ayalew and Daniel Shebeshi, of the Unity for Democracy and Justice (UDJ) Party, and Yeshewas Asefa of the Semayawi Party were arrested in Addis Ababa. Abraha Desta of the Arena Tigray Party, and a lecturer at Mekele University, was arrested in Tigray, and was transferred to Addis Ababa. They were detained in Maikelawi and initially denied access to lawyers and family. In late October, they were charged under the Anti-Terrorism Proclamation. Yeshewas Asefa complained in court that he had been tortured in detention.
The Semayawi Party reported numerous arrests of its members, including seven women arrested in March during a run to mark International Women’s Day in Addis Ababa, along with three men, also members of the party. They had been chanting slogans including “We need freedom! Free political prisoners!” They were released without charge after 10 days. In late April, 20 members of the party were arrested while promoting a demonstration in Addis Ababa. They were released after 11 days.
In early September, Befekadu Abebe and Getahun Beyene, party officials in Arba Minch city, were arrested along with three party members. Befekadu Abebe and Getahun Beyene were transferred to Maikelawi detention centre in Addis Ababa. In the initial stages of detention, they were reportedly denied access to lawyers and family members. In late October, party member Agbaw Setegn, was arrested in Gondar, and was also transferred to Maikelawi, and held incommunicado without access to lawyers or family.
On 27 October, editor Temesgen Desalegn was sentenced to three years’ imprisonment for “defamation” and “inciting the public through false rumours”, in the now-defunct publication Feteh, after a trial that had lasted more than two years. The publisher of Feteh was also convicted in their absence.
People were detained arbitrarily without charge for long periods in the initial stages, or throughout the duration, of their detention including numerous people arrested for peaceful opposition to the government or their imputed political opinion. Arbitrary detention took place in official and unofficial detention centres, including Maikelawi. Many detainees were held incommunicado, and many were denied access to lawyers and family members.
Numerous prisoners of conscience, imprisoned in previous years based solely on their peaceful exercise of their freedom of expression and opinion, including journalists and opposition political party members, remained in detention. These included some convicted in unfair trials, some whose trials continued, and some who continued to be detained without charge.
Access to detention centres for monitoring and documenting the treatment of detainees continued to be severely restricted.
Torture and other ill-treatment
Torture took place in local police stations, Maikelawi federal police station, federal and regional prisons and military camps.
Torture methods reported included: beating with sticks, rubber batons, gun butts and other objects; burning; tying in stress positions; electric shocks; and forced prolonged physical exercise. Some detention conditions amounted to torture, including detaining people underground without light, shackled and in prolonged solitary confinement.
Torture typically took place in the early stages of detention, in conjunction with the interrogation of the detainee. Torture was used to force detainees to confess, to sign incriminating evidence and to incriminate others. Those subjected to torture included prisoners of conscience, who were arrested for their perceived or actual expression of dissent.
Defendants in several trials complained in court that they were tortured or otherwise ill-treated in detention. The courts failed to order investigations into the complaints.
In several cases, prisoners of conscience were denied access to adequate medical care.
Oromia region
Ethnic Oromos continued to suffer many violations of human rights in efforts to suppress potential dissent in the region.
Large numbers of Oromo people continued to be arrested or remained in detention after arrests in previous years, based on their peaceful expression of dissent, or in numerous cases, based only on their suspected opposition to the government. Arrests were arbitrary, often made pre-emptively and without evidence of a crime. Many were detained without charge or trial, and large numbers were detained in unofficial places of detention, particularly in military camps throughout the region. There was no accountability for enforced disappearances or extrajudicial executions during 2014 or in previous years.
In the aftermath of the “Master Plan” protests, increased levels of arrests of actual or suspected dissenters continued. Large numbers of arrests were reported, including several hundred in early October in Hurumu and Yayu Woredas districts in Illubabor province, of high-school students, farmers and other residents.
There were further reports of arrests of students asking about the fate of their classmates arrested during the “Master Plan” protests, demanding their release and justice for those killed, including 27 reported to have been arrested in Wallega University in late November.
Refugees and asylum-seekers
Forcible returns
Ethiopian government agents were active in many countries, some of which cooperated with the Ethiopian authorities in forcibly returning people wanted by the government.
In January, two representatives of the rebel Ogaden National Liberation Front were abducted and forcibly returned to Ethiopia from Nairobi, Kenya. They were in Nairobi to participate in further peace talks between the group and the government.
On 23 June, UK national Andargachew Tsige, Secretary General of the outlawed Ginbot 7 movement, was rendered from Yemen to Ethiopia. On 8 July, a broadcast was aired on state-run ETV showing Tsige looking haggard and exhausted. By the end of the year, he was still detained incommunicado at an undisclosed location, with no access to lawyers or family. The UK government continued to be denied consular access, except for two meetings with the Ambassador, to one of which Andargachew Tsige was brought hooded, and they were not permitted to talk privately.
In March, former Gambella regional governor Okello Akway, who has Norwegian citizenship, was forcibly returned to Ethiopia from South Sudan. In June, he was charged with terrorism offences along with several other people, in connection with Gambella opposition movements in exile.

የአድዋ ድልን እያከበርን ለዛሬ ነፃነታች ቃል እንግባ!

March 5,2015
pg7-logoመቶ አስራ ዘጠነኛውን የአድዋ ድል በዓል እየዘከርን እንገኛለን። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም ቀደምቶቻችን በርካታ የውስጥና የውጭ ችግሮች ነበሩባቸው። እንደዛሬው ሁሉ ያኔም በመካከላቸው የሀሳብና የጥቅም ልዩነቶች ነበሩ። ያም ሆኖ ግን ቀደምቶቻችን በአገር ነፃነት ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ መግባባት ላይ መድረስ በመቻላቸው በዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችና ድርጅት የተጠናከረውን የአውሮፓ ጦር በጥቁር የጦር አዛዦችና ተዋጊዎች መመከት ቻሉ። ከአድዋ በፊት አፍሪቃ በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ አውሮፓዊያን የተሸነፉባቸው ተናጠል አውደ ውጊያዎች ነበሩ፤ ጦርነትን ሲሸነፉ ግን አድዋ የመጀሪያው ነው። በዚህም ምክንያት ነው የአድዋ ድል የአፍሪቃውያን ከዚያም አልፎ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ ድል ተደርጎ የሚወሰደው።
ዛሬ ግን እኛ ያኔ የነበሩት አያትና ቅድመ አያቶቻችን እደረሱበት የመግባባት ደረጃ ላይ መድረስ ባለመቻላችን አገር በቀሉን ቅኝ ገዢ – ህወሓትን – ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ ላይ ማውረድ አቅቶን አገራችንና ሕዝቧን ከባዕድ በባሰ ሁኔታ እያዋረደ በመግዛት ላይ ይገኛል።
ያኔ ለሀገሩ፣ ለነፃነቱና ለክብሩ ቀናዒ የሆነው ኢትዮጵያዊ ራሱን ወታደር አድርጎ በየጎበዝ አለቃው አዝማችነት በጠላት ላይ ዘምቶ ድልን ተቀዳጅቷል። ዛሬ ግን ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ የመከላከያ ሠራዊት አባል ለህወሓት አዛዦች ሎሌነት አድሮ የራሱን ወገን ይፈጃል። ያኔ በአገዛዙ ላይ ብሶት የነበረው እንኳን ሳይቀር ብሶቱን ችሎ ለሀገር ሉዓላውነትና ክብር ሲል ተዋድቋል። ዛሬ ግን ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ወገኖቻችን የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም ከብሶቶቻቸው በላይ አሻግረው መመልከት ተስኗቸዋል።
ዛሬ 119ኛውን የአድዋ ድል በዓል አያቶቻችንን በማድነቅ ብቻ ልናሳልፈው አይገባም። የአያቶቻችንን ገድል ስናከብር ዛሬ የምንገኝበትን ሁኔታ መመዘን ይገባናል። ራሳችንን ከእነሱ ጋር በማስተያየት እንደምን ያለን ውለታ መላሽ ያልሆንን የልጅ ልጆች መሆናችንን መመዘን እና ራሳችንን መውቀስ ይገባናል። የሚሳዝነው ዛሬ ራሱን ከሚወቅሰው በላይ አያቶቹን የሚወቅስ መብዛቱ ነው። እነሱ ችግሮችን ተሻግረው የምንኮራበትን ድል አቀዳጅተውን አልፈዋል። እኛ ግን እነሱ ያቆዩልንን ድል እንኳን ማስጠበቅ አልቻልንም። ከአድዋ ድል አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ዓመታት በኋላ አገራችንን ለህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ማስረከባችን ሊያመንና ሊያንገበግበን ሲገባ ድሮ ሊደረጉ ሲችሉ አልተደረጉም በምንላቸው ነገሮች ላይ እየተከራከርን ግዜያችንን እናጠፋለን።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ታላቁን የአድዋን ድል ለአጎናፀፉን ቀደምቶቻችን ያለንን ክብር መግለጽ ያለብን ዛሬ አገራችን ከህወሓት የአገር ውስጥ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት በምንገባው ቃል ኪዳን ነው ብሎ ያምናል። አገራችንን በቅኝ ግዛትነት እያስገዛን የቀደምቶቻችንን ድል መዘከር ለእኛ ለልጆቻቸዉ የሚያሳፍር ተግባር ነው ብሎ ያምናል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አገር በቀል ቅኝ ገዥ በሆነው ሕወሓት እየተመራ የኢትዮጵያን ሕዝብ የማዳከሙን ተግባር በአስቸኳይ ማቆም ይኖርበታል ብሎ ያምናል። ስለሆነም የመከላከያ ሠራዊት አባላት ልባችሁንም ክንዳችሁንም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር አድርጉ። ቀደምት አባቶቻችን አድዋ ላይ ድል የነሱት ቅኝ ገዥ ዛሬ ቀለሙን ለውጦ “ህወሓት” ተሰኝቶ ያንተ አዛዥ ሆኗል። መሣሪያህን በህወሓት አዛዦችህ ላይ የምታዞርበት ወቅት አሁን ነው። ንቃ፤ ተነስ!
አገርን ለጠላት አስረክቦ በቀደምት ጀግኖች ታሪክ መኩራት አሳፋሪ ነው። አባቶቻችን በነፃነት ያቆዩልን አገር የህወሓት መፈንጫ ሆና ማየት የሚያሸማቅቅ ነው። የጀግኖች አያቶቻችን የልጅ ልጆች መሆናችንን የምናስመሰክረው አገራችንን ከህወሓት አገዛዝ ነፃ ስናወጣና የዜጎቿ መብቶች የተከበሩባት ፍትህና እኩልነት የሰፈኑባት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ስንመሠርት ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዚህ ታላቅ ዓላማ ይነሳ ሲል አርበኖች ግንቦት 7 ጥሪ ያስተላልፋል።
አርበኞች ግንቦት 7: የአድዋ ድልን እያከበርን ዛሬ ነፃነታችንን ለማስከር ለመታገል ቃል እንግባ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር በሰራው ዘፈን የተነሳ ከደህንነት ሃይሎች ማስፈራሪያ እየደረሰው መሆኑ ተሰማ * ስልኩ ተጠልፏል

March 5,2015
ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

ጃኪ እና ብርሃኑ ከሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር በስቱዲዮ ውስጥ                       ጃኪ የተቀረጸው ዘፈኑን በሄኖክ ነጋሽ ኮምፒውተር ሲያደምጥ

(ዘ-ሐበሻ) ብርሃኑ ተዘራ (ብሬ ላላ) ከጃኪ ጎሲ ጋር የሠራው ወቅታዊ ዘፈን በብዙዎች ዘንድ ተወዳጅነትን ካተረፈ በኋላ አዲስ አበባ የሚገኘው ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ስልኩ በደህንነቶች መጠለፉን እና በስር ዓቱ ሰዎችም ከፍተኛ ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰው እንደሚገኝ ለድምጻዊው ቅርብ የሆኑ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ አስታወቁ::

በዛሬው ዕለት ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ ፃፈው በሚል “ዘፈኑን ተሰርቄ ነው; ጃኪ የፖለቲካ ዘፈን አይዘፍንም” የሚል ጽሁፍ በፌስቡክ የተሰራጨ ሲሆን ይህ ጽሁፍ በአድናቂዎቹ እንጂ በጃኪ ጎሲ አለመፃፉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: የጃኪ ጎሲ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶቹ ላይ ይህ ዜና እስከተዘገበበት ጊዜ ድረስ ከብርሃኑ ተዘራ ጋር ስለዘፈነው ዘፈን የሰጠው አስተያየት የለም:: ሆኖም የድምጻዊው አድናቂዎች ዘፈኑ ካለርሱ እውቅና ውጭ የተሰራ አድርገው የለጠፉት መረጃ ብዙዎችን ከማደናገሩም በላይ በተለይ ለአራት ቀናት ጃኪ ጎሲ በዋሽንግተን ዲሲ የሙዚቃ አቀናባሪው ሄኖክ ነጋሽ ጋር ሄዶ ከብርሃኑ ጋር ሲቀረጽ የተመለከቱ የዓይን እማኞች “ጃኪ ለምን ይዋሻል?” የሚሉ አስተያየቶችን በየሶሻል ሚዲያው እያሰራጩ ነው:: ድምፃዊ ጃኪ ጎሲ በፌስቡክ ገጹ ምንም ያለው ነገር ባለመኖሩ አስተያየት ከመስጠት መቆጠብ ይሻላል የሚሉ ወገኖች; ጃኪ በስሙ በወጣ መግለጫ የተነሳ በስሙና በቀጣይ ሥራው ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ሳያደርስበት አቋሙን እንዲያሳውቅ ጠይቀዋል::

ጃኪ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የሚገኝ ሲሆን የደህንነት ኃይሎች ስልኩን በመጥለፍ ከማን ጋር እንደሚያወራ እንደሚከታተሉት ዘፈኑን እንዲያስተባብል ከፍተኛ ጫና እያደረጉበት መሆኑን ለድምፃዊው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ጠቁመዋል:: ጃኪ ከዚ ቀደም “ማን እንደ ሃገር” የሚል ነጠላ ዘፈን ሰርቶ የለቀቀ ሰሞን ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የድምፅአዊው የቅርብ ወዳጅ ተወዛዋዡ አብዮት መሃል ላይ ሰማያዊ የሌለበትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ በኪሊፕ ሰርቶ ሲለቅ ጃኪም ይህን የሙዚቃ ክሊፕ ፌስቡኩ ላይ ሼር ሲያደርግ ደህንነቶች እንዴት ሕገመንግስቱ የማይፈቅደውን ባንዲራ በክሊፑ ላይ ትጠቀማለህ? በሚል ባደረሱበት ማስፈራሪያ ከፌስቡክ ገጹ ዘፈኑን ማስወጣቱን የሚጠቅሱት እነዚሁ የቅርብ ወገኖች አሁንም ደህንነቶች በሚያደርሱበት ወከባ ከፍተኛ ጫና ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል::
በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም

በጃኪ ስም አድናቂዎቹ የለጠፉት አደናጋሪ የፌስቡክ መልዕክት; ይህ በጃኪ የግል 2 ፌስቡክ አካውንቶች ላይ አልወጡም

በዚህ ዘፈን ዙሪያ ድምፃዊው ብርሃኑ ተዘራን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም::


Wednesday, March 4, 2015

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አበል ካልተሰጠን ፍርድ ቤት አንቀርብም አሉ

March 4,2015
በከሳሽ ኣቃቤ  እና  ህግ በተከሳሽ አቶ ኣስገደ ገ/ሥላሴ መካከል ሲደረግ በነበረው ክርክር  ለምስክርነት የተጠሩት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሊቀርቡ ባለመቻካቸው  በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ  ቢታዘዝም፤  ባለስልጣናቱ  ከለመዱት ምቹ ህይወት አኳያ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ።
የህወሀት የደህንነት ሰራተኛው ብስራት አማረ  የመሰረተባቸውን ክስ  ተከትሎ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲከራከሩ  የቆዩት የቀድሞው የህወሀት ታጋይና የአሁኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባል አቶ አስገደ ገብረስላሴ ላይ  ክሳቸውን እንዲከላከሉ  በፍርድ ቤት ብይን መሰጠቱ ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ አቶ ኣስገደ ከጠሩዋቸው የመከላከያ ምስክሮች ውስጥ አራት ከፍተኛ  የህውሃት  አመራሮችና   ከፍተኛ  የመንግስት  ባለስልጣናት  ይገኙበታል። ለምስክርነት የተጠሩት እነኚህ ባለስልጣናት  እነ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አቶ ኣባይ ፀሃዬ፣ አቶ ስዩም መስፍን እና አቶ ኣርከበ ዕቁባይ ናቸው።
ባለስልጣናቱ  ለመጁመሪያ ጊዜ  ለ የካቲት 6 ቀን /2007 ዓመተ ምህረት  የመከላከያ ምስክርነታቸውን ለመስጠት እንዲቀርቡ ትእዛዝ ቢደርሰዋቸውም ፤ እዚያው መቀሌ ከተማ  ውስጥ እያሉ የዳኛውን ትእዛዝ በማጠፍ ሳይቀርቡ መቅረታቸውን አቶ አስገደ ገልጸዋል።
እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ለየካቲት  13  ቀን 2007 ዓመተ ምህረት  በፖሊስ እንዲቀርቡ ዳኛዋ  ቢያዙም፤ በድጋሚ እዚያው መቀሌ እያሉ  የሉም ተብለው ሳይቀርቡ ይቀራሉ።
ለ3ኛ  ጊዜ  ለየካቲት 24 ቀን 2007 ዓ/ም በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ  ሲታዘዝ  ፖሊስ ቅድመ ሁኔታ ማቅረቡን ያመለከቱት አቶ አስገደ፤  ከቅድመ ሁኔታዎቹም  አንዱ  ተጠርተው ሲመጡ ከፍተኛ የሃገር ባለስልጣናት ከመሆናቸው አኳያ  በሸራተን አዲሰ  ደረጃ  ባለ ሆቴል ማረፍ ስላለባቸውና  በመቀሌ  ያለው የዚያ  ተመሳሳይ ሆቴል “ፕላኔት ሆቴል” በመሆኑ፤  ምስክር ጠሪው አቶ አስገደ  በፕላኔት ሆቴል ለየአንዳንዳቸው ከነ ሁለት ኣጃቢዎቻቸው የአልጋ ዋጋ   ሊከፍሉ ይገባል የሚል እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለስልጣናቱ ከዚህም በተጨማሪ በከፍተኛ ፕሮቶኮል  ማለትም በቪ አይ ፒ ደረጃ  የኣየር ትኬት ከነ ኣጃቢዎቻችን  ለመቁረጥ የሚያስችለን ገንዘብ፣ መቀሌ ለምንቆይበትም ቀናት የውሎ አበል  ታስቦ ካልተሰጠን አንመጣም ብለውኛል ብሎ ፖሊስ  ለፍርድ ቤቱ በጽሁፍ  ሪፖርት ማቅረቡን አቶ አስገደ ገልጸዋል። አቶ አስገደ አስተያየታቸውን ሲያጠቃልሉ፦<<እዚህ ላይ የፖሊስ ሃላፊነት ምን መሆን ነበረበት? ተይዞ ይቅረብ የተባለው ድሃ ሰው ቢሆን ንሮ ምን ያጋጥመው ነበር?በኢትዮጰያ የህግ የበላይነት ተረጋግጧል ማለት ይህ ነውን?በማለት በ አጸንኦት ጠይቀዋል።
ምንጭ ኢሳት ዜና 

በግፍ ላይ ግፍ በህወሓት..! ቐሺ ሕሉፍ ኸሕሳይ የዓረና-መድረክ ኣባል በመሆናቸው ብቻ ዘግናኝ ድብደባ ደርሰባቸው

March 4,2015
ቐሺ ሕሉፍ ኸሕሳይ ይባላሉ። በምዕራባዊ ዞን ቓፍታ ሑመራ ወረዳ በረኸት ከተማ(ቀበሌ) ኑዋሪ የሆኑት የዓረና-መድረክ ኣባል ናቸው።በፎተው እንደሚታዩት የዓረና-መድረክ ኣባል በመሆናቸው ብቻ ይህ ዘግናኝ ድብደባ ደርሶባቸው ሂወታቸው ልታልፍ ምንም ኣልቀረላቸውም ነበር።ይህ ድብደባ በ17/ 2007ዓ/ም ማታ 1 ሰዓት ኣከባቢ በ1ፖሊስ ድምብ ልብስ የለበሰ፣ 1 የፈጥኖ ደራሻ ደንብ ልብስ የለበሰ፣ 1 የመከላከያ ደንብ ልብስ የለበሱ ሰዎች ከለላነት ተደብቆ የነበረ ሰው በድንጋይ ደጋግሞ በመደብደብ ለዚህ ኣደጋ እንዲዳረጉ ኣድርገዋል።
3ቱ የታጠቁ ሰዎች ሰው እርዳታ እንዳያደርግ የተከላከሉ ሲሆን ደብዳቢውም በቁጥጥር ስር እንዳይውል ከፍተኛ ከለላ ሰጥተዋል።ቐሺ ሕሉፍ ኻሕሳይ በክረምት 2006 ዓ/ም በቀበሌው ህዝብ ፊት ቀርበው "..ይህ ሰውየ ዓረና ነው፣ በቤታቹ ቃጠሎ እንዳያደርስባቹ፣ እንዳይሰርቃቹ.." ወዘተ የመሳሰሉ የስም ማጥፋት ዘመቻና ማስፈራርያ ከሌሎች3 የዓረና ኣባላት ጋር ደርሶባቸው ነበር።ኣቶ መዓሾ ኣስመላሽ የተባለ የቀበሌ ኣመራርም ሰበካ ጉባኤ(የቤተክርስትያን ሃላፊዎች) በመሰብሰብ "...ቐሺ ሕሉፍ በዓረናነት ስለተጠረጠረ እንዳይቀድስ .." የሚል ትእዛዝ ባስተላለፈው መሰረት ከቅዳሴ ታገዱ።
ቐሺ ሕሉፍ የካድሬው እገዳ ተከትለው ወደ ቀበሌው ፖሊስ ኣቤቱታ በማሰማታቸው የቅስና ምስክር ወረቀታቸው እንድያመጡ በታዘዙት መሰረት ምስር ወረቀታቸው ለፖሊስ በማስረከብ ፍትህ እንዲያገኙ ጥረት ኣደረጉ።

ፖሊስም በተረዋ ምስክር ወረቀታቸው ለሁለት ሳምንት ይዞ ያለ ምንም መፍትሄ ኣቆየባቸው።
የምስክር ወረቀቱ ለማስመለስም ተጨማሪ ክስ ኣስፈለጋቸው። ፖሊስ በስንት ውጣ ውረድ ወረቀታቸው የመለሰላቸው ሲሆን ከዚህ በሗላም ስንት ዛቻ ደረሳቸው።
ዘግናኝ ድብደባ የተፈፀመባቸውም ከዚህ ሁሉ ውጣ ወረድና ማንገላታት በሗላ ነበር። ህግ ባለበት ሃገር የሰው ልጅ እንዲህ ተቀጥቅጦ ይጣላል እንዴ...?
እነዚህ ለለውጥ ብለው የተሰዉ 60 ሺ ሰማእታት፣ 100 ሺ ኣካል ጉዳተኞች ውጤታቸው መሆን የነበረበት ይህ ነው...? በጣም ሗላቀርና ህወሓት ታግየ ጣልኩት ካለቸው ደርግ በእኩልነት የሚያስመድባት ኣፀያፊ ተግባር ነው። በትግራይ የዓረና መድረክ ኣባል መሆን ይሄ የመሰለ መስዋእትነት ያስከፍላል።
በሉ ያገራችን ሰዎች ..! ታፍሩበት ትኮሩበት ዘንድ ይሄውላቹ የኛ ዲሞክራሲ፣ የኛ ፍትህ፣ የኛ ነፃነት።
ይህ ኣስቃቂ ተግባር ሁሉም ዜጋ ሊቃወመው ይገባል።
ነፃናታችን በእጃችን ነው..!
IT IS SO..!

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርን ከኃላፊነቱ አነሳ

March4,2015

<<ውሳኔው ፖለቲካዊ ነው›› አቶ አዲሱ ጌታነህ

11043128_885271564848776_4028315024485403437_n
የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን ተወካይ እንዲሁም የምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና አዊ ዞን የምርጫ ግብረ ኃይል አባል የሆነውን አቶ አዲሱ ጌታነህን ‹‹ማኔጅመንቱን ያውካል፣ የስራ ተነሳሽነት የለውም›› በሚል ከኃላፊነቱ ማንሳቱን በደብዳቤ አሳውቋል፡፡

ይሁንና መስሪያ ቤት ጥቅምት 23/2007 ዓ.ም በብቃቱ መሰረት በኃላፊነት እንደመደበው በደብዳቤ የገለጸ ሲሆን አሁን የተወሰደው እርምጃ ከወቅቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ መሆኑን አቶ አዲሱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

‹‹ባህርዳር ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ኃይል እየተፈጠረ ነው፡፡ በተለይ የአንድነት መዋቅር ሰማያዊን ከተቀላቀለ በኋላ ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ይህንም ተከትሎ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች ጋር ያደረግናቸው ውይይቶች ብአዴንን አስደንግጦታል›› ያለው አቶ አዲሱ መስሪያ ቤቱ የወሰደበት እርምጃ ፖለቲካዊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የምዕራብ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ መዋቅር በአካባቢው ህዝብ ላይ የሚደርሰውን በደል፣ እንዲሁም ምርጫ ቦርድ ከዕጩ ምዝገባ ጋር በተያያዘ የሚፈጥራቸውን ችግሮች ለሚዲያ በማጋለጥ ላይ መሆኑ ከኃላፊነት ለመነሳቴ አንድ ምክንያት ነው ሲል ገልጾአል፡፡

የአማራ ክልል ከተሞች ልማትና ግንባታ የቦርድ አባላት የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ሲሆኑ ከእነዚህም መካከል የባህርዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ላቀ አያሌው፣ የክልሉ ም/ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ያለው አባተ፣ የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ኃላፊ አቶ አየነው ይገኙበታል፡፡

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰማያዊ ፓርቲን የቅስቀሳ መልዕክት ‹‹አላስተላልፍም›› ብሎ መለሰ

March 4 ,2015
• ‹‹ቀድሞውንም እንዳያማ ጥራው፣ እንዳይበላ ግፋው ነው›› አቶ ስለሽ ፈይሳ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹እንደገና አስተካክሎ ካልላከ ለማስተላለፍ እቸገራለሁ›› በሚል መመለሱን ለፓርቲው በፃፈው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡
ኢብኮ አላስተላልፍም ብሎ ለመመለሱ በዋነኛነት የጠቀሰው ምክንያት ‹‹ለማጀቢያነት ለተጠቀማችሁት ሙዚቃ የባለመብቶቹን ፈቃድ ስለመኖሩ ማረጋገጫ አላመጣችሁም›› የሚል ነው፡፡ ኢብኮ ሌሎች ጉድለቶችን ያልጠቀሰ ቢሆንም በጥቅሉ ‹‹የምርጫ ህጉን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ፣ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ህጎች ወይንም ማንኛውም ህግ የሚተላለፍ መሆኑን በቂ ምክንያት ካለው መልዕክቱን አላስተላልፍም የማለት መብት አለው....›› በሲል ፓርቲው የላከውን የቅስቀሳ መልዕክት ለማስተላለፍ እንደሚቸገር ገልጾአል፡፡
በሌላ በኩል የፓርቲው የምርጫ ጉዳይ ኃላፊና ም/ሊቀመንበር አቶ ስለሽ ፈይሳ ገዥው ፓርቲ የግለሰብና የፓርቲ ስም እያጠፋ፣ የመደራጀት፣ ሀሰብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመምረጥና የመመረጥ መብትን በጣሰ መልኩ ቅስቀሳ እያደረገ እንደሆነ ገልጸው ሰማያዊ ፕሮግራሙ ላይ ያስቀመጣቸውን ሀሳቦች እንዲቀይር እየተጠየቀ መሆኑ ሚዲያዎቹ ለገዥው ፓርቲ ያላቸውን ወገንተኝነት በድጋሜ ያጋለጠ ነው ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
‹‹የመንግስት ሚዲያዎች ተግባር ቀድሞውንም እንዳያማ ጥራው እንዳይበላ ግፋው ነው፡፡ ቢያንስ በዚህ ጊዜ እንኳን ፍትሓዊ መሆን ነበረባቸው›› ያሉት አቶ ስለሽ የመንግስት የሚባሉት ሚዲያዎች በወንጀል ሊያስከስስ የሚችለውን የኢህአዴግ ቅስቀሳ ያለ ምንም ምርመራ እያስተላለፉ ሰማያዊ ላይ ህገ ወጥ ቅድመ ምርመራቸውን ቀጥለዋል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
ኤፍ ኤም 96.3 ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ በላከው መልዕክት ላይ በማጀቢያነት የተጠቀመበት ሙዚቃ የባለ መብቱን ፈቃድ አላገኘም በሚልና መልዕክቱ ላይ የተጠቃለሉትን የፓርቲው አቋሞች እንዲያስተካክል በሚል የቅስቀሳ መልዕክቱን መመለሱ ይታወሳል፡፡