Wednesday, January 14, 2015

በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣

January 14,2015

በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በዛሬው ዕለት፣ ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ ለዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ፣ ድርጅቶች፣ ተዋህደን “አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ”፣ በሚባል ሥም መጠራት መጀመራችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስናበስር፣ እጅግ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ባለፉት በርካታ አስርተ አመታት፣ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለነጻነት፣ መብትና አንድነት፣ ከፍተኛ ትግል ሲያካሂድ ቆይቷል። በአደረገውም ትግል እጅግ ከፍተኛ መስዕዋትነት ከፍሏል። ለከፈለው ከፍተኛ ዋጋ የሚመጥን ግን ምንም ዓይነት ውጤት አላገኘም። እንዲያውም ከጊዜ ወደ ጊዜ የመብት ረገጣው፣ አድሎው፣ ማስፈራራቱና ማዋከቡ ተጠናክረው መቀጠል ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደ ሀገር ልትቀጥል የማያስችል ከፍተኛ የመበታተን አደጋ አንጃቦባት ትገኛለች ።
በሀገራችን ላይ ላንጃበበው ከፍተኛ የመበታተን አደጋ ምክንያት የሆነው በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ የአምባገነን ቡድን ነው። ይህ ዘረኛ አምባገነን ቡድን በሀገራችን ታሪክ በሥልጣን ላይ ከመጡ የገዥ ሃይሎች ጋር ሲወዳደር ሀገርን ለከፍተኛ አደጋ በማጋለጥ፣ ሕዝቧን በማወረድ፣ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ዕኩይ ሃይል መሆኑን በበርካታ ተግባራቶቹ ያለ ምንም ጥርጣሬ አረጋግጧል።
በሌላ በኩል ለቀድሞቹም ሆነ ለዛሬው ዘረኛው የወያኔ አምባገነን ገዥ በሕዝብና በሀገር ላይ በደል እየፈጸመ በሥልጣን መቆየት የቻለበት ምክንያት፣ በተቃዋሚነት የሕዝቡን ትግል ለመምራት የተንቀሳቀስን ድርጅቶች፣ የተቋቋምንበት ዓላማ መለያዬት ብቻ ሳይሆን፣ አንድ ዓይነት ዓላማ ያለንም ብንሆን፣ ከድርጅቶቻችን ጠባብ ፍላጎቶችና ስሜቶች ባለፈ፣ የሀገርና የሕዝብን ጉዳይ በማስቀደም በጋራ መሰባሰብና መታገል ስላቃተን ነው። በዚህም ድርጊታችን የራሳችንን ብቻ ሳይሆን የወገናችንንም የመከራ ዘመን እያራዘምን እንገኛለን ።
ይህ ሁኔታ በተለያዩ ተቃዋሚ ድርጅቶች መሀል ከፍተኛ ጥርጣሬና ፍርሀት ከመፍጠሩ የተነሳ በምንም ዓይነት ሁኔታ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶች በጋራ በሀገርና በሕዝብ ደረጃ ትርጉም ያለው ስራ መስራት አይችሉም፣ የሚለው አመለካከት የበላይነት እንዲያገኝ አድርጎታል።
በዛሬው ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም ወደ ውህደት የመጣነው፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣፡ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መዋሃድ መወሰናችንን ፣ ስንገልጽ በተናጠል ከሚደረጉ በጋራ የሚደረጉ የትግል ጥረቶች ውጤታማ ይሆናሉ በሚል ብቻ ሳይሆን፣ የተቃዋሚ ድርጅቶች፣ በምንም ዓይነት ሁኔታ በሀገርና በሕዝብ ደረጃ ትርጉም ያለው ሥራ በጋራ መስራት አይቻሉም የሚለውን፣ አስከፊ ተመክሮና አመለካካት ለመስበርም ነው።
በእኛ እምነት ከትናናሽ ድርጅቶች ዙሪያ ከሚሽከረከሩ ሀሳቦችና ስሜቶች ለመውጣትና ሀገራዊና ሕዝባዊ የሆነው ጉዳይ ለማስቀደም የወሰነ ማንኛውም ድርጅት፣ አርበኞችና ግንቦት7፣ የደረሱበት የውህደት ውሳኔ ወይም በሌሎች በጋራ ሊያሰሩ በሚችሉ ስምምነቶች አብሮ ለመስራት መወሰን የማይችልበት ምንም ምክንያት አይታየንም። በወያኔ አድሎ ስርዓት የተንገፈገፈና ትግሉን ለመቀላቀል የቆረጠ ማንኛውም ዜጋ፣ የተገኘውን አጋጣሚ በመጠቀም ትግሉን መቀላቀል ይችላል፣ የኢትዮያ ሕዝብ በአንድነት የተነሳ ቀን ደግሞ፣ የወያኔ ግብዓተ መሬት ይፈጸማል፣ ብለን ከልብ እናምናለን።
ይህም በመሆኑ፣
ለተቃዋሚ ድርጅቶች፣
ዛሬ በአርበኞችና በግንቦት 7፣ የተጀመረው ጉዞ ውጤታማ በመሆን ሀገራዊና ታሪካዊ ትርጉም እንዲኖረው፣ ሌሎችም በተግባር የምትንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ድርጅቶች፣ ወያኔን የማስወገድንና ብሎም ሀገር የማረጋጋቱን ሀላፊነት በጋራ እንድንወጣ የሚያስችል መቀራረብ እንድናደርግ ፣ በውህደት በመሰረትነው፣ በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ፣ ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ለወታደራዊና የፖሊስ ሠራዊት አባላት፣
የወያኔ ዘረኛና አምባገነን ቡድን ዕድሜን ለማሳጠርና ሁላችንንም በእኩልነት የምታስተናግድ ሀገር እንድትኖር ፣ በየቦታው የሚደረገውን ትግል፣ የሰሞኑን ቆራጥ የዓየር ሃይል መኮንንኖች ያሳዩትን ዓርያነት በመከተልና በተገኘው አጋጣሚና ሁኔታ በመጠቀም፣ እንድትቀላቀሉ በውህደቱ ድርጅት፣ በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ፣ ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የተከበርከው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ፣
በረጅም ታሪክህ አይተሄው ለማታውቀው፣ ውርደት፣ ክፋት፣ የመከፋፈልና የመጋጨት አደጋ፣ የመብት እረገጣና አፈና፣ ሀገርና ሕዝብን የማራከስና የመሸጥ፣ ዕኩይ ተግባር፣ የተጠናወተው ወያኔ እና የግብር አበሮቹን፣ ጠራርጎ ለማስወገድ በተጀመረው የጋራ ትግል ውስጥ በቀጥታ እንድትሳተፍም ሆነ በምትችለው ሁሉ እርዳታ እንድታደርግ፣ በዛሬው ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም የአርበኞችና የግንቦት 7 ውህደት በወለደው፣ በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ ሥም፣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ድል ለኢዮጵያ ሕዝብ!!!
አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ፣
ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ምርጫ መቆመሪያ ተቋም ገመና

January 13,2015
በዳንኤል ተፈራ
10485535_718983234881727_4513979552309356105_n (1)
ያሳለፍነው ሳምንት በሕወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ተሰልተው፣ ታስቦባቸው ይፋ ከተደረጉና አሻንጉሊቱ ምርጫ ቦርድ እንዲፈጽመው በህወሃት ሰዎች ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቶት ገቢራዊ እንዳደረገው የሚጠረጠረው የፖለቲካ ጉዳይ ይፋ የተደረገበት ነበር፡፡ ይሄው ጉዳይ በአይረቤ ሰበብና በምክንያት አልባ ሁነት ግን ዳግም ከቤተ-መንግስት በወጣ ትዕዛዝ በሚመሰል መልኩ አንድነት እና መኢአድ ወደ ምርጫ ፍክክሩ እንዳይገቡ አይን ያወጣና የሰዎችን የስልጣን ብልግና ባጋለጠ መልኩ መግለጫ የሰጡበት ነው፡፡
እንደዚህ ዓመቱ ምርጫ ቦርዱ የተጋለጠበት ጊዜ አለ ብዬ አላምንም፡፡ ይሄው የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደ ጫጩት ፍፁም ጠቅላላ ጉባዔ አድርገው የሚያውቁ፣ ቢሮም ሆነ ስራ አስፈፃሚ የሌላቸውን ተቃዋሚ ተብዬዎች በጉያው ሸጉጦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ እያላገጠ መሆኑ ሳያንስ የገዥውን ፓርቲ ኃላፊነት የጐደለው ተግባር ተቋቁመው ለሃገራችን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እየደከሙ ያሉ ፓርቲዎችን እየገፉ ያለበት አግባብ ተቋሙን ከምርጫ መቆመሪያ ማዕከልነት ባለፈ ፋይዳ የሌለው፣ በህወሃት/ኢህአዴግ ማንቁርቱ የታነቀና የራሱ ሳንባ የሌለው ምስኪን ተቋም እንደሆነ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡
ይሄው የተጨመደደ ቦርድ ተብየ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ገለልተኛነቱ አጠራጣሪ ቢሆንም እንደ ሰሞኑ ገለልተኛ አለመሆኑን በይፋ ያረጋገጠበት ወቅት ያለ አይመስለኝም፡፡ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደሚጠቁሙት ቦርዱ በዋናነት የሚመራው በፕ/ር መርጋ በቃና ሳይሆን በምክትልነት በተቀመጠው የትግራዩ ሰው ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሄር ነው፡፡ ለዚህም ነው በኢህአዴጉ አፈ-ቀላጤ ፍና እና ሌላው ቀላጤ ኢቲቪ በኩል ፓርቲዎችን በህገ ወጥ መንገድ መገፋታቸውን እየገለፀ ያለው፡፡ ሰውየው የቦርዱን ህገ ወጥ ተግባር ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሚችል ሰው ነው፡፡ ዶ/ር አዲሱ የፓርቲዎችን የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር አዘጋጅቶ ያቀረበ፤ በዚህ ቀመርም በፓርላማ መቀመጫና በክልል ም/ቤት መቀመጫ 55% እንዲይዝ ለማሳመን የጣረ የህወሃት የቁርጥ ቀን ልጅ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም 55% ጠቅልሎ የሚወሰደው ኢህአዴግ ነው፡፡
ቦርዱ ገለልተኛ አይደለም ስንል እንዲሁ በግብታዊነት ሳይሆን ተጨባጭ መከራከሪያዎችን የማቅረብ አቅም ስላለን ነው፡፡ አንድ ወዳጄ የኢትዮጵያውን ምርጫ ቦርድ በማገዝ ከመቆሪያ ተቋምነት መገላገል እንደሚገባ ስነግረው ተስፉ በቆረጠ ስሜት ግን ደግሞ በምፀት ፈገግ ብሎ “ወዳጄ ቦርዱ እኮ ግንባሩን ከመሰረቱ ፓርቲዎች አምስተኛው ፓርቲ ነው፡፡ የሚያስፈልገው ቦርዱን ማገዝ ሳይሆን አፍርሶ እንደገና መስራት ነው፡፡ በታሪክ ከሚጠየቁ ተቋማት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡” ነበር ያለኝ፡፡ እውነትም መፍረስ የሚገባው አይረቤ ተቋም ነው፤ ራሱን ነፃ ያላወጣና የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደሆነ ግብሩ አረጋገጠ፡፡
አንድነት ፓርቲ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ከለቀቁ በኋላ አንድነት በመዋቅሩ በአመራርነት የማያውቃቸው ግለሰቦች ተሰባስበው ኢ/ር ግዛቸውን የተካውን አመራር ህግ የጣሰ ለማስመሰል ጥረት ጀመሩ፡፡ የቦርዱ የፖለቲካ ቁማርም ከዚህ ሁነት ይጀምራል፡፡ አንድነትን አስቀድሞ ከምርጫው ለማስቀረት እነዚህን ተራ ግለሰቦች “ጐሽ፣ ጐሽ” ማለት ጀመሩ፡፡ እነዚህ “አንድነት ነን፣ መርህ ይከበር” የሚሉ ጥቂት ግለሰቦች የተንኮል ፖለቲካው አድራሽ ፈርሶች እንጅ በራሳቸው ምንም አይደሉም፡፡ የእነዚህ አፍራሽ ግለሰቦች ያላቸው ብቃት የሚለካው ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባፈነገጠ መልኩ ለመዋሸት የማይሳቀቁ፤ ተልዕኳቸውን ለመፈፀም አይናቸውን በጨው ያጠቡ የዘመናችን ባንዳዎች መሆናቸው ነው፡፡
ለዚህ ምሳሌ የሚሆነው የመቆመሪያው ተቋም ሳያፍር “አመራር” እያለ የሚጠራው የማነአብ አሰፋ የሚባል የትግራይ ተወላጅ ሲሆን ዕድሜው በሃያዎቹ መጀመሪያ የሚገኝ፣ በተግባሩ ስለሚያፍር በቆብና በጃኬት ራሱን ደብቆ የሚዞር ወጣት ነው፡፡ ይሄ ልጅ አንድነት ቤት ተቀጣሪ ሆኖ ለተወሰኑ ወራት የድርጅት ጉዳይ ተላላኪ ሆኖ ሰርቷል፡፡ አንገት ደፊና አይናፋር በመምሰል የተወነው ትወና አስደናቂ ነው፡፡ የኢህአዴግ ክትትል እንዳላስቀመጠውና ስራ መቀጠር እንኳን እንዳልቻለ እንባ እየተናነቀው ለመናገር የሚችለው ይሄ ወጣት ምርጫ ሲደርስ እንዲፈነዳ ህወሃት አቀባብሎ ያስቀመጠው ፈንጂ እንደሆነ ያወቅነው ቦርዱ “አመራር” እያለ ቢሮው ጐልቶት ስናገኘው ነው፡፡ ወደ ነጥቡ ስንመለስ እነዚህ “አንድነት ነን” የሚሉ በተግባር ግን የአንድነት ወገን ያልሆኑ ስብስቦች ም/ቤቱ በደንቡ መሰረት የተካውን አመራር “ህገ-ወጥ ነው” በማለታቸው ብቻ የምርጫ መቆመሪያው ተቋም በችኮላ አንድ ደብዳቤ ለፓርቲው ፃፈ፡፡ ይሄ የመጀመሪያው ደብዳቤ ኢ/ር ግዛቸውን ፕሬዝዳንት አድርጐ የመረጠውን ጉባኤ ዕውቅና በመንፈግ ዶ/ር ነጋሶን እንደሚያውቅ የሚጠቅስ ነው፡፡ ቦርዱ በችኮላ በየዋህነት የፃፈው ደብዳቤ ለቁማሩ በጆከርነት የሚያገለግሉ ግለሰቦችን ከጨዋታ ውጭ የሚያደርግበት መሆኑን ሲረዳ ምናልባትም አለቃቸው ህወሃት /ኢህአዴግ ለአንድነት ቦርድ የፃፈውን ዝርዝር ደብዳቤ ሲመለከት ለሴራ ፖለቲካ እንደማይመች ሲረዳ በአስቸኳይ ቀይር ብሎት ይመስለኛል፡- “እሱን ደብዳቤ ተውት” ከሚል መልዕክት ጋር ሌላ 3 ነጥቦችን የያዘ ደብዳቤ ላከ፡፡
የመጀመሪያውን ደብዳቤ ተውት ያለበት ምክንያት ለአፍራሽ ተልዕኮ የተዘጋጁ ገልቱ ግለሰቦች ከጨዋታ ውጭ ስለሚሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ግለሰቦች በዶ/ር ነጋሶ የአመራር ዘመን አይታወቁም ወይም የሉም ነበርና፡፡ ባለ ሦስቱ ነጥብ ደብዳቤ ሲመጣ ግን አንድነት የፖለቲካ ዕደንድምታውን በጥንቃቄ ገምግሟል፡፡ ምነው ቢሉ ይሄ ከቦርዱ በስተጀርባ የሚደንስ አካል እንዳለ በመረጋገጡ ነው፡፡ ዳንሰኞቹ ምርጫን ለማስመሰያና ማወናበጃ እንጅ በትክክል ሊጠቀሙበት አይፈልጉም፡፡
የደብዳቤው ሦስት ነጥቦች የሚከተሉት ነበሩ አንደኛው ም/ቤቱ የጠቅላላ ጉባኤ ውክልና እንዳለውና ም/ቤቱ ፕሬዘዳንት መምረጥ እንደሚችል አብራሩ፤ ሁለተኛው የጠ/ጉባኤ ሪፖርት በጊዜ አስገቡና የመጨረሻው የጠቅላላ ጉባኤ የኮረም ቁጥር ግለጹልን የሚል ነበር፡፡ በጣም ቀላልና ተራ ጥያቄ የሚመስል ነበር፡፡ አንድነት በፍጥነት ምላሽ ሰጠ፡፡ የመቆመሪያው ተቋምም የሰጠነውን ምላሽ “በቅንነት” እንደተቀበለው ገልጾ ነገር ግን የጠ/ጉባኤ ቁጥር በደንቡ እንድናካትት የሚጠይቅ ደብዳቤ ፃፈ፡፡ በቅንነት የምትለውን ግን በቅንነት አልተመለከትነውም፡፡ ጉባኤ በፍጥነት መጠራት እንዳለበትና ምርጫ ቦርዱ የጠየቀውን አሟልተን በሙሉ ልብ ወደ ምርጫ መግባት እንደሚገባ በመታመኑ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የምርጫ ቦርድ ተወካይ ባለበት በስኬት ተጠናቀቀ፡፡
አንድነትም ገዥዎች ባዳፈኑት የፖለቲካ ምህዳር እና ልፍስፍሱ ቦርድ ቢኖርም ህዝቡን አንቀሳቅሽ በ2007 ዓ.ም የአምባገነኑ ስርዓት ፍፃሜ ይሆናል በሚል ፅኑ እምነት ሙሉ ለሙሉ በስራ ተጠመደ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜም የህዝብ ታዛቢዎችን ምርጫ በመላ ሀገሪቱ ያሉ ቢሮዎቹን በመዝጋት በንቃት ተከታተለ አጋለጠ፡፡ ህዝቡ የምርጫ ካርድ የሚወስድበትንና በካርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸናፊ የሚሆንበትን ስትራቴጂ መንደፍንና ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደሚያስፈልግ ይፋ ማድረጉ ተከትሎ የ40 እና 50 ዓመት የመግዛት ህልም ያላቸው “ነፃ አውጭዎች” መንደር ጫጫታና ጭንቀት ፈጠረ፡፡
ይህንን ጭንቀት ለማርገብ አንድነትን ከምርጫ ጫወታ ማስወጣት እንደሚገባ ታመነበት፡፡ ለዚህ ማስፈፀሚያ የመቆመሪያው ተቋም አለ፡፡ በጠቅላላ ጉባኤው ተወካዩን የላከው ቦርዱ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመስራት ደፈረ፡፡ ከቦርዱ በስተጀርባ ያሉ ዳንሰኞች ማንቁርቱን ስላነቁት ምርጫ አልነበረውም፡፡ ይሄ ተራ ጨዋታ በፋና እና ኢቲቪ ታጅቦ ለህዝብ ቀረ፡፡ ድራማው “የውስጥ ችግሮቻቸውን ካልፈቱ ወደ ምርጫ አይገቡም” የሚል ነው፡፡ የውስጥ ችግር ከማን ጋር? እንዴት? መልስ የላቸውም፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ለቀው ወደ ግል ጉዳያቸው ገብተዋል፡፡ ታዲያ እነዚህ አመራር ተብየዎች እነማን ናቸው? እነዚህ የአንድነት አመራር እንዲደራደራቸውና ችግሩን እንዲፈታ የተጠየቁት ግለሰቦች በፓርቲው የአመራር መዋቅር የማይታወቁ፤ ከየመንገዱ ተለቃቅመው የመጡ ተራ ሰዎች ናቸው፡፡
ህወሃት/ኢህአዴግ በቦርዱ በኩል ይህንን ተራ ድራማ እየሰራ ያለው አንድነት ወደ ምርጫ እንዳይገባ ለመከልከል የወሰነው የፖለቲካ ውሳኔ ስጋ ለማልበስ ነው፡፡ የእርኩም ስጋ፡፡ ሁሉም በሰፈረው ቁና የሚሰፈርበት ቀን እንደሚመጣ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡ እየተካሄደ ያለው ሰላማዊ ትግል ከዚህ ዓይነት ተራ ድራማ በላይም ነው፡፡ ትግሉ የነፃነት የመውጣትና ተደፍቆ የመኖር ነው፡፡ ወደ ምርጫ እንገባለን ስንላቸው በዚህ ደረጃ ተርበትብተዋል፡፡ ምርጫ ቦርድም ያለውድድር ለኢህአዴግ ተጨማሪ የአገዛዝ ዘመን ለመስጠት ዝግጅቱን የጨረሰ ይመስላል፡፡ ይሄ የስርዓቱን የውድቀት ፖለቲካ የሚያሳይ ነው፡፡ የዚች ሀገር ትግል የቦርድ ወይም የሌላ ትግል አይደለም፡፡ ትግሉ በሕዝቡ እጅ ላይ የወደቀበት ታሪካዊ ወቅት ነው፡፡ ታሪካዊ ጊዜ ዴሞክራሲን እናሰፍናለን የሚሉ ሰዎች በግብራቸው ያፈሩበት ታሪክ፡፡ ይህንን በአደባባይ ቆመን የምንናገርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡
2007 ለለውጥ!!!

Tuesday, January 13, 2015

የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመባት

January 13,2015
የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፀመባት
ወይዘሪት ወይንሸት፣ ንፍስ ስልክ አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ ሁለት ሰዎች ከረፋዱ 5፡30 ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመባት ለፍኖተ-ነፃነት የደረሰው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወይዘሪት ወይንሸት፣ ነፍሰጡር መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን ደብዳቢዎቹም ሆዷን በመርገጥ ድብደባውን ሲፈፅሙባት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ደብዳቢዎቹ ድብደባውን ፈፅመው የተሰወሩ ሲሆን ወይዘሪት ወይንሸት፣ በአሁኑ ሰዓት ራሷን ስታ ሆስፒታል መግባቷን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወይንሸት፣ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማካሄድ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በከፍተኛ ድምፅ የአስመራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆና በመመረጥ በምርጫው ላይ ጉልህ ሚና በመጫወት ድርሻዋን መወጣቷ ይታወሳል፡፡ በእለቱ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአንድነት ስም የሚነግዱትን ግለሰቦች በማውገዝ አስተያየቷን መሰንዘሯን ተከትሎ ድብደባው ሊፈፀምባት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ወይዘሪት ወይንሸት፣ በፓርቲው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ያላት ወጣት ከመሆኗም በተጨማሪ የአንድነት ፓርቲ ሴቶች ጉዳይ ምክትል ሀላፊ በመሆን በመስራት ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ሳምንት ብቻ በአንድነት አባላት ላይ ድብደባ ሲደርስ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ባለፈው እሁድ በአቶ መሳይ ትኩ፣ ላይ ድብደባ መፈፀሙ ይታወሳል፡፡

Monday, January 12, 2015

ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ከውንጀላ እንዲቆጠብ ጠየቀ

January 12,2015
• ይቅርታ ጠይቅ መባሉ ህገ-ወጥ መሆኑን ገልጾአል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታህሣሥ 28/2007 ዓ.ም ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ህገ-ወጥ ተግባራት›› እየፈጸመ እንደሆነ በመግለጽ ይቅርታ እንዲጠይቅ ለጻፈው ደብዳቤ፣ ሰማያዊ ፓርቲ በፃፈው መልስ ምርጫ ቦርድ ያቀረባቸው ውንጀላቸው ህገ-ወጥ በመሆናቸው ቦርዱ ከውንጀላዎች እንዲቆጠብ ጠይቋል፡፡

ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲ ህጋዊ እውቅና ሳያገኝ ሲንቀሳቀስ እንደቆየ፣ ቦርዱ ያዘጋጃቸውን ስብሰባዎች ረግጦ ወጥቷል፣ ከቦርዱ እውቅና ውጭ ፓርዎቹን እያስተባበረ ነው በሚል ውንጀላ ማቅረቡ ይታወቃል፡፡፡ ሆኖም ሰማያዊ ፓርቲ በጻፈው ደብዳቤ በተሻሻለው የፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ምርጫ ቦርድ በሶስት ወር ውስጥ ፓርቲዎች ላቀረቡት የእውቅና ጥያቄ መልስ ካልሰጠ ማመልከቻውን ያቀረበው ፓርቲ እንደተመዘገበ እንደሚቆጠር እና ሰማያዊ ፓርቲም ይህን ህጋዊ መሰረት ተጠቅሞ ህጋዊነቱን እንዳወጀ በደብዳቤው የገለጸው ፓርቲው ‹‹ድርጊታችን ህጋዊ ስለነበር ቦርዱ የህጋዊ እውቅና እና የምስክር ወረቀት ከመስጠት ውጭ በወቅቱ ምንም አይነት ውንጀላ እና ክስ አላቀረበም›› ሲል የአሁኑ ውንጀላ መሰረተ ቢስ መሆኑን ገልጾአል፡፡

ቦርዱ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹በተለያዩ አፍራሽ ተግባራት ውስጥ እየተሰማራ ይገኛል›› በሚል በተለያዩ ጊዜያት ቦርዱ ያዘጋጃቸውን ስብሰባዎች ለመበተን ሙከራ አድርጓል፣ ጥሎም ወጥቷል በሚል ለቀረበበት ውንጀላም ፓርቲው ቦርዱ ባዘጋጃቸው ስብሰባዎች አጀንዳዎችን አቅርቦ በቦርዱ በተደጋጋሚ ውድቅ እንደተደረገበት ገልጾ ቦርዱ ‹‹የእኔን አጀንዳ ስሙኝ›› በሚልባቸው ስብሰባዎች ሙሉ ጊዜ መሳተፍ ግዴታም ሆነ ፍላጎት እንዳልነበረበት ገልጾአል፡፡ ‹‹ባላመንባቸው አጀንዳዎች ላይ ያለመሳተፍ ህጋዊ መብታችን ነው›› ያለው ፓርቲው ወደፊትም ቢሆን ቦርዱ በተመሳሳይ አቀራረብና ይዘት የሚቀጥል ከሆነ ስብሰባዎችን እየጣለ እንደሚወጣ ገልጾአል፡፡

ቦርዱ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ከቦርዱ እውቅና ሳያገኝ ትብብር የሚባል አደረጃጀት መስርቶ ህገ-ውጥ እንቅስቃሴ አድርጓል›› በሚል ላቀረበው ክስም በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝባ አዋጅ 573/2000 32፣ 34ና 35 ውህደት፣ ቅንጅትና ግንባር ካልሆነ በስተቀር ፓርቲዎች በሚያግባቧቸው ጉዳዮች ተባብረው ሲሰሩ የምርጫ ቦርድ እውቅናን መጠየቅ እንደማይጠበቅባቸው ገልጾ፣ ቦርዱ በፓርቲዎች በነጻነት የመንቀሳቀስ ህጋዊ መብትን እየተጋፋ መሆኑን አውቆ ከእንደዚህ አይነት ውንጀላዎች እንዲቆጠብ ጠይቋል፡፡
በመሆኑም ምርጫ ቦርድ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ይቅርታ ይጠይቅ›› ብሎ ያቀረባቸው ክሶች መሰረተ ቢሶችና ህጋዊ መሰረት የሌላቸው በመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም ብሏል፡፡ ‹‹ይህ አይነት የይቅርታ ጠያቂና ይቅርታ አድራጊ ግንኙነት ለምርጫ ቦርድ በህግ ከተሰጡት ስልጣንና ተግባራት ውጭ በመሆኑ የቦርዱና የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊ ግንኙነትን ያልተከተለና ተቀባይት የሌለው መሆኑን እንገልጻለን›› ሲል ይቅርታ ጠይቅ መባሉ ህገ-ወጥ መሆኑን ገልጾአል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ

ሕወሃት በመንግስት ስልጣን ባለቤትነትና በወንበዴነት መሐል ያለው ልዩነት ተምታቶበታል

January 12,2015
ኢትዮጵያን በግፍና በዝርፊያ የሚገዛው የህወሀት ጉጅሌ በመንግስትነትና በወንበዴነት መሀል ያለውን ልዩነት ከ፪፫ ዓመት ስልጣን ዘመን ብኋላ እንኳን ሊገለጥለት አልቻለም። ወይም እንዳመችነቱ ሁለቱን እያምታታ መቀጠሉን እንደብልህነት ቆጥሮታል። መንግስት መሆንንና ባለህገመንግስት መባልን ከመቆነጃጃ ኩልነት ባልተናነሰ በለጋሾቻቸው ባዕዳን ፊት ይጠቀሙበታል እንጂ ለኛ ለዜጎቹማ ወንበዴነታቸውን ሊደብቁን እንኳን አይጨነቁም።
በቅርቡ ህወሀት የትግራይ ሪፐብሊክ ለማቋቋም የክህደት ተግባሩን የጀመረበትን ፵ኛ ዓመት በዓሉን ትግራይ ውስጥ በማክበር ላይ ሳለ የቀድሞው የህወሀት ታጋይ ያሁኑ የሀገሪቱ ጦር ሎች ኤታማዦር ሹም ተብዬው ሳሞራ የኑስ የህወሀት መንግስት ያገራችን ገበሬ ወፎችን ከማሽላው ለመከላከል እንደሚጠቀምበት መስፈራሪቾ የሚጠቀምበት ሕገ መንግስት ላይ የተጠቀሰውን የሀገሪቱን ሰራዊት የፖለቲካ ገለልተኝነት ድንጋጌና ሰራዊቱ “ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ ይሆናል” የሚለውን የይስሙላ ህግ ባደባባይ አውልቆ ጥሎ ተቃዋሚዎችን የሚወነጅል ሰፊ ንግግር ሲያደርግ ተደምጧል። ሳሞራ ይህን ንግግር በሚደረግበት ቦታ አፋቸውን ከፍተው ከሚያደምጡት ውስጥ የሀገሪቱን መንግስት እንዳሻቸው የሚዘውሩት የወያኔ ሹማምንት ነበሩ። በዚህ ንግግር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የባዕዳን መሳሪያ ሆነው የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እንደሚፈታተኑ ሀይሎች በመቁጠር ፍጹም ሀሰትና ጅምላ ፍረጃ ሲያደርግ “እረ ይህ ነገር በመደበኛ ስራህ የስራ ዝርዝር ውስጥ አለመኖር ብቻ ሳይሆን የተከለከለ ነው” ያለው አልነበረም። ይህን መርዝ ከተናገረና ተቃዋሚዎችም ላይ ዛቻውን ካሰማና ከወነጀለ በኋላ የህወሀት ልዩ አገልጋይነቱንም ካረጋገጠ በኋላ “ለማንኛውም እኔ ወታደር ስለሆንኩ አይመለከተኝም” ይምትል የፌዝ የግርጌ ማስታወሻ ብጤ በመናገር ህወሀት እያምታታ የሚጠቀምበትን ውንብድናና መንግስትነት አደባልቆ የሚያደርገውን ጉዞ ካላንዳች ሀፍረት አመልክቶናል። መሰረታዊ መንግስታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ባለባቸው ሀገሮች የዚህ ዓይነት እነጋገር ባደባባይ አሰምቶ ለቀናት በያዙት ስልጣን ላይ መቀመጥ አይቻልም። ውንብድናና መንግስትነት ድንበር ባጣባት ኢትዮጵያ ይህ ህግ መተላለፍ ሳይሆን በገሀድ የምንኖረው የውርደት ህይወት ከሆነ አመታት ተቆጠሩ።
ግንቦት ሰባት የፍትሕ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ሀገሪቱን በቅንነት ለማገልገል ሰራዊቱን የተቀላቀለው ተራው ወታደርና የበታች ሹማምንት ይህንን መልዕክት በቅጡ ሊያደምጡት ይገባል ብሎ ያምናል። በየትኛውም ዘርፍ ያለው ሰራዊት አለቆቹ የህወሀት ስንቅ ተሸካሚዎች እንጂ የውዲቱ ሀገራችን ዘበኞችና ሉዓላዊነት አስከባሪዎች አለመሆናቸውን ጠንቅቆ ማወቅ አለበት። ሰራዊቱን እያዘጋጁት ያሉትም በደል የበዛበት የገዛ ወገኑ መብቱን በሚጠይቅበትና ለመብቱ በሚታገልበት ስዓት አፈሙዝ ወገኑ ላይ እንዲያዞር እንጂ የሀገርና የህዝብ ከለላ እንዲሆን አይደለም። ለነዚህ የወያኔ የጦር አለቆች መታዘዝ ለሀገሪቱ ዘብ መቆም ሳይሆን የህወሀት ሎሌነት መሆኑንም በቅጡ መገንዘብ ያሻል። ብዙዎች የሰራዊቱ አባላት ከዚህ ቀደም እንዳደረጉትና ዛሬም እያደረጉ እንዳሉት በተገኘው አማራጭ ሁሉ ሰራዊቱ ይህዝቡን ወገኖች እንዲቀላቀል ጥሪያችንን እናቀርባለን። በየከተሞቹ በራሳቸው በቁባቶቻቸውና በዘመዶቻቸው ስም የጦፈ ንግድ ፣ ፎቅ ግንባታና ፈንጠዝያ ላይ ያሉት የወያኔ የጦር አለቆች የቆሙት የራሳቸውን የዝርፊያ ስርዓት አደረሳቸው ድረስ ለማቆየት እንጂ ለሀገር ዘብነት አይደለም።
ሀገራችን የዜጎቿ ሁሉ መብት ተጠብቆ ስልጣኑ በህገመንግስት ተገድቦ የሚሰራ መንግስት ያስፈልጋታል ይገባታልም። በህግ አምላክ ተባብለው ህግ አክብረው መኖር ባህላቸው ላደረጉ ህዝቦች ህግና ውንብድናን አደባልቆ የሚገዛ መንግስት አይገባንም። ሰራዊቱም ለሀገር አገልግሎቱ የሚገባውን ክብር የሚያገኝበት ስርዓት እንጂ ነጋ ጠባ በወያኔ ግምገማ ከሚሸማቀቅበት በወገኖቹ ላይ እንደባዕድ እንዲተኩስ ከመታዘዝ የሚላቀቅበት ስርዓት ይገባዋል።
ከሳሞራ የእብሪትና ማናለብኝነት ንግግር የምንማረው የህወሀት የጦር አዛዦች የሀገሪቱ ወታደሮች ሳይሆኑ ህዝብ የናቁ ጭፍን ራስ ወዳድ፣ ዘረኛና ሀገር ዘራፊ ማፊያዎች መሆናቸውን ብቻ ነው። ይህን ሀቅ በተለይ በቅርብ ሆናችሁ የምትታዘቡ በተራ ውትድርናና የበታች መኮንኖች ሆናችሁ ሀገሪቱን ለማገልገል የገባችሁ የሰራዊቱ አባላት የህዝብና የሀገር ወገንተኝነታች ሁን ማረጋገጫ ጊዜው ነገ ሳይሆን ዘሬ መሆኑን ላፍታም ልትዘነጉ አይገባም።

Sunday, January 11, 2015

ትናንት ከዉጭ ወራሪዎች የታደገን መከላከያ ሠራዊታችን ዛሬም ከአገር ዉስጥ ወራሪዎች ይታደገናል

January 11,2015
አስተዋዩ የኢትዮጵያ ህዝብ እድገቱን ለሚመኙ አስተዋይ መሪዎች እለታደለምና ደሃ ነዉ፤ ረሀብተኛ ነዉ አልተማረም ወይም ኋላ ቀር ህዝብ ነዉ ማለት ይቻል ይሆናል፤ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ ያሰኘዉን ያክል ቢደኸይ ወይም ኋላ ቀር ቢሆን ለነፃነቱ፤ ለአንድነቱና ለግዛት አንድነቱ መከበር ያለስስት ደሙን የሚያፈስ ጀግና ህዝብ ነዉ። ይህ ጀግንነት ደግሞ አንደተረት በአፍ ተነግሮ የሚያበቃ ሳይሆን በመተማ፤ በአድዋ፤ በማይጮዉ፤ በወልወል፤ በፊልቱና በጎዴ የጦር ሜዳዎች ሊወጉትና ሊወሩት የመጡ ጠላቶቹ ጭምር የመሰክሩለት የታሪክ ሐቅ ነዉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ከጀግንነቱ ጋር አርቆ አስተዋይና ታጋሽ ህዝብ ነዉ፤ ሆኖም ይህንን ህዝብ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ በተከታታይ የገዙት የገዢ መደቦች ጀግንነቱን ለራሳቸዉ ክብርና ዝና ታጋሽነቱን ደግሞ ለስልጣን ዘመናቸዉ ማራዘሚያ አድርገዉ የመከራ ዘመን እያስቆጠሩ ኖረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ታጋሽ ህዝብ ቢሆንም እርግጫዉና ጭቆናዉ በበዛበት ቁጥር አምርሮ የሚነሳ ለገዢ መደቦች የማይመች ቁጡና እልህኸኛ ህዝብ መሆኑንም በተከታታይ አሳይቷል። ይህንን ደግሞ በ1966 ዓም ከዳር ዳር ባቀጣጠለዉ ህዝባዊ አብዮት በ1983 ዓም ደግሞ በአራቱም ማዕዘናት ባካሄደዉ ህዝባዊ አመጽ አሳይቷል። ሆኖም አብዮቱንና ህዝባዊ አመጹን ከትግል ሜዳ እስከ ፖለቲካ ስልጣን አደባባዮች ድረስ አቀነባብሮ የሚመራ የተደራጀ ህዝባዊ ኃይል ባለመኖሩ የኢትዮጵያ ህዝብ የታገለላቸዉ የትግል ዉጤቶች ሁሉ የአምባገነኖች መጠቀሚያ ሆነዉ ቀርተዋል።
የኢትዮጵያ ህዝብ ጀግና ነዉ፤ ተጋሽ ነዉ፤ ወይም አርቆ አስተዋይ ነዉ ሲባል እንዚህ እሴቶች ወንዱን፤ ሴቱን፤ ምሁሩን፤ ገበሬዉን፤ ሰራተኛዉንና መለዮ ለባሹን ሁሉ የሚያጠቃልሉ ህዝባዊ እሴቶች ናቸዉ እንጂ የአንድ ህብረተሰብ ክፍል ልዩ ንብረቶች አይደሉም። በእርግጥም አብዛኛዉ የታሪካችን ክፍል በአገር አንድነት ግንባታና ይህንኑ አንድነት ከዉጭ ወራሪዎች በመከላከል ጦርነት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ጀግንነትን በቀጥታ የምናያይዘዉ ከዚሁ አገርንና የአገር አንድነትን ከማስከበር ስራ ጋር ነዉ። በእርግጥ አገርን ከጠላት መከላከል ጀግንነት ነዉ፤ ሆኖም መሳሪያ ተሸክሞ አገሩን ከጠላት የሚከላከል ሠራዊት ምን እለብሳለሁ፤ ምን እበላለሁ፤ በምንስ እዋጋለሁ ከሚለዉ ስጋት ተላቅቆ በሙሉ ኃይሉና አዕምሮዉ መዋጋት የሚችለዉ እንደነሱ ጀግና የሆነና በደጀንነት የተሰለፈ ህዝብ ሲኖር ብቻ ነዉ።
እስከ አድዋ ጦርነት ድረስ አገራችን ኢትዮጵያ የመሪዉን የክተት አዋጅ ጥሪ እየሰማ የሚዘምት ህዝብ እንጂ ቋሚ የመከላከያ ሠራዊት አልነበራትም። ባለፉት 60 አመታት ግን ኢትዮጵያ የምድር ጦር፤ አየር ኃይል፤ ብሔራዊ ጦርና እስከ ቅርብ ግዜ ድረስ ደግሞ የባሕር ኃይልን ጭምር ያካተተ ዘመናዊ የመከላከያ ሠራዊት ነበራት። ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የአገራችንን በትረ ስልጣን እስከጨበጠበት እስከ 1983 ዓም ድረስ የነበረዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሞላ ጎደል በመስኩ ልምድ፤ ችሎታና እዉቀት ባካበቱ ባለሙያዎች የተሞላና የአገረን ዳር ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር ለወገናቸዉ ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ደህንነት ቀና አመለካከት ባላቸዉ አገር ወዳዶች የተገነባ ሠራዊት ነበር። ወያኔ በ1983 ዓም አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ይህንን አገር ወዳድ የሆነ ፕሮፌሺናል ሠራዊት በትኖ ነዉ ለአንድ ድርጅት ጥቅምና ዝና በቆሙ፤ ፊደል ባልቆጠሩና ሙያዊ ብቃት በሌላቸዉ መሀይሞች የተሞላ መከላከያ ሠራዊት የተካዉ። እንደዚህ ስንል ግን ወያኔ በገነባዉ የአገር መከላከያ ሠራዊት ዉስጥ አገራቸዉ ኢትዮጵያን ከራሳቸዉ በላይ የሚወዱና ለአገራቸዉና ለወገናቸዉ ክብርና ጥቅም መስዋዕት ለመሆን የቆረጡ ሰዎች የሉም ማለት አይደለም፤ እንዲያዉም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚመራዉና የግዳጅ ትዕዛዝ የሚወስደዉ አገራቸዉን በሚጠሉ ዘረኞች መሆኑ ነዉ እንጂ ዛሬም ቢሆን አብዛኛዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባል የእናት አገሩ ዳር ድንበር መደፈርና የወገኖቹ መረገጥ የሚያንገበግበዉ አገር ወዳድ ሠራዊት ነዉ።
የ1966ቱ ህዝባዊ አብዮት ሲፈነዳ የነበረዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የፊዉዳሉ መንግስት የደሞዝ ጭማሪ አድርጎለት ከህዝባዊ ኃላፊነቱ ሊያዘናጋዉ ሲሞክር – “ሎሚ ተራ ተራ፤ “ሎሚ ተራ ተራ እኛስ አግኝተናል ሲቪሉን አደራ” ብሎ የህዝብ ወዳጅነቱን ያረጋገጠ አገር ወዳድ ሠራዊት ነበር። አመጸኛዉ ደርግ ይህንን ሠራዊት ተጠቅሞ ነዉ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤን ስርዐት ያስወገደዉና የመሬት አዋጅን የመሳሰሉ ስር ነቀል አርምጃዊዎች መዉሰድ የጀመረዉ። አምባገነኑ ደርግ ቁልፍ በሆኑ የመከላከያ ሠራዊት ተቋሞች ዉስጥ ታማኝ የሆኑ የራሱን ሰዎች አስቀምጦ ለ17 አመታት የኢትዮጵያን ህዝብ ቢረግጥም ጄኔራል ተፈሪ በንቲን፤ ኮሎኔል አጥናፉ አባተን፤ ተስፋዬ ትርፌን፤ ጄኔራል መርዕድ ንጉሴን፤ ቁምላቸዉ ደጄኔን፤ አምሀ ደስታንና ፋንታ በላይን የመሳሰሉ እስከመጨረሻዉ ትንፋሻቸዉ ድረስ ህዝባዊ አደራቸዉን የጠበቁ ታማኝ የህዝብ አገልጋዮች በመከላከያ ሰራዊቱ ዉስጥ ነበሩ። በንጉሰ ነገስቱም ዘመን ቢሆን ገና ከጥዋቱ ከዝናና ጥቅም ይልቅ የአገራቸዉን ጥቅም ያሰቀደሙ እንደ ጀኔራል መንግስቱ ነዋይ አይነት የለዉጥ አርበኞች ነበሩ።
ወላድ በድባብ ትሂድ – ዛሬም ቢሆን እጅግ በጣም ጨለማ በሆነዉ ጨካኝና ዘረኛ ስርዐት ዉስጥ ጨለማዉን እየገለጡ በድፍረት የአገራቸዉን ህዝብ ጩኸትና ሰቀቃ አዳምጠዉ ዘረኝነት በቃ ያሉ ጀግኖች በመከላከያ ሠራዊቱ ዉስጥ አሉ። በአንድ ቋንቋና በዘር ሰንሰለት ተሳስረዉ የሚሰሩ የወያኔ ደህንነቶች መግቢያዉንና መዉጪያዉን ቆልፈዉ ለጌቶቻቸዉ ዘብ ቢቆሙም ጀግናና ጭስ መዉጪያ አያጣምና ከፍተኛ ልምድና ችሎታ ያላቸዉ የወያኔ መከላከያ ሠራዊት አባላት ከወያኔ ጎራ እየወጡ የህዝባዊ አመጹን ጎራ እየተቀላቀሉ ነዉ። ሁላችንም በየቀኑ በግልጽ እንደምናዉ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያ ዉስጥ ሁለት አይነት ዜግነት ፈጥረዋል። አንደኛዉ ዜግነት ወያኔና አገራቸዉን ከድተዉ የወያኔ ተላላኪ በሆኑ እንደነ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ፤ አዲሱ ለገሰና ሬድዋን ሁሴንን በመሳሰሉ ሆድ አደሮች የተሞላ ሲሆን፤ ሁለተኛዉ ዜግነት ደግሞ አገር ወዳዶችና የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ያሉበት ነዉ። ከእንደዚህ አይነቱ በዘር ከተከፋፈለና እያንዳንዷ ኮሽ ያለች ነገር በወያኔ ደህንነት ሰራተኞች ተመዝግባ በምትመረመርበት አገር ዉስጥ ለህዝባዊ አላማ ጸንቶ መቆምና ስርዐቱን አልፈልግም ብሎ የነፃነት ኃይሎችን መቀላቀል ከፍተኛ ጀግንነትንና ቆራትነትን ይጠይቃል። ቆየት ባለዉ ግዜ እነ መቶ አለቃ ተሾመ ተንኮሉና ጄኔራል ከማል ገልቹ፤ አሁን በቅርቡ ደግሞ ሦስቱ የተዋጊ ሂሊኮፕተር አብራሪዎችና አራቱ ባለከፍተኛ ማዕረግ የአየር ኃይል ተዋጊ ጄት አብራሪዎች የወሰዱት ህዝባዊ እርምጃ ከሆነ በኋላ በሰበር ዜና ስንሰማዉ ቀላል ይመስላል እንጂ እርምጃዉ ጀግንነትን፤ ቆራጥነትንና በህይወት መወራረድን ይጠይቃል። እነዚህ ለፍትህ፤ ለነጻነትና ለእኩልነት የቆሙ ቆራጥ ዜጎች በወሰዱት እርምጃ አገር ዉስጥና ከአገሩ ዉጭ የሚኖረዉን ኢትዮጵያዊ እጅግ በጣም ደስ አሰኝቷል። በእርግጥም እነዚህ ጀግኖች የወሰዱት እርምጃ ህዝባዊ ትግሉን የሚያነቃቃና የሚያጠናክር ነዉና በልጆቻችን እርምጃ ልንኮራና ደስ ሊለን ይገባል። ሆኖም ይህ ቆራጥ እርምጃ የትግል ጥሪም ነዉና ሁላችንም ጥሪዉን አዳምጠን ዛሬ ነገ ሳንል አሁኑኑ አቤት ማለት አለብን።
ዛሬ ለአመታት በላይ ሲታመስና ሲብሰለሰል የቆየዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ብሶት ገንፍሎ ወጥቶ ወደ ለየለት ህዝባዊ አመጽነት እየተቀየረ ነዉ። ይህንን ህዝባዊ አመጽ በትክክል መርቶ ከግቡ ለማድረስና ከዚህ በፊት በተከታታይ የተፈጠሩትን የስልጣን ከፍተቶችና ስህተቶች አርሞ ትግሉን በእስማማኝ መሰረት ላይ ለማቆም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊና አገራዊ ሃላፊነት አለበት። በቅርቡ ተዋጊ የጦር ሂሊከፕተራቸዉን እንደያዙ የወያኔ ስርዐት በቃን ብለዉ የነጻነት ሀይሎችን የተቀላቀሉት ጀግኖች ዜና ሲሰማ ወያኔ ከፍሎ ያሰማራቸዉ ተናካሽ ዉሾቹ ያንን የለመዱትንና የተካኑበትን እንቆርጣችኋለን እንፈልጣችኋለን የሚል ተራ ዛቻቸዉን አሰምተዉናል። ከዚህ አልፈዉም ወያኔ የታጠቀዉን መሳሪያ ዘመናዊነትና ያደራጀዉን ሠራዊት ብዛት ደጋግመዉ በመጥቀስ እነሱን መንካት ከእሳት ጋር መጫወት እንደሆነ ሊነግሩን ሞክረዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ በወቅቱ ስሙን እንኳን አጣርቶ የማይጠራዉ ህወሓት ከሰሃራ በታች ተወዳዳሪ የለዉም የተባለዉ ሠራዊት የገነባ ኃይል ለምን አንደሚዋጋ እንኳን በማያዉቅ ጀሌ ጦር ማሸነፍ ከቻለ ዛሬማ ፍጹም የሆነ ህዝባዊ መሠረት ያላቸዉና ለምንና ለማን እንደሚዋጉ ጠንቅቀዉ የሚያዉቁ የነጻነት ኃይሎች ካሰቡበት ለመድረስ የሚያግዳቸዉ ምንም ምድራዊ ኃይል እንደሌለ ወያኔና ሆድ አደር ደጋፊዎቹ ተንቅቀዉ ሊያዉቁ ይገባል። ወያኔ ልቡ ስላበጠ የተለቀ ይምሰለዉ እንጁ የትልቅነቱ መገለጫ አድርጎ የሚተማመንበት የመከላከያ ሠራዊት ያቺ የፍጥጫ ቀን ስትመጣ ወያኔን ለመደምሰስ ወገኖቹን የሚቀላቀል ሠራዊት ነዉ። ባለፉት ሁለት ሳምንታት ጀግኖቹ የኢትዮጵያ አየር ኃይል አባላት የወሰዱት ህዝባዊ እርምጃም በአየር ኃይሉ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን ቀን፤ ግዜና ሁኔታ እየመረጠ እግረኛ ሠራዊቱም የሚወስደዉ እርምጃ እንደሆነ ያለ ጥርጥር እናምናለን።
ዉድ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሆይ – አንተንና ወገኖችህን በዘር ከፋፍሎ እየገዛ አገርህን የሚያፈርሰዉ ወያኔ ለዚህ እኩይ ስራዉ የሚጠቀመዉ አንተኑ ከህዝብ አብራክ የወጣኸዉን የህዝብ ልጅ ነዉ። በቅርቡ ባህር ዳር ዉስጥ የቅዱስ ታቦት ማደሪያ የሆነዉን ቦታ ከቤ/ ክርሲቲያን ቀምቶ የሸቀጥ መሸጫ ለማድረግ ያደረገዉን ሙከራ የተቃወሙ ኢትዮጵያዉያን ወንድሞችህና ወንድሞችህ እንዲሁም አለም በቃኝ ያሉ መነኩሴ ጭምር በጥይት ጨፍጭፏል። በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ወልቃይት ጠገዴን ከጎንደር ቆርጦ ትግራይ ላይ የቀጠለዉ ወያኔ ይህ ፀረ ህዝብና ፀረ አገር ወንጀል አልበቃ ብሎት ለዘመናት አብሮ የኖረዉን የትግራይንና የጎንደርን ህዝብ ለማባላት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ነዉ። በታህሳስ ወር አጋማሽ ጎንደር ዉስጥ የትግራይና ክልልና የጎንደር ሚሊሺያዎች የተኩስ ልዉዉጥ ካደረጉ በኋላ ወያኔ አገርን ለመዉረር በሚመጣ ጠላት ላይ እንጂ በራሱ ወገን ላይ መዝመት የሌለባቸዉን ከ30 በላይ ታንኮችና ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ወታደሮች ወደ ጎንደር በማሰማራት አገሩንና ወገኑን መጠበቅ ያለበትን ሠራዊት ከገዛ ወገኖቹ ጋር እንዲፋጠጥ አድርገዋል።
በዚህ ፈታኝና እጅግ በጣም አስቸጋሪ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሂድና ግድል በተባለ ቁጥር መጠበቅና መንከባከብ የሚገባዉን የገዛ ወገኖቹን የማይገድል አስተዋይና ወገንተኛ ሠራዊት መሆኑን በተግባር ማሳየት አለበት። አዎ! የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ምንግዜም ቢሆን በአገሩ ጠላቶችና ወራሪዎች ላይ ብቻ እንጂ እያበለና እያጠጣ ባሳደገዉና እኔንና አገሬን ጠብቅ ብሎ ባስታጠቀዉ ህዝብ ላይ በምንም አይነት አፈሙዙን አያዞርም። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ህዝብ ከወያኔ በላይ ጠላት የላቸዉም። ህዝብና አገር እስከ ምድር ፍጻሜ ድረስ አብረዉ የሚዘልቁ ተከታታይ ክስተቶች ናቸዉ፤ ወያኔ ግን ትናንት በጠመንጃ ሀይል መጥቶብን እኛንና አገራችንን ለማጥፋት የሚታገል የለየለት ጠላት ነዉ። ከዛሬ ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባገኘዉ አጋጣሚ ሁሉ ወያኔን ከዉስጥ ሆኖ መቦርቦር አለበት፡ ይህንን ማድርግ ካልቻለ ደግሞ ወያኔ ከወገኖቹ ጋር እንዲዋጋ ሲያሰማራዉ ወያኔን እየከዳ ከነጻነት ኃይሎች ጋር ተቀላቅሎ ወያኔን ለመደምሰስ በሚደረገዉ ትግል ዉስጥ ወሳኙን ሚና መጫወት ይኖርበታል። ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከዚህ ቀደም እንዳደረገዉ ሁሉ አሁንም እንደገና ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት . . . ና ተቀላቀለንና አንድ ላይ ሆነን ወያኔንና ወያኔ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት ቀብረን የኢትዮጵያን ህዝብ ከዉርደት፤ ከእስር፤ ከድብደባ ከግድያና ከስደት እናድን የሚል አገራዊ ጥሪዉን ከአደራ ጋር ያስተላልፋል።

ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት (ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ)

Biniam Gizaw
ይሄ ምርጫ መቼስ ስንቱን ያስታውሰናል?በደርግ ዘመን እናቶች ወንድ ልጃቸውን ከየጉያቸው እየተነጥቁ እና እየታፈሱ በጦርነት ሲማገዱ ወንድ ልጅ ላለመውለድ. . . ትዝም አላለሽ ወይ የክፉ አመቱ ላንቺና ለልጅሽ ያለቀ ስንበቱ ማህጸኔን ዝጋ ይቅር ምን አባቱ በእንባ እየዳከርሽ ብለሽ ያልሽበቱ። እያሉ ፈጣሪን ወንድ ልጅ እንዳይሰጣቸው የለመኑትን ቤቱ ይቁጠራቸው። የአፈሳና የሀገራችንን አንድምታ ለመረዳት ከሰሞኑ በየከተማዎችና ጎዳናዎች ያለው የድብደባ የአፈሳና የሞት ፍርሀት ድባብ ተቀባብሎ ለቃታ የተዘጋጁ ጥይት በእያንዳንዱ ሰላማዊ ዜጋ ጆሮ ስር ተደግኖ እንደሚራመድ በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
. . . ጭቃ ከማቡካት ጀምሮ አብሬው ያደኩት ጓደኛዬ ስሙ ጌታቸው ይባላል። እንዴት እንደምንዋደድ እንደምንተሳሰብ እና እንደምንመካከር አትጠይቁኝ። በቃ ጌቾ ምርጥ ጓደኛዬ ነው።
እናም በጊዜው ወያኔ መዲናችን አዲስ አበባ ገቡ ገቡ የሚባልበት ሰአት ኖሮ ግራ መጋባቴን ከባልንጀራዬ ላወራ በአጥር በኩል ጌቾ!ጌቾ! ብል እናቱ ወ/ሮ በለጥሻቸው ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ከበሮአቸውን ጸሀይ ላይ እያገላበጡ ግቻ ያርግህ. . . ጎይቶም አትልም! ብለው ቀልቤን ገፈፉት። ነገሩ ወዲህ ኖሮ እሳቸውም ወ/ሮ በለጥሻቸው ታጋይ ትብለጽ ተብሎ ስማቸው መተርጎሙን ያወኩት ቆይቼ ነገር ከገባኝ በኋላ ነው። ከዚያማ እነአቶ ክፍሉ (ክፍለእግዚእ) እነአዲስ (ታጋይ ሀዲሽ) ወዘተ ስናዳምጥ የጫካ ስም ብቻ ሳይሆን የከተማም ስም እንደነበራቸው ተረዳን።
ከዛ በኋላማ ምኑን ልንገራችሁ በኳስ ሜዳ ሰው የጠፋ ጊዜ በረኛ ካልሆነ ወደ ውጪ የወጣ ኳስ አቀባይ የነበረው ጊቾ በግልጥ ፎሪ የወጣውን እንደፈለገ እና ደስ እንዳሰኘው ጎል ብሎ ሲያፀድቀው ቢደብረንም መስማማት ብቻ ሆነ። አይ የቀን ክፉ! ግንቦት 20። ይኽው እስክንበታተን ድረስ ጎይቶምም እንደኛ ባሉት ላይ ተቀይሮ ሲጎለብት ታጋይ ትብለፅ ደግሞ እነማዘርን በዳቦ ተቆጣጥረው ሲጠረንፉን ከረሙ። 
ጦጣ በአንድ ወቅት ለቃለ መጠይቅ ቀርባ ኖሮ ምን ትወጃለሽ? ተብላ ብትጠየቅ የዛፍ ላይ ትግል አለች አሉ። በፀዳ ሜዳ ግልፅነትና እውነት ባለበት ምርጫ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ማየት ከንቱ እየሆነ መምጣቱ በዕጅጉ ያሳዝነናል ። አንድ ጎጠኛ ብሔረሰብ ብቻ በሚመቸው ፓርላማና በየቀበሌው እንደ ጦጣ በስልጣኑ ላይ እየተንጠላጠለ 23 ዓመት መግዛቱ ስርዓቱ ምንኛ አስከፊ መሆኑን የሚያሳይ ነው። 
ኢትዮጵያ ለዘመናት ተከብራ የኖረችና ህዝቦቾም ልዩነትን ወደሆላ በመተው በጋራ ፣በመቻቻል ፣በመካባበር ሀገራቸውን አስከብረው ከዘር እና ከእምነት ይልቅ ኢትዮጵያውነትን በማስቀደም ኢትዮጵያዊነት የገነነባት ሀገር እንደነበረች ይታወቃል እነሆ ዛሬ ወያኔ የሁትሱና ቱትሲን ስርዓት ናፍቆ ገዢ ከኔ ዘር ሌላ ለአሳር እያለ ሰፊውን ህዝብ ለጦርነት ጋብዞታል። ወያኔ ፈጽሞ በኢትዮጵያዊነት የማያምን እና የኢትዮጵያ ህዝበም በአንድነትና በፍቅር እንዲኖር የማይፈልግ ጸረ ኢትዮጵያዊ ሲሆን ይህንንም በመረዳት እኛ ኢትዮጵያኖች አንድነታችን ለወያኔ የራስ ምታት መሆኑን አውቅን  አንድነታችንን የሚያጠናክር ስራዎች ላይ ልናተኩር ይገባል :. ዘረኛው የህህዋት መንግስት በአንድ ወቅት አርሱ አደሩ የሀገሬን ገበሬ እኔ አውቅልሀለሁ እያለ ካለበት ሀገር መሬትና ቀኤ ድረስ መጥቶ ልግዛህ እያለ መከራውን ሲያበላው . . .
ሳለቅስ ሳነባ የሰጠኽኝ ሸማ ጉድ በል ያገሬ ልጅ እንካ መርዶ ስማ የወንዝህ ማዕረግ በትግሬ ተቀማ
እያለ ለአያትና አባቱ በቅኔ ብሶቱን መናገሩ አፈናና ረግጣውን ቅሚያና ዘረፋውን መቋቋም ቢያቅተው መሆኑ ልብ ይሏል። የፈረንሳዩ ደራሲና ፈላስፋ ቪክቶር ሁጎ "When dictatorship is a fact, revolution becomes a right." ብሎ ማለቱ አንደ ወያኔ ላለ በአንድ ብሔር የበላይነት ተንፈናጥጦ እንደፈለኩ ልግዛህ ለሚል መንግስት ትክክለኛ አባባል ነው።
ምርጫ ፍትህና ዴሞክራሲ ምን እንደሆነ ለማይገባው መብት ማስከበሪያው ብቸኛ መንገድ ለለውጥ ፀንቶ መታገል ብቻ ነው። በአሳማ መንጋ የምርጫ ውድድር ያው አሸናፊው አሳማ እንጂ ነብር ወይ አንበሳ አይሆንም። በመሆኑም ያው አሳማ ነገም ልርገጣችሁ ማለቱ አይቀርም። በሰብዓዊ ትግል ተስፋ አይቆረጥም የሰፊው ህዝብ መብት ታላቅ ውቅያኖስ ነውና ጥቂት የአምባገነን ጠብታ ሰፊውን ባህር አያደፈርሰውምና አሁንም የሰብዓዊ መብት ትግል አሸናፊ ነው። በጥቂት ዘረኞችና በአንድ ጎሳ የበላይነት የተያዘው የወያኔ አገዛዝ የሰፊውና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በምንም መልኩ ሊገታው አይገባም ይልቁንም ''ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት'' እንዲሉ በማን አለብኝነት የተንሰራፋውን ወያኔና አግዛዙ መቃብሩ ተምሶ ያለቀ መሆኑ ግልፅ ነው። እናም በሁሉም አቅጣጫ የትግላችንን ትንቅንቅ ልንቀጥል ይገባል እላለሁ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

Friday, January 9, 2015

የመከላከያ ሰራዊት በትግራይ እና አማራ ተዋጊዎች መካከል ሰፈረ (ከዚያስ?)

January9,2015

ዳዊት ከበደ ወየሳ
በሰሜን ጎንደር, አርማጭሆ አውራጃ ልዩ ስሙ "ገ'ጨው" በተባለው ስፍራ የመከላከያ ሰራዊት ከትላንት ጀምሮ እንዲሰፍር ተደርጓል:: ማዶ እና ማዶ ሆነው እየተዋጉ ባሉት የትግራይ ወታደሮች እና በአማራ ህዝብ መካከል መከላከያ ሰራዊት ከሰፈረ በኋላ ጦርነቱ አሁን ለጊዜው ጋብ ብሏል:: የቀድሞ የህወሃት ወታደሮችን ሁመራ ላይ በማስፈር አካባቢውን ለራሱ ያደረገው ህወሃት - አሁን ደግሞ በአርማጭሆ መስፋፋት በመጀመሩ ነው - በአካባቢው ከሚኖረው የአማራ ህዝብ ጋር ግጭቱ የተቀሰቀሰው::

ሰሞኑን ግጭቱ ከመባባሱ በፊት የአማራው ህዝብ ተዋጊዎች - ህወሃት በአጭር ጊዜ ውስጥ አካባቢውን ለቅቆ እንዲወጣ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነበር:: ሆኖም የህወሃት ወታደሮች አካባቢውን ለቅቀው ባለመሄዳቸው በተለይ በማይ'እምቧ በርካታ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ - ህወሃት አባላት ሞተዋል:: በወያኔዎቹ ላይ የደረሰው አደጋ ያስደነገጣቸው እና ወደ አርማጭሆ ያመሩት ሌሎች የህወሃት አባላት - ከአካባቢው ነዋሪ ጋር ጦርነት ሲያደርጉ ነበር የከረሙት:: በዚህ ጦርነት የሞቱት ሰዎች ቁጥር በትክክል ባይታወቅም የተኩስ ልውውጡ ከፍተኛ ነበር:: አሁን የመከላከያ ሰራዊት በሁለቱ ወገኖች መካከል ከሰፈረ በኋላ ግን ጦርነቱ ለጊዜው ጋብ ብሏል:: ሆኖም ሁለቱ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች - ማለትም የህወሃት እና ብአዴን አመራሮች ውስጥ ውስጡን እየተናቆሩ ናቸው::

 ህወሃት በድንበር ጉዳይ ካደረጋቸው የአገር ውስጥ ጦርነቶች ይሄኛው ጠንከር ያለ ነው:: ከዚህ ቀደም የህወሃት ወይም የትግራይ ታጣቂዎች የአማራውን መሬት ሲወስዱ - ህዝቡ "በህግ አምላክ" ብሎ እየጮኸ ከመሞት ውጪ ብዙ ምርጫ አልነበረውም:: አሁን ግን እየጮኸ ሳይሆን ጥይት እያጮኸ መሞትን የመረጠበትን አጋጣሚ ለማየት እየበቃን ነው:: አሁን የደረንበትን የቅርቡን ታሪክ እንዳየነው ከሆነ - ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) የአማራውን ህዝብ ከሁመራ እና ጠለምት: ከበየዳ, ከወልቃይት, ከድብ ባህር, ከአብደራፌ, ከብራ ዋድያ, ከሻግኔ እና ላሄን እያፈናቀሉ መሬቱን ለቀድሞ የወያኔ ወታደሮች ሲሰጡ ቆይተዋል:: በአካባቢው የአማራው መሬት ብቻ አይደለም ተወሰደው:: ወንዶቹን እያፈናቀሉ: ያንገራገረውን እየገደሉ ሚስቶቻቸውን እና ሴት ልጆቻቸውን በሙሉ ነው ነጥቀው የወሰዱት:: [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]



Thursday, January 8, 2015

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

January8,2014
በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡

Ryotየኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ የዝግጅት ክፍላችን አንድ ጽሑፍ የቀረበበት አካል ምላሹን በዚያዉ በተፃፈበት የህትመት ዉጤት ላይ ማስነበብ እንደሚችል በህግ የተደነገገ መሆኑን ከማወቁም በላይ የትኛዉንም አይነት ሀሳብ ለማስተናገድ ክፍት ነበርና ምላሻቸዉን በጋዜጣችን ላይ ታተመ፡፡ በዚህ ብቻ ግን አልተገቱም፤ በወቅቱ የገዢዉ ፓርቲን ሀሳብ በማቀንቀን ይታወቁ የነበሩት እንደ ዳጉ ኢትዮጵያና ሰነድ ያሉ ጋዜጦች ሀሳቦቼን በሃሳብ መምታት ባለመቻላቸዉ ይሁን ባለመፈለጋቸዉ ተራ ዘለፋዎችን ያወርዱብኝ ጀመር፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የገዢዉ ፓርቲ ደህንነቶች ስልክ በመደወል፣ በዝግጅት ክፍላችን አድራሻ በስሜ ደብዳቤ በመላክና በአካልም በማግኘት ጭምር መንግስትን የሚተቹ ፅሑፎችን እንዳልፅፍ ሊያስፈራሩኝ ሞከሩ፡፡ “ማስፈራራት የሚቻለዉ የሚፈራ ሲኖር ነዉ” እንዲሉ ሙከራቸዉ ዋጋ አልነበረዉም፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያ ፅሑፌን ለህትመት ከማብቃቴ በፊት ልከፍለዉ ስለምችለዉ መስዋዕትነት በሚገባ አስቤበታለሁ፡፡ የሀገሬን ጉዳይ በንቃት የምከታተል ዜጋ እንደመሆኔም ከገዢዉ ፓርቲ የተለየ ሀሳብ ያቀነቀኑ ሰዎች የደረሰባቸዉን በሚገባ አዉቃለሁ፡፡ በመሆኑም ከሁለት መጥፎ ምርጫዎች አንዱን ማለትም እነሱ የደረሰባቸዉን ግፍ እንዳይደርስብኝ የሀገሬን ጉዳይ በተመለከተ ፍዝ ተመልካች መሆንን ወይም በሙያዬ የምችለዉን አስተዋፅኦ አበርክቼ የሚመጣዉን መቀበል መምረጥ ነበረብኝ፡፡ ሁለተኛዉን የተሻለ መጥፎ ምርጫ ከመረጥኩ የሰነበትኩ በመሆኑም እየበረከቱ የመጡትን ማስፈራሪያዎች ከቁብ ሳልቆጥር የጋዜጠኝነት ስራዬን መቀጠል ቻልኩ፡፡ በዚሁ መሰረት ስራ ለመያዝ፣ የደረጃ እድገት ለማግኘትም ሆነ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከደህንነት ስጋት የፀዳ ኑሮ ለመኖር የኢህአዴግ አባል ካልሆነም ደጋፊ መሆን ከጊዜ ጊዜ ግድ እየሆነ መምጣቱን የሚያሳዩ፣ ገዢዉ ፓርቲ እንዳጎናፀፈን የሚገልፅልን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በተጨባጭ አለመኖሩን የሚሞግቱ፣ የኢህአዴግን እንደሀገር የማሰብ ችሎታ ወይም ፍቃደኝነት አናሳ መሆን የሚተቹና ሌሎችም መንግስት ቀናነት ቢኖረዉ ኖሮ ሊታረምበት የሚያስችሉትን በርካታ ፅሑፎች አቀረብኩ፡፡ አንድ ቀን ጧት ግን አምባገነኑ መንግስታችን ከጀመርኩት ጉዞ ገታኝ፡፡ ሰኔ10/2003 በወቅቱ እሰራባት በነበረችዉ ተወዳጇ ፍትህ ጋዜጣ ላይ የቀድሞዉን ጠቅላይ ሚኒስትር በተመለከተ ፅሑፍ ለህዝብ ማቅረቤን ተከትሎ ሰኔ14/2003 ዓ.ም ለእስር ተዳረግሁ፡፡
ማዕከላዊና ቃሊቲ ምንና ምን ናቸዉ?
ዉድ አንባብያን፤ ፊዘኛዉ መንግስታችን በሽብርተኝነት እንደሚጠረጥረኝ ገልፆ በእጆቼ ካቴና በማጥለቅ በቁጥጥር ስር አዋለኝ ካዋለኝ ከዚያ ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለቁጥር የሚያታክቱ የመብት ጥሰቶችን እየፈፀመብኝ ይገኛል፡፡ ለአብነት ያህል እጅግ በጣም ጥቂቶቹን እነሆ!
ከህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነዉ የሚባልለት ህገመንግስት በጥበቃ ስር ያሉ ሰዎች በጠበቆቻቸዉ የመጎብኘት መብት እንዳላቸዉ ቢገልፅም እኔና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ግን ይሄ መብታችን በማዕከላዊ አለቆች ተጥሷል፡፡ ጠበቃዬን ለማግኘት የተፈቀደልኝ ምርመራዉ ከተጠናቀቀና ቃል ከሰጠሁ በኋላ ወደቃሊቲ ለመዉረድ የአስርቀናት ዕድሜ ያህል ሲቀረኝ ነበር፡፡ በቤተሰብና በጓደኞቼ ለመጎብኘት የተፈቀደልኝም ሁለት ወር ከ3 ሳምንታት ክልከላ በኋላ ነበር፡፡ ከጠበቃዬ ጋር እንዳልገናኝ ተደርጎ የሚካሄደዉ ምርመራ የፃፍኳቸዉን ፅሑፎች ለምን እንደፃፍኩ፣ ከበስተኋላዬ ሆኖ የሚገፋኝ አካል ስለመኖር አለመኖሩና የመሳሰሉት ጥያቄዎች ላይ ያተኮረ ቢሆንም አልፎ አልፎ ደግሞ መልኩን ይቀይራል፡፡ አንዳንድ ቀን መርማሪዎቹ በማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በተካሄዱ ስብሰባዎች ላይ ያቀረብኳቸዉን ሀሳቦች እያነሱ ከመንግስት የደህንነት ሀይሎች የሚያመልጥ ምንም ነገር እንደሌለ በመግለፅ ቢጤ ያሰሙኝ እንደነበር ሳልጠቅስ ማለፍ አልፈልግም፡፡፡ እንዲህ አይነቱ ንግግራቸዉ አሰልቺዉን ምርመራ ዘና እልበት ዘንድ የሚረዳኝ የእፎይታ ጊዜ ሰጥቶኛል፡፡ 
በአደባባይ ስብሰባዎች ላይ የተናገርኩትንና ደህንነት ሊሰልለዉ የማያስፈልገዉን ግልፅ ነገር እንደ ትልቅ የደህንነቶች የስራ ዉጤት ተደርጎ ሲገለፅ ከመስማት በላይ ምን የሚያዝናና ነገር ይገኛል? የት/ቤት ርዕሰ መምህራኖች በሙሉ የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ የተደረገበት ምክንያት መንግስት እንደሚለዉ የትምህርት ፖሊሲዉን ለማስፈፀም ሳይሆን የመምህራንንና የተማሪዎችን የፖለቲካ አቋም ለማወቅና ይህንኑ ሪፖርት ለማድረግ መሆኑን የማይረዳ መምህር ይኖራል? ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆኑ ርዕሰ መምህራኖች ሰበብ እየተፈለገላቸዉ ከቦታቸዉ እንዲነሱ ሲደረግስ ስንታዘብ አልኖርንም? “ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል” አለ ያገሬ ሰዉ! ሆዴ ባዶ እንዳይቀር ሁሉን መተንፈሴን ትቼ የጀመርኩትን የማዕከላዊ ምርመራ ጉዳይ ልቀጥል፡፡

የምርመራዉ ይዘት ከጥቂት ሳምንታት በኋላ መልኩን እየቀየረ መጣ፡፡ በሪፖርተርነት እሰራበት የነበረዉ የኢትዮጵያ ሪቪዉ ድረገፅ አዘጋጅ ኤልያስ ክፍሌ የሽብር ተልዕኮ እንደሰጠኝ በሀሰት እንድናገርና ተከሳሽነቴ ቀርቶ ምስክር ሆኜ እንድፈታ ለማድረግ የተለያዩ ጫናዎቸው ይደርሱብኝ ጀመር፡፡ ለአምስት ደቂቃ ያህል ጧትና ማታ ወደመፀዳጃ ቤት ለመሄድ ከሚከፍቱልኝ በስተቀር ለአስራሶስት ቀናት ያህል ብቻዬን አንድ መጥፎ ሽታ ያለዉ ክፍል ዉስጥ ተዘግቶብኝ ከረምኩ፡፡ በዚህ ወቅት ጉዳዬን የያዘዉ ዐቃቤህግ ማዕከላዊ በመምጣት እያስጠራኝ ሀሳቤን የማልለዉጥ ከሆነ እድሜ ልክ ወይም ሞት እንደሚያስፈርድብኝ ይዝትብኝ ነበር፡፡ ሀሰን ሽፋ በበኩሉ በሀሳባቸዉ የማልስማማ ከሆነ የያዘኝን የወጣት ጀብደኝነት ማስተንፈስ ለነሱ ከባድ ስራ አለመሆኑን ነግሮኛል፡፡ በኔ በኩል ደግሞ ከተጠረጠርኩበት ወንጀል ንፁህ መሆኔ እንጂ ኤልያስ ላይ በሀሰት መመስከሬ ሊያስፈታኝ እንደማይገባ ስለማምን ይህንኑ በተደጋጋሚ አስታዉቄ ተከሳሽ መሆንን መረጥኩ፡፡ ኢህአዴግ እስካለ ድረስ የተሻለዉን መጥፎ እየመረጡ መኖር ዕጣፋንታችን ከሆነ ቆየ አይደል?

ማዕከላዊ እያለሁ ከተፈፀሙብኝ የመብት ረገጣዎች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ በአንድ ፖሊስ የተሰጠኝ ጥፊና ከግድግዳ ጋር ማጋጨት በተለይ ወንድ የፖለቲካ እስረኞች ከሚፈፀምባቸዉ ለዘላቂ የአካል ጉዳት የሚዳርግ ከባድ ድብደባ አንፃር ሳስተያየዉ የማዕከላዊ መርማሪዎች እንደሚሉት “ቁንጥጫ” ተብሎ ከመግለፅ የሚያልፍ ባለመሆኑ ብዙ ልልበት አልፈልግም፡፡ በወቅቱ የነበርነዉ ሴት እስረኞች ላይ ያን ያህል የከፋ አካላዊ ድብደባ አልተፈፀመም ማለት ግን የማዕከላዊ መርማሪዎች ለሴቶች ይሳሳሉ ማለት አይደለም፡፡ ለማሳያነት እስካሁን ድረስ ማዕከላዊ በተፈፀመባት ከባድ ድብደባ የተነሳ በህመም የምትሰቃየዋን የፖለቲካ እስረኛ እማዋይሽ አለሙን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አይ ማዕከላዊ! ማዕከላዊ ዘና ብለዉ የሚራመዱ ኩሩ የኢትዮጵያ ልጆች በገቡ ሳምንት በማይሞላ ጊዜ ዉስጥ በቃሬዛና በሰዎች ድጋፍ በሸክም ሲያሳልፉና የድረሱልኝ ዋይታ ሲያቀርቡ የሰማሁበት አሰቃቂ ቦታ ነዉ፡፡ ምስላቸዉ ከአይኔ ላይ፣ ጩኸታቸዉ ከጆሮዬ ተጣብቆ የሚኖረዉ እነዚህ ወገኖቼን እያሰብኩ መናደድ መቆጨት የዕለት ተዕለት የኑሮዬ አካል ሆኗል፡፡

የማዕከላዊዉን የመብት ረገጣ እዚህጋ ገታ ላድርገዉና በተለይ የፖለቲካ እስረኞችን ሰብአዊ መብት ከመጨፍለቅ አንፃር አምሳያዉ ወደ ሆነዉ የቃሊቲ እስር ቤት ልለፍ፡፡ ጳጉሜ3/2003 ዓ.ም ቃሊቲ እንደገባሁ በኋላ ላይ የጥበቃ ክፍል ሀላፊ እንደሆነች በተገነዘብኩት ሀላፊ አማካኝነት ጋዜጠኝነቴ ከታሰርኩ በኋላ የቀረ በመሆኑ ግቢዉ ዉስጥ በሚኖረኝ ቆይታ አርፌ መቀመጥ እንደሚኖርብኝ ተነገረኝ፡፡ አልጋ እስከሚለቀቅ ተብሎም እኔና በአንድ መዝገብ የተከሰስነዉ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ ምንም እንኳን ሁለታችንም የሳይነስ በሽታ ያለብን ቢሆንም ሽንት ቤት አጠገብ መሬት ላይ ፍራሽ አንጥፈን እንድንተኛ ተደረገ፡፡ ዉድ አንባቢያን ስለቃሊቲ ስታስቡ ወደ አዕምሮአችሁ የሚመጡት ያማሩ ግንብ ቤቶችና የተዋቡ አልጋዎች ከሆኑ ኢቲቪ እንደሸወዳችሁ ልነግራችሁ እወዳለሁ፡፡ የፓስተር ዳንኤል ገ/ስላሴ ፕሪዝን ፌሎሽፕ የተባለ ድርጅት እንዳሰራቸዉ የሚናገሩት እነዚህ ያማሩ ግንብ ቤቶች ሁለት ክፍሎችና መፀዳጃ ቤት ብቻ ያሏቸዉ ሲሆኑ የተቀሩት በሴቶች ዞን ዉስጥ ያሉ ክፍሎች ከሁለት ያረጁ ግንብ ቤቶች በስተቀር በቆርቆሮ የተሰሩና እስረኞች በተጨናነቀ ሁኔታ የሚኖሩባቸዉ ናቸዉ፡፡ የቃሊቲ ምቾት አልባነት የሚሰማዉ አካልን ብቻ አይደለም፡፡ ቃሊቲ ከአካል በከፋ ሁኔታ ለነፍስና ለመንፈስ ይጎረብጣል፡፡ እንዴት ቢሉ እንዲህ እልዎታለሁ፡፡ የቃሊቲ የሴቶች ዞን ቤተመፃሕፍት ከጥቂት ወራት ጀምሮ በመፅሐፍቱ አይነትም ሆነ ቁጥር መሻሻልን ቢያሳይም እኔ ቃሊቲ ከገባሁ ጀምሮ እስከቅርብ ጊዜያት ድረስ ግን ከመኖር በማይቆጠር ደረጃ የሚገኝ ነበር፡፡ ይህንን ክፍተት ቤተሰብና ጓደኞቼ በሚያስገቡልኝ መፀሐፍት ለመሙላት ባስብም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሚመጡልኝ መፅሐፍት የቃሊቲን ሳንሱር እንደወደቁ ተገልፆ እኔጋ ሳይደርሱ ይመለሳሉ፡፡ ከነዚህ መፅሐፍት ዉስጥ አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የሚሳትማቸዉ የታሪክ መፅሐፍት ሳይቀር ይገኙበታል፡፡ ቃሊቲ ለመንፈስም አይመችም ያልኳችሁ በዚህ ብቻ አይደለም፡፡ በራሴ ወጪ ኢንድራ ጋኒዲ ናሽናል ኦፕን ዩኒቨርስቲ በርቀት ፖለቲካል ሳይንስ ለማጥናት ከብዙ ዉጣዉረድ በኋላ ተፈቅዶልኝ የተበዘገብኩ ቢሆንም የመማሪያ ሞጁሎቹን ለማስገባት ግን የቃሊቲ አለቆች ፍቃደኛ አልነበሩም፡፡ ከብዙ ደጅጥናት በኋላ ሞጁሎቹ ሲገቡ ደግሞ በትምህርቱ ዙሪያ ላነባቸዉ የሚገቡኝ አጋዥ መፅሐፍት ስለፖለቲካ የሚያወሩ በመሆናቸዉ በፍጹም ሊገቡ እንደማይችሉ የመፅሐፍት ገምጋሚዎቹ አረዱኝ፡፡ ይባስ ብሎ በዚያን ወቅት ከሌላዉ ጊዜ በተለየ ሁኔታ ምንም አይነት መፅሐፍት እንዳይገቡልኝ በመደረጉ ለጠቅላላ ዕዉቀት ያህል ሞጁሎቹን ማንበቤን ብቀጥልም ትምህርቱ ግን በዚህና በሌሎች ምክንያት ለማቋረጥ ተገደድኩ፡፡

በቃሊቲ የኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔ ጋር የተቀራረቡ ወይም ደግሞ ሰላምታ ያቀረቡልኝ ሰዎች ሳይቀር መብታቸዉ ተጥሷል፡፡ ከሁለት አመታት በላይ የሚሆነዉን ጊዜ በርካታ እስረኞች በነበሩበት ክፍል ያሳለፍኩ ቢሆንም እኔን እንደሌላዉ እስረኛ ለመቅረብ የሞከሩ በሙሉ ስሜትን የሚጎዳ ወከባ፣ዘለፋና ለየት ያሉ ፍተሻዎችን አስተናግደዋል፡፡
በህክምና ጉዳይ የነበሩብኝን ችግሮች በተመለከተ ቤተሰቦቼ ደጋግመዉ የገለፁት መሠረታዊ ችግር በመሆኑ በዚህ ፅሑፍ ነካ አድርጌዉ ብቻ አልፋለሁ፡፡ ጡቴ ዉስጥ በበቀለዉ እጢ ምክንያት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የህክምና ክትትል በማደርግበት ወቅት በቀጠሮዬ ቀን ወደ ሆስፒታሉ ከምወሰድባቸዉ ይልቅ የማልወሰድባቸዉ ጊዜያት ይበዙ ነበር፡፡ የግራ ጡቴ ቀዶጥገና ከተደረገለት በኋላ በወቅቱ ክትትል ታደርግልኝ የነበረችዉ ዶክተር በሶስተኛ ቀን የቁስሉ ፕላስትር መቀየር እንዳለበትና በሳምንቱ ደግሞ ክሩ መዉጣት እንዳለበት ገለፀችልኝ፡፡ አብረዉኝ የሚሄዱት አጃቢ ፖሊሶች ከዶክተሬም ጋር ስነጋገር እዛዉ ነዉና የሚቆሙት እንዲህ አይነቱን ነገር ለማድረግ የሚችል ጤናጣቢያ ማረሚያቤቱ እንዳለዉ ተናገሩ፡፡ እኔም ቀጠሮ ቢሰጠኝ እንኳ በዚህ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ወደሆስፒታሉ ተመልሼ መሄድ አዳጋች መሆኑን ስለማዉቅ የተባሉት ነገሮች ቃሊቲ መፈፀማቸዉን አልጠላሁትም፡፡ በመሆኑም ለህክምና ክትትል የሶስት ወራት ቀጠሮ ተሰጠኝ፡፡ ክሩ መዉጣት ባለበት ቀን ስለጉዳዩ ለጥበቃ ክፍሉ አስታወቅኩ፡፡ እነሱም አሁን ደቡብ ሱዳን ከሚገኝዉ ጦር ጋር አብራ ከተጓዘች አንዲት የህወሐት ታጋይ የነበረች ነርስ ጋር አገናኙኝ፡፡ እሷም እዛዉ ጨርሼ መምጣት እንደነበረብኝና እዚህ ክሩን ማዉጣት እንደማይችሉ ነገረችኝ፡፡ የምታሳየኝ ጥላቻ በሷ እጅ የህክምና አገልግሎት ከማግኘት ቢቀር የሚሻል መሆኑን የሚጠቁም በመሆኑ ብዙም ልከራከራት አልፈለኩም፡፡ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ ሌሎች ሀላፊዎች ወደጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲወስዱኝ ብጠይቅም “ቀጠሮ የለሽም” በሚል ሰበብ ሳይወስዱብኝ ቀሩ፡፡ በአሁኑ ወቅት የቀኝ ጡቴም ተመሳሳይ እጢ ያለበት በመሆኑ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ቀዶጥገና አደርግ ዘንድ የላከኝ ቢሆንም (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በእድሳት ላይ በመሆኑ)እጅግ የከፋ ህመም ካልታመምኩ በቀር ቃሊቲ ሆኜ ቀዶጥገና ማድረጉን አልፈለኩም፡፡ በመሆኑም አልፎ አልፎ የሚሰማኝን ህመም በህመም ማስታገሻ መድሀኒቶች በማቃለል የቃሊቲን አስቀያሚ ቀኖች በመግፋት ላይ እገኛለሁ፡፡
ሌላዉ የቃሊቲ ቆይታዬን በተመለከተ ልጠቅሰዉ የምፈልገዉ ጉዳይ ከመንግስት አካላትና ከተለጣፊዎቻቸዉ ጋር ካለፍላጎቴ እንድንገናኝ እየተደረገ የሚፈፀምብኝ የሰብአዊ መብት ረገጣ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ያህልአንዱን ብቻ ልጥቀስ፡፡ አምና መጋቢት ወር ዉስጥ አምባሳደር ጥሩነህ ዜናን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መምጣታቸዉን የገለፁ ሌሎች አስር ሰዎች ከአመት በፊት ወደገባሁበትና ከሌሎች ከአራት ሰዎች ጋር ብቻ ወደምኖርበት ክፍል መጡ፡፡ እኔም ኮሚሽኑ በተለይም ደግሞ አምባሳደሩ የሰብአዊ መብት አከባበርን አስመልክቶ የሚሰጧቸዉ ከእዉነት የራቁ መግለጫዎች የሚያሳዝኑኝ በመሆኑ ለመነጋገር ፍቃደኛ አለመሆኔን በማስታወቅ ከክፍሉ ወጥቼ በሩ ላይ ቆምኩ፡፡ ከሰዎች አንዱ የምኖርበትን ክፍልና አልጋዎቻችንን ፎቶ ሲያነሳ ተመለከትኩ፡፡ ገረመኝ፤ መሬት አንጥፌ ስተኛ፣በተደራራቢ አልጋ የላኛዉ ክፍል ላይ ከጡት ህመም ጋር እየታገልኩ ስተኛና በተፋፈገ ክፍል ዉስጥ ስኖር ለምን የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ፎቶ አላነሳም? ማረሚያ ቤቱ በጥሩ ሁኔታ እስረኞቹን የያዘ መሆኑን ማሳያ ለማድረግ እንደተፈለገ ገመትኩ፡፡ እዉነታዉ ግን ይቺ ያለሁባት በቆርቆሮ የተሰራች ክፍልና ጠባቧ ግቢ አምና መስከረም ላይ በጠያቂዎች የመጎብኘት መብቴ መጣሱን ተከትሎ በጥድፊያ የተዘጋጀች ማግለያ ቦታ መሆኗ ነዉ፡፡ ክፍሉን ብቻ ፎቶ አንስተዉ መሄዳቸዉ ያላረካቸዉ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰዎች በማግስቱ አራት ሆነዉ መጡ፡፡ ሁለቱ ወደግቢዉ ዉስጥ ሲገቡ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ በሩጋ ቆሙ፡፡ ግቢዉ ዉስጥ ከገቡት አንዱ ትላንት ለምን ላናግራቸዉ እንዳልፈለኩ ጠይቆኝ በድጋሚ ከነሱ ጋር መነጋገር ያልፈለኩበትን ምክንያት እያስረዳኋቸዉ እያለ የግቢዉ በር ክፍት ስለነበር ግቢዉ በርጋ ከቆሙት አንዱ ፎቶ ሊያነሳኝ ሲሞክር ለመመልከት ቻልኩ፡፡ ምስሌን አንስቶ ቢሆንና ስለኔ አንዳች አይነት ዉሽት ሲናገሩ ብሰማ ጉዳዩን በዝምታ እነደማላልፈዉ ነገርኩትና ወደቤት ዉስጥ ገብቼ በሩን ዘጋሁት፡፡
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ከክፍሉ ወጥቼ ኢህአዴግ ማሰሩ ሳይበቃዉ ሰብአዊ መብትን ለማስከበር እንዳቋቋማቸዉ በሚናገረዉ ተለጣፊ ድርጅቶቹ ሳይቀር ሰብአዊ መብቴን ለምን እንደሚጥስ ከሀላፊዎቹ አንዷን በማስጠራት ጥያቄ አቀረብኩላት እሷም ሰዎቹ ካሜራ መያዛቸዉን እንደማታዉቅ ነገረችኝ፡፡ በ2005ዓ.ም ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግኑኝነት ክፍል እኔን ለማናገር እንደመጣ የገለፀልኝ ሰዉ ኮቱ ዉስጥ ደብቆ በያዘዉ ሪከርደር ድምፄን ለመቅረፅ ሲሞክር ደርሼበት ይህንን ማድረግ የሚችለዉ የግል ፕሬስም ተገኝቶ ንግግራችንን የሚቀርፅ ከሆነ ብቻ መሆኑን ነግሬዉ ነበር፡፡ ይሄንን ያልኩበት ምክንያት የግል ፕሬሱ ባልተገኘበት ለመንግስት ሚዲያዎች ብቻ አስተያየታቸዉን የሰጡ ግለሰቦች ሀሳባቸዉ ተቆርጦና ተቀጥሎ ለማለት ያልፈለጉት ይዘት ይዞ እንደሚቀርብ አዉቅ ስለነበር ነዉ፡፡ የተናገርኩትን ሙሉዉን ነገር ቀርፀዉ ሊያወጡልኝ የሚችሉ አካላት በሌሉበት ለሰዉዬዉ አስተያየቴን መስጠት ያለፈለኩትም ይኸዉ እንዳይደርስብኝ በመስጋት ነበር፡፡ አስገራሚዉ ነገር ይቺ የኮሚሽኑ ሰዎች ካሜራ መያዛቸዉን እንደማይታወቅ የገለፀችልኝ ሀላፊ ያኔም የሰዉየዉን የድምፅ ሪከርደር መያዝ በተመለከተ ላቀረብኩላት ጥያቄ የሰጠችኝ ተመሳሳይ መልስ ነበር፡፡
የቃሊቲ ጉድ ማብቂያ ስለሌለዉ አንድ የመጨረሻ ጉዳይ ላንሳና የፅሁፌ መነሻ ወደሆነዉ የአመክሮ ጉዳይ አልፋለሁ፡፡ ዉድ አንባቢያን በሀገሪቱ ዉስጥ ያሉ የትኞቹንም እስረኞች አያያዝ የተመለከቱ ህጎችን፣ አዋጆችን፣ ደንቦችንም ሆኑ መመሪያዎችን በጣሰ ሁኔታ ከወላጆቼ በቀር ጠበቃን ጨምሮ በሌላ በማንም ሰዉ የመጎብኘት መብቴን ከተነጠቅኩ አመት ከኣራት ወራት አልፎኛል፡፡ አዛዉንት እናትና አባቴም ከእርጅና፣ ህመምና ድካም ጋር እየታገሉ የቃሊቲን ፈታኝ መንገድ መዉጣትና መዉረዳቸዉን ቀጥለዋል፡፡
ነገረ አመክሮ
ያለፈዉ አመት ነሐሴ ስምንት ቀን ከሰአት በኋላ ወደ ጠበቃ ክፍል ሃላፊዋ ቢሮ በአንዲት ፖሊስ ተጠርቼ ተወሰድኩ፡፡ እዚያም ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዋናዉ መስሪያ ቤት የይቅርታና የአመክሮ ጉዳይ ክፍል እንደመጣና ኮማንደር አስቻላዉ እንደሚባል ከነገረኝ ሰዉ ጋር ተገናኘሁ፡፡ ኮማንደሩ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ያቀረበልኝ የመጀመሪያዉ ጥቃቄ “ይቅርታ ለምን አልጠየቅሽም? ይቅርታ በመጠየቅ ላይ ያለሽ ሀሳብስ አልተቀየረም ወይ?” የሚል ነበር፡፡ ይቅርታ ያልጠየኩት ስላላጠፋሁና የተፀፀትኩበት ጉዳይ ስለሌለ በመሆኑና አሁንም ምንም የተቀየረ አቋም እንደሌለኝ አስረዳሁተ፡፡ “ይሄ የፍርድቤት ጉዳይ ነዉ፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ እስካለሽ ድረስ ወደዚያ መመለስ አይኖርብንም” አለኝ፡፡ እኔም አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት እንዳሻዉ የሚያሽከረክረዉ ፍርድቤት በንፁሃን ላይ የጥፋተኝነት ዉሳኔና ፍርድ ማስተላለፉን አሜን ብዬ ይቅርታ የምጠይቅበት ምንም አይነት ምክንያት እንደሌለ ገለፅኩለት፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ያህል ስለጤንነቴና በጊቢዉ ዉስጥ ስለሚያጋጥሙኝ ችግሮች በተመለከተ ጥያዎችን ስያቀርብልኝ ቆየና ወደ መጣበት ሌላዉ ዋና ጉዳይ ተመለሰ፡፡
“ቅድም ይቅርታ የማልጠይቀዉ ስላልተፀፀትኩ ነዉ ብለሻል፡፡ አመክሮ እኮ የሚሰጠዉ ለተፀፀተ ሰዉ ነዉና እንዴት ልታደርጊ ነዉ?” በማለት ስለ በአመክሮ የመፈታት አካሄድ አንዳንድ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ደንቦችን ጭምር በመጥቀስ ሊያብራራልኝ ሞከረ፡፡ “ታዲያ እንዲህ ከሆነ በይቅርታና በአመክሮ መሀል ምንም አይነት መሰረታዊ ልዩነት የለም ማለት ነዋ?” ለሚለዉ ጥያቄ ቀጥታ መልስ ሊሰጠኝ አልፈለገም ይልቁኑ ሁሉም ታራሚ 2/3ኛዉን የእስር ቅጣቱን ለመፈፀም ሁለት ወራት ገደማ ሲቀሩት እንደታረመና እንደተፀፀተ የሚገልፅ ፎርም መሙላት ስለሚኖርበት እኔም ለመፈታት ከፈለኩ ይህንኑ ማድረግ እንደሚጠበቅብኝ አስረግጦ ነገረኝ፡፡ የፃፍኩት የማምንበትንና መቼም ልቆምለት የምችለዉ እዉነት መሆኑን፣ በዚህ የተነሳ አሸባሪ መባሌ ደግሞ የበለጠ ኢህአዴግን እንድታገለዉ የሚየደርገኝ እንጂ የሚያፀፅተኝ ባለመሆኑ እንዲህ አይነቱን ከማንነቴ ጋር የሚቃረን ፎርም እንደማልሞላ አስረግጬ ነገርኩት፡፡ ኮማንደሩም ላልታረመና ለልተፀፀተ ሰዉ አመክሮ መስጠት ለእነሱም እንደሚከብዳቸዉ ከገለጸልኝ በኋላ “እኛ ፎርሙን ብንሞላልሽስ?” የሚል አስገራሚ ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ እኔ “ታርሜያለሁ” እንዳልኩ ተደርጎ ምንም አይነት ነገር ቢደረግ ሀሰት መሆኑን ከማጋለጥ ወደኋላ እንደማልል አስታወቅኩት፡፡ በዚህ አይነት ተመሳሳይ ሀሳቦች ላይ እየተሸከረከርን ጥቂት ጊዜ ከፈጀን በኋላ እንዳሰብበት አሳስቦኝ ተለያየን፡፡
ይህ ከሆነ ሀሁለት ወራት በኋላ የመፈቻዬ ቀን የነበረዉ ጥቅምት 14/2007 ማለፊን ተከትሎ “የአመክሮ ፎርሙን ለምን አትሞይም?” የሚል ጥያቄ ከተለያዩ ሀላፊዎች ይቀርብልኝ ጀመረ፡፡ ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ ጥያቄዉ እየጨመረ መጣ፡፡ በተለይ በመጨረሻዎቹ የህዳር ወር ቀናት በአንዱ አራት ሆነዉ ክፍሌ ድረስ በመምጣት አነጋገሩኝ፡፡ ለኮማንደሩ የሰጠሁትን ምላሽ ሰጠኋቸዉ፡፡ የሃለፊዎቹ ሁኔታ ከሁለት አመት በፊት የሆነዉን አስታወሰኝ፡፡ ያኔም የይቅርታ ፎርም ለመሙላት ፍቃደኛ ሳልሆን በመቅረቴ እንዳሁኑ ሰላማዊ በሆነ መልኩ ፎርሙን እሞላ ዘንድ ይጠይቁኝ ነበር፡፡ በእንቢታዬ ስፀና ግን የተለያዩና አብዛኛዎቹም እስከዛሬ የዘለቁ የመብት ጥሰቶችን ይፈፅመብኝ ጀመር፡፡ ያሁኑስ እምቢታዬ ምን ያስከትል ይሆን? አላዉቅም፡፡ አንድ ነገር ግን አዉቃለሁ፡፡ መታረምና መፀፀት ያለብን ኢህአዴግ በሀገር ላይ የሚያደርሰዉን ጥፋት በመቃወማችን ምክንያት የታሰርን እኛ ሳንሆን አምባገነኑ መንግስት መሆኑን!
ዉድ አንባቢያን በመጨረሻ ሰብአዊ መብቶች የተከበሩባት ኢትዮጰያን ለማየት እንዲያበቃን እየተመኘሁ፣ ለተግባራዊነቱም የምችለዉን ሁሉ እንደማደርግና እንደምከፍል ቃል እየገባሁ እሰናበታችኋለሁ፡፡ “ምን ልታደርጊ ትችያለሽ?” የምትሉኝ ካላችሁ መልሴ የሚሆነዉ ማን እንደተናገረዉ ባላስታዉስም “የፍቅር አብዮት” የተሰኘ መጸሀፍ ሳነብ ያገኘሁት አንድ አባባል ነዉ ፡፡
” ሁሉን ማድረግ አልችልም ሁሉን ማድረግ አለመቻሌ ግን የምችለዉን ከማድረግ ወደ ኋላ አያስቀረኝም”
ርዕዮት አለሙ
ከቃሊቲ እስር ቤት

Wednesday, January 7, 2015

ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!

January7,2015
በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፓሊስ በእሁድ ታህሣሥ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አቅርቦት ነበር። ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ብዛት ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑ አቶ አንዳርጋቸው ምን ተጠይቆ ምን እንደመለሰ ማወቅ አይቻልም። ስለሆነም በንግግሩ ይዘት ላይ አስተያየት መስጠት ይናገረው አይናገረው በአልታወቀ ጉዳይ ማብራሪያ መስጠት ይሆናል።  ስለዚህም፣ በንግግሩ ይዘት ላይ ጊዜ ከማጥፋት ህወሓት አንዳርጋቸው ጽጌን አሁን ማቅረብ ለምን እንደፈለገ መተንተን ይበልጥ ጠቀሜታ  አለው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል።
አሁን ህወሓት በውስጥም በውጭም ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባበት ጊዜ ነው፤ በራሱ በድርጅቱ ውስጥም ሰላም የለም። ህወሓት የትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ስር እንደሆነ አድርጎ በመቁጠር መላዋን ኢትዮጵያን ለመዝረፍና ለማጥቃት እንደ መንደርደሪያ፤ በሌላኛው የኢትዮጵያ ክፍል ተቃውሞ ሲበዛበት ደግሞ እንደ መደበቂያ ዋሻ ሲጠቀምበት የነበረው ጊዜ አብቅቶ የትግራይ ሕዝብ በህወሓት ላይ ማመጹ በግልጽ በተግባር እየታየ ነው። በርካታ የትግራይ ልጆች በህወሓት ላይ ነፍጥ አንስተዋል፤ ከፊሎቹ ደግሞ በሰላማዊ ትግል ህወሓትን ማስወገድ ይቻላል ብለው በክልላቸውም ከክልላቸውም ውጭ ከህወሓት ጋር ፍልሚያ ገጥመዋል። ህወሓት መሠረቴ ነው ከሚለው የትግራይ ክልል ፈጽሞ ሊነቀል የሚችል መሆኑ ግልጽ ምልክቶች እየታዩ ነው። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ከትግራይና ከተቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያገናኘው የአማርኛና የትግርኛ የቴሌቪዥን ፕሮግራም መጀመሩ የህወሓት ሹማምንትን ናላ ያዞረ እርምጃ ሆኗል።
የህወሓት ሌላው መተማመኛው የጦር ሠራዊቱ ነበር። ህወሓት፣ የኢትዮጵያን መከላከያ ጦር ሠራዊት ዘረኛ በሆነ መንገድ አደራጅቶ፤ ከፍተኛ አመራሩን በታማኝ አባላቱ ሞልቶ ተደላድሎ  የተቀመጠ መስሎ  ታይቶ ነበር። አሁን ግን ይህም ምስል አሳሳች እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን ህወሓትን የማገልገል ፍላጎት የሌላቸው መሆኑን፤ እንዲያውም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን በመቆም የህወሓትን ውድቀት ለማፋጠን ያላቸውን ጉጉት በግልጽ እያሳዩ ነው። አየር ኃይል ውስጥ ያለው ተቃውሞ ገሀድ የወጣ  ዜና ሆኗል። እንደ አየር ኃይል ገሀድ የወጣ ዜና አይሁን እንጂ በሌሎችም የሠራዊቱ ክንፎች ያለው አመጽ ተመሳሳይ የጡዘት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ብአዴን እና ኦህዴድ ውስጥ ለአገራቸው ለኢትዮጵያ፣ እንወክለዋለን ለሚሉት ሕዝብ እና ለራሳቸው ክብር ያላቸው አባላት ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ብአዴንንና ኦህዴድ እንደ ድሮ ፍጽም ታማኝ አገልጋዮች የመሆናቸው ጊዜ እያበቃ ነው። ደኢህዴንም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የሚታመን አይደለም። ጊዜው ለህወሓት እጅግ የመክፋቱ ምልክት ደግሞ እራሱ ህወሓት ውስጥም ስምምነት የሌለ መሆኑ ነው። ህወሓት ይይዘው ይጨብጠው ጠፍቶታል።
ለዓመታት የዘለቀው የሙስሊም ወገኖቻችን ተቃውሞ እረፍት ነስቶት እያለ በባህርዳር የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ተቃውሞ ተጨመረበት። የአምቦውን ተቃውሞ አዳፈንኩ ሲል የጎንደር ተቀሰቀሰበት። ለጉራና ለሀብት ዘረፋ ሲል ያስጀመረው  የአባይ ግድብ፣ ጥበቃው ብቻ እንኳን ፋታ የሚነሳ ሥራ ሆነበት። ጋምቤላ፣ አፋርና፣ ሶማሊ የግጭት ቀጠናዎች ከሆኑ ዓመታት አስቆጠሩ።
ከላይ የተዘረዘሩት ጉምጉምታዎች፣ ተቃውሞዎችና አመጾች ተቀናጅተው የመጡ ዕለት መድረሻ እንደሚያጣ የተገነዘበው ህወሓት ትኩረት ማስቀየሻ መፈለጉ ግድ ነበር። በግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እምነት በአሁኑ ሰዓት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ ሚዲያ መቅረብ ምክንያቱ ይህ ነው። አንዳርጋቸውን ወደሚዲያ በማቅረብ ትኩረትን የማስቀየስ ስትራቴጂ!
የፊልሙ ማጀቢያዎች የነበሩት የሂውማን ራይትስ ዎች ሪፓርት፣ ስለእንግሊዝ ጋዜጣ የተነገረው፣ አሜሪካ ስለምትፈጽመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት የተዘከረው፣ ወዘተ … ወዘተ የሚያመላክቱት አንድ አቢይ ሀቅ አለ። ይህም ኢትዮጵያዊያን ፀሐይና ብርድ ሳይበግራቸው “እኔ አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ” እያሉ በእንግሊዝ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች እና በአውሮፓ ኅብረት ሲያደርጓቸው የቆዩ ተቃውሞዎች ውጤታማ መሆናቸው ነው። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የፈጠሩት ጫና ወያኔን ወደ ተከላካይነት አውርዶት “እኔ ንፁህ፣ አሜሪካ ርኩስ” እንዲል አድርጎታል።  ወያኔ፣ ስለንፅህና ምስክርነትት ይሰጥልኛል ብሎ ተስፋ ያደረገው ደግሞ ራሱ ነፃነቱን ገፎ እስረኛው ያደረገው ሰው መሆኑ ጥረቱ እንደምን ውል አልባ እንደሆነበት ያሳያል። ንፅህናን ነፃ ባልሆነ ሰው ማስመስከር ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው? ይህ ክስተት፣ የኢትዮጵያዊያን ዘርፈ ብዙ ተቃውሞ የወያኔን የመከላከል አቅም ማዳከሙን በግልጽ ያሳያል። ይህ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብሥራት ነው።
ከላይ የተዘረዘሩት ምክንያቶች ህወሓት አንዳርጋቸውን ወደሚዲያ ለማቅረብ ምክንያት ይሁኑ እንጂ የአንዳርጋቸው ለሶስተኛ ጊዜ በወያኔ ቴሌቬዥን መታየት በኢትዮጵያዊያን ላይ የፈጠረው ስሜት ህወሓት ከጠበቀው ፈጽሞ የተለየ ነው።
ኢትዮጵያዊያን አንዳርጋቸውን ሲያዩ የሚታያቸው ጽናት፣ አርበኝነትና አልበገር ባይነት ነው። የአንዳርጋቸው ምስል በታየ ቁጥር ኢትዮጵያዊያን ፀጉራቸው ይቆማል፤ ደማቸው ይፈላል። ወያኔዎች አንዳርጋቸውን የፈለጉትን ቢያናግሩት ችግር የለም። ለጊዜው በእጃቸው ውስጥ ስለሆነ ያላለውን ያለ ሊያስመስሉ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል። ወደፊት ደግሞ ሊናገር ያልፈለገውን ያናግሩት ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚያመጣው ለውጥ የለም። አንዳርጋቸው ስለወያኔ ምንነትና ማንነት ማንም ሳያስገድደዉ በነፃነት አገር ዉስጥ በግልጽ ተናግሯል፣ አሁንም ወያኔዎች እራሳቸዉ በሰሩት ፊልም ዉስጥ እነሱ በማይገባቸው መንገድ ለኢትዮጵያን ሕዝብ ተናግሯል። እንኳንስ እነሱ እሱም ራሱ በማይገባው መንገድ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያዊያን ልብ ውስጥ ገብቷል። አንዳርጋቸውን ስናይ በህወሓት ፋሽስታዊ መዳፍ ውስጥ የወደቁብንን ጀግኖቻችንን ሁሉ ያስታውሰናል። በአስር ሺዎች ይቆጠራሉ። የአንዳርጋቸው ምስል ለግላጋ ወጣቶች፣ በሳል አዛውንት፣ ምርጥ ወንድሞችና እህቶች በወያኔ እስር ቤቶች ፍዳቸውን እያዩ መሆኑን ያስታውሰናል። ምስሉ ብቻውን ያናግረናል፣ ያነቃናል፣ ያነሳሳናል!!!
ግንቦት 7:  የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አንዳርጋቸው ጽጌን፣ በርካታ ጀግኖቻችንን፣እራሳችንንና አገራችንን ከወያኔ እስር ነፃ ለማውጣት ክንዳችንን እናበርታ፤ ሁላችንም “እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነን” እንበል፤ ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Tuesday, January 6, 2015

The people pushed out of Ethiopia’s fertile farmland

January 6, 2015
(BBC) The construction of a huge dam in Ethiopia and the introduction of large-scale agricultural businesses has been controversial – finding out what local people think can be hard, but with the help of a bottle of rum nothing is impossible.The construction of a huge dam in Ethiopia
After waiting several weeks for letters of permission from various Ethiopian ministries, I begin my road trip into the country’s southern lowlands.
I want to investigate the government’s controversial plan to take over vast swathes of ancestral land, home to around 100,000 indigenous pastoralists, and turn it into a major centre for commercial agriculture, where foreign agribusinesses and government plantations would raise cash crops such as sugar and palm oil.
After driving 800km (497 miles) over two days through Ethiopia’s lush highlands I begin my descent into the lower Omo valley. Here, where palaeontologists have discovered some of the oldest human remains on earth, some ancient ways of life cling on.
Some tourists can be found here seeking a glimpse of an Africa that lives in their imagination. But the government’s plan to “modernise” this so-called “backward” area has made it inaccessible for journalists.
As my jeep bounces down into the valley, I watch as people decorated in white body paint and clad in elaborate jewellery made from feathers and cow horn herd their cows down the dusty track.
I arrive late in the afternoon at a village I won’t name, hoping to speak to some Mursi people – a group of around 7,000 famous for wearing huge ornamental clay lip plates.
The Mursi way of life is in jeopardy. They are being resettled to make way for a major sugar plantation on their ancestral land – so ending their tradition of cattle herding.
Meanwhile, a massive new dam upstream will reduce the Omo River, ending its seasonal flood – and the food crops they grow on its banks.
It is without doubt one of the most sensitive stories in Ethiopia and one the government is keen to suppress.
Human rights groups have repeatedly criticised schemes like this, alleging that locals are being abused and coerced into compliance.
I’d spoken to local senior officials in the provincial capital of Jinka, before travelling into the remote savannah.
The suspicion is palpable as the chief of the south Omo zone lectures me. Local people and the area’s reputation have been greatly harmed by the negative reports by foreigners, he says.
Eventually a frank exchange takes place and I secure verbal permission to report on the changes taking place in the valley. Read more…

ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ዝዋይ የታሰሩ 16 የፖለቲካ እስረኞች ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ

January6,2015
• የሰማያዊ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ እንዳይጠይቁ ተከልክለዋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ በዝዋይ የፌደራል ማረሚያ ቤት ታስረው የሚገኙ 16 የፖለቲካ እስረኞች ባልታወቀ ምክንያት ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው ተከለከሉ፡፡
ዛሬ ታህሳስ 28/2007 ዓ.ም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ም/ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ የገናን ዋዜማ ዝዋይ ከሚገኙ እስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ዝዋይ አቅንተው የነበር ቢሆንም ሊጠይቋቸው ያስጠሯቸው የፖለቲካ እስረኞች ‹‹በማንኛውም አይነት ሰው መጠየቅ አይችሉም፡፡ ምግብም አይገባላቸውም፡፡›› ተብለው ሳይጠይቁ ለመመለስ ተገደዋል፡፡
ጠያቂዎቹ ‹‹የመጠየቅ መብት አለን›› በሚል ወደ ውስጥ ለመግባት ግፊት በማድረጋቸው ፖሊሶች ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ አበበ ቀስቶ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ ጄኔራል አሳምነው ጽጌና ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጨምሮ ጠያቂና ምግብ እንዳይገባላቸው የተከለከሉትን የ16 የፖለቲካ እስረኞችን ስም ዝርዝር አሳይተዋቸዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ባልደረባ ለእስረኞቹ ምግብና ጠያቂ እንዳይገባ የተከለከለበትን ምክንያት ለማጣራት ቢሞክሩም ፖሊሶች ‹‹የሚጣራ ነገር ስላለ ነው፡፡ እሱ እየተጣራ ነው፡፡›› ከማለት ውጭ ምክንያቱን በግልጽ ሊነግሯቸው አልቻሉም፡፡
ክልከላው እስከመቼ እንደሚቆይ በውል የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን ከአዲስ አበባ ተነስቶ የገናን በዓል ዋዜማ ከእስረኞቹ ጋር ለማሳለፍ ወደ ዝዋይ ካቀናው የሰማያዊ ፓርቲ ልዑክ በተጨማሪ የእስረኞቹ ቤተሰቦችም በክልከላው ምክንያት ሳይጠይቁና ምግብ ሳያስገቡ ተመልሰዋለል፡፡

Monday, January 5, 2015

አቃቤ ህግ በጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ላይ የቀረበውን ክስ እንዲያሻሽል በድጋሜ ታዘዘ

January5,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ዛሬ ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓ.ም ለ14ኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ቀደም ብሎ የቀረበውን የክስ ማሻሻያ በተመለከተ ብይን ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ የተሰየመው ቀደም ብሎ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ እንዲሻሻል ባዘዘው መሰረት የፌደራል አቃቤ ህግ ክሱን ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት አሻሽሏል ወይስ አላሻሻለም በሚለው ጉዳይ ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የተከሳሽ ጠበቆች ተሻሻለ የተባለው ክስ በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መሰረት አለመሻሻሉን ያቀረቡትን አቤቱታ እና አቃቤ ህግ ይህንኑ አቤቱታ በተመለከተ የሰጠውን መልስ አገናዝቦ የሰጠውን ብይን በንባብ አሰምቷል፡፡
በመሆኑም አቃቤ ህግ ተከሳሾች በጸረ ሽብር አዋጁ ላይ ከተመለከቱት የሽብር ተግባራት የትኞቹን ፈጸሙ የሚለው በክሱ ላይ አልተጠቀሰም በተባለው ጉዳይ ላይ ያቀረበውን ማሻሻያ እና ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹ የ‹ሽብር› ድርጊት ግብና ስትራቴጂን አስመልክቶ በግልጽ ተብራርቶ ክሱ እንዲሻሻል ተሰጥቶት የነበረውን ትዕዛዝ በተመለከተ በማሻሻያው ላይ የቀረበው በቂ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ እነዚህን ፍሬ ነገሮች እንደተሻሻሉ አድርጎ ተቀብሎታል፡፡
በቀሪዎቹ ነጥቦች ላይ አቃቤ ህግ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ማሻሻያውን አለማድረጉን ፍርድ ቤቱ በብይኑ ላይ አመልክቷል፡፡ በተለይም ይሻሻሉ ተብለው ትዕዛዝ በተሰጠባቸው አራት ነጥቦች ላይ፣ ማለትም በተከሳሾች ተመሰረተ የተባለውን ድርጅት (ቡድን) ከተቻለ በስም በመግለጽ ወይም ከሌሎች ድርጅቶች (ቡድኖች) ለይቶ እንዲገልጽ፣ የእያንዳንዱን ተከሳሽ የውስጥ የስራ ክፍፍል ለይቶ እንዲያመለክት፣ ተከሳሾች በተከሰሱበት ጉዳይ ወሰዱ ተብሎ በክሱ የተጠቀሰው ስልጠና በማን፣ የትና መቼ እንደተሰጠ ተለይቶና ተገልጾ ክሱ እንዲሻሻል፣ እንዲሁም ለአመጽ ተግባር እንዲውል ውጭ ሀገር ከሚገኙ ገንዘብ (48 000 ብር) ተላከ የተባለውን ገንዘብ በተመለከተ፣ ገንዘቡ ከማን እንደተላከና ለምን ዓላማ እንደዋለ ተገልጾ ክሱ እንዲሻሻል የሚሉት ፍሬ ነገሮች በትዕዛዙ መሰረት አለመሻሻላቸውን ፍርድ ቤቱ በብይኑ አመልክቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ እንዲሻሻሉ ትዕዛዝ ከሰጠባቸው ነጥቦች መካከል አብዛኞቹ በአቃቤ ህግ አለማሻሻላቸውን በብይኑ ላይ አስፍሯል፡፡ ስለሆነም አቃቤ ህግ ያልተሻሻሉ ነጥቦችን አሻሽሎ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ለጥር 6 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Friday, January 2, 2015

የወያኔ ከንቱ ፈሊጥ! “ጅብን ሲወጉ በአሕያ ተጠግቶ ነው”

January2,2015
(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
cart
ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ጅብ እንደሆነ አድርጎ ያስባል፡፡ ይታያቹህ! ከየትኛውም ሀገር ሕዝብ በተለየ መልኩ ታጋሹን፣ ቅኑን፣ ቅዱሱን፣ ስስት ስግብግብነት የሌለበትን፣ አስተዋዩን፣ እሱ እየተቸገረ እየተራበ እነሱን ያጠገበውን ያደለበውን ቸር ምስኪን ሕዝብ ጅብ ነው ብሎ ማሰቡ አይደንቃቹህም? ምን ይደረግ ድንቁርና ተጭኗቸው ይሄን አስከፊ ድንቁርናቸውን ገንዘባችን ብለው አጥብቀው ይዘውት በየት በኩል አስተውለው ይሄንን ማንነቱን ይረዱለት? እናም ጅብ ነው ብለው በማሰባቸው አሕያ እየፈለጉ እሱን በመጠጋት በእሱ በመከለል ሲዎጉት ቆይተዋ ሰሞኑንም በሰፊው ይሄንን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
ወያኔ በዚህ በያዝነው በታሕሳስ ወር 2007ዓ.ም. ከታዋቂ ሰዎችና “ከከያኔያን (Artists)” ለ ሕዝብ ለሕዝብ አቅንኦተ ግንኙነት (Public diplomacy) እና ሕዝብን ለመደለል ተልእኮ በቻለው መጠን እሽ ያሉትን ከያሉበት ሰብስቦ ሁለት ቡድን አዋቅሮ አንዱን ወደ ግብጽ አንዱን ደግሞ የሕወሀት መሪዎች ለትግል አነሣስቶ ወኔ ከሰነቀላቸው ከኢሐፓ እየተነጠሉ ወጥተው ሕወሀትን የመሠረቱበትን 40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓላቸውን ምክንያት በማድረግ “የትግራይ ሕዝብ ትግል” ሲሉ በሐሰት የሚጠሩትን ትግል ለመዘከር ወደ ደደቢት በረሀ ልኮ ወይም ሰዶ ነበር፡፡
በእርግጥ ግን ይሄ የሕወሀት ስኬት የትግራይ ሕዝብ አስተዋጽኦ ብቻ ነው? ወያኔዎች እየዋሹና የማይፈጽሙትን ወይም ያልፈጸሙትን ቃል እየገቡ የአማራ ገበሬዎችን አታለው ስንቅ ከመስፈር መረጃ እስከማቀበል፣ ፊት ለፊት እንዲጋፈጡ ተደርገው የመጀመሪያውን ጥይት ቀማሽ እንዲሆኑ ፈንጅ ማምከኛ እንዲሆኑ የተደረጉ ልጆቹን አብረው እንዲታገሉ ከመስጠት እስከ በጉልበቱ በገንዘቡ መደገፍ ከዚያም አልፎ በደርግ ሠራዊት ላይ ፊቱን በማዞርና በመውጋት ሁለንተናዊ ድጋፍ ከአማራ ገበሬ ባያገኙና የአማራ ገበሬ እንደ ጠላት ቢያያቸው ባያቀርባቸው ባያምናቸው ባይደግፋቸው ኖሮ ተከዜን አይሻገሩ እንደነበር ጠንቅቀው እያወቁ እዚህ ለመድረሳቸው ተመስጋኙ ተወዳሹ የትግራይን ሕዝብ ብቻ ሲያደርጉ እንደሰው ውለታ ይዟቸው ትንሽ እንኳን ስቅጥጥ አይላቸውም፡፡
በተደጋጋሚ በቴሌቪዥን (በምርአየ ኩነት) እየቀረበ እንዳያቹህት የወያኔ ባለሥልጣናት ከአማራ ገበሬዎች ጋር ምን ያህል በቅርበት በአካል ገጽ ለገጽ እንደሚተዋወቁ፣ በትግል ወቅት ያደረጉላቸውን ውለታ እንዳይረሱና የገቡትንም ቃል እንዲፈጽሙ ሲጠይቁ ሲያሳስቡ በተገጋጋሚ ተመልክታቹሀል፡፡ እንግዲህ ትውውቃቸውና ቅርርባቸው የዚህን ያህል ነበር፡፡ እንዴት አድርገው አታለው ያንን ሁሉ ድጋፍ ያገኙ እንደነበር ይሄ በቂ መረጃ ይመስለኛል፡፡ እነሱ ግን ቃላቸውን ጠብቀው እናደርግልሀለን ይሉት የነበረውን ሊያደርጉለት ይቅርና ውለታውን ከመርሳትምና ከመካድም አልፈው ጭራሽም ሊያጠፉት በሰይጣናዊ ሸር ሌት ተቀን ያሴሩበታል ይዶልቱበታል በተግባርም ይፈጽሙበታል፡፡ እንዴ! ደግፈን ተዋግተን ለዚህ ያበቃነው ጭራሽ ሊያጠፋን ተነሣብን? ብሎ ተነሥቶ እንዳይቀብራቸውም ሀገሪቱን ከተቆጣጠሩ ማግስት ጀምሮ “እንግዲህ ሀገር ሰላም ሆኗል ለትንንሹ ነገርም እኔ አለሁ እኔ እጠብቃቹሀለሁ” እያለ በየጊዜው በዘመቻ መሣሪያውን አስፈትተው ወስደውበታል፡፡ መጨረሻ ላይም ደብቀህ ያስቀረኸው አለ እያሉ እየቀጠቀጡ ሥራ የሚሠራበት ገጀራ እንኳን ሳይቀር ሰብስበው ወስደውበታል፡፡ ይሄንን ካደረጉ በኋላ ነው እንግዲህ ምንም እንደማያመጣ ሲያውቁ አናቱ ላይ ፍጢጥ ብለው ሊጨማለቁበት በነፍስ በሥጋው ሊጫወቱበት የቻሉት፡፡ ታዲያ በምኑ ይውጋቸው? እንጅ የዋሁ ወገኔ እንዲህ መቀለጃ መጫወቻ ይሆን ነበር? ሽሩድነታቸውን አያቹህት? ግን ሰዎች ናቸው ትላላቹህ? እኔ እኮ ልቡሳነ ሥጋ አጋንንት እንጅ ሰዎች ናቸው ብየ አላምንም፡፡
ወያኔ በእነኝህ ሁለት ቡድኖች ያቀፋቸውን ሰዎች በተለይም በ “ከያኔያኑ” ቡድን በርካቶችን በተለይም ለወያኔ ባለማጎብደድ የሚታወቁትን ከያኔያን እነሱን ለፖለቲካዊ ዓላማው የሕዝብ ግንኙነት (Public relation) ትርፍ መጠቀሚያ ለማድረግ እንዲካተቱ ለማድረግ ያልፈነቀለው ድንጋይ ያላቀረበው የመደለያ ዓይነት ይሄም አልሆን ሲል ያልሞከረው የማስፈራሪያና ማዋከቢያ ዓይነት አልነበረም፡፡ የውርደቱ ውርደት በፊቱኑ ከጣላቸውና ካንበረከካቸው ካዋረዳቸው በስተቀር አዲስ ምርኮ አዲስ ሰለባ መጣል ሳይችል ቀርቷል፡፡ እነኝህን በሁለቱም ቡድን ያሰባሰባቸውን ግን የተለያየ መደለያና ጥቅማጥቅም በማቅረብ ደልሎ በእነዚህ ሁለት ቡድኖች አካቶ ለተልእኮው ተጠቅሞባቸዋል እየተጠቀመባቸውም ይገኛል ገናም ይጠቀምባቸዋል፡፡ አብዛኞቹም እንኳን ተጠይቀው በር እያንኳኩ በመልከስከስ የሚታወቁ በመሆናቸው ጭራሽ እንድች እንድች ዓይነት ነገር ስትኖርማ አጋጣሚውን ለመጠቀም እየተጋፉ እየተሸቀዳደሙ ከወያኔ እግር ስር በመልከስከስና ሕዝብን በማስጠቃት በማሳዘን የሚታወቁ በመሆናቸው እየተጋፉ እየተራኮቱ ነበር የታደሙት፡፡
ሕዝብ ለሕዝብ እንዲኖር ለሚፈለገው ዝምድና ለአቅንኦተ ግኑኝነት (diplomacy) ወደ ግብጽ ከተላከው ቡድን አንዷ ለምን እንደሔደች ስትናገር ምን አለች “መቸም በማንኛችንም ዘንድ የቱንም ያህል የፖለቲካና የአስተሳሰብ ልዩነት ቢኖርም በዐባይ ጉዳይ ላይ ግን አስተሳሰባችን አንድ በመሆኑና የተለየ አቋም ያለው ባለመኖሩ በዚህ መሠረት ነው የሔድኩት” ስትል ተናገረች፡፡ ሲጀመር ያለችው ነገር የተሳሳተ ነው፡፡ ነገሩን ለስሕተቷ እንዲመች ለማድረግ ካልሆነ በስተቀር ከተጨባጭ እውነታዎችና ሥጋቶች አንጻር የዐባይ ግድብ በወያኔ እጅ መገደቡን የማይፈልጉ የሚቃወሙ በርካታ ዜጎች እንዳሉ ይታወቃልና፡፡ አንዱም እኔ ነኝ፡፡
ታስታውሱ እንደሆን ከዓመት በፊት “በዘመነ ወያኔ ዐባይ ቢገደብ የነዳጅ ዘይት ቢገኝ ለሀገራችን በረከት ወይስ መርገም?” በሚል ርእስ ሰፊ ትንታኔና መረጃ የያዘ ጽሑፍ አቅርቤ ነበር፡፡ እስካሁን በወያኔ እጅ ከተሠሩ እንደ የመንገድ፣ የቴሌኮሚውኒኬሽን፣ የመብራት ኃይል አቅርቦትና ስርጭት የመሳሰሉት የመሠረተ ልማት ሥራዎች በሙስና ቡጥቦጣ ምክንያት አደገኛ አስደንጋጭና አሳሳቢ በግልጽ የሚታዩ ከባባድ የጥራት ችግሮች፣ የአቅም ውስንነት ሊፈጥረው ከሚችለው የጥራትና ተያያዥ ችግሮች፣ የወያኔ በተፈጥሮው ጠባብና ለኢትዮጵያ እንደ ኢትዮጵያነቷ ለሕዝቧም እንደሕዝብ ክብርና ፍቅር የሌለውና ይሄንንም ከበፊት ጀምሮ በተለያዩ የክህደት ድርጊቶቹ በተደጋጋሚ አድርጎት ያሳየ ያረጋገጠ ከመሆኑ እንዲህ ዓይነት የሀገር ፍቅር፣ ቁርጠኝነት፣ ጽናት፣ ትጋት፣ ንጽሕና፣ ቅንነት፣ ሕብረት፣ አንድነት፣ በሙሉ ተነሣሽነት ፈቃደኝነትና ወኔ የሕዝብን ፍላጎት እምነት አቅምና ድጋፍ መታጠቅን የሚፈልግንና የሚጠይቅን ግዙፍ የልማት ሥራ ቀርጾ የመገንባት ሞራላዊ (ቅስማዊ) እና መንፈሳዊ አቅምና ብቃት የሌለው በመሆኑ፣ በእንዲህ እንዲህ ዓይነት ችግሮች ተተብትቦ ግድቡ ቢጠናቀቅም “የሰብአዊ መብቶችን አክብር” ከሚል አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ጋር በሚያገኘው የእርዳታ ገንዘብ የዚህን ያህል ጨክኖብን የቀጠቀጠን የቀፈደደን የደቆሰን ያንገላታን የገደለን ያሳደደን አውሬና አንባገነን አገዛዝ ቅድመ ሁኔታ የሌለበትን የራሱን የገቢ ምንጪ ቢያገኝ በሀገርና በሕዝብ ላይ ሊፈጥረው ከሚችለው ጭንቅ ችግር አንጻር ግድቡ ተጠናቆ ገቢ ማስገኘት ቢጀምር የወያኔን ጨካኝ ጡንቻ አፈርጥሞ ሕዝብን ለከፋ አደጋ መዳረግ እንጅ ሀገርንና ሕዝቧን የሚጠቅም ባለመሆኑ በእነዚህና በሌሎችም ተጨባጭ ሥጋቶችና ችግሮች ምክንያት ይሄ በወያኔ እጅ እየተሠራ ያለ የግድብ ሥራ ሀገርንና ሕዝብን የሚጎዳ እንጅ በፍጹም የሚጠቅም ካለመሆኑ አንጻር የዚህን የግድብ ሥራ እንደማልደግፍ እንደምቃወም ገልጨ ነበር፡፡ አብዛኛው ሕዝባችንም በተለያዩ ነውሮቹ ምክንያት ፈጽሞ እምነት በማይጥልበት በወያኔ መሠራቱን በመቃወም ይሄንን የኔን ሥጋትና ሐሳብ የሚጋራ ነው፡፡
እነዚህ የሕዝብ ግንኙነት አቅኝ (Public diplomat) ተብየዎች ሻል ሻል ያለ ደረጃ ላይ እንደመገኘታቸው የጥቅም ነገር ሆኖባቸው ነው እንጅ ይሄ ይጠፋቸዋል ብየ አልገምትም ነገር ግን ተደልየ ነው ጥቅም ፈልጌ ነው ላለማለት “የፈለገውን ያህል ልዩነት ቢኖረንም ይሄንን የዐባይ ግድብ ሥራውን የሚቃወም የለም” በሚል ብልጠት መሰል የሐሰት ምክንያት ራሳቸውን ለመከለል ሞከሩ፡፡
ወደ ከያኔያኑ (አርቲስቶች) ስመለስ በእርግጥ ሰዎቹ የከያኔን ሰብእና የያዙ ባለመሆናቸው ማለትም “የቱንም ያህል ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆን ለእውነትና ለፍትሕ መረጋገጥ፣ ለሕዝብ መብቶች መጠበቅ፣ ለሀገር ጥቅሞችና እሴቶች መጠበቅና መከበር ጽናትን ታጥቀው በሥነ-ኪን ሥራዎች (በተውኔት፣ በሙዚቃ ወይም ዘፈን፣ በግጥም፣ በመጽሐፍ ድርሰት ወዘተ.) ታማኝና ጠበቃ የመሆንን ሰብእና የያዙ” ባለመሆናቸውና ለሆዳቸው ያደሩ እንደ እንስሳ ያለሆዳቸው ምንም ነገር የማያውቁ የማይታያቸው፣ ሕሊናቸውን የሸጡ፣ እራሳቸውን ያዋረዱ፣ ማሰብ የተሳናቸው፣ ምን ይሉኝን የማያውቁ፣ ያልበሰሉ እንጭጮች፣ ርካሾች፣ ነውረኞች፣ በመሆናቸው እነሱን ከያኔያን ብሎ መጥራት ቢከብድም ወይም የማይቻል ቢሆንም በዚያ አርቲስቶች (ከያኔያን) በተባለው ቡድን የተካተቱ ጥቂት ግለሰቦች በጉብኝታቸው መጨረሻ ላይ ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ከዚያች ቀን ጀምሮ ከሕወሀት ጎን መቆማችንን እናረጋግጣለን! በማለት ለሀገራቸውና ሕዝቧ ከወያኔ ጋር በማበር በጠላትነት መነሣታቸውን አረጋግጠዋ፡፡ እንደምገምተውም ወያኔ ከያኔያን ተብየዎችን ይሄንን ቃል እንዲገቡ ያደረጋቸው “እነሱ ካሉ ሕዝቡ ይሰማል” ከሚል የጅል ሐሳቡ በመጪው ምርጫ በካድሬነት ሕዝብን በመቀስቀስ እንዲያገለግሉት በማሰብ ነው፡፡ ከያኔያን ተብየዎቹ ይሄንን ያውቁ ይሆን? ወያኔ ይህ ድርጊቱ እንኳን ድጋፍ ሊያስገኝለት ሐዝብን ይባስ እንደሚያስቆጣ እልህ ውስጥ እንደሚከት የሚማር ጭንቅላት የለውም እንጅ ከዚህ ቀደም ሞክረው ካስከተለባቸው መጥፎ ውጤት መማር በቻሉ ነበር፡፡
አቶ ስብሐት ነጋም ትዕዛዝ አዘል በሆነ ቃል ከያኔያኑን “በጉብኝታቸው የተገለጸላቸውን የሕወሀትን ወይም የወያኔን ትግል ተግባር እንቅስቃሴ ዓላማ በጥበብ ሥራዎቻቸው እየገለጹ ለሕዝብ ማስተዋወቅ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል” ብለዋል፡፡ ከያኔያኑም ይሔንን እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ ችግሩ ለማን ነው የሚያቀርቡት? የሚለው ነው፡፡ ወይስ ወያኔ ሕዝቡን እያስገደደ አድምጡ ሊል ነው?
እዚህ ላይ አንድ ልንዘነጋው የማይገባን ነገር ቢኖር በዚህ ቡድን እንዲካተቱ የተደረጉ የቲያትር (ተውኔት) ቤቶች ሠራተኞች ከያኔያን የመንግሥት ሠራተኞች እንደመሆናቸው በዚህ ጉብኝት ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲል በተደረጉ ሌሎች ዝግጅቶችም በግዳጅ እንዲሳተፉ ሲደረግ ቆይተዋል፡፡ አንሳተፍም ያሉትን ደግሞ አገዛዙ የሥራ ዋስትናቸውን እንዲያጡ ወይም እንዲባረሩ ሲያደርጋቸው ቆይተቷል፡፡ ይሄ ችግር በእነሱ ብቻ ያለ አይደለም አጠቃላይ በመንግሥት ሠራተኛው ሁሉ እንጅ፡፡
ከዚህ አንጻር እነዚህ የቲያትር ቤቶች ሠራተኞች ይሄ ችግራቸው ግንዛቤ ውስጥ ሊገባላቸው የሚገባ ይመስለኛል፡፡ የፈለገው ይምጣ እራሴን አላረክስም በማለታቸው ተባረው ለችጋር የተዳረጉ ኩሩ ቆራጥ ባለ ሕሊና ጀግና ወገኖች እንዳሉ ሁሉ ልጆቸን ምን ላደርጋቸው ነው? እንዴትስ ብየ እኖራለሁ? ብለው አማራጭ ከማጣት አንጻር አጣብቂኝ ውስጥ የሚገቡ ሳይወዱ ሳይፈልጉ ሕሊናቸው ሳይፈቅድላቸው ውስጣቸው እየተቃጠለ እንባቸውን ወደ አምላካቸው እያፈሰሱ ችግር ላይ ላለመውደቅ የወያኔን ፈቃድ የሚፈጽሙ ወገኖቻችንም አሉ፡፡ ሁሉም ግን ማን ምን እንደሆነ ማለትም ተገዶ አማራጭ በማጣት እንዲያ ያደረገውንና አማራጭ ሳያጣ የሚበላው ሳያጣ ለማይሞላ ሆዱ ሲል እየተስበደበደ ወያኔ ከጠየቀውም በላይ የወያኔን ፈቃድ በመፈጸም ሕዝብን የሚያበግነው የሚያስጠቃውና ወያኔን የሚያገለግለው ማን እንደሆነ ከሕዝብ የተሠወረ አይደለምና በዚያ መልክ የሚታዩ ይሆናል፡፡ ይሄ እንግዲህ ነጻነቴን ክብሬን ሰብእናየን ሕሊናየን ማንነቴን የሚል ዜጋ ሁሉ የግድ የሚከፍለው ዋጋ ነው፡፡ ይሄንን ዋጋ እየከፈሉ ያሉ ወገኖች ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በእኔ ላይ የደረሰው የኑሮ መመሰቃቀልም አንዱ ማሳያ ነው፡፡ እስር እንግልት በደል ቢያጋጥምም ለችግር መዳረግ ቢከሰትም ሆድ ይራብ ይጠማል እንጅ ሕሊና ግን ይጠግባል ይረሰርሳል ይረካል ይለመልማል፡፡ እንደ እንስሳ ሆኘ ለሀገሬና ለሕዝቤ ጠላት ሆኘ በልቸ ሆዴ ከሚጠግብ ሰው የሰው ልጅነቴን አረጋግጨ ለሀገሬና ለሕዝቤ ህልውና እየታገልኩ ሆዴ ተርቦ ሕሊናየ ቢጠግብ ሽ ጊዜ እመርጣለሁ ስለሆነም አደረኩት፡፡ ቅንጣትም አልጸጸትም ከዚህም በላይ በቅርብ ጊዜ እንደሚደፉኝ ነግረውኛል ይሄም ቢሆን በሀገሬ በሕዝቤና በሃይማኖቴ ስም ለመቀበል ዝግጁ ነኝ፡፡ ሕዝቡ ቆርጦ እኔንና እኔን የመሰሉ ሰዎችን ቢመስልና መድፈር ቢችል ይደርስብኛል ብለን በየግል የምንፈራው ነገር አንዱም ሳይደርስብን እራሳችንን ነጻ ማውጣት በቻልን ነበር፡፡
እዚህ ላይ አንድ ሊነሣ የሚገባው ጥያቄ “ለመሆኑ ግን ወያኔ የመንግሥት መዋቅር በመጠቀም የመንግሥት ሠራተኞችን እያስገደደ የሕወሀትን ዓላማና ሥራን የማስፈጸም የማሠራት መብት አለው ወይ?” የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ መልሱ ቀላልና ግልጽ ነው ሕገ ወጥና ከአንባገነናዊ ማንነታቸው በመነሣት የሚፈጽሙት ግፍ ነው የሚለው ነው፡፡ ይሄንን እያደረጉት ያሉት የገዛ ሕገ መንግሥታቸውን በመጣስ በመጻረር በመተላለፍ ነው፡፡ ወያኔ በሕገ መንግሥቱ ሌላው ቀርቶ እንኳን በተቃውሞ እንቅስቃሴ ሳይሳተፉ ከተቃዋሚም ከወያኔም ሳይሆኑ ገለልተኛ ሆነው ይቅርና በተቃውሞው ጎራ ውስጥ ተሰልፈው የነቃ ተሳትፎ እያደረጉም እንኳን ቢሆን ያለአንዳች የሥራ ዋስትናን የማጣት ሥጋትና ችግር የመንግሥት ሥራቸውን በነጻነት እየሠሩ መኖር እንደሚችሉ አረጋግጦ ባለበት ሁኔታ ነው እንዲህ ዓይነቱን ሕገ ወጥና ነውረኛ ቆሻሻ ተግባር እየፈጸመ ያለው፡፡ የመንግሥት ሠራተኛው ይሄንን መብቱን እያወቀም ነው መብቱ ቢሆንም መብቱን ማስጠበቅ የሚችልበት ቁርጠኝነት ጽናት ሕብረትና አንድነት ስለሌለው መፍጠር ስላልቻለ ወያኔ እንደፈለገ እየተጨማለቀበት ያለው፡፡
ወገን ሆይ! ተዋርደሀል እኮ! ተንቀሀል እኮ! በቁምህ ቀብረውሀል እኮ! መቸ ነው በቃ! የምትለው? እየከፋ መጣብህ እንጅ እየተሻለ እየተማረ እየተመከረ እየሠለጠነ እኮ አይደለም የመጣው፡፡ ታግሰህ ያሳለፍከው ጊዜ የከፈልከው ዋጋ ሁሉ እኮ ምንም ጥቅም ፋይዳ ሳያስገኝልህ ከንቱ መሥዋዕትነት ሆኖ እኮ ነው የቀረው፡፡ ከዚህም በኋላ ልታገስ ብትል በመታገስ እየከፈልክ ያለውን ከንቱ መሥዋዕትነት የማይጠቅም ዋጋ ሕይዎትህን ያመረው ያከፋው ካልሆነ በቀር ምንም እኮ የሚጠቅምህ የሚረባህ የሚለውጥልህ ነገር የለም፡፡ ኧረ በቃ! በል? ኧረ ውርደትህ ይሰማህ? ኧረ መናቅህ ያንገብግብህ? የገዛ እንጀራህን እንዲህ ተዋርደህ ተንቀህ ተበሻቅጠህ እየተቃጠልክ እያረርክ ከወያኔ እጅ መብላት አለብህ እንዴ? ወያኔ እኮ የራስህን የሀገርህን ገንዘብ ሳይሆን ልክ ከኪሱ አውጥቶ በችሮታው እንደሚሰጥህ እንደሚከፍልህ አድርጎ እኮ ነው እንድታስብ ያደረገህ፡፡
ወያኔ በወረቀትና በብዙኃን መገናኛው ሌላ እያወራ በተግባር ግን ፍጹም የዚያን ተቃራኒ እየሠራ እንዲህ አድርጎ ሲጫወትብህ ዝም ብለህ ተንከርፍፈህ ታየዋለህ? ማንን ነው የምትጠብቀው? ማን ከየት መጥቶ ላንተ መሥዋዕትነት ከፍሎልህ ነጻ እንዲያወጣህ ነው የምትጠብቀው? ኧረ ተው ከከንቱና ባዶ ምኞትህ ውጣና ሕልምና ምኞትህን ተጨባጭ አድርገህ ለራስህ ደራሽ እራስህ መሆንህን አውቀህ በጊዜ አንድ ነገር አድርግና እፎይ በል? ተው በዘገየህ ቁጥር ነጻ ልትሆን የምትችልበትን ዕድል እያጠበብክ እንዳይቻል እያደረክ ነውና ያለኸው ከቶም ወደማትወጣው አዘቅት ውስጥ ጠልቀህ ከመግባትህ በፊት ሆ! ብለህ ተነሥና አሜከላህን ነቅለህ ጣለው? ራስህን ነጻ አውጣ? እየተሰደድክ ሳታልቅ በገዛ ሀገርህ ሆነህ ያገርህ የእንጀራህ ባለቤት ሁን? ነጻ ሆኖ በነጻነት ማሰብ፣ መናገር፣ መሥራት፣ መውጣት መግባት፣ እፎይ! ብሎ መተንፈስ አይናፍቅህም? እንደዚህ መሆን አያስጎመጅህም? ባርነት አልሰለቸህም? ያውም በወያኔ! ሥነ-ሥርዓት ሥነ-ምግባር ግብረ-ገብ በማያውቀው ባለጌ ስድ ቆሻሻ ነውረኛ ደንቆሮ ጠባብ ጎጠኛ ቡድን?
የሆነ ቦታ ላይ እንቢ ማለት ካልቻልክ እኮ የዘለዓለም ባሪያው ሆነህ መቅረትህ እኮ ነው! ለልጆችህ የተሻለች ሀገር የተሻለ ሕይዎት እንዲኖራቸው አትፈልግም? እየከፋ የሚሔደውን የዚህን ቆሻሻ ወራዳ አገዛዝ ልታወርሳቸው ነው የምትፈልገው? ኧረ እባክህ ተነሥ? ኧረ ስለምትወደው ነገር ሁሉ ብለህ መጫወቻ መቀለጃ አትሁን በቃ! በል???
እስኪ ከያኔያን (አርቲስቶች) እኛ ጋዜጠኛ ተብየዎች ይህችን ግጥም ተጋበዙልኝ ሊንኩን (ይዙን) ክፈቱ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

Thursday, January 1, 2015

ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

January1,2015
ኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡
ባጠቃላይ ላለፉት 23 አመታት ወያኔ ማድረግ የሚችለውን አስከፊ ነገር ሁሉ በሀገርና በህዝብ ላይ ሲፈፅም ቆይቷል፡፡ ዛሬ ከ23 አመ ታት በዃላ ሀገራችንና ህዝባችን ያልተዘፈቁበት የችግር ማጥ፤ ያልደረሰ የሀብትና የሰብአዊ ውድመት፤ ያልተፈፀመ የግፍና የሰቆቃ አይነት የለም፡፡ ወያኔ ይህን ሁሉ ሲፈፅም መሳሪያ አድርጎ ከተጠቀመባቸው ተቋማት ውስጥ ዋነኛዎቹ የመከላከያ፤ ፍርድ ቤትና የፖሊስና የደህንነት መሆናቸው ጥያቄ የለውም፡፡ የእነዚህ ተቋማት አባላት ከወያኔ ጥቃት ሰለባ ከመሆን ባይተርፉም የዚህን ወንጀለኛና ዘረኛ ቡድን እድሜ በአንድ ቀን በመጨመሩ ስራ ላይ ከፍተኛውን ድርሻ እንደያዙ ዛሬም መገኘታቸው አሌ የማይባል እውነት ነው፡፡ይህ ሲባል ግን በሀገርና በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ክህደት፤ ግፍና ሰቆቃ የሚያማቸው፤ መከራው መረራቸው፤ ብሶቱ ብሶታቸው የሆኑ አባላት የሉም ማለት እንዳልሆነ፤ ይልቁንም አብዛኛዎቹ የዚህ ስሌት ተካፋይ ስለመሆናቸው የሚጠራጠር የለም፡፡
ነገር ግን ከህዝብ አብራክ በወጡና ልጆቹን ሳይመግብ በከፈለው ታክስ በተደራጀ የመከላከያ፤ የፖሊስና የደህንነት ተቋማት ውስጥ የምትገኙ አብዛኛውና የግፉ ቀማሽ የሆናችሁ አባላት ዛሬ የምትገኙበት ሁኔታ እንደ አለፉት 23 አመታት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፤ ከዛሬ ነገ የተሻለን ነገር ተስፋ በማድረግ፤ በግርግሩ ፍርፋሪ ሊወድቅልኝ ይችላል ከሚል ራስ ወዳድነት…… ወዘተ በመሳሰሉ በርካታ ምክንያቶች ለፍትህ፤ ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ብሎም ለኢትዮጵያችን ቀጣይ ህልውና በሚደረጉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ላይ በመቆም ብሎም የጥቂት ዘረ ኛች ስልጣንና ምቾት እድሜ ለማራዘም የተጓዛችሁበት መንገድ ብዙም ማስኬድ ከማያስችልበት፤ ይልቁንም ዛሬ ከሁለት መንታ መንገድ የ ደረሳችሁበትና ቆም ብሎም ማየትና ማገናዘብን ከሚጠይቅ ወቅት ላይ ትገኛላችሁ፡፡ አንዱ በዘረኝነት በትር እየተወቀጡ የወያኔ ሎሌ ሆኖ መቀጠል፤ ሌላው ከህዝብ አብራክ የተገኛችሁ ናችሁና ከህዝብ ወገን ተቀላቅሎ ሀገርን፤ ወገንንና ራስን ነፃ ለማውጣት መነሳት..
ለመከላከያ ሰራዊት፦ ላለፉት 23 አመታት ከጠመንጃ ተሸካሚነት ላለፈ ለማይፈልጉህ፤ ለአንተነትህ መለኪያው እውቀትህ፤ ችሎታ ህና አገልግሎትህ ሳይሆን የተገኘህበት ዘውግ መስፈሪያህ ለሆነበት ዘረኛ ስርአት፤ መቀየሪያ መለያ ልብስ ተነፍጎህ ቀዳዳ እየጣፍክ የልጆችህን የረሀብ ልቅሶ እያዳመጥክ በአንተ ትከሻ በዘረፉት ሀብት የገነቧቸውን ህንፃዎች ጠባቂ ላደረጉህ፤ ፍትህ ነፃነት ሲል በተራበ አንጀታቸውና በደ ከመ ድምፃቸው በጠየቁ ወገኖችህ ላይ ይህ ቀረ የማይባል ግፍ ሲያ ስፈፅምህ ለቆየው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ዛሬም ተገቢውን ምላሽ የመስጠት እድሉ አለህ፡፡አልረፈደምና ተጠቀምበት!!!
የፖሊስ ሰራዊት አባላት፤- ፍትህ ላሉ ጥይትን፤ ነፃነት ላሉ የጭካኔ በትርን፤ ሀገሬን ላሉ ከጨለማ ዘብጥያ መወርወርን.. ዋነኛ ተግባርህ በሆነበት በዚህ ዘረኛና በወንጀል የተጨማለቀ ስርአት ውስጥ የቆየህበት ያለፉት 23 አመታት ለአንተም፤ ለቤተሰብህም፤ ለተገኘህበት ህብረ ተሰብ ሆነ ለሀገርህ የፈየደው አንዳች ነገር ያለመኖሩን ይበልጡኑ ከእሳት ወደ እረመጥ ከሆነው የወያኔ ጉዞ ራስህን አውጥተህ ከህዝባዊው ወገን የምትቀላቀልበት የመጨረሻው ሰአት መሆኑን ተገንዝበህ ምርጫህን ከወገንህ አድርግ፡፡ ለአንተም አልረፈደም!!
የደህንነት አባላት፦ ለሀገር ደህንነት ለህዝብ ሰላም ሲባል በህዝብ ሀብት በተደራጀ ተቋም ተጠቅመህ በሀገርህ ላይ ክህደትን፤ በወገ ንህ ላይ ግፍና ሰቆቃን ስትፈፅም መቆየትህ ከወንጀሎች ሁል የከፋ ወንጀል መሆኑን ተገንዝበህ ለፍትህ ለነ ፃነትና ለዲሞክራሲ ሲሉ በተነሱ ወገኖችህ ላይ ስትሰነዝር የቆየኸውን በትር በፍትህ በነፃነትና በዲሞክራሲ ላይ በቆሙት ዘ ረኛ አዛዦችህ ላይ የማሻው ጊዜ አሁን ነው፡፡ ስለ ዚህም ከህዝባዊው ወገን ተቀላቅለህ ህዝባዊ ወገንተኝነትህን የምታሳይበት ብሎም የበደልከውን የምትክስበት ጊዜውም እድሉ አለህና ተጠ ቀምበት፡፡ላንተም አልረፈደም!!
በመጨረሻም ልጇን የምትጠላ እናት፤ ወገኑን የሚገፋ ህዝብ፤ ዜጎቹን የማይቀበል ሀገር የለምና ይህን በአስከፊነቱ ወደር የማይገኝለት የወያኔ ዘረኛ ስርአት ደግፎ ማቆየት ከማይቻልበት ይበልጡንም እንደ ትሪፖሊና ኢያሪኮ የግፈኞች ግንብ በህዝባዊ ሀይል ከሚገረሰስበት ከ መጨረሻዋ ደቂቃ ከመደረሱ በፊት ከእናታችሁ እቅፍ ከወገናችሁ መሀል ግቡ!! ተቀላቀሉ!! ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባልና ጊዜ ሳታጠ ፉ ፈር ቀዳጅ ወንድሞቻችሁን መከተል ብልህነት ነው እንላለን!!!
የኢያሪኮም የጋዳፊም ግንብ ተንዷል፤ የወያኔም ይናዳል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

January 1,2015
መልዕክት ከቂሊንጦ እስር ቤት!
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
‹‹እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም›› አብርሃ ደስታ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)
Abrha Desta“እዚህ እስር ቤት ውስጥ በሽብር ስም የገባ ሰው በፈጠራ ወንጀል እንደገባ ነው የሚታመነው፡፡ ስለዚህ የሽበር ክስ ተመስርቶባቸው የታሰሩትን ሰዎች ማንም ወንጀለኛ አድርጎ አይመለከታቸውም፡፡ በእርግጥም አሸባሪ የለም፤ የፈጠራ ክስ ነው ያሳሰራቸው፡፡ አሸባሪ አለ ከተባለም እንደ ኢህአዴግ ያለ አሸባሪ የለም፡፡
ነጻ መውጣት ያለበት ቡድን አለ፣ እሱም ኢህአዴግ ራሱ ነው፡፡ እኔ አልታሰርኩም፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እስር የአዕምሮ ነው፡፡ እኔ አዕምሮየ አልታሰረም፡፡ ነጻ ሰው ነኝ፤ ውስጤ በጣም ነጻነት አለው፡፡ የታሰሩት ኢህአዴጎች ናቸው፡፡
እኔ እስር ቤት እንድገኝ ያደረገኝ ወንጀል አይደለም፡፡ መቃወሜና ይህን ተቃውሞየን በጽፍም በፊት ለፊትም መግለጼ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ብዙ ኢትዮጵያውያን ያውቁልኛል፡፡ ሌላው ቢቀር ጥቂት የህወሓት ሰዎችም ያለ መረጃ እንደታሰርኩኝ በማመን እስሩን እየተቃወሙ ይመስለኛል፡፡ አንድ ቀን ወደ ህሊናቸው ከተመለሱ ስህተታቸው በህዝብ ፊት ያዋርዳቸዋል፡፡”
‹‹በሐሰት ፕሮፖጋንዳ ሰው ማሳበድ ይፈልጋሉ›› ኦኬሎ አኳይ፣ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት
“የሆነ ያልሆነውን የሚያወራው በዙሪያዬ ቢሰበሰብም እኔ በጣም ሰላም ይሰማኛል፡፡ ካድሬዎች አብረውን እስር ቤት አሉ፡፡ ወሬ ነው የሚለቃቅሙት፡፡ ይህን ወሬ ሲለቃቅሙ ይቆዩና የሆነ ያልሆነውን እያወሩ፣ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ እየነዙ ሊያሳብዱህ ይሞክራሉ፡፡ እስር ቤትም ችግር ፈጣሪዎች ራሳቸው ኢህአዴጎች ናቸው፡፡ እኔማ ሰላማዊ ሰው ነኝ፡፡ ጉዳዩንም ፍርድ ቤት ይጨርሰው፡፡ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ባላስብም ፍርድ ቤት የሚወስነውን እጠብቃለሁ፡፡
እየመጡ የሚጠይቁኝ ዘመዶች አሉኝ፡፡ ቤተሰቦቼ ደህና መሆናቸውን መረጃ አገኛለሁ፡፡ ስለዚህ ምንም የምረበሽበት ነገር የለም፡፡ በህግ የምከራከርባቸው ብዙ ነጥቦች አሉ፡፡ ቢሆንም ከውሳኔ በፊት ምንም ባልናገር ጥሩ ነው፡፡ እዚህ ድረስ እየመጡ ለሚጠይቁኝ ሁሉ ክብር አለኝ፡፡”