Tuesday, July 8, 2014

የአሸባሪነት ሕግና እኛ

July7/2014
terrorism


የግንቦት ሰባቱ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በዚያ ኢትዮጵያዊያኑን በሚበላው ምድርና በሚበሉት አራዊት ከአካላቸው በስተቀር የሰውነት መገለጫ በሌላቸው ማሰብ የሚባል ነገር በማያውቁት ዘገምተኞች እጅ ሲታገትና በኋላም ተላልፎ ተሰጠ ሲባል ይሄንን ድንገተኛ አሳዛኝና ልብ ሠባሪ ዜና የሚገልጹትን ይዞች (ሊንኮች) እንዳየሁት ተጋርቸ (ሼር አድርጌ) በመጽሐፈ ገጼ (በፌስቡኬ) ለጠፍኩት (ፖስት አደረኩት) በማግስቱ አንድ ወዳጀ ምን ይለኛል? ኢትዮጵያ ውስጥ ይሄንን ዜና ፖስት ያደረገ (የለጠፈ) አንተ ብቻ ሳትሆን አትቀርም አለኝ፡፡ አንተስ አላደረከውም? ስል ጠየኩት የለበጣ ፈገግታ እያሳየኝ “አዬ አንተ! ይሄንን ማድረግ በአሸባሪነት ሊያስከስስ እንደሚችል አታውቅም?” ሲለኝ እየቀለደ መስሎኝ ነበር በኋላ ላይ ኮስተር ብሎ “ቆይ! ምን አስበህ ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ እየኖርክ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ? በገዛ እጅህ እኮ ገመዳቸው ውስጥ ገባህላቸው” ምንትስ ሲለኝ የምሩን እንደሆነ ገባኝና የትኛው ሕግ ነው ይሄንን የሚለው? ስል ጠየኩት፤ የቻለውን ያህል ይሄ አገዛዝ (ወያኔ) “የአሸባሪነት ሕግ” ሲል ያወጣውን አስቂኝና አስገራሚ ሕግ አስረዳኝ፡፡ ሕጉ ሥራ ላይ እንደዋለም በብዙኃን መገናኛ ተገልጾ እንደነበረ ነግሮኝ እንዴት ግንዛቤው ሳይኖረኝ እንደቀረ ተገርሞ ጠየቀኝ፡፡ ቶሎ ብየም የለጠፍኩትን እንዳጠፋ መከረኝ፡፡
በእርግጥ ዝርዝሩን ባላውቀውም “የአሸባሪነት ሕግ” እያሉ ሲጠቅሱትና ዜጎች እየተወነጀሉ ወህኒ ሲወርዱማ እሰማለሁ፡፡ እንግዲህ አንዳንዴ ለመንፈሳዊ ጉዳይ ለሳምንታት ለወራት ወደ ገዳም ወጣ የምልባቸው ጊዜያት አሉና በዚህ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ሳልሰማቸው ከምቀራቸውና ካመለጡኝ ጉዳዮች አንዱ ነው ማለት ነው ስል መለስኩለት፡፡ በብዙ አጋጣሚዎች እንዲያውም “እንዴ መቸ?” እያልኩ የምጠይቅባቸው ጉዳዮች ይበዙብኛል፡፡
ለማንኛውም እሱ እንዳለኝ ከሆነ “ግንቦት 7” በአገዛዙ በአሸባሪ ድርጅትነት ተፈርጇልና እንደ ሕጉ ስለዚህ ድርጅትና ስለ አመራሮቹ ምንም ዓይነት መረጃ ቢሆን መቀበልና መስጠት ማስተላለፍ፣ ማንኛውንም ዓይነት እርዳታና ድጋፍ ማድረግ በአሸባሪነት አስወንጅሎ እንደሚያሰቀጣ አስገንዝቦኛል፡፡
አሀ! ይሄንንማ ከአንባቢያን ጋራ ነው ላወራው የሚገባ ብየ ለአገዛዙም ላቀርባቸው የፈለኳቸው እንደ ዜጋ ሊመለሱልኝ የሚገቡ ጥያቄዎች አሉና ወደ እናንተ አመጣሁት፡፡ በጣም ይገርማል ለካ ለዚህ ኖሯል ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶችና ምዕራባዊያን መንግሥታት ይህ የአሸባሪነት ሕግ የራሱን ሕገ መንግሥት፣ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎችን፣ የተለያዩ ዓለም ዓቀፋዊ ድንጋጌዎችንና ስምምነቶችን ይቃረናል ይጥሳል ማለታቸው? በጣም ይገርማል፡፡
እዚህ ላይ ለአገዛዙ ጥያቄ ማንሣት እወዳለሁ “ግንቦት 7” አሸባሪ የተባለው ምን አድርጎ ነው? የሚያሸብረውስ ማንን ነው? በንጹሐን ዜጎች ላይ የፈንጅ ጥቃት የፈጸመበትና ለመፈጸም የዛተበት ጊዜ አለ ወይ? የድርጅቱ የትግል ዓላማ ማዕከል ያደረገው ምን ሆኖ ነው በአሸባሪነት ያስፈረጀው? የድርጅቱ ዓላማ አንድን ሃይማኖታዊ ወይም ጽንፈኛ የግል ወይም የቡድን አቋም ወይም አስተምህሮ በሕዝቡ ላይ በግዳጅ ለመጫን ለማስረጽ ነው ወይ? እናንተ እንዳላቹህት ሁሉ የኢትዮጵያም ሕዝብ  ግንቦት ሰባትን በአሸባሪነት መፈረጅ ካለበት የግድ በእነኝህ በጥያቄ መልክ በቀረቡት ጉዳዮች ላይ መኖሩን እርግጠኛ መሆን ይፈልጋል፡፡ አገዛዙ እነኝህን ጥያቄዎች ያለ እብለት በግልጽ ለሕዝቡ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡ ይሄንን ማድረግ ካልቻለ ግን ስም ማጥፋት ነውና ያንን “የአሸባሪነት ሕግ” ስትሉ ያወጣቹህትን ኢፍትሐዊ “ሕግ” የመቀበልና በእሱም የመገዛት ግዴታ አይኖርበትም ማለት ነው፡፡ እናንተ ስላላቹህ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደዚያ ብሎ የሚያምን ይመስላቹሀል? እርግጠኛ ነኝ የፈለጋቹህትን ብትሉ እንደዚያ ብሎ ያምንልናል ብላቹህ እንደማታስቡ፡፡ በሕዝቡ ልብ ውስጥ ያላቹህን ቦታ አሳምራቹህ ታውቃላቹህና፡፡ እድሜ ዘመናቹህን እራሳቹህን እንዳጃጃላቹህ አላቹህ፡፡ የዚህ “ሕግ” ኢፍትሐዊነት ከላይ እንዳየነው ከአመክንዮ (ከሎጂክ) እና ከተለያዩ ድንጋጌዎች አንጻር ሲታይ ብቻ አይደለም ከሃይማኖትም፣ ከባሕልና ወግም አንጻር ሲታይም ጭምር እንጅ፡፡
ይህ የአገዛዝ ሥርዓት ከምዕራባዊያን መንግሥታትና ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች “የተቃውሞ እንቅስቃሴንና አሸባሪነትን ለያይቶ አያይም በጣም በተሳሳተ መንገድ አንድ ላይ ደባልቆ ይፈርጃል ” እያሉ ለሚያቀርቡበት ክስ ደባልቄ አላየሁም አላይምም ይላልና እንግዲያው እንዲህ ከሆነ በዚህች ሀገር ያሉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችና አንቀሳቃሻቸው እነማን ናቸው??? ከጋዜጠኞች እስከ ፖለቲከኞች ከሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እስከ የሃይማኖት መሪዎች በአሸባሪነት ወንጅሎና ፈርዶ ወህኒ እየወረወረ ያለው ማን ነው? እንግዲህ እንደ ሕጋቹህ ሁሉ እነዚህን በሐሰትና በፈጠራ በአሸባሪነት ተወንጅለው ወይም መብታቸውና የዜግነት ግዴታቸው የሆነውን ትግል በመታገላቸው ወህኒ የተወረወሩትን ወገኖች መጠየቅ መጎብኘት መርዳት በአሸባሪነት ያስፈርጃል ያስወነጅላል ያሳስራል ማለት ነዋ?
የአሸባሪዎች ሕግ ከሃይማኖት አንጻር፡-
እኔ እንግዲህ ክርስቲያን ነኝ፡፡ እንደ ክርስቲያንነቴም እድን ዘንድ ክርስቶስ እንዳደርግ ያዘዘኝ ትዕዛዝ አለ፡፡ በወንጌሉ ላይ ሉቃ. 10፤25-37 ያለ አንድ ታሪክ ትዝ አለኝ “ እነሆም አንድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ተነሥቶ መምህር ሆይ! የዘለዓለም ሕይዎት እንድወርስ ምን ላድርግ? አለው፡፡ እሱም በሕግ የተጻፈው ምንድን ነው? እንዴትስ ታነባለህ? አለው፡፡ እሱም መልሶ ጌታ አምላክህን በፍጹም ኃይልህም በፍጹም ሐሳብህም ውደድ አለው፡፡ እውነት መለስክ ይሄንንም አድርግ አለው፡፡
እሱ ግን ራሱን ሊያጸድቅ ወዶ ኢየሱስን ባልንጀራዬስ ማን ነው? አለው፡፡ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለ አንድ ሰው ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ወረደ በወንበዴዎችም እጅ ወደቀ እነርሱም ደግሞ ገረፉት ደበደቡትም በሕይዎትና በሞት መካከልም ትተውት ሄዱ፡፡ ድንገትም አንድ ሌዋዊ ወደዚያ ስፍራ መጣና አይቶት ገለል ብሎ አለፈ፡፡ እንዲሁም ደግሞ አንድ ሌዋዊ ወደዚያ ስፍራ መጣና አይቶት ገለል ብሎ አለፈ፡፡ አንድ ሳምራዊ ግን ሲሄድ ወደ እርሱ መጣ አይቶትም አዘነለት ቀርቦም ዘይትና የወይን ጠጅ በቁስሎቹ ላይ አፈስሶ አሰራቸው በራሱ አህያም ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደሪያ ወሰደው ጠበቀውም በማግስቱም ሁለት ዲናር አውጥቶ ለባለቤቱ ሰጠና ጠብቀው ከዚህም በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሀለሁ አለው፡፡ እንግዲህ ከእነዚህ ከሦስቱ በወንበዴዎች እጅ ለወደቀው ባልንጀራ የሆነው ማንኛው ይመስልሀል? እሱም ምህረት ያደረገለት አለ፡፡ ኢየሱስም ሒድ አንተም እንዲሁ አድርግ አለው፡፡” ይላል ቃሉ፡፡
ታዲያ እንግዲህ እኔም እንደ ክርስቲያን እድን ዘንድ ቃሉ እንዳዘዘኝ ሁሉ የዘር የሃይማኖት የአመለካከት ልዩነትን ሳላደርግ ዘሩ ሃይማኖቱ አመለካከቱ ወይም አስተሳሰቡ የራሱ ነውና ያንን አክብሬ በሰውነቱ በወገንነቱ በወንበዴ እጅ ወድቆም ይሁን ችግር ደርሶበት ለተቸገረ ወገኔ ባዝን አቅም ካለኝም ከደረሰበት አደጋ ወይም ችግር እንዲድን ብረዳው ሥርዓቱ በአሸባሪነት ሕጉ መሠረት ለምን ሃይማኖታዊ ግዴታህን ተወጣህ ብሎ በአሸባሪነት ወንጅሎ ሊቀጣኝ ነው? እኔስ ይሄንን ፈርቸ የጌታየን ቃል አለማክበር ይኖርብኛል? እንዲህ ካደረኩስ የክርስቶስ ፍቅር በውስጤ አለ? ክርስቲያንስ ነኝ ማለት እችላለሁ? እንዲህም ብሎ ክርስትና የለ! በሉ አርፋቹህ ተቀመጡ እራሳቹህን ነው የምታጃጅሉት ሌላ ማንንም አይደለም፡፡ እንዲህ የምታስቡና የምትኖሩም ካላቹህ ክርስቲያን ነኝ እንዳትሉ አይደላቹህምና፡፡
በእውነት ለመናገር በዚህች ሀገር ለክርስቶስ ያደሩ መልካም እረኞች እውነተኛ የሃይማኖት አባቶች (መሪዎች) ቢኖሩ ኖሮ የዚህ ሕግ ተብየ የመጀመሪያ ተቃዋሚዎች እነሱ በሆኑ ነበር? “ጽድቁ ቀርቶ አሉ” አብረው እየዶለቱ ሕዝቡን የሚያስጨንቁ መለካዊያን ተኩላና ይሁዳ እነሱ አይደሉም እንዴ? ምእመናን ሆይ! ተስፋ ቁረጡ ለአምላክ ያደሩ ስለ በጎቹ እራሳቸውን አሳልፈው የሚሰጡ አባቶች ያላቹህ እረኞች ያላቹህ እንዳይመስላቹህ ምንደኛና ነጣቂ ተኩሎች እንጅ፡፡
የአሸባሪነት ሕግ ከባሕላችንና ወጋችን አንጻር፡-
ስለ እውነት ለመናገር በጣም ደገኛ ባሕል ነበረን አለንም ምንም ዓይነት ልዩነት አለመግባባት ይኑረን በችግር ጊዜ ግን የራሴ ይቅርብኝ ብሎ እስከመደጋገፍ የሚደርስ፡፡ እንግዲህ በዚህ “ሕግ” መሠረት ወያኔ በራሱ ቡድናዊ ጥቅሙ ምክንያት ከወነጀላቸው ዜጎች ጋራ ኃዘንን ጨምሮ ሠርግ ማኅበር ክርስትና ቡና መጣጣት ወዘተ. የተከለከለ ነው ማለት ነው? አገዛዙ ስለጠላቸው ብቻ ጠላቶቻችን እንዳልሆኑ እያወቅን ከአጠቃላይ የማኅበራዊ ሕይዎት መስተጋብር ማግለል አለብን ማለት ነው?
ቆይ ቆይ ቆይ ቀይ መስቀል ከዚህ “ሕግ” በኋላ እንዴት ነው እየሠራ ያለው? ነው ወይስ ለቅቆ ወጥቷል? እንደምታውቁት ቀይ መስቀል ለሚሰጠው ሰብአዊ አገልግሎት በዘር በሃማኖት በማንኛውም ዓይነት የአስተሳሰብና የአመለካከት ልዩነት ያልተገደበ ዓለማቀፋዊ በሆነ መርሑ መሠረት አገልግሎት እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ እንግዲህ በዚህ “ሕግ” መሠረት ቀይመስቀልም ሰብአዊነት በተሞላው መርሑ ሳቢያ ችግር ለገጠማቸው ወገኖች አገልግሎቱን በሚሰጥበት ጊዜ በአሸባሪነት ሊከሰስ ነው ማለት ነው? ምንድን ነው እያወራቹህኝ ያለው? ወያኔ በቀዘነና በቃዠ ቁጥር ከሰብአዊ መብቶች፣ ከዓለማቀፋዊ ስምምነት ድንጋጌዎች፣ ከባሕልና ሃይማኖት ከገዛ ሕገ መንግሥቱም ሳይቀር የሚቃረን የሚጣረስ የአውሬና አረመኔያዊ ቡትቶ በቸከቸከ ቁጥር ሐግ እያልን ልንቀበል ነው እንዴ? ይሄ ሕግ ተብየው የሚያስጠብቀውስ ጥቅም የማንን ነው? የሀገርን? የሕዝብን? ወይስ ጥቂቶችን ብቻ ያቀፈውን ቡድን ጥቅም? ጉዳዩ በጣም ግልጽ ነው ሕጉ የሚያስጠብቀው የሀገርንና የሕዝቧን ሳይሆን የቡድንን ነው፡፡ የሀገርንና የሕዝብን ጥቅም ግን ለአደጋ ይዳርጋል፡፡
ጥሩ እንግዲያውስ ቅዱስ ቃሉ “ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባናል” የሐዋርያት ሥራ 5፤29 ይላልና እኔ በበኩሌ የፈለጋቹህትን አድርጉ ይሄንን ስትደነብሩ ስትንቦቃቦቁ ስትቀዝኑ ስትንቀጠቀጡ ስትሸበሩ ስትቀዝኑ የሞነጫጨራቹህትን ፀረ ሃይማኖታዊ ሕግጋት፣ ፀረ ወገወና ባሕል፣ ፀረ ሰብአዊ መብት፣ ፀረ ሰብአዊ መብቶች የሆነውን የጫካ የአውሬ “ሕግ” ቡትቶ አልቀበለውም ቀቅላቹህ ብሉት፡፡ ዜጎችን በግዳጅ እኔ እንደማስበው ካላሰባቹህ ብሎ ማሰብና ተፈጥሯዊና ሰብአዊ መብቶችን፣ ሃይማኖታዊና ባሕላዊ መብቶችን መንፈግ ወንጀል ነው፡፡ መንጋ ወንጀለኛ ሁሉ እደግመዋለሁ ቀቅላቹህ ብሉት አልቀበለውም፡፡ ግንቦት 7 አይደለም ሌላም ይሁን ብቻ ሰው ይሁን እጠይቀዋለሁ እጎበኘዋለሁ በችግሩም እረዳዋለሁ እሄንን የማደርገው የግንቦት 7 አባል ስለሆንኩ አይደለም ልብ አድርጉ አባል አይደለሁም ሃይማኖታዊ ባሕላዊ ሰብአዊ ግዴታየ ስለሆነ እንጅ፡፡ ይሄ አሸባሪነት ነው ካላቹህ አንድ ሽህ ጊዜ ልሁን፡፡
ወንድ ከሆንሽ ልብ ካለሽ ዙሪያውን የሐገሪቱን አጎራባች ሀገራት ፍጹም መንግሥት ነኝ ከሚል አይደለም ከተራ ዜጋ እንኳን በማይጠበቅ ክህደትና ነውረኝነት የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅሞች መሬት ቆርሶ ከመስጠት አንስቶ በስደት ያሉትን ዜጎቻችንን ሕይዎትና ክብር ለባዕዳን መጫወቻነትና ለግፍ  አሳልፈሽ እየሰጠሸ በወዳጅነት ሳትይዥ ተቃዋሚዎች ሌላው ሁሉ ቀርቶ አንቺ ከሱዳን ስታገኝው የነበረውን ያህል ሁለንተናዊ ድጋፍ እንኳን ባይሆን መንደርደሪያ ቦታ ብቻ እንኳን እንዳያገኙ ሳትከላከይ አትፋለሚም ነበር? አይደለም 24 ዓመታት መንፈቅ እንኳን እንደማትቆዪ ታውቂዋለሻ፡፡ ወንድነት ማለት ጀግንነት ማለት እሱ ነበር እንጅ ነውረኛ በሆነ “በእኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” የአሕያ አስተሳሰብ የሀገርንና የሕዝብን ጥቅም በቡድን ጥቅም በመለወጥ የሥልጣን ዘመንን ለማራዘም መቃተት መንፈራገጥ አይደለም፡፡ ደሞ እኮ አያፍሩም እንደ ወንድ ይፎክራሉ ይወነናሉ ጉራቸውን ይነፋሉ፡፡ ሳትዋጋ የእግር መንገድ ተጉዛ ገብታ፡፡ ይችን ጥጥ ልብ ይዛቹህ አትፎክሩብን፡፡ ድንቄም! “አቅም ስለሌለን ልብ ስለሌለን ነው” ካላቹህ ደግሞ ዜጎች በሰላማዊ ትግል ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉበትን መድረክ ክፍት ማድረግ ዕድል መስጠት ነዋ! ሁለቱንም ጥርቅም አድርጎ ዘግቶ መፈናፈኛ አሳጥቶ ይሆናል እንዴ? ቦቅቧቃ ቅዘናም ሁሉ! እናንተ በተንቦቃቦቃቹህ በቀዘናቹህ ቁጥር እኛ ሰላም ማጣት መታመስ አለብን እንዴ?
እናንተን መንግሥት ብሎ ለማለት ባይቻልም አንድ መንግሥት ተጠሪነቱ ለሕዝብ ነው እንጅ ሕዝብ አይደለም ተጠሪነቱ ለመንግሥት
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
የሆነው፡፡ እናም ማንም የመሰለውን የቃዠውን ሁሉ አስገድዶ በሕዝብ ላይ መጫን አይችልም፡፡ ያለመቀበል ሙሉ መብት አለው፡፡ በምንም ነገር ላይ የመጨረሻው ባለሥልጣን ሕዝብ ነው፡፡ የሕዝብና የመንግሥት ሐሳብ ከተስማማና አንድ ልብ ከሆነ ብቻ መንግሥት የመሰለውን የማድረግ መብት አለው፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ይሄንን የመንግሥትና የሕዝብ ስምምነት ልናይ አልቻልንም እየተጠበቀና እየተፈጸመም ያለው የቡድን ጥቅምና ሐሳብ ብቻ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ወዳጅና ጠላቱን አሳምሮ ያውቃል ነጋሪ አይፈልግም፡፡ የአንዳርጋቸውና የጓዶቹ ሐሳብ  ይጠቅመኛል ካለ ያንን የመቀበል ካላለ ደግሞ የመጣል ያለመቀበል ሙሉ መብት አለው፡፡ እናንተ ለራሳቹህ አንቀበልም አይስማማንም የማለት መብት አላቹህ፡፡ እናንተ እንዳላቹህ ሁሉም ሕዝቡም ደግሞ አለው፡፡ ይሄንን መብቱን በመንፈግ የእናንተን አስተሳሰብ በግድ በሕዝብ ላይ መጫን አይቻልም ወንጀል ነው ሕግ ይከለክላል፡፡ ይህ አንባገነንነት ፈላጭ ቆራጭነት ነው፡፡ ልታውቁት ልትረዱት ሊገባቹህ ያልቻለው ነገር ይሄ ነው፡፡ ለዚህች ሀገርና ሕዝቧ ከእናንተና ከመሰሎቻቹህ በላይ ጠላት የለባቸውም፡፡ ደኅና ሁኑ
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

Monday, July 7, 2014

ስብሃት ነጋ ከአሜሪካ መንግስት በወር 10.000 ዶላይ ደምወዝ ይከፈለዋል።

July7/2014
ምንሊክ ሳልሳዊ
ሕወሃት በኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አይሁድ ስርአትን የመዘርጋት ምስጢራዊ እቅድ አለው።

በአሁን ወቅት ስብሃት ነጋ የያዘውን ስልጣን የቀድሞው የኢንስቲትዩቱ ፕረዝዳት የነበረው ዶክተር ክንፈ አብርሃ እንደሞተ ወያኔ ዶክተሩን የሚተካ ሰው በማጣቱ በትም ተቸግሮ ስለነበር ቦታውን እንዲይዝ የተፈለገው የትግራይ ተወላጅ ስለነበር አቶ መለስ ዜናዊ በዘር ቆጠራ ሲያጠያይቁ አንድ በሃይለስላሴ ጊዜ ወደ ካናዳ ለትምህርት ሂደው ደርግ ሲመጣ በዛው በጥገኝነት የቀሩ ህይወታቸውን ሙሉ ወርልድ ባንክ የሰሩ እና የተማሩ በጡረታ የሚኖሩ ዲያስፖራ አዛውንት ኢትዮጵያን በዘረኝነት ሳይሆን በኢትዮጵያዊነት መንፈስ ብቻ የሚያውቛትን ዶክተር የትግራይ ተወላጅ አስጠርቶ ሊሾማቸው አስቦ አልተሳካለም። ለምን ?

እኚህ ካናዳ በጡረት የሚኖሩ አዛውንት በጊዜው የመለስ ዜናዊን ጥሪ ተቀብለው ወደ አዲስ አበባ መጥተው ነበር ። ገና ከአይሮፕላን ወርደው ወደ ኤርፖርቱ ከገቡ ጊዜ ጀምሮ እንዲሁም በሆቴሎች በመንገዶች ላይ የተመለከቱት በዞሩባቸው መስሪያ ቤትች ያሉ ነገሮችን በመታዘብ አስደንጋጭ ገተመኝ ሆኖባቸው ነበር ። ሁሉንም ሲያዩት ከአንድ ብሄር እና ከአንድ ቤተሰብ የተሳስረ ሃገሪቷ የአንድ ሰው ንብረት በሚመስል መልኩ ብሰንሰለት አደጋ ውስጥመሆኗን ሲናገሩ ተደምጠዋል። የአገሪቱ ተቋማት በአንድ ቋንቛ ተገጣጥመው እንደተሰሩ አላቂ ምርቶች አዲስ አበባ በመሰለ ሜትሮ ፖሊቲይን ከትማ ውስት መመልክታቸው እጅግ አስደንግጧቸው ነበር።

እኚህ ለጊዜው ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉት ካናዳ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ በጥሪው መሰረት ከመለስ ዜናዊ ጋር በአካል ተገናኝተው በነበረ ጊዜ መለስ ዜናዊ የዶክተር ክንፈን ቦታ እንዲይዙልኝ ፈልጌ ነበር ያስመጣዎት ምክንያትም ይህ ቦታ እንደርሶ ያለ ልምድ ያለው ሰው እንዲይዘው ስለተፈለገ ስለሆነ እርሶን መሾም በ እጅጉ ያስፈልገናል ሲላቸው... ዶክተሩ ነገሩ ስለገባቸው የተጠሩት በ እውቀታቸው ሳይሆን የትግራይ ተወላጅ ብቻ ስለሆነ እንደሆነ ስለተደረዱ የገመቱትም ሆኖ ስለገጠማቸው መለስ ዜናዊን አንድ ጥያቄ ጠየቁት ... ለመሆኑ አገሩን ሁሉ ከላይ እስከ ታች በአንድ ጎሳ አዋቅራችሁ እስከመች መዝለቅ ትችላላችሁ ? በዚህ ዘመን በተለይ ፕራክቲክል ነው? ባላንስ ኦፍ ፓውር / የሃይል ሚዛኑ / ሽፍት ባይደረግ ምን ይውጣቹሃል ? ወዘተ የሚል ጥያቄ አንስተውበት ነበር፡፤

የመለስ መልስ ግን በወቅቱ አጭር ነበር " ይህ ነገር የትም እንደማያደርሰን እንውቀዋለን ።ነገር ግን በተቻለን መጠን ስልጣናችንን ሉዝ (ከማጣታችን) በፊት የትግራይ አይህድ ፈጥረን ማለፍ አለብን ብለን ወስነናል፡፤ ቁርጥ ያለ መልስ ነግሯቸዋል። በጥሪያቸው መሰረት ወደ አዲስ አበባ የመጡት አዛውንት ሃገሪቷ በአደገኛ የጎሳ ቫይርስ ውስጥ መሆኗን ተገንዝበው ከደሙ ንጹህ ነኝ ብለው መልሰውለት ወደ መጡበት ካናዳ ተመልሰዋል።

የትግራይ ይሁድ ለመፍጠር ማለት ልክ እስራኤላውያን በአለም ተሰራጭተው ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ እይስፈራሩ እንደሚኖሩት ሁሉ የትግራይ ተወላጆችም በህወሃት ውሳኔ መሰረት በአገሪቷ ቁልፍ ቦታዎችን በምያዝ ኢትዮጵይውያንን እያስፈራራ ለማኖር እና ለመግዛት እቅድ እንዳለው እኚሁ አዛውንት ተናግረዋል፤፡

እኚህ ምሁር አዛውንት አልቀበለውም ብለው ጥለው የሄዱትን ስልጣን ለስብሃት ነጋ ተሰጥቶት ደምወዙም 10.000 ዶላር ሲሆን ደሞዙንም የምትከፍለው አሜሪካ መሆኗን መረጃዎች ጠቁመዋል። 

Ethiopia: Fears for Safety of Returned Opposition Leader

Yemen Unlawfully Deported Andargachew Tsige, Concerns over Possible Mistreatment

JULY 7, 2014
HRW.svgHRW.svg(London) – An exiled Ethiopian opposition leader unlawfully deported by Yemen back to Ethiopia is at risk of mistreatment including torture. Andargachew Tsige is secretary-general of Ginbot 7, a banned Ethiopian opposition organization, and was convicted and sentenced to death in absentia in separate trials in Ethiopia in 2009 and 2012.

The current whereabouts of Andargachew, a British national, is unknown, raising concerns for his safety. The Ethiopian government should take all necessary steps to ensure Andargachew’s safety and his right to a fair trial. Many individuals arrested in politically related cases in Ethiopia are detained in Addis Ababa’s Maekelawi prison. In an October 2013 report, Human Rights Watch documented the use of torture by authorities against detainees in Maekelawi, including members of opposition political parties and organizations, as well as journalists.

“We are deeply concerned for Andargachew Tsige’s safety,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Ethiopia needs to demonstrate that it is holding Andargachew in accordance with its international obligations, and he should be allowed immediate access to a lawyer, his family, and to British consular officials.”

Yemeni officials arrested Andargachew at El Rahaba Airport in Sanaa, Yemen, on June 23 or 24, 2014, while he was in transit on a flight from Dubai to Eritrea. They did not permit him consular access to UK embassy officials and summarily deported him to Ethiopia, credible sources told Human Rights Watch, despite his being at risk of mistreatment.

Yemeni authorities initially denied any knowledge of Andargachew’s detention and transfer to Ethiopia. Ethiopian government officials publicly called for his extradition from Yemen on July 3.

Under the Convention against Torture, which Yemen ratified in 1991, a government may not “expel, return (‘refouler’) or extradite a person to another State where there are substantial grounds for believing that he would be in danger of being subjected to torture.” These protections override any extradition treaty or other security arrangement that may exist between Yemen and Ethiopia.

Trials in absentia generally violate the defendant’s right to present an adequate defense, concerns heightened in cases involving the death penalty.

“Yemen blatantly violated its international legal obligations by deporting someone to Ethiopia who not only is at serious risk of torture, but also faces the death sentence after being tried in absentia,” Lefkow said.

Ginbot 7, of which Andargachew is a founding member, was established in the aftermath of Ethiopia’s controversial May 2005 national elections. The Ethiopian government banned Ginbot 7, which has advocated the armed overthrow of the Ethiopian government, and officially considers it to be a terrorist organization.

The government has prosecuted Ginbot 7 members and leaders in trials that did not meet international fair trial standards. In November 2009, a court convicted Andargachew and 39 others under the criminal code on terrorism-related charges. Andargachew, who was tried in absentia, was sentenced to death. In June 2012, he was convicted again in absentia, this time under the abusive 2009 anti-terrorism law, along with 23 journalists, activists, and opposition members. Again, he was sentenced to death.

Human Rights Watch has repeatedly criticized provisions in Ethiopia’s anti-terrorism law that violate due process rights guaranteed under Ethiopian and international law. At least 34 people, including 11 journalists and four Ginbot 7 leaders, are known to have been sentenced under the law since late 2011 in what appeared to be politically motivated trials; the real number is likely much higher. Suspects held under the law may be detained for up to four months without charge, among the longest periods under anti-terrorism legislation worldwide.

Ethiopian courts have shown little independence from the government in politically sensitive cases. Defendants have regularly been denied access to legal counsel during pretrial detention, and complaints from defendants of mistreatment and torture have not been appropriately investigated or addressed – even when defendants have complained in court.

The Ethiopian government routinely denies that torture and mistreatment occurs in detention. It restricts access to prisons for international observers, monitors, and consular officials, making it difficult to monitor the number and treatment of prisoners. In several cases documented by Human Rights Watch, Ethiopian security officials have arrested foreign nationals, denied knowledge of their whereabouts, and delayed access for consular officials for long periods.

In 2007 Human Rights Watch documented the forced transfer of scores of men, women, and children from Somalia and Kenya to Ethiopia. One of the men, Bashir Makhtal, a Canadian citizen of Ethiopian origin who was accused of membership of the Ogaden National Liberation Front (ONLF), a banned armed movement in Ethiopia, was denied consular access for 18 months. Meanwhile in 2010 and again in 2012, refugees registered with the United Nations High Commissioner for Refugees in Kenya were unlawfully returned to Ethiopia and told Human Rights Watch that they were subsequently tortured in detention. In all of these cases, the individuals were accused of belonging to groups that the Ethiopian government has designated as terrorist groups.

“Given its appalling track record of mistreating members and perceived supporters of banned groups, Ethiopia should know that the world will be watching how it treats Andargachew Tsige,” Lefkow said.

የአቶ አንዳርጋቸዉ እገታና የመብት ተሟጋቹ ተቋም

July 7/2014
የአዉሮጳ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የመን-ርዕሠ ከተማ ሰነዓ አዉሮፕላን ማረፊያ ተይዘዉ ወደ ኢትዮጵያ ተግዘዋል የተባሉትን የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌን ለማስፈታት እንዲጥሩ GESELLSCHAFT FÜR BEDROHTE VÖLKER የተሰኘዉ የጀርመን የመብት ተሟጋች ድርጅት ጠየቀ።
Schnell Wachsende Städte Sanaa
ሰነዓ ከተማ
ለተጨቆኑ ሰዎች ጥብቅና የቆመዉ ድርጅት ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ አቶ እንዳርጋቸዉ ፅጌንም ሆኑ ሌሎች ኢትዮጵያ ዉስጥ የታሠሩ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ለማስፈታት የአዉሮጳ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሠብአዊ መብት ምክር ቤት ጣልቃ መግባት አለባቸዉ።
Flash-Galerie Airbus A 350 800 XWB
የመን አየር መንገድ

GESELLSCHAFT FÜR BEDROHTE VÖLKER ማለት የሚታወቀዉ በጀርመን ጎቲንገን ከተማ የሚገኘዉ ለተጨቆኑ ሰዎች ጥብቅና የቆመዉ ድርጅት የአዉሮጳዉኅብረት እና የተመ የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ናቪ ፒላይ፤ የት እንደደረሱ እስካሁን በግልፅ ያልታወቀዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ መሪ የአቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ የት እንደሚገኙና፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እንዲያደርጉ ጠየቀ።«ለዲሞክራሲያዊትዋ ኢትዮጵያ የሚናገሩት የታዋቂዉ የተቃዋሚዎች መሪ የአቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ ደህንነት እጅግ አሳስቦናል ሲሉ የድርጅቱ የአፍሪቃ ጉዳዮች ኃላፊ ኡልሪሽ ዲሉስ ዛሪ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታዉቀዋል። በእዉነት በአሁኑ ወቅት አቶ እንዳርጋቸዉ ፅጌ የት እንደሚገኙ ድርጅታቸዉ የሚያዉቀዉ ነገር የለምን?
«በጣም ከባድ ነዉ በአሁኑ ግዜ ያለዉን መረጃ ሁሉ መመርመር ያስፈልጋል። በሳምንቱ መጠናቀቅያ ላይ የተቃዋሚዎች መሪ እንዳርጋቸዉ ፅጌ ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈዉ ተሰጥተዋል የሚል ዘገባ በተደጋጋሚ ተነቧል፤ ተሰምቶአል። እስካሁን ግን ይፋዊ ማረጋገጫን አላገኘንም። በዚህም የአዉሮጳዉ ኅብረት እና የተመ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር መጀመርያ የአንዳርጋቸዉ ፅጌን የደህንነት ሁኔታ እንዲያጣሩ ፤ ማለትም በየመን የፀጥታ ጥበቃ ሥር መሆናቸዉን እልያም ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈዉ
Gesellschaft für bedrohte Völker Logo Grafik
የጀርመኑ የሰብዓዊ መብት ድርጅት አርማ
መሰጠታቸዉን አጣርተዉ ፤ የተረጋገጠ መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀናል። በርካቶች እንደሚገልፁት፤ አንዳርጋቸዉ ፅጌ ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈዉ መሰጠታቸዉን እያወሩ ነዉ፤ እኛ ግን እስካሁን ምንም አይነት ማረጋገጫ አላገኘንም። ስለዚህም የት ቦታ እንደሚገኙ እንዲጣራ ጠይቀናል»
ኢትዮጵያ በአሸባሪነት ለዓመታት ስትፈልጋቸዉ የነበረዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ የግንቦት ሰባት ፓርቲ ዋና ፀሃፊ፤ ከሰኔ 16 አዉሮፕላን ለመቀየር ሰንዓ አየር ጣብያ ሳሉ በፀጥታ አስከባሪዎች ከተወሰዱ በኃላ ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ግዜ ድረስ ያሉበት በግልፅ አልታወቀም። በሳምንቱ መጨረሻ ፓርቲያቸዉ ባወጣዉ መግለጫ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈዉ ተሰተዋል። ይን በማያያዝ አቶ አንዳርጋቸዉ በኢትዮጵያ የሚጠብቃቸዉ እድሜ ይፍታህ እስር አልያም የሞት ቅጣት መሆኑን ለተጨቆኑ ሰዎች ጥብቅና የቆመዉ ድርጅት ስጋቱን ባወጣዉ መግለጫ አስነብቦአል፤
«ነገሩ አሳፋሪ እና ትርጉም የለሽ ነዉ። ግለሰቡ በዜግነት እንግሊዛዊ ናቸዉ ። አዉሮፕላን ለመቀየር ማለት ትራንዚት ለማድረግ ባረፉበት ሀገር በቁጥጥር ሥር ማዋልና እያደናቸዉ ወዳለዉ ሀገር መንግሥት አስተላልፎ መስጠት ተቀባይነት የሌለዉ ሥራ ነዉ። እኝህ ፖለቲከኛ በኢትዮጵያ በአሸባሪነት ወንጀል ፤ በባልሠሩት የተወነጀሉ፤ እና ለዓመታት የኢትዮጵያ መንግሥት ሲፈልጋቸዉ እንደነበር በግልፅ ይታወቃል። በኢትዮጵያም ትክክለኛ ፍርድ እንደማይጠብቃቸዉ በግልፅ እናዉቃለን። እዚህ ላይ ጉዳዩ አሸባሪነት ሳይሆን በመንግስት ላይ ትችትና ሂስ የሚያቀርቡ በዓለም ዘንድ ታዋቂ የሆኑ ፖለቲከኛ አፍ ለማዘጋት የተደረገ ርምጃ ነዉ። ሥለዚህም ጥያቄያችን የአዉሮጳዉ ኅብረት ይህ ፖለቲከኛ በዚህ ፍርድ ላይ እንዳይቆሙና በነፃ ወደ ብሪታንያ እንዲለቀቁ አስቸኳይ ጫና እንዲያደርግ ነዉ። ይህ ካልሆነ ደግሞ በአዉሮጳ በብሪታንያ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለዉ ግንኙነት ሥጋት ላይ ይወድቃል።»
Karte Äthiopien englisch

የድርጅቱ መግለጫ ከአቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌ በተጨማሪ በኢትዮጵያ የታሰሩ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ እንዲሁም ባለፈዉ የሳምንት መጨረሻ ዳግም በርካቶች ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት የታሠሩ የሙስሊም መሪዎች እንዲፈቱ ይጠይቃል፤ ዲሊዩስ በዚህ ጉዳይ የላሉ
«ሁኔታዉ በጣም ከባድ ነዉ። ኢትዮጵያ ዲሞክራስያዊ መርህን ይዛ እንድትራመድ ለማድረግ በሚደረገዉ ጥረት የሚታየዉ ችግርን፤ ለመቅረፍ ምንም አይነት የፈዉስ መድሃኒት አላገኘንም። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ዉስጥ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይደረጋል። በተለያዩ ጎሳዎች፤ የኃይማኖት ተቋማት እንዲሁም ባጠቃላይ በጋዜጠኞች እና በፕሪስ ነፃነት ላይ የሚደረግ ከፍተኛ ጫና እና የመብት ጥሰት አለ። በዚህም የአዉሮጳ ኅብረት በኢትዮጵያ ትክክለኛ መንግሥትና የሀገር መሪ እንዲመጣ፤ በተጨማሪም ለዲሞክራሲ ሰፊ የሥራ ቦታ እንዲፈጠር እንዲያደርግ ጥያቄ እያቀረብን ነዉ። በኢትዮጵያ ይህ ሁሉ የለም። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዉስጥ በፊደራል መንግሥት ስር ያለዉ መንግሥት የአንድ ቡድን ክምችት፤ የራሱን ፍላጎት ብቻ ሌሎች እንዲሰሩ የሚስገድድ ጨቋኝ መንግሥት ነዉ፤ የአዉሮጳ ኅብረት በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲሰራ ጠይቀናል»

አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC


Amnesty International: Ethiopian activist Andargachew Tsige at risk of torture

July 7, 2014

URGENT ACTION ETHIOPIAN ACTIVIST AT RISK OF TORTURE

Andargachew Tsige, an Ethiopian political activist in exile, appears to have been arrested in transit in Yemen on 24 June and forcibly returned to Ethiopia. He is at risk of torture and other ill-treatment. Andargachew Tsige is a British national of Ethiopian origin and Secretary-General of Ginbot 7, an outlawed Ethiopian opposition group. He disappeared on 24 June at Sana’a airport in Yemen, while in transit between the United Arab Emirates and Eritrea. Although no official statements have been released by the Yemeni or Ethiopian authorities about his current whereabouts, human rights activists in Yemen told Amnesty International that he was forcibly returned to Ethiopia the same day he landed after being detained at the Sana’a airport.Amnesty International on Andargachew Tsige
He is at high risk of torture and other ill-treatment in Ethiopia, where political detainees are frequently tortured in order to extract information and confessions. His incommunicado detention in an unknown location increases this risk.
Ginbot 7 is one of five organisations proscribed as terrorist organisations by the Ethiopian parliament in 2011. In 2012, Andargachew Tsige was prosecuted in absentia on terrorism charges (alongside journalist and prisoner of conscience Eskinder Nega, and others) and sentenced to life imprisonment. Previously, in 2009, he was convicted in absentia on charges related to an aborted coup attempt and was sentenced to death. He was also tried in absentia in the 2005-2007 trial of political opposition members, journalists, activists and others.
In recent years, many Ethiopians wanted by the authorities on the grounds of their political activities have been kidnapped in neighbouring countries and forcibly returned to Ethiopia. This has often involved the collaboration of security forces in those countries. Another of the defendants in the 2012 trial had been kidnapped and forcibly returned from Sudan. All those returned are at risk of arbitrary detention, torture and unfair trial.
Please write immediately in Amharic, English or your own language:  Calling on the authorities to guarantee Andargachew Tsige is not subjected to torture or other forms of ill- treatment;  Calling on the authorities to immediately provide information on the location where he is being held, and to ensure that he has full and immediate access to legal and consular representation and family members;  Calling on the authorities to ensure that Andargachew Tsige is not required to serve any sentence for a conviction in absentia and must be retried on any charges against him in a trial that meets international standards, before a new court and without the possibility of the death penalty.
PLEASE SEND APPEALS BEFORE 8 AUGUST 2014 TO: Minister of Justice Berhanu Hailu Ministry of Justice, PO Box 1370, Addis Ababa, Ethiopia Fax: +251 11 5517755 Salutation: Dear Minister
Minister of Federal Affairs D. Shiferaw Teklemariam Ministry of Federal Affairs P.O.Box 5718 Addis Ababa, Ethiopia Email: shiferawtmm@yahoo.com Salutation: Dear Minister
And copies to: Prime Minister His Excellency Hailemariam Desalegn Office of the Prime Minister, PO Box 1031, Addis Ababa, Ethiopia Fax: +251 11 552030 (keep trying)
Also send copies to diplomatic representatives accredited to your country. Please insert local diplomatic addresses below: Name Address 1 Address 2 Address 3 Fax Fax number Email Email address Salutation Salutation Please check with your section office if sending appeals after the above date.
ADDITIONAL INFORMATION Andargachew Tsige is a former member of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) party and was Deputy Mayor of Addis Ababa from 1991 to 1994, when he resigned on account of differences with the government.
Based in the UK, he travelled to Ethiopia shortly before the 2005 elections to support the opposition party Coalition for Unity and Democracy (CUD). On 8 June 2005, in the wake of the controversial election results, he was detained in Ethiopia and held at Ziway army camp. He was released on bail in July of that year. Like many detainees, Andargachew was accused of organizing the demonstrations, seeking to subvert the Constitution and other offences, which he denied, but he was not formally charged with any offence. After he was released he returned to the UK, but was subsequently named, tried and convicted in absentia in a major political trial of the leadership of the CUD, journalists, human rights activists and others, on charges including high treason, in 2005-2007. At the time he was the CUD representative in the UK.
After the CUD trial, fellow defendant Berhanu Nega founded the ‘Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy’ from exile in the US, of which Andargachew Tsige became Secretary General. Berhanu Nega was also tried in absentia in the 2009 and 2012 trials.

Sunday, July 6, 2014

ከግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ

July6/2014

ከግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪ
ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን!!!

ሰኔ 29 ቀን 2006 ዓ.ም
በየጊዜው እየከረረና እየገረረ የመጣው ትግላችን “ሁላችን አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን” ወደ ተባለ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ይህ ጽሁፍ የዚህን የትግል ምዕራፍ ምንነትና ይዘት በአጭሩ ያብራራል። በዚህ ጽሁፍ ላይ የሰፈሩት ዓረፍተ ነገሮች ተነበው የሚታለፉ ሳይሆን በተግባር የሚተረጎሙ ሥራዎች ናቸው።
አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ምን ማለት ነው? አንዳርጋቸው ጽጌ ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለዲሞክራሲና ለእኩልነት በጀግንነት የቆመ፤ ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ሁሉ ሲከፍል የነበረና አሁንም እየከፈለ ያለ መሪያችን ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ልክ እንደሱ ትሁት ሆኖም ግን ቆራጥ፤ ሆደ ሰፊ በዚያው ልክ ደግሞ መራር፤ አስተዋይና ብልህ ሆኖም ተግባር ተኮር መሆን ማለት ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ወያኔን ለማስወገድ መደረግ የሚገባውን እርምጃ ለመውሰድ የተዘጋጀ ሰው መሆን ማለት ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ለአገርና ለትውልድ ቤዛ መሆን ማለት ነው።
ወያኔ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ካተኮረባቸው ምክንያቶች አንዱ የወያኔን የዘር ፓለቲካና ፕሮፖጋንዳ በሚያመክን መልኩ በተግባር ትግል ውስጥ ካሉ የኦሮሞ፣ የአፋር፣ የኦጋዴን፣ የጋምቤላ እና ሌሎች ዘውግ ተኮር ድርጅቶች ጋር ንቅናቄዓችን ተግባራዊ ትብብር ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ድረስ ማቀራረብ የቻለ መሪ መሆኑ ነው። ከሁሉም በላይ ለወያኔ የጉሮሮ ቁስል የሆነበት ደግሞ ከትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ጋር ግንቦት 7 የፈጠረው ጠንካራ ትብብር ነው። ከትህዴን ጋር በመሆን አቶ አንዳርጋቸው ወያኔ በትግራይ ሕዝብ ጀርባ መንጠልጠል እንዳይችል አድርጎታል። እናም አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት ከዘረኝነት ፀድቶ መገኘት ማለትም ጭምር ነው። አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ማለት በኢትዮጵያዊያን እኩልነት እና እኩል ባለመብትነት ከልብ ማመን እና ለእኩልነት በጽናት መታገል ማለት ነው።
አንዳርጋቸው ጽጌን ለመሆን የግድ የግንቦት 7 አባል መሆንን አይጠየቅም። አንዳርጋቸው ጽጌን ለመሆን ለመልካም ዓላማዎች መሳካት ዋጋ ለመክፈል መዘጋጀትን እንጂ የግድ ከአንድ ወይም ከሌላ ድርጅት ጋር መወገንን አያሻም። ያም ሆኖ ግን አንዳርጋቸው ጽጌን የሆነ ሰው በጠንካራ ድርጅት የታገዘ ትግል አስፈላጊነት ይረዳል።
በመጨረሻም አንዳርጋቸው ጽጌን መሆን ኦኪሎ ኦኴኝ፣ አንዱዓለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ በቀለ ገርባ፣ ኦልባና ሌሊሳ እና እዚህ ዘርዝረን ልንጨርሳቸው የማንችላቸው ጀግኖቻችንን ሁሉ መሆን ማለት ነው።
“የሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን” ዘመቻ ትኩረቶችን በየጊዜው የምንገልጽ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ በሥራ ላይ መዋል ያለበት የዓለም ዓቀፍ ዘመቻው የመጀመሪያ እርከን ትኩረቶች ከዚህ በታች ቀርበዋል
የዘመቻው የመጀመሪያው እርከን ትኩረቶች
ይህ የመጀመሪያ እርከን ሶስት ቦታዎች ላይ ያተኩራል፡- የመን፣ ብርታኒያ እና ወያኔ
 የመንን በተመለከተ
የየመን መንግሥት የዓለም ዓቀፍ ህግም ሆነ የየመን የራሷን ህግ በመተላለፍ መሪያችንን ለእርድ አሳልፎ ሰጥቶብናል። ከመጀመሪያው ጀምሮ ለየመን መንግሥት የተደረገው ተማጽኖ ሰሚ ጆሮ አላገኘም። እስካሁንም ድረስ የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸውን ማሠሩና ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱ በይፋ አላመነም። እኛ ባለን መረጃ መሠረት በአይሮፕላን ማረፊያው ከማገት ጀምሮ በልዩ በረራ ወደ ኢትዮጵያ እስከ መላክ ድረስ ያለውን የውንብድና ሥራ በየመን በኩል ሆኖ የሠራው ቀጥታ ተጠሪነቱ ለየመን ፕሬዚዳንት የሆነው የስለላ ድርጅት ነው። በዚህም ሳቢያ የየመን መንግሥት ሊቀለበስ የማይችል እና በቀላሉ የማይፋቅ ታሪካዊ ስህተት ፈጽሟል። የየመን መንግሥትና ሕዝብ ይህን እንዲያውቁት ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀው የተግባር እንቅስቃሴ አካል ነው።
የመንን በተመለከተ የሚቀጥለው ሳምንት ዘመቻችን ግብ ቁጣችንን የየመን ፕሬዚዳንት እና የየመን መንግሥት ብቻ ሳይሆን የየመን ሕዝብም እንዲያውቅ ማድረግ ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ያህል ተጠቅሰዋል።
  1.  ለየመን ፕሬዚዳንት አዲስ መረር ያለ ደብዳቤ ተጽፎ በፋክስና በኢሜል በየመን መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶችና ኤምባሲዎች አድራሻዎች መላክ። በመልዕክት መጨናነቅ ከሚገባቸው የየመን ተቋማት አንዱ አዲስ አበባ የሚገኘው የየመን ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ሆናችሁ በዘመቻው የምትሳተፉ የሕዝብ ስልኮችን እንድትጠቀሙ፤ የኢንተርኔትና የፋክስ መልክቶችን ስትልኩ ራስን ለጉዳት በማያጋልጥ መንገድ መደረግ ይኖርበታል።
  2. የየመን ኤምባሲዎችን ሥራ ማወክ በሚችሉ ሰልፎችና ተቃውሞዎች ማጨናነቅ። የፕሬዚዳንቱን ፎቶና የአገሪቱን ባንዲራ ማቃጠል። ይህ በውጭ አገራት ብቻ መደረግ ያለበት ነው።
  3. በውጭ አገራት በየከተሞች ለሚገኙ የየመን ኮሚኒቲዎች ደብዳቤ መፃፍና መንግሥታቸውን እንዲቃወሙ መገፋፋት፤ ይህንን ካላደረጉ ግን የመናዊያን ከመንግሥታቸው ጎን ተሰልፈው በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት እንዳወጁ የምንቆጥረው መሆኑን በማያሻማ መንገድ መንገር፤
  4. በየመን አየር መንገድና በማናቸው የየመን ቢዝነስ ላይ እቀባ ማድረግ፤ በቢዚነሶቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ። ይህ ተግባር በኢትዮጵያም ከኢትዮጵያ ውጭም በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን መተግበር የሚኖርበት አቢይ ተግባር ነው።
  5. በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የየመን ቢዝነስን መርጦ ምርቶቶቻቸው እና አገልግሎቶቻቸው እንዲጠሉ ማድረግ። ከእንግዲህ በየመን ገንዘብ የተሠራ ወይም ከየመን የመጣ ብስኩትም ይሁን ሲጃራ የወገናች ደም የነካው እቃ ነው።
 ብርታኒያን በተመለከተ
የእንግሊዝ መንግሥት ማድረግ የነበረበትን እና ማድረግ ይችል የነበረውን ሁሉ አድርጓል ብለን አናምንም። እርምጃው ፈጣን አልነበረም፤ አሁንም አይደለም።
ስለሆነም እንግሊዝን በተመለከተ የዘመቻችን ግብ የእንግሊዝ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት በመንፈጉ መክሰስ እና ከአሁን በኋላም ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ እንዲከታተለውና መሪያችንን እንዲያስፈታ መወትወት ነው። የሚከተሉት ተግባራት ለአብነት ተዘርዝረዋል።
  1. የእንግሊዝ መንግሥትን በህግ መክሰስ (ይህ በንቅናቄው ጽ/ቤት የሚሠራ ነው)፤
  2. ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ደብዳቤ ጽፎ በፋክስና በኢሜል ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ለኤምባሲዎች በብዛት መላክ። አንዱ ትኩረት የሚደረግበት ኤምባሲ አዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ በዘመቻው የሚሳተፉ ወገኖች አስፈላጊው ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
  3. በለንደን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደጃፍ፤ በሌሎች አገሮች ደግሞ በእንግሊዝ ኤምባሲዎች ቁጣ የተቀላቀለበት የተቃውሞ ሰልፎችን ማካሄድ።
 ወያኔን በተመለከተ
ወያኔን በተመለከተ የሚደረጉ ትግሎች በሙሉ ወያኔን ከስልጣን ማስወገድን ያለሙ መሆን ይኖርባቸዋል። ወያኔም ለመጣል ትልቁን ድርሻ የሚያበረክተው ሕይወታቸውን ለመስጠት የቆረጡ ወገኖቻችን የሚያደርጉት ተግባር ነው፤ እንቀላቀላቸው።
በተለያዩ ምክንያቶች ወሳኙን ትግል መቀላቀል የማይችሉ ወገኖቻችን በያሉበት ሆነው ይህንኑ የሚያግዙ ተግባራት መፈጸም ይኖርባቸዋል። እነዚህ ተግባራት፣ የወያኔ ባለሟሎች በገቡበት እየገቡ በማሳፈር እረፍት በመንሳት፤ የፈፀሟቸውን ወንጀሎች በአደባባይ በመናገር እንዲሸማቀቁ በማድረግ፤ ማንነታቸው ለሸሪኮቻቸው ወይም ለሥራ ባልደረቦቻቸው በመንገር ወዳጅ በማሳጣት፣ ቢዚነሶቻቸው እንዲከስሩ በማድረግ የፋይናንስ አቅማቸውን በማዳከም ረገድ የሚኖራቸው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ሊጤን ይገባል። ከዚህ አኳያ ሊደረጉ ከሚገቡ ተግባራት የሚከተሉት በምሳሌነት ተዘርዝረዋል።
  1. በየአገሩ በተለያዩ ሽፋኖች ተሰግስገው ያለት ወንጀለኞች የወያኔ ሹማምንትና ደጋፊዎችን ለፍርድ ማቅረብ፤
  2. የወያኔ ኤምባሲዎች ሥራ መሥራት የማይችሉበት ሁኔታ መፍጠር፤
  3. የወያኔ አባላትና ደጋፊዎችን ከያሉበት (በሰፈር፣ በዩኒቨርስቲዎች፣ በንግድ የተሰማሩ ..) በማደን ማስነወር፣ ማግለል፣ ማዋረድ፤ ከእነሱ ጋር አንዳችም የንግድም ሆነ የሥራ ትብብር አለማድረግ፤ በሥራዎቻቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳዎችን ማካሄድ። ይህ ኢትዮጵያም ውስጥ በስፋት በሥራ ላይ መዋል ይኖርበታል።
  4. ለሥራ ወይም ለሽርሽር የሚዘዋወሩ ከፍተኛ የወያኔ ባለሥልጣኖችና የጦር መኮንኖችን እየተከታተሉ ማሸማቀቅ፣ ማስነወር፣ መገታተር፤
  5. የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በወያኔ መንግሥት የሚመሩ ቢዝነስች ላይ እቀባ ማድረግ፤ በእነሱ ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማድረግ። ይህ በኢትዮጵያም በውጭ አገራትም መደረግ ይኖርበታል።
  6. በዌስተር ዩኒየን እና በወያኔ ደጋፊዎች በኩል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ አለመላክ፤ በየአካባቢው አማራጭ መላኪያ መንገዶችን መፈለግ።
  7. ከወያኔ ጋር የሚሠሩ የውጭ አገር ድርጅቶች ከወያኔ ጋር ያላቸውን ሽርክና እንዲያቋርጡ መወትወት፤ አልሰማ ካሉ በቢዝነሳቸው ላይ አሉታዊ ቅስቀሳ ማካሄድ።
  8. የምዕራብ አገራት ዩኒቨርስቲዎች ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት እንዲመረምሩ ማሳሰብ። በወጉ ሳያስተምሩ ለወያኔ ሹማምንቶች ዲግሪ የሚያድሉ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማስጠንቀቅ፤ ተግባሮቻቸውን ለተማሪዎቻቸው ጭምር መንገር (ለምሳሌ University of Greenwich ከ International Leadership Institute ጋር ያለውን ግኑኝነት እንዲሰርዝ፣ እስከዛሬ የሰጣቸውንም የማስትሬት ዲግሪዎች እንዲመረመር የሚጠይቅ ደብዳቤ ጽፎ በብዛት በፋክስ መላክ፤ ተመሳሳይ ደብዳቤ Open University እና ከወያኔ ጋር ተሻርከው ለሚሠሩ ዩኒቨርስቲና ኮሌጆች መላክ)
  9. ይህ ዘመቻ ለጊዜው በወያኔ ላይ ያነጣጠረ ቢሆንም፣ የሕዝቡን የነፃነትና የፍትህ ጥረት የሚያደናቅፉ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ አገር ዜጎች በሆኑ ቱጃሮች የተያዙ ቢዝነሶችም የዘመቻው ዒላማ ሊሆኑ ይችላሉ።
በመጨረሻም የወጣቱ የማያልቅ የፈጠራ ችሎታ ከላይ በዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተቱ ሆኖም ግን ውጤታማ የሆኑ የተቃውሞ መግለጫ ዘዴዎች ያፈልቃል ብለን እናምናለን። ስለሆነም ዘመቻውን በየአካባቢው በሚገኝ ሀሳብና ፈጠራ ማዳበር ይቻላል።
ይህ ዘመቻ ወያኔን ከስልጣን ለማባረር ምድር ላይ ከምናደርገው የመረረ ትግል ጋር ሲቀናጅ የሚፈለገውን ውጤት ስለሚያስገኝ ለነፃነቱ ግድ ያለው ዜጋ ሁሉ በሙሉ ሃይሉና አቅሙ ተሳትፎ እንዲያደርግ ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራዊ ጥሪ ያቄርባል ::
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን !!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

ከግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ኃይል የተላለፈ አዋጅ

July6/2014
Ginbot 7 Popular Force Song – Ethiopiaአዋጅ አዋጅ !!! ቀን 28/10/2006

ልብ ያለው ልብ በል፤ ጆሮ ያለው ይስማ
የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በየመን መታገት አስመልክቶ አጭር መግለጫ ማውጣቱ ይታወቃል። በመግለጫችን የመን ታግዩን ልታግት የምትችልነት የጸጉር ስንጣቂ የምታክል ምክንያት እንደሌላት ሊኖራትም እንደማይችል ስለሆነም ታጋዩ ባስቸኳይ እንዲለቀቅ በተደጋጋሚ ጠይቀን፤ ይህ ሳይሆን ቀርቶ የነፃነት ታጋዩ በፋሽስቱ የወያኔ ቡድን ተላልፎ ቢሰጥ የመን የማይሰረዝ ታሪካዊ ስህተት የምትሰራ መሆኑን ሕዝባዊ ኃይላችንም የበቀል እርምጃዎችን እንደሚወስድ አሳውቀን ወያኔም ምናልባት ትግሉን አስቆማለው በሚል የሞኝ ስሌት ያደረገው ከሆነ ድርጊቱ ትግሉን በዕልህ እና በበቀል አጅቦ ከመውሰድ እና ከማፋጠን የዘለለ ትልቅ የሃሳብ አባት አንዳርጋቸው በሃገሪቱ ሰማይ ላይ የለቀቀውን የኢትዮጵያዊነት ጸረ ወያኔ መንፈስ አስሮ አሰቃይቶ ገሎ ማስቆም እንደማይችል አሳስበን አስገንዝበን ነበር:: መግለጫችን የተጻፈበት ቀለም ሳይደርቅ ግን የየመን መንግስት እንደሰጋነው ትልቁን የቁርጥ ቀን ልጅ ለወያኔ አሳልፎ መስጠቱን አውቀናል።

በእኛ እምነት አንዳርጋቸው ቀድሞ የቤት ስራውን ጨርሶል (ወጣት ዘመነ ካሴ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሀይል ቃል አቀባይ)

July 5/2014

ወጣት ዘመነ ካሴ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሀይል ቃል አቀባይ የግንቦት7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ  ስለሆኑት ስለ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታገትና ለወያኔዎች ተላልፎ መሰጠት ዙሪያ በኢሳት ሬዲዮ የተናገረው 

በእኛ እምነት አንዳርጋቸው ቀድሞ የቤት ስራውን ጨርሶል እያለቀሰ ተናግሮ ፣ እያለቀሰ ሰብኮ፣ እያለቀሰ ያለፈውን ታሪክ እያነሳ ከወደፊት አቅጣጫችን ጋር እያቀናጀ በመንገር ንጹህ ኢትዮጵያዊነትን መብት እንዲፈጠር በተለይ በእኛ በአዲሱ በወጣት ትውልድ  ንጹህ የሆነ ራዕይ እንዲኖረን በማድረግ በኩል  መስራት የሚገባውን ስራ ቀድሞ አጠናቋል ::

ምን አልባት አንዳርጋቸውን የያዙትም አካላት ወይም አስያዦቹ  አልገባቸውም እንጂ የመኝታ ቤታቸው ድረስ የሚያንኮኮና የሚንሳፈፈ የትግል መንፈስ ኢትዮጵያ ውስጥ አንዳርጋቸው ፈጠሮል::የቤተ መንግስት አትክልቶች ጋር አትክልቶች ጋር እኩይ እየተንከባከቡ የሚያሳድጉት እሾህ የሆነ የትግል መንፈስ፣ጸረ ወያኔ የሆነ የትግል መንፈስ አንዳርጋቸው ፈጥሯል:: ከተማ ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አለ,፣ ገጠር ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አy ለ ፣ደቡብ ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አለ፣አፋር ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አለ፣አዲስ አበባ ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አለ፣ አማራ ውስጥ፣ ጉራጌ ውስጥ፣ ጋምቤላ ውስጥ፣ኦሮሚያ፣ትግራይ  አፋር፣ሱማሌ ውስጥ፣ ባጠቃላይ መለው ኢትዮጵያዊ  ውስጥ የአንዳርጋቸው መንፈስ አለ::ያን መንፈስ ከቶ ማሰር አይቻልም::አንዳርጋቸውን በካቴና አስሮ ከሰነአ አዲስ አበባ መውሰድ ይቻላል አድርጋቸውን የፈጠረው ትጉህ ፣ ታታሪና ቀና የሆነውን ወጣት የኢትዮጵያዊ መንፈስ ማሰር ግን ፈጽሞ በጭራሽ አይቻልም:: አንዳርጋችው በየሂዱበት የሚወጋቸው፣ በተኙበት የሚቆረቁራቸውና የሚጎረብጣቸው መንፈሰ ጸረ ወያኔ የሆነ መንፈስ በመላው በኢትዮጵያ ወጣት ላይ ዘርቷል፣
አስቀምጦል::

አንዳርጋቸው ኢትዮጵያዊነትን ቁልጭ አድርጎ አሳይቶናል ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ በዚህ ኢትዮጵያዊነት መነጽር ፀረ ኢትዮጵያዊነት የሆነ አቋም ሁሉ እስከመጨረሻው እንታገላለን የየመን መንግስትም ሊገነዘበው የሚገባ ጉዳይ ነው አንዳርጋቸውን አስተላልፎ መስጠት ማለት አንድ በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የተፈጠረ ንጹህ ራዕይ ያለው ኢትዮጵያዊ አሳልፎ መስጠት ብቻ አይደለም አንዳርጋቸው የፈጠራቸው መንፈሶች የሚፈጥሯቸውን ቀጣይ ትውልዶች መንፈስ ጭምር የሚጎዳ እና ነገሩን ጥሩ ባልሆነ ሁኔታ ምንአልባት በቀጣይ የወደፊት የኢትዮጵያንና የየመንን ትውልዶች ግንኙነት በሚያበላሽ ሁኔታ የምናየው መሆኑን ሊያውቁት ይገባል

Saturday, July 5, 2014

የአቶ አንዳርጋቸው መስዕዋትነት ለትግላችን መፋፋም፣ ለትብብራችን ተግባራዊነትና፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት እውን መሆን ወሳኝ ምዕራፍ ነው!

July5/2014
ጋዜጣዊ መግለጫ
EYNM New Logoየኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ላይ በተፈጠረው ልብ የሚሰብር ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ፤ ይህ ፋሽስት የወያኔ/ኢህአዴግ ሥርዓት የፈፀመውን አሳፋሪና ህገወጥ አፈና በከፍተኛ ምሬት፣ ቁጭትና፣ እልህ አጥብቆ እንደሚቃወም ያሳውቃል። የጎረቤት ሃገራት አቶ አንዳርጋቸውን ጨምሮ በስደት ላይ በሚገኙ አያሌ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ የአፈና ወንጀልን በመፈፀም ንፁሃን ዜጎችን ለሰው በላው የወያኔ/ኢህአዴግ ሥርዓት አሳልፈው ሲሰጡ በተደጋጋሚ ሰምተናል አይተናልም። ድርጅታችን ይህ የወንበዴ መንግስታት አይን ያወጣ ወንጀል ነፃነቱንና ህልውናውን ለማስጠበቅ ከፍተኛ ጀግንነትንና ጀብድን በመፈፀሙ፤ ለአለም ጥቁር ህዝቦች ብቸኛው የነፃነት ምሳሌ ሆኖ በአለም አቀፍ ደረጃ ለዘመናት በክብር የኖረው መላው የኢትዮጵያ ህዝብን የናቀና ያዋረደ፤ የሃገሪቱን ሉአላዊነትና ክብር በጅጉ የደፈረ፤ ይቅር የማይባል ብሄራዊ ወንጀል መሆኑን በፅኑ ያምናል። በመሆኑም ሥርዓቱ እየፈፀመ በሚገኘው አስከፊና አሳፋሪ ወንጀል ወደፊት ከመጠየቅ በፍፁም እንደማይድንና ምናልባትም እጅግ የከፋ ዋጋ እንደሚያስከፍለው ተገንዝቦ፤ ከዚህ የወንጀል ድርጊቱ በመታቀብ አቶ አንዳርጋቸውንም ሆነ ሌሎች በተመሳሳይ መልኩ ከጎረቤት ሃገራት ታፍነው በየእስርቤቱ የሚማቅቁ አያሌ ንፁሃን ዜጎችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ ከወዲሁ በጥብቅ ያስጠነቅቃል።

አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የስደተኛው “ሲኦል ምድር ” የመን እና የእኛ ስጋት …

Andargachew TsigeJuly5/2014
እግረ መንገድ…
   ሰሞነኛው የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታገትና ወደ ኢትዮጵያ የመተላለፍ ዜና ብዙዎችን እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ሆኗል። በአረብ ሃገር የሚገኙን ጨምሮ ኢትዮጵያውያንን በመላ አለም ከአድማስ አድማስ በተቃውሞና በድጋፍ እያነቃነቀም ይገኛል። 
   
   ምሽቱን በፊስ ቡክ በ Facebook ማህበራዊ ገጽ ከተንሸራሸሩት አስተያየቶችና ወቅታዊ መወያያ ርዕሶች መካከል የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታገት ሲሰማ የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፋ እንደምትሰጥ ምንጩን ሳይነግረን መረጃ ያቀበለን የአውራምባ ታይምስ አዘጋጅ ዳዊት ከበደ ያስተላለፈው የማወያያ መጠይቅ አስገርሞ አሳዝኖኛል። ዳዊት በዚህ መጠይቁ”…አቶ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያ ፖስፖር ይዞ መቆየት የለበትም ትላላችሁ ? ” በማለት ዳዊት ራሱ ለመረጃ ቅርብ እንደሆነ ባለሙያ በአለማችን ነባራዊ ሁኔታ የነጻነት ታጋዮችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እያወቀ እንዳላወቀ ሆኖ በለቀቀው በሚመስለኝ መጠይቁ ሊያወያየን ከጅሏል…

    ወዳጀ የአውራንባው ታይምስ ጋዜጠኛ  ዳዊት Dawit Kebede ይህን ጉዳይ ሲያነሳ በዘመነ ደርግ  “ሽፍታ ፣ ወንበዴ እና ገንጣይ! ” በሚል ስም ይወገዙ የነበሩት የወያኔ መሪዎች በሃገር ቤት ፣ እውቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ፣ የኩርዱ ነጻነት ታጋይ ኦጀላንን ጨምሮ በርካታ በአለማችን የምናውቃቸው የነጻነት ታጋዮች አንባገነን የሚሉትን መንግስት ለመጣል የሃገራቸው ፖስፖርት ይዘው እንዳልነበር ጠፍቶት አይመስለኝም። ሌላው ይቅርና በኢትዮጵያ ውስጥ የኤትራውን ጨቋኝ የኢሳያስን መንግስትን ለመጣል በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሰው ቡድን መሪዎች በኤርትራ ፖስፖርት ይሆን የሚንቀሳቀሱት ?  ብየ ዳዊትን እንድጠይቀውም አድርጎኛል። ይህ በዳዊት አፍንጫ ስር ያለ መረጃ ነውና ወዳጀ ዳዊት እንዲፈትሸው በማሳሰብ ዳዊት የአቶ አንዳርጋቸውን እንቅስቃሴ የማይደግፍ ከሆነ እንደ ዜጋ በግልጽ የራሱን ሃሳብ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ እንደሆነ የወንድም ምክሬን መክሬዋለሁ። በእኔ በኩል ግን ከላይ በሰጠው የወረደ ማወያያ ሃሳብ መነሻ ሚዛናዊነት መጉደል አካሄዱ ስላላማረኝም። ይህም በመሆኑ ወዳጀ ጋዜጠኛ ዳዊት ያነሳው ማወያያ ሃሳብ አላስደሰተኝም!  … ዳዊት የጀመረው ተራ ብሽሽቅ እንጅ መረጃ ቅበላ አልመሰለኝምና አዝኛለሁ! እግዚአብሔር ዳዊትንም እኛንም ይታረቀን ብየ ብዘለው ይሻለኛል: ( ከመነሻ እግረ መንገዴ ይህን ካልኩ ወደ የመን ሰሞነኛ እርምጃ እና እርምጃው ወዳስከተለው ስጋት በጨረፍታ ላምራ …

     የየመን መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት “ቀንደኛ” ተፈላጊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በማገትና በማስተላለፉ ረገድ ያሳየው ፍጥነት ብዙዎችን አስገርሟል። ላለፉት አስርት አመታት በየመን ምድር ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ ግፍ በኢትዮጵያውያን ላይ ሲፈጸም ተመልካች የሆነው የየመን መንግስት የዛሬ አርምጃ ፍጥነት ብዙዎችን አስገርሟል።

   ያልታደሉ ስደተኞች ኢትዮጵያውያን ግፍ ከተበራከተባቸው አረብ ሃገራት መካከል የመንን የሚተካከላት የለም። ግፍ ተፈጽሞባቸው እዚህ ሳውዲ አረቢያ ያገኘኋቸው ግፉአን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በየመንን ምድር እንደ እንስሳ ተቆጥረው ያዩትን የስደትና እንግልትና እገታ ሲገልጹት “የሲኦል ምድር!” ማለት ይቀናቸዋል።  ስደተኛ ወገኖቻችን ዛሬ ድረስ በየመን ከተማ ፣ጉራንጉሮችና በየበርሃው የከፋ በደል እየተፈጸመባቸው ለመሆኑ የአደባበይ ሚስጥር በመሆኑ ዋቢ የሚያሻው አይደለም። የኢህአዴግ መንግስት  በኢኮኖሚ ሰደተኞች በሆኑ ዜጎቹ ላይ በየመን ምድር የሚፈጸመውን ግፍ ተቃውሞ አርባና ያለው እርምጃ መውሰድ ባለመቻሉ እስካሁን ያለው የስደተኞች ይዞታ አሳሳቢ እንደሆነ ቀጥሏል ።  በግዛት መሬቱ ላይ በዜጎቹ ግፍ ሲፈጸምብን መገደብ የተሳነው የየመን ስንኩል መንግስትም ቢሆን አለም አቀፍ ህግጋትን አክብሮ የወሰደው ቅንጣት እርምጃ ካለማሳየቱ በተዛማጅ የዛሬ አቶ አንዳርጋቸውን የማስረከብ እርምጃ ለኢትዮጵያ ሰላም በማሰብ ሳይሆን የፖለቲካ ጥቅምን ለማጋበስ የወሰደው እርምጃ ነው በሚል ብዙዎችን ቂም አስቋጥሯል።  

     በየመን በሽዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በግፍ በየባህሩና በርሃው ወድቀው ሲቀሩ የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮች የዜጎቻቸውን መብት ሲያስከብሩ አይተን ለማናውቅ ዜጎች የመንና ኢትዮጵያ  “አሸባሪ! ” ያሏቸውን ግለሰብ በታገቱበት ጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ሃገር ቤት ማስተላለፋቸው ዜና መሰማቱ ብዙዎቻችን አስደምሟል። ይህ ያልተጠበቀ ክስተትና በየመን የተወሰደ የማስተላለፍ እርምጃን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በየአቅጣጫው የተለያየ አስተያየት በመስጠት ላይ ናቸው። በርካታ ነዋሪዎች  ” አቶ  አንዳርጋቸውንና የሚመሩትን ድርጅት ስም ማንሳት በወንጀለኝነት ያስቀጣል ” የሚለውን ማስጠንቀቂያ እየጣሱ መንግስት “በአሸባሪነት ” ስለፈረጃቸው የቀድሞ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ የመጣው ይምጣ በሚል አንድምታ ድፍረት በተቀላቀለበት መንገድ ዋንኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

  በኢትዮጵያ መንግስት  “ነውጠኛ አሸባሪ ” የተፈረጁት እና በኢህአዴግ ላይ ጦር የሰበቀው የግንቦት 7 ድርጅት” አራጊ ፈጣሪ ናቸው” የሚባሉት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ” ለዲሞክራሲና ነጻነታቸው የተጉ፣ ብርቱ አርበኛና ታጋይ !” እያለ ከንፈሩን የሚጥላቸው እና የሚያደንቋቸው ብዙ ነዋሪዎች አጋጥመውኛል። የመንግስት ደጋፊዎች በበኩላቸው “ትልቁ አሳ ወጥመድ ውስጥ ገብቷል!” ብለው ያምናሉና ጮቤ ከመርገጥ ባለፈ በትምክህት ” እኛ እንዲህ ነን! ” በሚል በኩራት ሲናገሩ አድምጫለሁ  ! በማህበራዊ ድረ ገጾችና በሰሚ ሰሚ ወሬው ደርሶት አስተያየት ላለመስጠት የሚሸሸው ነዋሪ ብዙ ቢሆንም በሆነው ሁሉ ያደረበትን ስጋት ከመግለጽ የተቆጠበ ግን የለም ። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታገትና ለኢትዮጵያ መንግስት መተላለፍ ከተደሰቱት ውጭ ያለው ብዙ ነዋሪ የበቀል እርምጃ እንደሚፈጽሚ ሲዝቱ ተስተውሏል። 

     “ዲሞክራሲና ሰብአዊ መብትን አላስከበራችሁም !” በሚሉ ተቃዋሚ ቡድኖችና ” በሁለት አስርት አመታት ዲሞክራሲን አስፍኛለሁ፣ ሰብአዊ መብት አስከብሬያለሁ! ” በሚለው ኢህአዴግ መካከል አመታት የዘለቀው መጓተት ባመጣው ጣጣ በርካቶች “ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ !” በሚል ዘብጥያ ወርደዋል። አቶ አንዳረጋቸውም ቢሆን በኢህአዲግ ላይ ጠንስሰዋል በተባለው መፈንቅለ መንግስት በሌሉበት የሞት ፍርድ የተበየነባቸው መሆኑ ሲታወስ “ተይዘው ወደ ኢህአዲግ እጅ  ተላልፈዋል !” የመባሉ ዜና በቀል አስቋጥሮ ፣ በዛቻና ፉከራው ታጅቦ ዳግም በፖለቲካ ትርምስ ፍጥጫ እንዳይከታትና ኢትዮጵያን ወደ ሌላ የመጠፋፋት አዙሪት እና ብጥብጥ እንዳይዶላት በነዋሪው ላይ ታይቶ የማይታወቅ ስጋት አጭሯል ። 
   
  አዎ !  አረብ ሃገራት እንዲህ ናቸው ፣ በአረብ ሃገር  ያለን ስደተኞች መከራ ብዙ ነው :( እኔም የሃገሬ ህዝብ በነቂስ ስለሚነጋገርበት ሰሞነኛ አጀንዳ ቢያገባኝ ይህችን ታክል መረጃ አቀብል ዘንድ ነፍሴ ፈቅዳለች ። ከዚህ ባለፈ መጻፍና መናገር ግን አቅሙ የለኝም ልበል ይሆን? 

እስኪ ቸር ያሰማን !

ነቢዩ ሲራክ

ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር እርምጃ እወስዳለሁ አለ

July 5, 2014
ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር/ኢሕአግ/የተሰጠ መግለጫ


የማፈኛ መዋቅሩን መሰረት በማድረግ በርካቶች ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን እጅግ በከፋና በሚዘገንን ሁኔታ በማጥፋት እኩይ ተግባሩ የሚታወቀው አረመኔው የወያኔ ስርዓት በአገራችን የተንሰራፋውን መጠነ-ሰፊ ተግዳሮት ከመሰረቱ ለመንቀል በሚደረገው ትግል ብርቱ ጥረትና እንቅስቃሴ ሲያደርጉ በነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከየመን መንግስት ጋር በማበር የአንድን ሰው ከአገር አገር የመንቀሳቀስ መብት በመጣስ የየመን መንግስት ለወያኔው ማስረከቡ አጥብቀን የምናወግዘውና የምንቃወመው ሲሆን ድርጅታችን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ በደረሰው አፈና መሰረት በማድረግ ማንኛውንም አይነት እርምጃ የምንወስድ መሆናችንን አበክረን እናስታውቅለን።

ለአገርና ለወገን ዕድገት ብልጽግና ሲሉ በመታገላቸው ሳቢያ የየመን መንግስት እሳቸውን አፍኖ በማስረከቡ ምክንያት አገር ውስጥ እየተካሄደ ያለውን ትግል ለአንድም ደቂቃ ቢሆን የሚገታው አለመሆኑን እብሪተኛው ቡድን ሊረዳው ይገባል።በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በደረሰው የተቀነባበረ አፈና ዛሬ ላይ መግለጫ የማውጣታችን ምክንያት ጉዳዩ እስኪረጋገጥ በሚል እንጂ ቀደም ባሉት ቀናቶች መግለጫ ማውጣት ይጠበቅብን እንደነበረ እናምናለን ስለሆነም መላው የአገራችን ለውጥ ናፋቂ ወገናችን ሁሉ ይሄንኑ ሃሳባችንን በቅጡ እንዲረዳልን እናስገነዝባለን።

እንደ አንድ ታጋይና አታጋይ እሳቸውን በተቃውሞ ትግል ማጣታችን ቃላት ሊገልጸው ከሚችለው በላይ በውስጣችን ቁጣን ፈጥሯል ። አገዛዙ አቶ አንዳርጋቸውን ከየመን መንግስት መረከቡ ለውጥ ናፋቂው ሕዝብ በፍርሃት ተሸብቦ ለትግል እንዳይነሳሳና ማንኛውም ተቃዋሚ የትም ሄደ የትም ከገባበት ገብተን በእጃችን ለማስገባት የሚያስችለን የዲፕሎማሲ ግንኙነት አለን በሚል ስጋት ለመፍጠር የተሰራ ቀመር ስለመሆኑ ለማንም የተሰወረ አይደለም ።

ትምተኛውና ዘራፊው ቡድን ያልተረዳው ነገር ቢኖር ሕዝቡ ለሚያነሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች ትኩረት ሰጥቶ በማዳመጥ አግባባዊ በሆነ መልኩና ሕዝቡን ተጠቃሚ ሊያደርግ በሚችል መልኩ ምላሽ እስካልሰጠ ድረስ በማፈን፣ በማሳደድ፣ በማዋከብና በመግደል የሚመጣ መፍትሄ አለመኖሩን ብቻም ሳይሆን በሕዝብ ላይ የሚወሰዱ ጭፍን ኢ-ሰብአዊድርጊቶች በጨመሩ ቁጥር ስርዓቱ ራሱን ወደ መቃብር ጉድጓድ እያስጠጋ እንዳለ ሊረዳው ይገባል።

አንድነት ሃይል ነው!
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/
ሰኔ 28 -2006 ዓ/ም

አዜብ መስፍን በጠና ታመዋል፤ የአባዱላ ገመዳ ልጅ አረፈ – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

July5/2014
ከባለቤታቸው ህልፈት በኋላ ከፖለቲካው መድረክ እየተገለሉ የመጡት ወ/ሮ አዜብ መስፍን በጠና መታመማቸውን ቅርበት ያላቸው ታማኝ ምንጮች አስታወቁ። በስኳር ህመምና በደም ግፊት እየተሰቃዩ የሚገኙት አዜብ መስፍን የሰውነት ክብደታቸው እንደቀነሰና የመጎሳቆል ሁኔታ በገጽታቸው እንደሚታይ የጠቆሙት ምንጮቹ ለስኳር በሽታ በየእለቱ ከሚወስዱት መድሃኒት በተጨማሪ ለደም ግፊትም እንክብሎችን እንደሚወስዱ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። አዜብ በመኖሪያቸው አብዛኛውን ቀናት እንደሚያሳልፉ የጠቆሙት ምንጮቹ በፖለቲካው የደረሰባቸው ኪሳራ ብስጭት ውስጥ እንደከተታቸውና ለበሽታ እንደዳረጋቸው አያይዘው ገለጸዋል።
ቦሌ ከሳይ ኬክ ቤት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ የሚገኘውና አቶ ስዩም መስፍን ለ19ዓመት የኖሩበት እንዲሁም አቶ ሙክታር ከድር ለሁለት አመት የኖሩበት መኖሪያ ቪላ ውስጥ የሚኖሩት አዜብ መስፍን ከዚህ በተጨማሪ ቦሌ ሩዋንዳ መታጠፊያ ላይ የሚገኘውን የቀድሞ የደህንነት ቢሮ ለአዜብ በቢሮ መልክ እንደተሰጣቸው ምንጮቹ ጠቁመዋል።
azeb
ቀን ቀን በዚህ ቢሮ ለብቻቸው ያሳልፉ የነበሩት አዜብ መስፍን በጠና ከታመሙ ወዲህ ላለፉት አምስት ሳምንታት ወደዚህ ቢሮ ገብተው እንደማያውቁና በቤታቸው እንደሚያሳልፉ ያስታወቁት ምንጮቹ አክለውም ፓርቲው በሚያካሂዳቸው ስብሰባዎች መገኘት እንዳቆሙና ለመጨረሻ ጊዜ የተገኙት ከሁለት ወር በፊት ኢህአዴግ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚሁ ጉባኤ ከተሰብሳቢው ኋላ ለብቻቸው ተቀምጠው የታዩት አዜብ ምንም ሳይናገሩና አስተያየት ሳይሰጡ ስብሰባውን ከመጨረሳቸው ባሻገር ከስተውና ተጐሳቁለው እንደነበር ምንጮቹ አስታውሰው ከዚያ ወዲህ ህመሙ እየጠናባቸው እንደሄደ አያይዘው ገለፀዋል። አዜብ የባለቤታቸውን ቦታ በመተካት የጠ/ሚ/ርነቱንና ፓርቲውን የመምራት እቅድና ምኞት በተቀናቃኛቸው ስብሃት ነጋ ከከሸፈባቸውና የሚተማመኑባቸው የደህንነት ባለስልጣናትና የፓርቲው ቁልፍ ሰዎች እስር ቤት መወርወርና መባበረር ለከፍተኛ የሞራል ድቀትና ለበሽታ እንደዳረጋቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። አዜብ የኤፈርት ኤክስኪውቲቭ ዳይሬክተር ተብለው ቢሰየሙም ምንም አይነት የአመራር ሚና እንደሌላቸው የጠቆሙት ምንጮቹ በነስብሃት ተመድበው ተቋሙን ሲመሩ የቆዩት አቶ ብርሃነ ኪዳነማርያም ወደ ራዲዮና ቴሌቪዥን ስራ አስኪያጅ እንደሆኑና ከርሳቸው በኋላ ደግሞ የአርከበ እቁባይ ታናሽ ወንድም ጌታቸው እቁባይ እየመሩት መሆኑን አያይዘው ገልፀዋል።
ከአዜብ ጋር በተፈጠረ ያለመግባባት ከኤፈርት ለቀው የቆዩት ጌታቸው እቁባይ የአቶ መለስ ዜናዊን ሞት ተከትሎ እንዲመለሱ መደረጉን አመልክተዋል። አዜብ ወደ ትግራይ -መቀሌ ከተጓዙ 6 ወር እንዳለፋቸው አክለዋል። በኤፈርት ውስጥ የአዜብ ደጋፊዎች በነስብሃት ተለቅመው መውጣታቸውን ያስታወሱት ምንጮቹ በቅርቡ ኤክስኪውቲቭ ዳይሬክተር የሚለውን የአዜብ ስልጣን በመግፈፍ ሊያባርሯቸው መሆኑን አረጋግጠዋል። …ይህ በእንዲህ እንዳለ የአባዱላ ገመዳ ልጅ ወጣት ኮሚያስ አባዱላ ከዚህ አለም በሞት እንደተለየ ታውቋል። የ26 አመቱ ወጣት ኮሚያስ አባዱላ በጉበት በሽታ ምክንያት ወደ ታይላንድ- ባንኮክ ተልኮ ለአንድ አመት ሲታከም ከቆየ በኋላ ሊድን ባለመቻሉ ከአራት ሳምንት በፊት ህይወቱ አልፏል። በባንኮክ ለአንድ አመት የሆስፒታል ቆይታው ለህክምና ብቻ ከ880ሺህ ዶላር ወጪ እንደተረገለት ታውቋል። በተመሰሳሳይ ሶስተኛ ታናሽ እህቱ (የአባዱላና ራሄል ልጅ) ከአምስት አመት በፊት በገጠማት የሳንባ፣ የአንጀትና የአእምሮ በሽታ በባንኮክ ሆ/ል ለሁለት አመት ህክምና የተከታተለች ሲሆን፣ ለህክምናው ጠቅላላ የወጣው 2.5ሚሊዮን ዶላር እንደሆነ ከዚህ ቀደም ይፋ በተረገው መረጃ መገለፁ ይታወሳል። ይህ ሁሉ ገንዘብ ከህዝብ የተዘረፈ ለመሆኑ አያጠያይቅም። ይህቺ ናት አገሬ! ..ለማንኛውም የአባዱላ ወንጀል ልጁን አይመለከተውም። ወጣት ኮሚያስ በአባቱ ድርጊት ነፃናነት ስለማይሰማው – በየእለቱ አልኮል ይጠጣና ይበሳጭ እንደነበረ ቅርብ የሆኑ ጓደኞቹ ተናግረዋል። የጉበት በሽታውም መንስኤ ይኸው ነው። 

ኢሳት ከኢትዮጵያ ውስጥ በሚደወሉ የስልክ ደወሎች መጨናነቁን እየገለጸ ነው።

July 4, 2014
ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም በፌስቡክ ላይ ባስቀመጠው መልክት ላይ በርካታ በሽዎች የሚቆጠሩ ስልኮች የቴሌቪዥን እና ሬዲዮ ጣቢያውን ማጫናነቁን ሲገልጽ ስልክ በመመለስ ተጠምደን ነው የዋልነው በርካታዎቹ ግንቦት 7 አሁኑኑ ለመቀላቀል እና የጀግናውን አንዳርጋቸው ጽጌን ሃሳብና ፍላጎት ለማሳካት መዘጋጀታቸውን እየገለጹ ነው። በሁሉም እድሜ ክልል የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ስልክ በመደወል ማዘኑና መቆጨቱን እየገለጸ ሲሆን ሁላችንም አንዳርጋቸው ነን የሚሉ መፈክሮችን ሁሉ እያስቀመጡ ነው።
በተያያዘ ዜና ግንቦት 7 ትግሉ ይፋ መጀመሩን አስታውቋል። ከአዲስ አበባ በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ የህወሃት/ ወያኔ ባለስልጣናት ከዚህ ጋር በተያያዘ ስብሰባ ላይ መቀመጣቸውን ያረጋገጥን ሲሆን ይህም ከፍተኛ የሆነ የፌድራል ሰራዊቱን የማዘጋጀትና በተጠንቀቅ እንዲሆን ለማዘዝ መሆኑን ዘግቢያችን ጨምሮ ተናግሯል። በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ምንም አይነት ከወትሮው የተለየ እንቅስቃሴ ባይኖርም በአብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን በየቤቱ እየተነጋገረ መሆን በተዘዋወረበት መንደሮች ለመረዳት ችሏል። በቦሌ ክፍለ ከተማ መድሃኒያለም አካባቢ ፍሪ አንዳርጋቸው ጽጌ የሚል ጽሁፍ በአውቶብስ መጠበቂያ ተጽፎ መመልከቱንም አክሎ ዘግቦል።
bole_church_ethiopia
ይህ በእንዲህ እንዳለ የወያኔ መንግስት በሀገርና ከሀገር ውስጥ እየተነሳ የመጣውን ቁጣ ሽሽት በሚመስል አንዳርጋቸው ጽጌን አላየሁትም የሚል ወሬ እያስወራ ነው።
ይህ ጠንካራ ታጋይ ወያኔዎቹ ከዚህ በኋላ እያንዳንዷን ጣቶቹ እንኳን እየቆረጡ መግደል ቢጀምሩ አንዳርጋቸው እየሳቀባቸውነው የሚሞተው ያሉት ዶ/ር ብርሃኑ ከዚህ በኋላ ትግሉን ወያኔዎች አስጀምረውታል እየሞትን ልንገድልም ዝግጁ ነን። የኢትዮጵያ ህዝብ ለአንዳርጋቸው አታልቅሱ የጀመረውን ትግል ከግብ አድርሱ ያኔ ነው አንዳርጋቸውን የምታስደስቱት። አንዳርጋቸው ስራውን ጨርሶ ተቀምጧል። ማየት የሚፈልገው ልጆቹን ነው። ሲሉ ተናግረዋል፡፡
10409455_647654315329663_5484929445468543318_n


    የህዝባዊ ሃይሉን ተጠሪ ለማናገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካልንም።