Friday, March 7, 2014

ወያኔ በግንቦት 7 ስም ሠላማዊ ዜጎችን ማሰቃየቱን ባስቸኳይ ማቆም አለበት

march7/2014

ባለፉት አራትና አምስት አመታት በግልጽ እንዳየነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እኩልነቱን፤ መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የሚያደርገዉ ትግል ጫና በፈጠረበት ቁጥር ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የራሱን ህገመንግስት የሚደፈጥጡ ህጎች አርቅቆ አያጸደቀ ሠላማዊ ዜጎችን አስሯል፤ ገድሏል ከአገር እንዲሰደዱም አድርጓል። ለምሳሌ በ2003 ዓም የኢትዮጵያ ፓርላማ ከቤተመንግሰት የተላለፈለትን ትዕዛዝ አክብሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነፃነት መከበር የሚታገለዉን የግንቦት 7 ንቅናቄ ሽብርተኛ አድርጎ ፈርጇል። ይህ ፈር የለቀቀ ፍረጃ ደግሞ ወያኔ የሱን ዘረኛ ስርዐት የሚቃወሙ ግለሰቦችን፤ ሀሳባቸዉን በነፃነት የሚገልጹ ዜጎችን፤ ጋዜጠኞችን፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና ከወያኔ ጋር አናብርም ያሉ ወጣት ኢትዮጵያዉያንን “ግንቦት ሰባቶች” ናችሁ እያለ በጅምላ እያሰረ እንዲያሰቃይ ህጋዊ ሽፋን ሰጥቶታል። ለምሳሌ ከፍትህና ከነጻነት ጥማት ዉጭ ከግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለዉን የፖለቲካ ፓርቲ መሪዉን አንዱአለም አራጌን፤ ታዋቂዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና መምህርት ርኢዮት አለሙን የግንቦት 7 አባላት ናቸዉ የሚል ሰንካላና መሠረተ ቢስ ክስ መስርቶ ለረጂም ዘመን እስራት ዳርጓቸዋል።
ወያኔ እንደ ዛሬዉ ከተማ ዉስጥ ሆኖ ሥልጣን ሳይቆጣጠር ገና ጫካ ዉስጥ እያለ ጥርሱን ከነከሰባቸዉና ከተቻለ አጠፋቸዋለሁ ካለዚያም አሽመደምዳቸዋለሁ ብሎ አስራ ሰባት አመት ሙሉ ከተዘጋጀላቸዉ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የአማራ ብሄረሰብ ነዉ። በለስ ቀንቶት ሥልጣን ከጨበጠ ማግስት ጀምሮም በወሎና በጎንደር በኩል ከትግራይ ጋር የሚያዋሰኑ ሰፊ የሆነ ለም መሬቱን ጠቅልሎ በመውሰድ ዘረኛ ሥርዓቱን ዕድሜ ሊያራዝሙልኛል ይችላሉ ብሎ የሚተማመንባቸውን የቀድሞ የትግል አጋሮቹንና ካድሬዎቹን አስፍሮበታል:: ይህ በደልና ግፍ አልበቃ ብሎትም ቀደምቶቹ የኢትዮጵያ ገዥዎች ለፈጸሙት ግፍና የአስተዳደር በደሎች ሁሉ አማራዉን በጅምላ ተጠያቂ የሚያደርግ ፕሮፖጋንዳ እነሆ እስከዛሬ በመርጨት ለዘመናት በሠላም ከኖረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በጠላትነት እንዲተያይ አድርጎታል:: በወያኔ አጋፋሪነት በበደኖ ፡በአርሲ በአረካና ሌሎች አካባቢዎች አማራው ላይ በግፍ የተፈጸመው ጭፍጨፋና ከ2004 እስከ 2005 ዓም አማራዉን ከጉራፈርዳና ከቤንሻንጉል ለማፈናቀል የተወሰደው እርምጃ የዚህ የወያኔ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ውጤት መሆኑን የምስት የለም::
ሟቹ መለስ ዜናዊና በህይወት የሚገኙ ቀንደኛ የወያኔ መሪዎች የተጠናወታቸው የአማራ ጥላቻ በጸረ ፋሽስት ዘመቻ ወቅት ባንዳ ከነበሩ አባቶቻቸዉና አያቶቻቸዉ የተወረሰ ፋሽስት ጣሊያን ለደረሰባት ሽንፈት በዘርና በሃይማኖት ተከፋፍለን እርስ በርሳችን እንድንጠፋፋ ተክላብን የሄደቺው ተንኮል አካል ነው ::
የዚህ የጥፋት አጀንዳ አስፈጻሚ የሆነው ወያኔ የጀመረውን አገር የማፍረስና ህዝብ የመከፋፈል አጀንዳ ለማሳካት በየክልሉ የተኮለኮሉ ምስሌኔዎች እንወክለዋለን በሚሉት ህዝብና ክልል ላይ እየፈጸሙት ያለው በደልና ሰቆቃ አዲስ ምዕራፍ በያዘበት በአሁኑ ወቅት እራሳቸዏን ለባርነት አዋርደው ህዝባቸውን በማዋረድ ላይ የሚገኙት የብአዴኑ አለምነህ መኮንንን የመሳሰሉ ሆድ አደሮች ውርደት በቃን ዘረኝነት በቃን ብለው በተነሱ ዜጎች ላይ እየወሰዱ ያለው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እጅግ አሳሳቢ ሆኖአል::
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና ሞክራሲ ንቅናቄ ከሰሞኑ በደረሰው መረጃ ወያኔ ከአማራው ቀምቶ በትግራይ ክልል ባስገባቸው ወረዳዎች ላይ የሚኖሩ ንጽሃን ዜጎች ለምን በወያኔ የግፍ አገዛዝ ትማረራላችሁ እየተባሉ በወያኔ ታማኝ ሚሊሻዎች
እስር እንግልትና ድብደባ እየተፈጸመባቸው መሆኑን አረጋግጦአል:: በዚህ በአዲስ መልክ በተጀመረዉ የወያኔ የጥቃት ዘመቻ መሳሪያ ያነገቡ የህወሃት ሚሊሻዎች ከክልላቸዉ ዉጭ ወደ ተለያዩ የአማራ ከተማዎችና ወረዳዎች ሰርገዉ እየገቡ የእነሱን ቋንቋ የማይናገረዉን ሁሉ የግንቦት 7 ተላላኪዎች ናችሁ በሚል እያሰሩ በመደብደብ ላይ ናቸዉ።
ይህ በመሆኑ ዛሬ አትዮጵያን ከሱዳንና ትግራይን ከጎንደር ጋር በሚያዋስኑ የአማራ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ገበሬዎች እጃቸዉ እርፍ ከሚጨብጥበት ግዜ በወያኔ ሰንሰለት የሚታሽበት ግዜ ይበልጣል፤ የመንግስት ሰራተኛዉና የከተማ ነዋሪዉም ቢሆን አብዛኛዉን ግዜ የሚያጠፋዉ ከወያኔ ካድሬዎች ጋር ግምገማ በመቀመጥ ሲሆን ተማሪዉና ወጣቱ ህብረተሰብ ደግሞ “መጡ አልመጡም” እያለ ሌሊቱን የሚያሳልፈዉ በየጫካዉ እየተሸሸገ ነዉ።
የዚህ አይነት አስከፊ ግፍና መከራ በአፋር ፡ በጋምቤላ በኦጋዴንና በኦሮሚያ በሚኖሩ ዜጎቻችን ላይ ሲፈጸም ቆይቶአል:: ? ወያኔ እራሱ አርቅቆ ባጸደቀውና በሐምሌ ወር 1987 ዓም በስራ ላይ የዋለዉ የወያኔ ህገ መንግስት ኢትዮጵያ በዘጠኝ የፌዴራል ክልሎች መከፈሏንና እያንዳንዱ ክልል እራሱን በእራሱ የማስተዳደር መብቱ የተረጋገጠ እንደሆነ ይደነግጋል። በዚህ ህገ መንግስት መሠረት እያንዳንዱ ክልል የራሱ ቋንቋ፤ የአስተዳደር ማዕከልና እንዲሁም የክልሉን ሠላምና ጸጥታ የሚያስከብር የፖሊስ ኃይል ይኖረዋል ይላል። ታድያ ለምንድነዉ እያንዳንዱ ክልል የራሱ ፖሊስ ኃይል አያለዉ ከትግርኛ ቋንቋ ዉጭ ሌላ ቋንቋ የማይናገሩ የህወሃት ታማኝ ሚሊሻዎች አማራ ክልል ዉስጥ እየገቡ አማራዉን የሚያሰቃዩት?
መልሱ ቀላል ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ህዝባዊ አምቢተኝነቱ እያየለ በመጣና የነጻነት ኃይሎች ጡንቻ በፈረጠመ ቁጥር ወያኔ አንገቷ ላይ ቀጭል እንደታሰረባት በቅሎ ይደነብራል። የደነበረ ደግሞ መራገጡ አይቀርምና መሳሪያ ያነገቡ ኃይሎችን እንቅስቃሴ እገታለሁ በሚል ከንቱ ጥረት ደንባራዉ ወያኔ የፈሪ በትሩን በድንበር አካባቢ በሚኖሩ የአማራ ክልል አርሶ አደሮች፤ ወጣቶችና ሠራተኞች ላይ ማሳረፍ ጀምሯል።
ወያኔ እንደ ግንቦት ሰባት የኮነነዉና የህዝብና የአገር ጠላት አድርጎ የሳለዉ ድርጅት የለም፤ የወያኔ የዜና ማሰራጫዎችም ይህንን የአገዛዙን አቋም በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ህዝብ አሰምተዋል።የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ማን ለመብቱና ለነጻነቱ እንደቆመና ማን መብቱና ነጻነቱ ላይ እንደቆመበት ለይቶ የሚያዉቅ ህዝብ ነዉ። ስለዚህም ግንቦት ሰባት ወያኔዎች አላፊዉንና አግዳሚዉን “ግንቦት ሰባት” ነህ እያሉ ከሚያሰቃዩ፤ ህዝብንና ግንቦት ሰባትን ያስተሳሰረዉ ነጻነት፤ ፍትህና ዲሞክራሲ ነዉና የኢትዮጵያን ህዝብ ጥያቄ ቢመልሱ ለእነሱም፤ ለእኛም ለአገርም ይበጃል የሚል የጸና እምነት አለዉ። ወያኔ በኢህአዴግ ስም ያሰጠጋቸዉን ምሰለኔዎች ጨምሮ ከራሱ ዉጭ ሌላ ማንንም አያምንም፤ ስለዚህም ነዉ የአገሪቱን የመከላከያ፤ የደህንነትና የፖሊስ ተቋሞች በራሱ ሰዎች ቁጥጥር ስር ያደረገዉ። ዛሬ በግልጽ እንደምንመለከተዉ ወያኔ በጉልበት ለያዘዉ ስልጣን ያሰገኛል ብሎ በሚጠረጥረዉ ቦታ ሁሉ የራሱን ልዩ ሚሊሺያ እየለላከ የኢትዮጵያን ህዝብ መኖሪያ ቤቱ ድረስ አየሄደ እያጠቃ ነዉ። ግንቦት ሰባት ወያኔና የፈጠረዉ ዘረኛ ስርዐቱ የቆሙት በፍጹም ማንሰራራት የማይችሉበትት የመጨረሻ መቀበሪያ ጉድጓዳቸዉ ጫፍ ላይ ነዉ የሚል ጽኑ እምነት አለዉ። ሆኖም ጉድጓድ ጫፍ ላይ የቆመ ጠላት በራሱ ተወርዉሮ ጉድጓዱ ዉስጥ አይገባምና ይህንን የተዳከመ ጠላት እተፈራገጠ ጉዳት ከማብዛቱ በፊት ለመደምሰስ ክንዳችንን አጠናክረን በህብረት እንደ አንድ ሰዉ እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

በፈረንሳይ ፓሪስ ከጎዳና ተዳዳሪነት ያወጡትን እናትና ልጅ ገድሎ ተሰወረ!

march7/2014

እናትና ህጻን ልጅዋን ገድሎ የተሰወረው ሰውዬ ትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን በፈረንሳይ ፓሪስ ክርተማ የጎዳና ላይ ተዳዳሪ ነበር:: ሟች ወ/ሮ ክውን ገዳሙ ትባላለች:: ከቤትዋ ወደ ስራ ቦታ ሲመላለሱ ተጠርጣሪውን የዩታል:: በጎዳናው የተጎሳቆለውን ሰው(ጉዳዩ በህግ ስለተያዘ ስሙን እዚህ ላይ አንጠቅሰውም) ስለሚያሳዝናቸው ባለፉ ባገደሙ ቁጥር እጃቸውን ይዘረጉለት ነበር::

ከግዜ በኋላ ከክረምቱ ብርድ እንዲገላገል ሲሉ ይህንን የጎዳና ተዳዳሪ ለግዜው በቤታቸው አስጠጉት:: የአቅማቸውን እየረዱት አብረው ለወራት ኖሩ::

ባለፈው ሳምንት አንድ አስደንጋጭ ክስተት በቤተሰቡ ውስጥ ተፈጸመ:: በችግሩ ያስጠጉት ሰው ከተኙበት በጭካኔ ገድሏቸው አመለጠ::

ወ/ሮ ክውን ገዳሙ የሶስት ልጆች እናት ሲሆኑ በፈረንሳይ ፓሪስ ለረጅም ግዜ ኖረዋል:: የሶስት ልጆች እናትም ናቸው:: ያለአባት ከሚያሳድጓቸውን ሶስት ልጆች ውስጥ አንደኛዋና የሁሉም ታናሽ ከሆነችው ጋር ላይመለሱ ይህችን አለም ባለፈው ሳምንት ተሰናበቱ::

ገዳዩ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በጩቤ ሰነጣትቆ ነው እናትና ልጅን ለህልፈት የዳረገው- እንደ ፈረንሳይ የዜና ምንጭ:: ባጎረሱት እጅ ተነከሱ:: ደግ ባደረጉ ምላሹ ግድያ ሆነ: ለዚያውም አረመኔያዊ ግድያ::

ነብሰ ገዳዩ ለግዜው ተሰውሯል:: የፈረንሳይ ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር በመሆን ጉዳዩን በጥብቅ ይዞታል:: እኛም እየተከታተልን ጉዳዩ ምን እንደደረሰ እናቀርብላችኋላን::
ክንፉ አሰፋ

መንግስቱ ኃይለማርያም ደርግ ከሱዳን ጋር በድንበር ጉዳይ የተፈራረመው ሰነድ የለም አለ

march7/2014

ሰሞኑን የወያኔወች ተላላኪ ኃይለማርያም ደሳለኝ በኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ የኢህአዴግ መንግስት ከሱዳን ጋር በድንበሩ ጉዳይ እየተዳደረና ተግባራዊ እያደረገ ያለው የቀድሞወች የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መንግስት እና የደርግ መንግስት ተፈራርመውት የነበረውን ነው ብሎ ተናግሮት የነበረውን አስመልክቶ የደርግ መንግስት ከሱዳን ጋር ምን የተፈራረመው ነገር አለ ተብሎ ለቀረበው ጥያቄ መንግስቱ ኃይለማርያም መልስ ሲሰጡ ምንም የተፈራረምነው ነገር የለም። ኃይለማርያም እና ወያኔ ውሸታሞች ናቸው። ደርግ ከሱዳን ጋር የተፈራረመው ሰንድ ካለ ለምንድን ነው ወያኔወች ሰነዱን ለህዝብ ይፋ የማያደርጉት ሲሉ መንግስቱ ኃይለማርያም መልሰው ጠይቀዋል።

መንግስቱ ኃይለማርያም ሰለ ኢትዮ፡ሱዳን ድንበር ጉዳይ የሰጠውን ቃለ መጠየቅ ሙሉውን ከዚህ ላይ ያዳምጡ

ሰላማዊ ወይስ የትጥቅ ትግል ወይስ ማንፈራጠጥ – መስፍን ወልደ ማርያም

March 6/2014

የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤

አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን ለይቶ ለመረዳት ችግር ሆኖ ቆይቶኣል፤ በሌላ አነጋገር ሰላማዊ ትግል በሀሳብ፣ በንግግር፣ በተለያዩ ሀሳብን ለማስለወጥ መቀስቀሻ በሚሆኑ መንገዶች ተቃውሞን መግለጽ ነው፤ በአንጻሩ የትጥቅ ትግል በጠመንጃ ወይም በጉልበት ያለውን የአገዛዝ ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ ሙከራ ነው፤

ሁለት፣ እንዲህ ከሆነ በሰላማዊ ትግል ለሚያምኑ ሰዎች ያለምንም ጥርጥር በተለያዩ ዓላማዎችና ዘዴዎች ላይ መከራከርና ሀሳብን ማጥራት አስፈላጊ ነው፤ በሰላማዊ ትግል ተግባር አለ ቢባልም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የድጋፍ ወይም የተቃውሞ አቅዋሞችን ከማሳየት አያልፍም፤ አገዛዞች ጃዝ! ብለው ውሻና ፖሊስ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ሲለቁ የጉልበት ጥርስና ዱላ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያርፋል፤ ጉዳት ይደርሳል፤ ሰላም ይቃወሳል፤ በሕዝብና በአገዛዙ መሀከል ቂም ይጀመራል።

ሦስት፣ የትጥቅ ትግል ደግሞ በተዋረድ በሚተላለፍ ትእዛዝ የሚፈጸም ግዴታ ነው፤ በትጥቅ ትግል ጉልበተኛ ከጉልበተኛ ጋር፣ ብረት ከብረት ጋር ይጋጠማል፤ የሰው ልጅ ለእርድ ይቀርባል፤ በሕይወታቸው በልተው ያልጠገቡ ምስኪኖች ለጥቂት ሰዎች የሥልጣን ጉጉት ይታረዳሉ፤ ያለቀባሪ በጅብና በአሞራ ይበላሉ፤ ዕድለኞች የሚባሉት እጆቻቸው፣ ወይም እግሮቻቸው ተቆርጠው፣ ወይም ዓይኖቻቸው ጠፍተው፣ ወይም ከዚህ ሁሉ የባሰ ጉዳት ደርሶባቸው በሕይወት የሚቀሩት ናቸው፤ ከነዚህ በሕይወት በቀሩት የጦር ጉዳተኞችና በጦርነቱ ላይ በሞቱት መሀከል የትኛው የተሻለ አንደሆነ የሞቱት ባይናገሩም ጉዳተኞቹ ይናገራሉ፤ ‹የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ!› እያሉ።

አራት፣ ሁለቱ የትግል ስልት ዓይነቶች በባሕርይ የተለዩ ናቸው፤ አንዱ ሌላውን የሚደግፍ አይደለም፤ ሰላማዊ ትግል የትጥቅ ትግልን ለመደገፍ ሰላማዊ የሚለውን ስያሜ መጣል አለበት፤ የትጥቅ ትግልም ሰላማዊ ትግልን ለመደገፍ ትጥቅ የሚለውን ስያሜ መተው አለበት፤ ሰላማዊ ትግልና የትጥቅ ትግል አራማጆች ድል ቢያደርጉ ማን ወንበሩ ላይ እንደሚወጣ ሳይታለም የተፈታ ነው፤ ጠመንጃ የያዘው ሥልጣኑን ሲይዝ ሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል! ያውም ከተፈቀደለት!

በኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ ታሪክ አርበኞች ሳይቀሩ በሩ ተዘግቶባቸው ለደጅ ጥናት እንደተዳረጉ አይተናል፤ መልኩን ለወጥ ቢያደርግም ደርግን ከተፋለሙት ውስጥ በአዲስ አበባና በአስመራ ወንበሮች ላይ ሲወጡ የተሸነፉት ወይ ለወያኔ ገብረው ሎሌነት ገቡ፤ ወይም በአሜሪካ መሽገው ያቅራራሉ፤ ዘመኑ እንዳለፈባቸውም ገና አልተረዱም።

አምስት፣ ሰላማዊ ትግልና የትጥቅ ትግል ሁለቱም ብርቱ ቃል ኪዳንን ይጠይቃሉ፤የቃል ኪዳናቸው ልዩነት አንዱ እስከሞት ለመታገል፣ ሌላው ደግሞ እስከመግደልና እስከመሞት ለመታገል መሆኑ ነው፤ ለሰላማዊው ትግል ከፍተኛ መንፈሳዊ ወኔ የሚያጎናጽፈው ለመግደል ያለው ተቃውሞ ነው፤ ሕይወትን ለማልማት ሕይወትን መቅጠፍ የአስተሳሰብም የመንፈስም ጉድፍ ያለበት ሥራ ነው።

የሰላማዊ ትግል ዋናውና ቀጥተኛው ተልእኮ ሕዝብን ለሥልጣን ባለቤትነት ማብቃት ነው፤ ሥልጣንን ለመያዝ አይደለም፤ ስለዚህም ኢላማው ሕዝብ ነው፤ በሥልጣን ወንበሩ ላይ ያሉት የሰላማዊ ትግሉን የሚቃወሙት በሕዝብ ዘንድ ተሰሚነትና ተቀባይነት እንዳያገኝ ለማድረግ ነው፤ ሰላማዊ ትግሉ የሚያተኩረው በሕዝቡ ጆሮ፣ አእምሮና ልብ ላይ ነው፤ አገዛዙ በበኩሉ ጸጥ-ለጥ ብሎ የሚገዛለት ሕዝብ እውቀቱ ዳብሮ፣ መብቶቹን ሁሉ ተገንዝቦ፣ በሕግ ለሕግ እንጂ ለሰው አልገዛም በማለት ልቡ እንዳይሸፍት አፈናውንና ማነቆውን በማጠናከር እያደነቆረ ለመግዛት ይፈልጋል፤ የሰብአዊ መብቶችን የሚያስተምሩና በአገዛዙ አካላት የሚፈጸሙትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያጋልጡ ድርጅቶችን ማዳከም ወይም ማጥፋት ለአገዛዙ አስፈላጊ የሚሆነው ለዚህ ነው፤ ኢሳት የሚባለው የቴሌቪዥንና የራድዮ ፐሮግራም ለወያኔ የውስጥ እግር እሳት የሆነበት ለዚህ ነው፡፡ በሰውነት ደረጃ ሕዝቡ መብቶቹን ሁሉ እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ፣

በዜግነት ደረጃ ሕዝቡ ለሥልጣን የሚያበቃውን የዜግነትና የፖሊቲካ መብቶች እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ፣ ሕዝቡ የሰውነትና የዜግነት መብቶቹን ተገንዝቦ በአገዛዝ ስር አልተዳደርም የማለት መንፈሳዊ እምቢተኛነት እንዲያድርበት ማድረግ፣ በግልጽ ጭቆናን የሚጠላና ለመብቶቹና ለነጻነቱ በቆራጥነት የሚቆም ሕዝብ እንዲፈጠር ማበረታታት፣ መብቶቹንና የሥልጣን ባለቤትነቱን የተረዳና ከጭቆና ጋር የተጣላ ሕዝብ በፖሊቲካ መስመር ቡድኖችን እየፈጠረ እንዲደራጅ ማድረግ፣ ያወቀና የነቃ፣ በፖሊቲካ መስመር የተደራጀና ማናቸውንም ዓይነት ጭቆና የሚጠላ ሕዝብ ለማንም ጉልበተኛ የማይንበረከክ ሕዝባዊ ኃይል እንዲሆን መጣር፣

የትጥቅ ትግል ዋናውና ቀጥተኛው ተልእኮ በሥልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ አውርዶ ወንበሩን ለራሱ ለመውሰድ ነው፤ ይህንን ሲያደርግ ሕዝቡን ወደጎን ትቶ ወይም ዘልሎ ነው፤ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ በጠመንጃ ሥልጣን የሚይዙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥልጣኑን ለሕዝብ እናስረክባለን፤ ትክክለኛ ምርጫ እናካሂዳለን በማለት ሕዝቡን በተስፋና በጠመንጃ ይዞ ነው፤ ነገር ግን ሥልጣንን ሕዝብ ለፈቀደው አስረክበው ከቤተ መንግሥት ሲወጡ አናይም፤ ሲሸሹ ወይም ሬሳቸው ሲወጣ እንጂ።

ብዙውን ጊዜ የማይታሰብ ወይም ብዙዎች የሚዘነጉት የሁለቱ ትግሎች የገንዘብ ወጪ በጣም ከፍተኛ ልዩነት ያለው መሆኑን ነው፤ ሰላማዊ ትግል በሕይወትም፣ በንብረትም፣ በመሣሪያም በዝግጅትም የሚያስከፍለው ዋጋ ከትጥቅ ትግል ጋር ሲወዳደር በጣም አነስተኛ ነው።

ስለዚህም በሁለቱ በተለያዩ ስልቶች አራማጆች መሀከል የሚደረግ ክርክር ምን ዓይነት ነው? የሰላማዊው የመጀመሪያ ደረጃ ኢላማው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፤ የትጥቅ ትግል የመጀመሪያ ደረጃ ኢላማው የወያኔ አገዛዝ ነው፤ በሌላ አነጋገር በሰላማዊ ትግል ሕዝቡ በሰላማዊ ትግል ትንሽም ቢሆን የነጻነትን አድማስ ለማስፋት እንዲችል ድፍረትን በማስተማር በኩል የማይናቅ አስተዋጽኦ ቢያደርግም አገዛዙን የመነቅነቅ ኃይል ገና አላዳበረም፤ አንድም ውጤት አላሳየም፤ የትጥቅ ትግሉ ከፉከራና ከሽለላ እስካሁንም አልወጣም፤ የሰላማዊ ትግል ዓላማ ሕዝቡ መብቶቹን እንዲያውቅ ለማንቃትና ለመብቶቹ እንዲታገል የሚያስችለውን ብቃት ለማስጨበጥ ነው፤ ስለዚህም ዘዴው በሕዝቡ ላይ ነው፤ የትጥቅ ትግሉ ዘዴ አገዛዙን በጉልበት ገልብጦ በዚያው ባልተለወጠ ሕዝብ ላይ ሌላ አገዛዝ ለመመሥረት ነው።

በኢትዮጵያ ለውጥ እናመጣለን የሚሉ ሁሉ የቆሙበትንና የቆሙለትን ዓላማና ዘዴ በግልጽ ተገንዝበው ካልተሰለፉ በተንፈራጠጠ አስተሳሰብ የተባበረ ተግባር ሊገኝ አይችልም።



Listen Audio : Colonel MENGISTU HAYLEMARIAM talking about Ethi- Sudan border dispute with ESAT

March6/2014

Ethiopia’s former president, Colonel Mengistu Hailemariam, denied on Thursday any border deal with neighboring Sudan during his presidency.

The former president in his interview with ESAT on Thursday said that Ethiopia didn’t sign any border deal with Sudan let alone with the Derg regime, but also with the earlier two regimes who ruled the country before he came to power.

The late Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi and the current PM, Hailemariam Desalegn, repeatedly claims that the former regimes have signed a border deal with Sudan.
Ethiopia recently signed a deal with Sudan to make a border demarcation based on what it claims to have been reached by the former regimes.

“There was no any border agreement that have been made during the emperor Menelek,or Hailesilassie’s ruling as well as during my presidency. I don’t really understand why the current regime is lying,” said the former president,Mengistu Hailemariam.

Mengistu also asked the current Ethiopian government to make public the “evidence”, which it claims to have been signed by the former regimes.

“The public has the right to ask the regime for such kind of documents. Let the government show this document for its citizen,” added the former president.
It was to be recalled that officials of the two countries have a signed in December 2013 a border demarcation deal.

The agreement, according to media reports from Sudan, is expected to be implemented soon.
Following the border deal, many Ethiopian scholars are expressing their anger over the deal saying that the agreement will give Ethiopia’s land to Sudan.(ESAT

http://ethsat.com/ESAT-Radio-player/archive/ESAT_Radio_Thu_06_Mar_2014.mp3
http://ethiopianewsforum.com/viewtopic.php?f=2&t=73985

Thursday, March 6, 2014

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችን በማጣቱ የትምህርት ክፍሉ አደጋ ላይ መውደቁን እያሳዘናቸው መሆኑን የታሪክ መምህራንና ተመራማሪዎች ገለፁ

March 6, 2014

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችን በማጣቱ የትምህርት ክፍሉ አደጋ ላይ መውደቁን እያሳዘናቸው መሆኑን የታሪክ መምህራንና ተመራማሪዎች ገለፁ። ሀገሪቱ ጥንታዊና መካከለኛ ታሪኮች ባለቤት ብትሆንም በአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው የታሪክ የትምህርት ክፍል ሊዘጋ መቃረቡ እያነጋገረ ነው።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል የሚያስተምሩ መምህራንና የታሪክ ተመራማሪዎች “ታሪክ ዳቦ አይሆንም” በሚል የተሳሳተ አመለካከትና የ70/30 የትምህርት ፖሊሲ የፈጠረው ችግር መሆኑን በመግለፅ አሰራሩን አምርረው ተችተዋል። ከታሪክ በላይ ዳቦ የሚሆን የለም። ታሪክ የአንድ ሀገር የማንነትና የእውቀት መሠረት መሆኑ እየታወቀ የትምህርት ክፍሉ በተማሪ እጦት በአደጋ ላይ መገኘቱ እንደሚያስቆጣቸው መምህራኑና የታሪክ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል። ሰሞኑን ዩኒቨርሲቲው የታሪክ ትምህርት የተከፈተበትን 50ኛ ዓመት ባከበረበት ወቅት በ2006 ዓ.ም አንድም የታሪክ ተማሪ ያልተመዘገበበት መሆኑ አሳፋሪም አሸማቃቂም መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያዎቹ ችግሩን ለማስተካከል ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቀዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ፕሬዝዳንት ዶ/ር በለጠ ብዙነህ ስለጉዳዩ ተጠይቀው የታሪክ ትምህርት ክፍሉ እየተዳከመ መምጣቱን አምነዋል። ለዚህም በዋናነት የሚጠቀሰው ምክንያት በታሪክ ትምህርት የሚመረቁ ተማሪዎች በመስኩ ስራ አናገኝም በሚል አመለካከት ዲፓርትመንቱን ባለመምረጣቸው ነው ብለዋል። ከዚህ ባለፈ በታሪክ ትምህርት የተመረቁ ተማሪዎች የታሪክ መምህር የመሆን ፍላጎት ባለማሳደራቸው ወደ ሌሎች ትምህርቶች እያተኮሩ በመሆኑ ነው ብለዋል። ዩኒቨርስቲው በ70/30 ፕሮግራም መሰረት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጠቅላላው በማኅበራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ በ2006 የትምህርት ዘመን ወደ 600 ብቻ ተማሪ መመዝገቡን ያስታወሱት ዶ/ር በለጠ እነዚሁ 600 ገደማ ተማሪዎች በሶሻል ሳይንስ ለ20 ዲፓርትመንቶች መከፋፈላቸውን ነው ያስረዱት። ከዚህም ውስጥ ተማሪዎቹ የተሻለ የሥራ ዕድል ወደሚያስገኝላቸው የትምህርት አይነት ነው የሚያተኩሩት ብለዋል።


የታሪክ ትምህርት መዳከም እንደ ሀገር ስለሚያመጣው ተፅዕኖ የተጠየቁት ዶ/ር በለጠ፤ ተፅዕኖ መፍጠሩ አይቀሬ መሆኑን ይስማሙበታል። ነገር ግን በመላው ሀገሪቱ በቅርቡ በተከፈቱ 32 ገደማ ከሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ወደ 17 ዩኒቨርሲቲዎች የታሪክ ትምህርት ስላላቸው በዘርፉ የሚመረቁ ተማሪዎችን ቁጥር በአንፃራዊነት ሊደግፈው እንደሚችል ተናግረዋል። ነገር ግን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያለው ሁኔታ ግን የታሪክ ትምህርት የሚማሩ ተማሪዎች ቁጥር ማነስ ግን አስጊ መሆኑ ተናግረዋል። ሁኔታውም በዚሁ ከቀጠለ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ የታሪክ መምህራን ላናገኝ የምንችልበት አደጋም ይታየኛል ብለዋል። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የታሪክ ትምህረት እንደ አንድ የትምህርት አይነት እየተሰጠ በመሆኑ በዩኒቨርሲቲዎች ያለው የታሪክ ተማሪዎች እጥረት መታየቱ ወደፊት የታሪክ መምህራን ላናገኝ እንችላለን ሲሉም ዶ/ር በለጠ ስጋታቸውን ገልፀዋል።


ከአመለካከት ጋር በተያያዘ “ታሪክ ዳቦ አይሆንም” የሚለው አተያይ ችግር መፍጠሩን የጠቀሱት ዶ/ር በለጠ የታሪክ ትምህርት ከገበያና ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጋር ብቻ የተያያዘ በመሆኑ ይሄንን አመለካከት ለመለወጥ ብዙ መስራት እንዳለብን እንረዳለን ብለዋል። በቀጣይም የክፍለ ትምህርቱን ህልውና ለማስቀጠል የmajor/miner ፓኬጅ ማጠናቀር እንደሚገባ ጠቅሰዋል። ለምሳሌ ታሪክን በዋናነት ተምሮ ጋዜጠኝነት ወይም ቋንቋን በሁለተኛ ደረጃ እንዲማር በማድረግ የስራ አማራጭን ለመፍጠር መሞከር አለበት ብለዋል። አሁን ባለው የካሪኩለም ሁኔታ የmajor/miner ፓኬጅ አለመኖሩ ለተማሪዎቻችን አማራጭ እንድንሰጣቸው አላደረገም ብለዋል።


የሀገሪቱ ታሪክ በአግባቡ ባልተጠናበትና ባልተተነተነበት ሁኔታ የታሪክ ትምህርቱ መዳከሙ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። ገዢው ፓርቲ ከሚመራበት ልማታዊ አቅጣጫም ጋር በማያያዝ የታሪክ ትምህርት መዳከሙን የሚተቹም አካላት አሉ።

(ሰበር ዜና) መርዝ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ አረፉ

March 6/2014

'

ዘ-ሐበሻ እንደዘገበው መርዝ ተሰጥቷቸው ነው ለዚህ የበቁት የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ለህክምና ብዙ ገንዘብ ወጣባቸው በሚል ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከስልጣናቸው እርሳቸው ባላወቁበት በፈቃዳቸው እንደለቀቁ ተደርጎ የተነገረባቸው የኦሮሚያው ክልል ፕረዚዳንት ኦቦ አለማየሁ አቶምሳ በተሰጣቸው የተመረዘ ምግብ ምክንያት የጀመራቸው በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ ጸንቶ በተደጋጋሚ በተለያዩ ሃገራት ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ግን በባንኮክ ታይላድ ለህክምና በሄዱበት ሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል።

በ45 ዓመታቸው በታይላንድ ባንኮክ ሕይወታቸው ያለፈው ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ በምን ምክንያት የተመረዘ ምግብ እንደተሰጣቸው ባይታወቅም ከርሳቸው ጋር ምግቡን በልቶ የነበረ ግለሰብም እስካሁን በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ለዘ-ሐበሻ ቅርብ የሆኑ የኦነግ የመረጃ ምንጮች “ኦህዴድን የድሮው ኦህዴድ እንዳይሆን ሊያደርጉ የሚችሉ ሰው ስላልነበሩ በሕወሓቶች መርዝ እንዲሰጣቸው ተደርጓል” የሚል አመለካከት ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሕወሓት አቶ ዓለማየሁን ቀጠፋቸው ሲሉ ይተቻሉ”፡
ከየካቲት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በባንኮክ ህክምና ላይ የከረሙት በምስራቅ ወለጋ ቢሎ ቦሼ ወረዳ ከአባታቸው አቶ አቶምሳ ሚጃ እና ከእናታቸው ወይዘሮ አየለች ብሩ በ1961 ዓ.ም ተወለዱት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ሕይወታቸው በእንዲህ ያለ ሴራ ማረፉ በኢሕአዴጎች መካከል አለመተማመንን ሊፈጥር እንደሚችል የተለያዩ የፖለቲካ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።



የኦህዴድ/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አቶ ዓለማየሁን “ላለፉት 24 ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ እና መላው የአገሪቱ ህዝቦች ዛሬ ለደረሱበት የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ተጠቃሚነት እንዲበቁ በቁርጠኝነት የታገሉ ነባር ታጋይ ነበሩ” ካለ በኋላ በ1981 ዓመተ ምህረት የደርግን ስርዓት ለመገርሰስ ሲካሄድ የነበረውን የትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውን፣ ከ1988 እስከ 1994 ድረስም የኦህዴድ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት እና የድርጅቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ማገልገላቸውን፣ ከ2002 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውን ጠቅሷል። ሆኖም ግን ድርጅቱ እንደተጠበቀው አቶ አለማየሁ በተመረዘ ምግብ መሞታቸውን ከሴራው በስተጀርባ ማን እንዳለ ያስቀመጠው ነገር አለመኖሩን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ለዘ-ሐበሻ በደረሱ መረጃዎች ቀጣዩ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ማሞ ይሆናሉ የሚለው ግምት ሚዛን እየደፋ ነው።

Wednesday, March 5, 2014

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ

March 5/2014

UDJየአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት እ.ኤ.አ በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተፈፀሙ ያላቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሪፖርት ተመልክተነዋል፡፡ በሪፖርቱ የተካተቱት የመብት ጥሰቶች አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በተደጋጋሚ ያጋለጣቸው እና ከፍተኛ ትግል እያደረግንባቸው የሚገኙ አስከፊ ተግባራት እንደሆኑ ቢታወቅም የቆምንለት ዓላማ እና እየታገልነው ያለው ስርዓት በሌሎች ዘንድም ድርጊቱ የታወቀ መሆኑን ያረጋገጥንበት ነው፡፡ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በሪፖርቱ ያካተታቸው እንደተጠበቁ፣ የተፈጸሙ እና እየተፈጸሙ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከዚያም የላቁ እንደሆኑ አንድነት በተጨባጭ ያውቃል፡፡
የኢህአዴግ መንግሥት ዜጎችን በማፈን፣ ሚዲያዎችን በመዝጋት፤ ለህግ የበላይነት ቁብ በማጣት፤ ድብቅ በሆኑ እስር ቤቶች ዜጎችን በማጎር፤ በጥርጣሬ ያዝኳቸው የሚላቸውን ዜጎች በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ በማስገደድ፤ በማሰቃየት፤ በማስፈራራት፤ በመግደልና አስገድዶ ከሀገር በማሰደድ የተመሰከረለት ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከገዥው የኢህአዴግ መንግሥት የተለየ አመለካከት ያላቸውና ስርዓቱን የሚተቹ ዜጎች የመከራ ገፈት የሚጋቱባት ሀገር እንደሆነች መቀጠሏም ከዜጎቿም ሆነ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ የተሰወረ አይደለም፡፡
ቀደም ሲል በግፍ ታስረው ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አንዷለም አራጌ እና ናትናኤል መኮንንን ከመሳሰሉ ብርቱ ሰላማዊ ታጋዬቻችን በኋላ እንኳን በቅርቡ የፓርቲያችን የቀድሞ ዋና ፀሐፊና የአሁኑ የብሔራዊ ም/ቤት አባል የሆኑት አቶ አስራት ጣሴ ሃሳባቸውን በመጽሔት ጽፈዋል ተብለው ለእስር መዳረጋቸው የስርዓቱ አፋኝነት መቋጫ ያጣ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሌላኛው አባላችን አቶ አለማየሁ ለፌቦ ከፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማግስት ጀምሮ ወደ ደቡብ ክልል ሲመለሱ የፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ለ27 ቀናት መታሰራቸው፤ በኦሮሚያ በደቡብ እና በሰሜናዊት ኢትዮጵያ በተለየ ሁኔታ አባሎቻችን በአመለካከታቸው ብቻ ከስራ እየተፈናቀሉ መሆኑ፤ ጋዜጠኞች እና የሙስሊሙ ማህበረሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ዛሬም በእስር ላይ መሆናቸው፤ ከዚህ በተጨማሪ ሙስና፤ የመሬት ቅርምት፤ የዜጎች መፈናቀል እና ህገ ውጥ አሰራር በበኩሉ ከስርዓቱ ጋር የተገነባ መሆኑ ሀቅ ነው፡፡
በሪፖርቱ የተዘረዘሩትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መድገም ባያስፈልግም በዚህች ሀገር የተንሰራፋው ህገ ወጥነት ይቀየር ዘንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ የሲቪክ ተቋማት፤ ድፕሎማቲክ ማህበረሰቡ እና የሚመለከተቸው አካላት ህጋዊ በሆነ ሁኔታ በመንግሥት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ ይህ ሁሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ባለበት ‹‹ጤነኛ እንደሆነ መንግሥት ›› ራሱን ለመቁጠር እንደሚያስቸግረው እንረዳለን፡፡ በመሆኑም የፖለቲካ ምህዳሩን ለሁሉም እኩል በማድረግ፤ የፀረ ሽብር፤ የፕሬስ፤ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት ማደራጃ፤ ህጎችን በመቀየር፤ የሊዝ አዋጁን እና በተሻሻለው የወንጀለኛ መቅጫ የተካተተውን የፕሬስ ነጻነት የሚገፋ አንቀጽ በመሰረዝ፤ ከዴሞክራሲና የፍትሕ ተቋማት ላይ እጁን በማንሳት ከሚመጣበት የህዝብ ቁጣም ሆነ የታሪክ ተወቃሽነት ቢያመልጥ መልካም ነው እንላለን፡፡ አንድነት፣ በሀገራችን ያሉትን የፖለቲክ ችግሮች በዉይይት ለመፍታት በኢሕአዴግ እና በተቃዋሚዎች መካከል ሁሉም አሸናፊ የሆኑበትና ቅንነት ያለበት ውይይት እንዲደረግ፣ ፍላጎት እንዳለው በተደጋጋሚ በገለጸው መሰረት፣ ኢሕአዴግ ወደ መሃል ሜዳ መጥቶ ለዉይይት እንዲዘጋጅም እንጠይቃለን።
በሪፖርቱ የተዘረዘሩ እና ሎችም የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በሚመለከት ግን በተለይ የተወካዮች ምክር ቤት፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮምሽንና የእንባ ጠባቂ ተቋማት ከፓርቲ ወገንተኝነት በፀዳ መልኩ መርምረውና አጣርተው የመብት ጥሰት የፈጸሙትን የመንግስት አካላት ለፍትህ ማቅረብ ግዴታቸው መሆኑን አንድነት ፓርቲ ያሳውቃል፡፡
ከሁሉም በላይ ዋነኛ የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆናችሁ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያላችሁ መላው የሀገራችን ዜጎች ሰፊው ህዝብ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት እንጂ ከጥቂት አምባገነን መሪዎች መብት የሚለምን አለመሆኑን በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ስርዓቱን ለመታገል በአንድ ድምጽ ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
የአሜሪካ መንግሥትም ቢሆን አንዲህ ዓይነቱን ከአሜሪካ ባህልና እሴት ጋር የሚቃረኑ ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተደጋጋሚ በየዓመቱ ሪፖርት ከማውጣት ባሻገር ትርጉም ያለው ጫና በማሳደር ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ለዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት መከበር ሊቆም ይገባል ብለን እናምናለን፡፡
ዘለዓለማዊ ክብር ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን!!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
የካቲት 26 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ መንግስትን በጎዳና ነውጥ መናድ፤ አዲሱ የኃይል ፍጥጫ

March 5/2014
የዓለም መገናኛን ብዙሃንን ተቆጣጥረው የሚገኙ ሶስት ሀገሮች አሉ። እነሱም ሶሪያ፣ ቬኑዝዌላ እና ዩክሬን ናቸው። እነዚህ ሀገሮች በተለይ የምዕራቡ ዓለም የዕለት ዕለት የዜና መረጃ ፎጆታዎች ናቸው። በእነዚህ ሀገሮች ውስጥ የሚደረጉ ማንኛውም ዓይነት የነውጥ እርምጃዎች የሚዘገቡት ወደ ዴሞክራሲያዊ የመንግስት ምስረታ የሚደረጉ የለውጥ ጉዞዎች ተደርገው ነው። ለዚህ ማረጋገጫ ለማቅረብ፣ ይህን ጽሁፍ እያነበበ ያለ ማንኛውም አካል አልጀዚራን፣ ቢቢሲ፣ ሲኤንኤን፣ ፎክስ ወይም የዩሮ ቻናሎችን በመከታተል ማረጋገጥ ይችላል።
እነዚህ የሚዲያ አውታሮች ለምን ማንኛውንም በእነዚህ ሀገሮች ውስጥ የሚደረጉ የጎዳና ነውጥ እንቅስቃሴዎችን ከዴሞክራሲያዊ ይዘት ጋር አስተጋብረው ይዘግባሉ? የሚል ጥያቄ ለሚያነሳ አካል መልሱ ብዙም አስቸጋሪ ወይም ውስብስብ አይደለም። ምክንያቱም ሚዲያውን በባለቤትነትና በቁጥጥር በያዙ አካሎች እንዲሁም የሚዲያ ተቋማቱን በገንዘብ ምንጮችነት በሚያሳድሩት አካሎች የሚደረግባቸው የዜና አደረጃጀት እና አዘጋገብ መመሪያዎች ጫና አማካኝነት የሚፈጠር መሆኑን ከግንዛቤ ስለሚወሰድ ነው።
EDWARD S. HERMAN and NOAM CHOMSKY “The Political Economy of the Mass Media” በሚል በፃፉት መጽሃፍ ላይ በአንድ የሚዲያ ተቋም ውስጥ መዋቅራዊ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ምክንያቶችን አስፍረዋል። ይህም ሲባል፣ “Structural factors are those such as ownership and control, dependence on other major funding sources (notably, advertisers), and mutual interests and relationships between the media and those who make the news and have the power to define it and explain what it means.”
ከላይ ከሰፈረው ፍሬ ነገር አንፃር መዋቅራዊ ተፅዕኖ በአንድ ሚዲያ ላይ ማሳረፍ ለምን አስፈለገ? የሚዲያ ተቋምን መቆጣጠር፣ የዜና አደረጃጀትና አዘጋገብን ላይ ተፅዕኖ ማሳደር እንዲሁም የሚዲያ ተቋሙን በልሂቃን ትንታኔ የሚዘውሩ ባለሙያዎችን በየቦታው መፍጠር ለምንስ አስፈለገ? የዜና አደረጃጀትና አዘጋገብ ለምንስ በሶስተኛ ወገኖች ፍላጎት ይቀረፃል? የሚዲያ ተቋም በመርህ ደረጃ ለጋዜጠኝነት መርህ ወገንተኛ መሆን ሲገባው ለምንስ ለሶስተኛ ወገኖች ያድራል? ሕገመንግስታዊ ስርዓት በጎዳ ነውጥ እንዲፈርስ ለምን ሚዲያ አይነተኛ ሚና ሲጫወት ይስተዋላል? ሌሎችም ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል።
ለተነሱትና ሌሎች ለሚነሱት የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ ለማቅረብ ጥልቅ ጥናት ያደረጉ ብዙ የምርመራ ተቋሞች አሉ። ከተደረጉት ጥናቶች ለመረዳት እንደሚቻለው፣ በአንድ ሚዲያ ተቋም ውስጥ መዋቅራዊ ተፅዕኖ ማሳረፍ የሚያስፈልገው ሚዲያ ተቋሙ በወጥነት በሚፈበርከው የመረጃ ፍሰት ሕብረተሰብ ውስጥ የሚፈለገውን አስተሳሰብ ለማስረፅ እና ሃሳቡም ቅቡልነት እንዲያገኝ ለማስቻል ነው። ወይም በግርድፉ ናዖም ቾሞይስኪ እንደሚለው “MANUFACTURING CONSENT” ለመፍጠር ነው።
ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነው፣ የምዕራቡ ዓለም እና ሩሲያ ፌዴሬሽን በዩክሬን ውስጣዊ ፖለቲካ የያዙት አቋም እና የዓለም ዓቀፉ አውራ የመገናኛ ብዙሃን የዘገባ አፈበራረክን መመልከት ተገቢ ነው። ሩሲያ ከምታነሳው የብሔራዊ ጥቅም አንፃር የተፈጠረውን ሁኔታ ብንመለከተው የዘገባዎችን ውስጣዊ የታሸ እምቅ ይዘት ለመረዳት ቀላል ያደርገዋል። ከዴሞክራሲያዊ መርህ አንፃር ስንመለከተው የምዕራቡ ዓለም የሚከተለውን የመንታ መንገድ ፖለቲካ ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
ለምሳሌ የግብፅ መንግስት በሱዳን ወይም በኤርትራ መንግስታት ላይ መፈንቅለ መንግስት በማድረግ የስርዓት ለውጥ በመዘርጋት ለግብፅ ብሔራዊ ጥቅም ያደረ የአሻንጉሊት መንግስት በእነዚህ ሁለት ሀገሮች ውስጥ ቢመሰርት የኢትዮጵያ መንግስት እና ሕዝብ አቋም ምን ሊሆን ይችላል? የሚመሰረቱት የአሻንጉሊት መንግስታት ዋና ስራቸው ሊሆን የሚችለው፣ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ማንኛውንም እርምጃ መውሰድ ነው። ይህን ተልዕኮ እንዲፈጽሙ የግብፅ መንግስት የመጀመሪያው ስራ የሚሆነው፣ በሕገወጥ መንገድ የተመሰረቱትን መንግስታትን ሕጋዊ ሽፋን በማልበስ የሕዝብ ውክልና ያላቸው መንግስት ማድረግ ነው። ይህም ሲባል በዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት በሁለቱ ሀገሮች የተደረገውን የስርዓት ለውጥ የሀገሮቹ የዴሞክራሲ ሂደት የመጀመሪያው መጨረሻው መሆኑን በስፋት ማዘገብና ቅቡልነት እንዲኖራቸው ማስቻል ነው።
በተነፃፃሪነት ለመመልከት የምዕራቡ ዓለም በተለይ የአሜሪካና የአውሮፓ ሕብረት ከዚህ በፊት ኢራንን ለማንበርከክ የመጀመሪያ ስራቸው የነበረው በሶሪያ ውስጥ የስርዓት ለውጥ ማምጣት ነበር። ይህን ፍላጎታቸውን በፈለጉት መልኩ ማስኬድ ባይችሉም አብዛኛውን የሶሪያ ክፍለ ግዛት መሰረተ ልማቶች ወደ ነበር ቀይረውታል። ሁለተኛ እቅዳቸው ሊባኖስን በማፈራረስ የሶሪያና የኢራን አጋር የሆነውን ሂዝቦላን ማዳከም ከተቻለ በማያባራ የነውጥ መረብ ውስጥ መጨመር ነው። ይህን ሁለተኛው እቅዳቸውን በአጥፍቶ ጠፊዎች በኩል በተገቢው መልኩ እየተገበሩት ይገኛሉ። ይህን መሰል ኢ-ዴሞክራሲዊ አማራጮች የሚጠቀሙት የዓለም ዓቀፍን ኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም ፍላጎት ለማስፈጸም መሆኑ ቢታወቅም፣ ዓለምን በተቆጣጠሩበት የኮርፖሬት ሚዲያ አማካኝነት የሶሪያ ሕዝብ ለዴሞክራሲ መንግስት ምስረታ የሚያደርገው ዴምክራሲያዊ ትግል ተደርጎ በስፋት ተዘግቧል፤ እየተዘገበም ይገኛል። በዚህም ሳያበቁ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የአልቃይዳ ክንፍ በሆነው የሽብር ቡድን አማካኝነት የሶሪያ ሕፃናት በኬሚካል ጦር መሳሪያ እንዲረግፉ እና የበሽር አል አሳድ መንግስት አለም አቀፍ ውግዘት እንዲደርስበት ተጠቅመውበታል።
የሶሪያ የስርዓት ለውጥ ውጥናቸው መቋጫ ሳያገኝ ባሳለፍነው ሳምንታት ውስጥ ደግሞ በዩክሬኗ ኬቨ ከተማ በኩል ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን የሚያደርሳቸውን መንገድ ጀምረዋል። ይህን መንገድ ልዩ የሚያደርገው እንደሌሎቹ በእጅ አዙር (proxy war) የሚደረግ ጦርነት ሳይሆን ከሩሲያ ፌዴሬሽን ቀጥተኛ የጦርነት አደጋ የተጋረጠበት ሁኔታ መፈጠሩ ነው። ከዚህ የጦርነት ፍጥጫ በላይ የምዕራቡ ዓለም የመንታ መንገድ አካሄድ ግምት ውስጥ የጣለው በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠውን የዩክሬን መንግስትን በጎዳና ነውጠኞች በአደባባይ ሲፈርስ እያዩ አለማውገዛቸው እንዲሁም ይህን የነውጥ ቡድን ሕጋዊ መንግስት መሆኑን በይፋ ማወጃቸውና ዲፕሎማሳዊ ግንኙነት መፍጠራቸው ነበር።
እንደውም አንዳንድ ፀሃፍት ይህን የምዕራቡ ዓለም ያሰናዳው የጎዳ ነውጥ አብዮትን “ኒዮ የብርቱካን አብዮት” እያሉ ይጠሩታል። ይህም ሲባል፣ በሕገ መንግስታዊ ስርዓት ስልጣን የያዘ መንግስትን በጎዳና ነውጥ በማፍረስ የሕዝብን ስልጣን በተወሰኑ ቡድኖች ውክልና መቆጣጠር ነው። በተለይ የምዕራቡ ዓለም “ዕሴቶች” ተደርገው ከሚጠቀሱት መካከል ሕገ መንግስታዊ ስርዓት፣ ዴሞክራሲና የሕግ የበላይነት በኬቭ አደባባይ ብትንትናቸው እንዲወጣ ዋነኛ ተዋናዮቹ ምዕራቦቹ ሆነው መቅረባቸው ቀጣዩን የዩክሬን ሕዝብ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አስቸጋሪ አድርጎታል።
ከዚህ የምዕራቡ ዓለም የመንታ መንገድ የፖለቲካ እርምጃ መረዳት የሚቻለው የኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም ሃይሎች ፍላጎታቸውን ለማስጠበቅ የሚሄዱበት ርቀት አደገኛነትን ነው። በተለይ ከፍተኛ የሃይል አቅርቦት ያላቸውን፣ ጂኦ ፖለቲካ ጠቀሜታቸው ከፍተኛ የሆኑ ቦታዎችን እንዲሁም ዲያመንድ ዩራኒየም የመሳሰሉ የሃይል ሚዛን የሚያዛቡ የተፈጥሮ ማዕድናት በሚገኙበት ቦታዎች ላይ በማንኛውም ዋጋ ክፍያ ለመቆጣጠር እንደሚሰሩ ነው።
ለምሳሌ ኢትዮጵያን እንውሰድ፤ በኦሞ፣ በኦጋዴን፣ በጋምቤላ እንዲሁም በወሎ አካባቢ ከፍተኛ የነዳጅ ክምችት ቢገኝ አሁን በእጃችን ላይ ያለውን ሰላም ለማስጠበቅ ይቻለን ይሆን? የብሔር ብሔረሰቦች መብት ከእውቅና በላይ በኢኮኖሚ የተሳሰረ እንዲሆን ስራዎች እየተሰሩ ባለበት ሁኔታ የኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም ሃይሎች በር ቢያንኳኩ እንዴት ፍላጎታቸውን ማስታረቅ ይቻላል? በተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የፖለቲካ ልዩነቶች በዴሞክራሲያዊ የይዘት ማዕቀፍ ውስጥ ባልተቀመጡበት ሁኔታ የኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም ፍላጎትን በቀላሉ ማስተናገድ ይቻላል ይሆን? በተለያዩ ፍላጎቶች የታጨቀው የሚዲያው ምህዳርስ የኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም መጠቀሚያ እንዳይሆን ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች ምንድን ናቸው?
      ከላይ የተቀመጡት ነጥቦችን ማንሳት ያስፈለገው በዩክሬን ግዛት ውስጥ የሚደረጉ የስርዓት ለውጦች ፍጥጫ ከዩክሬን ሕዝብ ፍላጎት በላይ የምዕራቡና የሩሲያ ፌደሬሽን የጥቅም ግጭት መሆኑን ለሚገነዘብ አካል የቤት ስራውን ቀድሞ ነው መስራት ያለበት። ተራራ ሲቃጠል መሬት ይስቃል እንደሚባለው፤ ከእያንዳንዱ ዓለም ዓቀፋዊ ክስተቶች ውስጥ የነገዋን ኢትዮጵያ እያሰቡ መሄድ ካልተቻለ የኮርፖሬት ኢምፔሪያሊዝም ፍላጎትን መቼና እንዴት እንደሚመጣ ለመገመት አስቸጋሪ ነው።
ንደቅ የተወሰደ

2013 የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርትና ያስነሳቸው ጥያቄዎች

March 5/2014
የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት በየዓመቱ የሚያወጣውን የሰብአዊ መብት ሪፖርት ዘንድሮም አውጥቷል። ሪፖርቱ የበርካታ ሀገራትን የሰብአዊ መብት አያያዝ በተመለከተ ያሉትን ጠንካራና ደካማ ጎኖች ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች በመሰብሰብ ያወጣል። በሪፖርቱ ከሚካተቱ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች።

በዘንድሮው የ2013 የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት በሰብአዊ መብት አያያዝ ጉድለቶች ከተተቹ አገራት ኢትዮጵያ አንዷ ናት። የዘንድሮው ሪፖርት በየዓመቱ ኢትዮጵያ ላይ “ጠንከር” ያለ መልዕክት እንዲያዝ የሚገልፁ አሉ። በሌላ ወገን ሪፖርቱ አምና እና ካቻምና የተንከባለሉ ጉዳዮችን ከማንሳቱ በስተቀር አዲስ ነገር እንደሌለው የሚገልፁም አልጠፉም።

በዚህም ተባለ በዚያ በዘንድሮው የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት ጎልተው ከታዩ ጉዳዮች መካከል ከእምነት ነፃነት ጋር በተያያዘ የተነሱ ተቃውሞዎችና በመንግስት በኩል የተወሰዱ እርምጃዎችን እንዲሁም ከመንደር ማሰባሰብ (Villagation) ጋር በተገናኘ ዜጎች በግዳጅ ከቦታቸው ተነስተው ወደ ሌላ ቦታ እንዲዛወሩ መደረጋቸውን አትቷል።

ሌሎች መሰረታዊ የሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አለመከበርን በተመለከተ ቀደም ሲል ከሚወጡ ሪፖርቶች እምብዛም የተለየ አይደለም። በሀገሪቱ የሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ መሰረታዊ ችግሮች መኖራቸውን በዚህኛውም ሪፖርት ተጠቅሷል። ምንም እንኳ በመንግስት በኩል የሰብአዊ መበት አያያዝን ለመሻሻል የተለያዩ የድርጊት መርሃግብሮች ቀርጾ እንደሚንቀሳቀስ ቢገልፅም፤ የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት የሀገሪቱ የሰብአዊ መብት አያያዝ ካለፉት ዓመታት አለመሻሉን አመልክቷል።

በሪፖርቱ መሠረት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለፍርድ ቤት መያዝ፣ ሕገ-ወጥ የፖሊስ ብርበራ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ፍርድ አለማግኘትና የእስረኞች አያያዝ ላይ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ዘርዝረዋል። በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የሚካሄደው ምርመራና የእስር ቤት አያያዝ ላይ እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ ችግሮች እንዳሉም አስቀምጧል። በፖሊስ ምርመራ ወቅት አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶች መኖራቸውንና ኢሰብአዊነት (Inhuman) የሆኑ አያያዞችንም እንዳሉ አስረድቷል።

የማረሚያ ቤቶች ሁኔታንም በተመለከተ እንዳለፉት ዓመታት ሪፖርትቱ “እጅግ አስቸጋሪ (Harsh)” በሚል ቃል ያስቀመጠው ሲሆን፤ ለታራሚዎችም የሚመደበው ዓመታዊ በጀት ከአምናው ያልተሻለ መሆኑንም ይኸው ሪፖርት ጠቁሟል። እንደ 2013 የስቴት ዲፓርትመንት የሰብአዊ መብት ሪፖርት መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ ለአንድ እስረኛ አማካኝ የቀን ወጪ ስምንት ብር (0.42) ዶላር ብቻ መሆኑንም አስረድቷል። በሪፖርቱ መሠረት ይህ ወጪ የታራሚውን የምግብ የውሃ እና የሕክምናን ወጪ የሚያጠቃልል ነው። በሀገሪቱ በፌዴራል መንግስት የሚተዳደሩ ስድስት እና 120 በክልል የሚተዳደሩ ማረሚያ ቤቶች እንዳሉም ሪፖርቱ ጠቁሟል። ማረሚያ ቤቶቹ ግን በርካታ ችግሮች እንዳሉባቸው ሳይጠቅስ አላለፈም። ከምግብ አቅርቦት ጀምሮ ንፁህ ውሃና የመኝታው አገልግሎት ብዙ የሚቀረው እንደሆነም በሪፖርቱ ላይ ተብራርቷል።

የሲቪል መብቶችንም በተመለከተም ልክ እንዳምናውና ካቻምናው ሪፖርት በዘንድሮውም መሻሻል አለመኖሩን ሪፖርቱ አመልክቷል። በሀገሪቱ በቂ የሆነ የሕትመትም ሆነ የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ አለመኖሩን፣ ያሉትም ቢሆን ችግር እንደለባቸው ጠቅሷል።

በተለይ ጋዜጠኞች የመንግስትን ጫና በመፍራት አደገኛ ጉዳዮችን (Sensitive Topics) ለመዘገብም ሆነ ለመመርመር እንደሚፈሩ ጠቅሷል። ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘም በጋዜጠኞች ላይ የተለያዩ ጫናዎች መኖራቸውን አስረድቷል።

የኢንተርኔት ነፃነት (Internet Freedom) በተመለከተም አልፎ አልፎ ፌስቡክ የማኅበራዊ ድረገፅን ጨምሮ በቋሚነት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታዩ የተደረጉ ድረገጾች መኖራቸውን ዘርዝሯል። በተጨማሪም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የአካዳሚክ ነፃነት አለመኖሩንና የትምህርት ሚኒስቴር ለገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች የፖስት ግራጁዬት ሥልጠና ቅድሚያ እየሰጠ እንደሆነም አመልክቷል።

የመሰብሰብና የመደራጀት መብትም አሁን ሙሉ በሙሉ አለመከበሩን ያተተው የ2013 የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት፤ ባለፈው ዓመት ሰላማዊ ሰልፎች አለአግባብ መከልከላቸውን አንዳንዶቹም በግዳጅ ጊዜና ቦታ በመቀያየር መብታቸው መጣሱን አመልክቷል። በዚህ ረገድ የሰማያዊ ፓርቲን ያጋጠመውን ችግር በምሳሌነት አንስቷል።

ሪፖርቱን ካነበቡት ምህሩን መካከል ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በርኸ አንዱ ናቸው። ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በመጀመሪያ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ሰብአዊ መብት ለማክበር ከአሜሪካ መንግስት ይልቅ የኢትዮጵያ መንግስት ሊጨነቅበት የሚገባ ጉዳይ እንደሆነ እና ጥያቄው ከአሜሪካ መንግሰት መምጣቱ ተገቢ አለመሆኑን ነው ያስረዱት።

በዚህኛው ሪፖርት ከመንደር ምስረታ ጋር በተገናኘ እና ግድብ በሚገነባበትና ሌሎች ሰፋፊ ልማቶች በሚካሄድበት ቦታ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች ሲነሱ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ነው የመከሩት።

ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር በተመለከተም ማንም ሀገር ፍፁም አለመሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ በዚህ ረገድ በወረዳ ሹመኞችና በአካባቢ አስተዳደሮች የሚፈፀም የሰብአዊ መብት ጥሰት በቀላሉ መታለፍ የሌለባቸው መሆኑን ሪፖርቱ ያስገነዝበናል ብለዋል።

የመንደር ምስረታና ከሰፋፊ የእርሻ ልማት መካሄድ እንዳለበት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ይስማማሉ። ሀገሪቱ 70 ሚሊዮን ሔክታር የሚታረስ መሬት እያላት ወንዞቿ በአራቱም አቅጣጫ እየፈሰሱ ባለበት ሁኔታ ከእህል ልመና መውጣት አለባት። ነገር ግን እነዚህ ልማቶች ሲካሄዱ ግን የሰዎች መብት መከበር ላይ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት ነው የጠቀሱት። ያም ሆኖ “ተጥሷል” የተባለው ሰብአዊ መብት በትክክል ሪፖርት እንዲደረግ ሂዩማን ራይስ ዎች ጨምሮ ለሁሉም የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ወገኖች በሩ ክፍት መሆን አለበት ብለዋል። በዚህ ረገድ መንግስት የሚደብቀው ነገር አለ ብለው እንደማያምኑ ያስረዱት ዶ/ሩ የማይደበቀውን ሁሉ የምንደብቅ ከሆነም አሉታዊ ውጤት ይኖረዋልም ሲሉ አስረድተዋል። በመጨረሻም የአሜሪካ እርዳታ ሲቀር የሚጎዳው እርዳታ የሚመጣለት ሕዝብ ነው። ዝሆኖች ሲጣሉ ሣሩ ይጎዳል እንደሚባለው የኢትዮጵያ መንግሰት ተቃዋሚዎች ጉዳዩን በአግባቡ ቢያጤኑት ጥሩ ነው ብለዋል።

በሪፖርቱ ላይ በኢትዮጵያ ሃሳብን በነፃ የመግለፅ መብትና የመገናኛ ብዙሃን በነፃ መንቀሳቀስ መብት ላይ ችግሮች የሉም ብሎ ማለት እንደማይቻል የሚጠቅሱት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ “መሻሻል ያለበት ገና ብዙ ነገር አለ” ብለዋል በተለይም ከሚታሰሩ ጋዜጠኞች አንፃር የሚነሳው ጉዳይ ችግር ያለበት መሆኑን ነው ያስረዱት። ሚዲያው እራሱን የሚመራበት የሚዲያ ካውንስልና የስነ ምግባር ደንብ ሊኖረው እንደሚገባም ጠቅሰዋል። በደፈናው ጋዜጠኛ ተበደለ የሚለውን ነገር ለማስቀረት ጠቃሚ መሆኑን፣ ሚዲያውም ነፃነቱን ከመንግስት ከመጠበቅ ይልቅ እራሱን በራሱ እንዲያስከብር የሚዲያ ካውንስልና የስነ-ምግባር ደንብ ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁመዋል። መንግስታት ሁልጊዜ ለስልጣናቸው ስለሚሰጉ ሚዲያውን የመጫን ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ነው የጠቀሱት።

ይሁን እንጂ ለሀገር የሚጠቅሙትን ሕዝብ የሚያስተምሩና የሚያነቁትን የሲቪል ማኅበረሰቡ ድምፅ የሚሆኑትን መንግስት በተቻለው መጠን በመደገፍ እንዲያድጉ ማድረግ እንዳለበትም የሚጠቅሱት ዶ/ሩ በዚህ ረገድ መንግስት መሄድ ያለበትን ርቀት ያህል እየሄደ አለመሆኑን ነው የጠቀሱት።

የሲቪል ማኅበረሰብን በተመለከተ በመንግሰት በኩል ሕጉን በተመለከተ መነጋገር አይቻልም የሚለውን ጉዳይ ቆም ብሎ ማየቱ እንደማይከፋ፣ በተለይ ዘጠና አስር የሚለው ድንጋጌ በሕፃናት፣ ሴቶች ደህንነት መብቶች ከፖለቲካ ጋር ተያይዞ መሄዱ ስራዎችን እየገታ እንደሆነ ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ጠቅሰዋል። መንግስት እራሱ በከፍተኛ እርዳታና ብድር እየኖረ ባለበት የሲቪል ማኅበራትን የመከልከሉ ተጠየቅ (logic) ግልፅ አይደለም ብለዋል። አዋጁ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሲቪል ማኅበረሰብ እንዲያድግ መደገፉ ተገቢም ተመካሪም እንደሆነ የሚጠቅሱት ዶ/ር ቆስጠንጢኖስ ነገር ግን ኢትዮጵያዊ የሆነ የሲቪል ማኅበረሰብን ለመፍጠር ትንሽ ጊዜ የሚጠይቅ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ብዙ ስራ ሊሰሩ የሚችሉ በዓመት እስከ 900 ሚሊዮን ዶላር ይዘው በመምጣት በሺህ የሚቆጠር ፕሮጀክት የሚያንቀሳቅሱና በሺህ ለሚቆጠር ሰው የስራ ዕድል ይፈጠር እንደነበርም አስረድተዋል። አሁን ባለው የአዋጅ አሰራርም 30 በ70 የሚለው አሰራርም እንደገና መታየት ያለበት ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሪፖርቱን ካነበቡ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች መካከል የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው አንዱ ናቸው። በአጠቃላይ መልኩ ሪፖርቱ ጥሩ የሚባል ቢሆንም፤ አንዳንድ የሚቀሩት ነገር እንዳለ ግን ሳይገልፁ አላለፉም።

በኢንጂነር ግዛቸው እምነት የሪፖርቱ ደካማ ጎኖች መካከል በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉልና በደቡብ ክልሎች በተለያየ ምክንያት የሚፈናቀሉ ሰዎች ተገደው ይነሳሉ የሚለውን ኀሳብ ከማጉላት ይልቅ ፈቃደኝነት እንዳላቸው ተደርጎ ቀርቧል። በአንፃሩ ከቀዬአቸው ሲነሱ መሰረታዊ አቅርቦት እንዳልተሟላላቸው የሚመስል ነገር አለው ብለዋል። በዚህ ረገድ ከስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት ይልቅ የኦክላንድ ኢንስቲትዩት፣ ሂዩማን ራይትስዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርቶች የተሻሉ መሆናቸውን አስረድተዋል። በእኛ እምነት ዜጎቻችን ለልማትም ሆነ በሌላ ምክንያት ከቀዬአቸው እንዲነሱ ሲደረግ መሰረታዊ የሰብአዊ መብታቸው እየተጣሰ ነው ብለን እናምናለን ሲሉ ገልፀዋል።

ሌላው በኢንተርኔት አፈና ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይታዩ ከሚደረጉ በርካታ ድረገጾች መካከል የተዘረዘሩት ጥቂቶቹ ከመሆኑም በላይ ከኢንተርኔት አፈና ጋር በተያያዘ በሪፖርቱ የቀረበው እውነታ ሀገሪቱ ያለችበትን ሙሉ ስዕል እንደማያሳይም ኢንጂነር ግዛቸው ተናግረዋል።

በተጨማሪም የአንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚለው የሕዝብ ንቅናቄ ወቅት በተጨባጭ በፍቼ፣ በባሌና በሌሎች አካባቢዎች በአባላቶቻችን ላይ ድብደባና ሰብአዊ መብት ተጥሷል፣ ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳያደርግ መደረጉን በአግባቡ ያዩት አይመስለኝም ብለዋል። የታሳሪዎችንም ጉዳይ ቢጠቅሱትም ከሕግ አኳያ (Legal Perspective) እንዳልታየም አስረድተዋል። በሪፖርቱ ላይ ከፖለቲካ ጋር በተያያዘ የታሰሩ ሰዎች አላግባብ መታሰራቸውን፣ እንዳይጎበኙ መደረጉን እኛም እነሱም ሁልጊዜ የምንለው ነገር ቢሆንም ከሕግ አንፃር አልታየም ብለዋል።

በሌላ በኩል የስቴት ዲፓርትመንት በየዓመቱ ሪፖርት ማውጣቱ መረጃ ከመስጠት አንፃር ጠቀሜታ ቢኖረውም የመጨረሻው ግብ (end result) ግልፅ አይደለም የሚሉት ኢንጂነር ግዛቸው፤ ቢያንስ ከመንግስት ጋር ገንቢ ዲፕሎማሲ በማካሄድ እንኳ አጠቃላይ ሁኔታውን የማስለወጥ ተነሳሽነት እያየን አይደለም ብለዋል።

“የሀገራችንን ሉአላዊነት ጥሰው በሀገራችን የውስጥ ጉዳይ ይግቡ ባንልም፤ ሪፖርቱን መነሻ አድርገው ቢያንስ የማሻሻያ እይታ ልናይ ይገባል። ባለፉት አምስት ዓመታት ተመሳሳይ ሪፖርቶች እያየን ነው። ተደጋጋሚነት ያላቸው ናቸው። እና ግባቸው ሪፖርት በየዓመቱ መፃፍ ይመስላል። ይሄ ደግሞ ማንንም አይጠቅምም” ሲሉ ኢንጂነሩ ሪፖርቱን በተመለከተ ያላቸውን ቅሬታ ገልፀዋል።

ከሪፖርቱ መውጣት በመቀጠል እንደተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ምን እንዲደረግ እንደሚፈልጉ ኢንጂነር ግዛቸው ተጠይቀው፤ የሚታይ የሚዳሰስ የዲፕሎማሲ ውይይት በመንግስትና በአሜሪካ መንግስት መካከል እንዲደረግ እንፈልጋለን ብለዋል። ሰዎች ያለ ሕግ ሲታሰሩ፣ ከታሰሩም በኋላ በወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዳይጠየቁ ሲደረግ፣ ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ ሲከለከሉ፣ ፕሬሱ ሲዳክም በዚህ ላይ ቢያንስ ጉዳዩ የሚያሳስባቸው ከሆነ የአሜሪካ መንግስትና የኢትዮጵያ መንግስት ሲነጋገሩ ማየት አለብን። ውጤቱንም ማየት አለብን። የአሜሪካ መንግስት ከዚህ መንግሰት ጋር ወዳጅ መንግስት መሆኑን እንረዳለን። ወዳጅነታቸውን በተሻለ ደረጃ ፍሬያማ ለማድረግ እነዚህ ችግሮች ላይ ሲነጋገሩ ማየት እንሻለን። በውጤቱም እኛ በምናካሂደው እንቅስቃሴ መገለፅ አለበት። በየዓመቱ ሪፖርት ማውጣት ግን ፋይዳው ምንድነው (So what?) ብለዋል።

“በእኛ በኩል እርዳታ ይከልከል የሚለው ጉዳይ በጥሞና መታየት እንዳለበት እናምናለን። በተለይ ለሕዝቡ መሠረታዊ አገልግሎት የሚሰጥ እርዳታ ላይ ጥንቃቄ መደረግ አለበት። በተለይ በጤና አገልግሎት ላይ ጥሩ ስራ እየሰሩ ነው። ግብርናውንም እያገዙ ነው። በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ መንግስት ማኅበራዊ አገልግሎቱንና ኢኮኖሚውን ወደማገዙ እያዘነበለ ነው። በእኔ እምነት በፖለቲካውም ንቁ ተሳታፊ በመሆን የዴሞክራሲ ሂደቱ የሚሻሻልበትን መንገድ መፈለግ አለባቸው። በእኛ እምነት ዴሞክራሲውና የዴሞክራሲ ተቋማቱ ነፃ አልሆኑም። የፖለቲካ ክንፍ ሆነዋል። የሕዝብ ሚዲያውና የምርጫ መዋቅሩ፣ የፍትህ ስርዓቱ ህይወት እንዲኖራቸው ስለምንፈልግ እንዲሻሻሉ የአሜካ መንግስት መርዳትና ግፊት ማድረግ አለበት። በደፈናው እርዳታ ይቁም የሚለው በጥንቃቄ መታሰብ አለበት። ከዚህ ባሻገር ከሕዝቡ መሠረታዊ ፍላጎት ውጪ በሆኑ እርዳታዎች ላይ ቅድመሁኔታዎችን ማስቀመጥ ይችላሉ። በተለይ ለሚሊተሪው፣ ለፖሊስና ለደህንነቱ የሚሰጡ ድጋፎች ቢያንስ የዴሞክራሲ ሂደቱን ሊያግዙ በሚችሉ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ ቢመሰረቱ የተሻለ ነው” ሲሉ ኢንጂነር ግዛቸው አብራርተዋል።

“ከዚህ ውጪ የፀረ-ሸብር ሕጉ፣ የፕሬስ ሕጉና የሲቪል ማኅበረሰብ ሕጎቹ በጥቅሉ የዴሞክራሲ ሂደቱን የሚያፍን የፖለቲካ ዓላማን ይዘው የተነሱ በመሆኑ በምትኩ ዴሞክራሲያዊ ስሜት (Democratic Sense) ሊኖራቸው ይገባል። ሕጎቹ ከተቻለ በሀገሪቱ የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ መግባት አለባቸው። አዋጆቹ አሁን ባላቸው ዓላማ የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያ ሊሆኑ አይችሉም። አዋጆቹ በአመዛኙ የዴሞክራሲ ስርዓት ማፈኛ ናቸው። ስለሆነም አዋጆቹ ወይ መሻሻል አለባቸው አለበለዚያ መሠረዝ አለባቸው” ሲሉ ኢንጂነር ግዛቸው ኀሳባቸውን አጠቃለዋል።

“ሪፖርቱ ከዓመት ዓመት የተለየ ነገር የለውም አላነበብኩትም። ባነበውም ተመሳሳይ ነው” ያሉት ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ፤ “ሪፖርቱ ለእንጀራ ሲባል የሚፃፍ ነው። ይሄንን ሪፖርት ካልፃፉ የማይኖሩ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ” በማለት ሪፖርቱን አጣጥለውታል።

አቶ ጌታቸው እንደ አሳሳቢነት የሚያነሱዋቸው የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በተመለከተ እኛም የምንጨነቅበት ጉዳይ ነው። ነገር ግን እነሱ የሚያቀርቡት መንገድ አያስማማንም ብለዋል።

“እንደ ችግር የሚያነሱዋቸው ነገሮች የሚያቀርቡበት መንገድ ጥሩ አይደለም። ዴሞክራሲ የራሳችን ጉዳይ ነው። አሜሪካኖች ስለተጨነቁ አይደለም፤ እኛ ስለዴሞክራሲ የምንጨነቀው። ለራሳችን ስለምናስብ ነው የምንጨነቅበት። ስለዚህ የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት ከስንፍናም ብዛት የሪፖርቱን አመተምህረት የማይቀይሩበት ጊዜ አለ። እና አንድ አይነትና ተደጋጋሚ ነው። አምና ያወጡት ከዘንድሮው ስለማይሻል ባላነበው እንኳ ምን እንደሚል ልነግርህ እችላለሁ” በማለት ሪፖርቱ አዲስ ነገር እንደሌለው ተናግረዋል።

ሪፖርቱን በአግባቡ እንዲጠናቀርና እውነታው ግልፅ እንዲሆን መንግስት ለሪፖርቱ አቅራቢዎች ምን ያህል በሩን ክፍት አድርጓል ለሚለው ጥያቄ አቶ ጌታቸው ሲመለሱ፤ “እኛ የግልፅነት ችግር የለብንም። እነሱ የእውነት ምርመራ ከፈለጉ በእኛ በኩል ችግር የለብንም። ነገር ግን ተመርምሮ የተሰጣቸውንም በአግባቡ አያቀርቡትም። ለምሳሌ ሞተ የሚሉት ሰው በህይወት አለ ተብለው ተነግሮአቸው በግድ ሞተ ነው የሚሉት። የእነሱ ምኞች እንዲሳካ ግለሰቡን መግደል አይኖርብንም።” ሲሉ በሪፖርቱ ጥራት ላይ አቶ ጌታቸው ያላቸውን ቅሬታ ገልፀዋል።

ሪፖርቱ ወጣም፣ አልወጣም ከአሜሪካ መንግስት ጋር ያለን ግንኙነት በጣም መልካም ነው ያሉት አቶ ጌታቸው በተለይም ስትራቴጂካዊ የጥቅም ጉዳዮች ላይ ችግር የለብንም። አሜሪካ ነፃ ሀገር ስለሆነችም የተለያዩ ተቋማት የተለያየ ኀሳብ ቢያንፀባርቁ የሚገርም አይሆንም ብለዋል።

     ሦስቱ አወዛጋቢ ሕጎች ማለትም የፀረ-ሽብር ሕጉ፣ የሲቪል ማኅበረሰብና የፕሬስ ሕጉን በተመለከተም አቶ ጌታቸው ሲመለሱ፤ “የሽብር አዋጁ ሽብርተኞችን እንዲያበረታታ፣ የፕሬስ አዋጁም ሁከትን እንዲያነሳሱ የሚፈልጉ ወገኖችን የበጎ አድራጎት አዋጁ የውጪ ድርጅቶችን ለምሳሌ የናሽናል ኢንዳውመንት ፎር ዴሞክራሲ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሂደቱ ውስጥ እንዲፈተፍት ካልፈቀደ ሰብአዊ መብት አይከበርም፣ ዴሞክራሲ አያድግምና ፀረ-ሽብር እንቅስቃሴ አይሳካም የሚል እምነት ያላቸው ሰዎች አሉ። በእርግጥም ሕጉን ለማስቀየር የሚጥሩም አሉ። በእኛ እምነት ሕጎቹን መቀየር የሚያስፈልግ ከሆነ በሂደት ከታለመላቸው ዓላማ አንፃር ያመጡት ስኬት ተመዝኖ የኢትዮጵያ መንግስት በራሱ መንገድ (Organic process) መልሶ የሚያያቸው ይሆናል። ከዚህ ውጪ እነዚህ ሕጎች ላይ ዝርዝር ችግሮችን ይዞ ይሄንን ችግር ይፈጥራል ብሎ ይዞ የሚመጣ የለም። ከዚህ ይልቅ መፈክር ነው የሚያሰሙት። መፈክር በተሰማ ቁጥር መፈክሩን ተከትለን የምንነጉድበት ምክንያት የለም” ሲሉ አቶ ጌታቸው መልሰዋል።

ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?

March 5/2014

eprdf t or a


ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ዛሬ የተነሳ አዲስ ነገር አይደለም። ኢህአዴግ መሰረቱን ዝርፊያ ላይ ያደረገ አገር አስተዳዳሪ መሆኑ ግብሩ ራሱ ምስክር ነውና “ሌባ አገር አስተዳዳሪ” ስለመሆኑ ማስተባበያ ሊያቀርብም አይቻለውም፤ አያስፈልገውም። ሌብነቱ አገርንና ህዝብን ወደ ገደል እየሰደደ መሆኑ ግን ሁሌም የሚያስጨንቅ ነውና ዛሬ እንደ አዲስ አነሳነው እንጂ!!
ኢህአዴግ ግዙፍ፣ ሃብቱ በዶላር ካልሆነ በብር የማይቆጠር፣ በህገወጥ ንግድ ሰላማዊ ነጋዴዎችን የሚውጥ፣ ለብቻው መግቢያና መውጪያ የተዘጋጀለት፣ የተለየ ጨረታና የነጻ ቀረጥ እድል የሚበጅለት፣ በየትኛውም ተቋም እንደፈለገ መጋለብ የሚችል ልጓም አልባ የሆነ፣ በፈለገው ቦታና ማህበረሰብ ጥቅም ላይ እንዳሻው ከበሮ እየደለቀ የሚጨፍር፣ ጡሩምባ ይዞ የሚያንጠራባ፣ የፈለገውን ማስወገድ፣ ማሳገድ፣ ማስከፈት፣ ማዘጋት የሚችል፣ ድንበርና ኬላ የማይዘው የንግድ ተቋም አለው። እወክላቸዋለሁ በሚላቸው የአንድ ክልል ሕዝብ ስም ባቋቋመው ሻርክ ኦዲት በማያውቀው የ”ንግድ” ተቋም አማካይነት አገሪቷን እየዘረፈና እየዋጠ ነው።
አገሪቱ አምጣ የምታገኘውን የውጪ ምንዛሬ በበላይነት ሲፈልግ ከራሱ ባንክ፣ ሲያሻው የራሱ ሰዎች በሚያዙበት የህዝብ ባንኮች በተራ ትዕዛዝ ያግበሰብሳል። በፋይናንስ ዘርፉ ውስጥ እጅና እግሩን ነክሮ እንዳሻው ያንቦጫርቃል። የሚቀናቀኑ ብቅ ሲሉ እየበለተ ይሰቅላቸዋል። ሲያሻው ፋይል አስከፍቶ በ”አጎብዳጅ ባንዳ” ዳኞች ያስፈርድባቸዋል። “ጸረ ልማት” ብሎ የፍየል ወጠጤ ያዘፍንባቸዋል።
እንቶኔን ያየ … በሚል አገር ወዳዶች ሸሽተው አለቁ። ምሁሩ አገሩን ከዳ። ነጋዴው ኮበለለ። ወጣቱ በኑሮ ጠኔ መጨረሻው በማይታወቅ ስደት የባህር ላይ ሞትን መረጠ። የቻሉ አረብ ምድር ገብተው በግፍ አለንጋ ተጠበሱ። ኢኮኖሚያዊ ቀውሱ የበረታባቸው ራሳቸውን ማጥፋት ጀመሩ። ይህ ሁሉ የማያስደነግጣቸው ህወሃትና ጭፍሮቹ በጥጋብ ያገሳሉ።
ተቀናቃኞቹን በሰበብ ለማላመጥ የተቋቋመው የፌደራል የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን በቅርቡ በሰጠው ማረጋገጫ ያለ ህጋዊ ቀረጥ ከሚነግዱ ድርጅቶች መካከል ይኸው የህወሃት ድርጅት ግንባር ቀደም ነው። ነገር ግን ጠያቂ የለውም። ለምን ቢባል ባለቤቱ ራሱ አገር መሪ ነውና። ሌባ አገር አስተዳዳሪ ነውና!!
“አስገራሚውና አነጋጋሪው ጉዳይ ህወሃት መቼ ነው ዘርፎ የሚጠግበው?” የሚለው ነው። አንድ ነጻ አውጪ ድርጅት አገር መምራቱ በራሱ ይገርማል፤ ምን አልባትም በዓለም ላይ በነጻ አውጪ የምትገዛ ብቸኛ አገር ኢትዮጵያ ትሆናለች ። በዚህም ላይ ይህ “ነጻ አውጪ” ከፍተኛ አመራሮቹ እንደሚሉት ከበረሃ ጀምሮ ዘርፎ ዘርፎ አለመጥገቡ ያስደንቃል። ከሁሉም በላይ የሚያስገርመው ግን በየቀኑ የጠላቶቹን ቁጥር በሺህዎች እያባዘ ነገ ምን ሊገጥመው እንደሚችል ያለመገመቱ ነው።
እዚህ ላይ አጠንክረን የምንለው ይኖረናል። ህወሃት አንዱን ከሌላው በማጋጨት መሰረት ላይ በተከለው ፖለቲካ የትግራይ ህዝብ የሌላውን ብሔረሰብ ህዝብ ሙሉ በሙሉ እንዲጠረጥርና ራሱን እንዲከላከል እየሰራ መሆኑን እናውቃለን። የማያውቁና መረጃ የሌላቸው ከግምት በላይ ይረዱታል። ይህ ሰይጣናዊ አካሄድ ዋጋው አስቀድመን እንዳልነው “ደም” ነውና ከወዲሁ ማርገቢያ እንዲበጅለት እናሳስባለን።
በቁጥር እየከፋፈሉ በምስጢር ከየአይነቱ በማስታጠቅ የትግራይ ህዝብን ከሌላው ህብረተሰብ ጋር ለማጋደል በምርጫ 97 ወቅት ሟቹ አቶ መለስ የሰጡትን ትዕዛዝ አጠንክሮ መያዝ አሁንም መዘዙ የከፋ ነውና ህዋሃት ከዚህ ተግባሩ እንዲታቀብ እንመክራለን። በወቅቱ “ራስህን ተከላከል፣ ሊያጠፉህ ነው” በሚል በመታጠቅ በየቀበሌው ለመተላለቅ መመሪያ የተጠበቀበት ደረጃ ተደርሶ እንደነበር ለምናውቅ ድርጊቱን ስናስበው ይቀፈናል። ያመናል። ያስበረግገናል። ተከስቶ ቢሆን ኖሮ ጠባሳው ምን ያህል በከፋ ነበር?
የትግራይ ህዝብ እንደ ህዝብ እንደ ማንኛውም የተረገጡ ዜጎች ሁሉ የስርዓት ለውጥ ያስፈልገዋልና ሌላው ህብረተሰብ ከጭፍን ጥላቻ ራሱን እንዲያርቅ እንመክራለን። የትግራይ ልሂቃንም በገለልተኛ ሚዛን በራሳቸው ላይ እንዲሆን የማይፈቅዱት በሌሎች ላይ እየተደረገ መሆኑንን በመቃወም በህዝብ መካከል የተረጨውን መርዝ በማምከን ተግባር ላይ ሊሰማሩ እንደሚገባ ለመጠቆም እንወዳለን። ዙሪያችንን የከበቡን ጠላቶች ይበቁናልና!!
ኢህአዴግ እንደ ገዢ ያለው አቅም ተቦርቡሯል። ሟርት ነው ካልተባለ የኑሮ ብሶት፣ ሌብነትና በሌላው ህዝብ ላይ የሚፈጽመው የግፍ ክምር ሊንደው ተቃርቧል። የሚመካበት የጦር ሃይልም ቢሆን ወገን አለውና አንድ ቦታ ከተፈረከሰ አደጋው የአገር ነው። በቡድን አደራጅቶ መሳሪያ በማደል በጎጥ ወኔ የህዝብን ቁጣና ምሬት መቋቋም የሚታሰብ አይደለምና ህወሃት በመፈክር አታሎ በጨረሳቸው ታጋዮች ደም ላይ የሚደንሰውን ከልክ ያለፈ የጥጋብ ጭፈራ ይግታው። በነጻ አውጪ ስም አገር እየመሩ ዝርፊያ ተራ የማፊያ ተግባር እንጂ አገር እምራለሁ ከሚል ወገን የሚጠበቅ አይደለምና ያደባባይ ዝርፊያ ይቁም!! ኢህአዴግ ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ በማለት የሚጠይቁ ሁሉ እውነት አላቸውና ልብ ያለው ልብ ይበል።
በግብር የምናየው ኢህአዴግ ከተዘፈቀበት ችግር ራሱን ከማጽዳት፣ ህዝብ የሚበጀውን እንዲመርጥ መንገድ ከማመቻቸትና አገሪቱን ወደ መልካም ጎዳና ከማሸጋገር ይልቅ፣ ህዝብን በጅምላ “ለሃጫም” እያለ መስደብ የሚያስደስተው ነው። ህዝብን “ጠባብ፣ አሸባሪ፣ ጸረ ልማት፣ …” በማለት መፈረጅ የድል ያህል የሚያስፈነድቀው ነው። ራሱ ስራ ፈት ያደረገውን ትውልድ “ቦዘኔ” ሲልና ሲሳደብ የስኬት ገድል ያስመዘገበ ያህል ይመስለዋል። ከሁሉም በላይ የህወሃት የእጅ ስራ ውጤት የሆኑ አሻንጉሊት ካድሬዎች እንደ ጌቶቻቸው “ለሃጫም” እያሉ ህዝብን ሲሰድቡ ሽልማት ለመስጠት ይሽቀዳደማል። ህዝብ ሲያኮርፍና ሲበሳጭ ይደሰታል። አገሪቱን ባህር አልባ አድርጎ ስለቀረቀረባት ኩራት ደረቱን ይነፋል። በማያገባው ጦርነት ምስኪን ወገኖችን ማሽጨፍጨፉ ልዩ ገድል ሆኖ ይታየዋል። ድንግል መሬት በሳንቲም ሲቸበቸበ ልማት ነው ይላል፡፡ ነዋሪዎችን ለትውልድ ከኖሩበት እያፈናቀለ መሬታቸውን ለውጪ ባለሃብቶች እየሰጠ “እስካሁን ያልሸጥነው መሬት ነው የሚያሳስበን” በማለት በሰው ደም ይቀልዳል፡፡ በዚህ ሁሉ ትዕቢቱ ላይ ንጹሃንን እያሰረ ማሰቃየቱ፣ መግረፉና መግደሉ፣ አሁን አሁን ይፋ የሆነበት የመርዝ ጣጣ ጀብድ ሆኖበታል። በልክ በልኩ የሰራቸውን አሻንጉሊት ተላላኪዎቹ ሰብስቦ በሚሰራው ድራማ መደነሱና ውሸታም አገር አስተዳዳሪ መሆኑ የኩራቱ ሁሉ ኩራቱ ነው። በዚህ ሁሉ ሲደመር ዜሮ በሚሆን ትምክህት ውስጥ ሆኖ አገር መምራቱ በእጅጉ ያሳስበናል፣ ያስጨንቀናል፣ ወደፊት የሚመጣውን ስናስበው እንደ ዜጋ ያስበረግገናል። ለዚህ ነው “ኢህአዴግ ሌባ – ወይስ አገር መሪ” ስንል የጠየቅነው። መልሱን የሚሰጥ ሁሉ እንዳመላለሱ ትግሉን ሊያካሂድ ይገባዋል እንላለን፡፡

Tuesday, March 4, 2014

ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ ኃይሎች በአደረጃጀቴ ሰርገው ገብተተዋል በሚል ግምገማ ለጀምር መሆኑ ታወቀ

march4/2014

ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ ኃይሎች በአደረጃጀቴ ሰርገው ገብተተዋል በሚል ግምገማ ለጀምር መሆኑ ታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮች በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮችን በመሰብሰብ “አንድነት ፓርቲ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀታችን ውስጥ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች በጊዜ በግምገማ ካልተራገፉ ቀጣዩ ምርጫ ከቁጥጥር ውጪ እንደማይሆን ማንም እርግጠኛ መሆን አይችልም፡፡” ማለታቸውን በስብሰባው ላይ የተሳተፉ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ተናግረዋል፡፡

ምንጮቹ ጨምረው እንደተናገሩት ኢህአዴግ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀቱን የሚያስተባብሩ ከፍተኛ ካድሬዎችን አንድ-ለ-ሰላሳ ማደራጀት መጀመሩን ተከትሎ አንድነት ፓርቲ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች አሉ በመባሉ ካድሬዎች እርስ በእርስ መሰላለል እና አለመተማመን ጀምረዋል፡፡ ይህ በካድሬዎቻቸው መካከል የተጠፈጠረው ትርምስ ያሰጋቸው የኢህአዴግ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት አመራሮች ለክፍለ ከተማ አመራሮቻቸው አንድነት ሊይዝብን የሚችለው 30 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ ነው የተቀረውን በኮንዶሚኒየም ፣ በአነስተኛ ጥቃቅንና በየአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀት ይዘነዋል ብለዋቸዋል፡፡
ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ መረጃ የሰጡት የስብሰባው ተሳታፊዎች «750ሺ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ፣ 30ሺ የኮንዶሚኒየም እጣ ተጠባባቂዎች ኢህአዴግን ነው የሚመርጡት» በሚል ከመድረክ የቀረበው መደምደሚያ እንዳላሳመናቸውም ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩን በሚመለከት ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ከአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የደረሰው ዶክሜንት እንደሚያስረዳው ፓርቲው የአዲስ አበባ አደረጃጀቱን ኢህአዴግ በዘረጋው ልክ 138 ያደረሰ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም የወረዳ ደረጃና የሴል አደረጃጀቶቹን በኢህአዴግ የአደረጃጀት ቁጥር ልክ የማድረግ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ያመለክታል፡፡

የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ቅሬታቸው ገለፁ (ከአብርሃ ደስታ)

March /2014

ባሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የዉኃና አፈር ጥበቃ (Water and Soil Conservation, ማይን ሓመድን ዕቀባ) ተግባራት የሚከናወኑበት ግዜ ነው። ህዝብ ስራው ትቶ ተገዶ በፕሮግራሙ ይሳተፋል። ለፖለቲካ ሲባል ህዝብ በፍላጎቱ ተሳተፈ ተብሎ ሪፖርት ይቀርባል። እውነታው ግን ሌላ ነው። በየዓመቱ ህዝብ ሳያምንበት ተገዶ ይሰራል። በግዜው ያልሰራ እስከ ሦስት መቶ (300) ብር ተቀጥቶ ይሰራል። በዚሁ ምክንያት ብዙ ሌሎች የግል ሥራዎች ይቆማሉ። ዜጎች ብዙ ኪሳራ ይደርስባቸዋል።

የዉኃና አፈር ጥበቃ ሥራ የጉልበት ስራ ነው። መስራት የሚችል ይሰራል፣ ወይ እንዲሰራ ይገደዳል። በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጣብያ ሩባ ፈለግ ግን ለየት ያለ ጉዳይ ተከስቷል። የዓፅቢ ወንበርታ ህዝብ በህወሓት የትጥቅ ትግል ወቅት ንቁ ተሳታፊ የመኖሩ ያህል ባከባቢው ብዙ አካል ጉዳተኞች (የቀድሞ ታጋዮች) አሉ። በጉልበት ስራ መሰማራት አይችሉም። ምክንያቱም አካላቸው ጎድሏል። እናም በጡረታ ገንዘብ በገጠር ህይወት ነው የሚኖሩ። የአካል ጉዳተኞች መሆናቸው ታውቆ ላለፉት ሃያ ሦስት (23) ዓመታት በዉሃና አፈር ጥበቃ ሥራ ተሳትፈው አያውቁም። ምክንያቱም አካላዊ ቁመናቸው አይፈቅድላቸውም፤ ግማሾቹ ዓይናቸው የጠፋ ግማሾቹ እግራቸው የተቆረጠ ወዘተ ናቸው።

አሁን ግን ለመጀመርያ ግዜ በተለየ ሁኔታ አካላቸው የጎደሉ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች በዉኃና አፈር ጥበቃ ፕሮግራሙ እንዲሳተፉ በመንግስት አካላት እየተገደዱ ይገኛሉ። ለምን አሁን እነሱን ማስገደድ ተጀመረ? የአፅቢ ወንበርታ ህዝብ በመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት በመንግስት አካላት ላይ ተቃውሞ አስነስቶ ነበረ። ህወሓቶች የቀድሞ ታጋዮቹ ዒላማ አድርገው በዉኃና አፈር ጥበቃ እንዲሳተፉ ያስገደዱበት ምክንያትም ህዝብ ፀረመንግስት ሲነሳ የቀድሞ ታጋዮቹ ከመንግስት ጎን ከመሰለፍ ይልቅ የህዝቡን ጥያቄ በመደገፋቸው ነው። ታጋዮቹ ዓፈና በዝቷል፤ ለዚህ አይደለም መስዋእት የከፈልነው፣ ፍትሕ ጠፍቷል ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች በማንሳታቸው ነው።

አሁን የድሮ ታጋዮቹ በግዝያቸው በፕሮግራሙ ባለመሳተፋቸው የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸው ለብቻቸው እንዲሳተፉ ይደረጋል። የገንዘብ ቅጣቱ እስከ ሦስት መቶ ብር ይደርሳል። ሦስት መቶ ብር ደግሞ መክፈል አይችሉም፤ ግድቡም መገደብ አይችሉም። ምክንያቱም ታጋዮቹ የሚተዳደሩት በጥሮታ ገንዘብ ነው። የጥሮታ ገንዘቡ ደግሞ ከሦስት መቶ ብር በላይ አይደለም። ታድያ ሦስት መቶ ብር (የጥሮታ) ለመንግስት ከፍለው በምን ሊተዳደሩ? ምን በልተው ሊገድቡ? በግድቡ ለመሳተፍም ይከብዳቸዋል። ምክንያቱም ግድብ የጉልበት ስራ ስለሆነ። አካላቸው አይፈቅድላቸውም፤ ምክንያቱም አካል ጉዳተኞች ናቸው።

በዚሁ ምክንያት በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ሩባፈለግ ጣብያ ከባድ ዉጥረት ነግሷል። በጣብያው (ንኡስ ወረዳ) እስካሁን ድረስ 963 ዜጎች በፕሮግራሙ ባለመሳተፋቸው ምክንያት ክስ ተመስርቶባቸዋል። ክስ ከተመሰረተባቸው ዜጎች ከ100-150 የሚደርሱ ሰዎች ተቀጥተዋል። ሌሎችም ቅጣታቸው እየተጠባበቁ ነው። የአከባቢው ህዝብ የካቲት 13, 2006 ዓም ይህ የመንግስት ካድሬዎች ተግባር በመቃወም “ሰሚ የለም ወይ?!” በማለት በጭኾት ተቃውሞውን አሰምቶ ነበረ።

የቀድሞ ታጋዮቹ ግን መንግስትን ክፉኛ እየወቀሱ ነው። አካላቸው በመጉደሉ ምክንያት ምንም ዓይነት የጉልበት ስራ መስራት የማይችሉ የመንግስት ተግባር ስለተቃወሙ ብቻ አሁን በፕሮግራሙ እንዲሳተፉ እየተገደዱ ካሉ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች መካከል ስማቸው እንዲጠቀስ ፍቃደኛ ከሆኑ (1) ሃምሳአለቃ ሃይለማርያም ገብረእግዚኣብሄር፣ (2) ሃምሳአለቃ አታኽልቲ ገብረኪሮስና (3) አስራአለቃ ወልዴብርሃ ገብረመድህን ይገኙባቸዋል። እነዚህ ሰዎች ደርግ ከወደቀ ከ1983 ዓም ጀምሮ በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት በምንም ዓይነት የመንግስት የጉልበት ስራ ተሳትፈው አያውቁም። አሁን መቃወም በመጀመራቸው ግን እየተገደዱ ይገኛሉ። አሁንም ቢሆን በጉልበት ሊገድቡ እንደማይችሉ የታወቀ ነው። የመንግስት ጥረት ግን ታጋዮቹ መንግስትን መቃወም እንደማያዋጣቸው ተገንዝበው ተቃውሞአቸውን እንዲያቆሙ ለማስገደድ ብቻ ነው። መንግስትን ከደገፉ ግን ነፃ ይሆናሉ። አይገደዱም። እንዲህ ነው የህወሓት ተቃውሞን የማፈን ስትራተጂ።

ቀደም ሲል የህወሓት ካድሬነታቸው በማቆማቸው ምክንያት መሳርያቸውን (ጠመንጃቸውን) በመንግስት አካላት ተነጥቀዋል። በአካላዊ ጉዳት ምክንያት ከህወሓት ዉትድርና ቢወጡም ጠመንጃቸው ግን ይዘውት ነበር የሚኖሩ። ጠመንጃቸው ይፈልጉታል። ምክንያቱም (አንድ) ራሳቸው የሚከላከሉበት ነው። ለብዙ ዓምታት ከነሱ ጋር የኖረ ስለሆነ ማንነታቸው አድርገውታል። እናም ጠመንጃቸውን ሲነጠቁ insecurity ይሰማቸዋል። ትልቅ የሞራል ውድቀት ይሰማቸዋል። የሞራል ኪሳራ ይደርስባቸዋል። ህወሓትም ይህን ያውቃል። እናም ነጠቃቸው። (ሁለት) ጠመንጃቸው በትንንሽ ከተሞች የሚገኙ ሃብታም የህወሓት ካድሬዎች የቤት ዘበኞች በመሆን ስራ የሚያገኙበት ነው። ጠመንጃ ከሌላቸው በዘበኝነት የመቀጠር ዕድል አያገኙም። ስለዚህ ስራ እንዳያገኙ ስለተፈለገ ነው። ስራ ካላገኙ በመንግስት ጥገኛ ይሆናሉ። ጥገኛ ከሆኑ ደግሞ መንግስትን ይደግፋሉ እንጂ አይቃወሙም። መንግስትን ካልተቃወሙ ደግሞ ህወሓት የፈለገውን ዓፈና የማድረስ መብት አገኘ ማለት ነው። ስለዚህ የዚህ ሁሉ ዓላማ ተቃውሞውን በማዳከም ህዝብን መጨቆን የሚቻልበት መንገድ ማመቻቸት ነው።

በብዙ የትግራይ አከባቢዎች የዉኃና አፈር ጥበቃ ፕሮግራም እየተሰራበት ያለ ሲሆን ባከባቢው ተገኝቶ በፕሮግራሙ ያልተሳተፈ ገበሬ መሬቱ እየተነጠቀ ይገኛል (እንደ ቅጣት መሆኑ ነው)። ነገሩ እንዲህ ነው። የህወሓት ካድሬዎች ማዳበርያ ለመሸጥ ሲባል ገበሬውን በአስገዳጅ እንዲገዛ ያደርጋሉ። ማዳበርያ ካልገዛ ይታሰራል፣ የመንግስት አገልግሎት አያገኝም፣ መሬቱም ይነጠቃል። ገብሬውም እነዚህ ሁሉ ቅጣቶች መሸከም ስለማይችል የማዳበርያ ዕዳ ይገባል። ማዳበርያውን ለመግዛት ገንዘብ ከተለያየ ተቋማት ይበደራል። ብድሩ ለመመለስ በከተሞች አከባቢ ወይ ሌላ ራቅ ያለ ቦታ በመሄድ ተጨማሪ ስራ ይፈልጋል። ዕዳውን ለመክፈል ስራ ፍለጋ ከቀዩ ይርቃል። ካድሬዎች ደግሞ “ባከባቢው እያለማ አይደለም” በሚል ምክንያት መሬቱ ተወስዶ ለሌላ ካድሬ ይሰጣል። ገበሬው ለዘላለሙ ከቀዩ ይፈናቀላል። ምክንያቱም መሬት የመንግስት ነው። መሬት የኔ ነው ብሎ ፍርድቤት ሂዶ መከራከር አይችልም። ሁሉም ነገር በሕግ ሳይሆን በመመርያ ነው የሚሰራው። እናም ህዝብ ችግር ላይ ወድቋል።

የታጋዮቹ ጉዳይ ግን አሳሳቢ ነው። ታጋዮቹ አካላቸው ጎድሏል። እኛን ከጨቋኞች ነፃ ለማስወጣት ሲሉ መስዋእት ከፈሉ። ለኛ ሲሉ አካላቸው ጎደለ። አሁን መስራት አይችሉም። መቃወምም እንዳይችሉ እየተደረጉ ነው። እነሱ የቤት ስራቸው ጨርሰዋል። ለኛ ሲሉ አካላቸው የጎደሉ ወገኖች አሁን እኛ ልንተባበራቸው ይገባል። እኛ ልንታገልላቸው ይገባል። እኛ ነፃ ልናወጣቸው ይገባል። ምክንያቱም እነሱ ዓቅሙ የላቸውም፤ እንደ ድሮ ሩጠው ጫካ መግባት አይችሉም። ከዚሁ ዓፋኝ ስርዓት እንገላግላቸው።
It is so!!!

በኢትዮጵያ የመብቶች ጥሰት ጉዳይ ከብሔራዊ አነታራኪ ፖለቲካዊ አጀንዳነት አልፎ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኗል።

March4/2014

ምንሊክ ሳልሳዊ :- ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመብቶች ሕጋዊነት በተጨበጨበለት ሁኔታ እና ይህ በማይባል ደረጃ በወረቀት ላይ ብቻ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለይስሙላ እና ለማስመሰል የተደነገጉባት አገር ነች፡፡ የቀድሞ መንግስትን ሽንፈት ተከትሎ በኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የፍፃሜ ምዕራፍ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን ጭራሽ ብሶበት ቁጭ አለ፡፡ የሕወሓት ወንበሩን መቆጣጠር ተንተርሶ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተለይም ሒዩማን ራይት ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል የወያኔን ጁንታ በሰብዓዊ መብት ጥሰት በማብጠልጠል ነበር የተቀበሉት፡፡ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት የሰብኣዊ መብት ጥያቄዎች አቤቱታ ማሰማታቸውን አላቆሙም፡፡ ጋዜጠኞችን የሃሳብ ነጻነት ከሚገድብ ጥቃት በመከላከል ላይ የተሰማሩ የመብት አስከባሪ ድርጅቶችም ወያኔ በሚፈጥረው ከባድ የሰብኣዊ መብት ጥሰት በየጊዜው መክሰስ ሥራቸው ሆኗል:: የአሜሪካው ስቴት ዲፓርትመንት በየጊዜው በሚያወጣው ዓመታዊ መግለጫው ወያኔን በሰብዓዊ መብት ጥሰትና የፖለቲካ መብቶችን ማፈን ይከሰዋል፡፡ ባሁን ወቅት የእነኚህን አካላት መግለጫዎች የታወቁ ዓለም አቀፍ መገናኛ ድርጅቶች በመቀባበል ኢትዮጵያ የዜጎቿን መብቶች በመጣስና በማፈን ወደር የሌላት አገር እንደሆነች ዓለም እንዲረዳው እያደረጉ ናቸው፡፡

ታዋቂነታችን በድርቅ በድህነት ብሎም በጭፍጨፋ ደሞ በሰብኣዊ መብት ጥሰት የሕወሓት መራሹ ጁንታ ወደ ስልጣን በጠበንጃ ሃይል ከመጣ ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ የተደነገጉ የሰብአዊ መብት ህጎችን ካለምንም ማርቅርቅ እና ድካም ከሌሎች በመገልበጥ በወረቀት ላይ ከማስፈሩም በተጨማሪ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በአለም ላይ የሰው አገር ህግን እና አለማቀፍ ድንጋጌን ከሃገራችን ሁኔታ ጋር ሳይገናዘቡ በስፋት በደመነፍስ ለፍጆታ የተጻፈበት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ሲሆን በየትኛውም አለም ሃገራት ያልተከሰተ የአለም አቀፍ ህጎችን ግልባጭ በከፊል በህገመንግስት እንዲሁም የገዢ ፓርቲን የፖለቲካ ፕሮግራም በከፊል ደባልቆ በጋራ እንደ አውራ ህግ የወጣባት ሃገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት::ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመብቶች ሕጋዊነት በተጨበጨበለት ሁኔታ እና ይህ በማይባል ደረጃ የተደነገጉባት አገር ነች፡፡ እንግዲህ ይህ ሆኖ እያለ ነው በአገሪቱ የመብቶች ጥሰት ጉዳይ ከአገሪቱ ብሔራዊ አነታራኪ ፖለቲካዊ አጀንዳነት አልፎ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::

ኢትዮጵያ በአስከፊ ድርቅና ረሃብ ለመታወቅ እንደበቃችው ሁሉ ወያኔ የዜጎችን መብቶች በመጣስና በማፈን እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ በሚፈጽመው ወንጀል በዓለም ላይ ታዋቂነትን እያተረፈ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም;ወያኔ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን መብቶች ለመጣስ ስለሚጠቀምባቸው ዘደዎች የሚቀርቡ ማስረጃዎች እና ማብራሪዎች እጅግ ዘግናኝ ናቸው፡፡የወያኔ መሪዎች የፖለቲካ ተቀናቃኖችን ለማዳከም ሲሉ ንፁኃንን ወንጀለኛ የሚያደርግ ዘዴዎችን ሥራ ላይ እንደሚያውሉ በተለያዩ ይፋዊ ሪፖርቶች ላይ ሁሉ ከነማስረጃው እየተነገረ ይገኛል::

ይህ የሰብኣዊ መብጥ ጥሰት እየተባባሰ የሚሄድበት ምክንያት ወያኔ በአብዛኛው ካድሬዎች ዘንድ በስፋት ሰርጾ እንዲገባ ያደረገው የተቃዋሚዎች ጥላቻ እና እንዲሁም የተቃዋሚው ቡድን የትግል አቅጣጫው በተመሳሳይ መልኩ በጥላቻ ላይ የተመረኮዘ መሆኑ ነው::ተቃዋሚዎች የታጠቁ ሃይላት ባለመሆናቸው የመርሃቸው እንቅስቃሴ የተገደበ እና ለፖለቲካ እና ለሚዲያ ፍጆታ የዋለ ተዳፍኖ የሚገኝ ሲሆን የወያኔው ግን በታጠቁ የጸጥታ ሃይሎች እና በፖለቲካ ማጭበርበሮች ላይ ስለተመረኮዘ ካድሬዎቹ በተሰጣቸው የጥላቻ ተግዳሮት እና ወያኔያዊ ስልቶች የፈጠሩትን ጥቅማጥቅሞች ጠብቀው ለማቆየት ሲባል ጥላቻ በፈጠረው ፍርሃት ብቻ የሃገሪቱን ህጎች ዜጎች ለመጥለፍ እያዋሉት ነው::

ይህ ፍርሃት እና ጥላቻ በወያኔ ከትልቅ እስከ ትንሽ ካድሬዎች አናት ውስጥ ስር ለስር በመስደድ የፈጠረው ነገር ቢኖር ማንኛውም ዜጋ ተቃውሞ ካሰማ በወንጀለኛነት በመፈረጅ በማሳደድ በማጥፋት እረፍት ለማግኘት እና ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲራወጡ የህዝብን የበላይነት አፈር ከተውታል::ማእከላዊ የወያኔ ጁንታ በዲሞክራሲ ባለመወቀጣቸው የህጎችን የበላይነት ማረጋገጥ ካለመቻሉም በተጨማሪ በህዝብ እና በዲሞክራሲ ላይ በደሎችን የሚያደርሱ ባለስልጣናት የሚጠየቁት በሃገሪቱ የበላይ ህጎች ሳይሆን በወያኔያዊ የፓርቲ መመሪያዎች በመሆኑ በጥቅም መተሳሰር በፈጠርው ዝግ መንገድ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች እየተብራከቱም ከመሆኑ አልፎ የእለት ተእለት ተግባራት አካል ሆነዋል::

የፈራ ይመለስ! (ከተመስገን ደሳለኝ)

March 472014

በ2004 ዓ.ም የካቲት 23 ቀን በታተመችው ‹‹ፍትሕ›› ጋዜጣ ላይ፣ ‹‹የፈራ ይመለስ!›› በሚል ተመሳሳይ ርዕስ፣ ከሰላማዊ አብዮት ውጪ አማራጭ ካለመኖሩም ባለፈ፣ ኢህአዴግ ቢያንስ ሕገ-መንግስታዊ ጥበቃ ላላቸው ሕዝባዊ ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠት አቅምም ፍላጎትም እንደሌለውለመሞገት ሞክሬ ነበር፡፡ ግና፣ አገዛዙ ለእንዲህ ያሉ ግዴታዎች የተዘጋጀ ባለመሆኑ ከማድመጥ-መዳ–መጥን፤ ከመመከር-መከራን፤ ከማሰብ-ቃሊቲ መሰብሰብን፤ ከመሻሻል-ከሀገር ማሸሽን፤ ከማመን-መርገጥን… በመምረጡ፤ ዛሬም ድረስ ነፃነት ናፋቂው ዘመነኛ ትውልድ፣ በፀጥታ አርምሞ ወደተዋጡት አደባባዮች ከማማተር ያለፈ አማራጭ እንዳያገኝ ገፊ-ምክንያት ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ያንን ጽሑፉም ከዓመት ከስድስት ወር በላይ ፍርድ ቤት ከምመላለስባቸው ክሶች የአንዱ መወንጀያ አድርጎ በተከበረችዋ ፍትሕ እየተሳለቀባት ነው፡፡ በርግጥ ጉዳዩ ገና እልባት ያላገኘ በመሆኑ፣ በዚህ ተጠየቅ አናነሳውም፡፡

ያ ጽሑፍ የታተመባት ‹‹ፍትሕ›› ጋዜጣ የስርዓቱ ቅጥ ያጣ አፈና ሰለባ የመሆኗን ጉዳይ ግን ሁሌም ስናወሳው እንኖራለን፤ ምክንያቱም የ‹‹ቅድመ-ምርመራ›› (ሳንሱር) ግብአተ-መሬት በግላጭ በሕገ-መንግስቱ ሳይቀር ከታወጀ ሃያ ዓመት ባስቆጠረበት ኢህአዴጋዊ ዘመን የተፈፀመ ታላቅ መብት ረገጣ ነውና፤ ያውም ተራ የወሮበሎች ረገጣ መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ፡፡ በመንግስታዊው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ለዚሁ ሕገ-ወጥ ተግባር አድፍጠው እንዲጠብቁ የተመደቡ ‹ግልገል› ካድሬዎች ጋዜጣዋ የምትታተምበትን ሐሙስ ቀንን በዝምታ አሳልፈው ነገር ግን ድንገት በዕለተ አርብ ማለዳ ‹‹ይህንን ዜና ማውጣት አትችሉም! ቆርጣችሁ አውጡ›› ማለታቸው ነው፤ ምን ዋጋ አለው ትዕዛዛቸው ተቀባይነት ባለማግኘቱ፣ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ገንዘብ ውጪ የተደረገበትን፣ 30 ሺህ የጋዜጣዋ ህትመት እንዲቃጠል በፍርድ ቤቱ አማካኝነት በጭካኔ በየኑ፤ ‹‹ፍትሕ››ንም በሕገ-ወጥ መንገድ ዳግም እንዳትታተም አገዱ፤ ይህ ሁሉ ከሆነ እነሆ ሃያ ወራት ተቆጥሯል፡፡ ግና፣ የተከፈለው ሁሉ ስለነገ የተሻለች ኢትዮጵያ ሲባል ነውና ባለፈ ጉዳይ ማለቃቀሱን እዚሁ ገታ አድርገን፣ ኩነቱንም ከነጋዴነት ለተሻገሩ ታሪክ ጸሐፊዎች ትተን፣ በአዲስ መስመር ወደ አጀንዳችን እንለፍ፡፡

የፈራ ይመለስ!

አዎ፣ ይመለስ!! ፍርሃቱን ‹‹አሜን›› ብሎ ተቀብሎ ለመመለስ ከወሰነ በመረጠው የጭቆና ቀንበር እየተቀጠቀጠ ማደር መብቱ ነው፤ ግና፣ አንዳንድ ፈሪዎች፣ አንዳንድ መሀል ሰፋሪዎች በስመ ‹‹ጸሐፊነት›› ጥያቄውን በማጣጣል ለውጡን ለማራዘም (ለማደናቀፍ) የሚያደርጉት ሙከራ ከንቱ እንደሆነ በቅድሚያ ላስገነዝብ እወዳለሁ፡፡ ደግሞም እነኚህ የጭቆና ዘመን አራዛሚዎች እያገለገሉት ያለው ስርዓት የሚያከፋፍለው ብሔራዊ ዳቦ እየተመናመነ መምጣቱን፣ ገዥዎቹ ራሳቸው የፓርቲያቸው ችግር (7 ሚሊዮን የሚደርሱ ካድሬዎችን ከማግበስበሱ አኳያ) ‹‹የጥቅመኞች መብዛት›› እንደሆነ በይፋ አምነው ከተቀበሉት ጋር ስንገምደው የነገ ቀናቸው ‹‹ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ›› እንዳልሆነ እግረ መንገዴንም ልጠቁማቸው እፈልጋለሁ፡፡ በአንፃሩ እነዚያ ሀገሪቷን እያሰመጠ ያለውን የመከራ ረግረግ ተረድተው አብዮቱን ተስፋ ያደረጉ ጎበዛዝት እና ወይዛዝርት ደግሞ ይበልጥ እንዲነቁ፣ ይበልጥ እንዲበረቱ… የጊዜውን መቃረብ ላስታውሳቸው እወዳለሁ፡፡ ምክንያቱም በቁጣ አደባባይ ለመውጣት እንቅፋት የሆነው ብሔራዊ ፍርሃት ይሰበር ዘንድ ለመስበክ፣ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ በነፃነቷ ትበጽህ ዘንድ ካስረገጠው ከዚህ መቶ አስራ ስምንተኛው የዐድዋ ድል ዋዜማ የበለጠ ምቹ ጊዜ የለምና (ይህ ድል በነፃነት የሚያምን የሰው ልጅ ሁሉ፣ ያለቀለም ልዩነት ሊዘክረው የሚገባ ስለመሆኑ ለእነርሱም ጭምር መመስክር ግዴታ ይመስለኛል)

እንዲህ በጽሑፍ ሲገለፅ በእጅጉ የሚቀለው የዐድዋ ገድል፣ እልፍ አእላፍ የሀገሬ ሰዎች መተኪያ አልባ ህይወታቸውን የገበሩበት በመሆኑ፣ በየዓመቱ ደግመን ደጋግመን የመዘከርና አደራውን የመቀበል ታሪካዊ ግዴታ ውስጥ ጥሎን ማለፉ እውነት ነው፡፡ ‹‹የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣ ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንት›› እንድትል እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ)፤ እኒያ ሰማዕታት ከዳር እስከዳር ነቅለው ‹‹…ሀገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል?›› በሚል መታመን ተቀስቅሰው፣ ባሕር አቋርጦ፣ አድማስ ተሻግሮ የመጣውን ወራሪ ሀፍረት አልብሰው፣ ሀፍረት አስታጥቀው፣ ሀፍረት አጉርሰው… የመመለሳቸው ብርታት ባለዕዳዎች መሆናችንን ዘመን ሊሽረው አይችልም፡፡ ያ ጣፋጭ ድል ኢትዮጵያችንን በዓለም ፊት ‹ነፃ ሀገር› የተሰኘ የታሪክ ሜዳሊያ አጥልቃ ትኮራ ዘንድ ካባ ማጎናፀፉም ዓመታዊ ዝክሩ መቼም ቢሆን በቸልታ እንዳይታለፍ አድርጎታል፡፡ እናም እነዛን ባለውለታዎች ከታላቅ የክብር ሰላምታ ጋር እንዲህ ስል ላወድሳቸው እገደዳለሁ፡-

ዘላለማዊ ክብር ለዐድዋ ጀግኖች!!!

የፈራ ይመለስ!

እንግዲህ ጀግኖች አባቶቻችን በዚህ መልኩ ላለፉት ሶስት ሺህ ዘመናት ለነፃነታችን ሲዋደቁ ኖረዋል፡፡ በውጤቱም ነፃ ሀገር አስረክበውናል፡፡ ይሁንና ዛሬም እኛ ዘመነኛ ትውልድ ‹‹ነፃነት›› እያለን የምንጮኽለት ይህ ክቡር ጉዳይ ገና ምላሽ ላገኘም፡፡ በርግጥ ጥያቄው ከባዕድ ወረራና ተወራሪ ጋር የሚጋመድ አይደለም፤ ከሀገር ልጆች ጭቆና እንጂ፡፡ እንዲህ ‹ነፃነታችንን!› እያልን የምንጮኽለት መንፈስም፣ ወራሪውን ጣሊያን ያሸነፉ ቀዳሚ አባቶች ያላቆዩልን፣ ግን ደግሞ በጥያቄው ስም ጥተው፣ መልሰው መንፈሱን የጨፈለቁት ገዥዎቻችን የነጠቁንን መብት የሚወክል ነው፡፡ በአናቱም የትግሉ መንገድ በቅኝ ግዛት ለማሳደር በቀቢፀ-ተስፋ ተሞልቶ ወሰን የተጋፋው ጣሊያን ተሸንፎ ከተባረረበት ጋር ዝምድና የሌለው መሆኑን መረዳት ያሻል፡፡ ምክንያቱም ዘመነኛው የነፃነት ጥያቄ፣ እንደ ዐድዋው መድፍ አጓርቶ፤ መትረየስ የሳት-ላንቃውን ከፍቶ ሞት እየረጨ ሊፈታው አይችልምና ነው፡፡ ይህ አይነቱ የፋኖ መንገድ አንድም ጊዜው ያለፈበት ሲሆን፤ ሁለትም ህወሓት-ኢህአዴግን ለአራት ኪሎው ቤተ-መንግስት ቢያበቃውም፣ የታየው ለውጥ መለዮ ለባሽ ወታደርን፣ ገና ዝላዩን ባልጨረሰ የተማሪ አምባገነን ከመተካት አለመዝለሉ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡

ስለሆነም ዛሬ ጭቆናን የማሸነፊያ ብቸኛ መንገድ የፍርሃት ሰንሰለትን ሰባብሮ፣ በጨቋኞች ፍቃድ ለቆመው ስርዓትም ሆነ በድምፀ-አልባ ተወካዮቹ አጃቢነት ለፀደቁት ሕግጋት አለመታዘዝ ላይ የተመሰረተ ብቻ ነው፡፡ በእምቢተኝነት ደም-አልባ ሰላማዊ አመፅ የገዥዎችን ሰፈር ማራድ፤ እኩይ አላማዎቻቸውን የሚያስፈፅሙ ተቋማትን ጥርስ አልባ ማድረግ፤ አደባባዮችን በሰው ጎርፍ ማጥለቅለቅ፤ የትኛውንም አይነት ተቋማዊ ትብብርን መንፈግ፤ ኤፈርትና መሰሎቹን የንግድ ድርጅቶቻቸውን ማግለል፤ ሁሉም ፖለቲካዊ ፍላጎቶቻችን በኢትዮጵያዊ ዜግነት ስር እንደሚፈቱ ከልብ በማመን-ነገን ማለም፤ ለጥያቄው እስኪንበረከኩ ድረስ በሰላማዊው ተቃውሞ ፀንቶ መቆምንና መሰል ስልቶችን መተግበር ብቸኛ አማራጭ ነው፡፡ ይህ ይፈፀም ዘንድም በራስ ጉያ ፀለምት ለብሶ የተሸሸገ ፍርሃትን የተሻገሩ ጎበዛዝትና ወይዛዝርት ሊፈተኑበት፤ ከሽፈው የቀሩት ደግሞ ጥያቄውን በማጥላላትም ሆነ የተራራ ያህል በማግዘፍ ፍርሃትን አንብረው የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም ደፋ-ቀና ከማለት ይታቀቡ ዘንድ የሚገደዱበት ዕለት ከደጅ መድረሱን ለመተንበይ ነብይ መሆንን አይጠይቅም፤ አይኖች-ያያሉ፤ ጆሮዎችም- ይሰማሉና፡፡

ግና፣ ይቺም ኑሮ ሆና እንዲህ የትውልድ ተጋሪዬ ጭሮ ግሮ ለማደር (አነስተኛና ጥቃቅንን ልብ ይሏል) በፖለቲካ አቋም እና በዘውግ ማንነት ተፈትኖ ማለፍ ግድ በሆነበት የሀገሬ ምድር፣ እውነት መመስከርን ስለምን በጀብደኝነት አንድምታ ታቃልለዋለህ? የተጠናወተህን ገደብ አልባ ፍርሃት፣ ለውጥ የሚጠይቁ ድምፆችን በማጣጣል ለመሸፋፈን መዳከር የት ያደርስሀል? የወላዋይ ብዕርህን ‹‹የለሁበትም!!›› ቅኔ ለበስ አቤቱታ እና ‹እውነት ለመናገር ጊዜና ቦታ አለው› የሚል ፍርሃታዊ ማምለጫህንስ ስለምን ለታናናሾችህ ለመጋት ትደክማለህ? በአገዛዙ መዝገበ-ቃላት ‹‹ፅንፈኛ፣ ጀብደኛ…›› ብለህ ማምታታትስ ባለፈ ዘመን ላይ መከተር አይደለምን? እውነት እውነት እልሀለሁም፡- በሰላማዊ መንገድ የስርዓት ለውጥን መጠየቅ፣ በ‹አትነሳም ወይ!› የሀገር ባለቤትነት ከፍታ ለአደባባይ ተቃውሞ ዘመነኞችን በእሪታ መጣራት፣ በየትኛውም የታሪክ ስፍር ጀብደኝነት ሆኖ አያውቅም፤ ለሕሊና መታመን እንጂ፡፡

በግልባጩ ነፃነትን ያህል ውድ ነገር የሚጠይቀውን ክቡድ መንፈስ ለማራከስ መሽቀዳደም፣ በንፁሀን ደም ከተጨማለቀው ጨቋኝ ገዥ የታማኝ ባለሟልነትን ማዕረግ ለማግኘት መባተል፣ ከዘመን መንፈስ ቀልባሽነት፣ በሞቀበት ከሚዘፍን ሆድ- አዳሪነት… ከቶስ ቢሆን በምን ይለያል? እመነኝ ‹ከአንድ እጅ ጣት በላይ የሚቆጠሩ ሀገራዊ የለውጥ ዕድሎች ስለምን ባከኑ ?› ብለህ ብታንሰላስል፤ ተጠያቂው የአገዛዙ አፈ-ሙዝ ብቻ አለመሆኑ ይገባሀል፤ ይልቁንም ሕዝብን በ‹ጎልያድ›፣ መንግስትን በ‹ዳዊት› መስለው የሚሰብኩ ሃሳዊያን ጻሐፍት ያነበሩት ታላቅ ፍርሃትም ድርሻ እንዳለው ትረዳለህና፡፡ ግና፣ ይህ ሁሉ ሆኖም አንድ ነገር እውነት ነው፤ ከገዘፈ የአመድ ተራራ ስር ፍንጥርጣሪ የጋሉ ፍሞችን የሚያገላብጥ ትውልድ እየመጣ ነው፡፡ ያን ጊዜም አንተን ዘንግቶ የትውልዱ መንፈስ ወካዮችን ብራና ላይ በክብር ይከትባል፡፡ ለነገሩ ቢዘገይም ታሪክ ከእውነት እንጂ ከፍርሃት ውል ኖሯት አያውቅም፡፡

የፈራ ይመለስ!

ጥቂት ጉልበታሞች ለሚንደላቀ ጥቂት ጉልበታሞች ለሚንደላቀቁበት፣ ዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ ለምን ይሰቃያል? ጭቆናን በዚህ ደረጃ ታግሶ መሸከምስ ከግዑዝነት በምን ይለያል? የወፍን ያህል የራስ ጎጆ መመኘት እንኳ እንደ ህብስተ መና በራቀበት ምድር፣ ግብር-ነጠቃን ባስከነዳበት ሀገር፣ ዜጎች በምርኮኛ ሕግ ተቀፍድደው ውለው በሚያድሩበት ክልል፣ መማር ድንጋይ ከመፍለጥ በማያሻግርበት ዘመን፣ የመኖርና ያለመኖር ግድግዳ ተደርምሶ ሁሉም ነገር ትርጉም የለሽ በሆነባት፣ ፍዘት፣ ቁዘማ ባረበበባት ኢትዮጵያ… ዝምታ ስንት ዘመን ይፈጃል? ኢህአዴግ እንዲህ በክፋት ጎዳና እየተመላለሰ፣ በጭካኔ በትር እያስገበረ፣ ፍትሕን የ‹አመፃ ድምፅ ማፈኛ›› አርጩሜ አድርጎ እያሴሰናት… ከሁለት አስርት በላይ ተደላድሎ እንዲቀመጥ ያደረገው የቀደሙት ትውልዶች ርግማን አይምሰልህ፤ አገር-ለበስ ፍርሃት እና ቸልተኝነት እንጂ፡፡ በአናቱም ስደት የስርዓቱ ማስተንፈሻ እንጂ የለውጥ ኃይል ሆኖ አያውቅምና ሲገፉህ- አትንደርደር፤ ሲያስሩህ-አትሸበር፤ ሲከሱህ-አትደንብር፤ ሲወነጅሉህ-አትሸማቀቅ፤ ሲያስፈራሩህ-አትደንግጥ፣ ሲያባራሩህ- አትሩጥ… ምክንያቱም ፍርሃትን የመስበሪያ ፅኑ አለት ይህ ብቻ ነውና፡፡ በተቀረ እነርሱ የሚለፍፉለት ‹‹ምርጫ›› ከአንድም አራቴ ሲያፋፍሩበት በመታየቱ ካለፈው ለውጥ ይኖረዋል ብለህ አትሞኝ፤ ከዚህ በኋላ ለውጥ ሊያመጣ የሚችለው ሰላማዊ እምቢተኝነት አንጂ፣ አባዱላ ገመዳን ተሸክሞት እስከመሮጥ ያደረሰው ያ የይስሙላ ኮሮጆ አይደለም፡፡ የኢኮኖሚ ዕድገትም ብቻውን የፖለቲካ ለውጥ አያመጣም፡፡ ዳሩ፣ ሲጀመርስ ዕድገቱ የት አለና?! ኢህአዴግ በነቢብ ‹መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ አፋፍ ደርሻለሁ› በሚል ፕሮፓጋንዳ ቢያሰለቸንም፤ በገቢር አዳዲስ ምሬቶችን እያቆረ ስለመሆኑ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ‹‹አደህይቶ ማዳከም!›› እንዲሉ ፕሮፌሰር መስፍን፣ ድህነትን የሚፈለፍሉ ኩሬዎችን በየመንደሩ ከመቆፈር ቸል ብሎ አያውቅም፡፡ ይሁንና የፍትህ መዛባት፣ ስራ-አጥነት፣ የመኖሪያ ቤት ችግር፣ መቆጣጠር የተሳነው የዋጋ ግሽበት፣ ማቆሚያ ያጣው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ፣ ባልተጠና እቅድ ተቆፋፍረው ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ መንገዶች፣ አመቺ የስራ ቦታን በድርጅት የድጋፍና ተቃውሞ ሚዛን ማከፋፈል፣ አድሎአዊ አሰራር…

ብሶት የሚወልዳቸውን ነፃነት አብሳሪ አናብስት ጋላቢ ጀግኖችን ማበራከቱ አይቀሬ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ዶ/ር መረራ ጉዲና ‹‹የራበው ሕዝብ መሪዎቹን ይበላል›› የሚል ቅድመ-ትንቢያ ቢነግረንም፣ ሰሞኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ጠልፎ ከመድረሻው ውጪ ያሳረፈው የኃይለመድህን አበራ ክስተት ደግሞ በአንፃሩ ርሃብን ያሸነፈው የማህበረሰብ ክፍልም ሰዋዊ ነፃነቱን ለማስረገጥ ሲል መሪዎችን ሊባላ እንደሚችል የሚያመላክት ነው፡፡ ይህ ሰው ማህበራዊ አክብሮትን በሚያጎናፅፍ ሙያ የተሰማራ ከመሆኑም በላይ፣ በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ እርከን እጅግ ከፍተኛ ሊባል የሚችል ደሞዝ ተከፋይ ነው፡፡ ከዚህ አኳያም በአስከፊ ደረጃ የተንሰራፋውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም ብዙም እንደማይቸገር በድፍረት መናገር ይቻላል፡፡ ሀገር ቤት መኖር ካልፈለገም፣ ወደበለፀጉት ሀገራት ተሻግሮ ስራ ማግኘት እንደማይሳነው ያውቃል ተብሎ ይታሰባል፡፡ 

ግና፣ ይህ ሁሉ እውነት ቢሆንም የመረጠው መንገድ በራስ ላይ ቀድሞ ሊገመት የማይችል አደጋ የሚጋብዝን ነው፡፡ እንግዲህ ከእነዚህ ተጨባጭ እውነቶች ተነስተን (እርሱ ራሱ ድርጊቱን የፈፀመበት ምክንያት ለስዊዘርላንድ ፍርድ ቤት እስኪናገር መጠበቁን ታሳቢ አድርገን) መላ-ምቶችን ማስቀመጥ እንችላለን ብዬ አስባለሁ፡፡ ለድርጊቱ በዋናነት መግፍኤ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው አየር መንገዱ የገባበት ችግር ነው፤ ምክንያቱም ድርጅቱ በሂደት ህልፈቱን ወደሚያውጅበት መስቀል (ችንካር) እንዲያዘግም ገፊ ከሆኑ ጉዳዮች አስተዳደራዊ በደል የአንበሳውን ድርሻ ይይዛልና፡፡ አገዛዙ አንዳንድ የድርጅቱን ሰራተኞች በመዓት አይኑ ወደሚመመለከትበት ጠርዝ ያደረሰው ከዚህ ቀደም ‹በአውሮፕላኖቹ ላይ ባለኮከቡን ባንዲራ አትማለሁ› በሚል የፈጠረው አንጃ-ግራንጃ፣ በተወሰኑ ነባርና በጣም ወሳኝ ሰራተኞች ፊት-አውራሪነት በተቀሰቀሰ ተቃውሞ የተስተጓጎለበት ደረቅ እውነታ አንዱ ተደርጎ ይጠቀሳል፤ ሌላው ደግሞ ጠንካራና በሚገባ የተደራጃ የነበረውን የሰራተኛ ማህበር ለመቆጣጠር ያደረገውን ሙከራ ተከትሎ የገጠመው ተግዳሮት ነው (ዛሬ ማህበሩን ማስገበር መቻሉ ሳይዘነጋ)፡፡ እንዲህ አይነት ሕገ-መንግስታዊ ድፍረቶችን የስርዓቱ ኤጲስ-ቆጶሳት በቸልታ የሚያልፏቸው ባለመሆኑ፣ የተወሰዱት የማባረርና ከቦታ ዝቅ የማድረግ ፖለቲካዊ እርምጃዎች አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት ውድቀት መንገድ ከመጥረጉም በላይ፣ ተማራሪ ሰራተኞች እንዲበዙ አድርጓል፡፡ በአመክንዮ ድርጅቱ ከባለሙያ እጥረት (አቅም ማነስ) ጋር ብቻ ተያይዞ እየደረሰበት ያለውን ችግር ለመረዳት በስምንት ወር ውስጥ ብቻ ያጋጠመውን አራት ትላልቅ አደጋዎች ልጥቀስ፡- ካርጎ (Cargo MD-11F) አውሮፕላን ልምድ ያላቸው ኦፕሬተሮች በመባረራቸው፣ አዳዲሶቹ አበባ ለመጫን ሲሞክሩ በቆመበት ቦታ በቂጡ ወድቆ ጉዳት ደርሶበታል፤ ቦይንግ 767 (Boing 767) ከሞተር ጋር በተያያዘ ችግር ሮም ላይ ተገዶ አርፏል (በኋላ በተደረገለት ምርመራም ጥቂት ደቂቃዎች በአየር ላይ ቢቆይ ኖሮ ሊጋይ ይችል እንደነበረ ታውቋል)፤ ፎከር (Foker) አውሮፕላን ሞተሩ ተቃጥሎ ካርቱም ላይ አርፏል (ይህም ጥቂት ደቂቃ ቢዘገይ ኖሮ ተመሳሳይ አደጋ ይደርስበት እንደነበር ተነግሯል)፤ ቦይንግ 767-383 ኢ.አር (Boing 767-383 ER) ታንዛኒያ ውስጥ ማረፍ የነበረበትን ቦታ ስቶ፣ ትናንሽ አውሮፕላኖች የሚያርፉበት አሩሻ አየር ማረፊያ ለማረፍ ባደረገው ሙከራ በርካታ ኪሎ ሜትሮችን ተጉዞ ትልቅ የእርሻ ማሳ ውስጥ ሊቀረቀር ችሏል፡፡ እነዚህና መሰል ችግሮች ከኃይለመድህን አበራ እርምጃ ጋር ሲደማመሩ አየር መንገዱ ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለመረዳት ያስችላሉ፡፡

በአናቱም የጄኔቫው ክስተት የመሪዎቻችንን ውሸታምነት ከመቼውም በላይ የከፋ ደረጃ መድረሱን አሳይቶ አልፏል፡፡ ይኸውም የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤትን በሚኒስትር ማዕረግ የሚመራው አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ጠለፋው በተሰማበት ሰዓታት ውስጥ ለሮይተር በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ‹‹ድርጊቱን የፈፀሙት ካርቱም ላይ የተሳፈሩ አሸባሪዎች ናቸው›› ከማለቱ ጋር ይያዛል፡፡ ይህ ንግግር እንደቀላል ስህተት መታየት ያለበት አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም መንግስት በሀሰት ንፁሀንን ለማሰር ሲያሴር የሚሰጠው ሰበብ እንዲህ አይነት ፈጠራ መሆኑን ያስረግጥልናልና (ይህንን ጽሑፍ እያዘጋጀሁ ሳለሁ እንኳ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የሰማሁት ዜና ሀገር ውስጥ ያሉ የተወሰኑ የግል ሚዲያዎችን ሁለት ኢምባሲዎች እንደሚያሽከረክሯቸው የሚወነጅል መሆኑ ተጨማሪ ማሳያ ይመስለኛል)፡፡ በርግጥ ስርዓቱ በከረባት ታንቀው የሀሰት ወሬዎችን ሚዲያ ፊት ቀርበው የሚያወሩ ደፋር ሚኒስትሮችን በብዛት መሰብሰቡ እውነት ቢሆንም፣ ከሬደዋን ሁሴን በፊት አቶ በረከት ስምኦን እንዲህ አይነት እጅና እግር የሌላቸውን ነጭ ውሸቶች ራሱ ከመጋፈጥ ይልቅ ብዙ ጊዜ በምክትሉ አቶ ሽመልስ ከማል በኩል ያስነግር እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይሁንና በረከት ቦታውን ለሬድዋን ካስተላለፈ በኋላ በሬድዋንና ሽመልስ መካከል ያለው የፖለቲካ ጉልበት ያን ያህል የሚበላለጥ ባለመሆኑ፣ እንደቀድሞ ሁሉ ሬድዋን፣ በምክትሉ ለመጠቀም አስቸጋሪ እንደሆነበት ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ የአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝም ‹አለቃ እኔ ነኝ› የሚለው የሰሞኑ መከራከሪያ፣ እነበረከት-ደብረፅዮንን ከጣራ በላይ ሳያስቃቸው የሚቀር አይመስለኝም)

የሆነው ሆኖ ከላይ የተጠቀሱት ክስተቶች ከፍተኛ ደሞዝ የሚከፍል ድርጅት ሰራተኞችንም ያሳተፈ መሆኑን፤ በአምስት መቶ ብር አምስት ቤተሰብ ለማስተዳደር ከሚባትለው ኢትዮጵያዊ ጋር ካጋመድነው ሀገሪቱ ያለችበትን የፖለቲካ ክስረት፣ የኑሮ ውድነት ያነበረው ምሬት፣. አድሎአዊ አስተዳደር፣ መንግስታዊ ሙስና የደረሰበት አስከፊ ገፅታ፣ ተጠያቂነት ያሌለባቸው የፀጥታ ሰራተኞች የሚፈፅሙት ሕገ-ወጥ ተግባር፣ የአጠቃላይ መብት ጭፍለቃ… ተደማምረው መነሻና መድረሻው የታወቀውን የለውጥ ንቅናቄ መቀላቀልን ብቸኛ አማራጭ ያደርገዋል ብዬ አስባለሁ፡፡
የፈራ ይመለስ!

የስርዓቱ ልዝብ ተቃዋሚዎች ቀጣይ የሀገሪቱ ዕድል አብዮት ስለመሆኑ በተነሳ ቁጥር በግርድፍ ትንታኔ ሊነግሩን የሚሞክሩት ‹ኢትዮጵያ በ40 ዓመት ውስጥ ሶስት አብዮት ማስተናገድ አትችልም› የሚል ነው፡፡ ይሁንና ሙግታቸው ሁለት ግድፈቶችን ያዘለ ይመስለኛል፡፡ የመጀመሪያው የብሉይ አብዮትን መሰረታዊ ባህሪ ካለመረዳት ይነሳል፤ ዛሬም ድረስ የ66ቱን አብዮት አስመልክቶ የሚነሳው ተዋስኦ፣ ክስተቱ ብሉይ ማህበራዊ አብዮቶች ከሚባሉት መካከል እንደሚያስመድበው የሚያስረግጥ ነው፡፡ ይህ ስሌትም ብሉይ አብዮቶች ራሳቸውን በተለያዩ የዘመን ወቅቶች የመደጋገም ተጨባጭ ባህሪ እንዳላቸው ያመላክታል፡፡ እናም የሙግቱ ጥራዝ ነጠቅ አቀንቃኞች በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ከሚመደቡት መካከል ሩሲያና ፈረንሳይ በሁለትና ሶስት አብዮቶች ከመናጣቸው አኳያ ‹ኢትዮጵያንስ ምን ያህል የተለየች ሊያደርጋት ይችላል?› ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ የሚኖራቸው አይመስለኝም፡፡ በ66ቱ ከተነሱት ሁለት ዋነኛ (የመሬትና የብሔር) ጥያቄዎች፣ በ83ቱ ማህበረ- ፖለቲካዊ ሽግግርም ተነስተው አለመመለሳቸውን፣ ያሳለፍናቸው ሃያ ሁለት ዓመታት በበቂ ሁኔታ አስረጅ ናቸው፡፡ ይህ እውነታም ነው ሀገሬ ሶስተኛውን አብዮት ከማስተናገድ ውጪ የተሻለ ምርጫ እንዳይኖራት ያስገደደው፡፡

ሁለተኛው ጭብጥ በኢህአዴግ ስር ያዘገመችው ኢትዮጵያ ለአብዮት መነቃቃት የሚያበቁ ስርዓታዊ ክሽፈቶች መኖራቸውን ክዶ ከማለፍ ጋር የሚያያዝ ይሆናል፡፡ ለከተማ አብዮት መፈንዳት ወሳኝ ሆነው ከሚጠቀሱ ጭብጦች ብዙዎቹን የእኛይቷም ምድር እንደምታሟላ ከዚህ በፊትም ለማስታወስ ሞክሬያለሁ፡፡ በተለይም ሥራ-አጥ የተማሩ ከተሜ ወጣቶች አለቅጥ መብዛት እና ወጣቶች ከአጠቃላዩ ሕዝብ ወደ 37% የሚጠጉ መሆናቸውን ከአረቡ ፀደይ መንፈስ አኳያ ስንቃኘው አብዮቱን አይቀሬ ያደርገዋል፡፡ በአናቱም የሁለቱ ኃይማኖት ተከታዮች በመንግስት ላይ የያዙት የቅራኔ ልክ፣ የተቋጠረ የምሬት ፅንስ ስለመኖሩ በድፍረት ለመናገር ያስችላል፡፡ ለሁለት ዓመታት የዘለቀው የሙስሊሙ ጥያቄም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የለዘበ ቢመስልም በሂደት እንደገና መቀስቀሱ አይቀሬ ነው፡፡ ምክንያቱም የእምነቱ ተከታዮች መሰረታዊ ጥያቄ የኃይማኖቱን ሙሉ ነፃነት መከወን ከመሆኑ ላይ ተነስተን፣ የተሰጠው መልስ መዋቅራዊ እንደነበረ ካስተዋልን ‹‹እንቅስቃሴው መለዘብ አለበት›› ያሉ ልሂቃንም ሳይቀሩ የነፃነቱ ጥያቄ በድጋሚ ተነስቶ መጅሊሱን እንዲነቀንቅ መፈለጋቸውን አምነን እንድንቀበል ያስገድደናል፡፡

ሌላው ጉዳይ የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታዮች ጉርምርምታ እና ማህበረ ቅዱሳን ላይ በሲኖዶሱ በኩል የሚካሄደው መንግስታዊ ጉንተላ፣ ምን ይዞ እንደሚመጣ ለመገመት የግድ ነገ ላይ መቆምን የማይጠይቅ መሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪ ዛሬም5 እየተነሱ ካሉት የማንነት ጥያቄዎች አልፎ፣ በቅርምቱ ከአያቶቻቸው መሬት ከተፈናቀሉ ወጣቶች ምሬት ጋር የኢኮኖሚውን ድቀት አዛምደን ስንመለከት፣ ፍርሃትን አቸንፈው ወደኋላ ላለመመለስ የደፈሩ ወጣቶች ስርዓቱን እንደሚንዱት ለመመልከት ጥቂት ወራትን ብቻ መታገስ ይበቃል፡፡ ‹‹አብዮት የወይን ዘለላ ነው፤ እስኪበስል እንጂ መሬት እስኪወድቅ አትታገሰውም›› እንዲል ቼ ጉቬራ፤ ያረገዘውን አብዮት ከማዋለድ ያለፈ ምርጫ የለም፡፡

በድጋሚ ክብር ለዐድዋ ጀግኖች!!!

እስክንደር የጻፈው ለነጻነት ነው፤ የሞራል ድፍረት ያለው ነው – ጆን ኬሪ

march 4/2014
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ሽብርተኛ ነህ በሚል መስረት የሌለዉ ክስ ተከሶ የ18 አመት እስራት ፣ በፖለቲካ ዉሳኔ እንደተፈረደበት ይታወቃል። የአሜሪካው የዊጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይሄን ይቃወማሉ። ጋዜጠኛ እስክንደር ነጋን፣ ለነጻነቱ የጻፈ ሲሉ፣ ከሌሎች አንጋፋ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እኩል አስቀምጠዉታል።
1394241_527514827333456_269824761_n
የጆን ኬሪ ይፋዊ ዘለፋ፣ የጋዜጠኛ እስክንደር ሆነ የሌሎች በርካታ ጋዜጠኞችና የሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች መታሰር፣ ኢሕአዴግ በአገሩ ካሉ ዜጎቹ ጋር ብቻ ሳይሆን ከበርካታ የአለም አቀፍ ማህበረሰብና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ጋር እንዲጋጭ እያደረገዉ እንዳለ የሚያመላክት ነው።
አሜሪካ የኢትዮጵያ መንግስት ዋና ደጋፊ እንደሆነች ይታወቃል። በርካታ የአገዛዙ ቱባ ቱባ ባለስልጣናር በአሜሪካ ቤት ያላቸው፣ በአሜሪካ ባንኮች ገንዘብ የሚያሰቀምጡ እንደሆነ ይነገራል። በአመት ከ370 ሚሊዮን ዶር እርዳታም አሜሪካ ለኢትዮጵያ እንደምትሰጥ ይታወቃል።
በአምባሳደሯ ወይም በስቴት ዲፓርትመንት በአፍሪካ ጉዳይ ሃላፊ ደረጃ ሳይሆን፣ በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደረጃ የነ እስክንደር ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶት፣ በጋዜጣዊ መግለጫቸው ጆን ኬሪ፣ በአደባባይ እስክንደርን መጥቀሳቸው፣ ምን ያህል በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ከላይ ያሉ የአሜሪካ ባለስልጣናት እያሳሰበ እንዳለ የሚያሳይ ነው።
ጆን ኬሪ የሚከተለውን ነበር ያሉት፡
“The truth is that some of the greatest accomplishments in expanding the cause of human rights have come not because of legislative decree or judicial fiat, but they came through the awesomely courageous acts of individuals, whether it is Xu Zhiyong fighting the government transparency that he desires to see in China, or Ales Byalyatski, who is demanding justice and transparency and accountability in Belarus, whether it is Angel Yunier Remon Arzuaga, who is rapping for greater political freedom in Cuba, or Eskinder Nega, who is writing for freedom of expression in Ethiopia, every single one of these people are demonstrating a brand of moral courage that we need now more than ever.”

የዩናይትድ ስቴት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ ዉስጥ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳለ ይፋ አድርጓል (ዜና ትንታኔ)

march 3/2014

ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 20/2006 (ቢቢኤን) ፦ የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (State Department) ባወጣዉ የዘንድሮ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ያከናዉናቸዋል ያለዉን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመዘርዘር ሰፋ ባለ መልኩ አቅርቦታል።
ቀድም ሲል ኢትዮጵያ ዉስጥ በ2003 በተደረገዉ ምርጫ፤ በሟቹና በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ ይመራ የነበርዉ ኢ.ህ.አዴ.ግ ከ547 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ 545 መቀመጫዎች አሸንፏል መባሉን ሪፖርቱ እያመላከተ የምርጫ ጣቢያዎች በመንግስት ሐይላት ቁጥጥር ስር እንደነበሩና አለምአቀፍ ታዛቢዎች ስራቸዉን በተገቢዉ መልኩ እንዳያከናዉኑ ገደብ እንደነበረባቸዉ ይገፃል።

በአገሪቱ ዉስጥ ባለዉ ከፍተኛ የመብት ረገጣ ሳቢያ ዜጎች የመሰብሰብ፣የመደራጀት፣የመናገር መብትን በገሃድ እንደሚነፈጉ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ያስደረግቸዉን ጥናቶች ተመርኩዞ ያብራራል። እነዚህን የዲሞክራሲ እሴቶችን ለመተግበር የሚሞክሩም ይታሰራሉ፣ይንገላታሉ፣ይዋከባሉ፣ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ ክብራቸዉ ተነክቶ እንዲሸማቀቁምይደረጋሉ በማለት ሪፖርቱ ያትታል።እርዳታን የሚያስተባብሩ፣ እርዳታን ለጋሽ የሆኑ ድርጅቶች፣ ማህበራዊና ትርፍ አልባ የሆኑ ተቋማት (NGO) የግብረ-ሰናይ ተልእኮ አቸዉን እንዳይፈጽሙ የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚከለክል፤ በሰዎች ላይ ህገ ወጥ የሆነ ግድያ እንደሚፈጽም፣ዜጎች ግርፋት-ድብደባ እንደሚደርስባቸዉ፣ ወጥ የሆኑ የማሰቃያ ተግባራት በመንግስት ሐይላት እንደሚፈጽምና በአገሪቱ እስርቤት የሚገኙ ታሳሪዎችን ህይወት ለአደጋ የሚያጋልጹ አሳቃቂ ተግባራትም እንዳሉም በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል።

ሰዎች በፍርድ ቤት ሳይበየንባቸዉ በጅምላ ተይዘድዉ ይታሰራሉ፤በፍርድ ቤት የአሰራር ዘይቤም ይሁን በፍትህ ሒደቱ ዉስጥ ግልጽ የሆነ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት አለበት፤ ፍርድ ቤቶችም ደካማ ናቸዉ! ሲል ሪፖርቱ ይደመድማል። መንግስት ሀሳብን በነጻነት ለመግለጽ የሚሞክሩ ያገሪቱ ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንደሚወስድ በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን፤ በነሐሴ 2/2005 የኢድ-አልፈጥር በዓል በሚከበርበት ወቅት፤ በሰላማዊ መንገድ ተቃዉሞ ያሰሙ ከነበሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዉያን መካከል ከ 1000 በላይ የሚሆኑት በጅምላ ተግበስብሰዉ መታሰራቸዉና ከመካከላቸዉም የሞቱ መኖራቸዉ በሪፖርቱ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶታል።የዜጎች ግላዊ መብትን በመግፈፍ፤ በሙስሊሙ ማህበረስብ ላይ ህገወጥ የሌሊት ፍተሻዎችም ተደርገዋል። ግልጽና ስልታዊ በሆነ መልኩም ከቦታ ወደ ቦታ ዜጎችን የማፈናቀል መርሃግብር በመንግስት መፈጸሙን የሚያስረዳዉ ሪፖርት ነጻ መሆን የሚገባዉ የመማርና የማስተማር ሒደት የመንግስት ጣልቃገብነት እንዳለበትም ይገልጻል።

ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ በነጻነት መንግስትን የመቀየር አቅማቸዉ ሆን ተብሎ የተገደበ ነዉ!በፖሊስ፣በፍርድ ቤቶችና በመንግስት አመራር ዉስጥ በስልጣን መባለግ-ሙሰኝነት-ጉቦኝነት በገሃድ ይተገበራሉ። መንግስት በስልጣን የባለጉንና የህዝብን አደራ ያጎሳቆሉ ወንጀለኞች ችላ በማለት ፖለቲካዊ ዉለታን ይዉላል፤ ፖለቲካዊ ምህረትን ለምግባረ ብልሹ የመንግስት አካላት እንደሚያደርግ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ያጋልጻል።

በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የጾታ እኩልነት የተረጋገጠ ቢሆንም በመንግስታዊ የአሰራር መዋቅር ዉስጥ ሴቶች ይጨቆናሉ። ህገወጥ የሆነ የሰዉ ዝዉዉር ይፈሰማል፣ የአካል ጉዳተኞች (የተሳናቸዉ) ማህበራዊ ጭቆና ይደርስባቸዋል፣የ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ህሙማን ማህበራዊ የሆነን በደል ይጋፈጣሉ፣የሰራተኖች መብት የተገደበ በመሆኑ ህፃናትን አስገድዶ የጉልበት ስራ ማሰራቱ የተለመደ መሆኑ በሪፖርቱ ላይ ተዘርዝሯል።

የመንግስት ሐይላት የሰዎችን ደብዛ ያጠፋሉ፤ የሰዎች መሰወር ይስተዋላል! በትግራይ ክልል በአላማጣ ከተማ መንግስት በልማት ስም ቤቶችን በሚያፈርስበት ወቅት አለመግባባት ተፈጥሮ የታሰሩ 12 የአካባዊ ተወላጆች የገቡበት እንደማይተዋቅ እና ተመሳሳይ በሆነ መልኩ በሶማሌ ክልል ያለዉ ልዩ የፖሊስ ሐይል በክልሉ ተወላጆች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ማንገላታት፣ማሰቃየት፤ ግድያ እደሚፈጽም መታወቁ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ህገመንግስት ቶርቸር (ግርፋት ድብደባ ማሰቃየት)ይከለክላል። ቶርቸርን የመሰሉ የሰዉ ልጅን ክብር ገፋፊ የሆኑ ጭካኔ የተሞላባቸዉ ተግባራት፤በመንግስት የደህነነትና የጥበቃ ሐይላት እንደሚፈጸሙ በማጋለፅ በጥር 9/2005 የተያዘዉ የሙስሊሞች ጉዳይ መጽሔት አምድኛ እና ማኔጂንግ ኢዲተር የነበረዉ ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ በተደጋጋሚ የዚሁ ህገወጥና አስከፊ ተግባር ሰለባ እንደነበር በዩናይትድ እስቴት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ላይ በዋቢነት ተጠቅሷል።

በጥቅምት 8/2006 ሁማን ራይትስ ዎች ያወጣዉን ሪፖርት እንደ አብነት በመጥቀስ በመጥቀስ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ መርማሪዎች ታሳሪዎችን በማስገደድ የእምነት ቃል እንደሰጡ እንደሚያደርጉ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት እየገለጸ፤ በማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ ቶርቸር (ግርፋት-ድብደባ-ማሰቃየትት)፣ ዛቻ፣ማስፈራራርት፣ እስረኞች ላይ ዉሃ መድፋት፣የእስረኞችን እጅ ጣራ ላይ አስሮ ለረጅም ሰዓታት ማቆም፣እሰረኞችን ነጥሎ ለብቻ ማሰርን የመሳሰሉ ኢሰብዓዊ ተግባራት እንደሚፈጽሙና ዲፕሎማቶች፣ኤንጂኦ (በጎ አድራጊ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ትርፍ አልባ ድርጅቶች) እስረኞችን የመጎብኘት ፍቃድ እንደሚነፈጉ ተገልጿል።

በመስከረም 2005 በተገኘዉ መረጃ መሰረት ከ70,000 እስከ 80,000የሚድርሱ እስረኞች መኖራቸዉ ሲታወቅ፤ ከነዚህም መካከል 2500ሴቶች ሲሆኑ 600 ህጻናት ከእናቶቻቸዉ ጋር መታሰራቸዉ እና ታዳጊ ወጣቶች ከአዋቂዎች ጋር አብረዉ እንደሚታሰሩ ተዘግቧል። የአገሪቱ እስር ቤቶች በጣም የተጣበቡ ከመሆናቸዉም ባሻገር ወታደራዊ ተቋማትም እንደ እስር ቤት ማገልገላቸዉ ተዘግቧል። በርካታ እስረኞች ከመጣበብ፣ተነጥሎ ከመታሰር፣ የተማሏ የጤና ግልጋሎት ካለመኖሩ የተነሳ ለአእምሮ ህመም ይዳረጋሉ። ለአንድ እስረኛ የምግብ፣ የዉሃ አቅርቦትን ለመለገስ እና የጤና ግልጋሎት ለመስጠት በቀን ስምንት ብር ከአስር ሳንቲም ብቻ እንደተመደበ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመታዊ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ይዘረዝራል።

ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ከ2004 ጀምሮ ሰላማዊ የሆነ ተቃዉሞን በአወሊያ የትምርት ተቋም ዉስጥ በመጀመር ከአርብ ስግደት (ከጁመዓ ሶላት) በሗላ በቀጣይነት የተቃዉሞ መርሃግብር እንደሚያከናዉኑና፤ ይህ የቅዋሜ ተግባር ምንም ሰላማዊ ቢሆንም የፖሊስ አካላት ሰዎችን በመያዝ አላስፈላጊ ሐይል እንደሚጠቀሙ ሪፖርቱ ያስረዳል። በሐምሌ 14/ 2004 በሙስሊሞች የተደረገዉን ሰላማዊ ተቃዉሞ ተከትሎ መንግስት “የደህንነት ሰጋት” የሚል ማመካኛን በመፍጠር 28 ሙስሊሞችን አስሮ በጥር 24/2005 ክስ ያቀረበባቸዉ ቢሆንም በታህሳስ 3/2006 አስሩን በነጻ አሰናብቶ በአስራ ስምንቱ ላይ ያቀረበዉን ክስ ዝቅ አድርጓል። መንግስት እነዚህን የሙስሊም ታሳሪዎች በአለማችን ላይ ከሚታወቁ አሽባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላቸዉ ብሎ በገሃድ ለመፈረጅ መሞከሩም በሪፖርቱ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግስት የመናገር-የመደራጀት-የመሰብሰብን መብት የሚተገብሩ ፖለቲከኞችናና ጋዜጠኞችን እንደሚያስር፣ እንደሚያሰቃይ፣ እንደሚያንገላታ፣ የሚገልጸዉ ሪፖርት ከፖለቲከኞች የመድረኩ አንዱአለም አራጌ ብሎም የኦሮሞን ማህበረስብ መብት በዲሞክራሲ ለማስከበር ከሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ተወላጆች በቀለ ገርባና ኦልባና ሌሊሳ ታስረዉ እየተሰቃዩ መሆናቸዉን፤ ተመሳሳይ በሆነ መልኩ ከጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ሪዮት አለሙና ሰለሞን ከበደ በእስር ይማቅቃሉ ሲልም ሪፖርቱ ያስረዳል።

መንግስት ነጻ-ፕሬስ እንዲከስም በሚያደርገዉ ከፍተኛ ጫና ጋዜጠኞች የእስርና የስደት ሰለባ መሆናቸዉ ቢታወቅም፤ዳግም መንግስት የአፈና መረቡን በመዘርጋት የኢንተርኔት፣ የሳተላይት-ቴሌቭዥን ስርጭትን፣የማህበራዊ መገናኛ መደረኮችን፣የድረ ገጽ የመረጃ አዉታሮችን በማወክ ህዝቡ ማግኘት የሚገባዉን መረጃ ከማፈኑም ባሻገር፤ የጋዜጠኖች፣ የፖለቲከኞች እና የአክትቪስቶችን ኮምፒዉተር ለመሰለል ህገወጥ የሆነ የኮምፒዉተር ቫይረስን መንግስት እንደሚልክ ሲት ዝን ላብ (citizen lab) የተባለዉን ድርጅትን መረጃ ዋቢ ያደረገዉ የዩናይትድ እስቴትስ አመታዊ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የኢትዮጵያ መንግስት የህዝብ የሆኑ የሬዲዮና የቴሌቭዥን ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ተጠቅሞ ለፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳ እየተገለገለባቸዉ መሆኑን ይፋ አድርጓል።
ከዘ -ሐበሻ የተወሰደ

የደሴ ሕዝብ በኢሕኣዴግ የግዳጅ መዋጮ ተማሯል::በደሴ ወንጀል በመበርከቱ የሰአት እላፊ ገደብ ተጥሏል:: በከተማዋ ፌዴራል ፖሊሶች በምሽት ወታደራዊ ልምምድ ያደርጋሉ::

February 3/2014

በምንሊክ ሳልሳዊ

የደሴ ሕዝብ ከመለስ ፋውንዴሽን ጋር በተያያዘ ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ይፈለግበታል::

 ከደሴ የሚደርሱኝ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት በሕወሓት አዛዥነት በብኣዴን ሰብሳቢነት የመለስ ዜናዊን አመራር አካዳሚ ሕንጻን ለመገንባት የመለስ ፋውንዴሽን ከህዝቡ ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚጠበቅበት እና ለግንባታው የግዴታ አስታውጾ እንዲያደርግ እያስገደዱት መሆኑን እና ሕዝቡም ከኑሮ ውድነት ጎን ለጎን ከአፉ ላይ ሊጎርሰውን ያዘጋጀውን በጉልበተኞች እየተነጠቀ መሆኑን በማማረር አቤቱታውን ማሰማቱን የደሴ የለውጥ ሃዋርያ ወጣቶች አንድነት ለምንሊክ ሳልሳዊ በላከው መረጃ ገልጽዋል::

መረጃዎቹ እንደጠቆሙት የገንዘብ አሰባሰቡ ሂደት በሁሉም ክፍለከተሞች ባሉ የወያኔ ካቢኔዎች ሲሆን እያንዳንዱ የካቢኔ አባል በግል እንዲሰበስብ የገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ የተሰጠው ሲሆን ከፍተኛ ገንዘብ ለሰበሰበ ሽልማት ስለሚሰጠው የሚል ቅል ስለተገባላቸው የስልታን እና የደሞዝ እድገት ለማግኘት እና ታማኝነታቸውን ለማረጋገጥ በሽፍን ድጋፍ ሕዝቡን በግዳጅ እና በማስፈራራት በዛቻ ገንዘብ እንዲያዋጣ እያደረጉት ሲሆን ይህንን በተመለከተ ሕዝቡ በቤቱ አሊያም በስብሰባ ካልተገኘ በቅጣት ሁሉ መልክ ተጨማሪ እንዲከፍል ይደረጋል የሉት የምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮች ሕዝቡ በሚሄድበት መስሪያቤት አሊያም ስብሰባ ቀደም ብሎ የከፈለ ሰው ደረሰኙን ካልያዘ ጉዳዩን ለማስፈጸም በድጋሚ እንዲከፍል የሚደረግ ሲሆን እረስቸዋለሁ ሄጄ ላምጣ የሚል ነገር ተቀባይነት የለውም::

እንዲሁም በደሴ የብኣዴን ጽ/ቤት ሃላፊነት ተጨማሪ ለመለስ ፋውንዴሽን በሚል በግዳጅ ገንዘብ እየተሰበሰበ ሲሆን የጽ/ቤቱ ሃላፊ የሆኑት አቶ ጌታዊ ይርጋ (የቀድሞ የኮምቦልቻ ከተማ ከንቲባ) ከዚህ ቀደም በሙስና ታስረው የነበሩ እና ከህግ ውጪ ለፖለቲካው አስፈላጊ ሆነው በመገኘታቸው በትእዛዝ ከተፈቱ በኋላ ሲቭል ሰርቭስ ኮሌጅ ተልከው ሰልጥነው በደሴ የብኣዲን ጽ/ቤት ሃላፊ ሆነው ከተመደቡ ጀምሮ በግዳጅ ከእጅ ወደ አፍ የሚኖረውን በኑሮ ውድነት የተማረረውን ህዝብ እያስገደዱ የመንግስት ሰራተኛውን ከደሞዙ ላይ 30% እንዲቆረጥ ውሳኔ በመስጠት እንዲሁም በየቤቱ የብኣዴን ካድሬዎች እየዞሩ ከቀበሌ ሰዎች ጋር በመሆን ሕዝቡ 100 ብር እንዲከፍል በበደል ላይ በደል እየፈጸሙበት ይገኛል:: እንዲሁም ባለሃብቱን እያስገደዱት ያሌለን ገንዘብ እንዲተፋ ወጥረው ይዘውታል ሲሉ ለምንሊክ ሳልሳዊ መረጃውን ልከዋል::

በሌላ ዜና በደዜ ከተማ ዙሪያ ጨለማን ተገን አድርገው የሰዎች ግድያ እና ዝርፊያ ወንጀሎች ከበፊቱ በበለጠ በመበርከቱ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ማንኛውም የከተማው ነዋሪ ከምሽቱ አራት ሰአት በኋላ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርግ የሰአት እላፊ ገደብ መጣሉን የከተማው ነዋሪዎች ለምንሊክ ሳልሳዊ በስልክ ገልጸውለታል::

ባለፉት ሁለት ቀናት በመላው አገሪቱ የተካሄዱትን ፍተሻዎች በተመሳሰለ መልኩ የሞባይል ቤቶች እና የኢንተርኔት ካፌዎችን እንዲሁም የመረጣቸውን ብሎም የጠረጠራቸውን ግለሰቦች በድንገት ፍተሻ በማካሄድ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሞባይሎች ላፕቶፖች ዲስክቶፖች ኮምፒተሮች እና የሚሞሪ ካርዶች ሰብስቦ የወሰደው የደሴ ፖሊስ ሰአት እላፊውን ጥሶ የተገኘ ነዋሪ በጸጥታ ሃይሎች ለሚወሰድበት ማንኛውም እርምጃ መንግስት ተጠያቂ እንደማይሆን ገልጿል::

ከዚሁ ጋር በተያያዘ መረጃ የደሴ ከተማ በፌዴራል ፖሊስ ወታደራዊ ልምምድ ተወጥራ እንደምታመሽ ታውቋል:; ቁጥራቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የፌዴራል ፖሊሶች ከምሽቱ 3 30 ጀምሮ ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግ በዋናው የከተማዋ መንገዶች በመጠቀም ላይ ሲሆኑ በህዝቡ ላይ ሽብር እየነዙ መሆኑን ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ነግረውታል::ይህንን እያደረጉ ያሉት የከተማውን ነዋሪ ለማስፈራራት እና ለማሸበር እየጣሩ እና በሃርቡ አከባቢ የሚንቀሳቀሱ የፌዴራል ፖሊሶች ለሊቱን በወታደራዊ ልምምድቸው ጊዜ ስለሚጮሁ ህዝቡን ከስራ ቤቱ ገብቶ እንዳያርፍ እንቅልፍ እየነሱት ሲሆን ምን ያክል መንግስት ጭንቀት ላይ እንዳለ ያሳያል ሲሉ መረጃውን የላኩት ነዋሪዎች ገልጸዋል::መረጃውን ላቀበላችሁኝ የደሴ ወጣቶች አመሰግናለሁ ::ምንሊክ ሳልሳዊ:

: